Professional Documents
Culture Documents
A&B Law Office
A&B Law Office
የሰ/መ/ቁ 228726
እንዳሻው አዳነ
ተሾመ ሽፈራው
መላኩ ካሳዬ
ነጻነት ተገኝ
ፍርድ
የሰበር አቤቱታው የቀረበው አመልካች ሰኔ 7/2014 ዓ.ም በተጻፈ አቤቱታ የአ/ብ/ክ/መ ጠቅላይ
ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 03-110565 በቀን 17/09/2014 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ
የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ይታረምልኝ በማለት ስለጠየቁ ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በጎንደር
ከመዝገቡ መረዳት እንደሚቻለው በስር ፍ/ቤት የአሁን ተጠሪ በቀን 07/01/2011 ዓ.ም ባቀረቡት
አቤቱታ ከአሁን አመልካች ጋር ህጋዊ ጋብቻ ፈጽመን ለ 2 ዓመታት ያህል እንዲሁም ከመጋባታችን
በፊት በወዳጅነት አብረን የኖርን ሲሆን በዚሁ ግኑኝነት ሁለት ልጆች ማለትም እዮብ አወቀ ዕድሜው 6
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ያፈራነው የጋራ ንብረት የለም፡፡ በመሆኑም በመካከላችን ያለው ጋብቻ በፍ/ቤት ውሳኔ እንዲፈርስ
አመልካች ባቀረቡት መልስ ጋብቻ የፈፀምነው መስከረም 8/2009 ዓ.ም ነው፤ ጋብቻው
እንዳይፈርስ እቃወማለሁ፤ ከወለድናቸው ልጆች ውስጥ ህፃን ሚካኤል አወቀ ሲወለድ ጀምሮ ማየት፣
መስማት፣ መናገር፣ መንቀሳቀስ የማይችል በመሆኑ ልጁን በብቸኝነት ማሳደግ አልችልም፡፡ ጋብቻ
ከመፈፀማችን በፊት ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በባልና በሚስትነት ለ 7 ዓመት አብረን ኖረናል፤ በዚህ ጊዜ
ውስጥ ሁለቱ ልጆች ተወልደዋል፡፡ በ08/01/2009 ዓ.ም የተደረገው ውል ፍላጎቴን መሰረት ያላደረገ
ነው፡፡ ከጋብቻ ውሉ በፊት እንደባልና ሚስት ባለ ግንኙነት 3 ዓመትና ከዚያ በላይ የቆዩ ከሆነ ያፈሯቸው
ንብረቶች የጋራ ይሆናሉ፡፡ በመሆኑም ከሳሽ በሆቴል ንግድ ሥራ ዘርፍ የተሰማራና እውቀት በር ሆቴል
የተባለ ድርጅት ያለው በመሆኑ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ሆቴሉ ያስገኘው ገቢ የጋራችን ነው፡፡ እንዲሁም
ሚስትነት አብረን መኖር ከጀመርንበትና ልጅ ከወለድን በኃላ የተገነባ በመሆኑ የጋራ ሃብታችን ነው
ቀኛችን በውሉ ውጤት ላይ ተወያይተን ሳይሆን የራሱን ሃሳብ እኔ በማላውቀው መንገድ ከሌላ ሰው
እንድፈርም አድርጎኛል፡፡ በመሆኑም ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 07/01/2009 ዓ.ም ድረስ እንደ ባልና
ሚስት አብረን ቆይተናል፤ በዚህ መልኩ የመኖር ውጤት ደግሞ አብረን እያለን የተፈራ ሃብት የጋራ
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ሺህ) እንዲከፍለኝ፤ እንዲሁም የጋራ ንብረት የሆነ ሚኒባስ መኪና ተሽጦ የተገኘው ገንዘብ ድርሻየን ብር
187,500.00 (መቶ ሰማንያ ሰባት ሺህ አምስት መቶ) እንዲከፍለኝ፤ የልጆች ቀለብም እንዲከፍል
እንደማይቻል በህጉ የተደነገገ በመሆኑ በምስክር ላስረዳ ብላ ማቅረቧ የህግ ድጋፍ የለውም፡፡ ውሉን
ወዳና ፈቅዳ ያደረገችው እንጂ የደረሰባት ተፅዕኖ የለም፤ ያቀረበችው ምክንያት ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1973
አንጻር ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ደረሰባት የሚያሰኝ አይደለም በማለት በንብረቱም ረገድ የተጠቀሱት
ክርክራቸውን አቅርበዋል፡፡
ጉዳዩ በዚህ መልኩ የቀረበለት የስር ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ አመልካችና ተጠሪ ውሉን
ወደውና ፈቅደው ግልጽ ስምምነት በማድረግ ስለንብረታቸው ተስማምተው እያሉ የአሁን አመልካች
የጋራ ንብረት በማለት የገቢ መጋራት ጥያቄ ማቅረባቸው ተገቢ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን የጋብቻ ውል
ካደረጉበት ቀን 08/01/2009 ዓ.ም ጀምሮ ያለ የሆቴሉ ገቢ የጋራ በመሆኑ ከግብር አስገቢው መ/ቤት
በተገለፀው የገቢ መጠን መሰረት ወጪው ተቀንሶ እኩል እንዲካፈሉ፤ በጋብቻ ውላቸው ላይ ግራቀኙ
በግላቸው የነበራቸው ንብረት የግላቸው ሆኖ እንዲቀጥል የተስማሙ ስለሆነ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ
