Professional Documents
Culture Documents
59
59
ይበልጣል ይመር
አፅሮተ-ይዘት
በአሁኑ ወቅት ፆታዊ ጥቃት የሚለዉ ሐረግ ለጆሮ አዲስ አይደለም፡፡ ይሁንና ፆታዊ ጥቃት
ማለት ምን ማለት እንደሆነ ትርጉም የሚያስቀምጥ የህግ ድንጋጌ በኢትዮጵያ የለም፡፡ ፆታዊ
ጥቃት፤ ፆታዊ ትንኮሳና አስገድዶ መድፈር የሚሉት ሃረጎች በተግባር ሲደበላለቁ ይስተዋላል፡፡
እነዚህ ሃረጎች በተወሰነ መልኩ የሚገናኙ ግን የሚለያዩም ናቸዉ፡፡ የፆታዊ ጥቃት ትርጉም
ከፅንሰ ሃሳቡ ጋር ሲጣመር ፆታን መሰረት ያደረጉ በሴቶች ወይም በወንዶች ላይ የሚፈፀሙ
ጥቃቶችን ሁሉ ያካትታል፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ ፆታዊ ጥቃትን የሚተረጉም ድንጋጌ
ባይኖረዉም በተበታተነ ሁኔታ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶችን አካቷል፡፡
በሴቶች ላይ የሚፈፀሙት ፆታዊ ጥቃቶች በከፍተኛ ደረጃ የስነ ልቦና ወይም የአእምሮ ጉዳት
በማድረስ ጥቃቱ ከተፈፀመበት ቅፅፈት ጀምሮ እስክ ህይወት ፍፃሜ ድረስ የሚዘልቅ ጠባሳ
ይጥላሉ፡፡ ጉዳቱ ከድብርት እስከ ራስን መጥላትና ራስን ማጥፋት እንደሚደርስ ጥናቶች
ያሳያሉ፡፡ በጤና ላይ ስነ ህይወታዊና አካላዊ መቃወስ ያስከትላሉ፡፡ እነዚህ የስነ ልቦናና የጤና
ጉዳቶች ያለን ንብረት የማጥፋት፤ ስራን መልቀቅ፤ የስራ ችሎታና ፍላጎትን ወዘተ በማሳጣት
የገንዘብ ጉዳት ያደርሳሉ፡፡ የገንዘብ፤ የጤናና የህሊና ጉዳት የደረሰበት ሰዉ ለጉዳቱ ከተቻለ
በተመዛዘነ መልኩ ካልተቻለ በርትዕ ካሳ ማገኘት የሰዎች ተፈጥሮዊ መብት ሲሆን
የመንግስታት ደግሞ ጉዳት ለደረሰበት ሰዉ ፍትህና ካሳ ማስከፈል ወይም መክፈል ግደታ
ነዉ፡፡ ይሁንና ለእነዚህ ጉዳቶች በተሟላ መልኩ የሚያስከፍል የህግ ድንጋጌ የለም፡፡ ይህ
ጥናት የፆታዊ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ሴቶች ያሏቸዉን ፍትሃ ብሔራዊ የህግ ማዕቀፎች ብቻ
የሚዳስስ በመሆኑ የጥናቱ ዘዴ ፅንሰ ሃሳባዊ (Doctrinal) ነዉ፡፡
1
1. መግቢያ
በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች (Violence against Women) እስከ 1980ዎቹ ድረስ በዓለም
አቀፍ ደረጃ ትኩረት ያልተሰጠዉ ጉዳይ ወይም ችግር ነበር፡፡1 ይሁንና በ1980ዎቹ መጀመሪያ
ጀምሮ በየአገራቱ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደራጁ የሴቶች ማህበራት በሴቶች ላይ
የሚፈጸሙ ፆታዊ፤ አካላዊ፤ ስነ ልቦናዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥቃቶች ዓለም አቀፍ
ትኩረት እንዲሰጣቸዉ ጥረት አድርገዋል2፡፡ በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጥቃት ምንድን እንደሆነ
እስከ አሁን ድረስ ሁሉን የሚያግባባና ወጥ የሆነ ትርጉም የለዉም በተለያዩ የሙያ ዘርፎች
እንዲሁም አካባቢዎች የተለያዩ ቃላቶች ይሰጡታል፡፡ ለምሳሌ Family Violence, Gender Based
Violence, Domestic Violence, Spose Abuse, Sexualized Violence, Intimate/ non-intimate partner
Violence…በሚል ይገለፃል፡፡ በዚህ ፅሁፍ በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ሁሉንም ዓይነት ጥቃቶች
ሳይሆን ከሴትነት ጋር የተያያዙትን ጥቃቶች ማለትም Sexual Violence3 ብቻ እንመለከታለን፡፡
ፆታዊ ጥቃት በ መዝገበ ቃላቶች ውስጥ ትክክለኛ ትርጉሙ ምን እንደሆነ ማወቅ አዳጋች
ነው4፡፡ የህግ ትርጉሙን በተመለከተ በኢትዩጵያ ህግጋት ውስጥ ፆታዊ ጥቃት ማለት ምን
1
Ellsberg Mary and Heise Lori, Researching Violence against Women; A Practical Guide for Researcher and
Activists, USA, World Health Organization, 2005, page, 5 available at
https://patth.azureedge.net/media/documents/GBV_rvaw_front.pdf
2
ዝኒ ከማሁ ገፅ 5
3
ለምሳሌ አንድ ወንድ አንዲት ሴትን ቢደበድባት የአካል ጉዳት ወንጀል ነዉ፡፡ ይህም ተራ ወይም ደረቅ ወንጀል ሲሆን አንድ
ወንድ አንዲትን ሴት ቢደፍራት ይህ አድራጎቱ በሴትነቷ ምክንያት የተፈፀመባት ድርጊት በመሆኑ በሴትነት ላይ የተፈጸመ
ወንጀል ወይም ጥቃት (Sexual Violence) በሚል ለመግለፅ ተሞክሯል፡፡
4
ለምሣሌ ዘርጋው ከፍተኛ የአማረኛ መዝገበ ቃላት፡- ጥቃት ማለት 1.ግፍ፣ ጭቆና፣ በደል፣ ወረታ፣ የሃይል እርምጃ ሢለው፡፡
Sexual Violence ምንድን ነው ስንል ደግሞ የተለያዩ መዝገበ ቃላቶች እንደሚከተለው ይተረጉሙታል፡፡ ለምሣሌ፡- Black’s
law Dictionary Sexual Violence The use of physical force, usually accompanied by fury Vehemence or
4
outrage, especially physical force, unlawfully exercised with the intent to harm.
