You are on page 1of 16

በአብ ስም አምኜ አብን ወላዲ አሥራጺ ብየ፣ በወልድ ስም አምኜ ወልድ ተወላዲ ብየ፣

በመንፈስ ቅዱስ ስም አምኜ መንፈስ ቅዱስን ሠራጺ ብየ ምንም ለአጠይቆተ አካላት በስም፣
በውስጣዊ ግብር፣ በአካል፣ በኲነት ሦስት ብል በባሕርይ፣ በውጫዊ ግብር፣ በሥልጣን፣
በህልውና፣ በመንግሥት፣ በዕሪና አንድ አምላክ ብየ አምኜ ረዴኤተ እግዚአብሔርን አጋዥ
በማድረግ ስለ ቊጣ ምንነት መጻፍ፥ እዠምራለኹ።

“ከቊጣ ራቅ” (መዝ ፴፯፥፰)

በገብረ ኢየሱስ
የመጸሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ቊጣን በሚገባ ወይም በማይገባ በሰው ላይ መፍረድ፣ መናገር፣
ሰውን መቅጣት፣ መገሠጽ በማለት ይተረጉመዋል።

ቊጣ ከፈጻሚው አንጻር የእግዚአብሔር ቊጣ እና የሰው ቁጣ ተብሎ በኹለት ይከፈላል።


የሰው ቊጣ ደግሞ የጻድቅ ሰው ቁጣና እና የኀጢአተኛ ቊጣ ተብሎ ለኹለት ይክፈላል።

፩. የእግዚአብሔር ቊጣ (ፍርድ)

እግዚአብሔር ቅዱስና ጻድቅ ስለኾነ ሰው የተሰጠው ትእዛዝ አፍርሶ ኀጢአት ሲፈጽም


ይቈጣል። “ምድርም በኹለንተናዋ ዲን እና ጨው መቃጠልም እንደ ኾነባት እንደትዘራም
እንድታበቅልም ማናቸውም ሣርና ልምላሜም እንዳይወጣባት እግዚአብሔር በቊጣውና
በመዓቱ እንደ ገለባበታቸው እንደ ሰዶምና ገሞራ እንደ አዳማና እንደ ሲባዮ እንደ ኾነች ባዩ
ጊዜ አሕዛብ ኹሉ ‘እግዚአብሔር በዚች ምድር ስለምን እንደዚኽ አደረገ? ይኽስ የቊጣው
ታላቅ መቅሰፍት ምንድር ነው?’ ይላሉ፤ ሰዎችም እንዲኽ ይላሉ፥ ‘የአባቶቻቸው አምላክ
እግዚአብሔር ከግብጽ ምድር ባወታቸው ጊዜ ከእነርሱ ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን ስለተዉ፣
ኼደውም የማያውቋቸን እና ያልታዘዙትን ሌሎችን አማልክት ስላመለኩ እና ስለሰገዱላቸው
፥ ስለዚኽ በዚኽ መጽሐፍ የተጻፈውን መርገም (ቅጣትና ፍርድ) ኹሉ ያወርድባት ዘንድ
የእግዚአብሔር ቊጣ በዚች ምድር ነደደ፤ ዛሬም እንዳሉ እግዚአብሔር በቊጣና በመቅሠፍት
በታላቅም መዓት ከምድራቸው ነቀላቸው ወደ ሌላም ምድር ጣላቸው” እንዲል መጽሐፍ፤ ዘዳ
፳፱፥፳፫። የእግዚአብሔር ቊጣ (ፍርድ) በእሳት ይመሰላል። “ስለዚኽ የማይናወጥን

1
መንግሥት ስለምንቀበል በማክበርና በፍርሀት እግዚአብሔር ደስ እያሰኘን የምናመልክበትን ጸጋ
እንያዝ፤ አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ እሳት ነውና” ዕብ ፲፪፥፳፰-፳፱፣ ራዕ ፲፮፥፭-፯፤
፲፱፥፩-፪።

የእግዚአብሔር ቊጣ እንደሰው ቊጣ ስሜታዊ በመኾን የሚመጣ (በስሜት የሚፈርድ)


