You are on page 1of 9

www.abyssinialaw.

com

የባንክ ዋስትና ሰነድች (Letter of Guarantees) በኢትዮጵያ ሕግ ያሊቸው ሽፋን

ገዙ አየሇ መንግስቱ
የዋስትና ሰነድች1 ባንኮች በተሇይም ሇዯንበኞቻቸው ከሚሰጧቸው የብዴር አገሌግልቶች
መካከሌ ዋነኞቹ ናቸው። የዋስትና ሰነድች በባንኮች የሚሰጡት ዯንበኞች የተሇያዩ
ስምምነቶችን ከላልች ሶስተኛ ወገኞች ጋር ፈጽመው ያሇባቸውን ግዳታ በአግባቡ
ሇመወጣታቸው ከባንኮች ዋስትና እንዱሰጥሊቸው በሚያቀርቡት ጥያቄ መሰረት ነው።
የዋስትና ዯብዲቤ የሚሰጠውም አንዴን ሰው የብዴር አገሌግልት ወይም እቃዎቸንና
አገሌግልቶችን ሇላሊ ሶስተኛ ወገን በብቃት እንዱያቀርብ መተማመኛ በመሆን ነው።2 ዋስትና
ሰነዴም አንዴ ሰው አንዴን የተሇየና የተወሰነ ስራ ሇላሊ ሰው ሇመስራት ግዳታ ከገባ ይኸው
ሰው በውለ መሰረት የገባውን ግዳታ መፈጸም የሚችሌ መሆኑን ሇማረጋገጥ ላሊው ሰው
የሚያቀርበው ውሌ ነው።3 የዋስትና ሰነድች የባንክ የብዴር አይነቶች ወይም የብዴር
አገሌግልት መሆናቸውን ከማየታችን በፊት ግን የዋስትና ሰነድች ምን ማሇት እንዯሆኑ ማየቱ
ተገቢነት ይኖረዋሌ።

የዋስትና ዯብዲቤ አንዴ ዯንበኛ የፈሇገውን የንግዴ እንቅስቃሴዎችና ግንኙነቶችን እንዱፈጽም


ሇማስቻሌ ዯንበኛው ሇአቅራቢው ወይም የአገሌግልት ተግባር ሇመፈጸም የተዋዋሇውን
ዯንበኛ ስራውን እንዱያከናውን ሇማስቻሌ የሚሰጥ ዯብዲቤ ሲሆን የዋስትና ዯብዲቤውን
የሚያዘጋጀው ባንክም ሰነደ የተዘጋጀሇት ዯንበኛ ግዳታውን መወጣት ባይችሌ ሇተጠቃሚው

