Professional Documents
Culture Documents
Tor 3
Tor 3
በሃገራችን የተማረ የሰው ኃይል ከማፍራት ባሻገር በየዘርፉ ገበያው የሚፈልገውን ተወዳዳሪ ፣ ጥራት እና ብቃት ያለው የሰው ኃይል ማፍራት ግድ ይላል።
የጀመርነውም የእድገት አቅጣጫ ጠንክሮ ይሄድ ዘንድ የቲቬት እስትራቴጂን በየዘርፉ መተግበር እና ማስቀጠልም ወሣኝነት አለው።
ይህንን መሠረት አድርጎ በየዘርፉ እድገታችንን የሚያስቀጥሉ እና ጉልህ ድርሻ በሚጫወቱ ዘርፎች ላይ የትኩረት አቅጣጫ ተነድፎ እየተሰራ ይገኛል። ከነዚህም
ዘርፎች አንዱ የተለያዩ ብረት ነክ የሆኑ አካላትን በማያያዝ ጉልህ ድርሻ ያለው የብየዳ ቴክኖሎጂ አንዱ ሲሆን በዘርፉ በተደረገው ጥናትም በሃገራችን ያሉትን
የልማት እንቅስቃሴ መሰረት አድርጎ እስከ አስር ሺህ (10,000) የሚደርሱ ብቁ የሰው ሃይል ማፍራት እንደሚጠበቅ ተለይቷል።
ይህንን የሰው ኃይል ለማፍራትና ወደ ገበያ ለማሰማራት በተለይም በዘርፉ ለተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ለመደገፍ በፌደራል ቴ/ሙ/ት/ስ/
ኤጀንሲ ምህንድስና ብቃት ማዕከል ስር የብሔራዊ የብየዳ ማሰልጠኛ ማዕከል በአዲስ አበባ እንዲሁም የመስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ማሰልጠኛ ተቋም
በመቀሌ ተቋቁሟል። ይሁን እንጂ እነዚህ ሁለት ተቋማት በዘርፉ ሊፈሩ የታሰበውን ባለሙያዎች በእድገት ዘመኑ ብቻቸውን ሊያሳኩ እንደማይችሉ ስለታመነበት
በዘርፉ የተመረጡ ሌሎች አብዢ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በክልሎች አቋቁሞ በትብብር ለመስራትና የተቋማቱን አብዢ መምህራንን በቅድሚያ በአለም አቀፍ
እውቅና በተቋሙ እንዲሰለጥኑ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።
በዚህም በተለይ በ Cee የሚገኘው የብሔራዊ የብየዳ ማሰልጠኛ ማዕከል ከአጫጭር የዘርፉ የብየዳ ሂደቶች በተጨማሪ የመካከለኛ ጊዜ ስልጠናዎች ከክልልና ከተማ
መስተዳድር ለሚመጡ አብዢ የቴ/ሙ/ ተቋማት አሰልጣኞች እና ለኢብኮ ባለሙያዎች እንዲሰጥ ታቅዶ የታቀደው እቅድም የተጀመረ ሲሆን በ 2007 ዓ.ም.