አይደለም፤ ማለትም ቶሎ የሚቈጣና የሚበርድ አይደለም።

የእግዚአብሔር ቊጣ በፍርዱ (በቅጣቱ) ይታወቃል/ ይታያል። ዘዳ ፱፥፭-፰፣ ዘካ ፰፥፲፬፣ ዮሐ


፫፥፴፮፣ ሮሜ ፩፥፲፰፤ ፪፥፭፤ ፱፥፳፪፤ ኤፌ ፭፥፮፣ ራእ ፲፮፥፩።

የእግዚአብሔር ቊጣ ተራሮችን የሚያቀልጥ ነው። ኖሆ ፩፥፮፣ ስቱ ፯፥፳፫፣ ዘኁ ፲፩፥፩፣ ዘዳ


፬፥፳፩፣ ፩መቃ ፳፯፥፲፱፣ መዝ ፳፥፱

ምእመናን ከሥላሴ ቊጣ (ፍርድ) በንስኃ፣ በጸሎት እና በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ይድናሉ።


“[ምናሴ] በተጨነቀ ጊዜ አምላኩን እግዚአብሔርን ፈለገ፤ በአባቶቹም አምላክ ፊት ሰውነቱን
እጅግ አዋረደ፤ ወደ እርሱም ጸለየ እርሱም ተለመነው ጸሎቱንም ሰማው ወደ መንግሥቱም
መለሰው” ፪ዜና ፴፫፥፲፪-፲፫። “እሥራኤላዊያን በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ …
የቀና መንገድንም መራቸው፤ … ከመከራቸውም አዳናቸው፤ ከጨለማና ከሞት ጥላ
አወጣቸው፤ እስራታቸውንም ሰበረ፤” መዝ ፻፮፥፮፣፲፫፣፲፱፣፳፰። “ከቊጣው (ከፍርዱ) በርሱ
(በኢየሱስ ክርስቶስ) እንድናለን”፤ ሮሜ ፭፥፱። “ለሕያውና ለእውነተኛ አምላክም ታገለጉ
ዘንድ ከሙታንም ያስነሣውን ልጁን ርሱንም ኢየሱስን ከሚመታው ቊጣ (ፍርድ) የሚያድነንን
ከሰማይ ትጠብቁ ዘንድ ከጣዖቶቻች ወደ እግዚአብሔር እንዴት ዘወር እንዳላችኹ [ሰዎች
ስለናንተ] ይናገራሉ” ፩ተሰ ፩፥፱-፲፤ እንዲል መጽሐፍ። ቅዱስ እግዚአብሔር ለምን ይቈጣል?
ቈጣው እንዴት ይተወቃል? ለሚለው ጥያቄ መልስ ይኾን ዘንድ ይኽን ካልን ስለ ሰው ቊጣ ሰፋ
ያለ ጊዜ ወስደን መተንተን እንጀምራለን።

፪. የሰው ቊጣ

መግቢያችን ላይ እንዳስቀመጥነው የሰው ቊጣ የጻድቅ ሰው እና የኀጢአተኛ ሰው ቁጣ ተብሎ


በኹለት ይከፈላል። ይኽ አከፋፈል መሠረት ያደረገው የቊጣውን ዓላማ ነው። የቊጣው
ዓላማ ለማነጽና ለተግሣጽ ከኾነ የጻድቅ ሰው ቊጣ ወይም ተገቢ ቊጣ ሲባል፤ ለመፍረድና
2
ለመኰነን (ከንቱ ቊጣ) ከኾነ ደግሞ የኀጢአተኛ ሰው ቊጣ ወይም ተገቢ ያልኾነ ቊጣ/ ከንቱ
ቊጣ ይባላል።

፪.፩ የጻድቅ ሰው ቊጣ - የሚገባ ቊጣ

“በከንቱ ወንድሙን የሚቈጣ የገሃነም ፍርድ ይገባዋል” (ማቴ ፭፥፳፪)፤ “በከንቱ ወይም
ያለምክንያት” የሚለው ቃል ምክንያታዊና ለመንፈሳዊ ሕይወት ጠቃሚ በኾነ ጉዳይ መቈጣት
የሚገባ መኾኑን ጠቃሚ ነው። ማለትም እግዚአብሔር አምላክ ከንቱ የኾነን ቊጣ እንጂ
ተገቢን ወይም ምክንያታዊ የኾነን ቊጣን አልከለከለም። ምክንያቱም፥