1
የዋስትና ሰነድች በተሇያዩ ስያሜዎች የሚጠሩ ሲሆን በዚህም መሰረት በእንግሉዝኛ ‘independenundertakings’, ‘performance
bonds/guarantees’, ‘tender bonds/guarantees’, ‘independent (bank) guarantees’, ‘demand guarantees’, ‘first demand
guarantees’, ‘bank guarantees’, and ‘default undertakings’ በሚለ ስሞች ሉጠሩ ይችሊለ። ከዚህ በተጨማሪም እነዚሁ
ሰነድች’standby Letters of Credit’ ተብሇው ሉጠሩ እንዯሚችለ የተሇያዩ ጽሁፎች ያሳያለ። See M Coleman ‘Performance
Guarantees’ (1990) Lloyd’s Maritime and Commercial Law Quarterly 223 at 223. በዚህ መጽሀፍ ውስጥም
የዋስትና ሰነድች የሚሇው ጥቅሌ ስያሜን ሇመጠቀም የተሞከረ ሲሆን አንዲንድቹ ስያሜዎችም የዋስትና አይነቶችን የሚያመሇክቱ
መሆኑን መገንዘብ ያስፈሌጋሌ።
2
MC Kuchhal (2015), Merchantile Law, VIKAS PUBLISHING HOUSE PVT LTD.
3
የፌዯራሌ ጠቅሊይ ፍርዴ ቤት ሰበር ሰሚ ችልት የሰበር መዝገብ ቁጥር 47004፤ በአመሌካች የኢትዮጵያ መዴን ዴርጅት እና ተጠሪ
ባላ ገጠር ሌማት ዴርጅት፤ ቅጽ 12 የተሰጠ የሰበር ውሳኔ።
www.abyssinialaw.com
በቀጥታ ግዳታውን እንዯሚወጣ በማረጋገጥ የሚዘጋጅ ነው። የዋስትና ሰነድችን በተመሇከተ
የህግ ሽፋን የሰጠው የተባበሩት መንግስታት ኮንቬንሽን (UN Convention on
Independent Guarantees and Standby Letters of Credit) የዋስትና ዯብዲቤ ምን
ማሇት እንዯሆነ እና የዋስትና ዯብዲቤ አይነቶችንም ሇመዘርዘር ሞክሯሌ።4 በዚሁ አሇም
አቀፍ ህግ መሰረትም የዋስትና ዯብዲቤ በአዘጋጁ (በብዛት ባንኮች ሲሆኑ) ዯብዲቤው
ሇተዘጋጀሇት ተጠቃሚ ዋስትና የተገባሇት ግዳታ በባሇዕዲው የማይከፈሌ ቢሆን የዋስትና
ዯብዲቤውን የጻፉት ባንኮች ባሇዕዲውን ተክተው ክፍያውን (ዕዲውን) ሇመክፈሌ ዋስትና
እንዯሚሆኑ በመግሇጽ የሚሰጥ ዯብዲቤ ነው። ይሁንና ግን ይህ ኮንቬንሽን የሚያገሇግሇው
አሇም አቀፍ የሆኑ ግብይቶችን በተመሇከተ እንዯሆነ ተገሌጿሌ።5 ኮንቬንሽኑንም የፈረሙት
ሀገሮች ጥቂት በመሆናቸው ሁለም ሀገሮች በዚህ ስምምነት መሰረት ይዲኛለ ባይባሌም
አብዛኛው ሀገራት ግን የዋስትና ሰነድችን በተመሇከተ በሚያወጧቸው ህጎች የዚህን ስምምነት
አንቀጾች ከግንዛቤ በመክተት ሉሆን ይችሊሌ። ኮንቬንሽኑ በተሇይም የተሇያዩ አይነት የዋስትና
ዯብዲቤ አይነቶች እንዲለ ዯንግጓሌ።

ከዋስትና ሰነድች ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ህግ ያሇው ዋናው ችግር የዋስትና ዯብዲቤ ምን


ማሇት እንዯሆነና ምን ምን ነገሮችን ማካተት እንዲሇበት እንዱሁም የእነዚህ የዋስትና
ዯብዲቤዎች ያሊቸው ህጋዊ አስገዲጅነትስ እስከምን ዴረስ ነው? የዋስትና ሰነድች ከላልች
የዋስትና አይነቶች (እንዯ ሰው ዋስትና እና የንብረት ዋስትና) ጋር ያሊቸው አንዴነት እና
ሌዩነት ምንዴነው? እንዱሁም የዋስትና ሰነድች እየተሰራባቸው ካሇው ሌማዲዊ አሰራር መነሻ
ያዯረገ ላሊ ህግ ይኖራሌ ወይ የሚለት ነጥቦች መብራራት ያሇባቸው ናቸው።

ዋስትና የገንዘብ፣ የሰው እንዱሁም የንብረት እና የሰነዴ ዋስትና ሉሆን ይችሊሌ። እነዚህ
የዋስትና አይነቶች ግን በየራሳቸው ሌዩነት ያሊቸው ሲሆን ሁለንም በተመሳሳይ መሌኩ
ትርጉም በመስጠት ወይም አንደን በአንደ እያቀያየርን መጠቀም በመሰረታዊነት ያለትን
የተሇያዩ የዋስትና አይነቶች እና ያሊቸውን ጠቀሜታ የሚያጠፋ ይሆናሌ። በዋናነት በንብረት፤

4
UN Convention on Independent Guarantees and Standby Letters of Credit, articles 1 and 2.
5
ዝኒ ከማሁ፤ አንቀጽ( 1)።
www.abyssinialaw.com
በሰው እና በሰነዴ ዋስትና መካከሌ ያሇውን ሌዩነት ሇመገንዘብ የፍትሐብሔር ህጉን
ዴንጋጌዎች መመሌከት ያስፈሌጋሌ።