ይህም ወደ አማረኛ ሢመለስ ብስጭት ና በደል የተቀላቀለበት አካላዊ ጐልበትን በመጠቀም ሌሎችን ለመጉዳት በማሠብ
በጉልበት ከህግ ውጭ የፈፀመ ጥቃት ነው ማለት ይቻላል፡፡ Oxford Dickonary በበኩሉ Violence Behavior involving
physical force intended to hurt damage or kill some one or something. በማለት ተርጉሞታል፡፡
2
ማለት እንደሆነ በግልፅ ትርጉም አልተቀመጠለትም፡፡ የኢ.ፊ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግን ብንመለከት
በመፅሃፍ አምስት ስር በሌሎች ሠዎችና በቤተዘመድ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ከአንቀፅ
538 - 661 ደንጓል፡፡ በውስጡ አራት ርዕሶች፣ በእያንዳንዱ ርዕሰ ስር ምዕራፎች፣ በየምዕራፎቹ
ስር ክፍሎች ተዋቅረዋል፡፡ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃት እየተባሉ በልምድ የሚታወቁ
ወንጀሎች በየርዕሶች፣ ምዕራፎችና ክፍሎች ተበታትነው ይገኛሉ፡፡ ለማሣያ ያህል የቤት ውስጥ
ጥቃት /አንቀፅ 564, የሴትን ልጅ ብልት መስፉት አንቀፅ 566 በርዕስ 1 በምዕራፍ 3 ስር
ሢገኙ አስገድዶ መደፈር (አንቀፅ 620) በርዕሰ 4 ምዕራፍ 1 ክፍል 1 ይገኛል፡፡5 በመሆኑም
ፆታዊ ጥቃት ማለት ምን እንደሆነ ትርጉም ካለማስቀመጡም ባሻገር በተበታተነ ሁኔታ
መደንገጉ ድርጊቱን ለመረዳት አደጋች ያደርገዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ የፆታዊ ጥቃት ትርጉምን ስንመለከት የዓለም ጤና ድርጅት (WHO)
Sexual Violence is ‘Any sexual act, attempt to obtain a sexual act, unwanted sexual comments or
advances, or acts to traffic or otherwise directed against a person’s sexuality using coercion, by
any person regardless of their relationship to the victim, in any setting, including but not limited
to home and work’6 በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡ ይህም በግርድፉ ወደ አማርኛ ሢመለስ
“ፆታዊ ጥቃት ማለት ማንኛውም ፆታዊ ድርጊት፡- ፆታዊ ድርጊት ለማግኘት መሞከር፣
ያልተፈለገ ፆታዊ አስተያየት ወይም ሙገሣ ወይም ለማዘዋወር የሚደረግ ድርጊት፡- ወይም
የሰዎችን ፆታዊ ጥቅም በሃይል ለማግኘት የሚደረጉ አድራጐቶች ሆነው፤ ከተጐጅው ጋር
ያለው ግንኙነት ከግምት ውስጥ ሳይገባ በማናቸውም ሁኔታና በስራና በመኖሪያ ቤት ሣይገደብ
የሚፈፀም ድርጊት ነው፡፡” የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡
በሌላ በኩል የጥናትና ምርምር ድርጅቶች7 Sexual violence is defined as: being physically
forced to have sexual intercourse when you did not want to, having sexual intercourse because
you were afraid of what your partner might do, and/or being forced to do something sexual that
you found humiliating or degrading በማለት የስራ ትርጉም ሰጥተዉታል፡፡ ሌላዉ በሴቶች ላይ
የሚደርሱ ፆታዊ ጥቃት ምን እንደሆነ ትርጉም የሠጠው ህግ በ1993 (እ.ኤ.አ) በተባበሩት
መንግስታት ዉሳኔ የፀደቀዉ (Declaration on the Elimination of Violence against Women)
5
የአ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አዋጅ ቁጥር 414/1996፤
6
The World Health Organization (WHO), report, Understanding and addressing violence against women, 2013,
page 2
7
Global and regional estimates of violence against women, page 13
3
/DEVAW/ በሚባል የሚጠራው መግለጫ ነው፡፡ በዚህ ህግ አንቀፅ 1 ላይ “Violence against
women” means any act of gender-based violence that results in, or is likely to result in, physical,
sexual or psychological harm or suffering to women, including threats of such acts, coercion or
arbitrary deprivation of liberty, whether occurring in public or in private life.8
በሴቶች ላይ የሚፈፀም ጥቃት ማለት ፆታን መሰረት ያደረገ ማንኛውም ድርጊት ሆኖ አካላዊ፣
ፆታዊ ወይም ስነ-ልቦናዊ ጉዳትን ወይም ስቃይን በሴቶች ላይ ያስከተለ ወይም ሊያስከትል
የሚችሉ ድርጊቶች፣ ማስገደድ ወይም የጋራ ና የግል ህይወት ነፃነትን ያለህግ መቀማት ነው፡፡
በሚል ሊተረጐም ይችላል፡፡ በተጨማሪም በዚሁ ህግ በአንቀፅ ሁለት ላይ Violence against
women shall be understood to encompass, but not limited to, the following (a) Physical, sexual
and psychological violence occurring in the family, including battering, sexual abuse of female
children in the household, dowry- related violence. Marital rape, Female genital mutilation and
other traditional practices harmful to women, non-spousal violence and violence related to
exploitation.
(b) Physical, sexual or psychological violence with in the general community, including rape,
sexual abuse, sexual harassment and intimidation at work in educational institutions and
elsewhere, trafficking in women and forced prostitution.9 በማለት በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ
ጥቃቶችን ስንረዳ ማካተት ያለባቸውን ብቸኛ ያልሆኑ ድርጊቶችን ዘርዝሯል፡፡ በመሆኑም
በቤተሠብ ውስጥ የሚታዩ አካላዊ፣ ፆታዊና ስነ ልቦናዊ ጥቃት ስንል መጐንተልን ጨምሮ
እንደ በቤት ውስጥ ያሉ ህፅናት ሴቶች ላይ የሚደረጉ ፆታዊ በደሎች፣ በከጥሎሽ ጋር የተያያዙ
ጥቃቶች፣ የጋብቻ ላይ አስገድዶ መደፈር፣ የሴት ልጅን ብልት መተልተል፣ እና ሌሎች ሴቶች
ላይ የሚያደርሱ ጐጅ ልማዳዊ ድርጊቶች እንዲሁም ከጋብቻ ዉጭ ያሉ ጥቃት ነክ
ብዝበዛዎችን ያካትታል፡፡ በማህበረሠቡ ውስጥ ያሉ አካላዊ፣ ፆታዊ ና ስነ-ልቦናዊ ጥቃቶች