እስከ 08/01/2009 ዓ.ም ላለው ጊዜ የአሁን አመልካች የጠየቀችውን ልታገኝ አይገባም፤ የልጆች ቀለብ
በዚህ ውሳኔ ላይ ይግባኝ የቀረበለት የማእከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በበኩሉ በስር
ይህንንም የአመልካች ምስክሮች እና የተጠሪ 1 ምስክር የሚያስረዱ ሲሆን ተጠሪ እራሱ የምስክርነት
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ግንኙነት ደስተኛ ባለመሆናቸው መሆኑን ገልጿል፤ ይህ ደግሞ የግራ ቀኙ ግንኙነት ተራ ከመሆን ባለፈ
እንደባልና ሚስት መሆኑን ነገር ግን የማህበረሰቡ ልምድና ባህል ወደሚያከብረው ጋብቻ ከፍ እንዲል
ያደረጉት መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ስለዚህ አመልካች ግንኙነታቸው እንደባልና ሚስት እንደነበር
አስረድታ እያለ በ2009 ዓ.ም የጋብቻ ውል በመፈፀማቸው ብቻ ቀድሞ የነበረውን በህግ ተቀባይነት
ያለው እንደባልና ሚስት ግንኙነት የልነበረ ሊያደርገው አይችልም በማለት የስር ፍርድ ቤት ያሳለፈውን
ውሳኔ ሽሯል፡፡ ይህን ተከትሎም ከ2003 እስከ 2009 ዓ.ም የነበራቸው ግንኙነት እንደ ባልና ሚስ ነው፤
በዚህ ጊዜ ውስጥም ሆነ ከጋብቻ በኃላ እስከ ፍቺ ድረስ ከሆቴሉ የተገኘው ገቢ የጋራ ነው፤ የመኖሪያ
ቤቱም በግንኙነታቸው ጊዜ የተጀመረና መሰረቱ የወጣ እንዲሁም ጋብቻ ከፈፀሙ በኃላ የማጠናቀቂያ
ስራዎች የተሰሩለት በመሆኑ ቤትና ቦታው የጋራ ነው፤ የልጅ ቀለቡም ተሻሽሎ በተለይ 2ኛው ልጅ
ያለበትን የጤንነት ችግር ግምት ውስጥ በማስገባት ለሁለቱ ልጆች በየወሩ 6000.00 ሊከፍል ይገባል
በማለት ወስኗል፡፡
የአሁን ተጠሪ በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኝት ለአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ
ፍ/ቤት የይግባኝ ቅሬታ አቅርበዋል፡፡ ችሎቱም ጉዳዩን መርምሮ ግራቀኙ ወደውና ተዋደው የጋብቻ
ህብረተሰቡ በሚያውቀውና በሚረዳው መልኩ እንደባልና ሚስት አብረው ይኖሩ እንደነበር በምስክሮች
ስለተነገረ ከ2003-2009 እንደባልና ሚስት ኖረዋል በ8/01/2009 ዓ.ም የተፈፀመው የጋብቻ ውሉም
አይደለም በማለት የጋብቻ ውሉን ወደጎን በመተው የሰው ምስክርን መሰረት በማድረግ ከጋብቻ
ውጪ እንደባልና ሚስት ለኖሩበት ጊዜም ሆነ ከጋብቻው በኃላ እስከፍቺ ድረስ ከሆቴሉ የተገነኘውን ገቢ
እንዲካፈሉ መወሰኑ፤ እንዲሁም መኖሪያ ቤቱም የጋራ ሀብት ነው በማለት መወሰኑ ከማስረጃ ምዘና
አልተገኘም በማለት ውሳኔውን ሽሯል፡፡ የጋብቻ ውሉ ከጋብቻ በፊት የተፈራ ንብረት ከጋብቻ በፊት
ለነበረው ግለሰብ ይሆናል ስለሚል የአሁን አመልካች ከ2003 – 2009 ዓ.ም ድረስ ያለውን የሆቴሉን
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
የአሁን አመልካች በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኝት የሰበር አቤቱታ ለክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር
ሰሚ ችሎት ያቀረቡ ሲሆን ችሎቱ ጉዳዩን መርምሮ ከቀረቡት ማስረጃዎች ይዘት አኳያ ሲታይ ከጋብቻ
በፊት እንደ ህጉ አነጋገር ጥበቃ የሚደረግለት እንደ ባልና ሚስት አብሮ የመኖር ግንኙነት ነበራቸው
ለማለት የሚቻል ሆኖ አላገኘነውም፤ በዚህ ጊዜ ተገኙ የተባሉት ንብረቶች በግንኙነቱ ውስጥ የተፈሩ
ናቸው የሚያሰኝ ካለመሆኑም በላይ ግንኙነታቸው እንደባልና ሚስት ግንኙነት ነበር የሚባል ቢሆን
እንኳን ጋብቻቸውን ሲፈጽሙ ከጋብቻ በፊት የነበሩትን አከራካሪ ንብረቶች የተጠሪ የግል ንብረት
እንዲሆኑ እስከተስማሙ ድረስ የተጠሪ የግል ንብረት ከመሆን የሚድኑም አይሆንም በማለት ጠቅላይ
የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ነው፡፡ አመልካች ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ጽፈው ባቀረቡት
ማመልከቻ ግራቀኝ የጋብቻ ውል የፈፀምነው መስከረም 8 / 2009 ዓ.ም ነው፤ ከዚህ ጊዜ በፊት
ከ2003 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 2009 ዓ/ም ድረስ እንደ ባልና ሚስት አብረን ኖረናል፤ አንድ የጋብቻ ውል
ውጤት የሚኖረው ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑ እየታወቀ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት እና ሰበር ሰሚ
ችሎት ከጋብቻ ውሉ በፊት የነበረን እንደ ባልና ሚስት የመኖር ጉዳይ የጋብቻ ውል እያለ የሰው ማስረጃ
