You are on page 1of 32

በAዲሱ የAማራ ክልል የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ሕግ ላይ የተካተቱ ዋና ዋና

ለውጦች Eና የሚታዩ ችግሮች


በሪሁን Aዱኛ ምሕረቱ
1. መግቢያ
መሬት በተፈጥሮ የተገኘ የማይንቀሳቀስ ንብረት ከመሆኑም በላይ ሌሎች የሚንቀሳቀሱና የማይንቀሳቀሱ
ንብረቶችን ለማፍራት Aስፈላጊ የሆነ መተኪያ የሌለዉ ሀብት ነው፡፡ መሬት ከንብረት መብት Aኳያ
ለሀገራችን Aርሶ Aደሮች የኑሮ ዋስትና ነው። ማህበራዊና Iኮኖሚያዊ ጠቀሜታን በማረጋገጥ ረገድ
ለመንግስት ቁልፍ የፖለቲካል Iኮኖሚው መገለጫ የሆነ ሀብት ነው። ይህን ትልቅ ዋጋ ያለው
የሕዝብና የመንግስት ሀብት በAግባቡ ለማስተዳደርና Aጠቃቀሙን ለማሳለጥ የሚያገለግሉ በፌደራል
መንግስት Eና በክልሎች የሕግ ማEቀፎች ወጥተው Eየተሰራባቸው ይገኛል።

ከግንቦት 21 ቀን 1998 ዓ/ም ጀምሮ በAማራ ክልል ሥራ ላይ የነበረው የገጠር መሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም ሕግ Aዋጅ ቁጥር 133/1998 Eና ማስፈጸሚያ ደንቡ ቁጥር 51/1999 መሆኑ ይታወቃል፡፡
ሆኖም Eነዚህ ሕጎች ተግባራዊ ሲደረጉ በርካታ ችግሮች በማጋጠማቸው1 ሕጎቹን ማሻሻል በማስፈለጉ
የተሻሻለው የAማራ ክልል የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም Aዋጅ ቁጥር 252/2009 ታውጇል፡፡
የዚህ Aዋጅ ማስፈጸሚያ ደንብ ቁጥር 159/2010ም Eንዲሁ ጸድቆ ወጥቷል፡፡


በሪሁን Aዱኛ ምሕረቱ (LL.B, LL.M)፣ ቀደም ሲል የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ Eና በAማራ ክልል የፍትሕ
ባለሙያዎች ማሰልጠኛና የሕግ ምርምር Iኒስቲትዩት Aሰልጣኝ፣ ቀጥሎም የAማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
ዳኛ በመሆን የሠራ ሲሆን በAሁኑ ጊዜ ጠበቃ Eና የሕግ Aማካሪ በመሆን Eየሠራ ይገኛል፡፡
1
ፍትሕ ለማግኘት በሚደረግ ጥረት ውስጥ በAማራ ክልል ፍርድ ቤቶች ከሚቀርቡ ጉዳዮች ውስጥ Eጅግ
የሚበዛው የመሬት ክርክር ነው፡፡ ክርክሮቹ ከወረዳ ፍርድ ቤት ጀምሮ Eስከ ክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ
ችሎት Eንዲሁም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስ የሚደርሱ Eና በቅርቡ ደግሞ Eስከ
ፌደሬሽን ምክር ቤት የሚዘልቁና መቋጫ የሌላቸው ሲሆኑ ይታያሉ። መቋጫ የለሽ ለሆነ የመሬት ክርክር ወይም
የተዛባ ፍርድ መንስኤዎች ምንድን ናቸው? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ በተግባር ከሚታዩ ችግሮች በመነሳት
ፀሐፊው “ለገጠር መሬት ክርክር መበራከት መንስኤዎችና ዋና ዋና መገለጫዎች በAማራ ክልል” በሚል ርEስ
በAማራ ክልል ምክር ቤት በመጋቢት ወር 2009 ዓ/ም በተካሄደው ክልል Aቀፍ የገጠር መሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም ኮንፈረንስ ላይ ሁለት መሰረታዊ ምክንያቶችን በመተንተን Aቅርቦ ነበር። ከቀረቡት ምክንያቶች
Aንደኛው በመሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ሕጎች ላይ የሚታዩ ችግሮች የሚል ነበር፡፡ ይኸውም፡-
1. የክልሎች ሕግ የማውጣት ስልጣን በዜጎች ላይ ያመጣው የመብት መለያየት፡- በውርስ፣ በኪራይ፣ በስጦታ
መብት Eና ይዞታ መብት የሚታጣባቸው ሁኔታዎች ላይ ከክልል ክልል ሰፊ ልዩነት መኖሩ፤
2. የገጠር መሬት ውርስ ቅደም ተከተል ፍትሐዊ Aለመሆኑ፤
3. የገጠር መሬት ክርክር በይርጋ የሚታገድ መሆን Aለመሆኑ በAግባቡ ሳይደነገግ መታለፉ፤
4. የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ሕጎች በየወቅቱ ለባለይዞታዎች የተለያየ መብት በመስጠታቸው
ቋሚና የተረጋጋ መብት Aለመኖሩ፤
5. ወጥ የሆነ የመሬት ግብይት ፎርማሊቲ Aለመደንገጉ፤
6. የከራይ ዘመን መርዘም Eና የኪራይ ተመን ገደብ Aለመኖር፤
7. የመሬት ስጦታ ሊሻር የሚችል መሆን Aለመሆኑ Aለመደነገጉ፤ Eና
8. የገጠር መሬት Aጠቃቀም ፖሊሲና ሕግ Aለመኖሩ የሚሉ ነበሩ፡፡
ሁለተኛው ምክንያት በገጠር መሬት ሕጎች Aፈጻጸም ላይ የሚታዩ ችግሮች ሲሆን ይህም በየደረጃው ባሉ የመሬት
Aስተዳደርና Aጠቃቀም መስሪያ ቤቶች፣ በተከራካሪ ወገኖች በራሳቸው Eንዲሁም በፍርድ ቤቶች ላይ የሚታዩ
ችገሮችን የሚመለከት ነው፡፡
1
Aዲሱ Aዋጅ ከቀድሞው Aዋጅ በEጥፍ ቁጥር ድንጋጌዎችን የያዘ፣ በጣም ሰፊ መግቢያ Eና በርካታ
የትርጓሜ ንUስ Aንቀጾችን ያካተተ Eንዲሁም Aዳዲስ ሀሳቦችን ያቀፈ ሆኖ ታውጇል፡፡ ለAዋጁ መሻሻል
ምክንያት የሆኑ Aስር መሰረታዊ ነጥቦችም መግቢያው ላይ ተካተዋል፡፡ ይኸውም፡-

1. Aርሶ Aደሮችም ሆነ ከፊል Aርብቶ Aደሮች በያዙት የገጠር መሬት ላይ ያላቸውን የተጠቃሚነት
መብት ይበልጥ ማስፋት ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ፤

2. በክልሉ ዉስጥ ተበታትኖ የሚኖረዉን Aርሶ Aደርና ከፊል Aርብቶ Aደር ወደ ተወሰኑ ማEከላት
በማሰባሰብ ሁለንተናዊ ለሆነ Eድገት ተጠቃሚ የሚያደርግ ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፤

3. ሀገራችን የAርብቶ Aደሮችን በመሬት የመጠቀም መብት Aስመልክቶ በAህጉራዊና በዓለም


Aቀፋዊ ደረጃ የፈረመቻቸውን ስምምነቶች በክልሉ ዉስጥ ተግባራዊ ማድረግ Aስፈላጊ ሆኖ
በመገኘቱ፤2

4. የግል ባለሀብቱ Eና Aግባብ ያላቸዉ ድርጅቶች መሬትን በAግባቡ በማልማት፣ በመጠቀምና


በመጠበቅ ረገድ የሚኖራቸዉን ተሳትፎ ለማጠናከር Eና ጥረታቸዉ ከክልሉ መንግሥት
የልማት ዓላማዎች ጋር Aንዲቀናጅ ለማድረግ በማስፈለጉ፤

5. በክልሉ ዉስጥ የገጠር መሬት ምዝገባ መረጃን በጥራት ለማደራጀትና ለባለይዞታዎች በAግባቡ
ለማሰራጨት የሚያስችል ምቹ Eና ደረጃዉን የጠበቀ የሕግ ማEቀፍ በመፍጠር ሕጋዊ የመሬት
ባለይዞታዎች የይዞታ ዋስትናቸዉ ተጠናክሮ ማየት በማስፈለጉ፤

6. ሕገ-ወጥ የወል መሬት ወረራን በመከላከልና በግልም ሆነ በወል ይዞታቸዉ ላይም ቢሆን
ያልተፈቀዱ ግንባታዎችን በመቆጣጠር የገጠር መሬትን ዉጤታማና ዘላቂ Aጠቃቀም ማረጋገጥ
Aስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤

7. ከመሬት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ግጭቶችን ለመቀነስ የክልሉ መንግስት Eና ባለይዞታዎች


Aስተማማኝ የመረጃ Aገልግሎት የሚያገኙበትን ዘመናዊ የመሬት መረጃ ስርዓት መዘርጋት Eና
ተግባራዊ ማድረግ በማስፈለጉ፤

8. በተለያዩ የክልሉ የስነ ምህዳር ቀጠናዎች ላይ ተመስርቶ ፈርጀ-ብዙ የገጠር መሬት Aጠቃቀም
Eቅድ በማውጣትና በመተግበር የተፈጥሮ ሀብታችን በዘላቂነት በመጠበቅ Eና በማልማት
ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ Aንዲቻል Aስተዳደሩንና Aጠቃቀሙን በሕግ መደንገግ
Aስፈላጊ በመሆኑ፤

9. ሴቶች፣ ሕጻናት፣ Aካል ጉዳተኞች፣ Aቅመ ደካሞች Eና Aረጋዊያን የገጠር መሬት ባለይዞታ
የመሆን መብታቸው Eንዲጠናከር በዝርዝር መደንገግ በማስፈለጉ፤

2
See UN Interenational Convention to Combat Desertfication in Countries Experiencing Serious Drought and/or
Desertification, Particularily in Africa, enacted in 1994, in which Ethiopia is Signatory.
2
10. በክልሉ ዉስጥ Aንዳንድ የገጠር ቀበሌዎች ወደ Aቅራቢያዉ የከተማ Aስተዳደር ክልል
በሚጠቃለሉበት ወይም የገጠር መሬት ለሕዝብ Aገልግሎት Aንዲዉል በሚፈለግበት ጊዜ
ለሕዝብ ጥቅም ሲባል ከይዞታቸዉ Eንዲነሱ ሲደረግ ተገቢና ተመጣጣኝ ካሳ በቅድሚያ
የሚያገኙበትንና በዘላቂነት የሚቋቋሙበትን Aሠራር በሕግ መደንገግ Aስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ
የሚሉ ናቸው፡፡

የዚህ ጽሑፍ Aላማም የተሻሻለውን ገጠር መሬት Aስተዳዳርና Aጠቃቀም Aዋጅ ከማስፈጸሚያ ደንቡ
ጋር በማገናዘብ Aጭር ዳሰሳ ማድረግ Eና ሕጎቹ ላይ የሚታዩ መልካም ጎኖች Eና ችግሮችን ለመጠቆም
ነው፡፡ በመሆኑም ፅሑፉ በሀገራችን ብሎም በክልላችን Eስካሁን ያሳለፍነውን የመሬት ስሪት ታሪካዊ
ዳራ በመዳሰስ ይጀምራል፡፡ Aሁን ባለው ሁኔታ በክልላችን ውስጥ የገጠር መሬትን በማግኘት፣
በመጠቀም፣ በማስተላለፍ Eና መብቱ ቀሪ በሚሆንባው ሁኔታዎች ላይ ከቀድሞው ሕግ Aንጻር
የተጨመሩ ወይም የተሻሻሉ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ፡፡ Eንዲሁም Aዋጁ ያካተታቸውን መልካም ነገሮች Eና
ችግሮችን ይተነትናል፡፡ ለችግሮቹም የመፍትሔ Aቅጣጫ ይጠቁማል፡፡
2. የገጠር መሬት ስሪት በIትዮጵያ፡- ከታሪካዊ ዳራው Eስከ Aሁን Aጭር Eይታ
የመሬት ስሪት (Land Tenure) ማለት Aርሶ Aደሮችና ሌሎች የመሬት ተጠቃሚዎች መሬት
የሚይዙበትን ሁኔታ Eና የAጠቃቀሙን ስርዓት የሚገልጽ ጽንሰ ሀሳብ ነው፡፡3 ይህ ትርጉም የመሬት
ስሪት መሬት ከማግኘት መብት የሰፋና የመብቱን ደረጃም ሆነ መብቱን ተግባራዊ ለማድረግ
የሚያስፈልጉ ተቋማትን የሚያካትት መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ በAንድ ሀገር ያለው የመሬት ስሪት
ግንኙነት በመሬት ባለይዞታ መሆንንና በመሬት መጠቀምን በተመለከተ Aንድ ሰው ከሌላው ሰው ጋር
Eንዲሁም ግለሰቦች ከመንግስት ጋር ያላቸውን ማህበራዊ፣ Iኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ግንኙነት
የሚገለፅበት ጽንሰ ሀሳብ ነው፡፡

በAንድ ሀገር ያለው የመሬት ስሪት ዓይነት የመሬት ባለይዞታዎችን መብት በማስፋትም ሆነ በማጥበብ
ረገድ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ በተለይ Eንደ Iትዮጵያ ባሉ ለንብረት መብት ዋናው መሰረት መሬት
በሆነባቸው Eና Aብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል በባህላዊ የግብርና ስራ በሚተዳደርባቸው ሀገሮች የመሬት
ስሪቱ የመሬት ባለይዞታዎችን የንብረት መብትም ሆነ የEያንዳንዱን ባለይዞታ ማህበራዊና Iኮኖሚያዊ
ደረጃ በመወሰን ረገድ ከፍተኛ AስተዋፅO ይኖረዋል፡፡ የቅደመ 1967 ዓ/ም Iትዮጵያ የገጠር መሬት
ስሪትም የራሱ የሆነ ባህሪይ የነበረውና በውስጡ በርካታ ስሪቶችን ያካተተ ነበር፡፡4 ከ17ኛው ክፍለ ዘመን
ጀምሮ የሀገራችን የገጠር መሬት ስሪት የጋራ ይዞታ፣ የግል ይዞታና የመንግስት ይዞታ በሚል ሊከፈል
ይችላል፡፡5 በEነዚህ ስሪቶች ስር ሊካተቱ የሚችሉ የመሬት ይዞታ Aይነቶች ደግሞ በርካታ ነበሩ፡፡

3
Kenneth H. Parsons, Land Tenure, the University of Wisconsin press, Wisconsin (1963) p. 44; see also W.D.
Ambaye, Land Rights and Expropriation in Ethiopia, Springer Interenational Publishing Switzerland 2015, p. 36
4
Aberra Jembere, Legal History of Ethiopia 1434 - 1974: Some Aspects of Substantive and Procedural Law, Lieden
Arika-studie centrum (1998) p.123
5
Ibid
3
ለምሳሌ፡- የቤተክርስቲያን ይዞታ፣ የጉልት ይዞታ Eና የርስት ጉልት ይዞታን የሚያካትቱ ናቸው፡፡
በሰሜን Iትዮጵያ የነበረው የመሬት ስሪት ለብቻው ተለይቶ ሲታይ ደግሞ የግል ይዞታ፣
የቤተክርስቲያን ይዞታ Eና የመንግስት ይዞታ ተብሎ ይከፈል ነበር፡፡6

የርስት ይዞታ የሚባለው በሰሜኑና በመካከለኛው Iትዮጵያ በከፊል የነበረ የመሬት ስሪት ሲሆን የዚህ
ስሪት መለያ ባህሪው ዘራቸውን ወደ ላይ ቆጥረው የስሪቱ ቆርቋሪ ሰው የጋራ ተወላጆች መሆናቸውን
የሚያረጋግጡ ሰዎች የጋራ ይዞታ መሆኑ ነው፡፡7 የጉልት ይዞታ የሚባለው ለተፈፀመ ውለታ
ባለመሬቶች ለመንግስት የሚከፍሉትን ግብር ተቀብሎ ለግል ለመጠቀም Eንዲቻል የሚሰጥ መብት
ሲሆን ባለፈው ለተፈፀመና ወደ ፊትም ሊፈፀም የሚችል የAንድን Aካባቢ የማስተዳደርና ፀጥታ
የማስከበር ተግባር ለሚፈጽም ሰው በግል የሚሰጥ የመሬት ይዞታ መብት በመሆኑ ለልጅ የሚተላለፍ
Aይደለም፡፡8 የርስት ጉልት ይዞታ ደግሞ በርስት ስሪት Aካባቢዎች ከርስት ይዞታ በተጨማሪ በግል
ይዞታ Aካባቢ ደግሞ ከግል ባለቤትነት በተጨማሪ ከመሬቱ የሚሰበሰበውን ግብር ሰብስቦ ለግል
ለመጠቀም ከመንግስት የሚሰጥ መብት ሲሆን መብቱ የሚሰጠውም ለመንግስት ለተሰጠ Aገልግሎት
ነው፡፡ በመሬቱ ላይ ካሉ የርስተኝነት ይዞታ ወይም ከግል ባለቤትነት በተደራቢነት የሚሰጥ በመሆኑም
መልሶ ሊወሰድ የማይችልና ለተወላጅ ሁሉ በማንኛውም ሁኔታ ሊተላለፍ የሚችል ይዞታ ነው፡፡9

የግል የመሬት ስሪት በAብዛኛው በደቡብ የIትዮጵያ ክፍል የነበረ ሲሆን ለEያንዳንዱ ባለይዞታ ሙሉ
የመሬት ባለቤትነት መብት የሚሰጥ ስሪት ነበር፡፡ የግል የመሬት ስሪት የግል ባለቤትነት መብት ያለበት
ስሪት በመሆኑም መሬቱ ሊሸጥ ወይም በሌላ ሁኔታ ለማንኛውም ሰው ሊተላለፍ የሚችልበት የይዞታ
ዓይነት ነበር፡፡10 የመንግስት ይዞታ በየትኛውም የIትዮጵያ ክፍል የነበረ ስሪት ሲሆን መሬቱን
መንግስት ለሚፈልገው ተግባር የሚያውልበት፣ ሲፈልግ ለባለሟሎቹ Eንደመተዳደሪያ የሚሰጥበት
ወይም ለመንግስት ለሚገብር ተጠማጅ የሚሰጥበት የይዞታ ዓይነት ነበር፡፡11

በAጠቃላይ በሀገራችን ቀደም ሲል በነበረው የመሬት ስሪት በርስት ስርዓት ከሚመራው Eና


በቤተክርስቲያን ይዞታ ሥር ከነበረው መሬት በስትቀር12 የገጠር መሬት Eንደሌሎች ንብረቶች ያለምንም
ገደብ በሽያጭ፣ በውርስ፣ በስጦታም ሆነ በሌሎች ሁኔታዎች ከAንድ ሰው ወደ ሌላ ሰው የሚተላለፍ

6
Ambaye, Supra note 3, p. 39
7
የገጠር መሬትን የሚመለከቱ ሕጎችና Aፈጻጸም በፍትሕ Aካላት ባለሙያዎች ስልጠና ማEከልለ ረጅም ጊዜ ስራ
ላይ ስልጠና ፕሮግራም የተዘጋጀ (ያልታተመ)፣ ገጽ 8
8
Aberra Jembere, Supra note 4, p. 141
9
Ibid
10
ማህተመስላሴ ወልደ መስቀል ስለ Iትዮጵያ የመሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ግብር ጠቅላላ Aስተያየት፣ 1970
(ያልታተመ)፣ ገጽ 14
11
Desalegn Rahmatto, Agrarian Reform in Ethiopia, Scandinivian Institute of African Studies, uppsala (1984), p. 20
12
ሞላ መንግስቱ፣ የገጠር መሬት ስሪት በIትዮዽያ፡- በሕግ የተደነገጉ መብቶችና በAማራ ብሔራዊ ክልል ያለው
Aተገባበር፣ የIትዮዽያ የሕግ መጽሔት፣ 22ኛ ቮልዩም፣ ቁጥር 2፣ 2001 ዓ/ም፣ ገጽ 157 Eና 158
4
ነበር፡፡13 ይኸውም በሰሜኑና መካከለኛው Iትዮዽያ በከፊል የነበረው የገጠር መሬት ስሪት የርስት ይዞታ
ስለነበር መሬት ከAንዱ ወደ ሌላው ሰው የሚተላለፈው ዘራቸውን ቆጥረው በሚመጡ የጋራ ተወላጆች
መካከል ብቻ ነበር። Eንደዚህ Aይነት ስሪት ባለበት Aካባቢ የርስት ተወላጆች መሬታቸውን ለመጠየቅ
ምንም ነገር የማያግዳቸው መሆኑን ከፍ/ሕ/ቁ 1168(1) ድንጋጌ ይዘት መረዳት ይቻላል። Eንዲሁም
በEነዚህ Aካባቢዎች ሲሶ መሬት በIትዮዽያ Oርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ይዞታ ሥር ሆኖ
ለቤተክርስቲያን Aገልግሎትና ለካህናት መተዳደሪያ ያገለግል የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ስለሆነም በዘውዳዊ ስርዓት የነበረው የመሬት ስሪት ለAርሶ Aደሩ የመሬት ባለቤትነትም ሆነ የመሬት
ባለይዞታነትና ተጠቃሚነት ምንም ዓይነት ዋስትና የማይሰጥ የሀገሪቱን የEርሻ መሬት በEጣት
ለሚቆጠሩ ሰዎች ባለቤትነትና Aዛዥነት ስር ያደረገና ሰፊውን Aርሶ Aደር ለጭሰኝነት Eና ለባርነት
የዳረገ Eንደነበር ይህም በ1966 ዓ/ም ለተደረገው ህዝባዊ ቁጣና Aብዮት መሰረታዊ ምክንያት የነበረ
መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡

በ1967 ዓ/ም የተደረገው የመሬት ስሪት ለውጥ በ1966 ዓ/ም የተካሄደው ሕዝባዊ Eንቅስቃሴ በሀገሪቱ
ያስከተለው Aጠቃላይ የስርዓት ለውጥ ውጤት Aካል ነበር፡፡ ሕዝባዊ Eንቅስቃሴውን ተከትሎ የደርግ
መንግስት የዘውድ Aገዛዙን ተክቶ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ የሀገሪቱ የፖለቲካ ስርዓት ሶሻሊስታዊ
ርEዮተ ዓለምን Eየተከተለ በመምጣቱ የIኮኖሚ ስርዓቱም Aብሮ በመለወጡ የመሬት ስሪት ለውጥ
ተደርጓል፡፡ የገጠር መሬት ስሪት ለውጡ በAዋጅ ቁጥር 31/1967 ሲታወጅም በመጀመሪያ AጽንOት
የሰጠው Eንደ Iትዮጵያ ባሉ በEርሻ የሚተዳደሩ ሀገሮች Aንድ ሰው በህብረተሰቡ ውስጥ ሊኖረው
የሚችለው የኑሮ ደረጃ፣ መብት፣ Eንዲሁም ክብርና ማEረግ የሚወሰነው ከመሬት ጋር ባለው ግንኙነት
በመሆኑ የዜጎችን Eኩልነት ለማስከበር የመሬት ስሪቱን መለወጥ Aስፈላጊ መሆኑን ነው፡፡14 የፖለቲካ
ስርዓቱ የሶሻሊስት ርEዮተ ዓለም ተከታይ በመሆኑም መሬትን የመሳሰሉ ሀብት ማፍሪያዎች የግል
ባለቤትነት መብት በስርዓቱ ተቀባይነት ስለማይኖረው የመሬት ስሪቱ በሀገሪቱ Aንድ ወጥ ሆኖ በAዋጁ
Aንቀጽ 3(1) “የሕዝብ ይዞታ” ተብሎ ታውጇል፡፡ የመሬት ስሪቱ የህዝብ ይዞታ Eንዲሆን በመታወጁ
መሬት ሊሸጥ ሊለወጥ የማይችል የህዝብ ሀብት Eንዲሆን ተደረገ፡፡ ስለዚህም በርስት፣ በግል ወይም
በመንግስት ይዞታ ስር የነበረው የገጠር መሬት ሁሉ የህዝብ ይዞታ በመደረጉ ማንኛውም በEርሻ
ለመተዳደር የሚፈልግ ሰው መሬት የማግኘት Eኩል መብት Eንዲኖረው ተደርጓል፡፡

ይሁን Eንጅ የመሬት ስሪቱ መሰረታዊ መርህ በዚህ መልኩ ቢታወጅም Aርሶ Aደሮች በመሬት ላይ
ያላቸው የመጠቀም መብት Eጅግ የጠበበ Eንዲሆን ተደርጎ ነበር፡፡ የመጀመሪያው የመብቱ ውሱንነት

13
የIትዮጵያ ንጉሰ ነገስት የፍትሐ ብሔር ሕግ፣ 1952 ዓ/ም፤ ለምሳሌ በቁጥር 2875 Eና ተከታይ ድንጋጌዎች
መሠረት መሬት በሽያጭ ይተላለፍ ነበር፡፡ በቁጥር 826 Eና ተከታይ ድንጋጌዎች መሠረት በውርስ ለወራሾች
በተቀመጠው ቅደም ተከተል Eና ከቁጥር 2427 Eስከ 2470 በተደነገገው Aግባብ በስጦታ ከAንዱ ወደ ሌላው
መተላለፍ ይችል ነበር። (ከዚህ በኋላ የፍትሐ ብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ሲጠቀሱ “የፍ/ሕ/ቁ” Eየተባለ ይገለጻል።)
14
የገጠር መሬትን የህዝብ ሀብት ለማድረግ የወጣ Aዋጅ ቁጥር 31/1967፣ መግቢያ
5
የሚታየው በAዋጁ Aንቀጽ 5 ላይ የይዞታ መሬትን በውርስ፣ በስጦታም ሆነ በሌላ መንገድ ማስተላለፍ
በመከልከሉ ነው፡፡ ባለይዞታው ሲሞት/ስትሞት ብቻ የትዳር ጓደኛው ወይም Aካለ መጠን ያላደረሰ ልጅ
Eነዚህ ከሌሉ ደግሞ Aካለ መጠን ያደረሰ ልጅ ተተክቶ በመሬቱ የመጠቀም መብት Eንደሚኖረው በዚሁ
Aዋጅ Aንቀጽ 5 በልዩ ሁኔታ ተደንግጓል፡፡ በዚህ ክልከላ ምክንያትም የመሬት ባለይዞታው ያለው
መብት ከAንድ የመሬት ተከራይ ያለፈ Aልነበረም፡፡ ሁለተኛው ውስንነት ማከራየትን ጨምሮ በሌላ
ሁኔታ የመሬት ይዞታ መብትን መገልገል መከልከሉ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በEርጅና፣ በህመም፣
Aካለ መጠን ባለማድረስ ወይም ለሴቶች ካልሆነ በቀር በይዞታ መሬት ላይ ሌላ ሰው ቀጥሮ ማሳረስ
የተከለከለ Eንደነበር ከAንቀጽ 4(1) መረዳት ይቻላል። ይህም ሲታይ በሕግ የተሰጠውን መሬት
የማግኘት መብት በተግባር ለመጠቀም የነበረውን የመብት ጠባብነትና Aስቸጋሪነት ያስገነዝበናል፡፡

በ1980 ዓ/ም የወጣው የIሕድሪ ሕገ መንግስትም የገጠር መሬት ስሪትን በተመለከተ ቀደም ብሎ
ከታወጀው ስሪት የተለየ ያመጣው ለውጥ Aልነበረም፡፡ ስለሆነም የደርግ የመሬት ስሪት ለAብዛኛው
የህብረተሰብ ክፍል መብት የሚነፍገውን ነባሩን የመሬት ስሪት በማስወገድ መልካም ገጽታ ያለው
ቢሆንም የመሬት ባለይዞታዎችን መብት በማጥበቡ ከንብረት መብት Aንፃር ለAርሶ Aደሮች የጎላ
የመሬት የተጠቃሚነት ለውጥ ሳያመጣ ቀርቷል፡፡

በ1983 ዓ/ም ደርግን ከስልጣን ያስወገደው IሕAዴግ በትግል ወቅት Eንደመታገያ ያነሳቸው ከነበሩ
ጥያቄዎች Aንዱ ደርግ የገጠር መሬት ጥያቄን በAግባቡ Aልመለሰውም የሚለው ነበር፡፡ ሆኖም ሐምሌ
15 ቀን 1983 ዓ/ም የወጣው የሽግግር መንግስት መተዳደሪያ ቻርተር Aንዳንድ መሰረታዊ የፖለቲካ
Aቅጣጫዎችን ከመጠቆሙ በስተቀር15 ቻርተሩ በሕገ መንግስት Eስኪተካ ድረስ የገጠር መሬት ስሪቱ
በነበረበት በመቀጠሉና የመሬት Aስተዳደሩም የEለት ከEለት ችግሮችን በማቃለል ላይ ተወስኖ በመቆየቱ
ስለመሬት ስሪት ለውጥ ከሚወጣው Aዲስ ሕገ መንግስት ድንጋጌ ሲጠበቅ ቆይቷል፡፡

ይህ ሕገ መንግስትም በደርግ መንግስት ከነበረው በተለየ ሁኔታ የሀገሪቱ የንብረት ባለቤትነት መብት
ሥርዓት በግል ባለቤትነት ላይ የተመሰረተ መሆኑን በAጠቃላይ ደንግጐ የገጠር መሬት የባለቤትነት
መብት የመንግስትና የህዝብ ብቻ ነው በማለት Aውጇል፡፡16 የIፌዲሪ ሕገ መንግስት Aንቀጽ 40(3)
የገጠር መሬትን በተመለከተ የሚደነግገው ሁለት መሰረታዊ ነጥቦችን ነው፡፡ Aንደኛው የመሬት
ባለቤትነት የመንግስትና የሕዝብ ነው የሚለው ሲሆን ሁለተኛው መሬት ሊሸጥ ሊለወጥ Aይችልም
የሚለው ነው፡፡ ሁለቱም ነጥቦች ለገጠር መሬት ባለይዞታዎችና ተጠቃሚዎች መብት የሚሰጡ ሳይሆኑ
በተጠቃሚዎች መብት ላይ የተጣሉ ገደቦች ናቸው፡፡ ሕገ መግስቱ የመረጠው በመሬት ላይ የተፈቀዱ
መብቶችን በሙሉ ዘርዝሮ በመደንገግ ፈንታ Aንድ የንብረት ባለመብት ሊኖሩት ከሚችሉት መብቶች

15
የሽግግሩ መንግስት ቻርተር ቁጥር 1/1983፣ Aንቀጽ 10
16
የIፌዲሪ ሕገ መንግስት፣ Aዋጅ ቁጥር 1/1987፣ Aንቀጽ 40(1) ማንኛውም Iትዮጵያዊ የግል ንብረት ባለቤት
የመሆን መብት Eንዳለው ሲደነገግ የዚሁ Aንቀጽ ንUስ Aንቀጽ 3 ግን ከንUስ Aንቀጽ 1 በተለየ ሁኔታ የገጠርም
ሆነ የከተማ መሬት ባለቤትነት መብት የመንግስትና የሕዝብ ብቻ መሆኑን ደንግጓል፡፡
6
ውስጥ መሬትን በተመለከተ የተከለከሉትን በዝርዝር ማስቀመጥን ነው፡፡ ስለዚህ በIትዮጵያ የገጠር
መሬት ስሪት መሰረት Aንድ የመሬት ተጠቃሚ ከAንድ የንብረት ባለቤት ከሚኖረው መብት በተለየ
የከለከለው መሸጥና መለወጥን ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ሕገ መንግስቱ የይዞታ ወይም የመጠቀም
መብትን በሌላ ሁኔታ ማስተላለፍን መከልከለ Aለመፈለጉን የሚያሳይ ነው፡፡

በሌላ Aገላለጽ የገጠር መሬት ስሪት የመሬት ባለቤትነቱ የመንግስትና የህዝብ መሆኑን Eና Aርሶ
Aደሮች17 ከሚያገኙት መሬት ያለመነቀል መብት Eንዳላቸው መደንገጉ የሚያስገነዝበው በመሬት ላይ
የሚኖራቸው መብት የይዞታ መብት መሆኑን ነው፡፡ የይዞታ መብት በይዞታ መብቱ ላይ ተመስርቶ
ከሚገኘው የመጠቀም መብት የተለየ ነው፡፡ ይኸውም የባለቤትነት መብት፣ የይዞታ መብትና የመጠቀም
መብት የተለያዩና ከመጀመሪያው ወደ መጨረሻው በቅደም ተከተል Eየጠበቡ የሚመጡ ናቸው፡፡
ምክንያቱም የባለቤትነት መብት መሸጥን ጨምሮ ማንኛውንም በንብረት ላይ ሊኖር የሚችል መብት
ሁሉ የሚያካትት ከመብቶች ሁሉ የሰፋ መብት ሲሆን የይዞታ መብት ደግሞ በIፌዲሪ ሕገ መንግስት
መሰረት የገጠር መሬትን በተመለከተ Aንድ የመሬት ባለቤት ሊኖረው ከሚችለው መብት ላይ በመሸጥ
ወይም በመለዋወጥ መሬትን ለሌላ ሰው ማስተላለፍን ብቻ ለይቶ በመከልከል ሌሎችን መብቶች ግን
የጠበቀ የመብት ዓይነት ነው፡፡ የመጠቀም መብት ደግሞ Aንድ የገጠር መሬት የይዞታ መብት ያለው
ሰው በመሬቱ የመጠቀም መብቱን ለሌላ ሰው ሲያስተላልፍ የተላለፈለት ሰው የሚኖረው መብት ነው፡፡18

የብሔራዊ ፖሊሲ መርሆዎችና ዓላማዎች በተዘረዘሩበት የIፌዲሪ ሕገ መንግስት ምEራፍ Aስር


Aንቀጽ 89(5) ላይ መንግስት መሬትና የተፈጥሮ ሀብትን በሕዝብ ስም በይዞታው ሥር በማድረግ
ለሕዝቡ የጋራ ጥቅምና Eድገት Eንዲውሉ የማድረግ ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ተደንግጓል፡፡ መሬትና
የተፈጥሮ ሀብት Aጠቃቀምና ጥበቃን በተመለከተ ሕግ የማውጣት ስልጣን የፌደራል መንግስት
Eንደሆነ የሕገ መንግስቱ Aንቀጽ 51(5) ይደነግጋል፡፡ በዚሁ ሕገ መንግስት Aንቀጽ 52(2)(መ) ድንጋጌ
መሰረት ደግሞ ክልሎች የፌደራሉ መንግስት የሚያወጣውን ሕግ መሰረት Aድርገው መሬትንና
የተፈጥሮ ሀብትን የማስተዳደር ስልጣን Aላቸው፡፡ በሌላ መልኩ የሕገ መንግስቱን Aንቀጽ 50(9)
የፌደራል መንግስቱ በዚሁ ሕገ መንግስት Aንቀጽ 51 ከተሰጡት ስልጣንና ተግባሮች መካከል Eንደ
Aስፈላጊነቱ ለክልሎች በውክልና ሊሰጥ Eንደሚችል ደንግጓል፡፡

ሕገ መንግስቱ ከጸደቀ በኋላ የፌደራል መንግስት የገጠር መሬትን በተመለከተ ስለ ስሪቱ፣ ስለመብቱ
ወሰንና ስለAስተዳደሩ የሚደነግግ ሕግ ለመጀመሪያ ጊዜ ያወጣው Aዋጅ ቁጥር 89/1989ን ነው፡፡19
Aዋጁ ለክልሎች ሕግ Aወጣጥ Eንደመመሪያ የሚያገለግሉ መርሆዎችን የያዘ Eንጅ ዝርዝር ድንጋጌዎች
Aልነበረውም፡፡ ክልሎች Eንዲያወጡ ለሚጠበቀው ዝርዝር ሕግ Eንደመመሪያ ሆኖ ለማገልገልም

17
ለዚህ ጽሑፍ Aላማ ሲባል “Aርሶ Aደሮች” የሚለው Aገላለጽ ከፊል Aርብቶ Aደሮችን Eና Aርብቶ Aደሮችንም
ያካትታል፡፡
18
ለምሳሌ በኪራይ ለተወሰነ ጊዜ ቢያስተላልፍ
19
የፌደራል መንግስት የገጠር መሬት Aስተዳደር Aዋጅ ቁጥር 89/1989፣
7
ግልጽነት የጎደለው ነበር፡፡ Aዋጁ የመሬት ባለይዞታዎች መሬታቸውን ለግብርና ስራ የማዋል፣
የማከራየትና ለቤተሰብ Aባላት የማውረስ መብት ያላቸው መሆኑን የሚጠቁሙ Aቅጣጫዎችን በAንቀጽ
2(3)፣ 5 Eና 6 ያካተተ ነበር።

ቀጥሎም Aዋጅ ቁጥር 89/1989ን ማሻሻል በማስፈለጉ የተሻሻለው የገጠር መሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም Aዋጅ ቁጥር 456/1997 ወጥቷል፡፡20 ይህ Aዋጅ ከAዋጅ ቁጥር 89/1989 በተሻለ መልኩ
ከመሬት Aጠቃቀምና Aስተዳደር ጋር የተያያዙ መብትና ግዴታዎችን የሚመለከቱ ዝርዝር ድንጋጌዎችን
ይዟል፡፡ Aዋጅ ቁጥር 456/1997 ከሞላ ጎደል የIፌዲሪ ሕገ መንግስትን መሰረት በማድረግ የወጡ
የIኮኖሚ ልማት ፖሊሲዎችና ስትራቴጅዎችን ተግባራዊ ለማድረግ በሚያስችል መልኩ የወጣ ሕግ
ነው፡፡ ከAዋጁ መግቢያ መረዳት የሚቻለውም በርካታ የገጠር ልማት ዓላማዎችን የያዘ መሆኑን ነው፡፡
Eነዚህንም ዘላቂ ልማት (sustainable development) ማረጋገጥ፣ Aርሶ Aደሩ በመሬት ላይ ያለውን
የንብረት መብት ማጠናከር፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ሴቶች በመሬት ላይ ያላቸውን መብት
ማረጋገጥ፣ ማህበራዊ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ Aጥጋቢ የገጠር መሬት መረጃ ስርዓትን ማረጋገጥ Eና
ቀልጣፋ የገጠር መሬት Aስተዳደር ስርዓት መዘርጋት የሚሉ ናቸው፡፡

በAዋጅ ቁጥር 456/1997 Aንቀጽ 17(1) መሰረት ክልሎች ይህን Aዋጅ ለማስፈጸም የሚስፈልጉ ዝርዝር
ድንጋጌዎችን የያዘ የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ሕግ Eንዲያወጡ ውክልና ሰጥቷል፡፡21
ይህንን Aዋጅ ተከትሎ የAማራ ክልል የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ሕጎችን Aውጥቷል፡፡
Eነዚህም ቀደም ሲል Aዋጅ ቁጥር 46/1992፣ በኋላም ይህን Aዋጅ ያሻሻለው Aዋጅ ቁጥር 133/1998
Eና ማስፈፀሚያ ደንቡ ቁጥር 51/1999 ወጥተው ለAመታት ሥራ ላይ ቆይተዋል፡፡22 Aሁን ደግሞ
በቅርቡ Aዋጅ ቁጥር 252/2009 Eና ማስፈጸሚያ ደንብ ቁጥር 159/2010 ተሻሽለው ወጥተዋል፡፡
ሎሎች ክልሎችም የየራሳቸውን ሕጎች Aውጥተዋል፡፡23
3. በAዲሱ የAማራ ክልል የገጠር መሬት Aስተዳዳርና Aጠቃቀም ሕግ የተካተቱ ዋና ዋና
ጠቃሚ ጉዳዮች (መልካም ጎኖች)
የIትዮጵያ Aርሶ Aደሮች ለEረሻም ሆነ ለግጦሽ የሚጠቀሙበት የገጠር መሬት በነጻ የማግኘት፣
የመጠቀም Eና ከመሬታቸው ያለመፈናቀል መብት ያላቸው መሆኑን የIፌዴሪ ሕገ መንግስት Aንቀጽ

