Professional Documents
Culture Documents
በእንዳልካቸዉ ወርቁ
የፌ/ዐ/ሕግ
የካቲት 2007
መግቢያ
ሀ. የጋብቻ ምንነት
በውጭ ሀገር የተፈጸመ ጋብቻ በዛ ሀገር ጋብቻ አፈፃፀም ህግ መሰረት የተፈጸም ከሆነ እና
የዚህን ሀገር (ኢትጵያ) ህዝብ ሞራል እስቃልተቃረነ ድረስ በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ
መሰረት ከላይ በተገለጸው ሶስት አይነት ስርዓቶች ከተፈጸሙ ጋብቻዎች ጋር እኩል
እውቅናና ተቀባይነት አለው፡፡
ለ. ጋብቻን ለመፈጸም በቅድሚያ መሞላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች
1. ፈቃደኝነት (Consent)
2. እድሜ
3. ዝምድና
4. በጋብቻ ላይ ጋብቻ
የፀና ጋብቻ ያለው አንድ ሰው ይህ ጋብቻ ጸንቶ እያለ ሌላ ጋብቻ መፈጸም እንደማይችል
(የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 11) ክልከላ ተጥሎበታል፡፡
ይሄኛው ክልከላ ወይም ቅድመ ሁኔታ ከላይ ካሉት አራት ቅድመ ሁኔታዎች ለየት ባለ
መልኩ በሴቶች ላይ ብቻ የተጣለ ነው፡፡ አንዴት ሴት አስቀድሞ የነበራት ጋብቻ ከቀረ
በኋላ አንድ መቶ ሰማኒያ ቀን ካላለፈ በቀር ሌላ ጋብቻ መፈጸም እንደማትችል ክልከላ
ተጥሎባታል፡፡ ነገር ግን ይህ አንድ መቶ ሰማኒያ ቀን ሳይደርስ የወለደች እንደሆን ወይም
ጋብቻ የምትፈጽመው ከቀድሞ ባሏጋር ከሆነ ወይም ዕርጉዝ አለመሆኗ በህክምና
ከተረጋገጠ ወይም ይህን ጊዜ እንዳትጠብቅ በፍ/ቤት የተወሰነ እንደሆነ ይህን ጊዜ
ሳትጠብቅ ጋብቻ ልትፈጽም እንደምትችል በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 16 (2) ላይ
ተቀምጧል፡፡ ይህ ክልከላ በመሰረታዊነት የተቀመጠው የህፃናትን መብት ለመጠበቅ ነው፡፡
ህፃናት ወላጆቻቸውን የማወቅና ከወላጆቻቸው እንክብካቤ የማግኘት መብት እንዳላቸው
በህገ መንግስታችንና አለማቀፍ ስምምነቶች ላይ የተቀመጡ እና የተረጋገጠ መብታቸው
ነው፡፡ በመሆኑም ይህን ክልከላ በማድረግ የሕፃናትን መብት ለማስከበር የወላጆቻቸውን
ማንነት ላይ አከራካሪ ሁኔታ እንዳይፈጠር ነው፡፡
ጋብቻ የቤተሰብ መመስረቻ መሰረታዊው እና ዋናው መንገድ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ቤተሰብ
ደግሞ የህብረተሰብና የሀገር መሰረት እና መሰሶ ነው፡፡ ይህ የህብረተሰብ እና የሀገር መሰሶ
የሆነው ጋብቻ የተጋቢዎቹ ብቻ ሳይሆን የህብረተሰቡ እና የሀገርም ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህም
የህብረተሰብ እና የመንግስት ጥበቃና እንክብካቤ የሚያስፈልገው ተቋም ነው፡፡ ይህም
በመሆኑ ጋብቻው ከመፈጸሙ በፊት መሞላት ያለበት ቅድመ ሁኔታ ወይም ክልከላዎች
