You are on page 1of 6

መለከት #1

www.tlcfan.org 0
መለከት #1

የመንግስቱ ሕጎች መግቢያ


የእግዚአብሔር የመንግስቱ ሕጎች ከጻፎችና ፈሪሳዊያን ወግና ስርዓቶች ፈጽሞ የተለዩ ናቸው።
ማቴ.23፥23 “እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ከአዝሙድና ከእንስላል ከከሙንም አሥራት ስለምታወጡ፥ ፍርድንና
ምሕረትን ታማኝነትንም፥ በሕግ ያለውን ዋና ነገር ስለምትተዉ፥ ወዮላችሁ፤ ሌላውን ሳትተዉ ይህን ልታደርጉ ይገባችሁ
ነበር።” በማለት ኢየሱስ ግብዝ ሃይማኖተኞችን ይገስጻቸዋል። በዚህ ተከታታይ ትምህርት ክፍሎች ላይ ትኩረት
የምናደርገው የመንግስቱ ዋና ክፍል በሆኑት በእግዚአብሔር ሕጎች (በቶራ) ዙሪያ ላይ ነው። ይህንንም ስናደርግ
ከፍ ባለው በእግዚአብሔር ሃሳብ፣ ፍቃድና ሕግ ላይ የሚነሳውን እናፈርሳለን። አዳማዊ የሆነ የሰው አስተሳሰብ፣
ወግ፣ ስርዓትና ደንቦችና ሃይማኖታዊ ዶክትሪኖችን እንደ እግዚአብሔር ቃል እናፈርሳለን። “የሰውንም አሳብ
በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ
እንማርካለን፥” 2.ቆሮ.10፥5

የእግዚአብሔር ሕጎች ሕይወት ያለባቸው ቃሎች ናቸው። ሐዋ.7፥38 ይህን ትምህርት መማር
ያስፈለገው ትውልዱን ወደ እውነተኛው የእግዚአብሔር ቃልና የመንግስቱ ሕግ ወደ ሆነው “ቶራ” ሚስጥር ዞር
ለማድረግ፣ ወደ መንግስቱ ሕግና ስርዓት ለመመለስ፣ ድል ነሺ የሆኑ አማኞችን ለመንግስቱ እንዲበቁ እንደ ቃሉ
ለማዘጋጀት ታስቦ ነው። ይህም በእግዚአብሔር መንፈስ ቃሉን በቃሉ ብቻ በመፍታት የሚፈጸም ነው።
የእግዚአብሔር ሕጎችን ኢየሱስ እንዳስተማረውና እንደተረጎመው ማየት ተገቢ ነው። ሉቃ.24፥44-45 “በዚያን
ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤” እንግዲህ ይህ ሳምንታዊ በእግዚአብሔር ሕጎች
ዙሩያ የሚያጠነጥነው የመንግስቱን ሕጎች ትምህርት በመግቢያዬ ነው። ጌታ አእምሮአችንን እንዲከፍት ጸሎቴ
ነው።

የምድር ሕግ ለምን አስፈለገ? መንግስታት ሕግ አያስፈለግም ዝም ብላችሁ ኑሩ አይሉንም።


በእውነት የምድር መንግስታት ሕግ ፈጽሞ ቢያነሱ በእውነት ሰው ያለ ሕግ በሰላም መኖር ይችላልን? በዚሁ
መልኩ ደግሞ እግዚአብሔር ሕጎቹን ፈጽሞ ያስወግዳልን? ያንን ሁሉ ስቃይ በኢየሱስ ከሚያወርድ ዝም ብሎ
ሕጉ ለምን አይሽረውም ነበር? የተለያዩ የእግዚአብሔር ሕጎች በኢየሱስ ክርስቶስና በሐዋርያት በትምህርት
ሲሰጡና አማኞችም ይህንን ፈለግ እንዲከተሉ ሲታዘዙ እናገኛለን። አንዳንድ ጥቅሶችን አስቀድመን እንመልከት፦

