Professional Documents
Culture Documents
07.
07.
7
www.tlcfan.org 0
የእግዚአብሔር መንግሥት ሕጎች #7
“Mercy and truth are met together; righteousness and peace have kissed each other.”KJV
ታዲያ ይህ ክንውን በምሕረትና በእውነት በጽድቅና ሰላም መካከል እንዴት ሊሆን ወይም
ሊፈጸም ይችላል? ለመጀመሪያ ጊዜ ይህን መሳሳም ወይም መስማማት የምናየው በማደሪያው ድንኳን
ውስጥ በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ባለው ታቦት ላይ ነው። የእግዚአብሔር ሕግ እውነት ሲሆን በታቦቱ
ሳጥን ውስጥ ሲቀመጥ ምሕረት ደግሞ ታቦቱ ከድኖ የሚይዘጋው ኪሩቤሎቹ የተሸከመው መክደኛ
ነበር። ምሕረትና እውነት በቅድስተ ቅዱሳን ተሳስመዋል። ያቆብም በያቆ.2፥13 “ ምሕረት በፍርድ ላይ
ይመካል” ብሎ ይህን መሰከረ። ያቆብ ይህን ማለቱ ምሕረት ሕግን ወይም ፍርድን አስወገደ ማለቱ
ነውን? ምሕረት ፍርድን እና ሕግን ያጠፋልን ወይስ ያስወግዳልን?
www.tlcfan.org 1
የእግዚአብሔር መንግሥት ሕጎች #7
www.tlcfan.org 2
የእግዚአብሔር መንግሥት ሕጎች #7
www.tlcfan.org 3
የእግዚአብሔር መንግሥት ሕጎች #7
ንጉስ ዳዊት በንግሥናው ዘመን ወደ ፍርድ ውስጥ ያስገባውን ሃጢያት ሰራ። ይህም ሃጢያት
ሁላችን እንደምናውቀው ከኦሪዮን ሚስት ከቤርሳቤ ጋር የሰራው የዝሙት ሃጢያት ነው። ዳዊት በዝሙት
አላበቃም። በመቀጠልም ሃጢያቱን ለመደበቅ በሄደበት መንገድ ባሏን በማስገደል አውቆና አሰላስሎ
የሰው ነፍስ በማጥፋቱ ነፍሰ ገዳይም ሆኗል። 2.ሳሙ.11 እንደ እግዚአብሔር ሕግና እውነት መሰረት
ዝሙት ያደረገም ሆነ ነፍስ የገደለ ቅጣቱ ወይም ፍርዱ ሞት ነው። ዘጸ. 21፥12-14, ዘዳ.22፥22
www.tlcfan.org 4
የእግዚአብሔር መንግሥት ሕጎች #7
ንጉስ ዳዊት እረኛ ነበርና በበግ በኩል ይግባኙ ግልጽ ሆኖ ሲቀርብለት ፍርድን በራሱ ላይ
እየፈረደ እንደሆነ ሳያውቅ ፈረደ። ነብዮ ናታንም ያ ሰው አንተ ነህ ብሎ ፍርዱን በገዛ አንደበቱ እንደበየነ
አበሰረለት። ይህ ለንጉስ ዳዊት ትልቅ በፍርድ የሆነ የምሕረትና ስለላም የሚቀበልበት ጅማሬ የሆነና ወደ
ንስሃ ያመጣው ነበር። ቃሉ እንደሚል በራሳችን ብንፈርድ ባልተፈረደብንም እንደሚል። ለንጉስ ዳዊት
በራሱ ላይ ፈረደ። ፍርዱ የሚያመጣበትንም ስላወቀ ወዲያው እልፍኙን ዘግቶ ወደ እግዚአብሔር በንስሃ
ቀረበ።
“በከረጢትህ ውስጥ ታላቅና ታናሽ የሆነ ሁለት ዓይነት ሚዛን አይኑርልህ። በቤትህ ውስጥ
ታላቅና ታናሽ የሆነ ሁለት ዓይነት መስፈሪያ አይኑርልህ። ይህን የሚያደርግ ሁሉ
ክፋትንም የሚያደርግ ሁሉ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነውና አምላክህ
እግዚአብሔር በሚሰጥህ ምድር ላይ ዕድሜህ ይረዝም ዘንድ እውነተኛና ፍጹም ሚዛን
