You are on page 1of 4

ሣምንት አንድ

ከቡስካ በስተጀርባ
ምእራፍ አንድ

እስከ ገፅ አስራ አንድ ያለውን ገለጣ በወጉ ተረዱት፤ ከዚያም ተከትለው የመጡትን
የማስተዋወቂያ ጥያቄዎች መካከል የፈላጋችሁትን ሦስቱን በመምረጥ ምላሽ ስጡበት

1.እስከ ገፅ አስራ አንድ ባነበባችሁት ገለፃ የደራሲው ሰብእናን እና ሊያስተላልፍ የፈለገውን መልዕክት
ለመጠቆም ሞክሩ ከሁሉ አስቀድሞ የደራሲውን ሙሉ ስም መፃፍ ይገባል፡፡

2፣ደራሲው በገጽ5 ላይ በመጀመሪያው አንቀጽ ውስጥ የባኞ ቤቱን አጠቃለይ ሁኔታ እንዴት ገለፀው?
ይታዩ ከነበሩትን ውጫዊ ገፅታዎች መካከል አምስቱን ግለፁ

3.ካርለት አልፈርድ በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲት በሶስዮሎጂ የመጀመሪያ ድግሪዋን ከወሰደች በሁዋላ


አስከትላ ያደረገችው ምን ምን ነበር?

4.የአንትሮፖሎጂ ጥናት በሥራ ሲተረጎም ‹‹መከራም ደስታም በውስጡ ይዙዋል››ይህን ጥቅስ


ትክክልነት በምክንያትያዊ ምላሽ አብራሩ

5.ካርለት እንግሊዛዊት ነች፡፡ አገሩዋ፣አባቱዋ እና እናቱዋ በካርለት ሕይወት የነበራቸው አስተዋፅኦ ምን


ነበር?ቻርለስ አልፈርድ ማን ነበር? ይሰራ የነበረውስ ሥራ ምን ነበር?ካርለት ለጥናትዋ ኢትዮጵያን
የመረጠችበት ምክንያት ምን ነበር? በቤተሰቡዋ ታሪክ ውስጥ በ1970 ምን ሆነ? ከዚያስ?(በሀምሳ
ቃለት ግለፁ)

ምእራፍ ሁለት

ጥያቄዎቹ ከገፅ 12-18 ወይም በምዕራፍ 2 ላይ ብቻ ያተኩራሉ፡፡ (ከሰባቱ ጥያቆዎች አራቱን


ብቻ በመመረጥ መመለስ ትችላለችሁ)

1.‹‹ከርለት ለስቲቭ‹የጉጉት ዘዴ፣የንስርን ማስተዋል፣የአንበሳን ልብ፣የኢዮብን ትዕግስት፣የአባትሽን


ተስፋ አይቆርጤነት እና አእምሮ ይስጥሽ በለኝ››ብላ ጉንጩን ሳም ያደረገችበት አገላላፅ ምንነትን
በቅደም ተከተል አብራሩ(ገፅ 12)

2.‹‹ማፍቀር ያለብህ እኔን ብቻ ሳይሆን ፍላጎቴንም እንዲሆን እፈልጋለሁ››የሚለው አገላለፅ ምን ያህል


ትክክል ነው?(ገፅ 13)

3.ከሎ ሆራ በልብ ወለዱ ውስጥ የተከሰተ ሁነኛ ገፀ ባህሪይ ነው፤የዚህን የገፀባህሪው ውጫዊና ውስጣዊ
ማንነት መረጃ እየጠቀሳችሁ ገልፁት(ገፅ 14-18)
4.የከሎ ዝምታ እና የስቲቭ ቅብጥብጥነት ለምን ለከርለት አልስማማሽ አላት የሁለቱ ወንዶች ሰብዕና
እንደ ‹‹አራማባና ቆቦ ተመሳሰለ? (ገፅ 18

5.‹‹መማሬን እርሳው››ካርለት ለስቲቭ የሰጠችው ያልተጠበቀ ምላሽ ነው፤ ይህን ያስባለትን መሰረታዊ
ምክንያት ከገፀባህሪያት አደረጃጀት አኳያ በማት ማብራሪያ ስጡ፡፡

6.ከትመህርት ዘርፍ ለከሎ ሰብዕና ቀረፃ ‹‹ከሶሲዮሎጂ ይልቅ የሳይኮሎጂ ተመህርትን ከሎ በእጅግ
ይጎዳል ›› ይህ የሆነበትን መሰረታዊ ምክንያት ምዕራፍ ሁለት በየገፁ አብራርቱዋል፡፡ ለዚህ አባባል
መልሳችሁን መረጃ በመስጠት ለማብራራት ሞክሩ፡፡

7.በምዕራፉ መደምደሚያ ላይ ደራሲው ሁለቱን ወንዶች ‹‹በዝምተና በቅብጥብጥነት


ገልጦዋቸዋል፡፡ይህን ከባህላዊ እሴቶቸና ከአስተዳደግ አኳያ በማየት ማብራሪያ ስጡበት፡፡

ምዕራፍ ሦስት

1. ‹‹አዎ! የከሎ ባህርይ ራሱ መጠናት የሚገባው ነው፡፡ እሱን ለማጥናት ግን አስፈላጊውን ቁልፍ
ማዘጋጀት አለብኘ፤›› አለች ካርለት፡፡ (ገጽ 22) ካርለት ይህን ለማለት የበቃችው ለምን ነበር? ይህን
ስትልስ ምን ለማለት ፈልጋ ነው?