ኢየሱስ “እንግዲህ ከነዚህ ከሁሉ ካነሱት ትእዛዛት አንዲቱን የሚሽር ለሰውም እንዲሁ
የሚያስተምር ማንም ሰው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ ታናሽ ይባላል፤ የሚያደርግ ግን የሚያስተምርም ማንም
ቢሆን እርሱ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላል።እላችኋለሁና፦ ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥
ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” ማቴ.5
“ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል፤”
ሮሜ.8፥7፣ ዳንኤል.7፥25
ኢየሱስም “እነሆም፥ አንድ ሰው ቀርቦ፦ መምህር ሆይ፥ የዘላለምን ሕይወት እንዳገኝ ምን መልካም ነገር
ላድርግ? አለው። እርሱም (ኢየሱስ)፦ ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም የሆነ አንድ ነው፤ ወደ ሕይወት
መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ አለው። እርሱም፦ የትኞችን? አለው። ኢየሱስም(ኢየሱስ)፦ አትግደል፥
አታመንዝር፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥አባትህንና እናትህን አክብር፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው።”
ማቴ 19፣ ገላ.5፥21

“ወይም ሌቦች ወይም ገንዘብን የሚመኙ ወይም ሰካሮች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች
የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።” 1.ቆሮ.6፥10
“ ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ
ይሰጣችኋል፤” ዮሐ.14፥15

www.tlcfan.org 1
መለከት #1

“እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፥ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ
ትኖራላችሁ።…እኔ ያዘዝኋችሁን ሁሉ ብታደርጉ እናንተ ወዳጆቼ ናችሁ።” ዮሐ.15

“ትእዛዛቱንም ብንጠብቅ በዚህ እንዳወቅነው እናውቃለን። አውቄዋለሁ የሚል ትእዛዛቱንም


የማይጠብቅ ውሸተኛ ነው እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም።’ 1ዮሐ.2፥1-3

“እግዚአብሔርን ስንወድ ትእዛዛቱንም ስናደርግ የእግዚአብሔርን ልጆች እንድንወድ በዚህ እናውቃለን።


ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤
ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም።” 1ዮሐ.5:፥1-3

“እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? አይደለም፤ ሕግን እናጸናለን እንጂ።” ሮሜ.3፥31

“በነጻነት ሕግ ፍርድን ይቀበሉ ዘንድ እንዳላቸው ሰዎች እንዲህ ተናገሩ፥ እንዲህም አድርጉ።ምሕረትን
ለማያደርግ ምሕረት የሌለበት ፍርድ ይሆናልና፤ ምሕረትም በፍርድ ላይ ይመካል።. . . ከነፍስ የተለየ
ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።” ያቆብ 2

“ስለዚህም ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ።በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ


ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም። በዚያ ቀን ብዙዎች፦ ጌታ ሆይ፥
ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ
ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል።የዚያን ጊዜም፦ ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች
(ትክክለኛ የዓመፀኛ ትርጉም ሕግ የለሾች ሕግን የማይታዘዙ ማለት ነው። በግሪኩ “አኖሚያ”)፥ ከእኔ ራቁ ብዬ
እመሰክርባቸዋለሁ።” ማቴ.7

ቀደም ብዬ ያነሳሁት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚፈልግ አንድ አማኝ በሚገባ ስለ ሶስቱ የሕይወቱ
መንፈሳዊ እድገት ደረጃዎች ትክክለኛ የሆነ እውቀት ሊኖረው ይገባል። አማኝ መንፈሳዊ እድገቱ ከየት ጀምሮ
እስከ የት ድረስ እንደሆነ በደንብ ጠንቅቆ ማወቅ ይጠበቅበታል። 2.ጴጥሮስ.3፥18 “ነገር ግን በጌታችንና
በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን“
እያንዳንዱ አማኝ በቃሉ ውስጥ ለማደግ በተለያየ ስፍራ ላይ በእግዚአብሔር ተጠርተናል። እድገታችን ግን ከየት
ተነስቶ የት ጋር የሚያበቃ እንደሆነ ስንቶቻችን እንናውቅ ይሆን? ሶስቱን የመንፈሳዊ የእድገታችን መነሻና
መድረሻዎችን በቃሉ ውስጥ በተለያየ ምሳሌዎች ተመስለው የተቀመጡልንን አስቀድመን እንመልከት፦

