You are on page 1of 5

የደብዳቤ ቁጥር

Ref.No. ____________________
ቀን
Date_______________________

ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅ


አዲስ አበባ

የረጲ ደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ኘሮጀክት ግንባታ ሥራ በአብዛኛው ተጠናቆ በኮሚሽኒንግ እና
ቴስት ላይ ባለበት ሰዓት ነሐሴ 13 ቀን 2010 ዓ.ም ክቡር የኢፌዲሪ ኘሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ
በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል፡፡

ሆኖም ቀሪ የኮሚሽኒንግ ሥራዎች እና እርማቶች የማስተካከል ስራዎች በተገቢው መጠናቀቅ


ስላለባቸው በአሁን ጊዜ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ለሚቀጥለው አንድ ወር ጊዜ ጣቢያው ቆሞ
የኮሚሽኒንግ ሥራው እና የማስተካከል ስራው የሚቀጥል ይሆናል፡፡

ከላይ በተጠቀሰው ምክንያት የደረቅ ቆሻሻ አቅርቦት በጊዜያዊነት የተስተጓጐለ የሚገኝ ሲሆን በዚህ
አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለኮሚሽኒንግ ሥራ ጣቢያው ወደ ኦፕሬሽን መግባቱ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ
የተወሰነ ቆሻሻ አቅርቦት እንዲቀርብልን የምናደርግ መሆኑን እየገለጽን የኮሚሽኒንግ ሥራ በተባለው
አንድ ወር ጊዜ ሲጠናቀቅ ጣቢያው ሙሉ ለሙሉ ሥራ ላይ የሚውልና ቆሻሻ መቀበሉ በተገቢው
የሚከናወን መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ከሠላምታ ጋር
የደብዳቤ ቁጥር
Ref.No. ____________________
ቀን
Date_______________________

በአሽከርካሪ ተሸከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን


ለቂርቆስ ቅርንጫፍ ጽ/ ቤት
አዲስ አበባ

ለረጲ ደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ኘሮጀክት ኮንትራክተር 3 ተሸከርካሪዎችን ከሞኤንኮ ገዝቶ
ያቀረበልን ሲሆን ተሸከርካሪዎቹን የገዛበትን ደረሰኝ እና ሌሎች ተዛማጅ ኦርጅናል ዶክመንቶች
ታርጋ በምናወጣበት ጊዜ የወሰዳችሁ በመሆኑ ለኮንትራክተሩ ክፍያዎችን ለመፈጸም ተቸግረናል፡፡

ስለሆነም የኮንትራክተሩን ክፍያ ለመፈጸም እንድንችል ዝርዝራቸው ከዚህ በታች ለተጠቀሱት


ተሸከርካሪዎች ኮፒ የክፍያ ደረሰኞ እና ተዛማጅ ዶክመንቶች ላይ ህጋዊ ማህተም እንድታደርጉልን
እንጠይቃለን፡፡

1. ኮድ 4-23445 ኢት
2. ኮድ 4-23446 ኢት
3. ኮድ 4-22447 ኢት

ከሠላምታ ጋር
የደብዳቤ ቁጥር
Ref.No. ____________________
ቀን
Date_______________________

ለኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት


አዲስ አበባ

ጉዳዩ፡- በወደብ የገቡ እና የሚገቡ ዕቃዎችን እንዲንቀሳቀሱልን ስለመጠየቅ

የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችን በተለያዩ


ጊዜያት በድርጅትችሁ በኩል ከውጭ አገር ወደ አገር ውስጥ ገቢ ተደርገው የማጓጓዣ እና የዲመሬጅ
ክፍያዎችን እንድንከፈል መጠየቃችሁ ይታወቃል፡፡

