Professional Documents
Culture Documents
43414
43414
ሐጐስ ወልዱ
ሂሩት መለሰ
አልማው ወሌ
ዓሊ መሐመድ
ፍርድ
ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው የአሁኑ
ተጠሪ በአሁኗ አመልካች ላይ ሕዳር 26 ቀን 1998 ዓ.ም በመሠረተው ክስ መነሻ ነው፡፡ የክሱ ይዘትም፡-
በቀድሞው ወረዳ 21 ቀበሌ 19 ውስጥ የሚገኘውን ቁጥሩ 255 የሆነውን ቤት የአመልካች እናት ወ/ሮ
ስልሳ ብር) ለመክፈል በመኖሪያ ቤት አገልግሎት ሊጠቀሙበት ከተጠሪ ተከራይተው ሲኖሩ ከቆዩ በኋላ
ተከራይዋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የካቲት 08 ቀን 1996 ዓ.ም በተጻፈ የማመልከቻ
በስማቸው እንዲዛወር ለኤንጂው አቤቱታ አቅርበው ውዝፍ የኪራይ እዳውን በመክፈል በስማቸው
1
1998 ዓ.ም ድረስ ያለው ውዝፍ የቤት ኪራይ ብር 13‚920.00 ፣ ወለድ በብር 6635.00 ተጨማሪ
እሴት ታክስ እስከ ታህሳስ 23 ቀን 1995 እስከ ህዳር 30 ቀን 1998 ዓ.ም ድረስ የለው ብር 846
በድምሩ ብር 21‚401.24 (ሃያ አንድ ሺህ አራት መቶ አንድ ብር ከሃያ አራት ሳንቲም) እንዲሁም
ቤቱን እስከሚያስረክቡ ድረስ ያለውን ኪራይ እንዲከፍሉና ቤቱን እንዲያስረክቡ ይወሰንለት ዘንድ
ዳኝነት መጠየቁን የሚያሳይ ነው፡፡ የአሁኗ አመልካችም በተከሳሽነት ቀርበው በሰጡት መከላከያ መልስ
ተጠሪ ክስ ለመመስረት መብት ወይም ጥቅም የሌለው መሆኑን ጉዳዩ በይርጋ የታገደ መሆኑን
የሚያሳዩ ነጥቦችን በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት አንስተው የተከራከሩ ሲሆን በፍሬ ነገር ረገድም
የኪራይ ገንዘቡ ከመቼ እስከመቼ እንደሆነ ያልተጠቀሰ እና የዳኝነት ጥያቄው ስሌትም መሠረቱ
በሰኔ 01 ቀን 1974 ዓ.ም ተደረገ የተባለው ውልም በኃይል የተደረገና ፎርሟሊቲውን ያልጠበቀ
ስለአደረገ ይህንኑ ይዞታ በደጅ ለማቆየት ያህል ውል እንድፈጽም የጠየቅሁት ማመልከቻ ሀሳብን ብቻ
የሚገልጽ ፁሑፍ እንጂ እንደውል ሊቆጠር የሚችል አይደለም በማለት ዘርዝረው ክሱ ውድቅ ሊሆን
ይገባል ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤትም በአልካች በኩል
የቀረቡትን መከራከሪያ ነጥቦችን ውድቅ አድርጐ በተጠሪ እና በሟች አምሳለ ማንያህላል መካከል ሰኔ
01 ቀን 1974 ዓ.ም በቀድሞው ወረዳ 21 ቀበሌ 19 የቤት ቁጥር 255 የተደረውን የኪራይ ውል
ዓ.ም እስከ ታህሳስ 30 ቀን 1998 ዓ.ም ድረስ ያለውን የሰባት ዓመት ከሦስት ወር ውዝፍ የቤት ኪራይ
1998 ዓ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ 9(ዘጠኝ ከመቶ) እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ
2
አቀርበው ግራ ቀኙ ከተከራከሩ በኋላ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ፀንቷል፡፡ የአሁኑ የሰበር አቤቱታ
የአመልካች ጠበቃ የካቲት 04 ቀን 2001 ዓ.ም በፃፉት ሦስት ገጽ የሰበር አቤቱታ በበታች