ስንል በስራ ቦታ ና በትምህርት ተቋማቶች የሚታዩ የአስገድዶ መደፈር፣ ፆታዊ ጉዳትና ፆታዊ
ትንኮሣና ማስፈራሪያዎችን ያካትታል፡፡ እንዲሁም የሴቶች ህገወጥ ዝውውርና የግዳጅ ሴተኛ
አዳሪነትንም ይጨምራል፡፡
8
.Declaration on the Elimination of Violence against Women Proclaimed by General Assembly resolution
ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች በተለያዩ መልኩ ይገለፃሉ፡፡ ከእነዚህም ዉስጥ ዋና ዋናዎቹ
sexual violence, Sexual harassment, Sexual assault, Sexual abuse ,rape ናቸዉ፡፡ እነዚህ
አገላለፆች በመለዋወጥ ስንጠቀምበት ይስተዋላል፡፡11 በተለይም Sexual Violence, Sexual
Harassment, Sexual Assault የሚሉትን ቃላቶች ልዩነቶች መረዳት ጠቀሜታዉ ከፍ ያለ
በመሆኑ በዚህ ፅሁፍ እንደሚከተለዉ ለማቅረብ ተሞክሯል፡፡
ፆታዊ ትንኮሳ በአለም አቀፍ ደረጃ እዉቅና እየተሰጠዉ የመጣዉ ከ1970ዎቹ በኃላ ነዉ፡፡ እስከ
1970ዎቹ ድረስ ስም እንኳን አልነበረዉም፡፡ በ1970ዎቹ መጀመሪያ ገደማ የአሜሪካ ሴቶች
በሚያደርጉት የሴቶች መብት እንቅስቃሴ (feminist movement) ዉስጥ ፆታዊ ትንኮሳን
በፌዴራሉ የፀረ- ልዩነት ህግ ስር እንዲካተት ጥያቄያቸዉን ማቅረብ ጀመሩ፡፡ በዚሁ መሰረት
በ1970ዎቹ አጋማሽ በወጣዉ የአሜሪካ የፌደራል ሰብዓዊ መብቶች ህግ (federal civil rights
act) ፆታዊ ትንኮሳ ፆታን መሰረት ያደረገ ጉዳት እንደሆነ እዉቅና በመስጠት የህጉ አካል
ተደረገ፡፡ ይሁንና ፆታዊ ትንኮሳ በአለም አቀፍ ደረጃ ብዙም እዉቅና ያልተሰጠዉና ገና በጅምር
ላይ ነበር፡፡ ለዚህም ይመስላል በተባበሩት መንግስታት በ1979 የፀደቀዉ በሴቶች ላይ
የሚደረግ ማንኛዉንም አድሏዊ ልዩነት ማስወገድ ስምምነት ( Conventions on the Elimination
of all forms of Discrimination Aganst Women) /CEDAW/ ላይ ፆታዊ ትንኮሳን አስመልክቶ
ግልፅ ክልከላ ያላስቀመጠዉ፡፡ የኃላ ኃላ በሴቶች ላይ የሚደረግ ማንኛዉንም አድሏዊ ልዩነት
ማስወገድ ስምምነት ኮሚቴዎች ፆታዊ ትንኮሳን እየተገነዘቡትና በሪፖርታቸዉ እያካተቱት
መጡ፡፡ በመጨራሻም በ1989 ፆታዊ ትንኮሳ በሴቶች ላይ የሚፈፀም ጥቃትና የእኩልነት
መብታቸዉን በእጅጉ እየጎዳ ያለ መሆኑን ባቀረቡት ሪፖረት አሳሰቡ፡፡ በዚሁ መሰረት
በተባበሩት መንግስታት ዉሳኔ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ማስወገድ ድንጋጌ
(Declaration on the Elimination of Violence Against Women) /DEVAW/ ፀደቀ፡፡ በዚህ ድንጋጌ
አንቀፅ 2 (ለ) … sexual harassment and intimidation at work in educational institutions and
elsewhere,… በሚል ተካተተ፡፡ ይህም ፆታዊ ትንኮሳና ማስፈራሪያ በትምህርትም ተቋማት፣
በስራ ቦታና በየትኛዉም አካባቢ መፈፀም በሴቶች ላይ የሚፈፀም ጥቃትና አካል ሆኖ ተቆጠረ፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የዓለም አቀፍ የሰራተኞች ድርጅት (ILO) በ1999 ባንግ ኮክ ላይ በካሄደዉ
4ኛዉ የሴቶች ስብሰባ ላይ ፆታዊ ትንኮሳን እዉቅና ሰጠ፡፡ ከዚህ ባሻገር የተባበሩት መንግስታት
ጠቅላላ ጉባኤ በቤጅንግ ቃልኪዳንና የድርጊት ምቹ ሁኔታ The Beijing Declaration and Platform
for Action በ1995 የፀደቀዉ ፆታዊ ትንኮሳ የሴቶችን የእኩልነት መብት የሚጋፋ ድርጊት ነዉ፡፡
ስለሆነም ይህን ድርጊት ለመዋጋት መንግስታት ልዩ ትኩረት በመስጠት እንዲሠሩ
13
ዝኒ ከማሁ ገፅ 2
6
ተስማምተዋል፡፡ ፆታዊ ትንኮሳ በብዙ መልኩ ይገለፃል14፡፡ እነዚህም በአካል ከመንካት እስከ
መጉዳት፣ ምልክት ከማሳየት እስከ ፆታ ነክ ግብዣ፣ በቃላት ወሲባዊ ቀልድ ከመቀለድ እስከ
ወስብ ነክ ስድቦች፣ እንዲሁም በማሞገስ፣ በማድነቅና ልዩ ስጦታ መስጠትን ያካትታል፡፡ ከዚህ
የምንገነዘበው ፆታዊ ትንኮሣ በአካል ወይም በምልክት የሚገለፀው ፆታዊ ፍላጐቶች
(ድርጊቶችን) በሌላኛው ሠው ላይ ማሣደር ነው፡፡ በመሆኑም ፆታዊ ትንኮሣ ድርጊቶች ወንጀል
ናቸው ተብለው በኢትዩጵያ የህግ ሥርዓት አልተካተቱም፡፡
አሁን በቅርቡ የወጣዉ የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር1068/2010 ፆታዊ ትንኮሳን
እንደሚከተለዉ ተርጉሞታል፡፡ “ፆታዊ ትኮሳ ማለት በስራ ቦታ የሚፈፀም ሆኖ ከሌላዉ ወገን
ፈቃድ ወጭ የሚቀርብ የወሲብ ሃሳብ ወይም ጥያቄ ወይም ሌላ ወሲባዊ ተፈጥሮ ያለዉ የቃል
ወይም የአካል ንክኪ ተግባር ሲሆን የሚከተሉትን ያካትታል፡፡
14
Physical conduct • Physical violence • Physical contact, e.g. touching, pinching • The use of job-related threats or
rewards to solicit sexual favours Verbal conduct • Comments on a worker’s appearance, age, private life, etc. •
Sexual comments, stories and jokes • Sexual advances • Repeated social invitations • Insults based on the sex of
the worker • Condescending or paternalistic remarks Non-verbal conduct • Display of sexually explicit or
suggestive material • Sexually-suggestive gestures • Whistling
15
የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር1068/2010 አንቀፅ 2/13 በተመሳሳይ አድሱ የአ.ብ.ክ.መ መንግስት ሰራተኞች
አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀፅ 2/13
7
አንቀፅ 560 የእጅ እልፊት፤ እንዲሁም በአንቀፅ 840 የእጅ እልፊትና ቀላል ሃይል ድርጊት
በሚል ያካተታቸዉን ወንጀሎች የእንግሊዝኛወ ቅጅ አንቀፅ 560 assault; ሲለዉ በአንቀፅ 840
assault and minor acts of violence በሚል ተክቶታል ወይም ተጠቅሟል፡፡ በአንቀፅ 560 ላይ
የተመለከተዉ የእጅ እልፊትን ወይም assault ይዘት ስንመለከት “ማንም ሰዉ የአካል ጉዳት
ወይም የጤንነት ጉድለትን ሳያደርስ በሌላዉ ሰዉ ላይ የእጅ እልፊት ወይም የመግፋት ድርጊት
መፈፀመ” እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ ይሁንና ቀላል የሆኑ ሰንበሮች የደም መቋጠር ምልክቶች
ወይም በቶሎ የሚያልፍ ህመም ወይም ስቃይ እንደ አካል ጉዳት ወይም እንደ ጤና ጉድለት
እንደማይቆጠር ድንጋጌዉ ይናገራል፡፡ በደንብ መተላለፍ ረገድ የተመለከተዉ አንቀፅ 840
እንዲሁ ማንም ሰዉ ሌላዉን ሰዉ ሳይመታ ወይም ሳያቆስል የእጅ እልፊት ወይም ቀላል