አማኝ እነዚህን የእድረት ደረጃዎች ወይም ሩጫዎች እንዲሮጥ ተጠርቷል። ከግልገልነት እስከ በግነት፣
ከአንደኛ ቀን እስከ ሶስተኛ ቀን፣ ከአደባባይ እስከ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከስጋ እስከ መንፈስ ፣ ከእምነት እስከ ፍቅር፣
ከ30 ፍሬ እስከ 100 ፍሬ፣ ከፋሲካ እስከ ዳስ በዓል፣ ከግብጽ እስከ ከነዓን ፣ ከመንገድ እስከ ሕይወት፣ ከአንደኛ
ሰማይ እስከ ሶስተኛ ሰማይ፣ ከውሃ ጥምቀት እስከ እሳት ጥምቀት. . .ወዘተ። ሁሉ አማኝ በቃሉ ውስጥ ለእድገት
ደረጃዎች በተቀመጡት ደረጃዎች ውስጥ የግድ ያልፍ ዘንድ የእግዚአብሔር ፍቃድና የመንግስቱ ሕግ ነው። ሰው
ዘሎ ከአንደኛው ወደ ሶስተኛው መግባት አይችልም። ግልገል ጠቦት ሳይሆን በግ አይሆንም። ደግሞም በግ እንጂ
ግልገል ድምጽ አይሰማም። ሰው ከግብጽ ዘሎ ከንዓን አይገባም። የግድ ምድረበዳውን ማለፍ አለበት።
ከአደባባይ ተዘሎ ቅድስተ ቅዱሳን አይገባም። ዛሬ ግን ብዙዎቻችን የተማርነው የተገላቢጦሽ ነው። ሰው እነዚህን
መንፈሳዊ እድገቶች ምን እንደሆኑ በትክክል ሲገባው የእግዚአብሔር መንግስት ሕግን ጥቅምንና አስፈላጊነት
በትክክለኛ መልኩ መረዳት ይችላል። (1) Justification (2) Santification (3) Glorification

“አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤


ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው።” ሮሜ.8:፥30

እርግጠኛ ነን ዛሬ ይህ የምንታነቡ ከእነዚህ ከታች ከዘረዘርኩት አራቱ አይነት ሰዎች አንዱ ላይ


እራሳችሁን እንደምታገኙት አምናለሁ፦

www.tlcfan.org 2
መለከት #1

1) አመጸኛዎች፦ (Lawlessnes ‘Anomia”) ሕግ እንዳለ እያወቁ ሕግ የለሽ ኑሮ የሚኖሩና ይህ አይነት


የአመጽ ሕይወት የሚያስደስታቸው። ይህን አይነት ሰዎች ስለ እግዚአብሔር ሕግ ያላቸው እውቀት
የተጣመመ ነው። የእግዚአብሔር ሕግና ትዕዛዛት ለመታዘዝ ምንም አይነት ፍላጎት የሌላቸውም።
ሕጉ ምንም እንደማያስፈልግ ቃሉን እንደፈለጉት በመጠምዘዝ ይህን ሃሳባቸውን ለማጽናት
የሚያስተምሩም ናቸው። የእግዚአብሔር ሕግ ሃጢያት እንደሆነ፣ ምንም የማይጠቅም እንደሆነ፣
በድፍረት በአንደበታቸው ጭምር የሚናገሩ፣ እግዚአብሔር እናገለግላለን የሚሉ ሃይማኖተኛ
ሰዎችና ተራ አመጸኛ አማኞችን ሁሉ የሚያጠቃልል ነው። “እንዲህም አላቸው፦ ወጋችሁን ትጠብቁ
ዘንድ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እጅግ ንቃችኋል” ማር.7፥9 “ኃጢአትን የሚያደርግ ሁሉ ዓመፅን ደግሞ
ያደርጋል፥ ኃጢአትም ዓመፅ (ሕግ የለሽነት) ነው።” 1.ዮሐ.3፥4፣ ማቴ 23 በሙሉ ያንብቡት።

2)በጭፍን የሚጓዙ፦ ይህ አይነት ሰዎች በተሳሳተ መረዳት የእግዚአብሔርን ሕግ የተማሩ፣


ከእግዚአብሔር ሕግ ውስጥም መርጠው የሚታዘዙ፣ ያልገባቸውን ቃሉን የማያነቡትን ምስኪኖች
ሰዎች ደግሞ ዝም ብለው በጭፍኑ የሚያስከትሉትንና የሚከተሉትንም ሰዎች የሚያጠቀልል
ነው። ልክ እንደ ፈሪሳዊያን አስራትን እንደ ሕጉ ከሁሉ ያስወጣሉ። ነገር ግን በሌላ በኩል ደግሞ
ሲመጣ ሕጉን ጥለው በጸጋ ብቻ ነው የምኖረው ይላሉ። “አባቱን ወይም እናቱን አያከብርም
ትላላችሁ፤ ስለ ወጋችሁም የእግዚአብሔርን ቃል (ሕግ) ሻራችሁ። . . . ተዉአቸው፤ ዕውሮችን የሚመሩ
ዕውሮች ናቸው፤ ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።” ማቴ.15፣ ማቴ 23