የፍትሐብሔር ህጉ የሰው ዋስትናን (Suretyships or Guaranteership) በተመሇከተ


ከአንቀጽ 1920 እስከ 1951 ዴረስ ባለት ዴንጋጌዎች ሰፊ ሽፋን ሰጥቷሌ። እነዚህ የህጉ
ዴንጋጌዎች ግን የሚገሇጹት ስሇ ሰው ዋስትና ሲሆን በዚህም መሰረት ግሇሰቦች ራሳቸውን
ሇአንዴ ብዴር ዋስትና አከፋፈሌ ባሇዕዲው በገባው ውሌ መሰረት ግዳታውን መፈጸም
እንዱችሌ ሇማረጋገጥ የሚሰጡት ዋስትና ነው። በፍትሐብሔር ህጉ ሊይ የተገሇጹት ዋስትናን
የተመሇከቱት ዴንጋጌዎች ከውሌ ህግ ጋር የሚያያዙ በመሆናቸው የባንክ የብዴር ግንኙነቶችን
አስመሌክቶ በባንክ የሚዘጋጁትን የዋስትና ዯብዲቤዎችን የማይወክለና የማይመሇከቱ
ናቸው። በባንክ የሚዘጋጁት የዋስትና ዯብዲቤዎች በባንኮች ከመዘጋጀታቸው በፊት ዋስትና
ዯብዲቤው እንዱዘጋጅሇት የጠየቀው ዯንበኛ የዋስትና ዯብዲቤውን ከማግኘቱ በፊት
ሇዯብዲቤው መሰረት የሆኑ ሁሇት አይነት የተሇያዩ እና በራሳቸው የቆሙ ውልችን
ይዋዋሊሌ። አንዯኛው ውሌ የዋስትና ዯብዲቤው እንዱዘጋጅሇት የጠየቀው ሰው ሉፈጽመው
የገባው የአገሌግልት ወይም የአቅርቦት ወይም ላሊ ግዳታን የተመሇከተና ከሶስተኛ ወገን ጋር
የሚገባው ውሌ ነው።ሁሇተኛው ውሌ ዯግሞ የዋስትና ዯብዲቤውን ከባንክ እንዱፈቀዴሇት
የሚጠይቀው ሰው ከባንኩ ጋር የሚገባው ውሌ ነው። ይህ ውሌ የዋስትና ዯብዲቤ
እንዱጻፍሇት ጥያቄ ያቀረበው ሰው ዯብዲቤው በባንኩ እንዱጻፍሇት ባንኩ የሚጠይቀውን
አይነት ዋስትና ማሇትም የንብረት ወይም የጥሬ ገንዘብ ዋስትና በማቅረብ የሚዋዋሇው
የመያዣ ውሌ ነው። እነዚህ ሁሇት ውልችም እርስ በእርሳቸው የማይገናኙ እና በራሳቸው
የቆሙ ናቸው ማሇት ይቻሊሌ። የዋስትና ዯብዲቤው ዯግሞ ከእነዚህ ውልች በኋሊ በባንኮች
የሚሰጥ የዋስትና ሰነዴ ሲሆን ይህንን በባንኮች ተዘጋጅቶ ሇባሇእዲው የሚሰጠውን ዯብዲቤ
ግን እንዯ ውሌ ሌንቆጥረው የምንችሇው ሳይሆን በቅዴሚያ ባንኮች እና የዋስትና ሰነደን
የጠየቀው ሰው በገቡት የመያዣ ውሌ አማካኝነት የሚዘጋጅ ዯብዲቤ እንዯሆነ የሚቆጠር
ነው።
www.abyssinialaw.com
በመሆኑም የዋስትና ዯብዲቤው የሚዘጋጀው በባንኮች በመሆኑና በዯብዲቤው ሊይ
የሚፈርመውም የሚያዘጋጀው ባንክ ብቻ በመሆኑና የዋስትና ዯብዲቤው ሊይ ዋስትና
የተገባሇት ሰውም ፊርማውን የማያኖር ሲሆን በዯብዲቤው ሊይም የምስክሮች ፊርማም ሆነ
ስም በአብዛኛው አይቀመጥም። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚያሳየው ዯብዲቤውን ውሌ
ሇማሇት የውሌ መሰረታዊ ሁኔታዎችን ያሊሟሊ መሆኑን ሲሆን ውሌ ነው የምንሌ ቢሆን
እንኳን ከራስ ጋር የተዯረገ ውሌ እንዯሆነ ከመቆጠር ውጪ ላልች ውልች የሚያሟለትን
ነጥቦች የሚያሟሊ አይዯሇም። በዚህም መሰረት የዋስትና ዯብዲቤን ሇማዘጋጀት በአብዛኛው
የሚቀርበው የመያዣ ንብረት በመሆኑና የሰው ዋስትና በፍትሐብሔር ህጉ በተቀመጠው
መሰረት የዋስትና ዯብዲቤ ሇመጻፍ እንዯመያዣ የማይቀርብ በመሆኑ በሰው ዋስትናና
በሰነድች ዋስትና መካከሌ መሰረታዊና ሰፊ ሌዩነት እንዲሇ መገንዘብ ያስፈሌጋሌ ማሇት ነው።
በመሆኑም ይህ የዋስትና አገሌግልት በዋናነት ሰውን እንዯዋስትና ወይም እንዯ መያዣ
ማቅረብን የሚመሇከት አይዯሇም። ሇዚህም ይመስሊሌ የፍትሐብሔር ህጉ ራሱ የሰው
ዋስትናን እንዯ አንዴ የዋስትና አይነት በዘረዘረበት የህጉ ዴንጋጌዎች አሁን ባንኮች
የሚጠቀሙባቸውን የመሌካም ስራ አፈጻጸም ዋስትና፣ የውሌ ማስከበሪያ ዋስትና፣ የጨረታ
ማስከበሪያ ዋስትና ዯብዲቤዎችንና ላልችንም የተሇያዩ ቅዴመ ሁኔታዎችን መሰረት አዴርገው
እና ሇተሇያዩ አሊማ የሚውለትን የዋስትና አይነቶችም ቢሆን ሇመዘርዘር ያሌቻሇው።