 አንደኛ ሰው ኾኖ ከቊጣ ስሜት ነጻ መኾን ስለማይቻል።

ምንም እንኳ ቊጣ ለሰው ልጅ የተፈጠረ ባይኾንም - “ትዕቢት ለሰው የተፈጠረ አይደለም፤


[ከንቱ] ቊጣና ጥፋትም ከሴት ለሚወለድ ሰው አይደለም” ሲራክ ፲፥፲፰ - ከውድቀት በኋላ
ግን ቊጣ ተፈፍጥሯዊ ስለኾነ፥ ሰው መጥፎ ነገርን ሲመለከት ሊቈጣ ይችላል። ቅዱሱና ነቢዩ
ሙሴ ቆሬ፣ ዳታንና አቤሮን በእርሱ ላይ በዐመጹበት ጊዜ አዝኗል፤ ጸሎታቸውንም እንዳይቀበል
እግዚአብሔርን ተማጽኗል (ዘኁ ፲፮፥፲፪-፲፱)፤ እንደ ልቤ የተባለው ቅዱስ ዳዊትም ወንድ
ልጁ አምኖን ከታናሽ እህቱ ከትዕማር ጋር እንደተኛ/ እንድረሰባት በሰማ ጊዜ ምንም እንኳ
የበኲር ልጁ ስለኾነ ሊገድለው ባይፈልግም ተቈጥቶበታል (፪ሳሙ ፲፫፥፩-፳፪)፤ አይሁድ
ከእግዚአብሔር ሕግ የሚጻረር ሥራን በሠሩ ጊዜ ከ፲፪ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የኾነው ነቢዩ
ነህምያ ተቈጥቷቸዋል(ነህ ፭፥፩-፲፫)። ከዚኽም የምንረዳው ነገር ቢኖር ምክንያታዊ ቊጣ
ከእኛ አቅም በላይና የማንቈጣጠረው ባይኾንም ተፈጥሯዊ መኾኑን ነው።

ነገር ግን ቊጣ ተፈጥሯዊ የኾነው ለእኛ ጥቅም ስላለው እንጂ ሰዎችን እንድንጎዳበት


አይደለም። ቊጣችንን በኃጢአት እንዳንወድቅ ለመከላከል፣ በእኛ ውስጥ ስላለው የኃጢአት
ምክንያትና ስለሚፈታተነን ነገር በራሳችን ላይ ተቈጥተን በቁጭት ወደ ንስሓ ለመመለስ፣
ይረዳናል፤ ከኃጢአት ለመራቅ መጠቀም ተገቢ ነው፡፡

ከዛሬው እኩይ ተግባራችን ለመመለስና ደካማ ማንነታችንን ለመቀየር በራሳችን ላይ


መቊጣታችን ተገቢ ነው፡፡ ራሳችንን ‹‹በእውነት መንገድ እየኼድን ነው?›› ብሎ ለመጠየቅ
ብርታት ይሰጠናል፡፡ ‹‹እኔ መኾን ያለብኝ በጐ ሰው ወይንም እውነተኛ ክርስቲያን ነው!››
3
ለማለትም ይረዳናል፡፡ ኃጢአት መሥራት ጥፋት መኾኑንና ከባድ ቅጣት እንደሚያስከትልም
አውቀን ዳግም እንዳንበድል ስናጠፋ በራሳችን መቈጣት አለብን፡፡ ይህም የባሰ ኃጢአት
ከመሥራት ለመቈጠብ ያግዘናል፤ በተሳሳተው መንገድም እንዳንጓዝም ራሳችን ለመከላከል
ይረዳናል፡፡

ጠላታችን ዲያብሎስም የእኛ ድክመት ስለሚያስደስተው በዓለማዊ ሐሳቦችና ምግባራት


ሰውነታችንን በመያዙ ከታሰርንበት የኃጢአት አረንቋ መላቀቅ አልተቻለንም፤ በዚህ መናደድና
መቈጣት ያስፈልጋል፡፡ ቊጣታችንም ወደ እግዚአብሔር እንድንመለስ ይረዳናል፡፡