20
የIትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም Aዋጅ ቁጥር
456/1997፣ ከዚህ በኋላ “Aዋጅ ቁጥር 456/1997” Eየተባለ ይጠራል።
21
በሕገ መንግስቱ Aንቀጽ 51 መሰረት ከፌደራል መንግስት ለክልሎች የሚሰጠው ውክልና ሕግ የማውጣት
(በAዋጅ ቁጥር 456/1998 Aንቀጽ 17 Eንደተሰጠው Aይነት)፣ ሕግ የመተርጎም (በህገ መንግስቱ Aንቀጽ 80
መሰረት የፌደራል ፍርድ ቤቶች ስልጣን ለክልል ፍርድ ቤቶች Eንደተሰጠው Aይነት) ወይም ሕግ የማስፈጸም
(ክልሎች የተጨማሪ Eሴት ታክስ ሰብስበው ለፌደራል መንግስት Eንደሚሰጡት Aይነት) ሊሆን ይችላል፡፡
22
በEርግጥ በክልሉ በመጀመሪያ የወጣው የመሬት ሽግሽግ የተደረገበት Aዋጅ ቁጥር 16/1989 ነው። የAዋጅ ቁጥር
133/1998 ማሻሻያ Aዋጅ ቁጥር 148/1999 ደግሞ ቀደም ሲል የመሬት ክርክር በቀበሌ ማህበራዊ ፍርድ ቤት
ጀምሮ ይካሄድ የነበረውን በማስቀረት ክርክሩ በወረዳ ፍርድ ቤት Eንዲጀምር ለማድረግ Aላማ መታወጁን
ማስታወስ ያስፈልጋል።
23
ጸሐፊው የሌሎች ክልሎችን የመሬት ሕጎች የመዳሰስ ዓላማ ስለሌለው በዝርዝር መግለጽ Aላስፈለገውም፡፡
8
40(4)(5) ይደነግጋል፡፡ በሕገ መንግስቱ Aንቀጽ 40(4) መሰረት የገጠር መሬት ባለይዞታ የሆነ ሰው
የሚከለከለው መሬቱን መሸጥ Eና በሌላ ንብረት መለወጥ ብቻ Eንደመሆኑ መጠን Aርሶ Aደሮች በነጻ
ያገኙትን መሬት በተለያየ መልኩ የመጠቀም፣ በስጦታ ወይም በውርስ የማስተላለፍ፣ የማከራየት Eና
ተያያዥ መብቶች ይኖራቸዋል፡፡ Aዋጅ ቁጥር 456/1997 Aንድ የመሬት ባለይዞታ ያሉትን መብቶች
በበቂ ሁኔታ ባይዘረዝርም መጠቀም፣ ማከራየት Eና ማውረስ Eንደሚችል በጥቅሉ ይጠቁማል፡፡ Aዲሱ
የክልላችን Aዋጅ ቁጥር 252/2009 የገጠር መሬት የይዞታ መብት የሚገኝባቸው መንገዶች፣ የገጠር
መሬት ለማግኘት የሚያስፈልጉ መስፈርቶችን፣ የባለይዞታዎችን መብትና ግዴታዎች፣ ግዴታን
Aለመወጣት የሚያስከትለውን Eርምጃ፣ የይዞታ መሬት የሚታጣባቸውን ሁኔታዎች፣ የመረጃ Aያያዝ
ስርዓቱን፣ የክርክር Aፈታት ዘዴዎችን Eና ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎችን ይዟል፡፡ ስለሆነም ቀጥለን
Aዲሱ Aዋጅ ከቀድሞው ሕግ Aንጻር ያመጣቸውን Aዳዲስ ሀሳቦች Eና መልካም ጎኖች Eንመለከታልን፡፡

3.1 Aነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች የመሬት ይዞታ ሊኖራቸው Eንደሚችል መደንገጉ


በAዋጅ ቁጥር 252/2009 Aንቀጽ 7(1) Eና 10(1) Eንደተደነገገው የገጠር መሬት ባለይዞታ ለመሆን
ወይም መሬትን ከሚያስተዳድረው Aካል መሬትን በነጻ በድልድል ለማገኘት ሶስት መሰረታዊ
መስፈርቶች ያስፈልጋሉ፡፡ Eነዚህም፡- የክልሉ ነዋሪ መሆን፣ በዋነኝነት በግብርና ሥራ መተዳደር ወይም
በዚሁ የሥራ መስክ ለመተዳደር መፈለግ Eና Eድሜ 18 ዓመትና በላይ መሆን የሚሉ ናቸው፡፡ ቀደም
ሲል የነበረው የክልላችን Aዋጅ ዝርዝሩ በደንብ የሚወሰን ሆኖ ከግብርና ውጭ በሆነ ሥራ ላይ
የተሰማራና ገቢ የሚያገኝበት ቋሚ መተዳደሪያ ያለው ሰው በመሬት ይዞታ የመጠቀም መብቱን
Eንደሚያጣ ይደነግግ ነበር፡፡24 ዝርዝር ሁኔታዎችን የሚወስነው ደንብ ደግሞ በዝቅተኛ መነሻ
ደመወዝነት Eንዲከፈል በመንግስት ከተወሰነው Aማካይ የወር ደመወዝ መጠን ያላነሰ ገቢ በሚያስገኝ
ቋሚ ስራ ላይ ተቀጥሮ መገኘት Eና ከግብርና ሥራ ውጭ በሆነና ግብር በሚያስከፍል የሥራ መስክ
ተሰማርቶ መገኘት የገጠር መሬት ይዞታ የሚታጣባቸው ሁኔታዎች መሆናቸውን ይደነግጋል፡፡25

ይሁን Eንጅ Aዲሱ Aዋጅ በልዩ ሁኔታ Aነስተኛ የወር ገቢ በሚያስገኝ Eንደ ዘበኛነት፣ ፅዳት፣ ተላላኪና
ፖስተኛ Aይነት ሥራ የተቀጠሩ ሠራተኞች በቀጥታ በግብርና ሥራ Eየተዳደሩ Aይደለም በሚል የገጠር
መሬት ባለይዞታ ከመሆን የማይከለከሉ መሆኑን ይደነግጋል፡፡26 ይህም ሕግ Aውጭው በዝቅተኛው
የመንግስት የሥራ መደብ Eና ተመሳሳይ ሥራ ላይ ተቀጥረው የሚገኙ ዜጎች የሚያገኙት ደመወዝ
በጣም Aነስተኛ ስለሆነ ለኑሮ Aስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ለማሟላት በቂ Aለመሆኑን ግምት ውስጥ
Aስገብቶ ያካተተው Aዲስ ድንጋጌ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡

24
የAዋጅ ቁጥር 133/1998፣ Aንቀጽ 12(1)(ሀ)
25
ደንብ ቁጥር 51/1999፣ Aንቀጽ 14(1)(ሀ)(ለ)
26
Aዋጅ ቁጥር 252/2009፣ Aቀንጽ 7(2)፤ ቀደም ሲል ደንብ ቁጥር 51/1999 Aንቀጽ 14(2) ላይ በብሔራዊ
Aገልግሎት የተመደበ ማንኛውም ሰው የገጠር መሬት ባለይዞታነቱ ቀሪ ሊደረግ Eንደማይችል ይደነግግ ነበር፡፡
9
በሌላ በኩል የገቢ መጠኑ የቱንም ያህል ቢሆን Aስቀድሞ የተሰማራበት ቋሚ መተዳደሪያ የግብርና
መስክ ሆኖ ሳለ በጥረቱ ተጨማሪ ሀብት በመፍጠርና ከዚሁ የተነሳም ወደ Iንቨስትመንት ሥራ
ለመሸጋገር የበቃ ማንኛውም ታታሪ Aርሶ Aደር ለግብርና ሥራ የተሰጠውን የገጠር መሬት ይዞታ በዚህ
Aዋጅ መሰረት Eንዲያጣ የማይደረግ ስለመሆኑ ተደንግጓል፡፡27 የዚህ ድንጋጌ Aላማም Aርሶ Aደሮች
ለዘመናት ከኖሩበት ከEጅ ወደ Aፍ የሆነ ኑሮ ተላቀው የተሻለ ቴክኖሎች በመጠቀም በመሬታቸው ላይ
በቂ ምርት Eያመረቱ በቂ ጥሪት Eያፈሩ ከEርሻ ሥራ ውጭም ወደ ንግድና Iንቨስትመንት ሥራ
Eንዲሰማሩ ለማበረታታት ነው፡፡ በዚህ ሂደት የሚቀየሩ Aርሶ Aደሮች መሬታቸውን Eንዲያጡ ከተደረጉ
ሌሎች Eነዚህን ውጤታማ Aርሶ Aደሮች Eያዩ Eንዳይበረታቱ ያደርጋል ተብሎ ይታሰባል፡፡28

3.2 ሴቶች፣ ህጻናት፣ Aካል ጉዳተኞች፣ Aረጋዊያንና Aቅመ ደካሞች ልዩ ትኩረት ማግኘታቸው፣
በAዋጁ መግቢያ ላይ የቀድሞው Aዋጅ Eንዲሻሻል ካስፈለገባቸው ምክንያቶች ውስጥ Aንዱ ሴቶች፣
ሕጻናት፣ Aክል-ጉዳተኞች፣ Aቅመ-ደካሞች Eና Aረጋዊያን ያላቸዉ በገጠር መሬት የመጠቀም መብት
Eንዲጠናከር ዝርዝር ሁኔታዎችን የሚደነግግ ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ነው ይላል፡፡ የAዋጁ
Aንቀጽ 5(6) መሰረታዊ መርሆዎችን ሲደነግግ የገጠር መሬት ድልድል በሚካሄድበት ጊዜ ወላጆቻቸውን
ላጡ ሕፃናት፣ ለAካል ጉዳተኞች፣ ለAቅመ ደካሞች፣ ለሴቶችና ለAረጋውያን ቅድሚያ Eንዲሰጥ
የሚያደርግ የAሠራር ስርዓት ተቀርጾ በሥራ ላይ Eንደሚውል ይገልጻል፡፡

የመሬት ድልድል በሚደረግበት ወቅትም Eነዚህ ወገኖች በግብርና ሥራ የሚተዳደሩ ወይም ለመተዳደር
የመረጡ ሆነው ሳለ ለዚሁ ዓላማ የሚያስፈልገው የEርሻ መሬት የሌላቸው ወይም ያነሳቸው Eንደሆነ
መሬት በማግኘት ረገድ የቀደምትነት መብት Eንደሚኖራቸው የAዋጁ Aንቀጽ 10(4) ይገልጻል፡፡ ሊሰጥ
የሚችለው የመሬት መጠን ችግሩ ላለባቸው ጠያቂዎች ሁሉ Eኩል ሊዳረስ የማይችል ከሆነ Eንደ
ቅደም ተከተላቸው ወላጆቻቸዉን በሞት ላጡ ሕፃናት፣ ለAካል ጉዳተኞች፣ ለAቅመ ደካሞች፣ ለሴቶችና
ለAረጋውያን ይሰጣል፡፡29 በመስኖ ልማት ፕሮጀክት ምክንያት የሚካሄድን የገጠር መሬት ሽግሽግ
ተከትሎ የመስኖ መሬት ክፍፍል በሚከናወንበት ጊዜ መሬታቸውን ያጡ ወይንም ይዞታቸው
የተቀነሰባቸው ሰዎች ከተስተናገዱ በኋላ ትርፍ መሬት የተገኘ Eንደሆነ Eንዲሁም በቀበሌ ማEከላት
ውስጥ ቤት መስሪያ ቦታ በማግኘት ሂደት Eነዚህ ወገኖች ከሌሎች ወገኖች ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡30

በተጨማሪም ሞግዚት ወይም ሕጋዊ ወኪል የሌላቸው ሕፃናት፣ የAካል ጉዳተኞች፣ የAቅመ ደካሞች፣
የሴቶችና የAረጋውያን ይዞታ የሆነ መሬት በሚመዘገብበትና በሚረጋገጥበት ወቅት Eነዚሁ ወገኖች
በስፍራው ካለመገኘታቸው የተነሳ መብታቸው Eንዳይጣስ ብርቱ ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል፡፡31

27
Aዋጅ ቁጥር 252/2009፣ Aንቀጽ 22(3)
28
ምናልባት የዚህ ድንጋጌ Aስፈላጊነት ጊዜያዊ ሊሆን ይችላል፡፡ በርካታ Aርሶ Aደሮች በዚህ ሂደት Eስከሚለወጡ
ተግባራዊ ሆኖ ሀገር ስትለወጥ ቀሪ ሊሆን የሚችል መብት ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡
29
Aንቀጽ 12(3)
30
የAዋጁ Aንቀጽ 14(4) Eና Aንቀጽ 31(6)
31
Aንቀጽ 39(1)
10
Eንዲሁም በሕጋዊ Aሳዳሪ ወይም በሞግዚት ጥበቃ ስር የሚተዳደሩ ሕፃናት፣ Aረጋዊያንና በፍርድ
የተከለከሉ ሰዎች ወይም የAEምሮ መታወክ ያለባቸው ስለመሆኑ በፍርድ የተረጋገጠላቸው
ባለይዞታዎች የመሬት ይዞታቸውን ሲያከራዩ ውሉ የነርሱን ጥቅም በማይጎዳ ሁኔታ ስለመደረጉ
ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ የቤተ-ዘመድ ጉባኤ የመከረበትና ውል ለመዋዋል ሥልጣን የተሰጠው Aካል
ያጸደቀው ሰነድ ከኪራይ ውሉ ጋር ተያይዞ ለምዝገባ መቅረብ ይኖርበታል፡፡32 የEነዚህ ሁሉ ድንጋጌዎች
ይዘት ሕግ Aውጭው ለEነዚህ ወገኖች ከፍተኛ ጥበቃ ለማድረግ የሞከረ መሆኑን ያሳያል፡፡

3.3 የመሬት ይዞታን ከማከራየት መብት ጋር ተያይዞ የተሻሻሉ ጉዳዮች መኖር


ማንኛውም የገጠር መሬት ባለይዞታ ራሱን ከይዞታው Eስከማፈናቀል በማያደርስ ሁኔታ በይዞታ መሬቱ
ላይ የመጠቀም መብቱን ለሌላ ለማንኛውም ለግብርና ሥራ ለሚያውል ሰው በኪራይ ውል ማስተላለፍ
Eንደሚችል Aንቀጽ 15(1) (2) ይደነግጋል፡፡ የገጠር መሬት ኪራይ ውል ስምምነት Eስከ ሁለት ዓመት
ለሚዘልቅ ጊዜ የተደረገ ከሆነ መሬቱ ለሚገኝበት ቀበሌ መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት Eና ከዚያ
ለበለጠ ጊዜ የተደረገ ከሆነ ደግሞ ለወረዳ የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት ቀርቦ
መመዝገብ ይኖርበታል፡፡33 ይህም ቀደም ሲል በነበረው ሕግ ከ3 ዓመት በታች የሚደረግ የመሬት
ኪራይ ውል የመመዝገብ ግዴታን የማይጥለውን ድንጋጌ Aሻሽሎታል፡፡34 ይህ መሆኑ በAንድ በኩል
Aዋጅ ቁጥር 456/1997 Aንቀጽ 8(2) ማንኛውም Aይነት የመሬት ኪራይ ውል Eንዲመዘገብ
የሚጥለውን ግዴታ ያከብራል፡፡ በሌላ በኩል ከ3 ዓመት በታች የሚደረግ ኪራይ Eንዲመዘገብ ግዴታ
Aለመቀመጡ ባለዞታዎች ያለጽሑፍ Eና ያለምዝገባ መሬታቸውን ካከራዩ በኋላ የኪራይ ዘመኑን በቃል
Eያራዘሙ ሲቆዩ ከረጅም ዘመን በኋላ Aልፎ Aልፎ በተግባር ይከሰት የነበረውን ተከራይ በራሱ ስም
Aስመዝግቦ የመገኘት ችግርን ያስወግዳል፡፡ ምክንያቱም ለሁሉም Aይነት የመሬት ኪራይ ውል ምዝገባ
ግዴታ ሲሆን Eና በዚህ መልኩ ሲደረግ ማስረጃ በቀላሉ ስለሚገኝ የዚህ Aይነት ችግርን ያቃልላል፡፡

በAዲሱ Aዋጅ መሰረት ከፍተኛው የገጠር መሬት ኪራይ ውል ዘመን ቋሚ የፍራፍሬ ተክሎችን ወይም
የተመረጡ የዛፍ ዝርያዎችን የተመለከተ Eንደሆነ 30 ዓመት ሲሆን ለዓመታዊ ሰብሎች ደግሞ 10
ዓመት ነው፡፡ ከ30 ዓመት Eና ከ10 ዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ ተደርጎ የተገኘ የመሬት ኪራይ ውል
ስምምነት ቢኖር Eንደቅደም ተከተላቸዉ ለ30 ዓመት Eና ለ10 ዓመት Eንደተደረገ ይቆጠራል፡፡35 ይህ
ድንጋጌ ከቀድሞው Aዋጅ በተሻለ ሁኔታ ነባራዊ ሁኔታዎችን ግምት ውስጥ ያስገባ ነው፡፡ ይኸውም ሕግ
Aውጭው ቋሚ የፍራፍሬ ተክሎችን ወይም የተመረጡ የዛፍ ዝርያዎችን የተመለከተ ኪራይን 30
ዓመት Eንዲሆን ማድረጉ Eነዚህን ተክሎች በመትከል Aሳድጎ ፍሬ ለማግኘት የሚፈጀውን ረጅም ጊዜ

32
Aንቀጽ 15(12)
33
Aንቀጽ 15(8)
34
Aዋጅ ቁጥር 133/1998፣ Aንቀጽ 18(2)(5)
35
Aዋጅ ቁጥር 252/2009፣ Aንቀጽ 15(9)
11
ግምት ውስጥ ያስገባ ነው፡፡ ለሰብል የሚውል መሬት ግን በየዓመቱ ፍሬ ስለሚሰጥ በAንጻራዊነት
የኪራዩን ዘመን Aጭር ጊዜ ማድረግ ለባለይዞታዎች የሚኖረውን ጥቅም ያገናዘበ ነው ማለት ይቻላል፡፡

በሌላ በኩል Aዲሱ Aዋጅ የኪራይ ውል Aደራረግ ፎርማሊቲን ከቀድሞው በተለየ ሁኔታ ደንግጓል፡፡
ይኸውም የገጠር መሬት ኪራይ ውል በጽሑፍ መሆን Eና የመሬቱን ስፋት፣ የኪራዩን ዘመን፣
የክፍያውን መጠን Eንዲሁም የAከፋፈሉን ሁኔታ በግልጽ የሚያሳይ መሆን Eንዳለበት ከቀድሞው ሕግ
ጋር ተመሳሳይ ድንጋጌ ይዟል፡፡36 በተጨማሪ ግን የኪራይ ዉል ስምምነቱ ሕጋዊ የዉል ማቋቋሚያ
ሁኔታዎችን Aሟልቶ ካልተገኘ ወይም ተከራዩ በተከራየዉ መሬት ላይ ጉዳት ካደረሰ ወይም
ከስምምነታቸው ዉጭ ፈጽሞ ከተገኘ ዉሉ ፈራሽ Eንደሚሆን ይደነግጋል፡፡37 በፍትሐ ብሔር ሕጋችን
ስለ ውል ሕግ በሚደነግገው መጽሐፍ ክፍል መረዳት Eንደሚቻለው የውል ማቋቋሚያ ሁኔታዎች
የሚባሉት ችሎታ፣ ጉድለት የሌለበት ፈቃድ፣ በቂ የሆነ Eርግጠኛነት ያለው የሚቻልና ህጋዊ የሆነ
ጉዳይ Eና የውል Aጻጻፍ ፎርም ናቸው፡፡38

3.4 የውርስ ቅደም ተከተሉ ለልጆች ቅድሚያ መስጠቱ Eና ተያያዥ መሻሻሎች መኖር
የገጠር መሬት ባለይዞታ የሆነ ማንኛውም ሰው የይዞታም ሆነ የመጠቀም መብቱን በግብርና ሥራ
ለሚተዳደር ወይም በዚሁ ሙያ መተዳደር ለሚፈልግ ማንኛውም ሰው በኑዛዜ ሊያስተላለፍ Eንደሚችል
Aንቀጽ 17(1) ይደነግጋል፡፡ የኑዛዜው Aደራረግ በፍትሐ ብሔር ሕግ ውስጥ Eንደተደነገገው ግልጽ
ኑዛዜ የሚደረግበትን መስፈርቶች ማሟላት Eና በወረዳ መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት ቀርቦ
መመዝገብ ያለበት መሆኑን Aንቀጽ 17(4) ይደነግጋል፡፡ በግልጽ የሚደረግ ኑዛዜ ተናዛዡ Eየተናገረ
ማንኛውም ሌላ ሰው ወይም ተናዛዡ ራሱ የሚጽፈው ሲሆን ኑዛዜው በተናዛዡና Aራት ምስክሮች ፊት
መነበብ፣ ቀን በግልጽ የተጻፈበት፣ የተናዛዡን ቃል ሊለውጥ የሚችል ፍቀት Eና ስርዝ ድልዝ
የሌለበት፣ ተናዛዡና ምስክሮቹ ወዲያውኑ የፈረሙበት መሆን Aለበት።39 ምስክሮቹም Aካለ መጠን
የደረሱ፣ በፍርድ ወይም በሕግ ያልተከለከሉ መሆን Eና ኑዛዜው የተጻፈበትን ቋንቋ የሚያውቁ
Eንዲሁም የተጻፈውን ለመስማት ወይም ለማንበብ ራሳቸው ችሎታ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል።40
በAዲሱ Aዋጅ ይህ የኑዛዜ ፍርማሊቲ መካተቱ ቀደም ሲል በነበረው ሕግ ስለኑዛዜ ምንም Aይነት
ፎርማሊቲ ባለመካተቱ በAሠራር Eያጋጠሙ የነበሩ ውዝግቦችን ያስቀራል ተብሎ ይታሰባል፡፡41