በመስማት ይህንኑ መሰረት በማድረግ ውሳኔ መስጠት በህጉ አግባብ አይደለም በማለት የሰጡት
ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ስለተፈፀመበት ነው፡፡ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ከ2003 እስከ 2009
ዓ.ም ድረስ ያለውን ጊዜ ከ2009 ዓ.ም በኃላ ካለው ጊዜና ከውሉ ይዘት ጋር በማምታታት እንዲሁም
በህግ ከተሰጠው ስልጣን አልፎ የፍሬ ነገር ጉዳይ ላይ በስር ፍርድ ቤቶች ሳይረጋገጥ የራሱን ድምዳሜ
በመውሰድ የሰጠው ውሳኔ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው፡፡ አመልካችና ተጠሪ በ2009 ዓ.ም
አደረግነው የተባለው የጋብቻ ውል ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ የነበረውን እንደ ባልና ሚስት አብሮ የመኖር
ውጤት የማይቀይር ሆኖ እያለ በውሉ ንብረቱ የግል ነው በሚል ተስማምተሻል በማለት አመልካች
ውሳኔ መሰጠቱ ስህተት ያለበት በመሆኑ ሊሻር ይገባል፡፡ በአጠቃላይ ውሳኔው ተሸሮ የማዕከላዊ ጎንደር
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሆቴሉን ገቢ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2011 ዓ.ም ድረስ ያለውን እንዲሁም
አቅርበዋል፡፡
ቅሬታው ተመርምሮ አመልካች ከተጠሪ ጋር ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ እንደ ባልና ሚስት ከጋብቻ
መፈጸማቸው ተጠቅሶ የአመልካች ክርክር ውድቅ የተደረገበትን አግባብነት ለማጣራት በሚል ጉዳዩ
ተጠሪ ባቀረቡት መልስ የስር ክርክራቸውን አጠናክረው አመልካችና ተጠሪ እንደ ባልና ሚስት
አብረን አልኖርንም፤ ልጆች የወለድነው ከጋብቻ ውጪ በነበረን ግንኙነት ነው፤ አመልካች የጋብቻ
ውሉን የፈረመችው ቤተሰቦቿ በተገኙበት ወዳ እና ፈቅዳ ነው፤ ግልጽ የሆነ ውል ባለ ጊዜ በሌላ ማስረጃ
ተጠሪ በአንድ ጣሪያ ስር ሆነን ያፈራነው ንብረት የለም፤ አለ ቢባል እንኳን ንበረቱ ለጋራ ጥቅም
ተፈጻሚ አይሆንም፤ ይህንን ጉዳይ በተመለከተም የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/መ/ቁ 41896 አስገዳጅ ውሳኔ
ሰጥቷል፡፡ የክልሉ ሰበር ችሎት በህግ ጥበቃ የሚደረግለት እንደባልና ሚስት አብሮ መኖርን በተመለከተ
ፍሬ ነገሩን መመርመሩ የህግ ጥሰት ነው ሊባል አይገባም፤ ቀድመን እንደባልና ሚስት ብንኖር ኑሮ
ደፍኖ መወሰኑ በአግባቡ ነው፡፡ መኖሪያ ቤቱን በተመለከተም የአመልካች ንብረቷ ያልተቀላቀለበት
መሆኑ ተረጋግጦ የተወሰነ በመሆኑ ቅሬታው ውድቅ ይደረግልኝ በማለት ተከራክረዋል፡፡ አመልካችም
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ከፍ ሲል በአጭሩ የገለጽነው የጉዳይ አመጣጥ ሲሆን የግራ ቀኙን ክርክር ቅሬታ ከቀረበበት
ውሳኔ እና ከተገቢው የህግ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ የተፈፀመ የህግ ስህተት መኖር አለመኖሩን
መርምረናል፡፡
ግራቀኙ መስከረም 8/2009 ዓ.ም የጋብቻ ውል የተባለ ሰነድ መፈራረማቸውን አልተካካዱም፡፡ በሌላ
በኩል አመልካች ከዚህ ጊዜ በፊት ከ2003 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 2009 ዓ/ም ድረስ እንደ ባልና ሚስት
አብረን ኖረናል፤ ይህ ግንኙነት በህጉ በንብረታችን ረገድ ውጤት አለው በማለት ይከራከራሉ፡፡ ተጠሪ
በበኩላቸው እንደ ባልና ሚስት አብረን አልኖርንም፤ ልጆች የወለድነው ከጋብቻ ውጪ በነበረን
ግንኙነት ነው፤ አመልካች እና ተጠሪ በአንድ ጣሪያ ስር ሆነን ያፈራነው ንብረት የለም ብለዋል፡፡ የስር
ፍርድ ቤቶች ከፍሲል እንደተገለፀው ውሉን እና ከውሉ በፊት ነበር የተባለውን ግንኙነትና ውጤቱን
1ኛ - ግራቀኙ ጋብቻ ከመፈፀማቸው በፊት ያለው ግንኙነት እንደባልና ሚስት አብሮ የመኖር ግንኙነት
ነው ወይስ አይደለም የሚለው ነጥብ አግባብነትና በህጉ ተቀባይነት ባለው ማስረጃ በስር ፍርድ ቤቶች
እንዲረጋገጥ ተደርጓል ወይስ አልተደረገም? ከዚህ ጋር በተያያዘ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ
ችሎት በዚህ ረገድ የቀረበውን የፍሬ ነገር ክርክርና ማስረጃ ሳይመለከት ማለፉ በአግባቡ ነው? የክልሉ
ሰበር ሰሚ ችሎትስ ማስረጃውን መዝኛለሁ በማለት ከውሉ በፊት እንደ ባልና ሚስት አብሮ የመኖር
ግንኙነት አልነበረም በማለት የሰጠው ውሳኔ የሰበር ችሎቱን ስልጣን መሰረት ያደረገ ነው ወይስ
አይደለም?