የሃይል ድርጊት መፈፀም እንደሆነ ያስረዳል፡፡
በመሰረቱ የወንጀል ህጉ በዚህ የእድሜ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ህጻናት ጋር የግብረ ስጋ ግንኙነት
መፈጸምን ብቻ በመቅጣት አልተወሰነም፡፡ ይልቁንም የግብረ ስጋ ግንኙነትም ባይሆን ይህን
16
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5፣ አንቀፅ 620(1)ና (2)
17
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5 አንቀፅ 625
18
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5 አንቀፅ 626(1)ና (2)
10
የመሰለ ድርጊት ወይም ለንጽህና ክብር ተቃራኒ የሆነ ማናቸውም አይነት ድርጊት የፈጸመ
ወይም በፊታቸው እንዲህ አይነት ተግባርን ያደረገ ወይም ይህ አይነት ድርጊት እንዲፈዕም
/እንድትፈጽም የገፋፋ ማንም ሰው ከሶስት ወር በማያንስ ቀላል እስራት ወይም እስከ አምስት
አመት ሊደርስ በሚችል ጽኑ እስራት እንደሚቀጣ ጨምሮ በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 3 ስር
አስቀምጦ እናገኛለን፡፡ በተለይም የግብረ ስጋ ድፍረቱ የተፈጸመበት ህጻን የአጥፊው ተማሪ
፣የቤት ሰራተኛ፣ በሞግዚትነት ወይም በአደራ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ በእርሱ ቁጥጥር
ስር በሚገኝ ልጅ ላይ ከሆነ አጥፊው ከሶስት አመት እስከ አስር አመት ሊደርስ በሚችል ጽኑ
እስራት የሚቀጣ ሲሆን በሌላ በኩል ተበዳዩዋ ሴት ከሆነች ደግሞ ቅጣቱ ይበልጥ ከብዶ
ከአምስት አመት እስከ ሀያ አመት ሊደርስ በሚችል ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ መሆኑን ከንዑስ
አንቀጽ 4 ለመረዳት ይቻላል፡፡ እንዲሁም የተፈጸመው ድርጊት በንዑስ አንቀጽ 3 የተገለጸው
ከሆነ አጥፊው ከሰባት አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል፡፡ ይህ ሁሉ ድርጊት ከዚህ
አልፎ በተበዳይ ላይ አካላዊ፣ ስነ ልቦናዊ ጉዳትን ወይም ሞትን ያስከተለ እንደሆነ እነዚህን
ድርጊቶች የተመለከቱ ድንጋጌዎች በተደራቢነት ተፈጻሚ እንደሚሆኑም መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡19
በእርግጥ እድሜቸው አስራ ሶስት አመት ያልሞላቸው ሴት ልጆች የአካላቸውም ሆነ የአዕምሮ
ብቃታቸው እድሜያቸው በአስራ ሶስት እና በአስራ ስምንት አመት መካከል ከሚገኙ ሴት ልጆች
ጋር የማይመጣጠን እና የሚፈጸምባቸውም ድርጊት የበለጠ ጉዳት የሚያስከትል ነው፡፡ በዚህም
ምክንያት ይህ ድፍረት የተፈጸመው እድሜዋ አስራ ሶስት አመት ባልሞላት ህጻን ላይ ከሆነ
አድራጊው ከአስራ አምስት አመት እስከ ሀያ አምስት አመት ለመድረስ በሚችል ጽኑ እስራት
ከብዶ የሚቀጣ ሲሆን ፈጻሚዋ ሴት ከሆነች ደግሞ ከአስር አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት
እንዲሆን ተደርጓል፡፡20 ይህ አድራጎት በተለይም ሞትን አስከትሎ ከሆነ ደግሞ ሞትን
የሚመለከተው የዚሁ የወንጀል ህግ ድንጋጌ በተደራቢነት ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ
የአስገድዶ መድፈሩ ወይም በግብረ ስጋ ድፍረቱ ድርጊት እርግዝና ከመጣ ፤ፈጻሚው በአባላዘር
በሽታ መያዙን እያወቀ ተበዳዩዋን /ተበዳዩን ካስያዘ ወይም ደግሞ በደረሰው በደል ጭንቀት
ምክንያት ተበዳይዋ/ተበዳዩ ራሷን/ራሱን ካጠፋ ደግሞ ህጉ ለድፍረት ወንጀሉ ከፍ ያለ ቅጣት
ካላስቀመጠ በቀር ከአምስት አመት እስከ ሀያ አምስት አመት ጽኑ እስራት እንደሚያስቀጣ21
ተቀምጧል፡፡ አስገድዶ መድፈር ወይም ሌሎች የግብረስጋ ግንኙነት በደል ወንጀል የፈጸመ ሰው
19
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5 አንቀፅ 626(4)ና (5)
20
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5አንቀፅ 627(1)ና (2)
21
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5 አንቀፅ 628
11
ብዙውን ጊዜ ከድርጊቱ በኋላ ከተበዳይዋ ጋር ጋብቻ ለመፈጸም የሚያደርገው መስማማት ከክስና
ከቅጣት ለመዳን በመሆኑ በነባሩ ህግ በዚህ አግባብ በሚደረገው ጋብቻ መሰረት የነበረው የክስና
የቅጣት ስረዛ ድንጋጌ ተሽሯል፡፡
23
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5 አንቀፅ 646 (1)ና (2)
24
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5 አንቀፅ 647(1-3)
13
ደግሞ ሴትን መግረዝ ነው፡፡ ይህ ድርጊት ከህጻናት ሴቶች በተጨማሪ በትላልቅ ሴቶች ላይም
ሊፈጸም የሚችል በመሆኑ የድንጋጌው ይዘት ጥበቃውን ሰፋ አድርጎ በየትኛውም የእድሜ ክልል
ያለችን ሴት ሁሉ የሚመለከት ሲሆን ቅጣቱም ከሶስት ወር በማያንስ ወይም ከአምስት መቶ ብር
በማያንስ መቀጮ ተደርጎ ተደንግጓል፡፡ የሴትን ብልት መስፋትም ሴቶችን ለከፍተኛ ስቃይና
ጉዳት የሚዳርግ ጎጂ ልማድ በመሆኑ በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ የሚጣለው ቅጣት ጠንከር ቢል
ውጤት ያስገኛል በሚል ግምት ከአምስት እስከ አስር አመት ሊደርስ በሚችል ጽኑ እስራት ከፍ
ብሏል፡፡ በዚህ ድርጊት ሳቢያም አካላዊ ሆነ የጤና ጉዳት ከደረሰም በወንጀል ሕጉ ከፍተኛ ቅጣት
የሚጥል ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ ቅጣቱ ከአምስት ዓመት እስከ አስር አመት የሚደርስ ጽኑ
እስራት ይሆናል25፡፡ ህጉ ከእነዚህ ልማዳዊ ድርጊቶች ውጭ ያለ፤ ኢ-ሰብአዊና ጎጂነቱ በህክምና
በተረጋገጠ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ምክንያት የአካል፣ የአዕምሮ ጉዳት ወይም ሞት እንዲደርስ
ያደረገ ሰውም በጉዳቱ ቅለትና ክብደት መሰረት እንደሚቀጣ በተጨማሪነት መገንዘብ ይገባል26፡፡
25
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5 አንቀፅ 566
26
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 5 አንቀፅ 567
14
የሚደርስ ጽኑ እስራት ተደርጓል፡፡ እነዚህ ድንጋጌዎች ሴትን መጥለፍ የተመለከቱ ድንጋጌዎች
በየትኛው የእድሜ ክልል የሚገኙትን ሴቶችን እንደሚመለከት ያስቀመጠ አይደለም፡፡ ከዚህም
በመነሳት ተጠላፊው ሴትም ሆነ ወንድ ድርጊቱ የተፈጸመው በእድሜያቸው የተነሳ ልዩ ጥበቃ
የሚያስፈልጋቸው አካለ መጠን ያላደረሱ ህጻናት (ማለትም ከአስራ ስምንት አመት በታች
የሆኑትን) ላይ በሆነ ጊዜ ተፈጻሚ የሚሆን ድንጋጌ በአንቀጽ 589 ተለይቶ ተቀምጧል፡፡
ድንጋጌው ከአምስት እስከ አስራ አምስት አመት ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ ሲሆን እንደወንጀሉ
የአፈጻጸም ሁኔታ፤ ክብደት እና ቅለት መሰረት ያደረጉ ቅጣቶችም በዝርዝር ተደንግገዋል፡፡