የተቀመጡት፡፡
መ. ስለ ጋብቻ ምዝገባ
ክፍል ሁለት
የጋብቻ ውጤት
በየትኛውም የጋብቻ አፈፃፀም ስርዓት ጋብቻው ቢፈፀምም የሶስቱም አይነት ጋብቻ ዉጤት
አንድ አይነት ነው፡፡(በተሸሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀፅ40)
1. የጋብቻ ውል
ከላይ እንደተገለጸው የተወሰኑ የጋብቻ ውጤቶች በውል ሊቀር ወይም ሊሻሻል ይችላል፡፡
ይህ ውል የጋብቻ ውል ተብሎ ይጠራል፡፡ ከተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 42(1) እና
(2) እንደምንረዳው የጋብቻ ውል ተገቢዎቹ የንብረት ግንኙነታቸውን እና አልፎ አልፎም
ግላዊ ግንኙነታቸውን አስመልክተው የሚፈራረሙት ውል ነው፡፡
በህጉ እምነት ተጋቢዎች የጋብቻቸውን ውጤት በውል ከወሰኑና የጋብቻ ውሉም አስገዳጅ
የህግ ድንጋጌዎችን ያልተቃረን ከሆነ የጋብቻ ውሉ የግልም ሆነ የንብረት ግንኙነታቸውን
እንዲገዛ ይደረጋል፡፡ ነገር ግን በሀገራችን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ተነስተን ስንመለከት
አብዛኛውን ጊዜ ተጋቢዎች የጋብቻቸውን ውጤት በውል አይወስኑትም፡፡በጥቂት ሁኔታዎች
እንኳን ውል ሲዋዋሉ ውሉ በህጉ የሚፈለገውን መመዘኛ አሟልተው የሚፈጽሙት እጅግ
በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡በመሆኑም ውሉ ውጤት አይኖረውም፡፡ እንደነዚህ ያለ ሁኔታ
ሲፈጠር ደግሞ ይህን ክፍተት የመድፈን ሀላፊነት የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ ነው፡፡በዚህም
የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ የተጋቢዎችን ግላዊ እና ንብረት ነክ ግንኙነቶች የጋብቻ ውል
በሌለበት ወይም ውሉ በህግ ፊት ውጤት አልባ በሆነ ጊዜ የሚመራበትን የህግ ድንጋጌ
አስቀምጧል፡፡
2. ጋብቻ ግላዊ ግንኙነት ላይ ስለሚኖረው ውጤት
ተጋቢዎች ትዳር የሚፈጽሙ እስከ መጨረሻው አብሮ ለመኖር መሆኑ እሙን ነው፡፡ በዚህ
በትዳር ባሉበት ጊዚያት በግል ንብረትነት ይዘዋቸው ያሉ ንብረቶችን መሸጥ መለወጥ
አይቀሬ ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህ የግል ንብረቶችና ሀብቶችን በመሸጥ ወይም በመለወጥ
የሚገኘው አዲስ ንብረትና ሀብት የግል ንብረት ይሆናል፡፡ ነገር ግን እነዚህ በግል ሀብት
የተገዙ ወይም የተለወጡ ንብረቶች የግል ሀብትና ንብርት እንደሆኑ የግል ንብረቱ ባለቤት
ለፍ/ቤት የግል ይባልልኝ በማለት ጥያቄ ማቅረብ እና ማፅደቅ አለበት፡፡ የተሻሻለው
የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 58(1)ና(2) ይህን ይገልፃሉ፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በአንቀጽ 62/2/