በሀገራችን በተሇይም እነዚህ የዋስትና አይነቶች በአሇም አቀፍ ዯረጃም በተገባር ሊይ መዋሌ
የጀመሩትና ይህ ሌማዴም ወዯ ሀገራችን ገብቶ በባንኮች መተግበር የጀመረውም የንግዴ ህጉና
የፍትሐብሔር ህጉ ከወጡ በኋሊ በመሆኑ የዋስትና ሰነድን በተመሇከተ የፍትሐብሔር ህጉን
መሰረት በማዴረግ የሚሰጡ የፍርዴ ቤት ውሳኔዎችም ሆነ የህግ ትርጉሞች በመሰረታዊነት
እነዚህ በባንኮች በአገሌግልት ሊይ የሚውለ የዋስትና ሰነዴ አይነቶችን የማይወክለ
የሚሆኑት።6 በአሇም አቀፍ ዯረጃም ቢሆን የዋስትና ሰነድችን በተሇይም (Independent
6
MICHELLE KELLY-LOUW (2008), SELECTIVE LEGAL ASPECTS OF BANK DEMAND GUARANTEES, PhD thesis.
Banks in the United States developed the use of standbyletters of credit as a result of the accepted construction of
the United States’ National Bank Act of 3 June 1864 (as amended) which precluded the United States banks from
giving guarantees as part of their banking business. በተጨማሪም በአብዛኛው የዋስትና ሰነድችን በአሇም አቀፍ ዯረጃ የሚገዙ
ህጎች፣ እንዯ URDG 458 እና URDG 758 በተግባር ሊይ የዋለት ከ1992 እስከ 2010 በሆኑት ጊዜያት እንዯሆነ ሰነድቹ ያሳያለ።
www.abyssinialaw.com
Letter of Guarantees) በተመሇከተ በኮዴ መሌክ የወጣውና በአብዛኛው ሀገሮችና
ተቋማት አገሌግልት ሊይ የሚውሇው URDG 458 የሚባሇው ሰነዴ ሲሆን ሰነደም ከጥቂት
አመታት በኋሊ URDG 758 በሚሌ ተሻሻል ቀርቧሌ።7 ስሇዚህም የዋስትና ሰነድች ታሪካዊ
አመጣጥና በተግባር አገሌግልት ሊይ መዋሌ የጀመሩትም የኢትዮጵያ የፍትሐብሔርና የንግዴ
ሕግ ከወጡ በኋሊ መሆኑን መገንዘብ ይቻሊሌ።

በፌዯራሌ ጠቅሊይ ፍርዴ ቤት ሰበር ሰሚ ችልት በሰበር መዝገብ 47004 በተሰጠ አስገዲጅ
የህግ ውሳኔ መሰረት የመሌካም ስራ አፈጻጸም ዋስትና ውሌ በፍትሐብሔር ሕግ ዴንጋጌዎች
መሰረት የሚገዛ መሆኑን ገሌጿሌ።8 ሰበር ችልቱ በርካታ ትንታኔዎችን በጉዲዩ ሊይ ሇመስጠት
የተጓዘበት ርቀት ጥሩ የሚባሌ ቢሆንም በመሰረታዊነት ግን ውሳኔው ሁለንም የህግ ባሇሙያ
ሉያስማማ የሚችሌ አይመስሌም። ሇዚህም ዋነኛ ምክንያቱ በውሳኔው ሊይ የዋስትና ሰነዴን
የዋስትና ውሌ ሲሌ የገሇጸው ሲሆን ከሊይ በተመሇከትነው መሰረት ግን ሰነደ በባንኮች
ተዘጋጅቶ የዋስትና ተጠቃሚውም ሆነ አበዲሪው በዚህ ሰነዴ ሊይ ምንም አይነት የስምምነት
ፊርማ ሳያስቀምጡ፤ እንዯላልች ውልችም ምስክሮች መኖርም ሆነ መፈረም ሳያስፈሌጋቸው
በባንኮቹ ብቻ ተፈርመው ሇዋስትና ተጠቃሚው የሚሰጡ ሰነድች ናቸው።