“በተፈጥሮ ቊጣ ተሰጥቶናል፤ በጎርቤቶቻችን ላይ የኀይለኝነት ድርጌቶችን እንድንፈጽም


አይደለም፤ በኀጢአት ያሉትን ሰዎች እንገሥጻቸው ዘንድ፣ ራሳችንን በቁርጠኝነትና በወኔ
እናነሳሳ ዘንድ፣ ልፍስፍሶችና ሰነፎች እንዳንኾን ነው እንጂ። ቊጣ በውስጣችን የተተከለው
(ማለትም ተፈጥሯዊ የኾነው) እንደ ነዳፊ ነገር ጥርሳችንን አፋጭተንበት በዲያብሎስ ላይ
እንድንነሣበት፣ በእርሱ ላይ ኀይለኛ እንድንኾንበት እንጂ እርስ በርሳችን በሰልፍ ተቡዳድነን
እንድንጣላበት አይደለም።” ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትርጓሜ ኤፌሶን ድርሳን ፪

 ኹለተኛ ቊጣ ጠቃሚ ስለኾነ

ጊዜውንና ቦታውን እንዲኹም እንዴት መጠቀም እንዳለብን ከአወቅንበት ቊጣ ጠቃሚ ነው።


ለምሳሌ የቤተ ክርስቲያን ማኅቶት የሚኾን ቅዱስ ጳውሎስ በመቈጣቱ ምክንያት በቆሮንቶስ
እና በገላቲያ ሰዎች ላይ ያመጣው በቈዔት ማየት ይቻላል።

“ወንድሙን በከንቱ የሚቈጣ የገሃነም ፍርድ ይገባዋል” (ማቴ ፭፥፳፪)። “በከንቱ የሚቈጣ”
ይላል እንጂ “የሚቈጣ” ብቻ አይልም። ሰዎች ከስሕተታቸው ለመመለስ፣ ለማነጽና
ለመገሠጽ፣ ሕጻናት ያልተማሩትን እንዲማሩ የተማሩትን እንዳይገድፉ፣ መናፍቃን
እንዳይሰለጥኑ፣ ሃይማኖት እንዳይጠፋ፣ ክህደት እንዳይስፋፋ የሚደርግ ቊጣ የጽድቅ ቊጣ
ወይም ተገቢ ቊጣ ይባላል። ተገቢ ቊጣ አስተዋይ ሰውን ከስሕተት አረንቋው ታወጣዋለች።
፩መቃ ፲፪፥፳፱፣ ዘፍ ፴፩፥፴፮-፶፭

ይኽም ማለት ቊጣ አለጊዜው ሲኾን እንጅ መቈጣት በራሱ በደል ወይም ኀጢአት አይደለም።
“ተቈጡ ግን አትበድሉ (ኀጢአትን አታድርጉ)” የሚለን ለዚኽ ነው፤ (መዝ ፬፥፬፤ ኤፌ
4
፬፥፳፮)። ነገር ግን መጽሐፍ “ተቈጡ” ሲል ትእዛዝ እያስተላለፍ ሳይኾን ሰው በተፈጥሮው
የሚቈጣ መኾኑን ለመግለጽ ነው። “ኃጢአትን አታድርጉ” የሚለንም ብትቈጡ እንኳ
ቊጣችኹን ፀሓይ ሳይጠልቅ አብርዱ ማለቱ ነው። ለዚኽ የቅዱስ ጻውሎስ ትምህርት
(በቈጣችኹ ፀሓይ አይግባ ለሚለው ትምህርት) መነሻው መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ
“እንግዲኽ መባኽን በመሠዊያው ላይ ብታቀርብ በዚያም ወንድምኽ አንዳች ከአንተ ላይ
እንዳለው ብታስብ በዚያ በመሠዊያው ፊት መባኽን ትተኽ ኺድ አስቀድመኽም ከወንድምኽ
ጋራ ታረቅ በኋላም መጥተኽ መባኽን አቅርብ” ብሎ በወንጌል ያስተማረን ትምህርት ነው
(ማቴ ፭፥፳፫-፳፬)።