ይሁንልህ፤ እውነተኛና ፍጹም መስፈሪያም ይሁንልህ።” ዘዳ.25፥13-16
ንጉስ ዳዊትን እግዚአብሔር በእኩል ሚዛን ሕግ ሊፈርደው ተነሳ። ፍርዱንም እራሱ በራሱ
ላይ በራሱ አንደበት እንዲፈርድ ወይም እንዲሰፍር አደረገው። እግዚአብሔር ለሌሎች ባለን የምሕረት
ልክ እኛንም ይፈርዳል ወይም የበይናል። ለዚህ ነው ጌታ በጸሎቱ የበደሉንን ይቅር እንደምንል እኛንም
ይቅር በለን ብለን ወደ እግዚአብሔር እንድንጸልይ ያስተማረን። ለንጉስ ዳዊት ምሕረትን ሊያበዛለት
ወደደ ነገር ግን ምሕረቱን እርሱ በሰፈረውና በፈረደው ፍርድ ልክ አደረገበት። ዳዊት በዚያች እለት
ትሕትናንና ንስሃን ተማረ። ምክንያቱም የእግዚአብሔር ሕግ ዋናው አላማው ሃጢያት ምን እንደሆነ
ማሳየትና ወደ ንስሃ እንድንመጣ ማድረግ ነው። እግዚአብሔር ከምሕረት መክደኛው ሆነ ሁሉን ሸፍኖ
እንደ ንጉስ ዳዊት የአፉ ቃል ሊፈርድበት ተነሳ። ዳዊት ያ ሰው እርሱ መሆኑን ሲያውቅ ወደ መለኮታዊው
የእግዚአብሔር ፍርድ ቤት በንስሃ ጸሎት የምሕረት ጥያቄን አስገባ። ነገ ግን ፍርዱን እራሱ አውጥቶ
ነበርና እንዳለውና እንደፈረደው ተፈጸመበት። በሰማዩ በእግዚአብሔር ፍርድ ቤት እውነትን (ሕጉን) እና
ምሕረን አስማምቶ ጽድቅንማ ስላምን ማድረግ ይችላል። በምድር ያሉ ፍርድ ቤቶች ግን ጽድቅንና
ሰላምን ላድርግ ቢሉም ለማድረግ ሰርዓትና ሕጋቸው ፈጽሞ ራሳቸውን እጃቸውን ያስራል።
www.tlcfan.org 5
የእግዚአብሔር መንግሥት ሕጎች #7
በእግዚአብሔር ምሕረት ባለጠገነት ብዛት እርሱ ከሞት ተረፈ። ነገር ግን የጥፋቱን ቅጣት
ሳይቀበል አልቀረም። ምንም እንኳን ዳዊት ሌሊቱን ሙሉ ቢጸልይና ቢጾም ከቤርሳቤ የጸነሰው ልጅ ሞተ።
2.ሳሙ.12፥15-17 “ናታንም ወደ ቤቱ ተመለሰ። እግዚአብሔርም የኦርዮ ሚስት ለዳዊት የወለደችውን
ሕፃን ቀሠፈ፥ እጅግም ታምሞ ነበር።” በመንፈሳዊ ትርጉሙ ካየነው ልጁ የክርስቶስ ኢየሱስም ጥላ ነው።
ሃጢያት ያላወቀው በኩር በመሞቱ ዳዊት ከሞት ተረፈ። ኢየሱስ ስለ አባቱ አዳም እንደሞተ ወንጌል
እንደሚናገር ማለት ነው። ዮሐ.11፥50 የሆነው ሆኖ ይህ የመጀመሪያው ልጅ ፍርድ ውጤት ከአራቱ
ፍርዶች ዳዊት እንደ ወሰነው የመጀመሪያው ነበር። የበኩር ልጁ ከሞተ በኋላ የንጉስ ዳዊት ሕይወት
የነበረው የቀሩትን ፍርዶች በየተራ መቀበል ነው። ይህም የእግዚአብሔር ቅጣትና ፍርድ ንጉስ ዳዊትን
ወደ ትሕትና ሕይወት ወደ ጽድቅና ሰላም በመጨረሻ አስገባው። ጽድቅና ሰላም ተሳሳሙ ወይም
ተስማሙ።
የእግዚአብሔር ሕግ አልተሻረም!
ሃጢያትን የሰራ ሰው ሁሉ የሃጢያቱን ቅጣት ልክ እንደ ሃጢያቱ መጠን ሳይቀበል አይቀርም!
እግዚአብሔር በሃጢያት ሳይፈርድ ምሕረትን አያመጣም!
እውነትና ምሕረት ሳይስማሙ ጽድቅና ሰላም አይመጣም።
ከንጉስ ዳዊት ሕይወት እንዳየነውና እንደተማርነው በሰዎች ላይ ከመስፈርና ከመፍረዳችን
በፊት ራሳችንን ዞር ብለን መመልከት እንዳለብን ነው።
www.tlcfan.org 6
የእግዚአብሔር መንግሥት ሕጎች #7
www.tlcfan.org 7