የዓለም አቀፍ የጤና ድርጅት (WHO) የ2013 ሪፖርት በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች
በየትኛውም የአለም ክፍል እየጨመሩ መሆኑን ያሳያል፡፡ እንደ ሪፖርቱ ግኝት ከሆነ በዓለም
ላይ ካሉ ሴቶች ውስጥ 35% ያህል በቅርብ ጓደኞቻቸው ወይም ጓደኞቻቸው ባልሆኑ ሠዎች
ጥቃት ይፈፀምባቸዋል27፡፡ እንደዚህ ሪፖርት ገልፃ በዓለም አቀፍ ደረጃ 38% የሚሆኑት ሴቶች
ግድያ የተፈፀመው በቅርብ ጓደኞቻቸው ነው28፡፡ በሴቶች ላይ ፆታዊ ጥቃት ከተፈፀመባቸው ጊዜ
ጀምሮ ተጎጅዎች የአካል፤ የስሜት፤ የአእምሮና የፀባይ መለዋወጥ እንዲሁም ያልተለመደ
ምልክት ይታይባቸዋል፡፡ በስሜታቸዉ ላይ የሚታዩ መለዋወጦች ከትንሹ ፍርሃት ጀምሮ ራስን
እስከ ማጥፉት29 ይደርሣል፡፡
የፆታዊ ጥቃት ሠለባ የሆኑ ሤቶች ቀድሞ ባልነበረባቸው ሁኔታ ፍርሃት (fear)
ያደርግባቸዋል፡፡ በተለይም ድጋሜ ጥቃት ይደርስብኛል በሚል መፍራት፣ ድርጊቱ
የተፈፀመበትን ሁኔታ መፍራት፤ ምሣሌ ጥቃቱ የተፈፀመው በማታ ቢሆን ማታን መፍራት፣
ማህበራዊ ግንኙነቶችን መፍራት ጥቃቱ የተፈፀመው ገበያ እሄደች ባለች ሴት ላይ ቢሆን ገበያ
መሄድን መፍራት በጥቃቱ የተነሣ የጤና ችግር ያደርስብኛል ብሎ መፍራት ሊሆኑ ይችላል30፡፡
27
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 7 ገፅ 9
28
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 7 ገፅ 9
29
Gender based violence, Health and the role of health sector, 2009, page3 available at
siteresources.worldbank.org/INTPHAAG/Resources/AAGGBVHealth.pdf
30
Evelyne Josse, “They came with two guns” The Consequences of Sexual Violence for the Mental Health of
Women in Armed Conflicts, 2010, The International Review of the Red Cross, Volume 92, Number 877, page 184
15
ሌላው ከፍርሃት ከፍ ያለው ደረጃ ስጋት (Anxity) የሚባለው ነው፡፡ ስጋት ከፍርሃት የሚለየው
ምንም ዓይነት የጥቃቱን አስታዋሽ ነገሮች በሌሉበት ደህንነት አለመሠማት ነው፡፡ ፆታዊ ጥቃት
የደረሰባቸው ሴቶች ሌላ ጥቃት በቤተሠቦቸ (በልጆቼ፣በእህቶቼ፣ በጓደኞቸቼ ወዘተ) ይደርሣል
ብሎ መስጋትም ሌላኛው አስከፊ ገፅታ ነው፡፡ ስጋቱ እየዋለ ሢያድር ትኩረት ማጣትና
እንቅልፍ ማጣትን ያስከትላል31፡፡
በሌላ መልኩ መገለፅ ያለበት ስነ-ልቦናዊ ጫና ድብርት (depression)33 ነው፡፡ ድብርት ውስጥ
ያለች የፆታዊ ጥቃት ሠለባ ሤት ተስፉ መቁረጥና ሀዘን ይታይባታል፡፡ በህይወት ለመኖር
ፍላጐት አይኖራትም ማልቀስ፣ ራስን ስለማጥፋት ማሠብ፣ ወዘተ የመሣሠሉ ምልክቶች
ይታዩባታል፡፡
በመጨረሻ ሊታይ የሚገባው ሄድ-መጣ የሚባለው የደስታ ስሜት (Euphoria) በጾታዊ ጥቃት
ተጐጅዎች ላይ ይስተዋላል፡፡ እንዲሁም ለሌላው ዓለም አለመጨነቅ በተለይም ለስራ፣
ለትምህርት፤ ለጓደኛ ግዴለሽ መሆን ያጋጥማል፡፡
31
ዝኒ ከማሁ ገፅ 185
32
ዝኒ ከማሁ ገፅ 186
33
ዝኒ ከማሁ ገፅ 184
34
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 1 ገፅ 23
16
ከዚህ በላይ የተመለከትናቸው የስነ-ልቦና ጉዳቶች የአካላዊ ምቾት ማጣት ምልክቶች
(Physiological Symptoms) ያመጣሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ ዋነኞቹ የውስጣዊ የአካል ክፍሎች
አሠራር ማዛባት፤ ማለትም የአተነፉፈስ፣ የደም ዝውውር፣ የምግብ መፈጨትና መወገድ
ሥርዓት ላይ ተፅእኖ ይፈጥራሉ፡፡ በፍርሃት፣ ስጋት፣ ጭንቀትና ድብርት ውስጥ ያሉ ሴቶች፣
ማስተወክ፣ ማላብ፣ ማስቀመጥ የመሣሠሉ ህመሞች ይታዩባቸዋል፡፡ ሌላኛው ጉዳት ወሢብ
የመፈፀም እክል (Sexual dysfunctions)35 ናቸው፡፡ የፆታዊ ጥቃት የደረሠባት ሴት የወሲብ
ፍላጐት የላትም ከዚህም አልፎ ወሲብን መጥላት፣ በወሲብ አለመርካት ይታይባታል፡፡ በሌላ
መልኩ ከወር አበባ አለመኖር፣ የወር አበባ መብዛት፣ እንዲሁም የተዛባ የወር አበባ (Menstrual
disorders) ያጋጥማታል፡፡
በእርግጥ የስነ-ልቦና ችግር የጤና ችግር ነው፡፡ የጤና ችግር ከዚህ በተጨማሪም በአካል ላይ
የሚታዩ የጤና መጓደሎችን ለማለት ነው፡፡ ፆታዊ ጥቃት የደረሠባቸው ሴቶች ውስብስብ ለሆኑ
የአካል ነክ ጤና ችግሮች ያደርጋሉ፡፡ በተለይም የአስገድዶ መደፈር ጥቃት የደረሠባቸው ሴቶች
§ ያልተፈለገ እርግዝና
§ ላልተፈለገና ያለጥንቃቄ ለሚፈፀም ውርጃ
§ ኤች አይ ቪ ኤዲስን ጨምሮ ለሌሎች በግብረ ስጋ ግንኙነት ለሚተላለፉ በሽታዎች
§ ግብረ ስጋ ግንኙነትን የመፈፀም እክል (Sexual dysfunctions)
§ መካንነት
§ ለሽንት ባንባ ቁስለት
§ የወገብ ህመምና /የወገብ አጥንት የሚያስቆጣ በሽታ36 (pelvic pain and pelvic
inflammatory disease) በሴቶች ላይ የሚፈፀም የአስገድዶ መደፈር ጥቃት በሴቶች
የመራቢያ አካላት (ብልት) ላይአካላዊ የሆነ የጤና ችግር ያስከትላል፡፡
በተለይም እንደ
v የብልት መቀደድ
v የብልት መላላጥ
35
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 30 ገፅ 3
36
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 11 ገፅ 12
17
v የብልት መቅላት
v የብልት ማበጥ (ደም መቋጠ)
v ሰንበር ማውጣት
v ራስ ምታት
v ድካም37፣ ወዘተ ህመም ያስከትላል::
37
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 11 ገፅ 12
38
Non fatal and Fatal Outcomes of sexual violence ( Direct & Indirect Physical and Mental Health proplems)
Injury, Post traumatic stress, Femicide , Functional impairment, Depression, Suicide, Physical symptoms,
Anxiety, Maternal mortality, Poor subjective health, Phobias/panic disorders, AIDS-related , Permanent
disability
39
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 1 ገፅ 9
40
Wafaa Abdelhadi Honour Crimes and Violence against Women Preventing and Punishing Honour Crimes 2016,
Tilburg University available at arno.uvt.nt/show.cgi?fid=139874, page 10
18
3. በኢትዮጵያ ህግጋት የተካተተ የፆታዊ ጥቃት መፍትሔዎች
3.1. በወንጀል የፍትህ አስተዳደር የተደነገጉ መፍትሔዎች
በወንጀል ህጉ
41
የወንጀል ህግ አንቀፅ 620(3)፤ 626(5)፤ 627(5) የአስገድዶ መድፈር ድርጊት ሞትን ያስከተለ እንደሆነ ቅጣቱ የእድሜ ልክ