መሰረት የጋራ ንብረት ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት
በመዝገብ ቁጥር 37275 ላይ ነአመልካች ሻ/ባሻ ገዛኸኝ ድልነሳዉ እና ተጠሪ ወ/ሮ ተዋበች
ደመቀ መካከል በነበረዉ ክርክር የአመልካች የግል ንብረት የነበረ ቤት በትዳር ባሉበት ጊዜ
ሽጠዉ በተሸጠዉ ገንዘብ ሌላ አዲስ ቤት ገዝተዋላል ነገር ግን አመልካች አዲስ የገዙትን ቤት
የግል ይባልልኝ በማለት ጥያቄ ለፍርድ ቤት ያላቀረቡ እና ያላጸደቁ በመሆነ የጋራ ንብረት ነዉ
በማለት ወስኖል፡፡
ተጋቢዎች በትዳር ከተሳሰሩበት እለት ጀምሮ ህይወታቸውን በጋራ ሲመሩ የጋራ ንብረት
ማፍራታቸው አይቀሬ ነው፡፡በጋብቻ ውላቸው ተጋቢዎች ከትዳር በፊት የነበራቸውን የግል
ንብረት የጋራ ንብረት ማድረግም ይችላሉ፡፡በጥቅሉ በትዳር ዘመናቸው ተጋቢዎች የግል
ንብረትና ሀብት እንደሚኖራቸው ሁሉ የጋራ ንብረትና ሀብት ሊኖራቸው
ይችላል፡፡ከተሻሻለው የቤተሰብ ህጋችን አንቀጽ 57 እና 58 ለመገንዘብ የምንችለው ነገር
በትዳር ውስጥ የተፈሩ ሀብቶችና ንብረቶች ፣ ለተጋቢዎቹ በጥቅሉ በውርስ ወይም በስጦታ
የተሰጡአቸው ሀብትና ንብረቶች በተጨማሪም የግል ሀብትና ንብረት ተሸጦ ወይም
ተለውጦ የተገኘ ንብረት ሆኖ የግል ንብረቱ ባለቤት በፍርድ ቤት ቀርቦ የግል ንብረት
መሆኑን ያላጸደቃቸው ንብረቶችና ሀብቶች ሁሉ የጋራ ንብረት እንደሆኑ ይቆጠራል፡፡ከዚህ
በተጨማሪ በአንቀጽ 62(1) ላይ ባልና ሚስት ከግል ጥረታቸውና ከግል ወይም ከጋራ
ንብረታቸው የሚያገኟቸው ገቢዎች ሁሉ የጋራ ሀብቶቻቸው እንደሚሆኑ ይገልፃል፡፡የግል
ንብረት የግል ቢሆንም ከንብረቱ የሚገኝ ገቢ ግን የጋራ ነው፡፡
ተጋቢዎች በትዳር ተሳስረው የጋራ ንብረት አፍርተው ሲኖሩ ይህን የጋራ ንብረት በጋራ
ማስተዳደር እንዳለባቸው ከላይ በተገለጸው መልኩ ለመረዳት ችለናል፡፡ እነዚህን የጋራ
ንብረቶች ተጋቢዎቹ በጋራ በሚያስተዳድሩበት ወቅት ንብረቱን መሸጥ መለወጥ
ያስፈልጋቸው ይሆናል፡፡ ይህ ጋራ ንብረት መሸጥ መለወጥ ከፈለጉ በሌላ የህግ የተለየ
ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር የተጋቢዎቹ የጋራ ስምምነት አስፈላጊ ነው፡፡ በአንቀጽ 68
የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው የጋራ ንብረትና ሀብት ወደሌላ
ሶስተኛ ወገን በሽያጭ ሆነ በስጦታ የሚቀየረው በተጋቢዎቹ የጋራ ስምምነት ብቻ መሆኑን
ይገልፃል፡፡ እዚህ ላይ በጋራ ንብረት የሆነውን አንደኛው ተጋቢ ሌላኛውን ተጋቢ ፈቃድ
ወይም ስምምነት ሳያገኝ ብቻውን ለሌላ 3ኛ ወገን በሽያጭም ሆነ በሌላ መንገድ
ቢያስተላልፍ ሌላኛው ተጋቢ ለፍርድ ቤት በሚያቀርበው ጥያቄ ግዴታው እንዲፈርስ