በመሆኑም በዚህ ሰነዴ ሊይ እንዯውሌ ሇመቆጠር ቢያንስ ሁሇት ወገኖች በውለ


ስሇመስማማታቸው በጸሁፍ በሆነ ሰነዴ ሊይ መፈረምና ምስክሮችም ስማቸውንና
ፊርማቸውን ማስቀመጥ እንዯሚገባቸው የውሌ ህግ እያስገዯዯ እነዚህ ነጥቦች ባሌተሟለበት
ሁኔታ ሰነደን ውሌ ማሇት መሰረታዊ የውሌ መርህን የሚጥስ ነው። ላሊው የሰበር ትንታኔው
የዋስትና ውሌ ብል የጠራውን ሰነዴ በፍትሐብሔር ሕጋችን አንቀጽ 1920 እስከ 1951
የተቀመጠ መሆኑን በመጥቀስ የዋስትና ውሌ በችሮታ ሊይ የተመሰረተ ግዳታ መሆኑን
በመግሇጽ ዋሱ ዋስ በመሆኑ የሚያገኘው ጥቅም የላሇ በመሆኑ አንዴ ሰው ባሇእዲው
ሳይጠይቅ ወይም ሳያውቅ ዋስ መሆን እንዯሚችሌ መመሌከቱ ግንኙነቱ የግዴ ጥቅም ሊይ

7
ዝኒ ከማሁ።
8
የፌዯራሌ ጠቅሊይ ፍርዴ ቤት ሰበር ሰሚ ችልት የሰበር መዝገብ ቁጥር 47004፤ አመሌካች የኢትዮጵ ያ መዴን ዴርጅት እና ተጠሪ
ባላ ገጠር ሌማት ዴርጅት፤ ቅጽ 12።
www.abyssinialaw.com
ያሌተመሰረተ መሆኑን የሚያሳይ ነው በሚሌ ያስቀመጠው ነው።9 ይህ ትንታኔም በአንዴ
በኩሌ የሰው ዋስትናን ከሰነዴ ዋስትና ጋር ሇማመሳሰሌ የተዯረገ ይመስሊሌ። ይሁንና ስሇሰው
ዋስትና የተቀመጠው ይህ ትንታኔ በምንም መሌኩ የሰነዴ ዋስትናን የሚወክሌ አይዯሇም።
ምክንያቱ ዯግሞ በባንኮችም ሆነ በኢንሹራንስ ዴርጅቶች የሚሰጡ የሰነዴ ዋስትናዎች
እስካሁን ባሇው ተጨባጭ ሁኔታ በችሮታ የሚሰጡ ሳይሆን በተሇይ ባንኮች የሰነዴ
ዋስትናዎችን ሇመጻፍ ከተጠቃሚው ጋር የንብረት ወይም የገንዘብ መያዣ ውሌ የሚገቡ
ሲሆን የዋስትና ሰነድቹንም ሇተጠቃሚው የሚጽፉት የዋሰትና መጠኑን መሰረት አዴርገው
በሚቀበለት የገንዘብ ኮሚሽን እንጂ በችሮታ አሇመሆኑ ነው።