36
Aንቀጽ 15(3)(4)
37
Aንቀጽ 15(11)
38
የፍትሐ ብሔር ሕግ፣ ቁጥር 1678
39
ዝኒ ከማሁ፣ Aንቀጽ 881 Eና 889(1)፣ በEርግጥ በAንቀጽ 882 Eንደተደነገገው ከምስክሮቹ መካከል Aንዱ ዳኛ
ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን የተሰጠው Aካል ሲሆን Eና ኑዛዜው የተደረገው ይህ ሰው ሥራውን
በሚያከናውንበት ቦታ ከሆነ የጸና ኑዛዜ ለማድረግ ሁለት ምስክሮች ይበቃሉ።
40
ዝኒ ከማሁ፣Aንቀጽ 883
41
በቀድሞው ሕግ በAዋጁም ሆነ በደንቡ ስለ ኑዛዜ ፎርማሊቲ በዝምታ ያለፈው ስለነበር Eና በመሬት Aስተዳዳርና
Aጠቃቀም ቢሮ በወጣው መመሪያ ላይ ብቻ ኑዛዜ በፍርድ ቤት መጽደቅ Aለበት የሚል ድንጋጌ በመካተቱ የሕግ
ባለሙያዎች ሁለት Aይነት Aተያየት ነበራቸው፡፡ የመጀመሪያው የመሬት ይዞታን በኑዛዜ ማስተላለፍ ራሱን የቻለ
ወይም ሌላ ንብረትን ከማስተላለፍ የተለየ በመሆኑ በፍርድ ቤት Eንዲፀድቅ መደረጉ ተገቢ ነው። ምክንያቱም
12
በሌላ በኩል ባለይዞታው መሬቱን በኑዛዜ ሳያወርስ የሞተ ወይም የሰጠው ኑዛዜ ፈራሽ ሆኖ የተገኘ
Eንደሆነ መብቱ Eንደ ቅደምተከተላቸው በግብርና ሥራ ለሚተዳደር ወይም በዚሁ ሙያ መተዳደር
ለሚፈልግ የሟች ልጆች፣ ወላጅ/ጆች ወይም ሕግ ለሚፈቅድለት ለማንኛውም ሌላ የቤተሰቡ Aባል
Eንደሚተላለፍ Aንቀጽ 17(5) ይደነግጋል፡፡ የሟች ልጆች ወይም ከልጆቹ Aንዱ ቀድመዉ ሞተዉ
ወይም ሞቶ Eንደሆነ Eና ወደታች የሚቂጠሩ ተወላጆችን ትተዉ/ትቶ Eንደሆነ Eነዚሁ ተወላጆቻቸዉ
ቀድመዉ በሞቱት ልጆች ምትክ ሆነዉ Eንዲወርሱ ይደረጋል፡፡42

ከዚህ Aንጻር Aዲሱ Aዋጅ ቢያንስ ሶስት መሰረታዊ መሻሻሎችን Aድርጓል፡፡ የመጀመሪያው የኑዛዜ
Aደራረግ ፎርም በፍትሐ ብሔር ሕጉ የተደነገጉትን ጥብቅ መስፈርቶች Eንዲከተል ማድረጉ ነው፡፡
ይህም ከኑዛዜ ጋር ተያይዞ የነበሩ የፎርማሊቲ ውዝግቦችን በማጥፋት ረገድ የራሱ ሚና ይኖረዋል፡፡
ሁለተኛው መሻሻል ልጆች ቅድሚያ የመውረስ መብት መስጠቱ ነው፡፡ ይህም ቀደም ሲል የቤተሰብ
Aባል ከልጆችም ቀድሞ የሚወርስበት Aሠራር ስለነበር ፍትሐዊነትን ከማስፈኑም በላይ የውሸት
የቤተሰብ Aባል ነን Eያሉ ሲወርሱ የነበሩ ሰዎች በመኖራቸው በዚህ የተነሳም የሟች ልጆች ላይ ይደርስ
የነበረውን ችግር ያስወግዳል፡፡ ሶስተኛው ማሻሻያ ምትክ ወራሽነትን ማካተቱ ነው፡፡ ይኸውም ከመሬት
ባለይዞታው ልጆች መካከል ከባለይዞታው ቀድሞ የሞተ ልጅ ቢኖርና ልጆች ወልዶ ከሞተ የዚህ ቀድሞ
የሞተ ሰው ልጆች በሟች Aባታቸው ተተክተው የAያታቸውን መሬት የመውረስ መብት ይኖራቸዋል፡፡43

3.5 የይዞታ መሬትን Aስይዞ ገንዘብ መበደር መፈቀዱ


ማንኛውም የገጠር መሬት ባለይዞታ በዚህ Aዋጅ ከተፈቀደው ከ30 ዓመት ላልበለጠ ጊዜ የመጠቀም
መብቱን በሀገሪቱ ብሔራዊ ባንክ Eውቅና ለተሰጠው ሕጋዊ የገንዘብ ተቋም የብድር ዋስትና Aድርጎ
ሊያስይዝ Eንደሚችል Aንቀጽ 19(1) ይደነግጋል፡፡ ተበዳሪው በብድር ውሉ ውስጥ በተጠቀሰው የጊዜ
ገደብ Eዳውን ያልከፈለ Eንደሆነ Aበዳሪው በብድር ውሉ ለተጠቀሰው ጊዜ በመሬቱ የመጠቀም መብት
የሚኖረው ሆኖ የተገኘ Eንደሆነ የዚሁ መብቱ ወሰን በመሬቱ ላይ ከተሰጠው የመጠቀም መብት ያለፈ
ሊሆን Aይችልም፡፡44 Aበዳሪው መሬቱን ራሱ የማያለማው ሆኖ ለሶስተኛ ወገን የሚያከራየው ከሆነ Eና
መሬቱን ከAበዳሪው በውል ለመውሰድ Eስከ ተስማማ ድረስ ተበዳሪው ቅድሚያ ይሰጠዋል፡፡45

ፍርድ ቤቱ ሲያፀድቅ ኑዛዜ የተደረገለት ሰው በሕግ የተፈቀደለት ሰው መሆን Aለመሆኑን Aረጋግጦ ስለሚሆን
የሕጉን ዓላማ ለማሳካት ይጠቅማል የሚል ነው፡፡ ሁለተኛው Aተያየት ደግሞ Aዋጁና ደንቡ የመሬት ኑዛዜ
ፎርማሊቲዎችን ያላስቀመጡ ስለሆነ የገጠር መሬት ኑዛዜ ፎርማሊቲዎች መታየት ያለባቸው ከፍትሐ ብሔር
ሕጉ የኑዛዜ ድንጋጌዎች Aንጻር መሆን Aለበት። በAዋጅና በደንብ ያልተደነገገን ግዴታ መመሪያ ሊደነግግ
Aይችልም የሚል ነው፡፡ በሪሁን Aዱኛ ምሕረቱ “የገጠር መሬት ይዞታን የሚመለከቱ ውሎች᎓- ፎርም፣ ምዝገባና
ሕጋዊ ውጤቱ በAማራ ክልል” የAማራ ክልል የፍትሕ ባለሙያዎች ማሰልጠኛና የሕግ ምርምር Iንስቲትዩት
የሕግ መጽሔት ቅጽ 2፣ ቁጥር 1፣ (2007 ዓ/ም) ገጽ 190-192 ይመለከቷል፡፡
42
Aንቀጽ 17(6)
43
በፍትሐ ብሔር ሕጉ ቁጥር 842(3) ላይ የተደነገገው መብት ለገጠር መሬት ውርስም ተግባራዊ Eንዲሆን
በAዲሱ Aዋጅ መካተቱን መገንዘብ ይገባል፡፡
44
Aንቀጽ 19(2)
45
Aንቀጽ 19(3)
13
Aርሶ Aደሮች መሬታቸውን በዋስትና Aስይዘው የመበደር መብት በAዲሱ Aዋጅ የተካተተ Aዲስ መብት
ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ መቀመጡ መሬት ለAርሶ Aደሩ የበለጠ Iኮኖሚያዊ ጠቀሜታው Eንዲጎላ Eና
መሬታቸውን መያዣ በማድረግ ብድር በመውሰድ ወደ ተሻለ ምርታማነት Eና የኑሮ ደረጃ Eንዲቀየሩ
የሚያግዝ ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ይህ መብት በፌደራል የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ረቂቅ
Aዋጅ Aንቀጽ 16 ላይም ተደንግጓል፡፡ የዚህ ረቂቅ Aዋጅ ሀተታ ዘምክንያት Eንደሚያሳየው Aበዳሪዎች
ግለሰቦችም ሊሆኑ Eንደሚችሉ የተገለጠ ቢሆንም Aዲሱ የክልላችን Aዋጅ Eና ማስፈጸሚያ ደንብ ቁጥር
159/2010 Aንቀጽ 9 ግን Aበዳሪዎች ብሔራዊ ባንክ Eውቅና የሰጣቸው የፋይናንስ ተቋማት ብቻ
መሆናቸውን ይደነግጋሉ፡፡46

መሬትን Aስይዞ የመበደር መብት በፍትሐ ብሔር ሕጉ ከተቀመጡት የመያዣ ድንጋጌዎች Aንጻር
ልዩነት Aለው፡፡ ይኸውም በፍትሐ ብሔር ሕጉ የተደነገገው የመያዣ ጽንሰ ሀሳብ ተበዳሪው ብድሩን
መክፈል ካልቻለ መያዣውን ለዘለቄታው ለAበዳሪው ለማስረከብ ሊስማማ ይችላል፤ ካልሆነም መያዣው
ተሸጦ Eዳው ይከፈላል፡፡47 የይዞታ መሬቱን መያዣ Aድርጎ የተበደረ ሰው ግን ብድሩን መመለስ ካልቻለ
ተበዳሪው የቀረበት የብድር ገንዘብ Eስከሚያልቅ ብቻ የኪራይ ውጤት ባለው መልኩ መሬቱን
በጊዜያዊነት ለAበዳሪው Aስረክቦ Eንዲቆይ ነው የሚገደደው፡፡

3.6 ይዞታ ለህዝብ Aገልግሎት ሲወሰድ የመልሶ ማቋቋም ሥራ ግዴታ ሆኖ መቀመጡ


ከሕገ መንግስቱ ጀምሮ ቀደም ሲል የነበሩ ሕጎች ባለይዞታዎች ይዞታቸውን ለህዝብ ጥቅም ሲለቁ
በቅድሚያ ተመጣጣኝ ካሳ ሊከፈላቸው Eንደሚገባ ከመደንገግ ባለፈ ተነሽዎችን መልሶ ስለማቋቋም
የሚሉት ነገር Aልነበረም፡፡ ሆኖም በተግባር የቱንም ያክል ካሳ ቢከፈል መልሶ የማቋቋም ሥራ
ካልተሰራ በተነሽዎች ላይ Eያጋጠመ ያለውን ችግር በመገንዘብ Aዋጅ ቁጥር 252/2009 Eንቀጽ 26(1)
በቅድሚያ ካሳ ከመክፈል ግዴታ በተጨማሪ ተነሽዎች በዘላቂነት የሚቋቋሙበትን Aማራጭ ማመቻቸት
ለAስተዳደሩ Eንደ ግዴታ ሆኖ ተደንግጓል፡፡

መልሶ ማቋቋም ማለት በሕግ መሰረት ካሳ ተከፍሏቸዉ የመሬት ይዞታቸዉ ለሕዝብ Aገልግሎት ሲባል
ከመወሰዱ የተነሳ የተፈናቀሉ ባለይዞታዎች ቀደም ሲል የነበራቸዉን ማኅበራዊና Iኮኖሚያዊ
ተጠቃሚነት ለማስቀጠል ወይም ለማሻሻል በክልሉ መንግስት የሚከናወን ተግባር መሆኑን የAዋጁ
Aንቀጽ 2(42) ትርጉም ሰጥቶታል፡፡ በዚህ Aዋጅ መሰረት በልማት ምክንያት ከመሬታቸው የሚፈናቀሉ

46
ይህ ሁኔታ በክልላችን Aዋጅ Eና በፌደራሉ ረቂቅ Aዋጅ መካከል ያለ Aንድ መሰረታዊ ልዩነት ነው፡፡ በረቂቅ
Aዋጁ መያዣው የሚቆይበት ከፍተኛው ጊዜ 15 ዓመት ቢሆንም የክልላችን Aዋጅ ግን የጊዜ ገደቡን 30 ዓመት
ማድረጉ ሌላ ልዩነት ነው፡፡ ሶስተኛው ልዩነት Aበዳሪው መሬቱን በማከራየት ወይም ራሱ በማልማት በውሉ
ውስጥ ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት ቀሪውን Eዳ ማግኘት ከቻለ በውሉ ከተጠቀሰው ጊዜ በፊት በመሬቱ የመጠቀም
መብቱ የሚቋረጥ መሆኑ ደንብ ቁጥር 159/2010፣ Aንቀጽ 9(5) መደንገጉ ነው፡፡ ረቂቅ Aዋጁ ግን Aበዳሪው
የፈለገውን ያህል ከቀሪው የብድር ገንዘብ በላይ ቢያመርትበት ጊዜ ገደቡ ከማለቁ በፊት መሬቱ የማይመለስ
መሆኑን ይጠቁማል፡፡
47
የፍ/ሕ/ቁ 3060(2) Eና 3061
14
ባለ ይዞታዎች ፍላጎታቸው Eየታየ በሚነደፉ የመልሶ ማቋቋሚያ ፕሮጀክቶች Eንዲታቀፉ ይደረጋል፡፡48
ዝርዝር የመልሶ ማቋቋም ተግባራት Eንዴት መሰራት Eንዳለባቸው ደግሞ በደንብ ቁጥር 159/2010
Aንቀጽ 15 ላይ ተደንግዋል፡፡49 ይኸውም Aግባብ ያለው የወረዳ Aስተዳደር ጽ/ቤት የገጠርን መሬት
ለህዝብ Aገልግሎት ለማዋል Aስፈላጊ ሆኖ ያገኘው Eንደሆነ ተገቢውን ካሳ በቅድሚያ በመክፈልና
ተፈናቃዩ በዘላቂነት የሚቋቋምባቸውን የተለያዩ Aማራጮች ከወዲሁ በማመቻቸት ማንኛውንም የመሬት
ባለይዞታ ወይም ተጠቃሚ ማስለቀቅ ይችላል፡፡ ሆኖም Eርምጃው ተግባራዊ የሚደረገው ለባለመብቶች
በቅድሚያ ተገቢው የቦታ Aቅርቦት መሟላቱ ከተረጋገጠ በኋላ ይሆናል፡፡50 በየትኛውም ከተማ የፕላንና
Aስተዳደር ወሰን ክልል ውስጥ ለሚኖሩ ባለይዞታዎች ትክ የመኖሪያና የመስሪያ ቦታ ተለይቶ
Eንዲዘጋጅና ለተፈናቃዮች Eንዲቀርብ ይደረጋል፡፡51 ከከተማ Aስተዳደር ውጭ በህዝብ ጥቅም
Aስገዳጂነት ከሕጋዊ ይዞታቸው የሚነሱ የገጠር መሬት ባለይዞታዎች በሕጉ መሰረት Aማራጭ የሰፈራ
ቦታ፣ ትክ የEርሻና የግጦሽ መሬት Eንዲያገኙ ይደረጋል፡፡52

ዝርዝር የመልሶ ማቋቋም ትግባራትን በተመለከተም በልማት ምክንያት ከመሬታቸው የሚፈናቀሉ ህጋዊ
ባለይዞታዎች ይኸው መፈናቀል የሚያስከትልባቸው ጉዳት ከወዲሁ ታይቶ፡-53
 Eንደየፍላጎታቸው በተናጠልም ሆነ በጋራ በመደራጀት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተፈላጊው
ፕሮጀክት ተቀርጾላቸው ወደስራ Eንዲገቡ ይደረጋል፤
 በራሱ በክልሉ መንግሥትም ሆነ በAልሚ ባለሀብቶች Aማካኝነት የስራ Eድል በቅድሚያ
Eንዲፈጠርላቸውና ለስራ የደረሱ የቤተሰብ Aባሎቻቸውም በAካባቢው በሚካሄደው ልማት
ተጠቃሚዎች Eንዲሆኑ ተገቢው ክትትልና ድጋፍ ይደረግላቸዋል፤
 Eንዳስፈላጊነቱ የብድር Aገልግሎት ወይም ሌላ Aይነት ልዩ ድጋፍ ይመቻችላቸዋል፤
 የሚያቀርቧቸው ምርቶች በገበያ ረገድ ተወዳዳሪዎች Eንዲሆኑ በስልጠናና በግብይት Eሴት
ሰንሰለት ትስስር ፈጠራ ረገድ ተገቢው ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡

3.7 የገጠር መሬት Aጠቃቀም Eቅድ ማዘጋጀት Eንደሚገባ መደንገጉ


Aዲሱ Aዋጅ ካካተታቸው ቁምነገሮች ውስጥ Aንዱ የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ Eንዲዘጋጅ የሚያስገድድ
ድንጋጌዎችን መያዙ ነው፡፡54 በዚህ Aንቀጽ መሰረት የክልሉ የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ቢሮ

48
Aንቀጽ 26(9)
49
በEርግጥ ብዙም ሥራ ላይ ባይውልም በቅርቡ የAብክመ ለህዝብ ጥቅም ሲባል መሬታቸውን የሚለቁ የገጠር
ባለይዞታዎችን መልሶ ለማቋቋም Eና ይዞታቸውን ለማስተዳደር የወጣ መመሪያ ቁጥር 26/2008 የነበረ መሆኑን
መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡
50
ደንብ ቁጥር 159/2010 Aንቀጽ 15(1)
51
Aንቀጽ 15(2)፤ በከተማ የፕላን ወሰንም ሆነ በገጠር ቀበሌ ማEከላት ውስጥ በግል ይዞታቸው ላይ የመኖሪያ
ቤት ወይም የንግድ ድርጅት የመገንባት ፍላጎታቸውን የገለጹ Eንደሆነ ተቋቋሚዎች ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡
Aንቀጽ 15(3)
52
Aንቀጽ 15(4)
53
Aንቀጽ 15(5)
15
Aገር Aቀፉን የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ መነሻ በማድረግ ወይም ከራሱ ነባራዊ ሁኔታዎች በመነሳት
በክልሉ ውስጥ የሚተገበር መሪ የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ ያዘጋጃል፡፡ የዞን ገጠር መሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም መምሪያዎች የክልሉን የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ መሠረት በማድረግ በዞኑ ነባራዊ ሁኔታ
የሚተገበር የራሳቸውን መሪ የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ ያዘጋጃሉ፡፡ የወረዳ መሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም ጽ/ቤቶችም የዞናቸውን የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ መሰረት በማድረግ Eንደ ወረዳቸው ነባራዊ
ሁኔታ የሚተገበር የራሳቸውን መሪ የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ ያዘጋጃሉ፡፡ Eንዲሁም Aካባቢያዊ
የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ ቀበሌን ወይም ተፋሰስን መሰረት ያደረገና ነዋሪውን ሕብረተሰብ ያሳተፈ ሆኖ
በወረዳ ገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት የቴክኒክ ድጋፍ ይዘጋጃል፡፡

የትኛውም የገጠር መሬት ለAንድ ለተወሰነ Aገልግሎት Eንዲውል የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ ሲዘጋጅ
የተሻለ የIኮኖሚ ጠቀሜታ የሚሰጥ መሆኑ፣ በAካባቢ ላይ የሚያስከትለው ተጽEኖ Aለመኖሩ ወይም
ተጽEኖው Aነስተኛ ሆኖ መገኘቱ Eና Aገልግሎቱ በተጠቃሚዎች ዘንድ ተቀባይነት ያለው መሆኑ
Eየተረጋገጠ መሆን ይኖርበታል።55 በጥናት ላይ ተመስርቶ ካልሆነ በስተቀር በማናቸውም የገጠር
መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለ ወቅታዊ የAጠቃቀም Eቅድ በዘፈቀደ Aይቀየርም፡፡56
በክልል፣ በዞንም ሆነ በወረዳ ደረጃ የሚዘጋጁ መሪ የገጠር መሬት Aጠቃቀም Eቅዶች Eንደተገቢነቱ
Aገር-Aቀፉን Eቅድ ወይም የAስተዳደር Eርከኑን Eቅዶች ታሳቢ በማድረግ ከ10 Eስከ 15 ዓመት
በሚሆን ጊዜ ውስጥ ወቅታዊ መደረግ ይኖርባቸዋል፡፡57