ጻድቅ “ሳትመረምር አትንቀፍ፤ አስቀድመኽ ተረዳ፥ በኋላም ትቅቈጣለኽ” የሚለውን


የጢቢቡን ሰው ምክር በልቡ ይዞ ፥ ሳይመረምር አይቈጣም (ሲራ ፲፩፥፯)። ጻድቅ ሲቈጣ
ጊዜና ቦታ ይመርጣል። የቊጣን ተገቢ ጊዜ የምንለው ሌሎች ሰዎች ከሥርዓት የለሽ
መንገዳቸው እንዲመለሱና ቸለኝትነታቸውን እንዲተው ስናደርጋቸው ነው። በሌላ ቋንቋ
ቊጣ የሚገባ የሚኾንበት ዋና ምንክያት የምንቈጣው አካል ባለማወቅም ይኹን በንዝህላልነት
የነገሮች ክብደትና ጉዳት የማይረዳ ፣ የሚሠራውንም ሥራ ትክክል አለመኾኑ የሚገነዘበው
በኃይለ ቃል ሲነገረው ኾኖ ሲገኝ ነው።

ይኽ የቊጣ ዓይነት ለበቀል ሳይኾን ስሕተት የሠራን ሰው (ሕዝብ) ለማስተካከል የሚደረግ


ተግሣጽ ነው። የቆሮንቶስ የገላቲያ ሰዎች የተፈወሱት - ወደ ጽድቅ ጎዳና የተመለሱት በቅዱስ
ጳውሎስ ቊጣ - ተግሣጽና ምክር - ነው። የጻድቅ ሰው ቊጣ (ተግሣጽ) የፍቅር መግለጫ ነው።
“እግዚአብሔር የወደደውን ይገሥጻልና አባት ልጁን እንደ ሚገሥጽ” (ምሳ ፫፥፲፪)፤ “ልዩ ልዩ
በኾነ እንግዳ ትምህርት አትወሰዱ፤ ልባችኹ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ። በመብል
አይደለም፤ በዚኽ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና።” (ዕብ ፲፫፥፱)።

ስለዚኽ ቅዱስ ጳውሎስ ለልጁ ለጢሞቴዎስ “ሽማግሌ የኾነውን አትገሥጸው፤ እርሱን ግን


እንደ አባት፣ ጎበዞችን እንደ ወንድሞች፣ ባልቴቶችን እንደ እናቶች፣ ቆነጃጅትንም እንደ
እኅቶች በንጽሕና ለምናቸው፤ በእውነት ባልቴት የኾኑትን ሴቶች አክብር” ብሎ እንደ መከረው
ወንድሞቻችንን ስንመክርና ስንገሥጽ በፍቅርና በማስተዋል ከስሜታዊነት በጸዳና በሰከነ
መንፈስ መኾን አለበት።
5
፪.፪ የኀጢአተኛ ቊጣ - የሚገባ ቊጣ

የኀጢአተኛ ቊጣ የምንለው ከቅናትና ከበቀል ስሜት፣ ከኲራት፣ ከስንፍና፣ ከንዴት የሚመነጭ


ሲኾን ነው። የኀጢአተኛ ቊጣ ትሕትና አልባ ነው። ይኽ ዓይነቱ ቊጣ የመግደል ሥር ነው (ዘፍ
፵፱፥፮)። ስለኾነም በከንቱ አትቈጣ የሚለው የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ
ትእዛዝ አትግደል የሚለውን የኦሪት ሕግ በውስጡ ጠቅልሎ ይዟል። ስለዚኽ መግደልን
ለመራቅ የሚማር ሰው እኩል ቊጣንም ማራቅ አለበት። ካልተቈጣ መግደልን ከሩቁ
ያርቃታል።

መዳን እንዳንችል ማለትም የእግዚ አብሔር ልጆች እንዳንኾን በዲያብሉስ ክሚዘጋጁ


ወጥመዶች አንዱ ከንቱ ቊጣ ነው። ቊጡ ኾንን ማለት የዲያብሎስ ወዳጆች ኾንን ማለት
ነው። የሰው ልጅ ጠላት ዲያብሎስ እንዲኽ ይላል፦ “[ለአዳምን ልጆች] የዚኽን ዓለም ግንዘብ
ባሳየኋቸው ጊዜ ከቀኣች መንገድ ልቦናቸውን አስታለኹ፤ መልከ መልካም ሴቶችንና
ቆነጃጅትንም ባሳየኋቸው ጊዜ በእነዚኽ ከቀናች መንገድ አርቃቸዋለኹ። … ስለ ቊጣና ጠብ
የትዕቢት ቀናትን ባሳየኋቸው ጊዜ በሂኽ ኹሉ ወደ እኔ መንገድ እመልሳቸዋለኹ። …
ስድብናንና ቊጣን በማብዛት በማስወደድ … መዳን እንዳይችሉ እኔ እጣላቸዋለኹ” (፫መቃ
፩፥፩- ፪፥፩-፯)።