ችሮታም የሰው ዋስትና መሰረታዊ መሇያ ባህሪ እንጂ ሇሰነድች ዋስትና የሚሰራ ጉዲይ
አይዯሇም። የሰነዴ ዋስትና ሇመጻፍም ባሇእዲው ሳያውቅ መጻፍ የማይቻሌ ሲሆን የሰነዴ
ዋስትናን ሇመጻፍ የግዳታ ባሇእዲው በአካሌ ቀርቦ ሇባንኩ ማመሌቻ ማስገባትና ሇሰነደ
መጻፍ መሰረት የሆነውን የመያዣ ውሌ መዋዋሌ ግዴ የሚሌ ነው። በመሆኑም የሰነዴ ዋስትና
ሇመስጠት የባሇእዲው መቅረብና ስሇዋስትናው ማወቅ የግዴ ነው። በላሊ በኩሌ ከሊይ
ሇመግሇጽ እንዯተሞከረው የዋስትና ሰነዴ የፍትሐብሔር ህጉ ከወጣ በኋሊ የመጣ ጽንሰ ሀሳብ
በመሆኑ ይህንን ግዳታ ወዯፍትሐብሔር ህጉ ወስዯን ትርጉም ሇመስጠት መሞከሩ አግባብ
ያሌሆነ መሆኑ ነው። በመሆኑም የሰበር ችልቱ የሰነዴ ዋስትናን ከሰው ዋስትና ጋር ሇማዛመዴ
የሞከረበት ትንታኔው ከዚህ በሊይ በተጠቀሱት ምክንያቶች ተቀባይነት ያሇው
አይመስሌም።ይህ የሚያመሇክተንም በመሰረቱ እነዚህ የዋስትና አይነቶች በሌማዴ ባንኮች
በተግባር በሰፊው ይጠቀሙባቸው እንጂ አገሌግልታቸው ተሇይቶ እንዳት እንዯሚዘጋጁ እና
በምን ህግ እንዯሚገዙም የሚገሌጽ ግሌጽ የህግ ዯንጋጌ አሁን ባለት የንግዴ ህግም ሆነ
በፍትሐብሔር ህግ ውስጥ የላሇ መሆኑን ነው።

የዋስትና ሰነድች በሁኔታ ሊይ የተመሰረቱና በሁኔታ ሊይ ያሌተመሰረቱ ሉሆኑ ይችሊለ።


በሁኔታ ሊይ የተመሰረተ ዋስትና የሚባሇው ዋሱ ባሇዕዲው ግዳታውን በማንኛውም ሁኔታ
ሳይወጣ ቢቀር ግዳታውን ያሌተወጣው በምንም ምክንያት ይሁን ምክንያቱን መጠየቅ

9
የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 921ን ይመሌከቱ።
www.abyssinialaw.com
ሳይጠበቅበት የተባሇው ግዳታ እንዲሌተፈጸመ በአበዲሪው ሲገሇጽሇት በዋስትና ዯብዲቤው
የጊዜ ገዯብ ውስጥ መሆኑን በማረጋገጥ የሚከፈለ የዋስትና ዯብዲቤዎች ናቸው። በሁኔታ ሊይ
የተመሰረቱ የዋስትና ዯብዲቤዎች ዯግሞ ዋሱ ሇአበዲሪው የዋስትና ግዳታውን ሇመወጣት
እንዱያስችሇው ባሇአዲው (ዋስትና የተገባሇት ሰው) ግዳታውን ያሌተወጣው በማን ጥፋት
ነው የሚሇውን ካረጋገጠ በኋሊ እና ጥፋቱ የባሇእዲው መሆኑ ከተረጋገጠ በኋሊ የሚወጣው
ግዳታ ነው።

ባንኮች በአሁኑ ወቅት እየሰጡዋቸው ካለ የዋስትና ሰነዴ አይነቶች ውስጥ የመሌካም ስራ


አፈጻጸም ዋስትና፣ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና፣ የውሌ ማስከበሪያ ዋስትና፣ የቅዴመ ክፍያ
ዋስትና፣ የአቅራቢነት ዋስትና ሰነድች (ዯብዲቤዎች) ናቸው። እነዚህ የዋስትና ሰነድች
በአብዛኛው ባንኮች ሇዯንበኞች የሚያዘጋጁሊቸው ዯንበኞች ሇባንኮች በሚያቀርቡት የመያዣ
ንብረቶች መሰረት የመያዣ ውሌ ከተዋዋለ በኋሊ ነው። አንዲንዴ ጊዜ ግን የዋስትና ዯብዲቤ
እንዱጻፍሇት የጠየቀ የባንክ ዯንበኛን ባንኮቹ ተመጣጣኝ የሆነ ገንዘብ በዝግ ሂሳብ
እንዱያስቀምጡ በማዴረግ በምትኩ ግዳታቸውን ሇመወጣት መተማመኛ የሚሆኑ ሰነድችን
ይሰጣለ። ይህ አይነቱ ዋስትና የገንዘብ ዋስትና ይባሊሌ። በብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር
SIB/24/2004 መሰረት የገንዘብ ዋስትና ሰነዴ አንዴ ሰው አንዴን የተሇየና የተወሰነ ስራ ሇላሊ
ሰው ሇመስራት ግዳታ ከገባ ይኸው ሰው በውለ መሰረት የገባውን ግዳታ መፈጸም የሚችሌ
መሆኑን ሇማረጋገጥ ላሊው ሰው የሚያቀርበው ውሌ ነው።10