ድረስ የግራቀኙ ግንኙነት እንደባልና ሚስት ነበር የሚባል ቢሆን እንኳን በንብረቱ ረገድ ውጤት
አይኖረውም የሚባልበት የህግ ምክንያት አለ? ወይስ የለም? የሚሉት ናቸው፡፡ በዚሁ ቅደም ተከተል
እንደሚከተለው መርምረናል፡፡
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ቀዳሚው ጭብጥ ግራቀኙ ውል አደረጉ ከመባሉ በፊት የነበራቸው ግንኙነት እንደባልና ሚስት
የሚመለከት ነው፡፡ በፌዴራሉ የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀጽ 106 ስር እንደተመለከተው
ጋብቻ ሳይፈፀም እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖሩን የግንኙነቱ ሁኔታ መኖሩን በማረጋገጥ ማስረዳት
እንደሚቻል፤ አንድ ወንድና አንድ ሴት ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደባልና ሚስት ይኖራሉ የሚባለው
የተጋቡ ሰዎችን ሁኔታ ሲያሳዩና ቤተዘመዶቻቸውና ማህበረሰቡ እንደተጋቡ ሰዎች የሚኖሩ ናቸው
ብለው ሲገምቷቸው መሆኑን፤ ይህን ሁኔታ አንደኛው ወገን ለማስረዳት የቻለ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ
እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ናቸው ሲል የህግ ግምት እንደሚወስድ፤ እንዲሁም ይህ ግምት
እንደሚቻል ይደነግጋል፡፡
ከጋብቻ ሥርዓት ወይም ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ ከመኖር ውጪ በአንድ
እንደማይኖራቸው በቤተሰብ ህጉ አንቀጽ 107 ይደነግጋል፡፡ የአማራ ክልል የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር
ከዚህ አንጻር አመልካች ከ2003 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 2009 ዓ/ም ድረስ እንደ ባልና ሚስት
አብረን ኖረናል፤ ይህ ግንኙነት በህጉ በንብረታችን ረገድ ውጤት አለው በማለት የሚከራከሩ በመሆኑ
የተጋቡ ሰዎችን ሁኔታ ያሳዩ እንደነበርና የግራቀኙ ቤተዘመዶችና ማህበረሰቡ እንደተጋቡ ሰዎች የሚኖሩ
ናቸው ብለው የሚገምቷቸው መሆኑን ማስረዳት እንደሚኖርባቸው መገንዘብ ይቻላል፡፡ በዚህ መልኩ
በቂ ማስረጃ አቅርበው ፍርድ ቤቱ እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ናቸው ሲል ግምት የሚወስድ
ከሆነ ተጠሪ ማስረጃ አቅርበው እንደ ክርክራቸው አብረው ያልኖሩ መሆኑን፤ ልጆች የተወለዱትም
ከጋብቻ ውጪ በነበረን ግንኙነት መሆኑን፤ አመልካች እና ተጠሪ በአንድ ጣሪያ ስር ሆነው ያፈሩት
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ይሁንና የስር ፍርድ ቤቶች በዚህ የህግ አግባብ ለጉዳዩ አግባብነትናተቀባይነት ያለው ማስረጃ
ሰምተው መወሰን ሲገባቸው በዋናነት የግራቀኙን ምስክርነት መሰረት አድርገው የወረዳው ፍርድ ቤት
እንደ ባልና ሚስት የመኖር ግንኙነቱ የለም ማለቱ፤ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ያንኑ ማስረጃ መዝኖ
አመልካች ግንኙነታቸው እንደባልና ሚስት እንደነበር አስረድታለች በማለት መወሰኑ፤ የክልሉ ጠቅላይ
ፍርድ ቤት በዚህ የፍሬ ነገር ክርክር ምንም ሳይል ማለፉ፤ እንዲሁም የክልሉ ሰበር ችሎት መሰረታዊ
የህግ ስህተት ከማረም ስልጣኑ ውጪ ማስረጃዎችን መዘንኩ በማለት ከቀረቡት ማስረጃዎች ይዘት
አኳያ ከጋብቻ በፊት እንደ ባልና ሚስት አብሮ የመኖር ግንኙነት ነበራቸው ለማለት የሚቻል ሆኖ
ሁለተኛው ጭብጥ ከጋብቻ ውጪ እንደ ባልና ሚስት ኖረዋል የሚባሉ ሰዎች ንብረታቸውን
በተመለከተ እንደባልና ሚስት የነበሩበት ጊዜ በንብረቱ ረገድ ውጤት አይኖረውም የሚባልበት የህግ
ባልና ሚስት አብሮ መኖር ግንኙነት የቤተሰብ መሰረት ሲሆን ህብረተሰቡም ሆነ ፍርድ ቤትን ጨምሮ
ጋብቻ ሲመሰርቱ፣ በጋብቻው ዘመን እና በፍቺ ወቅት እኩል መብት አላቸው፡፡ እንደባልና ሚስት
አንቀጽ 34(1) እና 35 እንዲሁም ተያያዥ ድንጋጌዎች የሚነሳ ነው፡፡ የህገ መንግስቱም ሆነ የቤተሰብ