3) ትንሽ ያወቁ ነገር ግን በደንብ ያልገባቸው፦ የእግዚአብሔር ሕግ እንዳለ ያምናሉ። ሕጉን መታዘዝም
እንደሚገባም ያምናሉ። ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕግ ምን እደሆነና እንዴት መጠበቅ ወይም
ለምን መታዘዝ እንዳለባቸው የማያውቁ ነገር ግን በጣም ቅን ልብ ያላቸው አስተዋዬች ናቸው። ”
ከጻፎችም አንዱ ቀርቦ ሲከራከሩ ሰማና መልካም አድርጎ እንደ መለሰላቸው አስተውሎ፦ ከሁሉ
ፊተኛይቱ ትእዛዝ ማናቸይቱ ናት? ብሎ ጠየቀው።ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ
ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው። አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም
ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ
ይህች ናት።. . .(የጠየቀው ሰውም) በፍጹም ልብ በፍጹም አእምሮም በፍጹም ነፍስም በፍጹም ኃይልም
እርሱን መውደድ፥ ባልንጀራንም እንደ ራስ መውደድ በሙሉ ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከሌላው መሥዋዕት
ሁሉ የሚበልጥ ነው አለው። ኢየሱስም በአእምሮ እንደ መለሰ አይቶ፦ አንተ ከእግዚአብሔር መንግሥት
የራቅህ አይደለህም አለው። ከዚህም በኋላ ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም።” ማር.12:፥26-35

4) ፈጽሞ ምንም የማያውቁ፦ እነዚህ ደግሞ የእግዚአብሔርን ሕግ ሰምተው የማያዉቁ፣ በሰዋዊ


ሞራል የሚኖሩ ሰዎች ወይም ሌላ ባዕድ አምልኮና ሃይማኖት የሚያምኑ ሰዎች ናቸው። ይሁንና
ወደዱም ጠሉም የእግዚአብሔር መንግስት ሕግ በውስጣቸው ይኖራል። በመጨረሻም
እግዚአብሔር የሚፈረድባቸው በዚሁ በልባቸው ባለው በእግዚአብሔር ሕግ ነው። ምክንያቱም
እግዚአብሔር በአዲሱ ኪዳን ውስጥ በልብ ላይ የመጻፍ ሃላፊነትን ለእራሱ ወስዷልና ነው። ደግሞም
“እግዚአብሔር ለሰው ፊት አያዳላምና። ያለ ሕግ ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ ያለ ሕግ ደግሞ ይጠፋሉና፤ ሕግም
ሳላቸው ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ በሕግ ይፈረድባቸዋል፤በእግዚአብሔር ፊት ሕግን የሚያደርጉት
ይጸድቃሉ እንጂ ሕግን የሚሰሙ ጻድቃን አይደሉምና። ሕግ የሌላቸው አሕዛብ ከባሕርያቸው የሕግን
ትእዛዝ ሲያደርጉ፥ እነዚያ ሕግ ባይኖራቸው እንኳ ለራሳቸው ሕግ ናቸውና፤ እነርሱም ሕሊናቸው
ሲመሰክርላቸው፥ አሳባቸውም እርስ በርሳቸው ሲካሰስ ወይም ሲያመካኝ በልባቸው የተጻፈውን
የሕግ ሥራ ያሳያሉ። ይህም እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ እኔ በወንጌል እንዳስተማርሁ በሰው
ዘንድ የተሰወረውን በሚፈርድበት ቀን ይሆናል።” ሮሜ.2

www.tlcfan.org 3
መለከት #1

እንግዲህ ከዚህ ከላይ ከዘረዘርኩት ውስጥ በአንዱ ላይ ራስዎን ካገኙ በዚህ ትውልዶችን ለማንቃትና
ለማዘጋጀት በሚነፋው መለከት ትምህርት ክፍል ላይ የሚሰጡት ተከታታይ ትምህርቶች ለእርሶ ያስፈልጎታል
ብዬ አምናለሁ። ደግሞም ለዚህ ትምህርት ዝግጅት የሚረዳዎትን ሕይወት ያላቸው ቃሎች የሚለውንና
የእግዚአብሔር መንግስት የሚለውን መጽሐፎቼን ያንብቡ።