እንደሚሆን ያሳያል፡፡
19
ቢሆንም እንዲሁም በአካል ከሚታዩ ጉድለቶች እስከ የአእምሮ ጠንቅ እስከሚሆኑት ጉዳቶች
ሁሉ ተበድያለሁ የሚል ሠው የጉዳት ካሣ የሚያገኝበት ሥርዓት ተዘርግቷል ማለት ነው፡፡
20
እልፊት፣ ማቁሠል ወዘተ እንደቀላል ጉዳት ተቆጥረው ካሣ አያስጠይቁም ወደሚል
ማደማደሚያ ያደርሠናል፡፡ ይህም ትክክል አይመስልም፡፡
21
ሌላው በዚህ ድንጋጌ መታየት ያለበት የካሣዎቹ ዓይነት ምንድን ናቸው የሚለው ነው፡፡
በድንጋጌው በግልፅ እንደሚታየው፡-
የጉዳት ካሣ ደግሞ በፍትሃብሔር ህጉ 2090ና 2092 ግልፅ የሆኑ ጉዳቶች (ዕለታዊና ለወደፊት
ሊደርስ የሊችሉ ጉዳቶች እንዲሁም 2105 የህሊና ጉዳት) ሁሉ ሊያካትት ይችላል፡፡
“(1) ወንጀለኛው ወይም ስለ እርሱ ተጠያቂ የሆኑት እንደነገሩ ሁኔታና ወይም በኑሮአቸው
ምክንያት በተበዳዩ ላይ ለደረሠው ጉዳት ሊክሱ የማይችሉ መሆናቸው በታወቀ ጊዜ
ከወንጀለኛው ላይ ከተያዘው ገንዘብ ውስጥ ወይም ከመቀጮው ውስጥ ወይም በጉልበት ሥራ
ተለውጦ ከሚያገኘው ገቢ ሂሣብ ውስጥ ወይም ከተወረሠው ንብረት ሂሣብ ውስጥ ለተበዳዩ
እንዲከፈል ፍርድ ቤቱ ለማዘዝ ይችላል፡፡
(2) መንግስት ለተበዳዩ በከፈለው የካሣ ገንዝብ ልክ ለተበዳዩ መብት ተተክቶ ጉዳቱን ባደረሠው
ወንጀለኛ ላይ በቀጥታ ሊጠይቅና ሊቀበል ይችላል” በሚል ተደንግጓል፡፡
ከዚህ ድንጋጌ የምንገነዘበው በዳዩ መካስ የሚችል ከሆነ በጉዳቱ ልክ እንዲከስ ማድረግ መርህ
ሆኖ በዳዩ መካስ የማይችል መሆኑ ከታወቀ ግን ከተያዘው ዕቃ፣ ከዋስትና መያዝ፣ ከመቀጮ፣
በጉልበት ስራ ከተገኘው ንብረትና ከተወረሠው ንብረት ላይ ለተበዳዩ ካሣ ሊካፈል እንደሚገባ
ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሁሉ ነገሮች ባይኖሩስ እንዴት ይሆናል? የሚል ጥያቄ ማንሳት
ይገባል፡፡ በተጨማሪም ንፁስ ቁጥር ሁለት መንግስት በተበዳዩ በከፈለው የካሣ ገንዘብ ልክ
በተበዳዩ መብት ተተክቶ በወንጀለኛው ላይ ጥያቄ እንደት ያቀርባል? ማለትም መንግስት ስለ
ወንጀለኛው ሆኖ ለተበዳዩ ካሣ የሚከፍልበት አጋጣሚ አለን? ወይስ ከላይ ከተዘረዘሩት
ማለትም ከዋስትና ገንዘቡ ከመቀጮው ከተወረሠው ወዘተ ንብረት ላይ ለተበዳዩ ስለተከፈለ
ይህንን ገንዘቡን ነው መንግስት ተተክቶ የሚጠይቀው የሚሉት ነጥቦች ምላሹ ያስፈልጋቸዋል፡፡
22
በሃተታ ዘምክንያቱ ላይ “በቁጥር 105 (2) በዳዩ ወይም ስለእርሱ መብት ያላቸው ለበዳዩ
ሊክሱ በማይችሉ ጊዜ ፍርድ ቤቱ ሊያዝባቸው ከሚችሉት አማራጮች ውስጥ በዋስትና መያዝ
ስም ካስያዘው ገንዝብ ውስጥ በሚለው ሀረግ በተጨማሪ “ከመቀጮው ውስጥ” የሚል ሃረግ
ተጨምሯል፡፡ ይህም ተበዳዩ ሊካስበት የሚችለው አማራጭ መንገድ ከፍ እንዲያደርግለት
ያስችላል በማለት ነው የሚል ምክንያት ተቀምጧል፡፡” ከዚህ ውጭ መንግስት ለተበዳዩ በአንቀፁ
ከተመለከቱት ውጭ ስለመክፈሉ ወይም ስላለመክፈሉ የተገለፀ ነገር የለም፡፡
በፀሃፊዉ እምነት የአንቀፀ 102 (2) መንግስት ለተበዳዩ በከፈለው የካሣ ገንዝብ ልክ ለተበዳዩ
መብት ተተክቶ ጉዳቱን ባደረሠው ወንጀለኛ ላይ በቀጥታ ሊጠይቅና ሊቀበል ይችላል የሚለዉ
አገላለፅ ከተያዘው ዕቃ፣ ከዋስትና መያዝ፣ ከመቀጮ፣ በጉልበት ስራ ከተገኘው ንብረትና
ከተወረሠው ንብረት ላይ ለተበዳዩ ካሳ በተከፈለዉ ጊዜ መንግስት ከእነዚህ ጉዳዮች ላይ
የሚያገኘዉ ገቢ ስለቀረበት (ማለትም ለተበዳዩ በካሳ መልክ ስለተከፈለ) ይህንን የቀረበትን ገቢ
ከጉዳት አድራሹ ላይ እንዲያገኝ ያለመ ነዉ፡፡ በመሆኑም አንቀፀ 102 (2) መንግስት ስለ
ወንጀለኛው ሆኖ ለተበዳዩ ካሣ የሚከፍልበትን ስልት የፈጠረ አይደለም፡፡ በሌላ አነጋገር የተያዘ
ዕቃ ወይም የዋስትና የመቀጮ ገንዘብ ወይም በጉልበት ስራ የተገኘና ከተወረሠው ንብረት በሌለ
ጊዜ መንግስት ለተበዳዩ ካሳ የሚከፍልበት ህግ አይደለም፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትህ ሚኒስቴር በ2003 ዓ.ም የወንጀል ፍትህ ፖሊሲ አዘጋጅቷል፡፡ ምንም እንኳ
ፖሊሲዉን መሰረት ያደረገ በዚህ ርዕስ ዙሪያ ስራ ላይ የዋለ የወንጀል ህግ ባይወጣም
የወንጀል ጉዳት የደረሰባቸዉ ሰዎች ካሳ እንዲያገኙ የሚያስችሉ የህገ ማዕቀፍ ሊኖሩ እንደሚገባ
ተመልክቷል፡፡ በፍትህ ፖሊሲዉ ክፍል ስድስት ስር በወንጀል ጉዳት የደረሰባቸዉን ሰዎች
መብት ስለማክበር በሚል ንዑስ ርዕስ ስር በወንጀል ጉዳት የደረሰባቸዉን ሰዎች መብት
በአግባቡ ማስከበር እንዲቻል የተፈፀመዉ የወንጀል ዓይነት ወይም የተጎጂዉን ግላዊ ሁኔታ
መሰረት ያደረገ እና ለልዩ ለልዩ ፍላጎቶቻቸዉም ተገቢዉን ምላሽ በመስጠት ላይ ያተኮረ
አሰራር በወንጀል ፍትህ ሥርዓቱ ዉስጥ እንዲዘረጋ ይደረጋል፡፡ ሕፃናትን ጨምሮ በሌሎች
ሁኔታዎች በወንጀል ድርጊት ለሚደርስ ጉዳት ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች ተገቢዉን ጥበቃ
እና ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችሉ ልዩ የድጋፍ እርምጃዎች ይወሰዳሉ፡፡ በወንጀል ድርጊት
ጉዳት የደረሰባቸዉ ሰዎች ለደረሰዉ ጉዳት በፍርድ ቤት ወይም በሌሎች አማራጭ ዘዴዎች
23
የካሳ ጥያቄ በማቅረብ ተገቢዉን ካሳ በአፋጣኝ እንዲያገኙ ማድረግ የሚያስችል አመች የሆነ
የአሰራር ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባል፡፡ የወንጀል ተጎጂዎች በተፈፀመባቸዉ የወንጀል ድርጊት
ሳቢያ ከደረሰባቸዉ ሥነ ልቦናዊ ቀዉስ እና ካጋጠማቸዉ ሌሎችም ተያያዥ ችግሮች በአግባቡ
እንዲላቀቁ ተገቢ የሆነ ድጋፍ እና የምክር አገልግሎት የሚያገኙበት ሥርዓት መዘርጋት
ይኖርበታል በሚል ተመልክቷል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ብሔራዊ የሰብዓዊ መብቶች የድርጊት መርሃ ግብር የፆታዊ
ጥቃት ተጎጂ ሴቶችን የሚደግፍና የሚንከባከብ ጊዜያዊ መጠለያ በሁሉም ክልሎችና የከተማ
አስተዳደሮች ቢያንስ አንደ መጠለያ ማዕከል ሊዘጋጅ እንደሚገባ ተቀምጧል፡፡
እዚህ ላይ የሌሎች ሃገራትን ተሞክሮ እንመልከት
እንግሊዝና ዊልስ
እንግሊዝና ዊልስ የወንጀል ጥቃት ሠለባ የሆኑ ዜጐች በመንግስት የሚካሱበት ሥርዓት አለ፡፡
ይህ ሥርዓት የሚተገበረውም የወንጀል ጉዳት ካሣ ባለስልጣን (Criminal Injuries Compensation
Authority (CICA)42 በሚባለው የመንግስት አደረጃጀት ነው:: ይህ መስሪያ ቤት የአካል
ጉዳቶችን እና የሚካሱበትን ታሪፍ በመዘርዘር ለተጐጅዎች ካሣ ይከፍላል፡፡ የአእምሮ ጉዳት
መነሻው የአካል ጉዳት ወይም የፆታዊ ጥቃት ከሆነ ካሣ ይወሠንለታል፡፡ በዚህ ህግ የአካል
ወይም የአእምሮ ጉዳት የደረሰባቸው ሠዎች እንደ ንፁሃን ተጐጅዎች ተቆጥረው ወንጀለኛዉ
ቢቀጣም፣ ባይጠየቅም ወይም ቢከሰስም ባይከሠስም እንዲሁም ቢታወቅም ባይታወቅም ካሣ
የማግኘት መብት አላቸው43፡፡ የተጐጅዎች ግዴታ ጥቃቱ በተፈፀመባቸው ጊዜ ለፖሊስ
ማሣወቅና ለምርመራ መተባበር ነው፡፡ የአእምሮ ጉዳት ደርሷል የሚባለውም በህክምና
የተረጋገጠ የሣይካትሪክ ወይም የሳይኮሎጅካል ህመም ሢኖር ነው44፡፡ እነዚህም ከጥቃት በኃላ