2.‹‹ካርለት፡- ከሎን ‹‹ይህች አገር ልምላሜ፣ ውበትና ጥሬ ሀብት ሳያንሳት ቀድማ ነቅታ ምነው ተመልሳ
ተኛች?የእንቅልፍ መድሀኒት ማን አዋጣት? የውስጥ ይሆን የውጭ ሐኪም?››ላለችው የሰጠው መልስ
ምን ነበር? መልሱን በበቂ ሁኔታ አብራሩ(ገፀ26)

ምእራፍ አራት

1.‹‹ሚንግ ነኝ››ያለበትን ባህላዊ እምነት ምንነቱን በዝርዝር ፃፉ (ገፅ 30-35)(ስለ ሚንግም


ያነበባችሁትን አምስት ነጥቦች አንሱ)

2.የሐመር ሴት ልጅን አጠቃላይ ሕይወት አብራሩ ከጋብቻ በፊት እና ከጋብቻ በሁዋላ፡፡(ገፅ 32-35)
3.እናቱ በንቲ ሀይሎ አባቱ ሆራ ሸላ የተባሉት የከሎ ወላጆች በልጃቸው ሕይወት ውስጥ ምን አይነት
ትዝታ ትተው ኖሩ(ገፅ 35-36)

ምእራፍ አምስት

ሁለቱን መርጣችሁ ሥሩ

1.ከሐመር አውራጃዎች መካከል የሁለቱን የዲመካና የቱርሚን መልክአ ምድራዊ ገለፃ በመዘርዘር
ፃፉ(ገፅ 39)

2.ሽማግሌዎች በካርለት የተበሳጩት ከምን የተነሳ ነው? በሐመርስ ‹ሴት ወንድን ለመርዳትና ለማገልገል
የተፈጠረች የእርሱ ፀጋ መሆኑዋ እንደት ይረጋገጥ ነበር?›› (ገፅ 42-44)

3.ካርለት ባል ያላገባች እና እጮኛ የሌላት መሆኑዋን ማሳወቅ ለምን ፈለገች? የዚህስ ገለፃ ምን ጠቃሚ
ወይም ጎጆ ውጤት አመጣ? (ገፅ 42-44)

4ካርለት ከገጠማት የባህል ግጭቶች መካከል ሦስቱን ጥቀሱ

ምዕራፍ ስድስት

1..ከምዕራፍ 1-6 የተዘረዘረውን የትረካ ሂደት በማስታወስ(ከዘጠኝ እስከ አስራ አንድ የተማራችሁትን
የልብ ወለድ አላባውያነን ከግመት በማስገባት) በታሪኩ ውስጥ ያሉትን፡-

ሀ.ገፀባህሪያት፣

ለ.ጭብጥ፣

ሐ.ግጭቶች

መ.መቼቱን በቅደም ተከተል ፃፉ

ከተከታዮቹ ጥያቄዎች ውስጥ ሁለቱን መርጣችሁ ሥሩ፤

1.ምዕራፉ ‹‹ሦስት ወራት አለፈ…››በማለት ይጀምራል በሀመር የካርሎ ቆይታ ላይ እነዚህ ሦስት ወራት
ያመጡት ለውጦች በሰብእናዋ (በማንነቱዋላይ) ላይ ምን ምን ነበሩ ትላላችሁ ምላሻችሁን በምዕራፍ
ስድስት ላይ ብቻ ሳትወሰኑ እስከ ገፅ አርባ ዘጠኝ ያለውን በመሸፈን መልሱ፡፡
2.ቡና በአለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅና የሚጠጣ ተወዳጅም የሆነ መጠጥ ነው፡ በሀመሮች ዘንድ የቡና
ስነ ስርአትን ከተቀሩት የኢትጵያ ሕብረተሰቦች አኩዋያ ስታዩ ምን የተለየ የአዘገጃጀት ልዩነት አለው፡፡ (ገፅ
27)

3.‹‹አየህ ስቲቪ ከርቀት ጠቦ የሚታይህ ደልድይ ስትደርስበት ግን ሰፊ ነው›› ይህን ካርለት መጠቀም
የፈለገችበትን መሰረታዊ ምክንያት በማብራራት መልሱ (ገፅ 49)

You might also like