ኢየሱስ በምድር በነበረበት ወቅት የሙሴን ሕግጋት በሙሉ ጠብቋል። ኢየሱስ የእግዚአብሔር
ሕግጋት የማይጠብቁትንና ጉልበት አልባ ያደረጉትን ጻፎችና ፈሪሳዊያንን ወቅሷል፣ ገስጿል። ኢየሱስም
የመጀመሪያውን የምድር አገልግሎቱን ጨርሶ ወደ አባቱ ሄደ። ኢየሱስ ከሄደ በኋላ የእርሱ ተከታዬች አማኝ
የሙሴን ሕግ መጠብቅ እንዳለባቸውና እንደሌለባቸው ለመነጋገር በኢየሩሳሌም ተሰብስበው ነበር። ከስብስባው
በኋላም ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል። ዛሬ እንደዚያ አይነት ስብሰባ ማድረግ ባንችልም። ዛሬ ስለ እግዚአብሔር
ሕግ ወይም ስለ ሙሴ ሕግ በአማኞችና በማያምኑ ዘንድ የሚነሱትን ጥያቄዎች በቃሉ ለመመለስ እውነቱንም
ለማስተማር ቃሉን የምናስተምር ሰዎች ሁሉ ሃላፊነት ነው። በዚህ መለከት ጹሁፍ ላይ በፌስ ቡክ ሕብረት
አባሎችና ተከታታዬቼ የተጠየቁትን ጥያቄዎች እንደ እግዚአብሔር ቃል እመልሳለሁ። ደግሞም በሌላ ጊዜ
ተመሳሳይ የሆነ ጥያቄ ለሚያነሱ ሰዎች ይጠቅም ዘንድ በማሰብ በትምህርት መልኩ መቀመጥ እንዲችን
የተለያዮ ሕጎችን ፍቺዎችንም እንደቃሉ በመለከት ላይ አስተምራለሁ። በሚቀጥለው መለከት ቁጥር ሁለት ላይ
የእግዚአብሔር ሕግ ለምን፣ ለማንና በማን እንደተሰጠ የሚለውንና የእግዚአብሔር ሕግና የሙሴ ሕግጋት አንድ
እንደሆኑ እንመለከታለን። እከዚያው ድረስ እነዚህን ጥቅሶች እናሰላስል፦ መዝሙረ ዳዊት 119 በሙሉ

“አብርሃም ቃሌን ሰምቶአልና፥ ፍርዴን ትእዛዜን ሥርዓቴን ሕጌንም ጠብቆአልና።” ዘፍ.26፥5

“የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው፤ ነፍስን ይመልሳል፤ የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው፤ ሕፃናትን
ጠቢባን ያደርጋል።” መዝሙር.19፥7

“የነገሩን ሁሉ ፍጻሜ እንስማ፤ ይህ የሰው ሁለንተናው ነውና፤ እግዚአብሔርን ፍራ፥ ትእዛዙንም


ጠብቅ።” መክብብ.12፥13

“መልካም ትምህርትን እሰጣችኋለሁና፤ ሕጌን አትተዉ።እኔም አባቴን የምሰማ ልጅ ነበርሁና፥ በእናቴም


ዘንድ እወደድ ነበር።ያስተምረኝም ነበር እንዲህም ይለኝ ነበር፦ ልብህ ቃሌን ይቀበል፤ ትእዛዜን ጠብቅ
በሕይወትም ትኖራለህ።” “ትእዛዜን ጠብቅ በሕይወትም ትኖራለህ፤ ሕጌንም እንደ ዓይንህ ብሌን
ጠብቅ፤” ምሳሌ.3፥1-4፣ 7፥2

“የሕጌን ብዛት ጽፌለታለሁ፤ እነርሱ ግን እንደ እንግዳ ነገር ቈጥረውታል።” ሆሴ.8፥12

“ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ ሕጌን በልቡናቸው
አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፥ እኔም አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑልኛል።”
ዕብ.8፥10
“መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ስለዚህ ይመሰክርልናል፤ ከዚያ ወራት በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ
ነው ይላል ጌታ፤ በልባቸው ሕጌን አኖራለሁ በልቡናቸውም እጽፈዋለሁ ብሎ ከተናገረ በኋላ፥”
ዕብ.10፥15-16
“ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን
ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ፤” ራእይ.12፥17

የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁት ኢየሱስንም በማመን የሚጸኑት ቅዱሳን ትዕግሥታቸው በዚህ


ነው” ራእይ14፥12

www.tlcfan.org 4
መለከት #1

www.tlcfan.org 5

You might also like