Aዲሱ Aዋጅ የገጠር መሬት በEቅድ Eንዲመራ ለማድረግ ትኩረት ከሰጠባቸው ሁኔታዎች Aንዱ ለገጠር
ቀበሌ ማEከላት መገንቢያ ቦታ Aመራረጥ Eና Aሰጣጥ ጉዳይ ነው፡፡ በAዋጁ Aንቀጽ 31 Eንደተደነገገው
በክልሉ በሚገኙ በሁሉም የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ የቀበሌ ማEከላት Eንዲኖሩ ይደረጋል፡፡ በገጠር ቀበሌ
ማEከላት ውስጥ የሚተገበረው የመኖሪያ ቤት ግንባታ ቦታ Aሰጣጥ ስርዓትና ግንባታው የሚያሟላቸው
ስታንዳርዶች በደንብ የሚወሰን ሆኖ Eድሜው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆነና በቀበሌው ውስጥ ቢያንስ
ለተከታታይ ሁለት ዓመት ነዋሪ ሆኖ በግብርና፣ በንግድ ወይም በሌሎች በማናቸውም መንግስታዊና

54
Aንቀጽ 29(1-6)፤ በAንቀጽ 2(4) ትርጉም መሰረት "የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ" ማለት Aካላዊ፣ Iኮኖሚያዊና
ማኅበራዊ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ የገጠር መሬት ሊሰጥ ከሚችለው የተለያዩ የመሬት Aጠቃቀም
Aማራጮች መካከል የመሬት መጎሳቆልንና የAካባቢን ብክለት ሳያስከትሉ ከፍተኛ Iኮኖሚያዊ ጠቀሜታ
የሚያስገኙት Aማራጮች ተወዳድረው የሚወሰኑበትና ተግባራዊ የሚደረጉበት የAሠራር ዘዴ ነው፡፡
55
Aንቀጽ 29(7)
56
Aንቀጽ 32(1)፤ ሆኖም ይህ ድንጋጌ ተዳፋትነታቸዉ ከ50% በላይ የሆኑ የመሬት ይዞታዎች ወደ ቋሚ ተክሎች
ማልሚያነት ከማሸጋገር የሚከለክል Aይሆንም::
57
Aንቀጽ 30፤ በAካባቢ ደረጃ የሚዘጋጅ Aሳታፊ የገጠር መሬት Aጠቃቀም Eቅድ EንደAስፈላጊነቱ የሚከለስበትና
ወቅታዊ የሚደረግበት ጊዜ ገደብ በደንብ ይወሰናል፡፡
16
መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች የሚሠራ ማንኛውም ሰው በገጠር ቀበሌ ማEከላት ውስጥ የመኖሪያ ቤት
መሥሪያ ቦታ ያገኛል፡፡58

በገጠር ቀበሌ ማEከላት ውስጥ የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች ቢሮው ለገጠር ቤቶች Aሠራር የሚያወጣውን
የዲዛይንና የግንባታ ጥራት መስፈርቶች Aሟልተው ስለመገኘታቸው በወረዳ ገጠር መሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም ጽ/ቤት ካልተረጋገጠ በስተቀር ሊሸጡ፣ የEዳ ዋስትና ሆነው ሊያዙም ሆነ በማናቸውም
መንገድ ለሶስተኛ ወገን ሊተላለፉ Aይችሉም፡፡59 Eንዲሁም የገጠር ቀበሌ ማEከላት ተብለው
ከተመረጡት ስፍራዎች ውጭ በEርሻ፣ በግጦሽ፣ በወል Eና በደን መሬቶች ላይ ማናቸውንም Aይነት
Aዲስ ግንባታ ማካሄድ የተከለከለ ነው::60 ሆኖም የመሬት Aጠቃቀም Eቅድ ተዘጋጅቶ ባልተሰጠበት
Aካባቢ Aርሶ Aደሩ በመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተሩ ላይ ባስመዘገበው የይዞታ መሬቱ ውስጥ ለራሱና
ለAካለመጠን ለደረሱ ልጆቹ በሚበቃ መጠን የመኖሪያ ቤት ከመገንባት Aይታገድም፡፡61

3.8 የገጠር መሬት መረጃ Aያያዝ ዘመናዊ Eንዲሁን መታሰቡ


Aዲሱ Aዋጅ ከቀድሞው በጠነከረ ሁኔታ በግል ይዞታነት፣ በወል ወይም በመንግስት የተያዘ፣ ለደን
ልማት ወይም ለሌሎች መሰል ተግባራት የተከለለ የትኛውም የገጠር መሬት በባህላዊ መንገድ ወይም
በዘመናዊ መሳሪያ ተለክቶ የባለይዞታዎችን የይዞታ መጠንና Aዋሳኝ ድንበሮች የሚያሳይ ካርታ
ተዘጋጅቶ ይህንኑ ከሚያረጋግጥ ደብተር ጋር Eንደሚሰጣቸው ይደነግጋል፡፡62 የትኛውም መሬት
በሚለካበት ጊዜ በተቻለ መጠን የመሬቱ Aዋሳኝ ባለይዞታዎች ወይም ተወካዮቻቸው በስፍራው
ተገኝተው ድንበሮቻቸውን Eንዲያሳዩ ጥሪ ይደረግላቸዋል፡፡63 መሬቱ ከተለካ በኋላ መጠኑ በተለያዩ
ምክንያቶች ተለውጦ የተገኘ Eንደሆነ Eንደገና ተለክቶ Aዲስ ካርታ ይዘጋጅለታል፡፡

በዚህ መልኩ Aግባብ ባለው የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም Aካል ኃላፊነት የተለካ ማናቸውም
የገጠር መሬት ይዞታ ለዚሁ ዓላማ በተቋቋመው የመሬት መዝገብ ውስጥ ይመዘገባል፡፡ ምዝገባውም
የመሬቱን ባለይዞታ ሙሉ ስም፣ ይዞታው የተገኘበትን ሁኔታ፣ የመሬቱን Aዋሳኞች፣ የለምነቱን ደረጃ፣
መሬቱ የሚውልበትን Aገልግሎትና ባለይዞታው ያሉበትን ግዴታዎች የሚገልጽ መረጃ Aካቶ መያዝ
ይኖርበታል፡፡64 የገጠር መሬት ምዝገባ መረጃ ባሕረ-መዝገብ በሁለት ቅጅ ተዘጋጅቶ Aንደኛው ቅጂ

58
Aንቀጽ 31(5)፤ ሆኖም ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ሕፃናት፣ Aካል ጉዳተኞች፣ Aቅመ ደካሞች፣ ሴቶችና
Aረጋውያን Eንደ ቅደም ተከተላቸው በማEከላቱ ውስጥ የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ በቅድሚያ የማግኘት መብት
ይኖራቸዋል፡፡
59
Aንቀጽ 31(5)
60
Aንቀጽ 32(1)
61
Aንቀጽ 32(2)
62
Aንቀጽ 33(1) - (3)
63
Aንቀጽ 33(4)፤ በመሬቱ Aለካክና በድንበሩ Aከላለል ረገድ ቅሬታ የተሰማው ማንኛውም ባለይዞታ ቅር
የተሰኘበትን ምክንያት በዝርዝር በመግለጽ ልኬታው በተጠናቀቀ 30 ቀናት ውስጥ ጉዳዩ Eንደገና ይታይለት ዘንድ
በየደረጃው ለሚገኘው የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም Aካል የማቅረብ መብት Aለው፡፡
64
Aንቀጽ 34(1)(2)
17
በሚመለከተው ቀበሌ ጽ/ቤትና ሁለተኛው ቅጅ ደግሞ ቀበሌው በሚታቀፍበት ወረዳ ገጠር መሬት
Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት ይቀመጣሉ፡፡65

በሀሰተኛ መረጃ ላይ ተመስርቶ የተካሄደ ማናቸውም ምዝገባ ሕጋዊ ውጤት Aይኖረውም፡፡ በመዝጋቢው
ስህተት ምክንያት በማንኛውም ሰው ላይ ጉዳት የደረሰ Eንደሆነ ስህተቱን የፈጠረው የመንግሥት Aካል
በፍትሐ ብሔር Eና በወንጀል ኃላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡66 Aስመዝጋቢዉም ቢሆን በምዝገባዉ
ለተፈጠረው ስህተት የራሱ AስተዋፅO Eንደነበረው የተረጋገጠ ከሆነ በፍትሐ ብሔርና ተገቢ ሆኖ
ሲገኝም በወንጀል ሕግጋት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

የገጠር መሬት ባለይዞታ ወይም የማሳ ወይም የሁለቱም ለውጥ በሚያጋጥምበት ጊዜ የመሬት ምዝገባ
ሰነዱም ወቅታዊ መደረግ ይኖርበታል፡፡ የምዝገባ መረጃውን ወቅታዊ የማድረጉ ተግባር በቀበሌ Eና
በወረዳ የመሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ኮሚቴዎች Aማካኝነት ይከናወናል፡፡ ለሚመለከተው Aካል
በጊዜው ቀርቦ ወቅታዊ ያልተደረገ ማናቸውም የገጠር መሬት የምዝገባ መረጃ ለውጥ ወይም ማሻሻያ
በሕግ ፊት ውጤት Aይኖረውም፡፡67 Eንዲሁም ከመሬቱ ጋር ተያያዥነት ያለውን መብትና ግዴታ
የሚመለከት ማናቸውም ጉዳይ መሬቱ በሚገኝበት ወረዳ ላለው የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም
ጽ/ቤት ቀርቦ ካልተመዘገበ በስተቀር በሶስተኛ ወገኖች ላይ መቃወሚያ ሆኖ ሊቀርብባቸው Aይችልም፡፡68

የገጠር መሬት ባለይዞታ የሆነ ማንኛውም ሰው የመሬቱ ዝርዝር የተመዘገበበት Eና በሕግ የተደነገጉ
ዋና ዋና መብቶችና ግዴታዎች የሚያሳይ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር በስሙ ተዘጋጅቶ Eና ፎቶግራፍ
ተለጥፎበት ይሰጠዋል፡፡69 የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር የባለይዞታው በሕግ የተጠበቀ መብት ማስረጃ
ነው፡፡ ይህንኑ የሚቃረን ጠንካራ የጽሑፍ ማስረጃ Eና ይበልጥ የሚያሳምን ምክንያት ካልቀረበ በስተቀር
የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር በስሙ ተዘጋጅቶ የተሰጠው ማንኛውም ሰው የመሬቱ ሕጋዊ ባለይዞታ
Eንደሆነ ይቆጠራል፡፡ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር Eያለ ዳኞች ሌሎችን የሰነድም ሆነ የሰው
ማስረጃዎችን ቅድሚያ ሰጥተው ሊቀበሉና ሊመለከቱ Aይችሉም፡፡70

Aዲሱ Aዋጅ በዚህ መልኩ የመሬት ይዞታ በAግባቡ ተለክቶ ካርታና ደብተር ተዘጋጅቶለት Eንዲያዝ
መደረጉ የባለይዞታዎችን የይዞታ ዋስትና ከማጠናከሩም በላይ ክርክሮች ሲኖሩ በቀላሉ ፍትሐዊ ውሳኔ
ለመስጠት የሚያስችሉ የሰነድ ማስረጃዎችን Eዲቀርቡ ያስችላል ብሎ መደምደም ይቻላል፡፡

65
Aንቀጽ 42(1)፤ በሁለቱ የባሕረ-መዝገብ ቅጂዎች መካከል ልዩነት ተፈጥሮ የተገኘ Eንደሆነ መረጃዉ Eንደገና
Eንዲጣራና Eንዲስተካከል ይደረጋል፡፡
66
Aንቀጽ 34(5)(6)
67
Aንቀጽ 43(1)፣(2) Eና (6)
68
Aንቀጽ 34(3)
69
Aንቀጽ 35(1) Eና (6)፤ የወል መሬት ተጠቃሚዎች የሆኑ ባለይዞታዎች ይህንኑ የሚያመለክት የመሬት ይዞታ
ማረጋገጫ ደብተር በስማቸው ተዘጋጅቶ ይሰጣቸዋል፡፡ የገጠር መሬት ባለይዞታ የሆኑ ተቋማትም ይዞታ
ማረጋገጫ ደብተር በስማቸው ተዘጋጅቶ ይሰጣቸዋል፡፡
70
Aንቀጽ 35(2) Eና (5)
18
3.9 በበርካታ ጉዳዮች ላይ ትርጉም በመስጠት ቀደም ሲል የነበሩትን የግልጽነት ችግሮች መቅረፉ
Aዲሱ Aዋጅ ከቀድሞው Aዋጅ በተሻለ ሁኔታ በርካታ ጉዳዮች ላይ በትርጉም ክፍሉ ግልጽ ትርጉም
መስጠቱ በAሠራር ያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን ይቀርፋል፡፡ ለምሳሌ በቀድሞው Aዋጅ Aስተዳደራዊ
ዉሳኔ ማለት ምን ማለት Eንደሆነ ትርጉም ባለመሰጠቱ ቀደም ሲል Aስተዳደራዊ ውሳኔ የሚሹ Eና
በፍርድ ቤት ሊወሰኑ የሚገባቸውን ጉዳዮች በመለየት ረገድ ሲያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት
ያስችላል፡፡ በAዲሱ Aዋጅ Aስተዳደራዊ ዉሳኔ ማለት Aንድ ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ባለጉዳዮች፣
በይዞታ መብትና መጠቀም ጥያቄ ሲያቀርቡ ወይም በተቃራኒው ግዴታወቻቸውን ሳይወጡ ሲቀሩ
Aግባብነት ያላቸዉን የመረጃ ምንጮች በመጠቀምና Aስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም በሕዝብ በማስተቸት ጉዳዩ
በሚመለከተው የመሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም Aካል ከተጣራ በኃላ በጽሁፍ የሚሰጥ ማናቸውም
ውሳኔ ሲሆን ከገጠር መሬት ልኬታ፣ ምዝገባ፣ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር Aሰጣጥ፣ ከመሬት
Aጠቃቀም Eቅድ፣ ከይዞታ መታጣት Eና ከሌሎች ተዛማጅ Eርምጃዎች ጋር በተገናኘ የሚተላለፉ
ትዛዞችን ያጠቃልላል በማለት የAዋጁ Aንቀጽ 2(44) ግልጽ ትርጉም ይሰጠዋል፡፡

ሌላ ምሳሌ ብንወስድ በቀድሞው Aዋጅ "የገጠር መሬት" ማለት ስልጣን ያለው Aካል ከተማ ብሎ
ከከለለው ውጭ የሚገኝ መሬት ነው በሚል ትርጉም በመስጠቱ በከተማ ክልል ውስጥ የሚገኙ የገጠር
ቀበሌዎች ላይ የሚነሱ የገጠር መሬት ክርክሮች በተለይ የከተማ ነክ ጉዳዩች ፍርድ ቤት
በተቋቋመባቸው ከተሞች ዙሪያ የመሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም Aካላት ተከራካሪ ሲሆን የሥረ ነገር
ስልጣን ያለው የከተማ ነክ ጉዳዮች ፍርድ ቤት ነው ወይስ መደበኛ ፍርድ ቤት የሚለው ብዙ ፍርድ
ቤቶችን ያወዛግብ ነበር፡፡ Aዲሱ Aዋጅ ግን "የገጠር መሬት" ማለት በገጠር የAስተዳደር ወሰን
የተጠቃለሉ የገጠር መሬት ይዞታዎችን Eና በከተሞች የAስተዳደርና የፕላን ወሰን ክልል ውስጥ ያለ
ማንኛውም የገጠር መሬት ነው በማለት ግልጽ ትርጉም በመስጠቱ የነበረውን ችግር ይቀርፋል፡፡

4. በAዲሱ Aዋጅ ላይ የሚታዩ ዋና ዋና ችግሮች


ከላይ በክፍል 3 ሥር ለማንሳት Eንደተሞከረው Aዲሱ Aዋጅ በርካታ በጎ ጎኖችን Aካቶ የወጣ ቢሆንም
ተገቢው ትኩረት ተሰጥቶት በቂ የባለሙያ Aስተያየቶችን ባለማካተቱ ወይም ለማካተት ባለመፈለግ Eና
በችኮላ በመታወጁ በርካታ ችግሮችንም ይዞ ወጥቷል፡፡ ከEነዚህም ዋና ዋናዎቹን Eንደሚከተለው
ለማቅረብ ተሞክሯል፡፡

4.1 የገጠር መሬት ይዞታ በነፃ ከማግኘት የEኩልነት መብት ጋር የተያያዙ ችግሮች
የIትዮጵያ Aርሶ Aደሮች ለግጦሽም ሆነ ለEርሻ Aገልግሎት የሚጠቀሙበት መሬት በነፃ የማግኘት
መብት ያላቸው መሆኑን የIፌዴሪ ሕገ መንግስት Aንቀጽ 40(4) Eና (5) ይደነግጋል፡፡ ይህን ሕገ
መንግስት ተከትሎ በፌደራል መንግስቱ የወጣው Aዋጅ ቁጥር 456/97 Aንቀጽ 5(1)(ሀ) በግብርና ሥራ
ለሚተዳደሩ Aርሶ Aደሮች የገጠር መሬት በነፃ Eንዲያገኙ Eንደሚደረግ ይደነግጋል፡፡

19
ይሁን Eንጅ የAማራ ክልል የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም Aዋጅ ቁጥር 252/2009 የገጠር
መሬትን በነፃ በማግኘት ረገድ Aላስፈላጊ ማዳላትን የሚፈጥሩ በርካታ ድንጋጌዎችን Aካቷል፡፡
የመጀመሪያው ሴቶችን በተመለከተ ያለAግባብ የገጠር መሬት ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ነው፡፡ የሕገ
መንግስቱ Aንቀጽ 35(7) ሴቶች ንብረት የማፍራት፣ የማስተዳደር፣ የመቆጣጠርና የማስተላለፍ መብት
ያላቸው መሆኑን ሲደነግግ በተለይ መሬትን በመጠቀም፣ በማስተላለፍ፣ በማስተዳደርና በመቆጣጠር
ረገድ ከወንዶች ጋር Eኩል መብት ያላቸው መሆኑን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይደነግጋል፡፡ የAዋጅ ቁጥር
456/97 Aንቀጽ 5(1)(ሐ) ድንጋጌ ከላይ ፊደል “ሀ” ላይ ሁሉም Aርሶ Aደሮች የገጠር መሬት በነጻ
Eንደሚያገኙ ካስቀመጠው ድንጋጌ በተጨማሪ በግብርና ሥራ መሰማራት የሚፈልጉ ሴቶች የገጠር
መሬት የማግኘትና የመጠቀም መብት ያላቸው መሆኑን ይደነግጋል፡፡ የሕገ መንግስቱም ሆነ የዚህ
Aዋጅ ድንጋጌዎች ዓላማ ቀደም ባሉት ዘመናት በሀገራችን ከነበረው ሴቶችን ከወንዶች Aንፃር Eኩል
ያለማየት ችግር ለመቅረፍ ሴቶች ከወንዶች ጋር Eኩል የመሬት ባለይዞታ Eንዲሆኑ ማረጋገጥ ነው፡፡71