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የውል ግንኙነት በመኖሩ ምክንያት ከፍሲል የጠቀስነውን የእኩልነት
መርህ የጣሰ ህገወጥ ስምምነት እንዳይሆን በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን ባለው አካል
መረጋገጥ ያለበት ስለመሆኑ ህጉ ጥንቃቄ ማድረጉን ከዚህ ህጉ ይዘት መገንዘብ ይቻላል፡፡ እነዚህ
ከፍሲል የጠቀስናቸው የቤተሰብ ህግ ድንጋጌዎች ጋብቻ ውስጥ ስላሉ ባልና ሚስት የሚደነግጉ ሲሆን
እንደባልና ሚስት ግንኙነት ውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ ተፈፃሚነት ያላቸው ስለመሆኑ በህጉ በግልፅ
አስገዳጅ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ከውሳኔዎቹ መገንዘብ እንደሚቻለው እንደ ባልናሚስት ያለው ግንኙነት ከ
3 ዓመት በላይ ከዘለቀ በንብረት ረገድ ያለው ውጤት ከጋብቻ የሚለይ ካለመሆኑም በላይ ግንኙነቱ
ሲቋረጥ እንደ ባልና ሚስት የኖሩ ሰዎች የጋራ ንብረትን ማጣራት የሚደረገው የጋብቻ ንብረትን
አንቀጽ 133 እና ከአንቀጽ 112 – 120 ይመለከቷል) ፤ የንብረቱ ማጣራት የሚደረገው ደግሞ
መሰረት በመሆኑ፤ ጋብቻ ሳይኖር እንደ ባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ አንድ ወንድ እና አንዲ ሴት
እንደ ባልና ሚስት አብረው በሚኖሩ ሰዎች ላይም በተመሳሳይ ተፈፃሚ የሚሆኑ መሆኑ (የቤተሰብ ህጉ
አንቀጽ 103 አና 114 ይመለከቷል) በህጉ ተቀባይነት ያገኘ ነው፡፡ ስለሆነም ጋብቻ ሳይፈፅሙ እንደ ባልና
እንዲኖረው ማድረግ ሁለቱ ግንኙነቶች (ጋብቻ እና ከጋብቻ ውጪ አብሮ መኖር) በንብረት ረገድ
ያላቸው ውጤት የተለያየ ስላለመሆኑ ይልቁንም በአንድ አይነት መልኩ እንዲታዩ በህጉ የተቀመጠውን
አስገዳጅ ድንጋጌ የሚፃረር እና በህግ አውጪው ያልታሰበውን ልዩነት መፍጠር ይሆናል፡፡ ስምምነቱ
አንዱ ወገን በሌላው ላይ የሚያሳድረው ጫና የእኩልነት መርህን የሚጥስ መሆን አለመሆኑን በፍርድ
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ከዚህ አንጻር ከጋብቻ ውጪ እንደ ባልና ሚስት ኖረዋል የሚባሉ ሰዎች በግንኙነታቸው ውስጥ
በቀር በተቃራኒው አስቀድሞ እንደባልና ሚስት የነበሩበት ጊዜ በንብረቱ ረገድ ውጤት አይኖረውም
የሚባልበት የህግ ምክንያት እንደሌለ ከፍሲል ከተጠቀሱት የህጉ እና የሰበር ችሎቱ ውሳኔዎች መገንዘብ
ይቻላል፡፡
በመሆኑም በተያዘው ጉዳይ የግራ ቀኙ ግንኙነት እንደባልና ሚስት ነበር የሚባል ቢሆን እንኳን
ንብረቶች የተጠሪ የግል ንብረት እንዲሆኑ እስከተስማሙ ድረስ የተጠሪ የግል ንብረት ከመሆን የሚድኑ
ውጪ አብረው መኖራቸው በተገቢው ማስረጃ ከተረጋገጠ በንብረት ክርክሩ ህጋዊ ውጤት የሚኖረው
በመሆኑ የስር ፍርድ ቤት ግንኙነቱ ስለመኖሩ ለማስረዳት በህጉ በተመለከተው አግባብ ተገቢ
ማስረጃዎች እንዲቀርቡ በማድረግ አጣርቶ ውሳኔ መስጠት ሲገባ ከውል በፊት የነበረው ግንኙነት
ውጤት እንደማይኖረው በመውሰድ እንዲሁም ተደረገ የተባለው ውል አስቀድሞ በህጉ አግባብ የጋራ
ቤቶች የተሰጠው ውሳኔ ከፍሲል የተጠቀሱትን የህግ ድንጋጌዎችና የሰበር ውሳኔዎች ያልተከተለ በመሆኑ
ውሳኔው በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ አንቀጽ 2(4)(ሸ) እና አንቀጽ 10(1)(ሐ) መሰረት በዚህ
ውሳኔ
1. የጎንደር ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በመ/ቁ 0134134 በቀነ 07/04/2012 ዓ.ም፤ የማዕከላዊ
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
3. የጎንደር ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት የተዘጋውን መዝገብ በማንቀሳቀስ ግራቀኙ ከ2003 – 2009
የመኖር ግንኙነት አለ የሚባል ከሆነ በዚህ ግንኙነት ጊዜ የተፈራ ንብረትን በተመለከተ ግራቀኙ
ማ/አ
የልዩነት ሃሳብ
እንደሚከተለዉ አስፍሬያለሁ፡፡
ከክርክሩ ሂደት መገንዘብ እንደሚቻለዉ ግራ ቀኝ በመካከላቸዉ መስከረም 08 ቀን 2009 ዓ.ም ባደረጉት የጋብቻ