ፍርድ በቶች ውሳኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል የሚሉበትን ምክንያት ዘርዝረው
አቅርበዋል፡፡ ይዘቱም ባጭሩ ተጠሪ የቤት ኪራይ ውል ያለው ከአመልካች እናት ጋር በመሆኑ
በሚጠይቀው ሀብት ወይም ጥቅም ላይ መብት ያለው ስለመሆኑ ሳይረጋገጥ ክስ መመስረት አይችልም
ከሃያ ሶስት አመታት በኋላ የቀረበው ክስም በይርጋ ቀሪ ነው በሚል የቀረበው መቃወሚያ መታለፍ
ያላግባብ ነው የእናቴን እዳን እንድከፍል የተወሰነው ባግባቡ አይደለም በቤቱ ላይ የተሻለ መብት ያለኝ
አመልካች እንጂ ተጠሪ አይደለም በማለት የበታች ፍርድ ቤቶች ውሳኔ እንዲሻርላቸው ዳኝነት
መታለፍ ባግባቡ ነው ወይስ አይደለም? የሚሉትን ነጥቦችን ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ ለሰበር ችሎት
እንዲቀርብ ተደርጐ የተጠሪ ነገረ ፈጅ ታህሳስ 21 ቀን 2002 ዓ.ም በፃፉት ሁለት ገጽ ማመልከቻ
በአመልካች አውራሽና በተጠሪ መካከል የተደረገውን የኪራይ ውልና በአመልካች በጽፎና በፊርማ
ተረጋግጦ የቀረበውን ደብዳቤ መሠረት በማድረግ የሠጠው ውሳኔ ሕጋዊ ስለሆነ ሊፀና ይገባል በማለት
መልሳቸውን ሠጥተዋል፡፡
የጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለፀው ሲሆን ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን
ክርክር ለሰበር አቤቱታ መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩ
3
አመልካች አከራካሪውን ቤት በተመለከተ የአውራሻቸው የግል ንብረት ስለመሆኑ ገልፀው
የሚከራከሩ ቢሆንም አከራካሪው ቤት የግል ንብረት ስለመሆኑ ያቀረቡት የይዞታ ማረጋገጫ ደብተርም
ሆነ ካርታ የሌለ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ እንዲሁም የስራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር መስከረም 11 ቀን
1983 ዓ.ም የፃፈው ደብዳቤም የሚያመለክተው በተክለሃይማኖት አውራጃ ቀበሌ 47 በውርስ ላገኙት
ቀበሌ 19 ከነማ ጽ/ቤ መፃፉን እንጂ ለዚህ ክርክር መነሻ የሆነው ቤት በተመለከተ የአመልካች አውራሽ
በአከራካሪው ቤት ከተጠሪ የተሻለ መብት ያለኝ እኔ መሆኔ ተጠሪ ክስ ለመመስረት በቤቱ ላይ ጥቅም
ወይም መብት የለውም በማለት አመልካች ያቀረቡት ክርክር በስር ፍርድ ቤት መታለፉ ባግባቡ ሆኖ
አግኝተናል፡፡
ውል የለም በማለት ነው፡፡ ተጠሪ ደግሞ ለዚህ የአመልካች ክርክር የሚሠጠው መልስ ከአመልካች ጋር
በቤቱ ላይ ሲኖሩ ከቆዩ በኋላ እናታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ አመልካች የካቲት 08 ቀን 1996
ዓ.ም ለተጠሪ በፃፉት ደብዳቤ ውዝፍ እዳውን ከፍለው የቤቱ የኪራይ መብት በራሳቸው ስም
ደብዳቤው የተፃፈው ተጠሪ አመልካች ቤቱን እንዲለቁ ስለአስፈራራቸውና የቤቱን ይዞታ በእጃቸው
በአልካችና በተጠሪ መካከል ከወ/ሮ አምሳለ ማንያህላል ሞት በኋላ የተደረገ የኪራይ ውል አለመኖሩን