በዚሁ መሠረት በቁጥር ፈ/አ/ሲተ/አሙ/849/10 ግንቦት 30 ቀን 2010 ዓ/ም ከድርጅታቸሁ ወጪ በሆነ


ደብዳቤ በላካችሁት መረጃ መሠረት ዝርዝር መረጃ ለተገኘላቸው ብዛት ላላቸው ክፍያዎች ተገቢው
ማጣራት ተደርጎ ክፍያው እንዲፈጸም ወይም የተለየ ሁኔታ ካለ እንዲያሳውቁ ለሚመለከታቸው
ፕሮጀክት ቢሮዎች በሎጅስቲክና ዌር ሃውስ አድሚንስትሬሽን ቢሮ በኩል እንዲያውቁት የተደረገ
ሲሆን በተቻለ ፍጥነት ውጤቱን ለማሳወቅ የሚመለከተው ቢሮ እየሰራ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ
ለአስቸኳይ ሥራ የሚያስፈልግ ከታች የተጠቀሰው የማስጫኛ ሰነድ ያለ ዕቃ ማንሳት በለመቻሉ
በአዳማ 2 የንፋስ ግንባታ ሥራ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳያሰድርብን በመሆኑም በማስጫኛ
ሰነድ B/L PENCB 18016333 በድርጅታችን ሥም ለገባ ዕቃ አስፈላጊውን የማጓጓዣና የዲመረጅ
ክፍያዎችን በወቅቱ ፈጽመው እንዲያስረክቡ ተገቢ ትብብር እንዲደረግላቸው እየጠየቅን
ከአገልግሎት አሰጣጡ ጋር በተያያዘ የሚከፈሉ ክፍያዎች በጠቅላላ መከፈል የሚገባቸው
ኮንትራክተር በሆነው Hydrochina-CGCOC JV መሆኑን እየሳወቅን ከክፍያው ጋ በተያያዘ ተቋማችን
የማይጠየቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ከሠላምታ ጋር

ግልባጭ፡-
 ሎጅስቲክና ዌር ሃውስ አድሚንስትሬሽን ቢሮ
አዲስ አበባ

የደብዳቤ ቁጥር
Ref.No. ____________________
ቀን
Date_______________________

ለኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት


አዲስ አበባ

ጉዳዩ፡- በወደብ የገቡ እና የሚገቡ ዕቃዎችን እንዲንቀሳቀሱልን ስለመጠየቅ

የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችን በተለያዩ


ጊዜያት በድርጅትችሁ በኩል ከውጭ አገር ወደ አገር ውስጥ ገቢ ተደርገው የማጓጓዣ እና የዲመሬጅ
ክፍያዎችን እንድንከፈል መጠየቃችሁ ይታወቃል፡፡

በዚሁ መሠረት በቁጥር ፈ/አ/ሲተ/አሙ/849/10 ግንቦት 30 ቀን 2010 ዓ/ም ከድርጅታቸሁ ወጪ በሆነ


ደብዳቤ በላካችሁት መረጃ መሠረት ዝርዝር መረጃ ለተገኘላቸው ብዛት ላላቸው ክፍያዎች ተገቢው
ማጣራት ተደርጎ ክፍያው እንዲፈጸም ወይም የተለየ ሁኔታ ካለ እንዲያሳውቁ ለሚመለከታቸው
ፕሮጀክት ቢሮዎች በሎጅስቲክና ዌር ሃውስ አድሚንስትሬሽን ቢሮ በኩል እንዲያውቁት የተደረገ
ሲሆን በተቻለ ፍጥነት ውጤቱን ለማሳወቅ የሚመለከተው ቢሮ እየሰራ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ
ለአስቸኳይ ሥራ የሚያስፈልግ ከታች የተጠቀሰው የማስጫኛ ሰነድ ያለ ዕቃ ማንሳት ባለመቻሉ
በአዳማ 2 የንፋስ ግንባታ ሥራ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳያሰድርብን በመሆኑም በማስጫኛ
ሰነድ B/L PENCB 18019472 በድርጅታችን ሥም ለገባ ዕቃ አስፈላጊውን የማጓጓዣና የዲመረጅ
ክፍያዎችን በወቅቱ ፈጽመው እንዲያስረክቡ ተገቢ ትብብር እንዲደረግላቸው እየጠየቅን
ከአገልግሎት አሰጣጡ ጋር በተያያዘ የሚከፈሉ ክፍያዎች በጠቅላላ መከፈል የሚገባቸው
ኮንትራክተር በሆነው Hydrochina-CGCOC JV መሆኑን እየሳወቅን ከክፍያው ጋ በተያያዘ ተቋማችን
የማይጠየቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ከሠላምታ ጋር

ግልባጭ፡-
 ሎጅስቲክና ዌር ሃውስ አድሚንስትሬሽን ቢሮ
አዲስ አበባ

You might also like