የሚከሰት የአእምሮ መታወክ (Post Traumatic Stress Disorder)፣ ድባቴና የመሣሠሉትን45
42
The Criminal Injuries Compensation Schame, 2012, Ministry of Justice available at
http://www.nationalarchives.gov.uk/doc/open-government-licence
43
Vinson and Elkins, Compensation for the Mental Suffering of Rape Victims and Rape and Prostitution Laws
Relating to Minors: A Comparative Study, 2013, Beijing Zhongze Women’s Legal Counseling and Service Center,
page 20
44
ዝኒ ከማሁ ገፅ, 18
እንደ
45
Anxiety, tension, insomnia, irritability, loss of confidence, agoraphobia and
preoccupation with thoughts of guilt or self-harm
24
ያካትታል፡፡ ድባቴው የሚቆይበት ጊዜን በግምት ውስጥ ያስገባ ካሣ እንደሚከፈል ታሪክ
ያሳያል46፡፡
የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ወይም ሙከራ የደረሠባቸው ሴቶች ጥቃቱ ወይም ሙከራዉ
ሊያስከትልባቸው የሚችልው የስነ-ልቦና ከፍተኛ ነው በሚል ምክንያት በቂ ካሣ መንግስት
ይክሣቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአስገድዶ መድፈር ጉዳት የደረሠባቸው ሴቶች በበዳዩ ላይ
የፍትሃብሔር ክስ የማቅረብ መብት አላቸው፡፡ እንድሁም የወንጀሉን ጉዳይ ለሚያየው ፍርድ
ቤቱ ለደረሠባቸው ጉዳት ካሣ እንዲከፈላቸው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ ይሁንና የወንጀሉን ጉዳይ
በሚያየው ፍርድ ቤት አማካኝነት ወንጀለኛው ወደ ማረሚያ ቤት ከተላከ በዚሁ ችሎት ካሣ
መጠየቅ አይችሉም47፡፡
ካናዳ
ካናዳ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የፌደራል ስርዓት የምትከተል ሃገር ነች፡፡ በመሆኑም በሁሉም
የሃገሪቱ ክልሎች ተፈፃሚነት ያለው የወንጀል ህግ አላቸው48፡፡ ይሁንና ክልሎች የራሣቸው
የሆነ የወንጀል ድርጊት ሠለባዎች ካሣ ህግ አላቸው፡፡ በተለይም የአልበርታና የኦንታርዮ
የተባሉትን ግዛቶች የወንጀል ፍትህ ሥርዓት በጥቂቱ እንመለከታለን፡፡ በአልበርታ ግዛት
የተጐጅዎች ወንጀል ህግ (Victims of Crime Act) ወይም የAlberta Compersation Act የሚባል
ህግ አለ፡፡ በዚህ ህግ የስነ-ልቦና ጉዳቶች ውስጥ በአስገድዶ መደፈር ጥቃት ስነ ልቦናቸዉን
የተጐዱ ሴቶች የሚካሡበት ደንብ ሲኖር ይህም የተጀመረው የወንጀል ተጠቂዎችን በገንዘብ
የመደገፍ ዕቅድ (The Victims of Crime Financial Benefits Program) አካል ነው49፡፡ ይህም
በግዛቷ የፍትህ ቢሮ የህዝብ ደህንነት ክፍል ሆኖ ተደራጅቷል፡፡ በመሆኑም ጥቃት የደረሠበት
ሠው ወንጀሉን በተገቢው ጊዜ ለፖሊስ ማመልከት ይኖርበታል፤ እንዲሁም አስፈላጊ የሚባሉ
መረጃዎችን፣ ሠነዶችን፣ የምርመራ ውጤቶችን ወዘተ ለፖሊስ ለመስጠት ተባባሪ መሆን
አለበት50፡፡ ካሣ ለማግኘት የሚቀርብ ማመልከቻ ከሁለት ዓመት በኋላ እንደማይቀርብ
ተደንግጓል፡፡ የጥቃቱ አደገኛነትና ጐጅነት ከግምት ውስጥ እየገባ እንደየ ጉዳዬች የሚከፈል
46
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 43 ገፅ 18
47
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 43 ገፅ 19
The Criminal Code of Canada, 1985
48
49
The Alberta Compensation Act established the Victims of Crime Fund and introduced the Victims of
Crime Financial Benefits Program.
50
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 43 ገፅ 12
25
የካሣ ገንዘብ አለ፡፡ የአስገድዶ መደፈር ወንጀልን አስመልክቶ በመንግስት ከሚከፈለው የጉዳት
ካሣ በተጨማሪ ተጐጅዎች በፍርድ ቤት ተጨማሪ ካሣ የሚጠይቁበት ሥርዓት አለ፡፡
በመሆኑም የግዛቱ ዐ/ህግ በወንጀለኛው ላይ ማንኛውንም ጉዳትና ኪሣራ አስመልክቶ ካሣ
ለተጐጅዎች እንዲከፈል መጠየቅ ይችላል፡፡ ጉዳቱም የስነ-ልቦና ችግሮች ጨምሮ ሌሎች
ጉዳቶች ሁሉ እንዲካሡ የሚደረግ ነው51፡፡
ሌላኛው የካናዳ ክልል (ግዛት) ኦንታርዮ ነች፡፡ በአንታርዬ የካሣ ህግ መሠረት የተቋቋመው
የወንጀል ተጠቂዎች የካሣ ቦርድ አለ፡፡ ይህ ቦርድ የወንጀል ጥቃት ያደረሡ ድርጊቶችን
በመዘርዘር እንዴት እንደሚካሱ ይሠራል፡፡ በዚህ ህግ መሠረት ፆታዊ ጥቃት በቀጥታም ይሁን
በተዘዋዋሪ መልኩ በሴቶች ላይ ጉዳትና ህመም እንዲሁም ሞት ያስከተለ እንደሆነ ካሣ
እንደሚከፈላቸው ይወሰናል52፡፡
51
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 43 ገፅ 12
52
የግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 43 ገፅ 13
53
የኢትዮጵያ ፍትሃብሔር ህግ (1952)፣ 4ኛ መፅሃፍ ስለግደታዎች በሚለዉ 13ኛ አንቀፅ ከቁጥር 2027-2161 ተደንግጓል፡፡
54
ንጋቱ ተስፋዬ ከዉል ዉጭ አላፊነት እና አላግባብ መበልፀግ ህግ፤ 1999 ዓ.ም ሁለተኛ እትም፤ ገፅ 129
55
ግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 53፤ (ኢትዮጵያ ፍትሃብሔር ህግ) አንቀፅ 2090፤ 2092፤ የህሊና ጉዳት አንቀፅ 2105
26
compensation)56ናቸዉ፡፡ በእነዚህ ዘዴዎች የሚካሱት የገንዘብ ወይም የህሊና ጉዳት
የደረሰባቸዉ ተጎጅዎች እንደሆኑ የኢትዮጵያ ፍትሃብሔር ህግ ከአንቀፅ 2090-2123
ያስገነዝባል፡፡ የካሳ አከፋፈል ስርዓቱም ለደረሰዉ የገነዘብ ጉዳት የተመዛዘነ ወይም የተመጣጠን
ካሳ መክፈል57፤ በርትዕ ካሳ መክፈል58፤ ዕቃን በመመለስ፤ በዓይነት በመተካት፤ የማደሻና
የማገጃ ትዕዛዝ በመስጠት59 መካስ እንደሚቻል ተመልክቷል፡፡
56
ግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 53፤ (ኢትዮጵያ ፍትሃብሔር ህግ)፣ በገንዘብ መካስ ከአንቀፅ 2090-2117 እንዲሁም በሌላ አኳኃን
መካስ ከአንቀፅ 2118-2123 ተመልክተናል፡፡
57
ግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 53፤ (ኢትዮጵያ ፍትሃብሔር ህግ)፣ አንቀፅ 2090፤ 2091
58
ግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 53፤ (ኢትዮጵያ ፍትሃብሔር ህግ)፣ ከአንቀፅ 2099- 2104
59
ግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 53፤ (ኢትዮጵያ ፍትሃብሔር ህግ)፣ ከአንቀፅ 2118-2123
60
ግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 54፤ (ንጋቱ ተስፋዬ)፤ ገፅ 54
