Professional Documents
Culture Documents
How Do I Know My Calling
How Do I Know My Calling
1
21 May 2023
2
21 May 2023
3
21 May 2023
ጥሪ ምንድን ነው?
ጥሪ እግዚአብሔር አስቀድሞ ( አለም ሳይፈጠር) ወደ አዘጋጀልን ሕይወትና የሕይወት
አላማ እንድንገባ የሚደረግ ግብዣ ነው።
ለሰው ሁሉ እጅግ ዋና ከተባሉ ክስተቶች ሁለቱ የተወለደበት ቀንና የሕይወት አላማውንና
ጥሪውን ያውቀበት ቀን ነው።
የሕይወት አላማና ጥሪ በሰው የሚገኝ እንጅ በሰው የሚዘጋጅ አይደለም።
የአንድ ሰው የሕይወት ጥሪ በሉአላዊ አምላክ ሉአላዊ ውሳኔ ላይ የተመሰረተ ነው።
ሉአላዊ አምላክ ማለት የፈለገውን ነገር በፈለገው ጊዜ፤ በፈለገው መንገድ የማንንም
ፈቃድ ሳይጠቅ የሚያደርግ ማለት ነው።
ይህን መረዳት ለሰው ልጅ እጅግ አስፈላጊ ነው። ያልከው ይሁን ብሎ ተስማምቶ የልዑል
አምላክን እርዳታና ይሁንታ የሚያገኝ ሕይወት ለመምራት ይረዳል።
4
21 May 2023
የፈቃድ ሁሉ ምንጭ አብ ነው
የሐዋርያት ሥራ 1፡7 እርሱም፦ አብ በገዛ ሥልጣኑ ያደረገውን ወራትንና
ዘመናትን ታውቁ ዘንድ ለእናንተ አልተሰጣችሁም፤
እዚህ ላይ ጌታችን መዳህኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰውነቱ ያልተሰጠው ድርሻ እንደሆነ
የሚያመላክት ነው።
የዮሐንስ ራእይ 4፡10-11 ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥
ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ፦ ጌታችንና አምላካችን ሆይ፥ አንተ
ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም
ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ።
እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ለፈቃዱ በፈቃዱ ፈጥሮታል። ባለሙሉመበት ነው። ባለቤት
ነው።
ለዚህ እውቅና መስጠት ብቻ ሳይሆን ሕይወትን መስጠት አምልኮ ነው። ምስጋናና ውዳሴ
ምንጫቸው ይሄ ነው።
ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ ይህም ርስት
በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል
ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል።
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1፡3 በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።
ጥሪ ቁልፍ ነው!
አንድ ሰው ጥሪውን ሲያገኝ እግዚአብሔር አለም ሳይፈጠር ለእርሱ ያዘጋጀለትን ሁሉ
የሚያገኝበትን ቁልፍ አግኝቶአል።
2 ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1፡9 ያዳነን በቅዱስም አጠራር የጠራን እግዚአብሔር ነውና፥
ይህም እንደ ራሱ አሳብና ጸጋ መጠን ነው እንጂ እንደ ሥራችን መጠን አይደለም፤
ይህም ጸጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰጠን፥
የዘላለም ሕይወት፤ በምድር የምንሆነውና የምናደርገው፤ በዘላለም የእግዚአብሔር አጀንዳ
ውስጥ ያለን ስፍራ ሁሉ በአምላክችን አስቀድሞ የተሰወሰነ ቢሆንም መግቢያው ግን ጥሪ
ነው።
ጥሪና የጸጋ ስጦታ የተለያዩ አለመሆናቸውን ተመልክተናል። ጸጋን መረዳት ወደ ጥሪያችን
ዘልቀን ለመግባት እጅግ ስለሚረዳን በሚቀጥለው የእግዚአብሔርን የጸጋ ስጦታ
እንመለከታለን።
ጸጋን ምን እንደሆነ በሚገባ ተረድተን ጸጋውን በሕይወታችን መቀበል ስንችል ባለጸጋ
እንሆናለን።
ጸጋ የበዛለት እንሆናለን።
7
21 May 2023
10
21 May 2023
11
21 May 2023
ትንቢተ አሞጽ 5፡8 ሰባቱን ከዋክብትና ኦሪዮን የተባለውን ኮከብ የፈጠረውን፥ የሞትን ጥላ
ወደ ንጋት የሚለውጠውን፥ ቀኑንም በሌሊት የሚያጨልመውን፥ የባሕሩንም ውኆች
ጠርቶ በምድር ፊት ላይ የሚያፈስሳቸውን፥
እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ነው ስንል ከዚህም ሁሉ ይልቃል።
ወደ ዕብራውያን 4፡13 እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና
የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።
ሁሉን ቻይ የሆነውን የእግዚአብሔር እውቀትና ጥበብ በእኛ ውስን እውቀትና ጥበብ
በመለካት ምርጫውንና ውሳኔውን መመዘን አንችልም።
እጅግ ደስ የሚለው ነገር የእግዚአብሔር ምርጫና ውሳኔ ልክ እንደ እግዚአብሔር የጸና
ነው። አይሻርም አይለወጥም።
13
21 May 2023
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1፡11 እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ፥
አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን።
የፈቃዱ ምክር ማለት የእርሱ አላማ ማለት ሲሆን አስቀድመን የተወሰንን ማለት ደግሞ
የእርሱ እቅድ ማለት ነው።
እግዚአብሔር ያለመው ነገር አለ። ለዚያ እኔና እናንተን አስቀድሞ ወሰነን።
የሰው ልጅ ሕይወት አላማ ምንድን ነው?