ከዚህ Aንጻር የክልላችን Aዋጅ ከሕገ መንግስቱ Eና ከፌዴራል የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም
Aዋጅ ባፈነገጠ መልኩ ሴቶች ከወንዶች በፊት መሬት Eንዲያገኙ የሚያደርጉ በርካታ Aላስፈላጊ
የማዳላት ድጋጌዎችን Aካቷል፡፡ ይኸውም በመርህ ደረጃ Aዋጅ ቁጥር 252/2009 Aንቀጽ 5(2) በክልሉ
ውስጥ የሚኖር ማንኛውም Aርሶ Aደር በፆታም ሆነ በሌላ ማናቸውም ምክንያት ልዩነት ሳይደረግበት
የገጠር መሬት ይዞታ በነፃ የማግኘት Eኩል መብት ያለው መሆኑን ቢደነግግም Aንቀጽ 5(6) ላይ ደግሞ
የገጠር መሬት ድልድል በሚካሄድበት ጊዜ ወላጆቻቸውን ላጡ ህፃናት፣ ለAካል ጉዳተኞች፣ ለAቅመ
ደካሞችች ለሴቶችና Aረጋዊያን ቅድሚያ Eንዲሰጥ የሚያደርግ የAሠራር ስርዓት ተቀርፆ በሥራ ላይ
Eንደሚውል ይደነግጋል፡፡ የገጠር መሬት ስለማግኘት የሚደነግገው የAዋጅ Aንቀጽ 10(4)ም Eነዚህ
ወገኖች በግብርና ሥራ የሚተዳደሩ ወይም ለመተዳደር የመረጡ ሆነው ሳለ ለዚሁ የሚያስፈልገው
የEርሻ መሬት የሌላቸው ወይም ያነሳቸው Eንደሆነ ይህንኑ በማግኘት ረገድ የቀደምትነት መብት
ያላቸው መሆኑን ይደነግጋል፡፡ የAዋጅ Aንቀጽ 12(3)ም መሬትን የሚያስታድረው Aካል ያለው መሬት
ለሁሉም መሬት ጠያቂዎች መደረስ የማይችል ከሆነ ለEዚህ ወገኖች ብቻ የሚሰጥ መሆኑን
ይደነግጋል፡፡ Eንዲሁም በAንቀጽ 13(4) መሰረት በመስኖ መሬት ሽግሽግ ወቅት Eዚህ ወገኖች ቅድሚያ
ያገኛሉ፡፡ በገጠር ቀበሌ ማEከላት ውስጥ የመሬት Aሰጣጥና Aጠቃቀም ስለመወሰን የተደነገገው Aንቀጽ
31(6) Eነዚህ ከላይ የተዘረዘረሩ ወገኖች በማEከላቱ ውስጥ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ በቅድሚያ
የማግኘት መብት ያላቸው መሆኑት ይደነግጋል፡፡

Aዋጁን ለማስፈፀም የወጣው ደንብ ቁጥር 159/2010ም Aንቀጽ 4(2)፣ 6(9)፣ 23(2) ተመሳሳይ
ሁኔታዎችን ይደነግጋሉ፡፡ ከEነዚህ ድንጋጌዎች በAጠቃላይ የምንረዳው በሕገ መንግስቱ Eና በAዋጅ
ቁጥር 456/1997 ከተደነገገው የEኩልነት መብት ውጭ በማንኛውም ጊዜ በትርፍነት የተያዘ መሬት

በEርግጥ በሀገራችን ከAዋጅ ቁጥር 31/67 መውጣት ጀምሮ የሴቶችን ከወንዶች Eኩል መሬት የማግኘት መብት
71

ለማረጋገጥ ጥረት መደረጉም ሊዘነጋ Aይገባም፡፡


20
ሲገኝ በቅድሚያ ለEነዚህ ወገኖች ብቻ በመስጠት ሌሎች ዜጎች መሬት Eንዳያገኙ ማድረግ ሕጋዊም
ምክንያታዊም Aይደለም፡፡ ምክንያቱም በAንድ በኩል ሕገ መንግስቱም ሆነ የፌዴራሉ Aዋጅ ሴቶችም
ሆነ ሌሎች ከላይ የተዘረዘሩ ወገኖ መብታቸው ሳይጣስ Eኩል መሬት የማግኘት መብትን Aጎናፀፉ Eንጅ
የማዳላት ወይም ለEነዚህ ወገኖች ቅድሚያ የሚሰጥ ድንጋጌ Aላካተቱም፡፡ ወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናት፣
Aካል ጉዳተኞች፣ Aቅመ ደካሞ፣ ሴቶችና Aረጋዊያን ልዩ የመብት ጥበቃ የሚያስፈልጋቸው መሆኑ
Aከራካሪ Aይደለም፡፡ ልዩ የመብት ጥበቃ ሲባል ግን ለመብት ጥሰት ተጋላጭ ወገኖች (Vurnerable
group) ስለሆኑ በEኩልነት Eንዲስተናገዱ Eንጅ ለEነሱ የበለጠ መብት ለመስጠት Aይደለም፡፡ የህፃናት
መብትን የሚደነግገው የሕገ መንግስቱ Aንቀጽ 36(2) ማንኛውም ተቋም ህጻናትን የሚመለከት Eርምጃ
በሚወስድበት ጊዜ የህፃናት ደህንነት በቀደምትነት መታሰብ Aለበት በማለት የሚደነግገው ህጻናት
ያላግባብ Eዳይበደሉ Eንጅ ለEነሱ በማዳላት ሌላ ሰው ለመበደል Aይደለም፡፡

ውስን ሀብት የሆነው መሬት ከላይ ለተዘረዘሩት ወገኖች ብቻ ቅድሚያ በመስጠት ከEነዚህ ወገኖች
ውጭ ያለው Aምራች ሀይል የራሱን መሬት Eንዳያገኝ ማድረግ Aብዛኛውን ሰው በተለይ የገጠሩን
ወጣት ሥራ Aጥነት በማስፋፋት የራሱን Aሉታዊ ችግር ይፈጥራል፡፡ ከዚህ Aንፃር በሕገ መንግስት ላይ
ሳይደነገግና ለAዋጅ ቁጥር 252/2009 መወጣት የውክልና ስልጣን የሰጠው Aዋጅ ቁጥር 456/1997
ያላካተተውን ከEኩልነት መርህ ያፈነገጠና Aብዛኛውን ማህበረሰብ ተጎጅ የሚያደርጉ ድንጋጌዎችን
ማካተቱ ተገቢነት የለውም፡፡

በሌላ በኩል Aዋጅ ቁጥር 252/2009 ከላይ ከተዘረዘሩት Aካላት ውጭ ባሉ የገጠር መሬት ጠያቂዎች
መካከል ልዩነት መፍጠሩም ሌላ ችግር ነው፡፡ ይኸውም ደንብ ቁጥር 159/2010 Aንቀጽ 4(3) መሰረት
Eነዚህ ወገኖች በሌሉበት ጊዜ ወይም ቅድሚያ Aግኝተው ከተስተናገዱ በኋላ ትርፍ መሬት
መኖሩ የታወቀ Eንደሆነ ይኸው መሬት በህዝብ ተሳትፎ ለሚለዩ ሌሎች Aመልካቾች ከዚህ
በታች በተገለፀው ቅደምተከተል Eንዲሰጣቸው ይደረጋል፡-
ሀ. ጎጆ የወጣና ልጅ ያለው፤
ለ. ጎጆ የወጣና ልጅ የሌለው፤
ሐ. ያላገባ ወይም ጎጆ ያልወጣ ወጣት፤
መ. ያገባ ሆኖ በትዳር ጓደኛው ስም የተመዘገበ የጋራ ይዞታ ቢኖረውም የራሱ ይዞታ የሌለው፤
ሠ. በህግ ከተፈቀደው Aነስተኛ የመሬት ይዞታ በታች መሬት ያላቸው ባለይዞታዎች ይላል፡፡

በዚህ ድንጋጌ ውስጥም የEኩልነት መርህ ተጥሷል፡፡ ለምሳሌ በፊደል “ሀ” Eና “ለ” መካከል ያለው
ልዩነት የተፈጥሮን ሕግ ሳይቀር የሚቃረን ነው፡፡ ልጅ መውለድ የEግዚAብሔር ስጦታ Eንጅ ሰዎች
በራሳቸው ችሎታ ብቻ የሚያገኙት Aይደለም፡፡ ከዚህ Aንፃር ልጅ የወለደን ሰው ልጅ ከሌለው ሰው
ማስቀደም ማለት ልጅ መውለድ ባልቻሉ ሰዎች ላይ ተጨማሪ የሞራል ድቀት የሚያመጣና Aላስፈላጊ
ማዳላትን የሚፈጥር ነው፡፡ Eንዲሁም በፊደል “ሐ” የተቀመጠው ያላገባን ወይም ጎጆ ያልወጣን ወጣት

21
ከፊደል “ሀ” Eና “ለ” ቀጥሎ በ3ኛ ደረጃ መሬት Eንዲያገኝ ማድረግም ተገቢ ያልሆነ ልዩነት መፍጠር
ነው፡፡ ብዙ ወጣቶች ትዳር መስርተው ልጅ ከመውለዳቸው በፊት የEኔ የሚሉት ንብረት ኑሯቸው
ቤተሰብ ለመምራት በማሰብ ትዳር ሳይመሰርቱ ይቆያሉ፡፡ መበረታታትም ያለበት ሰው መተዳደሪያ
ሳይኖረው Aግብቶ Eንዳይወልድ Eና ራሱም ሆነ ቤተሰቡ ለችግር Eንዳይጋለጥ ነው፡፡ ከዚህ Aንፃር
ባገባና ባላገባ ሰው መካከል ልዩነት መፍጠር በAግባቡ ያልተጠና Eና በዘፈቀደ የተደነገገ ሕግ መሆኑን
ያሳያል፡፡ በሌላ Aገላለጽ ከሕገ መንግስቱ ጀምሮ የፌዴራል መንግስት Aዋጅ ቁጥር 456/1997
Eንዲሁም Aዋጅ ቁጥር 252/2009 Eድሜው 18 ዓመትና በላይ የሆነው በEርሻ የሚተዳደር ወይም
ለመተዳደር የፈለገ ሰው የገጠር መሬት በነፃ የሚያገኝ መሆኑን ይደነግጋሉ Eንጅ ያገባና ያላገባ፣ ልጅ
ያለውና የሌለው Eያሉ ልዩነት Aያደርጉም፡፡ ስለሆነም ይህ ሁኔታ ተገቢነት የሌለው ልዩነት ወይም
የEኩልነት መብትን የሚጥስ መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡

4.2 የውርስ ድንጋጌዎች የፍትሐዊነት ችግር መኖር Eና ተያያዥ ችግሮች


ውርስን በተመለከተ የAዋጅ ቁጥር 252/2009 Aንቀጽ 17(1) የገጠር መሬት ባለይዞታ የሆነ ማንኛውም
ሰው የይዞታም ሆነ የመጠቀም መብቶቹን በግብርና ሥራ ለሚተዳደር ወይም በዚሁ ሙያ መተዳደር
ለሚፈልግ ማንኛውም ሌላ ሰው በኑዛዜ ሊያስተላለፍ ይችላል በማለት ይደነግጋል፡፡ የዚሁ Aዋጅ Aንቀጽ
16(1) ደግሞ ማንኛውም የገጠር መሬት ባለይዞታ የይዞታም ሆነ የመጠቀም መብቱን በክልሉ ዉስጥ
ለሚኖር Eና በግብርና ሥራ ለሚተዳደር ወይም በዚህ ሙያ መተዳደር ለሚፈልግ ልጅ ወይም የልጅ
ልጁ ወይም ለማንኛውም ሌላ የቤተሰብ Aባል ወይም መረጃውን በጽሑፍ Eስካረጋገጠ ድረስ በወቅቱ
Eየጦረው ላለና Aገልግሎኛል ወይም Eያገለገለኝ ነው ብሎ ላመነው ሌላ ማንኛውም ሰው በስጦታ
ማስተላለፍ Eንደሚችል ይደነግጋል፡፡

በኑዛዜ ጊዜ Aካለ መጠን ያላደረሰን የተናዛዡን ልጅ ከህጋዊ ወራሽነት የሚነቅል ከሆነ በሕግ ፊት
የማይፀና ስለመሆኑ Aንቀጽ 17(3) ሲደነግግ በስጦታ ጊዜ ባለይዞታው ያደረገው ስጦታ Aካለ መጠን
ያልደረሱ ልጆቹን ወይም የቤተሰብ Aባላትን መብት ሙሉ በሙሉ በሚጎዳ ወይም ለEነሱ በቂ ድርሻ
በማያስቀር ሁኔታ የተከናወነ ከሆነ በሕግ ፊት ተቀባይነት የማይኖረው ስለመሆኑ Aንቀጽ 16(3)
ይደነግጋል፡፡ በመሰረቱ ኑዛዜ ተናዝዡ ከሞተ በኋላ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑ ስጦታ ደግሞ ሰጭው
በህይወት Eያለ ጀምሮ የሚፈፀም መሆኑ ካልሆነ በስተቀር በሁለቱ መካከል ጉልህ ልዩነት የለም፡፡
በAዋጅ ቁጥር 252/2009 ግን በሁለቱ መካከል ሰፊ ልዩነት Aለ፡፡ የመጀመሪያው በስጦታ ጊዜ ሕጉ
የስጦታ ተጠቃሚዎችን በግልጽ ለይቶ ያስቀምጣል፡፡ በኑዛዜ ጊዜ ግን የገጠር መሬት ባለይዞታ የመሆን
መብት ላለው ለማንኛውም ሰው ማስተላለፍ Eንደሚቻል ይገልፃል፡፡ በሁለቱም ድጋጌዎች መካከል
ያለው ይህ ልዩነት ከምን Aንፃር Eንደሆነ ግልጽነት ይጎድለዋል፡፡

በኑዛዜ ጊዜ ከውርስ ሊነቀሉ የማይችሉት Aካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች ብቻ ሆኖ Eያለ በስጦታ ጊዜ
ስጦታው Aካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች ወይም የቤተሰብ Aባላትን ጥቅም ከጎዳ Eንደሚፈርስ መደንገጉ

22
ሲታይ Aጠቃላይ Aዋጁ ከያዛቸው መርሆዎች Aንፃር በስጦታ ጊዜ የቤተሰብ Aባልን መብት ከጎዳ
ይፈርሳል የሚለው ይዘት ፍፁም ያልታሰበበት ነው፡፡ ምክንያቱም Aዲሱ Aዋጅ ከቀድሞው Aዋጅ በተለየ
ሁኔታ የቤተሰብ Aባላትን በማራቅ ለልጆች ቅድሚያ በመስጠት Eንዲወርሱ ከመደንገጉ Aንፃር በስጦታ
ጊዜ Aካለ መጠን የደረሱ ልጆች መብት ቢጎዳም ስጦታው የማይፈርስ ሆኖ Eያለ የቤተሰብ Aባላትን
መብት ቢጎዳ ስጦታው በሕግ ፊት ተቀባይነት የለውም ተብሎ መደንገጉ ተገቢ ስላልሆነ ነው፡፡ ሕግ
ሲወጣ Aጠቃላይ Aዋጁ ያስቀመጣቸውን መርሆዎች ያልተቃረኑ ወጥነት ያላቸው (Consistent)
ድንጋጌዎችን መያዙ መረጋገጥ Aለበት፡፡ ስለሆነም Aዲሱ Aዋጅ ኑዛዜ ላይ Aካለ መጠን ላልደረሱት
ልጆች ብቻ ጥበቃ Aድርጎ ስጦታ ላይ ግን የቤተሰብ Aባላትን Aካለ መጠን ከደረሱ ልጆች Aስበልጦ
መብታቸው ከተጎዳ ስጦታው ይፈርሳል በማለት መደንገጉ ሲታይ በተለይ Aዋጁ የቤተሰብ Aባላትን
Aርቆ ለልጆች ልዩ ትኩረት በመስጠት መሬት Eንዲወርሱ ካስቀመጠው የውርስ ድንጋጌ Aኳያ
የሚጋጭና ፍጹም ስህተት ያለበት ነው፡፡

በሌላ በኩል የAዋጁ Aንቀጽ 17(5) ባለይዞታው በኑዛዜ ሳያወርስ የሞተ ወይም የሰጠው ኑዛዜ ፈራሽ
ሆኖ የተገኘ Eንደሆነ መብቱ Eንደ ቅደምተከታላቸው በግብርና ሥራ ለሚተዳደር ወይም በዚሁ ሙያ
መተዳደር ለሚፈልግ የሟች ልጆች፣ ወላጅ/ጆች ወይም ሕግ ለሚፈቅድለት ለማንኛውም ሌላ የቤተሰቡ
Aባል ይተላለፋል በማለት ይደነግጋል፡፡ ይህ ድንጋጌ ቀደም ሲል ከነበረው Aዋጅ ቁጥር 133/98 Eና
ደንብ ቁጥር 51/99 Aንፃር Aላስፈላጊ ልዩነቶችን (በተለይም በልጆች መካከል) በማስወገድ በAንፃራዊነት
የተሻለ ቢሆንም Aሁንም ግን ከችግር የፀዳ Aይደለም፡፡ ይኸውም ሁሉንም Aይነት የሟች ልጆች በAንድ
መደዳ Eኩል ወራሽ ማድረጉ የራሱ ችግሮች ይኖሩታል፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት የሟች Aካለ መጠን
የደረሱም ሆነ ያልደረሱ Eንዲሁም መሬት ያላቸውም ሆነ የሌላቸው ልጆች Eኩል የመውረስ መብት
Aላቸው ማለት ነው፡፡ ከቀድሞ ሕጎች Aንጻር Aዲሱ Aዋጅ Aካለ መጠን የደረሱና ያልደረሱ ልጆች
መካከል የነበረውን ልዩነት ማስቀረቱ Eና ከቤተሰብ Aባላት በፊት ልጆች Eንዲወርሱ መደንገጉ ተገቢ
ነው፡፡ ሆኖም መሬት ባላቸው Eና መሬት በሌላቸው ልጆች መካከል ልዩነት Aለመፈጠሩ Aሁንም
የፍትሐዊነት ችግር መከሰቱ Aይቀርም፡፡

ይኸውም በጸሐፊው Eምነት Aዲሱ ሕግ Eንደቀድሞው በደረቁ መሬት ባለውና መሬት በሌላው ልጅ
መካከል ልዩነት በመፍጠር ቆራጣ መሬት ያለው ልጅም መሬት Eንዳለው ተቆጥሮ መሬት Eንዳይወርስ
የማድረግ ውጤት ሳይኖረው ፍትሐዊነትን ለመጠበቅ በሁለቱ መካከል Aንጻራዊ ልዩነት መፍጠር
ነበረበት፡፡ ጉዳዩን የበለጠ በምሳሌ ለማሳየት ያክል ሟች ሁለት ልጆች Eና 4 ቃዳ መሬት Aለው
Eንበል፡፡ Aንዱ ልጅ የራሱ 8 ቃዳ መሬት ቢኖረው Eና ሌላው ልጅ ምንም መሬት ባይኖረው
የAባታቸውን መሬት Eኩል ሲካፈሉ መጨረሻ ላይ የራሱ መሬት የነበረው ልጅ 10 ቃዳ መሬት
ሲሆንለት መሬት ያልነበረው ልጅ ግን 2 ቃዳ መሬት ብቻ ይኖረዋል ማለት ነው፡፡ ይህ ሁኔታ
ፍትሐዊነትን Aያረጋግጥም፡፡ ከዚህ Aንጻር ሟች በርካታ መሬት ቢኖረው Eና Aንዱ ልጅ Aነስተኛ

23
መሬት ቢኖረው መሬት የሌለው ልጅ መሬት ያለውን ልጅ ያክል በቅድሚያ Aንስቶ ቀሪውን መሬት
Eኩል Eንዲካፈሉ የሚያደርግ Aይነት ድንጋጌ ቢካተት ኖሮ ፍትሐዊነት ይረጋገጥ ነበር፡፡ ምክንያቱም
መሬት በተፈጥሮ የሚገኝ ውስን ሀብት ስለሆነ ከAንዱ ሰው ወደ ሌላ ሰው ሲተላለፍ በተቻለ መጠን
ፍትሐዊ የተፈጥሮ ሀብት ክፍፍልን መሰረት Aድርጎ መሆን ይኖርበታል፡፡

ከዚሁ ከውርስ ድንጋጌ ሳንወጣ የAዋጁ Aንቀጽ 17(5) የወራሾችን ቅደም ተከተል ሲደነግግ ከልጆች
ቀጥሎ ወላጆች ወይም የቤተሰብ Aባላት ይወርሳሉ የሚለው Aገላለጽ በ"ወይም" በመያያዙ ወላጆች Eና
የቤተሰብ Aባላት የውርስ ቅደምተከተላቸው Eኩል Aይደለም ወይ? የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ በEርግጥ
ድንጋጌው Aቀማመጡ ችግር Aለበት፡፡ ምክንያቱም በተለምዶ "ወይም" የሚለው Aያያዥ ከሁለት
Aንዱን በAማራጭ በEኩልነት የሚያሳትፍ ነውና፡፡ ሆኖም በAንድ በኩል ድንጋጌው ከላይ ሲጀምር
በቅደምተከተል የሚል Aገላለጽ መጠቀሙ ሲታይ በሌላ በኩል ቀደም ሲል የሟች የቤተሰብ Aባል
ያልሆነ ሰው ሁሉ የቤተሰብ Aባል ነኝ Eያለ ያላግባብ መሬት ለመውሰስ የሚደረገውን ሽሚያ በማየት
ሕግ Aውጭው የቤተሰብ Aባላት መጨረሻ ላይ Eንዲወርሱ የማድረግ ሀሳብ ያለው ስለሆነ ከልጅች
ቀጥሎ ወላጆች ይወርሳሉ ብሎ መተርጎሙ የተሸለ ነው፡፡