ነው፡፡ የኪራይ ውልን ለማቋቋም በሕጉ የተለየ ፎርማሊቲ መከተል የማያስፈልግ ቢሆንም በተያዘው
ጉዳይ ግን አመልካች የቤቱ ኪራይ በራሳቸው ስም እንዲዞርላቸው ጥያቄ አቅርበው ተጠሪ ይህንኑ
ተቀብሎ አመልካች የኪራይ ውሉን እንዲገቡ ሲጠይቁ ፈቃደኛ አለመሆናቸው የተረጋገጠ በመሆኑ
4
በጥያቄአቸው መሠረት የኪራይ ውል ገብተዋል ለማለት የሚያስችል አይደለም፡፡ በመሆኑም ተጠሪ
በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2968 መሠረት ላልተወሰነ ጊዜ የኪራይ ውሉን አድርጓል ሊባል የሚችለው ከሟች
እናት ከወ/ሮ አምሳለ ማንያህላል ጋር ነው ከሚባል በስተቀር በአመልካችና በተጠሪ መካከል በሕጉ
አግባብ የተቋቋመ የኪራይ ውል የለም፡፡ ስለሆነም የስር ፍርድ ቤት በአመልካችና በተጠሪ መካከል
ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም አመልካች ቤቱን ያላግባብ
ምክንያት የለም፡፡ በዚህ ጊዜ ተጠሪ ሊያገኝ ይችል የነበረው ጥቅምም በይርጋ የሚታገድ አለመሆኑን
ተገንዝበናል፡፡ በመሆኑነም በዚህ ረገድ አመልካች ያቀረቡት ክርክር ተቀባይነት ያለው ሆኖ አልተገኘም፡፡
በዚህ መሠረት አመልካች ሊጠየቁ የሚገባው ቤቱን ራሳቸው ይዘው ከተጠቀሙበት ከየካቲት 08 ቀን
1996 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 30 ቀን 1998 ዓ.ም ድረስ ያለውን በቤቱ ላይ በኪራይ መልክ
የእናታቸው መብትና ግዴታ በሕጉ አግባብ የወረሱ መሆኑ ሲረጋገጥ እና በዚሁ የወራሽነት መብታቸው
የክርክሩ ተካፋይ መሆናቸው ሲረጋገጥ ብቻ ነው፡፡ በዚህ መዝገብ ግን ይኸው ሥርዓት ተሟልቶ
አመልካች የተከሰሱ ስለመሆኑ የሚያሳይ ነገር የለም፡፡ ሲጠቃለልም በአመልካችና በተጠሪ መካከል
ከሕጉ አግባብ የተቋቋመ የኪራይ ውል በሌለበት ሁኔታ ክርክሩ የኪራይ ግንኙነትን መሠረት አድርጐ
በሥር ፍርድ ቤት መታየቱ ያላግባብ ሲሆን አመልካች ያላግባብ የተጠሪን ቤት ይዘው ለተጠቀሙበት
ውሳኔ
5
1. በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመ/ቁጥር 61819 ጥር 14 ቀን 1999 ዓ.ም ተሰጥቶ
በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ/ቁጥር 53107 ሕዳር 05 ቀን 2001 ዓ.ም የፀናው ውሣኔ
3. አመልካች ለተጠሪ የሚከፍሉት የገንዘብ መጠን ከየካቱት 08 ቀን 1996 ዓ.ም ጀምሮ እስከ
ታህሳስ 30 ቀን 1998 ዓ.ም ድረስ ያለውን በወር 160.00 (አንድ መቶ ስልሳ ብር) እየታሰበ
የሚመጣውን የሃያ ሦስት ወራት ጥቅም ብር 3680 (ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ሰማንያ ብር)
በዚሁ ገንዘብ መጠን ከታህሳስ 06 ቀን 1998 ዓ.ም ጀምሮ የሚታሰብ ህጋዊ ወለድ 9 (ዘጠኝ
የኪራይ እዳ ተጠሪ ተገቢውን ወራሽ በሕጉ አግባብ ከስሶ ከመጠየቅ ይህ ውሳኔ አያግደውም
ብለናል፡፡
5. በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪና ኪሳራ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል፡፡
ፀ/መ