መጠየቅ ይችላል፡፡ ይህ ግዴታ እንደፈረሰ የሚጠይቀው ተጋቢ ለፍ/ቤት ጥያቄውን
የሚያቀርበው ግዴታው መገባቱን ካወቀበት ቀን ጀምሮ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ወይም በሌላ
በማንኛውም ሁኔታ በ2 አመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ይህ የተባለው ጊዜ ካለፈ ይህን
ጥያቄ ማቅረብ እንደማይቻል በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 69(2) ላይ ተገልፆል፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 38126 በአመልካች ዲያቆን
ኃ/ጊዮርጊስ ወንድም እና ተጠሪዎች እነ የሺ ተፈሪ መካከል በነበረዉ ክርክር የአሁኑ 2ኛ ተጠሪ
ከ1ኛ ተጠሪ ባለቤት ከሆኑት የጋራ ንብረታቸዉ የሆነዉን ቤት ለአሁኑ አመልካች
በ01/03/1995 ዓ.ም ያለ 1ኛ ተጠሪ ፍቃድ ይሸጥለታል፡፡ 1ኛ ተጠሪም በስር ፍርድ ቤት ዉሉ
ያለ እሳቸዉ ፍቃድ የተፈጸመ በመሆኑ እነዲፈርስ በማለት በ09/08/1999 ዓ.ም ክስ
ታቀርባለች፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰበር ችሎት የአሁን 1ኛ ተጠሪ የሆነችዉ ክስ ያቀረበችዉ
በተሻሻለዉ የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 69/2/ በተቀመጠዉ የጊዜ ገደብ ማለትም ሽያጩን
ካወቀችበት ጊዜ ጀምሮ በ6 ወር ጊዜ ዉስጥ ወይም በማንኛዉም ሁኔታ በ2 አመት ጊዜ ዉስጥ
ክሶን ያላቀረበች ስለሆነ (ክሶን ያቀረበችዉ ከ4 አመት በሆላ ነው) ዉሉ እንዲፈርስ ክስ
የማቅረያ ጊዜ አልፎል፡፡ ስለሆነም ውሉ አይፈርስም በማለት ዉሳኔ ሰጥቶላ፡፡
የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ ሲኖር እለት በለት ኑሮውን ለመደጎም ወጪዎችን ያወጣል፡፡
በትዳር ውስጥም ተጋቢዎ ትዳራቸውን ለማቃናትና ዘላቂነቱን ለማስቀጠል የተለያዩ
ወጪዎች ማውጣታቸው የማይቀር ሀቅ ነው፡፡ በመሆኑም ተጋቢዎች የትዳራቸውን ወጪ
ለመሸፈን እያንዳንዳቸው እንዳቅማቸውና ችሎታቸው አስተዋፅኦ የማድረግ ግዴታ
አለባቸው፡፡ የህይወት መንገድ ሁልጊዜም አልጋ በአልጋ አይሆንም ውጣ ውረድ በህይወት
ውስጥ ማጋጠሙ አይቀርም፡፡ በዚህ ጊዜ ወደ ብድር እና እዳ መገባት ሊያጋጥም
ይችላል፡፡ በትዳር ውስጥም ተጋቢዎቹ ለግላቸው ወይም ለትዳራቸው ሲሉ እዳ ውስጥ
ሊገቡ ይችላሉ፡፡ ይህ በሆነበት ጊዜ እዳውን ለመክፈል እዳው ለግል የተወሰደ ከሆነ
ከባለእዳው ተጋቢ የግል ሀብት ይሸፈናል፡፡ ነገር ግን የግል ሀብቱ ይህን ለመሸፈን
የማይችል ከሆነ ተጋቢዎች የመረዳዳትና የመተጋገዝ ግዴታ ስላለባቸው ይህ እዳ ከጋራ
ሀብታቸው ይከፈላል፡፡ እዳዉ ግን ለትዳራቸዉ ጥቅም ከሆነ ከጋራ ሀብታቸዉ የሚከፈል
