You are on page 1of 5

ተማሪና መምህር

ተማረው መምህሩን ጥያቄ ጠየቀው

መምህሩም በእርጋታ እድሉን ቢሰጠው

ለምን ነው የምማር ንገረኝ መምህሬ

እስከመቼ ይሆን ካንተ ጋር መኖሬ

መምህሩም መለሰ ስማኝ ልጀ አለ

አንተ የምትማር እንቅልፍህን አጥተህ

እኔም የምደክመው ዝም ብየ መሰለህ

የተደበቀውን ምስጢር ለመመርመር

ስለምትፈልግ ነው ይህች ውድ ሀገር

እናም ተማር ልጄ አትሰልች አደራ

ፈጥነህ እንድትደርስ እናትህ ስትጠራ

ድካሙንም ታገስ መራብ መጠማቱን

ችግሩንም ልመድ አገኝቶ ማጣቱን

ይህን ሁሉ ከታገስክ ሁሉን ታልዋለህ

በውጤት የታጀብክ ጀግና ትሆናለህ

አለና መምህር ለተሜ ነገረው

ተማሪውም ሰምቶ የመምህሩን ምክር

ማንበቡን ቀጠለ ምንም ሳያማርር

እንድህ ብሎ ሲማር ያ ደግ ተማሪ

የፊዚክስ ሊቅ ሆነ ቀመርን ቀማሪ

ኢንጂነርም ሆነ ፓይለትን አብራሪ

ብዚህ አላበቃም ጉዞውን ጀመረ

የኮምፒውተር ክህሎት ጥበብን ተማረ

ታዳ ይህኔ ነበር ሀገር የጠራችው

ልጄ ድረስልኝ ጠብቀኝ ያለችው


ያሁኑን ምሁር የትናንት ተማሪ

ልጁም ይህን ሰምቶ የእናት ሀገር ጥሪ

አለሁ እናታለም ደርሸልሻለው

መረብ ደህንነቱን እጠብቀዋለው

አለ ይኸ ምሁር የትናንት ተማሪ

ማስታወስ ጀመረ ያንን አስተማሪ

ለካስ የመከረኝ ለኔ ብሎ ነበር

እኔ እየረበሽኩት እሱ የሚመክር

እዚህ ለመድረሴ ምሁር ለመሆኔ

ያደግ መምህር ባይኖር ኑሮ ጎኔ

ስሜ ሌላ ነበር ምሁርነት ቀርቶ

አሁን እኖራለሁ ልቦናየ እረክቶ

አራብሳ ዑራኤል ቤ/ክ 12/02/2015

ታዛዥ ባለፀጋ

ሁሉ አለው ይህ ቀረህ ማይባል

ንብረት አውቀት ገንዘብ አደራጅቶ ይዟል

ግን ይህ ሁሉ የኖረው ባለፀጋ ሳለ

ለሁሉም ታዛዥነው እጅግ የታደለ

እኔና ዘመኑ

አንድ ቀን ከእንቅልፌ ስነቃ አንድ ትልቅ አባት ጺማቸው ነጭ ፀዓዳ የሆነ ከእርግናቸው የተነሳ ግርማቸው የሚያስፈራ ፣
ንግግራቸው የአዘነውን ሰው የሚያረጋጋ ፣ ከአንደበታቸው የሚወጡት ቃላት የታመመች አንደበትን የሚያክሙ ጽኑ
መድኃኒት ነበሩ ፣ ታዲያ ይህ አባት ድንገት ከአጠገቤ ከተፍ ብለው ይመጡና ሰላማደርክ ልጄ አሉኝ በአባትነት ለዛ፣ አ አባ
ደህና አደሩ አልኩ አፌ አየተሳሰረ ፣ልጄ ምን ሆንክ አይዞህ አትፍራ አሉኝ በሚያጽናና ቃላቸው እሺ አባ ምን ልታዘዝ
አልኩ አሁንም በፍርሃት መንፈስ ፣ ልጄ እኔ የመጣሁት ጥያቄ ልጠይቅህ ነው አሉኝ ልብን በሚያረሰርስ ቃላቸው ፣ልጄ
ለምን እስካሁን ተኛህ አሉኝ ፣ አይ አባቴ አሁን እኮ ገና ጧት ደግሞ የዘመኑን ነገር ያውቁታልጭንቀቱ ቀን ከሌት