27
ይሁንና የዚህን አንቀፅ ልዩ ሁኔታዎች ህጉ በዝርዝር በአንቀፅ 2039 ላይ ሰውነትን መጉዳት
በሚል ተከሳሽ የሆነ ሰዉ ጥፋተኛ የማያስብሉት በቂ ምክንያቶች ናቸዉ የተባሉትን ከዚህ
በታች በተመለከተዉ መልኩ በዝርዝር አስቀምጧቸዋል፡፡
ሌላዉ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃት የተመለከተዉ በአንቀፅ 2114 ላይ ያለዉ የንፅህና
ክብር ስለመድፈር (sexual outrage) ነዉ፡፡
ይህም ፡- (1) ማንኛዉም ሰዉ በመድፈር ስራ ወይም ለክብር ንፅህና ተቃራኒ በሆነ ተግባር
በወንጀል የተቀጣ እንደሆነ ዳኞቹ ለተደፈረችዉ ሴት ለደረሰባት የህሊና ጉዳት ማካካሻ
የሚሆን ተገቢ ካሳ ለመቁረጥ ይችላሉ፡፡
(2) አንዲት ሴት ወይም ልጃ ገረድ በሃይል የተደፈረች እንደሆነ ለሴቲቱ ባል ወይም
ለተገሰሰችዉ ልጃ ገረድ ቤተዘመዶች ተገቢ የህሊና ጉዳት ካሳ ሊቆረጥ ይቻላል፡፡
61
ግርጌ ማስታዎሻ ቁጥር 53፤ (ኢትዮጵያ ፍትሃብሔር ህግ)፣ አንቀፅ 2116(3)
28
ሊደርስባት የሚችለዉን የስነ ልቦና ጠባሳ (እንደ ፍርሃት፤ ጭንቀትና ድብርት የመሳሰሉትን)
ሙሉ በሙሉ ፍትሃብሔራዊ መፍትሔ አግኝቷል ለማለት አይቻልም፡፡
1. ማጠቃለያ
62
የባህር ዳር ከተማ ፍትህ ፅ/ቤት ዐ/ ህግ ከአቶ ዮሃንስ…. (መዝገብ ቁጥር 428/10 በቀን 3/02/10 ዓ.ም የቀረበ ክስ)
በአንድ የህክምና ምርመራ ዉጤት የተገለፁት ፍሬ ነገሮች የሚያሳየዉ “…በተደረገዉ የማህፀን አካላዊ ምርመራ
በታችኛዉ ብልቷ ጫፍ 2 ሴንቲ ሜትር የሚሆን የድንግልና ንጣፍ መሰንጠቅ ታይቷል፡፡ ይህም የክብረ- ንፅህና
መገርሰስን ያረጋግጣል፡፡ ብልቷም በደም ተነካክቷል፡፡ የኤች አይ ቪ፤ የጉበት ቫይረስ፤ የአባለዘርና የእርግዝና
ምርመራ ዉጤቱ ለጊዜዉ ነፃ እንደሆነች ያሳያል” ይላል፡፡ በዚሁ ክስ ዝርዝር ላይ ….ተከሳሹ የሃይል ድርጊት በመጠቀም
አስገድዶ በመድፈር ክብረ ንፅህናዋን የገሰሰና ግራ ጡቷንና ግራ ጆሮዋን ነክሶ ጉዳት ያደረሰባት መሆኑ ተመልክቷል፡፡ ይሁንና
የተከሰሰዉ በአስገድዶ መድፈሩ ብቻ ነዉ፡፡ የህክምና ምርመራዉና ዉጤቶም እነዚህን ሁሉ ጉዳቶች አላከተተም፡፡
63
የባህር ዳር ከተማ ፍትህ ፅ/ቤት ዐ/ ህግ ከአቶ ደርባቸዉ…..(መዝገብ ቁጥር 98/10 በቀን 6/11/09 የቀረበ ክስ) “ተከሳሹ የሃይል ድርጊት
በመጠቀም ወይም በብርቱ ዛቻ ግል ተበዳይን በግምት 5፡30 ፀጉሯን ይዞ በመጎተት ባጃጅ ዉስጥ አስገብቶ ወደ
ሆቴል ወስዶ አልጋ ይዞ አስገድዶ ደፍሯታል…”63 ይላል፡፡
29
ፍትህ ላንዱ ጉዳት ያደረሰበት ሰዉ በፈፀመዉ ጉዳት በወንጀል ተቀጥቶ ማየት ሲሆን ለሌላ
ፍትህ አገኘሁ የሚለዉ በወንጀል ድርጊቱ የተነሳ ያጣዉን ገንዘብና ጥቅም ወይም የተጎዳዉን
አካሉንና አእምሮዉን የሚጠግን ማካካሻ በካሳ መልክ ሲያገኝ ነዉ፡፡ ለሌላዉ ጉዳት አድራሹ
በፈፀመዉ ድርጊት ተፀፅቶና ደንግጦ ተጎጅዉን ይቅርታ ሲጠይቀዉ ፍትህ አገኘሁ ሊሆን
ይችላል፡፡ እንዲሁም አንዳዱ እዉነታዉን ለማህበረሰቡ ወይም ጉዳት አድራሹ በቀጥታ መናገር
ነዉ64፡፡ የኢትዮጵያ የወንጀል ህግ ዓላማ ለጠቅላላዉ ጥቅም ሲባል የህዝቦቹንና የነዋሪዎቹን
ሰላምና ደህንነት መጠበቅና ማረጋገጥ በመሆኑ ወንጀል ሲፈፀም ወንጀለኛዉ የሚቀጣዉ
ለጠቅላላዉ ጥቅም ሲባል (ማለትም ተጨማሪ ወንጀል እንዳይፈፅም ወይም ለሌላዉ
ማስተማሪያ እንዲሆን) በመሆኑ ተጎጅዎችን ያረካ የወንጀል ፍትህ ስርዓት ስለመረጋገጡ
ብዙዎች ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ ምንም እንኳ ይህ ፅሁፍ ተግባሩን ሳይሆን ህጉን ብቻ የዳሰሰ ቢሆንም
ህጉን ለመዳሰስ ያነሳሳን ነገር ግን የአስገድዶ መደፈር ጥቃት ሰለባ የሆኑ ሴቶች ከጉዳቱ በኃላ
ለንፅህና መጠበቂያ፤ ለመጠለያ ና ለህክምና ምርመራ የሚሆነ ገንዘብ ባለመኖሩ ባሰቃቂ ሁኔታ
በጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማገኘታችን ነበር፡፡ ዐ/ህግ ተጎጂዎቹ ምን መፍትሔ ያግኙ
የሚለዉ ብዙም አያሳስበዉም፡፡ ይልቁንም ትኩረቱ ወንጀል ፈፃሚዉን ማስቀጣት ነዉ፡፡
የተጎጅዎችም አስፈላጊነት ለምስክርነት እንጂ እነሱ ፍትህ ስለማገኘታቸዉ የሚጨነቅ አካል
የለም ቢባል ስህተት አይሆንም፡፡ በመሆኑም የፆታዊ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ሴቶች ለሚደርስባቸዉ
የስነ ልቦና ጉዳት በሥነ ልቦናና ሥነ አእምሮ ባለሙያዎች እየተረጋገጠ እንደጉዳቱ ልክ የገንዘብ
ካሳ የሚከፈልበት ስልት ያስፈልጋል፡፡ የፆታዊ ጥቃት የተፈፀመባቸዉ ሴቶች በተለይም
የአስገዲዶ መድፈር ድርጊት ተጠቂ ሴቶች ድርጊቱ ሊያስከትልባቸዉ የሚችለዉ የጤና
ችግሮችን በህክምና በመለየት ወይም ሙያዊ ግምት በማስቀመጥ የገንዘብ ካሳ የሚያገኙበት
ስርዓት ሊዘረጋ ግድ ይላል፡፡ የፍትሃብሔር ህጉ በአንቀፅ 2114 ላይ ያለዉ የንፅህና ክብር
ስለመድፈር የሰፈረዉ ድንጋጌ የሚያስክሰዉ የህሊና ጉዳት ብቻ ነዉ፡፡ ይሁንና የአስገዲዶ
መድፈር ድርጊት በርካታና የተወሳሰብ የጤና ጉዳት ሊያስከትል ይችላል፡፡ በመሆኑም እነዚህ
64
Amy Kasparian የተባለች ፀሃፊ በ2014 Justice beyond bars በሚለዉ ፅሁፏ “For some [‘victims/survivors’],
justice is simply the perpetrator’s conviction and incarceration. For others, justice is receiving
compensation from the offender or the state to help with civil matters like securing safe housing,
affording counseling, or repairing property damage. To others, it is having a meaningful opportunity to
tell one’s story to the community, or perhaps directly to the offender. And yet still, to other victims,
justice is having the offender publicly acknowledge and apologize for the harm caused. In short, justice
to rape victims can manifest itself in many diverse forms that often do not necessarily rely on the
traditional criminal justice idea of punishment” በማለት ትገልፃለች
30
ጉዳቶች የሚካሱበት ህግ ተሻሽሎ ሊወጣ ይገባል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጅል ህግ ከወንጀል ፍትህ
ስርዓቱ ጋር የጉዳት ካሳ ጥያቄዎች ተጣምረዉ እንዲቀርቡ የሚፈቅዱ በመሆኑ በሴቶች ላይ
በሚፈፀሙ የፆታዊ ጥቃት ክርክሮች ጊዜ የጉዳት ካሳ ጥያቄዎችን አካቶ በማቅረብ ተጠቂዎች
ካሳ እንዲያገኙ የሚያስችል ስራ ዐቃቢ ህግ ሊሰራበት ይገባል፡፡ የአብክመ
ፍ/ባ/ማ/ህ/ም/ኢንስቲትዩት ይህንን ፅሁፍ በማዳበር ለዳኞች፤ ዐቃቢያን ህጎችና መርማሪ
ፖሊሶች ጉዳዩ ትኩረት እንዲያገኝ የሚያስችል ስልጠና ማመቻቸት ይኖርበታል፡፡
31