ዉል በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 ቀጠና 02 የሚገኘዉ መለያ ስሙ ዕዉቀት በር ሆቴል ተብሎ የሚጠራዉ ባለ አራት
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ፎቅ ህንፃ እንዲሁም በጎንደር ከተማ ቀበሌ 20 አዘዞ አሜሪካን ሠፈር እየተባለ ከሚጠራዉ ሠፈር ባለአንድ ፎቅ
ቤቶች የተረጋገጠ ከመሆኑም በላይ አመልካችም ክዳ አትከራከርም፡፡ ለሁሉም ግልጽ እንደሚሆነዉ ዉል ተዋዋይ
ወገኖች በእራሳቸዉ ጉዳይ እራሳቸዉ ለመወሰን ያላቸዉን ነፃነት ተጠቅመዉ በሚያደርጉት ስምምነት
የሚያቋቁሙት መብትና ግዴታ ሲሆን፤ ስምምነቱን ሲያደርጉም የዉሉ ዓይነት፣ ይዘት እና ዉጤቱ ምን ሊሆን
እንደሚችል አዉቀዉ እና በአግባቡ ተረድተዉ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ተዋዋዮች በዚህ መልኩ ወደዉ እና ፈቅደዉ
በሚያደርጉት ስምምነት በህግ ጥበቃ የተደረገላቸዉን መብት ሊተዉ እንደሚችሉም እሙን ነዉ፡፡ በመርህ
ደረጃ ተዋዋዮች በእራሳቸዉ ጉዳይ ራሳቸዉ ለመወሰን ያላቸዉን መብት ተጠቅመዉ በፈለጉት ጉዳይ ላይ
በፈለጉት ዓይነት ሁኔታ (ፎርም) መስማማት የሚችሉ ቢሆንም አንድ ዉል ህጋዊ ዉጤት ያስከትል ዘንድ
ማሟላት ያለበትን ቅድመ ሁኔታ (መስፈርት) ህግ አዉጪዉ በግልጽ ያስቀመጣቸዉን አስገዳጅ ድንጋጌዎችን
ተከትሎ ሊደረግ ይገባል፡፡ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ፍትሐብሔር ህግ አንቀጽ 1678 አንድ ዉል ህጋዊ ዉጤት
ያስከትል ዘንድ እንዲያሟላ የሚጠበቅበትን ቅድመ ሁኔታዎች እንደ አጠቃላይ የሚደነግግ ሲሆን፣ በልዩ ሁኔታም
የዉሉን ጉዳይ መሠረት ባደረገ መልኩ ከግምት ዉስጥ ሊገቡ ይገባል የሚላቸዉን ቅድመ ሁኔታዎች ህግ
አዉጪዉ በሌሎች ህጎች ይደነግጋል፡፡ ከዚህም ዉስጥ ፎርም አንዱ ነዉ፡፡ በዚህም መሠረት ተዋዋይ ወገኖች
ፎርምን ጨምሮ በህግ የተመለከቱትን ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎችን መሠረት በማድረግ ወደዉ እና ፈቅደዉ
ያደረጉት ዉል የህግ ኃይል ተሰጥቶት ግራ ቀኝን የማስገደድ ዉጤት ያለዉ ሲሆን (በፍትሐብሔር ህጋችን አንቀጽ
1731/1 አና 2 ድንጋጌዎች ይመለከቷል)፣ በሌላ በኩል ዉሉ በህግ የተመለከተዉን አስገዳጅ ሁኔታ ያላማሏ ከሆነ
ምንም እንኳ የግራ ቀኝን ስምምነት መሠረት ያደረገ ቢሆንም ዉሉ ህጋዊ ዉጤት አያስከትልም፡፡
ስለሆነም አንድ ዉል አስገዳጅ ዉጤት ያስከትል ዘንድ እንዲያሟላ የሚጠበቅበት በህግ የተደነገገ ልዩ ሁኔታ ካለ
ተዋዋይ ወገኖች ተገቢዉን የህግ ድንጋጌ ከግምት ዉስጥ ባስገባ መልኩ ዉላቸዉን ሊያደርጉ ይገባል፡፡ ከዉሉ
አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ክርክር የቀረበ እንደሆነም፣ ክርክሩ የቀረበለት ፍርድ ቤት ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ ዉል
ተገቢዉን የህግ ድንጋጌ ተከትሎ የተደረገ መሆን አለመሆኑን በጥንቃቄ በመመርመር ዳኝነት የመስጠት ኃላፊነት
እንዳለበት የሚታወቅ ነዉ፡፡ ይህን በማድረግ ሂደት በአንድ በኩል ዉሉ የተወሰነ ፎርም ተከትሎ እንዲደረግ በህግ
የታዘዘ ሲሆን ይህንኑ ከግምት ዉስጥ በማስገባት፣ በሌላ በኩል ዉሉ የተወሰነ ፎርም ተከትሎ እንዲደረግ በህግ
በግልጽ የተመለከተ ድንጋጌ ከሌለ ግራ ቀኝ ወደዉ እና ፈቅደዉ ላደረጉት ስምምነት ዉጤት በመስጠት የተዋዋይ
ወገኖችን የመዋዋል ነፃነት ያከበረ ዉሳኔ ሊሰጥ ይገባል፡፡ ፍርድ ቤቶች ተዋዋዮች በዉላቸዉ ያመለከቱት
ስምምነት ግልጽ ከሆነ ግልጽ የሆነዉን ስምምነት መሠረት በማድረግ፣ ግልጽ ካልሆነ ተቀባይነት ያገኙትን የዉል
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
አተረጓጎም መርሆዎች መሠረት ያደረገ ትርጉም በመስጠት ለተዋዋይ ወገኖች ስምምነት ዋጋ በመስጠት ዉሉ
ተፈፃሚ እንዲሆን ከማድረግ ዉጪ በህግ ወይም በዉል ያልተመለከተ አዲስ መብትና ግዴታ ከመጨመር
መቆጠብ አለባቸዉ የሚለዉ መርህ በዉል ህግ ተቀባይነት ካገኙት አጠቃላይ መርሆዎች ዉስጥ አንዱ ሲሆን፤