በሁለት ዙር ሁለተኛ ሩብ ዓመትና አራተኛው ሩብ ዓመት ብቃታቸው የተረጋገጠ 38 ሰልጣኞችን ከጀርመኑ /SLV Manhaim/ የብየዳ ማሰልጠኛ ተቋም ጋር
በመተባበር ማሰልጠንና ማስመረቅ የተቻለ ሲሆን በተጨማሪም 30 ሰልጣኞችን አሰልጥኖ ፈተና በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።
በቀጣይ ቀድመው በሌቭል 4(አራት) የሰለጠኑትን ወደ ልቭል 6(ስድስት) የለማሳደግ ስልጠና ተቋሙ እንዲሰጥ የታቀደ ሲሆን እቅዱንም ለማስተግበር የሚያስፈልጉ
መስፈርቶችን እና የድርጊት መርሃ ግብሮችን የያዘ የ TOR ሠነድም እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል።
በኢንዱስትሪና በማሽነሪዎች ግንባታዎች ላይ የጥራት ቁልፍ ማነቆ የሆኑትን የብየዳ ቲክኖሎጂ ችግሮችን እና የዘርፉን ሥር የሠደደ የባለሙያዎችን የክህሎት
ክፍተቶች እንዲቀረፉ አለማቀፍ መስፈርትና ተወዳዳሪነትን የጠበቀ የክህሎትና የንድፈ ሃሣብ ሥልጠና በ MMA (Manual Metal Arc welding) እና MAG
(Metal Active Gas) በተባሉ የብየዳ ቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ 30 ሠልጣኞችን ለአራት ሣምንታት በአለም ዓቀፍ ደረጃ ማሰልጠን፡፡
1
በብየዳ ቴክኖሎጂ በእውቀትና በተግባር አንፀው ገበያው የሚፈልገውን የሠው ኃይል የሚያፈሩ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ መሪ
አሠልጣኞችን የቴክኒክ፣ የክህሎትና የንድፈሃሣብ ክፍተቶችን በመለየት አለምአቀፍ መለኪያን መሠረት ባደረገ ሥልጠና ማሰልጠን፡፡
አገረችን በጀመረችውና በማከናውን ላይ ላይ በምትገኘው ግዙፍ ፕሮጀክት ላይ እየሰራ ያለውን የብረታብረት ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) የዘርፉ
ባለሙያዎችን የክህሎት ሥልጠና ለመስጠት ጥራታቸውን የጠበቁ ሥራዎችና ምርቶችን ለማምረት እንዲችሉ ማብቃት፡፡
ሠልጣኝ መምህራኖች በቴክኒካል ክህሎት የአለም አቀፉን ተጨባጭ ተሞክሮ እንዲያውቁ በማስቻል፤ በሚሄዱባቸው ተቋማት ይህንን ተሞክሮ እንዲያበዙና
እንዲያሸጋግሩ ማገዝ፡፡
ሠልጣኞች በሚሠለጥኑባቸው የሥልጠና ዘርፎች ላይ ከክህሎትና ሥልጠና በተጨማሪ የማሽነሪ እንክብካቤና ጥገና ሥርዓት፤ የቅድመ ጥንቃቄ ልምዶችና
ተሞክሮዎችን ማሳወቅ፡፡
ሠልጣኝ የቴ/ሙያ መምህራን በሚሠለጥኑበት የብየዳ ዘርፍ ከአለም አቀፉ የሞጁል አሠራር በመነሳት ገበያና ተግባር ተኮር ሥልጠናዎችን እንዴት በአጭርና
በረጅም ጊዜ ከፋፍሎ ማሰልጠን እንደሚችሉ ልምድ መስጠት፡፡
የበያጆችና ቴክኒሻኖችን የሚያፈሩ ከክልልና ከተማ መስተዳድር ቴ/ሙ/ተቋማት ተመልምለው የመጡ 20 (ሃያ) አብዢ መምህራንን የላቀ የንድፈ ሃሣብና
የክህሎት ሥልጠና በመስጠት ማፍራት፤
በብሔራዊ ብየዳ ማሰልጠኛ ማዕከል ውስጥ ያሉትን 2 (ሁለት) አሰልጣኞች በደረጃ ስድስት ማብቃት፤
በብሔራዊ ብየዳ ማሰልጠኛ ማዕከል ውስጥ 1 (አንድ) አሰልጣኝ በማስመዘን ሪሰርተፊኬሽን ማሰጠት፤
በዌልዲንግ ቴክኖሎጂ በቴክኒክ ክህሎቶች ብቃታቸው የተረጋገጠ በአለም አቀፍ ደረጃ የሠለጠኑ ተወዳዳሪ ሊሆኑ የሚችሉና ኢንዱስትሪውን በቀጥታ
የሚደግፉ 7 (ሰባት) የኢብኮ ባለሙያዎችን ማፍራት፡፡