4.3 ከክርክር Aፈታት ዘዴዎች ጋር የተያያዙ ችግሮች


በመጀመሪያ ደረጃ Aማራጭ የሙግት መፍቻን በተመለከተ የAዋጅ ቁጥር 456/1997 Aንቀጽ 12
የመሬት ይዞታን Aስመልክቶ ክርክር ሲነሳ በቅድሚያ ተከራካሪ ወገኖች ክርክሩን በውይይትና
በስምምነት Eንዲፈቱ ጥረት ይደረጋል፤ በስምምነት መፍታት ካልተቻለ በተከራካሪ ወገኖች በተመረጡ
ሽማግሌዎች Aማካይነት በሽምግልና ይታያል፤ ወይም በክልሎች በሚወጣው የገጠር መሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም ሕግ መሰረት ይወሰናል በማለት ይደነግጋል፡፡ የክልላችን Aዋጅ ቁጥር 252/2009 Aንቀጽ 52
የገጠር መሬት ይዞታና የመጠቀም መብትን በሚመለከት የሚፈጠሩ Aለመግባባቶችና የሚነሱ ክርክሮች
የሚፈቱበትን ስነ ሥርዓት የደነግጋል፡፡ ይኸውም በመጀመሪያ ደረጃ በራሳቸው በባለጉዳዮቹ መካከል
በሚካሄድ ውይይት Eና በሚደረግ ስምምነት Eንዲፈቱ ይደረጋል፡፡ ተከራካሪ ወገኖች Aለመግባባታቸውን
በስምምነት ሊፈቱ ካልቻሉ ራሳቸው በሚመርጧቸው ሽማግሌዎች Aስታራቂነት ጉዳያቸው Eልባት
Eንዲያገኝ ይደረጋል፡፡

በተግባር በበርካታ ፍርድ ቤቶች የሚነሳው ጥያቄ የገጠር መሬት ክርክር ሲኖር ባለጉዳች Aማራጭ
የሙግት መፍቻ ዘዴዎችን ሳይጠቀሙ ወይም ሳይሞክሩ በቀጥታ በፍርድ ቤት ክስ ማቅረብ ይችላሉ
ወይስ Aይችሉም የሚለው ነው፡፡ ይህን ጉዳይ በተመለከተ Aዋጅ ቁጥር 133/1997 Aንቀጽ 29 Eና
ደንብ ቁጥር 51/1999 Aንቀጽ 35 ምርጫውን ለተከራካሪዎች በመተው በAማራጭነት ደንግገው የነበረ
መሆኑ ይታወቃል፡፡ Aዲሱ Aዋጅ በቅድሚያ Aማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴን መጠቀም Eንደግዴታ
ይደነግጋል፡፡ ይህም ምናልባት የፍርድ ቤቶችን መጨናነቅ በመቀነስ ረገድ Eና Aንዳንዴም ለባለጉዳዮች
ለራሳቸውም ጠቃሚ ውጤት ሊያስገኝ የሚችል ቢሆንም ባለጉዳዮች የAማራጭ የሙግት መፍቻ

24
ዘዴዎችን ጥቅም በመረዳት Aለመግባባትታቸውን ከመደበኛ ፍርድ ቤት ውጭ Eንዲፈቱ ጥረት መደረግ
ከሚኖርበት በስተቀር በAስገዳጅነት መደንገግ ተገቢ Aይደለም፡፡ ምክንያቱም Aማራጭ የሙግት መፍቻ
ዘዴ በፈቃድ ላይ የተመሰረተ የክርክር መፍቻ መንገድ Eንደመሆኑ መጠን ተከራካሪዎች በግዴታ
Eንዲገቡበት መደንገግ የለበትም፡፡ በግዴታ Eንዲፈጸም ሲደረግም ውጤታማ የመሆን Eድሉ ዝቅተኛ
ነው፡፡ AለምAቀፋዊ መርሁም የሚያሳየው ይህንኑ ነው፡፡72 በመንግስት በኩል ይህን ዘዴ ተግባራዊ
Eንዲደረግ የሚያግዝ ተቋም ሳይኖር Eንዴትስ በግዴታ ተግባራዊ ሊደረግ Eና ውጤት ሊያስገኝ
ይችላል? የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡

በተጨማሪም የAዋጁ Aንቀጽ 52(2) Aለመግባባቱ ያልተፈታ Eንደሆነ ይኸው ከታወቀበት ቀን ጀምሮ
ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ጉዳዩ ለAቅራቢያው ወረዳ ፍርድ ቤት ሊቀርብ ይችላል ብሎ መደንገጉ ሲታይ
በ30 ቀናት ውስጥ ለወረዳ ፍርድ ቤት ክሱ ሳይቀርብ ቢቀር ከዚህ ጊዜ በኋላ ክሱ ሊቀርብ Aይችልም
ማለት ነው? ይህ ገደብ የተቀመጠበት Aላማስ ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ያስነሳል፡፡ በጸሐፊው
Eምነት ይህ ድናጋጌ ታስቦበት የተቀመጠ ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡ ምክንያቱም ባለጉዳዮች
በመካከላቸው ያለውን Aለመግባባት በAማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴዎች ለመፍታት ጥረት Aድርገው
መስማማት ካልቻሉ ክስ የማቅረብ መብታቸው በይርጋ Eስካልታገደ ድረስ በፈለጉት ጊዜ ለመደበኛ
ለፍርድ ቤት ክስ የማቅረብ መብት Aላቸው፡፡ ከዚህ Aንጻር በ30 ቀናት ውስጥ የግዴታ ክሱ መቅረብ
Aለበት ማለት ከዚህ መርህ Aንጻር ተገቢ ካለመሆኑም በላይ የAርሶ Aደሩን የመሬት ይዞታ መብት
የማጥበብ ውጤት ስለሚኖረው ተቀባይነት ሊኖረው Aይገባም፡፡

Aስተዳደራዊ ውሳኔዎችን በተመለከተ የAዋጁ Aንቀጽ 33(5) በመሬት Aለካክና በድንበር Aከላለል ረገድ፣
Aንቀጽ 38(1) የገጠር መሬት ይዞታን በመመዝገብ Eና በማረጋገጡ ሂደት፣ Aንቀጽ 40(1) በምዝገባ
ሂደት ተረጋግጦ የተያዘ መረጃ የመጨረሻ ሆኖ መዝገብ ውስጥ ከመግባቱ በፊት Eና Aንቀጽ 43
የባለይዞታ ወይም የማሳ ወይም የሁለቱም ለውጥ በሚያጋጥምበት ጊዜ መረጃን ወቅታዊ በማድረግ
ሂደት የሚሰጡ Aስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ቅሬታ ያለው ባለይዞታ ቅሬታ የሚያቀርብባቸውን ተቋማት
Eና የሚያቀርብበትን ጊዜ የሚደነግጉ ናቸው፡፡ በAጠቃላይ ግን የAዋጁ Aንቀጽ 52(6) Eንደሚደነግገው
የገጠር መሬትን ከመለካት፣ ከማስተዳደርና ከሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ጋር በተየያዘ የወረዳ ገጠር መሬት
Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤቶች በሚሰጡት Aስተዳደራዊ ውሳኔ ላይ ቅር የተሰኘ ማንኛውም ወገን
ይኸው በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ክሱን ለወረዳዉ ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል፡፡ የወረዳዉ ፍርድ
ቤት የጽ/ቤቱን ውሳኔ ያጸናው Eንደሆነ ይግባኙን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ሊያቀርብ ይችላል፡፡ ይግባኙ
የቀረበለት ከፍተኛ ፍርድ ቤትም የሥር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ ያጸናው Eንደሆነ ውሳኔው የመጨረሻ
ይሆናል በማለት ይደነግጋል፡፡

72
Stacey Keare, Reducing the cost of Civil Litigation: Altrenative Dispute Resolution, PLRI Public Law Research
Institute; Fekadu Petros, Underlining Distinctions beteween Altrenative Dispute Resolution, Shimglina and
Arbitration, Mizan Law Review, Vol 3, No. 1, p. 116 & 119
25
በAዲሱ Aዋጅ በወረዳ መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት ውሳኔ ያልተስማማ ሰው ይግባኝ ለዞን
መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም መምሪያ ሊያቀርብ የሚችልበትን ሁኔታም የሚደነግግ ይዘት ያለው
Aንቀጽ Aካቷል፡፡ ለምሳሌ በAዋጁ Aንቀጽ 43(1)(2)(3) ድንጋጌዎች መረዳት Eንደሚቻለው የባለይዞታ
ወይም የማሳ ወይም የሁለቱም ለውጥ በሚያጋጥምበት ጊዜ የመሬት ምዝገባ ሰነዱ በቀበሌ Eና በወረዳ
የመሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ኮሚቴዎች Aማካኝነት ወቅታዊ መደረግ ይኖርበታል፡፡ ኮሚቴው
በሰጠው Aስተዳደራዊ ውሳኔ ቅር የተሰኘ ወገን Aቤቱታውን በጽሑፍ Aዘጋጅቶ ለወረዳ ገጠር መሬት
Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት ሊያቀርብ ይችላል፡፡ በጽ/ቤቱ ውሳኔ ያልተስማማ Eንደሆነ ደግሞ ለዞኑ
መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም መምሪያ ወይም ለወረዳ ፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላል፡፡

ከዚህ መረዳት የሚቻለው Aስተዳደራዊ ውሳኔዎች ከቀበሌ መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት
ጀመረው በይግባኝ ለወረዳ መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት ከቀረቡ በኋላ ቀጥሎ በቅሬታ
Aቅራቢው ምርጫ ለዞን መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም መምሪያ ይግባኝ ወይም ለወረዳ ፍርድ ቤት ክስ
ሊቀርብ Eንደሚችል ነው፡፡ ይኸውም በየትኛውም ሁኔታ በየደረጃው ባሉት በመሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም ተቋማት Aስተዳደራዊ ውሳኔ ያልረካ ሰው ለወረዳ ፍርድ ቤት ክስ ማቅረብ የሚቻል መሆኑን
ያሳያል፡፡ ይህም ከቀድሞው ሕግ በሁለት መልኩ የተለየ መሆኑን Eንገነዘባለን፡፡ የመጀመሪያው
የቀድሞው ሕግ በወረዳ መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት Aስተዳደራዊ ውሳኔ ያልተስማማ ሰው
ለዞን መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም መምሪያ ይግባኝ የማቅረብ መብት Aይሰጥም ነበር፡፡ ሁለተኛው
ልዩነት የቀድሞው ሕግ በወረዳ መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ጽ/ቤት Aስተዳደራዊ ውሳኔ ያልተስማማ
ሰው የነበረው መብት ለወረዳ ፍርድ ቤት ይግባኘ ማቅረብ ሲሆን በAዲሱ ሕግ ግን Aዲስ ክስ የማቅረብ
መብት Aለው፡፡ ከዚህ Aንጻር በAዲሱ Aዋጅ ከAስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ይግባኝ ጠይቆ ከማሳረም
ይልቅ Aዲስ ክስ Eንዲቀርብ መደንገጉ ተገቢ Aይመስልም፡፡ ምክያቱም የዚህ Aይነት የክርክር Aፈታት
መርህ Aላማ በAስተዳደራዊ ውሳኔ ያረካ ሰው በውሳኔው ላይ ይግባኝ ጠይቆ ማሳየት (review of
administrative decisions) Eና መፍትሔ ማግኘት Eንጅ Aዲስ ክስ የሚቀርብ ከሆነ መጀመሪያም
ቢሆን Aስተዳደራዊ ውሳኔ ለማግኘት መድከም Aያስፈልግም ነበር ማለት ነው፡፡ ከዚህ Aንጻር የቀድመው
ሕግ የተሸለ ነበር ማለት ይቻላል፡፡

በሌላ በኩል በፍርድ ቤት የሚደረግ የክርክር Aፈታት ዘዴን በተመለከተ Aዋጅ ቁጥር 252/2009 Aንቀጽ
52(2) የገጠር መሬት ይዞታና የመጠቀም መብትን በሚመለከት የሚፈጠር Aለመግባባት በEርቅ
ያልተፈታ Eንደሆነ ይኸው ከታወቀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ጉዳዩ ለAቅራቢያው ወረዳ
ፍርድ ቤት ሊቀርብ ይችላል በማለት ይደነግጋል፡፡ በAንቀጽ 52(3) መሰረት ደግሞ የወረዳዉ ፍርድ ቤት
በመጀመሪያ ደረጃ ተመልክቶ ውሳኔ የሰጠበት ማናቸውም ጉዳይ በ30 ቀናት ውስጥ ለከፍተኛ ፍርድ
ቤት ይግባኝ ሊቀርብበት ይችላል፡፡ በዚህ Aንቀጽ በወረዳ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቀር የተሰኘ ወገን ለከፍተኛ
ፍርድ ቤት ይግባኝ መጠየቅ የሚችለው በ30 ቀን ብቻ ሆኖ የተደነገገው ከምን Aንጻር Eንደሆነ ግልጽ

26
Aይደለም፡፡ ምክንያቱም ምንም Eንኳን ሕግ Aውጭው መደበኛው የፍትሐ ብሔር ክርክር ይግባኝ
ከሚጠየቅበት 60 ቀን ያነሰ የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ መደንገግ የሚችል ቢሆንም73 የዚህ Aይነት መብት
Aጥባቢ ድንጋጌ ሲቀመጥ በቂ Eና Aሳማኝ ምክንያት ያስፈልጋል፡፡ በገጠር መሬት Aስተዳደርና
Aጠቃቀም ሕግ ተጠቃሚም ሆነ ተጎጅ የሚሆኑት Aርሶ Aደሮች Eንደመሆናቸው መጠን ያልተማረና
መብቱን በAግባቡ የማያውቅ Aርሶ Aደር ባለበት ክልል Eንዲህ Aይነት መብት የሚያጠብ ሕግ
ማውጣት ተገቢነት የለውም፡፡
4.4 በሕጎቹ ላይ Aላስፈላጊ Aገላለጾችና ድግግሞሽ የማካተት ችግር
Aዲሱ Aዋጅ የራሱ የሆኑ በጎ ጎኖች ቢኖሩትም በርካታ የሀሳብ ድግግሞሽ ወይም Aላስፈላጊ ድንጋጌዎች
የያዘ ስለሆነ የሕግ Aወጣጥ መስፈርትን Aሟልቶ በAግባቡ የተረቀቀ ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡
ለማሳያ ያክል የሚከተሉትን ማየት በቂ ነው፡፡

1. ወላጆቻቸውን ያጡ ህጻናት፣ Aካል ጉዳተኞች፣ Aቅመ ደካሞችን፣ ሴቶችንና የAረጋዊያንን መብት


የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በየAንቀጹ ያላግባብ ተደጋግሟል፡፡ ይህም ከላይ በክፍል 4.1 ሥር
በተቀመጠው Aግባብ በሌሎች ዜጎች ላይ ያላግባብ የሚያዳላ ከመሆኑም በላይ በሕግ Aወጣጥ መርህም
Eነዚህን ወገኖች መጥቀም ከተፈለገ Eንኳን ጠቅለል Aድርጎ በAንድ ድንጋጌ ከገጠር መሬት ይዞታ
Aሰጣጥና ተያያዥ ተግባራት ጋር በተገናኘ የEነዚህ ወገኖች መብት ቅድሚያ Eንዲያገኝ Aድርጎ
መደንገግ ይቻል ነበር፡፡ ለምሳሌ በAዋጁ Aንቀጽ 39(1) ላይ ሞግዚት ወይም ሕጋዊ ወኪል የሌላቸው
ሕፃናት፣ የAካል ጉዳተኞች፣ የAቅመ ደካሞች፣ የሴቶችና የAረጋውያን ይዞታ የሆነ መሬት
በሚመዘገብበትና በሚረጋገጥበት ወቅት Eነዚሁ ወገኖች በስፍራው ካለመገኘታቸው የተነሳ መብታቸው
Eንዳይጣስ ብርቱ ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል በሚል Eንደተደነገገው Aይነት Aንድ Aንቀጽ
ማስቀመጥ ይቻል ነበር፡፡

2. ስለ ምትክ ወራሽነት የሚደነግገው የAዋጁ Aንቀጽ 17(6) የሟች ልጆች ወይም ከልጆቹ Aንዱ
ቀድመዉ ሞተዉ ወይም ሞቶ Eንደሆነና ወደታች የሚቂጠሩ ተወላጆችን ትተዉ/ትቶ Eንደሆነ
Eነዚሁ ተወላጆቻቸዉ የሟቹ የቤተሰብ Aባል ሆነዉ ተገኝተዉ ካልወረሱ በስተቀር ቀድመዉ
በሞቱት ልጆች ምትክ ሆነዉ Eንዲወርሱ ይደረጋል በማለት ይደነግጋል፡፡ በAዲሱ Aዋጅ የቤተሰብ
Aባል ከልጆች በፊት የሚወርስበት ሁኔታ የቀረ ከመሆኑ Aኳያ ቀድመው የቤተሰብ Aባል ሆነው
ካልወረሱ በስቀር የሚለው Aገላለጽ በከንቱ የገባ ነው፡፡

3. Aንቀጽ 17(7) በጋብቻ የተወለዱና ከጋብቻ ውጭ የተወለዱ ልጆች Eኩል የመውረስ መብት ያላቸው
ስለመሆኑ በቤተሰብ ሕጉ ተደንግጎ Aድሮ Eያለ በመሬት Aዋጁ Eንዲህ Aይነት ድንጋጌ ማካተት
በሕግ ስርዓቱ ውስጥ የድግግሞሽ ውጤት ያለው ነው፡፡

73
ለምሳሌ በAሠሪና ሠራተኛ Aዋጅ ቁጥር 377/1996 Aንቀጽ 138(3) የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ Aንድ ወር ነው፡፡
ይህ የሆነበት የራሱ ምክንያት Aለው፡፡ ለIንዱስትሪው የሥራ ፍጥነት ሲባል ነው፡፡
27
4. Aንቀጽ 17(8) ደግሞ ማንኛውም ሰው ሳይናዘዝ በሞተበት ወቅት በግብርና ሥራ የሚተዳደር ወይም
ለመተዳደር የሚፈልግ ወደታች የሚቆጠር ተወላጅ የሌለው ሆኖ በግብርና ሥራ የሚተዳደሩ ወይም
ለመተዳደር የሚፈልጉ ወላጅ/ጆች ካለው ወይም ካሉትና Aስቀድሞ ያላቸው የገጠር መሬት ይዞታ
መጠን ከከፍተኛው የይዞታ ጣሪያ በታች መሆኑ የታወቀ Eንደሆነ የመሬት ይዞታውን Eነርሱ
የመውረስ መብት ይኖራቸዋል፤ ዝርዝሩ በደንብ ይወሰናል፤ በማለት ይደነግጋል፡፡ ይህ ድንጋጌ
ጭራሽ Aስፈላጊ Aልነበረም፡፡ ምክንያቱም ወላጆች የልጆቻቸውን መሬት የሚወርሱበት ሁኔታ
በAንቀጽ 17(5) ሥር የተካተተ ሆኖ Eያለ በድጋሜ በAንቀጽ 17(8) ሥር ተመሳሳይ ሀሳብ
ማስቀመጡ Aስፈላጊ Aይደለም፡፡ በደንብ ሊወሰን የሚችል የወላጅ Aወራረስ ሁኔታ ሳይኖር ዝርዝሩ
በደንብ ይወሰናል መባሉም በጣም የሚገርም ነው፡፡ ካስፈለገም ዝርዝር በደንብ ይወሰናል ተብሎ
ለደንቡ ስልጣን መስጠት የነበረበት በAንቀጽ 17(5) ሥር ነው፡፡ በዚህ ንUስ Aንቀጽ ሥር ለደንቡ
ስልጣን ተሰጥቶ ቢሆን ኑሮ ምናልባልትም ከላይ የተነሳውን የፍትሐዋነት በችግር ይቀርፍ ነበር፡፡

