You are on page 1of 2

አርማ ኦሮሚያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.

ስልክ፡ 251-11-557-2121 ፋክስ ቁ. +251115572122 የመ.ሣ.ቁ፡ 10090 አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የቅድመ ክፍያ ዋስትና ውል


የዋስትና ውል ቁጥር፡ - ቢዲ/1/ቢኦኤዲ/0067/18 የዋስትና ውል ገንዘብ መጠን፡ ብር 268,000

እዚህ እንዲታወቅ የሚፈለገው ነገር አቶ ኃይለ ማርያም ፍቃዴ (ከዚህ በኋላ "ውል ተቀባይ" ተብሎ በሚጠራው) በአንድ ወገንና
ኦሮሚያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. ባሕር ዳር ቅርንጫፍ (ከዚህ በኋላ "ዋስትና ሰጭ" ተብሎ በሚጠራው) በሌላ ወገን ለሊቦ
ከምከም ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት (ከዚህ በኋላ "ቀጣሪው" ተብሎ ለሚጠራው) በአንድነትም ሆነ በተናጠል
የገንዘብ መጠኑ ብር 268,000 (ሁለት መቶ ስልሳ ስምንት ሺ ብር) እንደ አቅራቢና እንደ ዋስትና ሰጪ ክፍያውን ሊፈጽሙ ውል
መግባታቸውን ነው፡፡

ስለዚህ ተቋራጩ ለቀጣሪው የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ለሊቦ ከምከም ወረዳ ሊያቀርብ ታህሳስ 25/2011 ዓ.ም. የጽሑፍ ውል
የያዘ ሲሆን ለዚህም ሥራ ቀጣሪው ለውል ተቀባዩ ብር 268,000 (ሁለት መቶ ስልሳ ስምንት ሺ ብር) ለመክፈል የተስማማ
ሲሆን ክፍያውን የሚፈጽመው ግን ውል ተቀባዩ ተመሳሳይ የገንዘብ መጠን ያለው የቅድመ ክፍያ ዋስትና ውል ይህን የዋስትና
ውል ተቀባይነት እንዳያገኝ ከሚያደርጉ ሁኔታዎች በስተቀር ሁሉም ስምምነቶችና ሁኔታዎች አባሪ በሆኑበት ሁኔታ ሲያቀርብ
ብቻ ነው፡፡

ስለሆነም የዚህ ዋስትና ውል ተፈጻሚነት ከታህሳስ 25/2011 ዓ.ም. ጀምሮ ለ 30 ቀናት የጸና ይሆናል፡፡

ስለዚህ የቀደመው ግዴታ ሁኔታዎች በሙሉ የሚመለከቱት ውል ተቀባዩ ለተጠቀሰው የብር 268,000 (ሁለት መቶ ስልሳ ስምንት
ሺ ብር) ቅድመ ክፍያ ውል ደንቦች፣ ስምምነቶችና ሁኔታዎች በቅድመ ክፍያ ስምምነቱ መሠረት በአግባቡ በእውነተኛነትና በቅን
ልቦና ተገዥ እንዲሆን ማድረግ ሲሆን ውል ተቀባዩ ግዴታውን መወጣት ካልቻለ ግን ዋስትና ሰጭው ቀጣሪው በውሉ
የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን እስከሚሟላ ድረስ የሚጠይቀውን ገንዘብ የሚከፍል ይሆናል፡፡ ዋስትና ሰጭው ክፍያውን በውሉ
እስከተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ድረስ ሲፈጽም ውሉ ውድቅ የሚደረግ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ውሉ በጽናት የሚቆይ ይሆናል፡፡