ቊጣ የሥጋ ፍሬዎች ከሚባሉት አንዱ ሲኾን ውጤቱም ገነመ እሳት ነው። በከንቱ የሚቈጣ
ሰው ከዘለዓለም ሕይወት የተለየ ነው። “የሥጋ ሥራም የተገለተ ነው፤ እርሱም ዝሙት፣
ርኲሰት፣ መዳራት፣ ጣዖትትን ማምለክ፣ ሟርት፣ ጥል፣ ክርክር፣ ቅንዓት፣ ቊጣ፣ ዐድመኝነት፣
መለያየት፣ መናፍቅነት፣ ምቀኝነት፣ ይኽንም የሚመስል ነው። አስቀድሜ እንዳልኹ፥
እንደነዚኽ ያሉትን የሚያደርጉ ኹሉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም”፤ “ወደድሙን
በከንቱ የሚቊጣ የገሃነም ፍርድ ይገባዋል”። ገላ ፭፥፲፱-፳፪፤ ማቴ ፭፥፳፪፣ “ተሳዳቢዎች
(በከንቱ የሚቊጡ) የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም” ፩ቆሮ ፮፥፱-፲፤ ኤፌ ፭፥፫-፭።

ቊጣ ከመንግሥተ ሰማይ ብቻ የሚለየን አይደለም፤ እድሜያችን የሚያሳጥር፣ ሕይወታችን


ለጉስቈልና የሚያጋልጥ እና ማኅበራዊ ግንኙነታችንም የሚጎዳ፣ ቈጣው የተሰነዘረበትንም

6
ሰው ለድንጋጤ፣ ለስሜት መጎዳት፣ ለብስጭት፣ ለፍርሐት፣ ለሞት የሚያጋልጥ ብሎም ለበቀል
የሚያነሣሣ ክስተት ነው።

ቊጣ የጽድቅን ሥራ አያሠራም። ቊጣ ፀረ ፍቅር ነው ። “ነገረ ሰሪ አንደበት ብዙ ሰዎችን


አወካቸው፤ ከአንዱም ወገን ወደ አንድ ወገንም እንዲሰደዱ አደረጋቸው፤ ብዙ አምባዎችንም
አፈረሰች፤ የመኳንንቱንም ቤት አፈረሰች፤ ቀባጣሪ አንደበት ደጋግ ሴቶችን ከባሎቻቸው ቤት
አስወጥታ ሰደዳቸው፤ ገንዘባቸውንም አጠፋችባቸው፤ ከእርሷ ያልተጠበቀ ሰው ግን
ለዘለዓለሙ አያርፍም፤ በሰላምም አይኖርም። የግርፋት ቊስል መግል ይይዛል፤ የአንደበት
ቊስል (ክፉ ንግግር) ግን አጥንትን ይሰብራል። በጦር የወደቁ ብዙ ናቸው፤ ነገር ግን በአንደበት
እንደ ተፉ አይደለም። ከእርሷ [ከቊጣ] የዳነና በጥፋትዋ ያልተሰነካከለ፥ በቀንበሯም ያላረሰ፥
በእግር ብረቷም ያልታሰረ ብፁዕ ነው። ቀንበሯ የብረት ቀንበር ነውና፤ እግር ብረቷም የብረት
ነውና። ሞቷም ክፉ ሞት ነው፤ ከርሷም ሲኦል ትቀላለች። በጻድቃን ግን አትደርስባቸውም፤
በኣሳቷም አይቃጠሉም። እግዚአብሔርን የዘነጉ ሰዎች በእርሷ ይወድቃሉ፤ በማይጠፋ እሳቷም
ታቃጥላቸዋለች፤ እንደ አንበሳም ትወረወርባቸዋለች፤ እንደ ነብርም ትይዛቸዋለች።
ንብረትኽን በእሾኽ ብታጥር፥ ወርቅኽንም ብትቈልፍ፥ ነገርኽን በሚዛን ብትመዝን፥
ለአፍኽም መዝጊያና ቈልፍ ብታደርግ፥ ዳግመኛም በአንደበትኽ እንዳትሰነካከል፥
በሚያድንኽም ፊት እንዳትጥልኽ ተጠበቅ” ሲራ ፳፰፥፲፬-፳፮፤ “ቊጣና ቅናት በሕይወት
የሚኖርበትን ዘመን ያሳንሳሉ፤ የብስጭት ኀዘንም ጊዜው ሳይደርስ ያስረጃል” እንዲል
መጽሐፍ፤ ሲራክ ፴፥፳፬።