ይሆናል፡፡ ነገር ግን የጋራ ሀብቱ በቂ ካልሆነ ከተጋቢወቹ የግል ሀብት ይከፈላል፡፡
በዚህ ጽሑፍ ክፍል እንደ ውስጥ ዝምድና (የስጋም ይሁን የጋብቻ) በጋብቻ ቅድመ
ሁኔታነት የሚታይበትን መንገድና የሚያስከትለውን ህጋዊ ውጤት ተመልክተናል፡፡ የዚህ
የዝምድና ሌላኛው ውጤት ደግሞ በዘመዳሞቹ መካከል የሚፈጠረው ቀለብ የመስጠት
ግዴታ ነው፡፡በዚህ ክፍል ትኩረት ሰጥተን የምንመለከተው የጋብቻ ዝምድና
የሚያስከትለውን የቀለብ መስጠት ግዴታ ነው፡፡
ቀለብ የመስጠት ግዴታ በህግ ሲቀመጥ አራት መሰረታዊ መርሆዎችን ከግምት አስገብቶ
ነው፡፡
1ኛ/ ቀለብ የመስጠት ግዴታ የሚጣለው እንዲሁ የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመድ ነው ለተባለ
ሰው ሁሉ ሳይሆን ጠበብ ብሎ በጣም ቅርብ ለሆኑ ዘመዶች ብቻ ነው፡፡
2ኛ/ የግዴታው መጠን ለቀለብ ጠያቂው የእለት ተእለት ኑሮ መሰረታዊ የሆኑ ነገሮችን
በማቅረብ ላይ እንጂ የቀለብ ጠያቂውን ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ለማሟላት የሚያስገድድ
መሆን አይኖርበትም፡፡
3ኛ/ ቀለብ የመስጠት ግዴታው በቀለብ ጠያቂው ላይ የጥገኝነት ስሜት በሚፈጥር መልኩ
ሳይሆን ተቀጥሮ ወይም ስራ ፈጥሮ ራሱን ማስተዳደር የሚችልበት ሁኔታንና ስሜትን
በሚፈጥር መልኩ መሆን አለበት፡፡
4ኛ/ ቀለብ ጠያቂው ሠርቶ ለመኖር አቅም የሌለውና የተቸገረ መሆን አለበት
የቀለብ ሰጭው ግዴታ እንደባለጉዳዮቹ (ቀለብ ሰጪውና ተቀባዮ) ሁኔታና እንደ አካባቢው
ልማድ መሰረታዊ ፍላጎታቸውን ማሟላት እንደሆነ በአንቀጽ 197 ላይ ተገልፆል፡፡ ይህም
ማለት እንደ ቀለብ ሰጪውና ቀለብ ተቀባዩ አቅምና ፍላጎትን መሰረት ባደረገ መልኩ
የሚከናወን ነው፡፡ እነዚህ መሰረታዊ ፍላጎቶች ምግብ፣ መኖሪያ፣ ልብስ፣ ጤናውን
እንዲጠብቅ እና ትምህርት ናቸው፡፡ ስለሆነም የቀለብ ሰጭው አቅምና የቀለብ ተቀባዩን
ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ ቀለብ የመስጠት ግዴታው ይፈፀማል ማለት ነው፡፡
ለምሳሌ የአንድ አቶ አበበ የተባለ ግለሰብ የሚስቱ አባት የራሳቸው መኖሪያ ያለቻው ነገር
ግን የሚበሉትና የሚለብሱት ከቸገራቸው የአቶ አበበ ግዴታ ትምህርት እንደሚማሩ ወይም
እንዲታከሙ ማድረግ ሳይሆን እንደ አቅሙ የሚመገቡትን ምግብና የሚለብሱትን ልብስ
መስጠት ይሆናል፡፡
ቀለብ ጠያቂው ከቀለብ ሰጪው ጋር የቅርብ ዘመድ (በህጉ በተቀመጠው መሰረት) መሆኑ
ከተረጋገጠና ሰርቶ እራሱን ለማስተዳደር አቅም የሌለውና ችግር ላይ የወደቀ መሆኑ
ሲረጋገጥ ብቻ ነው ቀለብ መጠየቅ የሚችለው፡፡ ይህም ማለት ቀለብ የመጠየቅ መብት
ስራ በማግኘትና ባለማግኘት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን የመስራት አቅም መኖር እና