ባንኮችም የዋስትና ሰነዴን ሇዯንበኞች በመስጠት የሚያገኙት ገቢ በወሇዴ መሌክ ገንዘብን


መቀበሌንና የዋስትና ጊዜው ሲያሌቅ የሚመሇስ ገንዘብም በዋስትና ተጠቃሚው በኩሌ
እንዱከፈሌ አይጠበቅም። በመሆኑም የዋስትና ሰነዴ መጻፍ በተሇምድ የሚታወቀውን
የአበዲሪና ተበዲሪ የብዴር ግንኙነትን አይፈጥርም። ይሌቁንም ባንኮቹ ሇሚሰጡት የዋስትና
ሰነዴ የሚቀበለት ተመጣጣኝ የሆነ ኮሚሽን ብቻ ነው። ይህ ሁኔታ ታዱያ በተሇይ የዋስትና
ሰነዴ እንዯ ብዴር አገሌግልት የሚታይ አይዯሇም ሇሚለት ወገኖች እንዯ አንዴ መከራከሪያ
ሀሳብ ይነሳሌ። ምክንያቱም የባንክ የብዴር ግንኙነት የአበዲሪና የተበዲሪ ግንኙነትን
10
የብሔራዊ ባንክ የመዴን ዴርጅቶች ሉያዘጋጁዋቸው የሚችለዋቸው ዋስትና ሰነድች የትኞቹ እንዯሆኑ ሇመወሰን የወጣ መመሪያ፤
መመሪያ ቁጥር 24/2004፤ አንቀጽ (1)።
www.abyssinialaw.com
ሇመፍጠር አበዲሪው ሇተበዲሪው በገንዘብ የሆነ ብዴር የመስጠትንና ተበዲሪውም ይህንኑ
የብዴር ገንዘብ በአይነትም ሆነ በጥሬው የመመሇስ ግዳታን የሚጥሌ መሆኑ ግሌጽ
ነው።ይሁንና ግን የዋስትና ዯብዲቤ ሇዋስትና ተጠቃሚው ሲጻፍ ባንኮቹ የዋስትና ዯብዲቤ
እንዱጻፍሇት የጠየቀውን ዯንበኛቸው የገባውን ግዳታ እንዱፈጽም መተማመኛ ከመስጠት
ባሇፈ ሇዯንበኛቸው የሚሰጡት የብዴር ገንዘብ የሇም።

ላሊው መነሳት ያሇበት ጉዲይ ባንኮች በሚያዘጋጂዋቸው የዋስትና ዯብዲቤዎች ሊይ


የሚጠቀሱ የሰነደን ይዘቶች የተመሇከቱት ነጥቦቸ ናቸው። በተግባር በባንኮች የሚዘጋጁት
የዋስትና ሰነድች የተሇያዩ ቢሆኑም የሰነድቹ ይዘት ግን አንዲንዴ የህግ ክርክሮችን ሲያስነሱ
ይታያለ።የአንዲንዴ የዋስትና ዯብዲቤዎች ይዘቶች በተሇይም ዋስትና ሰጪውን ተቋም ሳይቀር
ባሇገንዘቡ የዋስትና ሰጪው እና ወራሾቹ በጋራም ሆነ በተናጠሌ በዯብዲቤው በተቀመጡት
ግዳታዎች መሰረት ራሳቸውን ህጋዊ ግዳታዎች ውስጥ ገብተዋሌ፤ የዋስትና ቦንደም
ሇተጠቀሰው የገንዘብ መጠን በቦንደ ውስጥ በሰፈሩት ህጋዊ ስምምነቶች እና ዴንጋጌዎች
መሰረት ሆኖ ይህንን ቦንዴ ምንም አይነት ቅዴመ ሁኔታ ሉቀርብበት የማይችሌ የሚያዯርጉ
ናቸው፤ ማንኛውም ዴርጊት ወይም ሳይፈጸም የቀረ ነገር በመኖሩ ሳቢያ ኪሳራ የሚዯርስ
መሆኑን ዋስትና የተሰጠው ባሇገንዘብ ከዯረሰበት ይህንኑ በዋስትና ጊዜው ውስጥ ሇዋሱ
ማሳወቅ አሇበት የሚለና የመሳሰለት ይገኙበታሌ። በመሰረቱ አንዲንድቹ ግዳታዎች በሌማዴ
የተጻፉ ከመሆናቸው ውጪ በተሇይ የዋሱን ወራሾች ሁለ ተጠያቂ የሚያዯርጉት የዋስትና
ግዳታዎች ባንኮችን በተመሇከተ ሉፈጸሙ የሚችለም ስሊሌሆኑ በአብዛኛው በሰነድቹ ይዘት
ሊይም ጥንቃቄን ማዴረግ ያስፈሌጋሌ። የዋስትና ዯብዲቤም በጊዜ ገዯብ የተወሰነ ግዳታ
ሲሆን ዯብዲቤውም በግሌጽ ዋስትና የተገባሇትን የገንዘብ መጠን ማመሌከት ይገባዋሌ።