5. የAዋጁ Aንቀጽ 35(2) Eና (5) ድንጋጌዎች የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር የባለይዞታው በሕግ
የተጠበቀ መብት ማስረጃ ነው፡፡ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር Eያለ ዳኞች ሌሎችን የሰነድም ሆነ
የሰው ማስረጃዎችን ቅድሚያ ሰጥተው ሊቀበሉና ሊመለከቱ Aይችሉም፡፡ ይህንኑ የሚቃረን ጠንካራ
የጽሑፍ ማስረጃ Eና ይበልጥ የሚያሳምን ምክንያት ካልቀረበ በስተቀር የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር
በስሙ ተዘጋጅቶ የተሰጠው ማንኛውም ሰው የመሬቱ ሕጋዊ ባለይዞታ Eንደሆነ ይቆጠራል፡፡
በማለት ይደነግጋሉ፡፡ ይህም በፍ/ሕ/ቁ 1195 Eና 2010(2) Aንጻር ለሰነድ ማስረጃ የተሰጠውን
ግምት Eና Eንዴት ማስተባበል Eንደሚቻል የተደነገገ ከመሆኑ Aኳያ በሕግ ስርዓቱ ውስጥ ሌላ
ድግግሞስ ከመሆኑም በላይ ለዳኞችም ሆነ ለሌሎች የሕግ ባለሙያዎች ግራመጋባትን የሚፈጥር
ነው፡፡ Aገላለጹም ሕጉን ግልጽ ከማድረግ ይልቅ የሚያወዛግብ ነው፡፡ Eነዚህ ድንጋጌዎች ባይኖሩም
ስለማስረጃ ሕጋችን የተደነገጉትን Aጠቃላይ መርሆዎች ግምት ውስጥ በማስገባት ሊመለስ የሚችል
ጉዳይን የበለጠ በሚያምታታ ሁኔታ መደንገግ ተገቢ Aልነበረም፡፡

6. Aመግባባቶች ስለሚፈቱበት ሁኔታ የሚደነግገው Aንቀጽ 52(4)-(8) ያሉት ድንጋጌዎች Aላስፈላጊ


ድግግሞሽ ናቸው፡፡ ይኸውም በስተዳደራዊ ውሳኔ ቅር በመሰኘትም ሆነ ጉዳዩ በEርቅ ባለማለቁ
ለወረዳ ፍርድ ቤት ቀርቦ በተወሰነው ጉዳይ ቅረታ ያለው ወገን ይግባኙን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት
ያቀርባል፡፡ ይግባኝ የቀረበለት የከፍተኛ ፍርድ ቤት የወረዳውን ፍርድ ቤት ውሳኔ ካጸናው ውሳኔው
የመጨረሻ ይሆናል፡፡ ይግባኙ የቀረበለት ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሥር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ የሻረው
ወይም ያሸሻለዉ Eንደሆነ ግን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተጨማሪ ይግባኝ ሊቀርብበት ይችላል፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል፡፡ በመጨረሻ ደረጃ በተሰጡ የከፍተኛም
ሆነ የጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ውሳኔዎች ላይ መሰረታዊ የሕግ ስህተት Aለበት የሚል ወገን
Aቤቱታዉን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሊያቀርብ ይችላል፡፡ Eነዚህ Aገላለጾች

28
የይግባኝ ስርዓቱን በተመለከተ በክልሉ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ Aዋጅ ቁጥር 223/2007 በግልጽ
ከተደነገገው Aገላለጽ Aኳያ Aላስፈላጊ ድግግሞሽ ስለሆኑ ምንም ጥቅም የላቸውም፡፡ በሌላ Aገላለጽ
በስተዳደራዊ ውሳኔ ቅር በመሰኘትም ሆነ ጉዳዩ በEርቅ ባለማለቁ ወረዳ ፍርድ ቤት ክስ
Eንደሚቀርብ መደንገግ ብቻ በቂ ነበር፡፡ ምክንያቱም ለወረዳ ፍርድ ቤት የቀረበ ክስ ውሳኔ ሲያገኝ
ቀጥሎ ወደየትኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ Eንደሚጠየቅ በፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ ሕግ ተደንግጎ ያደረ
ጉዳይ ነው፡፡
5. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ላይ የሚታዩ ችግሮች
Aዲሱ Aዋጅ የማጠቃለያ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ላይም በርካታ ጥያቄ የሚፈጥሩና ለAሠራር
የሚያስቸግሩ ድንጋጌዎችን ይዟል፡፡ Eነዚህ ችግሮች በተወሰነ መልኩ ማየት ይገባል፡፡
1. የፍትሐ ብሔር ሕግ Aግባብነት የሚለው የAዋጅ Aንቀጽ 54 በዚህ Aዋጅ Aንቀጽ 15፣ 16 Eና 17
ያልተሸፈኑ የገጠር መሬት ኪራይ፣ ስጦታ፣ ውርስና ሌሎች ፍትሐ ብሔር ነክ ጉዳዮችን
በተመለከተ Eንደነገሩ ሁኔታ Aግባብነት ያላቸዉ 1952 ዓ/ም የፍትሐ ብሔር ሕግ ድንጋጌዎች
ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል በማለት ይደነግጋል፡፡ ይህ Aገላለጽ ምን ማለት ነው? ለምሳሌ በመሬት
Aዋጁ መሰረት ሊወርስ ወይም ስጦታ ሊቀበል የማይችል ሰው የፍትሐ ብሔር ሕጉን መሰረት
ተደረጎ ሊወርስ ወይም ስጦታ ተቀባይ ሊሆን ይችላል ማለት ነውን? Aይደለም፡፡ ይልቁንም የዚህ
ድንጋጌ ይዘት በፍትሐ ብሔር ሕጉ የሚታወቁ ጽንሰ ሀሳቦች ለምሳሌ ከወራሽነት መንቀል፣
ለውርስ ያልተገባ መሆን፣ የመጥፋት ውሳኔ የሚሉና ተመሳሳይ ሀሳቦች ቢያጋጥሙ በቀጥታ
Eነዚህን ሀሳቦች የሚመለከቱ የፍትሐ ብሔር ሕጉ ድንጋጌዎች ተግባራዊ ይደረጋሉ ማለት ነው፡፡74

2. ስለ ይርጋ የሚደነግገው Aንቀጽ 55 የገጠር መሬትን በወረራ ወይም በሌላ በማናቸውም ሕገ ወጥ


መንገድ ይዞ በመገልገል ላይ የሚገኝ ማንኛውም ሰው መሬቱን Eንዲለቅ በማንኛውም ሌላ ሰው
ወይም ሥልጣን ባለው የመንግሥት Aስተዳደር Aካል ሲጠየቅ ወይም በመደበኛ ፍርድ ቤት ሲከሰስ
የይርጋ ጊዜ ገደብን በሥነ ስርዓት መቃወሚያነት ሊያነሳ Aይችልም በማለት ይደነግጋል፡፡ ይህ
Aገላለጽ ሁሉንም Aይነት የገጠር መሬት ክርክሮች ይርጋ የላቸውም የሚያስብል ሆኖ መወሰድ
Aይኖርበትም፡፡ ለምሳል ጉዳዩ የመሬት ውርስ ክርክር ቢሆን ይርጋ የለውም ብሎ ለመተርጎም ይህ
ድንጋጌ Aያካትተውም፡፡

74
ይህን ሀሳብ የበለጠ ለማጉላት በፌደራል የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ረቂቅ Aዋጅ ማብራሪያ ላይ
የተወሰደውን ሀሳብ ማየት ይጠቅማል፡፡ … በፍትሐ ብሔር ሕጉ የተቀመጡ ጉዳዮችን Eንደ Aግባብነታቸው
ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል፡፡ ለምሳሌ መጥፋትን ብንወስድ በፍትሐ ብሔር ሕጉ ተደንግጎ ያደረ ጉዳይ ነው፡፡
በመሆኑም Aንድ ሰው የመጥፋት ውሳኔ ከተላለፈበት በፍትሐ ብሔር ሕጉ በሚያስቀምጠው ገደብ መሰረት
በጠፋው ሰው ይዞታ ስር የነበረውን መሬት ወራሾች ጠይቀው ሊከፋፈሉት ይችላሉ፡፡ Eነዚህን ዝርዝር ጉዳዮች
በዚህ Aዋጅ ከማየት ይልቅ የፍትሐ ብሔር ሕጉ ድንጋጌዎች Eንደ Aግባብነታቸው ተፈጻሚ Eንደሚሆኑ
Aስቀምጦ ማለፉ የተሻለ ነው ይላል፡፡ ገጽ 33

29
በፌደራል የገጠር መሬት Aስተዳደርና Aጠቃቀም ረቂቅ Aዋጅ ማብራሪያ ላይ የተወሰደው ትንታኔ
ይህን ሀሳብ ያጠናክራል፡፡ ይኸውም የይርጋ ድንጋጌዎች ለምሳሌ ጉዳዩ ከውል ጋር የተያያዘ ከሆነ
የፍትሐ ብሔር ሕጉ Aንቀጽ 1845 Aግባብነት ይኖረዋል፡፡ ሌሎች ከወል መሬት ወረራ ጋር
የተያያዙ ጉዳዮች ከመጀመሪያም ሕገ ወጥ Eና ወንጀል በመሆናቸው መሬቱን ለማስመለስ
የሚደረግ ክርክር በይርጋ የሚታገድ Aይሆንም፡፡ Eንዲህ Eንዲህ Eያለ Eንደ ሁኔታው የፍትሐ
ብሔር ሕጉ የይርጋ ድንጋጌ ሕጉ ይቀበላቸዋል ይላል፡፡

3. የፍርድ ቤት ውሳኔ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ስለሚኖረው ውጤት የሚደነግገው Aንቀጽ 56


ማንኛውም የገጠር መሬት ባለ ይዞታ የፍርድ ቤት ውሳኔን ለማስፈጸም በሚሰጥ ትEዛዝ ከይዞታው
Aይፈናቀልም ወይም ይዞታው ለEዳ መክፈያ በሚል ለሌላ Aካል ሊተላለፍ Aይችልም በማለት
ይደነግጋል፡፡ ይህ ድንጋጌ የገጠር መሬት Aይሸጥም በሌላ ንብረት Aይለወጥም ከሚለው ህገ
መንግስታዊ ክልከላ ጋር ተያይዞ ነው መተርጎም ያለበት፡፡ ይህ ማለት በፍትሐ ብሔር ለተፈጠረ
ግንኙነት የገጠር መሬት ለEዳ መክፈያ ተብሎ Aይያዝም ለማለት ነው፡፡ ይህ Aተረጓጎምም ቢሆን
በጠባቡ መታየት ይኖርበታል፡፡ ለምሳል ከመሬቱ የሚገኘውን ምርት ወይም መሬቱን በማከራየት
Eዳ Eንዲከፈል ከማዘዝ የሚከለክል ተደርጎ ሊወሰድ Aይገባውም፡፡

4. የመሸጋገሪያ ድንጋጌዎችን የያዘው Aንቀጽ 57 ይህ Aዋጅ ከመጽናቱ በፊት ከገጠር መሬት ይዞታና
Aጠቃቀም ጋር በተያያዙ በሌሎች ሕጐች የተቋቋሙ መብቶችና ግዴታዎች ቀደም ሲል የነበሩ
ሕጐችን መሰረት Aድርገው Eስከተገኙና ይህንን Aዋጅ በግልጽ Eስካልተቃረኑ ድረስ
ተፈፃሚነታቸው ይቀጥላል፡፡ ይህ Aዋጅ ከመውጣቱ በፊት ፍርድ ቤት ቀርበው በመታየት ላይ ያሉ
ማናቸውም መሬት-ነክ ጉዳዮች በተጀመሩበት Aግባብ የመጨረሻ Eልባት Eንዲያገኙ ይደረጋል፡፡
ይላል፡፡ በዚህ Aንቀጽ ንUስ Aንቀጽ 1 ላይ ይህንን Aዋጅ በግልጽ Eስካልተ ቃረኑ ድረስ
ተፈፃሚነታቸው ይቀጥላል የሚለው Aገላለጽ ምን ማለት ነው? ለምሳሌ በቀድሞው Aዋጅ መሰረት
የቤተሰብ Aባል በመሆን መሬት ካለው የሟች ልጅ ቀድሞ የወረሰ ሰው ቢኖር Aሁን ካለው
Aወራረስ ቅደም ተከተል ጋር ይቃረናል ተብሎ ተፈጻሚነቱ ሊቀር ነው?

በመጀመሪያ ደረጃ ይህን Aዋጅ Eስካልተቃረኑ ድረስ ተፈጻሚነታቸው ይቀጥላል የሚለው ሀረግ ያላግባብ
የተቀመጠ ነው፡፡ ይህ ማለት ከፍትሐ ብሔር ሕጉ ድንጋጌዎች ጀምሮ በተለያዩ ጊዚያት በሀገራችን
በርካታ የገጠር መሬት ሕጎች ታውጀዋል። Eነዚህ ሕጎች በየዘመናቸው ለመሬት ባለይዞታዎች
የሚሰጡት መብት ወጥነት Aልነበረውም፤ Aሁንም የለውም፡፡75 ለምሳሌ በAዋጅ ቁጥር 133/1998 Eና
ደንብ ቁጥር 51/1999 መሰረት የቤተሰብ Aባል ከልጅ ቀድሞ የሚወርስበት Aጋጣሚ በጣም ብዙ ነበር፡፡
Aሁን በወጣው Aዋጅ ቁጥር 252/2009 ደግሞ ልጅ Eያለ የቤተሰብ Aባል ሊወርስ Aይችልም፡፡

75
ለምሳሌ Aዋጅ ቁጥር 133/1998 ከAዋጅ ቁጥር 46/1992 የተሻለ Eና የሰፋ መብት ለባለይዞታዎች Eና
ለወራሾቻቸው ይሰጣል፡፡ Aሁን ደግሞ Aዋጅ ቁጥር 252/2009 በAንጻራዊነት የተሻለ መብት ይሰጣል፡፡
30
ቀደም ብለው የተሰሩ ሥራዎች ይህን Aዋጅ Eስካልተቃረኑ ድረስ ተፈጻሚነታቸው ይቀጥላል የሚለውን
በደረቁ ብንወስደው ቀደም ብሎ በAዋጅ ቁጥር 133/1998 Eና ደንብ ቁጥር 51/1999 መሰረት ከልጆች
ቀድመው የወረሱ የቤተሰብ Aባላት በሙሉ ድርጊቱ የAሁንን Aዋጅ ስለሚቃረን መፍረስ Aለበት የሚል
ድምዳሜ ላይ ያደርሰናል፡፡ Eንዲሁም ቀደም ሲል የነበረው ሕግ በልጆች መካከልም ቢሆን Aካለ መጠን
የደረሰና ያልደረሰ፣ መሬት ያለውና የሌለው Eያለ ልዩነት ስለሚያደርግ ይህን መሰረት ተደርጎ ለዘመናት
ሲሰራበት ስለኖረ ከAሁኑ ሕግ Aንጻር ይቃረናል ማለት ነው፡፡ ይህ Aተረጓጎም ማህበራዊ Eና Iኮኖሚ
ቀውስ ያስከትላል፡፡ ምክንያቱም የቀድሞቹ የገጠር ሕጎች መሰረት Aድርገው በርካታ የመሬት ውርስ
ተከናውኖ ከነችግሩም ቢሆን የወረሱ ሰዎች የይዞታ መብታቸውን Aደላድለው Eየኖሩ ባለበት ሁኔታ
መብቱን ያገኘህበት ሕግ ከAዲሱ ሕግ ጋር ይቃረናል በሚል ማፍረስ ቢጀመር ክልላችን የማይወጣው
ችግር ውስጥ መውደቁ Aይቀርም፡፡76

76
ይህን Aዋጅ መሰረት Aድርገው በርካታ ሰዎች በዚህ መንገድ ቀደም ሲል የተወረሱ መሬቶች ላይ በርካታ ክሶች
በፍርድ ቤቶች Eያቀረቡ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የሚቀርቡት ጉዳዮች ላይ ጥንቃቄ የተሞላበት ትርጉም ተሰጥቶ
በቀድሞ ሕጎች የተሰሩ ሥራዎች Eንደረጉ Eንዲቀሩ ካልተደረጉ በስተቀር ውጤቱ Aደገኛ መሆኑ Aይቀርም፡፡
31
ማጠቃለያ
በAማራ ክልል ቀደም ሲል ሥራ ላይ የነበረው Aዋጅ ቁጥር 133/1998 Eና ማስፈጸሚያ ደንቡ ቁጥር
51/1999 ላይ በተግባር በርካታ ችግሮች በማጋጠማቸው Aዋጅ ቁጥር 252/2009 Eና ማስፈጸሚያ
ደንብ ቁጥር 159/2010ም ተሻሽሎ ወጥቷል፡፡ Aዋጁ የተሻሻለበት ዋና ዋና ምክንያቶች የAርሶ Aደሮችን
በመሬት የመጠቀም መብት ይበልጥ ለማስፋት፤ ተበታትኖ የሚኖረዉን Aርሶ Aደር ወደ ተወሰኑ
ማEከላት በማሰባሰብ ሁለንተናዊ ለሆነ Eድገት ተጠቃሚ ለማድረግ፤ የግል ባለሀብቶች መሬትን
በማልማት ረገድ ያላቸውን ሚና ለማጠናከር፤ የገጠር መሬት ምዝገባ መረጃን በጥራት ለማደራጀት፤
ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን Eና ሕገ ወጥ ግንባታን ለመቆጣጠር፣ የገጠር መሬትን በEቅድ በመጠቀም
ለመጭው ትውልድ ለማስተላለፍ፤ ለመብት ጥሰት ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን መሬት የማግኘትና
የመጠቀም መብት ይበልጥ ለማስከበር፤ የገጠር መሬት ለሕዝብ ጥቅም ሲወሰድ ለባለይዞዎች
ተመጣጣኝ ካሳ በቅድሚያ የሚያገኙበትን Eና በዘላቂነት የሚቋቋሙበትን Aሠራር በሕግ መደንገግ
በማስፈለጉ የሚሉ ናቸው፡፡

በዚህ መሰረት Aዲሱ Aዋጅ ከቀድሞው Aዋጅ በEጥፍ ቁጥር ድንጋጌዎችን የያዘ፣ በጣም ሰፊ መግቢያ
Eና በርካታ የትርጓሜ ንUስ Aንቀጾችን ያካተተ Eንዲሁም Aዳዲስ ሀሳቦችን ያቀፈ ሆኖ ታውጇል፡፡
በዚህ ጽሑፍ Aዘጋጅ Eምነት ይህ Aዋጅ ሁለት ገጽታዎችን ይዞ ወጥቷል፡፡ የመጀመሪያው ገጽታ
የAዋጁ መውጣት ያመጣቸው መልካም ነገሮች ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ Aዋጁ ያካተታቸው ችግሮች
ናቸው፡፡ Aዋጁ ያመጣቸው መልካም ጎኖች ውስጥ የሚመደቡት ዋና ዋናዎቹ Aነስተኛ ገቢ ያላቸው
ሰዎች የመሬት ይዞታ ሊኖራቸው Eንደሚችል መደንገጉ፤ ለመብት ጥሰት ተጋላጭ ለሆኑ ወገኖች ልዩ
ትኩረት መስጠቱ፤ የመሬት ይዞታን ከማከራየት መብት ጋር ተያይዞ የኪራይ ዘመኑ ለሰብልና ለቋሚ
ተክሎች በሚል ልዩነት ማምጣቱ፤ የውርስ ቅደም ተከተሉ ለልጆች ቅድሚያ መስጠቱ Eና ተያያዥ
መሻሻሎች መኖራቸው፤ የይዞታ መሬትን Aስይዞ ገንዘብ መበደር መፈቀዱ፤ ይዞታ ለህዝብ Aገልግሎት
ሲወሰድ የመልሶ ማቋቋም ሥራ ለመንግስት ግዴታ ሆኖ መደንገጉ፤ የገጠር መሬት መረጃ Aያያዝ
ዘመናዊ Eንዲሁን መታሰቡ Eና የገጠር መሬት Aጠቃቀም Eቅድ ማዘጋጀት Eንደሚገባ መደንገጉ
የሚሉት ናቸው፡፡

ሁለተኛው ገጽታ በAዲሱ Aዋጅ በርካታ ችግሮች መኖራቸው ሲሆን ዋና ዋናዎቹ የገጠር መሬት ይዞታ
በነፃ ከማግኘት መብት ጋር ተያይዞ የEኩልነት መብትን ያላከበሩ ድንጋጌዎች መኖራቸው፤ የውርስ
ድንጋጌዎች Aሁንም የፍትሐዊነት ችግርን መቅረፍ Aለመቻላቸው፤ ከክርክር Aፈታት ዘዴዎች ጋር
የተያያዙ በርካታ ችግሮች መኖራቸው፤ በAንዳንድ ድንጋጌዎች ላይ Aላስፈላጊ Aገላለጾችና ድግግሞሽ
መኖር Eና ከልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ላይ የሚታዩ ለAሠራር Aስቸጋሪ የሆኑ ችግሮች መኖራቸው የሚሉ
ናቸው፡፡ ከዚህ Aንጻር Eነዚህ ችግሮች በቶሎ ታይተው Eና በAግባቡ ተጠንተው በድንጋጌዎቹ ላይ
ተገቢው ማሻሻያ ቢደረግ መልካም ነው፡፡

32

You might also like