አለመኖር ላይ መሆኑን ከህጉ መረዳት ይችላል፡፡ በመሆኑን መስራት አቅም እያለው ስራ
ያላገኘ ሰው ቀለብ መጠየቅ አይችልም፡፡
ክፍል ሦስት
ስለፍቺና ውጤቶች
ሀ/ በስምምነት ፍቺ ስለመፈጸም
ሚስት ህጋዊ መንገድ የመሰረቱት ጋብቻ በህጋዊ መንገድ ሳያፈርሱ በመለያየት የየግል
ኑሯቸዉን ለረዥም ጊዜ መኖር ይጀምራሉ፡፡ ይህ አይነቱ መለያየት የፍቺ አይነት ዉጤት
እንዳለዉ የፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 20938 በአመልካች
ወ/ሮ ሸዋዬ እና በተጠሪ ወ/ሮ ሳራ መካከል በነበረዉ ክርክር ‘‘በወ/ሮ ሳራና በአቶ ይልማ
መሀል የነበረው ጋብቻ በሕጉ በተቀመጡ የጋብቻ ማፍረሻዎች ባይፈርስም በስር ፍ/ቤት ወ/ሮ
ሳራ የሰጡት ቃል መፍረሱን የሚያሳይ ነው። ወ/ሮ ሳራና አቶ ይልማ በጋብቻው መቀጠል
ባለመቻላቸው ተጣልተው ተለያይተው በየፊናቸው የየራሳቸውን ኑሮ ሲኖሩም ነበር። ለጋብቻው
መፍረስ የሚያበቁ ምክንያቶች መኖራቸውንና አቶ ይልማም ወ/ሮ ሸዋዬን ማግባታቸውን ወ/ሮ
ሳራ ያውቁት ነበር። ሆኖም ሁለቱም የየራሳቸውን ኑሮ እየኖሩ ስለነበር ወ/ሮ ሳራ አቶ ይልማ
ወ/ሮ ሸዋዬን ማግባታቸውን ቢያውቁም ሟች በህይወት እያሉ ጋብቻውን ‘በጋብቻዬ ላይ
የተፈፀመ ሕገወጥ ጋብቻ ነው’ ብለው አልተቃወሙትም። ሰለዚህ የስር ፍ/ቤቶች ይህን
ባረጋገጡበት ሁኔታ ‘ወ/ሮ ሳራ ሟች እስከሞቱበት እለት ሚስት ነበሩ’ ብለው መወሰናቸው
ትክክለኛውን የሕግ አተረጓጎም የተከተለ አይደለም። ፍቺ መፈፀሙን የሚያሳይ ማስረጃ
አለመቅረቡ ብቻ አንድን ጋብቻ የፀናና ውጤት የሚያስከትል ነው ሊያስብለውም አይችልም።
ባለመግባባት ተለያይተው ፍቺ ለመፈፀም የሚያስችል ምክንያት የነበራቸው ተጋቢዎች
የየራሳቸውን ኑሮ በየበኩላቸው ጀምረው ከኖሩ በኋላ ባል ወይም ሚስት ናቸው ሊባሉ
አይችሉም’’ በማለት ወስኖላ፡፡
ሐ/ የፍቺ ውጤቶች
ፍ/ቤቱ ፍቺውን ከወሰነ በኋላ የፍችውን ውጤት በተመለከተ ባልና ሚስቱ እዲስማሙ
ይጠይቃቸው፡፡ እዚህ ላይ የምንረዳው ነገር ፍቺውን ፍ/ቤቱ ከወሰነ በኋላ የፍቺውን ውጤት
ማለትም ስለልጆቻቸው፣ ስለጋራ ንብረታቸው እንዲሁም የገራ እዳወቻቸዉ በተመለከተ
ተስማምተው እንደወሰኑ ፍ/ቤት በጠየቃቸው መሰረት ተስማምተው ሊወስኑ እንደሚችሉ
ነው፡፡ ነገር ግን ባልና ሚስቱ የፍቺው ውጤት ላይ ያልተስማሙ ከሆነ ፍ/ቤቱ በራሱ
ወይም በሽማግሌዎች ወይም ፍ/ቤቱ በሚሾሟቸው ባለሙዎች አማካኝነት ወይም አመቺ
መስሎ በሚታየው በማንኛውም ዘዴ የፍችውን ውጤት ይወስናል፡፡
በዚህ ጽሑፍ ክፍል ሁለት ውስጥ ለመግለጽ እንደሞከረው ተጋቢዎች በጋብቻ ውላቸው
ውስጥ የጋብቻው መፍረስ በንብረት በኩል የሚያስከትሉ ውጤቶችን አስቀድመው ሊወስኑ
ይችላሉ፡፡ ነገር ግን የጋብቻ ውሉ የሌለ እንደሆነ ወይም በህግ ፊት የማይጸና ከሆነ ፍ/ቤቱ