ይህ የዋስትና ውል በዋስትና ሰጭው የተፈጸመው የቀጣሪውን መብት ሙሉ ለሙሉ ለማስጠበቅ ሲሆን የሚከተሉት ግልጽ
ሁኔታዎች አሉት፡-
ቅደመ ሁኔታዎች
1. ይህ የዋስትና ውል ዋና ቅጅ የውሉ ጊዜ ሲያበቃ ለዋስትና ሰጭው ይመለሳል፡፡ ዋስትና ሰጭው ውሉ ከሚያበቃበት ቀን
በፊትም ሆነ በውሉ ማብቂያ ጊዜ ውስጥ የይገባኛል ጥያቄ ከቀጣሪው ካልደረሰው በስተቀር ይህ ውል ለዋስትና ሰጭው
ቢመለስም ባይመለስም ውድቅ ይሆናል፡፡
2. ቀጣሪው ወይም የቀጣሪው እንደራሴም ሆነ ተወካይ ኪሣራ የሚያስከትል ድርጊት ወይም ስህተት ካገኙ ቀጣሪው
ወዲያውኑ ሙሉ መረጃ የያዘ የጽሑፍ መግለጫ ለዋስትና ሰጭው ዋና ጽ/ቤት ያቀርባል፡፡
3. የዚህ ውል ደንቦች የሚጣሱ ከሆነ ከውሉ የሚመነጩ የውል ተቀባዩን መብቶችና ንብረቶች ዋስትና ሰጭው ይቀዳጃል፡፡

በዚህ ውል መሠረት ከውል ተቀባዩ አዚህ የሚኖሩ


ኃይለማርያም ፍቃዴሁሉም
ነበበ የታገዱ ክፍያዎች፣ ኦሮሚያ
ገንዘቦችና ንብረቶች
ኢንሹራንስ በሙሉ
ኩባንያ አ.ማበዋስትና
.
0918353394
አቅራቢው ፈጻሚነት በሚያቀርበው ጥያቄ መሠረት ለቀጣሪው ይከፈላሉ፡፡ አርማ
ስለትርጉሙ
4. ትክክለኛነት ጠቅላላ ንግድ
ዋስትና ሰጭው እታች በተጠቀሱት ምክንያቶች ምክንያት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ባሕር ዳር ቅርንጫፍ
ለሚያጋጥሙ ክስተቶች ባለዕዳ
አይሆንም፡፡ እነርሱም፡ - ሁለት የማይነበቡ ፊርማዎች አሉበት
 ጦርነት፣ ወረራ፣ የባዕድ ጠላት ወረራ፣ ጥቃት፣ ጦርነት የሚመስሉ ድርጊቶች (ጦርነት ቢታወጅም
ባይታወጅም)፣ የእርስ በእርስ ጦርነት፤
 አመጽ፣ ሕዝባዊ ሽብር፣ ሕዝባዊ አመጽ፣ ወታደራዊ አመጽ፣ ሁከት፣ ተቃውሞ፣ አብዮት፣ ወታደራዊ ሽብር፣
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወይም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ መንስኤ የሚሆኑ የሽብር ተግባራት፤
 የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የጎርፍ አደጋ ወይም ሌላ የእግዚአብሔር ቁጣ ናቸው፡፡
5. ከዚህ የዋስትና ውል ልዩነቶች ከተከሰቱ ግራ ቀኝ ወገኖች በሚያቀርቡት የጽሑፍ መግለጫ መሠረት አንድ ገላጋይ
ልዩነታቸውን እንዲፈታው የሚሾሙ ሲሆን ይህ የማይሆን ከሆነ አንድ በግራ ቀኝ ወገኖች በጽሑፍ የሚሾም ገላጋይና
ሌላ ሁለተኛ ገላጋይ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ልዩነቱን ለመቅረፍ ይሞክራሉ፡፡ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን በገላጋዮች
የጽሑፍ ሹመት የሚሾም ሸምጋይ ዳኛ ልዩነቱን የሚቀርፍ ይሆናል፡፡ ሸምጋይ ዳኛው ከገላጋዮች ጋር በመሰየም ለተበደለ
አካል ያለአድልኦ የሚፈርድ ይሆናል፡፡

ለዚህም ምሥክርነት ውል ተቀባዩና ዋስትና ሰጭው ይህን የዋስትና ውል በታህሳስ 24/2011 ዓ.ም. ተፈራርመዋል፡፡

ውል ተቀባዩ ዋስትና ሰጭው


የማይነበብ ፊርማ የማይነበብ ፊርማ

ኃይለማርያም ፍቃዴ ነበበ ኦሮሚያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.


አርማ
0918353394 ባሕር ዳር ቅርንጫፍ
ጠቅላላ ንግድ

ባለ 5 ብር የቀረጥ
ቴምብር አለበት

ስለትርጉሙ ትክክለኛነት

You might also like