ፍርድ ቤቶች ዉል መተርጎምን ሰበብ በማድረግ ለተዋዋይ ወገኖች ዉል መፍጠር እንደማይችሉ፣ ዉለታዎች
ግልጽ በሆኑ ጊዜ የተዋዋይ ወገኖች ሃሳብ ምን እንደነበረ መተርጎም እንደማይችሉ እንዲሁም በህግ በግልጽ
የተመለከተ ካልሆነ በቀር ርትዕን ምክንያት በማድረግ ዉልን ማሻሻልም ሆነ መለወጥ እንደማይችሉ
በፍትሐብሔር ሕጋችን አንቀጽ 1714(2)፣ 1733 እና 1763 ላይ የተመለከቱት ድንጋጌዎችም ለዚህ ማሳያዎች
ናቸዉ፡፡
ከዚህ አንፃር የተያዘዉን ጉዳይ ስንመለከት አብላጫዉ ድምጽ ዉሉ ህጋዊ ዉጤት አያስከትልም ከሚል ድምዳሜ
ላይ የደረሰዉ በፍርድ ቤት ቀርቦ አለመመዝገቡን በመጥቀስ ነዉ፡፡ በሌላ በኩል ዉሉ የተደረገዉ ግራ ቀኝ እንደ
ባልና ሚስት አብሮ ሲኖሩ በነበረበት ወቅት ስለመሆኑ ማስረጃን መዝኖ ፍሬ ነገርን የማረጋገጥ ስልጣን
በተሰጣቸዉ የክልሉ ፍርድ ቤቶች የተረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2009 ዓ.ም ድረስ
ባለዉ ጊዜ ከተጠሪ ጋር የነበራቸዉ ግንኙነት እንደ ባልና ሚስት አብሮ የመኖር ግንኙነት መሆኑን አመልካች
ባቀረበችዉ የሰበር አቤቱታ ክዳ አትከራከርም፡፡ አንድ ወንድ እና አንድ ሴት እንደ ባልና ሚስት አብሮ በሚኖሩበት
ጊዜ የሚያደርጓቸዉ ዉሎች በፍርድ ቤት ወይም በህግ ስልጣን በተሰጠዉ አካል ሊመዘገቡ ይገባል የሚል ድንጋጌ
የለም፡፡ አብላጫዉ ድምጽ በዋቢነት የጠቀሰዉ ድንጋጌ የአማራ ክልል የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 84 ላይ
የሚያደርጓቸዉ ዉሎች ዉል ለማዋዋል ስልጣን የተሰጠዉ የፍትሕ አካላት ካላጸደቃቸዉ በስተቀር ዉጤት
እንደሌለዉ የሚያሳይ ነዉ፡፡ ድንጋጌዉ የተለያዩ ዓላማዎች እንዳሉት የሚታመን ሲሆን አንዱ ዓላማዉ ባልና
ሚስት በጋብቻ በሚኖሩበት ጊዜ አንደኛዉ ተጋቢ በሌላኛዉ ተጋቢ በሚደርስበት ተጽዕኖ ምክንያት ባላመነበት
ጉዳይ ስምምነት ሊያደርግ የሚችልበት አጋጣሚ በመኖሩ ስምምነቱ ስልጣን ባለዉ አካል ዘንድ ቀርቦ ሳይረጋገጥ
ዉጤት እንዳይኖረዉ በማድረግ የተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት እንዳይሻክር ጥበቃ ማድረግ ስለመሆኑ መገንዘብ
ይቻላል፡፡ በእርግጥም ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት በመሆኑም በተጋቢዎች መካከል የሚደረግ ስምምነት
የሚገዛበት ልዩ ድንጋጌ የሚያስፈልገዉ በመሆኑ ከላይ የተመለከተዉ ድንጋጌ አቀራረጽም ይህን ሁሉ ታሳቢ
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
እንደባልና ሚስት አብሮ ሲኖሩ በነበረበት ወቅት እንጂ ጋብቻ ከፈጸሙ በኋላ ባለመሆኑ ከላይ የተመለከተዉ
የክልሉ የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 84 ድንጋጌ ተፈፃሚነት የለዉም፡፡ በመሠረቱ በአብላጫዉ ድምጽ ዉሳኔ
በተገለጸዉ መልኩ እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር የቤተሰብ መሠረት ነዉ ለማለት የሚቻል ባለመሆኑ
የቤተሰብ ብሎም የማህበረሰብ ተቋም ከሆነዉ ጋብቻ ጋር እኩል የህግ ጥበቃ አይደረግለትም፡፡ ለዚህም
ይመስላል አንድ ወንድ እና አንድ ሴት አንደባልና ሚስት አብሮ ለመኖር ወስነዉ ስለሚገናኙበት፣ አብረዉ
በሚኖርበት ወቅት በመካከላቸዉ ሊኖር ስለሚገባዉ ግላዊ ግንኙነት ብሎም እንደባልና ሚስት አብሮ የመኖር
ግንኙነቱ የሚቋረጥበት ሥርዓት የሚመራበትን ሁኔታ አስመልክቶ የፌዴራልም ሆነ የአማራ ክልል የቤተሰብ
ህጉ ጥበቃ አያደርግም (በተለይም የክልሉ የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 118/1/ይመለከቷል)፡፡ በሌላ በኩል እንደባልና
ሚስት አብሮ የመኖሩ ሁኔታ ሁለት ዐብይ ዉጤቶችን ያስከትላል፡፡ የመጀመሪያዉ የሦስተኛ ወገን መብትና
ጥቅምን የሚመለከት ሲሆን፣ ይሄዉም በግንኙነቱ ወቅት ከአብራካቸዉ ልጆች ሊወለዱ ይችላሉ፤ እንዲሁም
በግንኙነቱ ምክንያት ከሦስተኛ ወገን የሚመጣ የገንዘብ ወይም የንብረት ዕዳ ሊኖር ይችላል፡፡ ሁለተኛዉ
በግንኙነቱ ወቅት በየግላቸዉ ወይም በጋራ በሚያደርጉት ጥረት ንብረት ሊያፈሩ ይችላሉ፡፡ ስለሆነም እነዚህን