የሥልጠናው ቦታ
ሥልጠናው ፌዴራል ቴ/ሙ/ት/ሥ/ኤጀንሲ ምህንድስና ብቃት ማዕከል(cee) በሚገኘው የብሔራዊ የብየዳ ማሠልጠኛ ማዕከል የሚካሄድ ይሆናል፡፡
የሥልጠናው ተጠቃሚዎች
በክልልና ከተማ መስተዳድር የሚገኙ የቴ/ሙ/ተቋማት የበቁ አሰልጣኞችን ለማፍራት እንዲችሉ አብዢ መምህራን በማሠልጠናቸው ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
የብረታብረት ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ለሚያካሂደው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፤ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታና ተከላ እንዲሁም ለዘርፉ
በሚያስፈልጉ ሌሎች ፕሮጀክቶች ተሳትፎ የሚደርግ የበቃ ባለሙያ በማግኘት ተጠቃሚ ይሆናል፡፡
ስልጠናው ሞጁል 5 እና 6 ስለሆነ ስልጠናውን ለመሳተፍ ማንኛውም ሰልጣኝ ከዚህ በፊት ከሞጁል 1 እስከ 4 ያለውን ስልጠና የወሰደ መሆን ይኖርበታል፡፡
የሥልጠናው አይነት
2
ሥልጠናው በሁለት የብየዳ ሂደቶች /Process/ የሚሠጥ ሲሆን እርሱም የ MMA /Manual Metal Arc/ እና MAG /Metal Active Gas/ የተሰኙ የብየዳ
አይነቶች ሲሆኑ፤ ስልጠናውም በሞጁል 5 እና 6 የአለም አቀፉን የንድፈሃሳብና ተግባር ተኮር ስልጠና መሠረት ያደረገ ይሆናል፡፡
የሥልጠናው ጊዜ
አጠቃላይ ስልጠናው የሚወሰወደው ጊዜ ከጥቅምት 1 እስከ 30/2008 ዓ.ም ለ 22 የሥራ ቀናት የሚሠለጥኑበት ይሆናል፡፡ የሥልጠናው ክፍፍልን ከሠንጠረዥ 3
ይመልከቱ፡፡
ለሠልጣኞች የሚደረጉ ጥቅማ ጥቅሞች
ከቴ/ሙ/ተቋማት ለመጡት ሰልጣኞች የጉዞና የቀን አበል ኤጀንሲው ይሸፍናል፡፡
ለሥልጠናው የሚመጡ ሁሉም ሠልጣኞች የመኝታ አገልግሎት በ cee ማዕከል ባሉት ማረፊያዎች ይሰጣል፡፡
በሥልጠናው ቀናት ለሚደረጉ የምሣ፣ የሻይ፣ ቡናና የውሃ ወጪዎችን ለቲቬት መምህራንና ለአሠልጣኞች ኤጀንሲው ይሸፍናል፡፡
ለንድፈሃሣብ ሥልጠና የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች እና ሃንድአውቶች ለሁሉም ሠልጣኞች ተባዝቶ ይሰጣል፡፡
ከሠልጣኞች ምን ይጠበቃል?
ሁሉም ሠልጣኞች መስከረም 30/2008 ዓ.ም እሁድ በማዕከሉ ግቢ ተገኝተው ሪፖርት ማድረግና አዳራቸውንም በማዕከሉ የሠልጣኞች ማደሪያ ክፍል
ይሆናል፡፡
ሁሉም ሠልጣኞች የሥራ ቱታና የሥራ ጫማ ለሥልጠናው ይዘው መምጣት አለባቸው፡፡
ሁሉም ሠልጣኞች በሥልጠናው ወቅት የሥራ ትጥቅ እና የቅድመ ጥንቃቄ ትጥቆችን መልበስና መሥራት አለባቸው፡፡
ለሁሉም የኢብኮ ሰልጣኞች የሚበቃ ማቴሪያል ስልጠናው ከመጀመሩ በፊት በቅድሚያ ለብሔራዊ ብየዳ ማሰልጠኛ ማዕከል ገቢ ያደርጋል ይኸውም ከዚህ
በፊት ተፈጥሮ የነበረውን የስልጠና ማቴሪያል ዕጥረትና የጊዜ ብክነትለመከላከል ይረዳል፡፡
አጠቃላይ ሥልጠናውን ለማካሄድ በብር 1,069,536.60 ሣንቲም የሆነ አጠቃላይ የበጀት ግምት የሚያስፈልግ ሲሆን፤ የዝርዝር በጀቶችን ክፍፍል ከሠንጠረዥ 1
ይመልከቱ
3
ሠንጠረዥ 1. ለሥልጠናው የሚውል ዝርዝር የበጀት ክፍፍል
የ/MMA/እና/MAG/
የመፈጸሚያ ጊዜያት ሳምንት 1 ሳምንት 2 ሳምንት 3 ሳምንት 4 ሳምንት 5
ሥልጠና