የሚያስተኛ አይደለም ፣ ግን አባ ታዝበውታል ምን አይነት ዘመን እንደደረስን ሰው ከሰው ጋር ተግባብቶ እማይኖርበት ፣
ፍቅር እሚባል ጠፍቶ ሰው አርስ በእርሱ ካልተጣላ መኖር የማይችል የሚስልበት ፣ አባ አሁንስ ሳስበው ዘመኑ ያረጀ
ይመስለኛል ፣ አልኩ መናገር በማይችለው በዚህ ኮልታፋ አንደበቴ ፣ ልጀ መልካም መስራት ቢያቅትህ ስህተትህን ለምን
ታሳብባለህ ፣ ተማሪ ስትሆን ከማንበብ ይልቅ ሁሌ ከመዝለል በቀር እራስክን ለማሻሻል የማትጥር ፣ የመፈጠርህ አላማ
ሰወችን መርዳት ሲሆን አንተ ግን እኔ ብቻ ይድላኝ ብለህ የምታስብ ፣ እውነትን እረግጠህ ሀሰት ማውራት የሚቀናህ ፣
ለሰዎች መልካም ነገር ከማሰብ ይልቅ ሀሜት የሚቀድምህ የ አንተ ማንነት ባረጀ ቁጥር ትናንት የነበርኩ ዛሬ ያለሁ ነገም
የምኖር እኔን ለምን ፣አረጀ ትለኛለህ ፣ አንተ ያረጀ ስራ በሰራህ ቁጥር የዘመን ሽፋን ይቅርብህ ፣ ልጄ እኔ ትናንት የነበርኩ
ዛሬ ያለሁ ነገም የምኖር የአንተ ታዛቢ ነኝና ምክንያቱ ቀርቶ መልካም ስራ ስራ ሲሉኝ አፈርኩ፣ አዎ አባ ልክ ነዎት
በእርሰዎ እያመካኘሁ እኔ ነበርኩ ያረጀሁ ፣ የፍቅር ጠብታ የሌለው ደረቅ ጭንጫ መሬት የኔ ልብ ነበር ያረጀ ፣ አባ ልክ
ነዎት ንግግሬ እንደ እሾክ የሚኮሰኩስ የኔ አንደበት ነበር ያረጀ ፣ አልኩና ለአባ ተናግሬ መለስ ብየ ሳስበው ለካስ
የምንሰራውን ስራ ከሰው በንሰውረው ከህሊናችንና ከጊዜ አንሰውረውም፣ ጥፋትን ስንሰራ ሰወች ከመውቀሳቸው በፊት
እኛን የኣሚወቅሰን ህሊና የሚባል ታላቅ ዳኛ አለ ብዬ እኔ ያላወቅኩት እርሱ ግን የሚያውቀኝን ዘመን እያሰብኩ ሥራየን
ጀመርኩ።

ሰው

ሁሉ የተሰጠው ሁሉን የሚገዛ


አንድ ፍጥረት አለ አዕምሮ የገዛ

ይህም ልዪ ፍጥረት ሁሉ የታደለው

የፍጥረታት አክሊል የሰው ልጅ ብቻ ነው::

እኔና ዘመኑ

ከእለታት አንድ ቀን ስነሳ ከእንቅልፌ

ልብሴን ለባብሼ አልጋየን አንጥፌ

የእለት ተግባሬን ልጀምር ስነሳ

አንድ አዛውንት ሰው ጀመሩ ወቀሳ

ምነው አባቴ ሆይ ከቶ ምን አጠፋው

አልሰረቅሁ አልዋሸው ምንም አላጠፋው

እንድህ ያስፈራሩኝ ምን ጥፋት አይተው ነው

ንገሩኝ አባቴ ያለብኝን ጥፋት

ብየ ጠየቅኋቸው በታላቅ ፍርሃት

አባም መለሱልኝ ጀሮ ስጠኝ አሉ

ነጩን ፂማቸውን እያፍተለተሉ

አልዋሸሁም ላልከኝ እጅግ ዋሽተኸኛል

ሰውነትክን ረስተህ አራዊት ሆነሀል

አልሰረቅኩም ላልከኝ እኔን ሰርቀኸኛል

የተሰጠኽን ዘመን በከንቱ አጥፍተሃል

ሁሌም አይሀለሁ እታዘብሀለው

ምንም አልሰራህም

You might also like