ጉዳዮች በተመለከተ ብቻ የህግ ጥበቃ የሚያስፈልግ ሲሆን፣ በዚህም መሠረት አንድ ወንድና አንዲት ሴት
እንደባልና ሚስት አብሮ በሚኖሩበት ጊዜ ለጋራ ኑሮአቸዉ ወይም ከግንኙነት የተወለዱ ልጆቻቸዉን መሠረታዊ
ፍላጎቶች ለማሟላት ሲባል የተገቡ እዳዎች ሲኖሩ ሁለቱም በአንድነትና በነጠላ ለዕዳዉ ኃላፊዎች እንደሚሆኑ፣
ከሦስት ዓመት ላላነሰ ጊዜ አብረዉ ከኖሩ በግንኙነቱ ዉስጥ እያሉ ያፈሯቸዉ ንብረቶች የጋራ ሀብቶቻቸዉ
እንደሚሆኑ የፌዴራል እና የክልሉ የቤተሰብ ህግ ይደነግጋል (የክልሉ የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 113 እና 115
ይመለከቷል)፡፡ ባልና ሚስትን አስመልክቶ በክልሉ የቤተሰብ ህግ የተመለከቱ ድንጋጌዎች እንደባልና ሚስት
አብሮ ለሚኖሩ ሰዎች ተፈፃሚነት እንዳላቸዉ ተለይተዉ የተገለጹትም የባልና ሚስት የጋራ ዕዳን፣ የባልና ሚስት
የጋራ ንብረት ዉጤት አስመልክቶ እንዲሁም ተወላጅነት የሚረጋገጥበትን ሥርዓት አስመልክቶ በቤተሰብ ህጉ
ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡ ከዚህ ዉጪ ባልና ሚስት አብረዉ በሚኖሩበት ጊዜ የሚያደርጓቸዉ ዉሎች
በህግ ስልጣን በተሰጠዉ አካል ፊት ሊረጋገጥ እንደሚገባ በክልሉ የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 84 ላይ የተመለከተዉ
ድንጋጌ እንደ ባልና ሚስት አብሮ የሚኖሩ ሰዎች በሚያደርጓቸዉ ዉሎች ላይ ተፈፃሚነት እንዳለዉ ህጉ
አይደነግግም፡፡ ከዚህ ሁሉ መገንዘብ የሚቻለዉ እንደ ባልና ሚስት አብሮ የሚኖሩ ሰዎች ግንኙነቱ ባለበት
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም
A&B Law Office
ወቅት የሚያደርጓቸዉ ዉሎች ህጋዊ ዉጤት ይኖራቸዉ ዘንድ ዉሉ ስልጣን ባለዉ አካል እንዲመዘገብ በህግ
አብላጫዉ ድምጽ ለዉሳኔዉ መሠረት ያደረገዉ በኢፌዲሪ ህገ መንግስት ዕዉቅና የተሰጠዉን የወንዶችና
የሴቶችን የእኩልነት መብት ነዉ፡፡ ይሁንና ማንም ሰዉ በመብቱ የመጠቀም እና ያለመጠቀም ነፃነት ያለዉ
በመሆኑ ይህን ነፃነቱን ተጠቅሞ በሚያደርገዉ ስምምነት መብቱን የተወ ወይም ለሌላ ወገን አሳልፎ የሰጠ
እንደሆነ ይህ ነፃነቱ ሊከበርለት እንደሚገባ መገንዘቡ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የዉሉን ህጋዊ ዉጤት የሚወስን
ፈቅደዉ ባደረጉት ዉል ንብረቶቻቸዉን አስመልክቶ ያደረጉት ስምምነት ህጋዊ ዉጤት አያስከትልም ማለት በቂ
እና አሳማኝ ምክንያት ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ እንደባልና ሚስት አብረዉ የሚኖሩ ሰዎች
ግንኙነቱ ባለበት ወቅት የሚያደርጓቸዉ ዉሎች የእኩልነት መብትን የሚጋፋ ነዉ ብሎ ካመነ የዉል ግንኙነቱ
የሚገዛበትን ልዩ ድንጋጌ በማካተት ለግንኙነቱ ጥበቃ ማድረግ ያለበት ህግ አዉጪዉ ሲሆን፣ የክልሉ ህግ
በአጠቃላይ አመልካች እና ተጠሪ እንደባልና ሚስት አብሮ በሚኖሩበት ወቅት ወደዉ እና ፈቅደዉ ስለ
ንብረቶቻቸዉ ያደረጉት ግልጽ ዉል መኖሩ ባልተካደበት፣ እንደባልና ሚስት አብሮ የሚኖሩ ሰዎች
የሚያደርጓቸዉ ዉሎች ስልጣን ባለዉ አካል ሊረጋገጡ እንደሚገባ በፌዴራልም ሆነ በአማራ ክልል የቤተሰብ
ህግ ግልጽ ድንጋጌ በሌለበት ሁኔታ ዉሉ ህጋዊ ዉጤት አያስከትልም ሊባል የሚችልበት ህጋዊ ምክንያት የለም፡፡
በዚህ ምክንያት ዉሉን ዋጋ ማሳጣት ፍርድ ቤቶች ለሰዎች የመዋዋል ነፃነት ዋጋ በመስጠት ዉሎችን ማስፈጸም
አለባቸዉ የሚለዉንም አጠቃላይ መርህ የሚጋፋ ነዉ የሚል ሃሳብ አለኝ፡፡ በመሆኑም በዚህ ችሎት
በሰ/መ/ቁጥር 185895 ላይ የተሰጠዉ እና አብላጫዉ ድምጽ የጠቀሰዉ ዉሳኔም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች
አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26(2) መሠረት ቢያንስ ሰባት ዳኞች ለተሰየሙበት ሰበር ችሎት ቀርቦ
ማ/አ
ማ ስታወሻ፡- ይህ የሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለጥናትና ምርምር ሥራ ወይም ለግንዛቤ እንጂ
ለፍርድ አፈጻጸም ዓላማ አያገለግልም