እንዯማጠቃሇያም የዋስትና ውሌ ማሇት ሁሇት ሰዎች ባዯረጉት የባሇገንዘብነትና የባሇእዲነት


ግዳታ ግንኙነት ውስጥ ከእነዚህ ተዋዋዮች ውጪ የሆነ ላሊ ሶስተኛው ባሇእዲው እዲውን
በሙለ ወይም በከፊሌ ያሌተከፈሇ መሆኑ ከተረጋገጠ ወይም ግዳታውን በውለ
በተመሇከተው አኳኋን በአግባቡ ያሌተወጣ ከሆነ እኔ በባሇእዲው ስፍራና አቋም ሆኘ
እዲውን እከፍሊሇሁ ወይም ግዳታውን እወጣሇሁ ሲሌ ሇባሇገንዘቡ ማረጋገጫ የሚሰጥበት
በሕግ አግባብ ከተረጋገጠ ከበስተጀርባው ሇአፈጻጸሙ የህግ ጥበቃ የሚያገኝ ውሌ ነው
www.abyssinialaw.com
በማሇት የፌዯራሌ ሰበር ሰሚ ችልት ማብራሪያ ሰጥቷሌ።11 ይሁንና ግን የዋስትና ሰነድች
ከአገሌግልታቸው አንጻር በህጋችን ሊይ ግሌጽና ሰፊ ሽፋን የተሰጣቸው አይዯለም።
በተሇይም በንግዴ ህጉን ውስጥ እነዚህ ሰነድች እንዯ ብዴር አገሌግልት የሚቆጠሩ መሆንና
አሇመሆናቸውን በሚገሌጽ መሌኩ እንዱሁም የተሇያዩ አይነት የዋስትና ዯብዲቤዎችን
አገሌግልት እና በምን ሁኔታ ሉጻፉ እንዯሚችለ በሚገሌጽ መንገዴ የተቀመጠ ግሌጽ ዴንጋጌ
ያስፈሌገናሌ። በመሆኑም የንግዴ ህጉ የዋስትና ዯብዲቤዎችን የተመሇከተ ሰፊ የህግ ሽፋን
መስጠትና ማካተት ይጠበቅበታሌ። ከዚህም ጋር ተያይዞ የዋስትና ሰነድችን ሌዩ ባህሪያትና
በተግባር ያለትን የባንኮችን አሰራሮች በመፈተሽ ዝርዝር የህግ ዴንጋጌ ማስቀመጡ አስፈሊጊ
ነው።

(ይህ ጽሁፍ ጸሀፊው በቅርቡ ‘የኢትዮጵያ የባንክ እና የሚተሊሇፉ የንግዴ ሰነድች


ሕግ’’ በሚሌ ካሳተመው መጽሀፍ ክፍሌ በከፊሌ የተቀነጨበ ነው። በመጽሀፉ
ሊይከባንክና ከሚተሊሇፉ የንግዴ ሰነድች ጋር ተያይዞ አዲዱስ የህግ ጉዲዮችና የህግ
ትንታኔ የቀረበበት ነው። መጽሀፉን ማግኘት የሚፈሌግ ማንኛውም ሰው መጽሀፉን
ከጃፋር መጽሀፍት ማከፋፈያ(ሇገሀር) እና ኤዞፕ መጽሀፍት መዯብር ( ፒያሳ
ጊዮርጊስ አካባቢ) ማግኘት ይችሊሌ።

11
የፌዯራሌ ሰበር ሰሚ ችልት መዝገብ ቁጥር 47004።

You might also like