በህግ በተቀመጠው መሰረት የፍቺውን ውጤት ይወስናል፡፡ በዚህም መሰረት በመጀመሪ
ደረጃ የግል ንብረት ክፍፍል ይካሄዳል፡፡ በተጋቢዎች እጅ ያሉ ንብረቶች ሁሉ የጋራ
ንብረት እንደሆኑ ስለሚገመት እያንዳንዱ ተጋቢ ይህ ንብርት የግሌ ነው የሚለውን
የማስረዳት ሸክም የሱ ወይም የሷ ይሆናል፡፡ የግል ንብረቱ መሆኑን ያስረዳው ተጋቢ የግል
የሆነውን ንብረቱን ይወስዳል፡፡ ይህ የግል ንብረቱ የሆነው ነገር ከጋራ ንብረታቸው ጋር
የተቀላቀለ ስለመሆኑ የተረጋገጠ ከሆነ ከግል ንበረቱ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ገንዘብ ወይም
ንብረቱን ከጋራ ንብረታቸው ውስጥ ይወሰዳል፡፡ የየግል ንብረታቸውን ወስደው ከጨረሱ
በሆላ የጋራ ንብርት ክፍፍል ከማድረጋቸው በፊት ዕዳዎችን መክፈል ይቀጥላል፡፡
በቅድሚያ ለትዳራቸው ያለባቸውን ዕዳ ከጋራ ንብረታቸው ይከፍላሉ ይህ የጋራ ሃብት
እዳቸውን የማይቻል ከሆነ ከግል ንብረታቸው ይከፍላሉ፡፡ ነገር ግን አንዳዴ ንብረቱ የግል
ነዉ የጋራ የሚለዉ ላያ ጭቅጭቅ ይነሳል ለምሳሌ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ
ችሎት በመዝገብ ቁጥር 46606 በአመልካች አቶ ገብረስላሴ አማረ እና ተጠሪ ወ/ሮ አብረኸት
ተጫነ መካከል በነበረዉ የፍቺ ክርክር ላይ የሚከተለዉን ዉሳኔ ሰጥቶል፡፡ የአመልካች እና
የተጠሪ ጋብቻ የፈረሰዉ መጋቢት 24 ቀን 2000 ዓ.ም ነዉ፡፡ አመልካች የኮንዶሚኒየም ቤቱን
የተመዘገበዉ ተጠሪን ከማግባቱ በፊት ቢሆንም እጣ የወጣለት ከተጠሪ ጋር የፀና ጋብቻ
በነበረነት ወቅት ነዉ፡፡ ጋብቻዉ ፀንቶ እስካለ ድረስ ተጠሪን ከማግባቱ በፊት ስለተመዘገበ ብቻ
ቤቱ የግል ንብረቱ እንደማይሆን በተሻሻላዉ የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 62/1/ ድንጋጌ መገንዘብ
የሚቻል በመሆኑ አመልካች ያቀረቡት ክርክር የሕግ መሰረት የሌለዉ ነዉ፡፡ በመሆኑም
የኮዶሚኒየም ቤቱ የጋራ ንብረት ነዉ፡፡ ጋብቻዉ ከፈረሰ በሆላ ሚከፈለዉ ክፍያ አመልካችና
ተጠሪ በጋራ የመክፈል ግዴታ አለባቸዉ፡፡ በተመሳሳይ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎቱ በመዝገብ
ቁጥር 51893 በአመልካች አቶ እንዳልካቸዉ ዘለቀ እና ተጠሪ ወ/ሮ ብሁዓለም መንግስቱ
መካከል በነበረዉ ክርክር የኮዶሚኒየም ቤት ጋር በተያያዘ ከጋብቻ በፊት በአንደኛዉ ተጋቢ
ምዝገባዉ የተካሄደዉ ቢሆንም የቤቱ ዕጣ የወጣዉ ብሎም የቤቱ ሽያጭ ዉል የተደረገዉ
በጋብቻ ጸንቶ በነበረበት ወቅት መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ ለቤቱ መገኘት ምክኛት የሆነዉ ተጋቢ
ቤቱ የግል መሆን አለበት በሚል የሚቀርብ ክርክር ተቀባይነት ሌለዉ ነዉ በማለት ወስኖል፡፡
ማጠቃለያ