መጀመሪያ ይህ ጥያቄ ሳይመለስ የግል ሕይወት አላማ ጥያቄ ሊመለስ አይችልም።
እግዚአብሔር ሰውን ለምን ፈጠረው የሚለውን ለእስራኤል ከተናገራት ቃል መረዳት
እንችላለን
ትንቢተ ኢሳይያስ 43፡1 አሁንም ያዕቆብ ሆይ፥ የፈጠረህ፥ እስራኤልም ሆይ፥
የሠራህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ተቤዥቼሃለሁና አትፍራ፤ በስምህም
ጠርቼሃለሁ፥ አንተ የእኔ ነህ።
በዚህ ስፍራ አንተን የፈጠርኩህ፤ ከዚያም የሰራሁህ፤ ከዚያም የተቤዥሁህና የጠራሁህ የእኔ
ስለሆንክ ነው ይላል።
ሰው የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ነው። ይህ መሰረታዊ መረዳት ለሁላችንም እጅግ
አስፈላጊ ነው። እኔ የእግዚአብሔር ነኝ። አንተ የእግዚአብሔር ነህ። አንች የእግዚአብሄር
ነሽ።
ቀጥሎ ያለውን የእግዚአብሔር ቃል ስንመለከት ደግሞ እግዚአብሔር ለምን ፈጥሮ፤
ሰሮቶና አብጅቶ የእራሱ እንዳደረገን ይናገራል።
ትንቢተ ኢሳይያስ 43:6-7 ሰሜንን፦ መልሰህ አምጣ፥ ደቡብንም፦ አትከልክል፤
ወንዶች ልጆቼን ከሩቅ ሴቶች ልጆቼንም ከምድር ዳርቻ፥ በስሜ የተጠራውን
ለክብሬም የፈጠርሁትን፥ የሠራሁትንና ያደረግሁትን ሁሉ አምጣ እለዋለሁ።
በስም መጠራት ማለት ቃልኪዳናዊ ትስስርን አመልካች ነው። ሚስት በባሏ ስም
እንደምትጠራ ለክብሩ የተፈጠረው ህዝቡም በእግዚአብሔር ስም ተጠርቶአል።
ሰራትና መደረግ ከምን ጋር እንደሚገናኝ አዳም ክላርክስ እንዲህ ይላል
16
21 May 2023
17
21 May 2023
18
21 May 2023
1. በልብ ብርሃን
2. በልባችን ውስጥ ከፍተኛ ፍላጎትና መሻት በመስጠት
3. በህልምና ራዕይ
4. በማረጋገጫዎች ይመራናል።
የጥሪ አይነቶች
የጥሪ አይነቶች ስንት ናቸው?
21
21 May 2023
23
21 May 2023
ነህምያ፦
መጽሐፈ ነህምያ 2፡12 በሌሊትም ተነሣሁ፥ ከእኔም ጋር አያሌ ሰዎች ነበሩ፤
እግዚአብሔርም ለኢየሩሳሌም አደርገው ዘንድ በልቤ ያኖረውን ለማንም
አላስታወቅሁም፤ ተቀምጬበት ከነበረው እንስሳ በቀር ከእኔ ጋር ምንም እንስሳ
አልነበረም።
24
21 May 2023
25
21 May 2023
መሾምና መቀባት
ጥሪያችን ያለእኛ ምንም አስተዋጽኦ በእግዚአብሔር ነጻ ምርጫ ወደ ተመረጥንበት የከበረ
ሕይወትና ፍጻሜ የሚደረግ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው።
ወደ ሮሜ ሰዎች 11፡29 እግዚአብሔር በጸጋው ስጦታና በመጥራቱ
አይጸጸትምና።
መወሰንም መጠራትም መመረጥም የእግዚአብሔር ጸጋ ውጤቶች ናቸው።
ወደ ሮሜ ሰዎች 11፡5 እንደዚሁም በአሁን ዘመን ደግሞ በጸጋ የተመረጡ
ቅሬታዎች አሉ።
ከሰው የሚጠበቀው ምላሽ መስጠት ብቻ ነው።
ለእግዚአብሔር ውሳኔና ጥሪ ከምስጋናና መሰጠት ጋር ምላሽ ስንሰጥ እግዚአብሔር ወደ
ተወሰነልና ስፍራና ወደተወሰነልን ጸጋ ያስገባናል።
ይሾመናል፤ ለተሾምንበት ስፍራ ሃይልን፤ ጥበብን፤ አቅምን የሚሰጠንን ጸጋ ይሰጠናል።
ለሕይወት ይቀባናል፤
2 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡21 በክርስቶስም ከእናንተ ጋር የሚያጸናንና የቀባን
እግዚአብሔር ነው፥
1 ኛ የዮሐንስ መልእክት 2፡20 እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም
ታውቃላችሁ።
1John 2፡20 But ye have an unction from the Holy One, and ye know all things.
1 ኛ የዮሐንስ መልእክት 2፡27 እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ
ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ
ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥
እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ።
( ይህ ቅባት የምንኖርበት ቅባት ነው)
ለቤት ስራችን ይቀባናል።
1 ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1፡12 ለአገልግሎቱ ሾሞኝ ታማኝ አድርጎ ስለ ቈጠረኝ፥ ኃይል
የሰጠኝን ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታችንን አመሰግናለሁ፤
ለተጠራንበትና ለተሾምንበት ስፍራ የሚሆን ኃይል ( ቅባት) እግዚአብሔር በአደራ
ይሰጠናል።
26
21 May 2023
1Tim 1፡12 And I thank Christ Jesus our Lord, who hath enabled me, for that he
counted me faithful, putting me into the ministry;
ኃይል የሰጠኝን የሚለው ቃል፡ 1743 endunamoo en-doo-nam-o'-o ሲሆን የተገኘው (from 1722 and
1412; to empower:--enable, (increase in) strength
27
21 May 2023
28