ቊጣ የጥላቻ ፣ የትዕቢት፣ እኔ እበልጣለኹ የሚል ስሜት መንፈስ መገለጫ ስለኾነ እንደ


መግደል ይቈጠራል። “ወንድሙን የሚጣላ ኹሉ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ ነፍሰ ገዳይ የኾነ ኹሉ
የዘለዓለም ሕይወት በእርሱ እንዳይኖር ታውቃላችኹ” እንደተባለ ጥላቻ ከመግደል
አይተናነስም (፩ኛ. ዮሐ ፫፥፲፭)

፪.፪.፩ ቊጣን ተፈጥሯዊ ከኾነ እንዴት መተው/ መራቅ ይቻላል?

ብዙ ጊዜ ሲቆጣ ለኖረና ቊጣ ልማዱ ለኾነበት ሰው ቊጣን መተው ከባድ እንደሚኾን


አያጠያይቅም። ነገር ግን ሰማያዊ ቤታችን እና ምድራዊ ሕይወታችን የተስተካከል ይኾን ዘንድ

7
ቊጣን ማስወገድ አለብን፤ እድናስወግድም ክርስትናችን ያስገድደናል። ስለኾነም ከቊጣን
ለመላቀቅ የሚከተሉትን መፍትሔዎች መተግበር ያስፈልጋል።

1. የቊጣ ምንጮቹን ጠንቅቆ ማወቅ እና ለቊጣ ከሚያነሣሱን


ሰዎችና ኹኔታዎች መራቅ
አንዳንድ ጊዜ ሰዎች በሌሎች ላይ ባላቸው ጥላቻ ወይንም በራሳቸው ድክመትም የተነሣ
ቊጣቸውን መቈጣጠር ያቅታቸውና ወደ አልተፈለገ ክርክር እንዲሁም ጥል ውስጥ ይገባሉ፡፡
ሥነ ልቡናዊ እንዲሁም አካላዊ ጒዳትም ያደርሱባቸዋል፡፡ በተለይም በዚህ ጊዜ ሰዎች
በእውነት መንገድ ላይ በሚጓዙ ክርስቲያኖች ላይ የሚያደርሱት ጒዳት ከፍተኛ ነው፤
ምክንያቱም እውነቱን ከመቀበል ይልቅ በእነርሱ ላይ ጥላቻ ስለሚያድርባቸው ከእነርሱ ጋር
ስምምነት ላይ አይደርሱም፡፡ ሐሰታቸው ተቀባይነት በማያገኝበት ጊዜም ባልተገባ ቊጣ ሆነው
በክፉ ቃላት ሰዎችን ያሳዝናሉ፤ ያስከፋሉ፤ ይጐዳሉም፡፡ ከዚያም ባሻገር ሥራዬ ብለው
በእነርሱም ዘንድ ንዴት በማጫር ወደ ድብድብ ውስጥ እንዲገቡ ይገፏፏቸዋል፡፡ በመሆኑም
ከእነዚህ ዓይነት ንዴትና ሰዎች መራቅና መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ “ከቊጡ ሰው ጋራ ባልጀራ
አትኹን” (ምሳ ፳፪፥፳፬) “በዝንጉዎች ምክር ያልኼደ፣ በኀጢአተኞች መንገድ ያልቆመ፣
በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ ሰው ምስጉን ነው” (መዝ ፩፥፩)

“ጌታችን ኢየሱስም ዮሐንስ እንደተያዘ በሰማ ጊዜ ወደ ገሊላ አውራጃ ፈቀቅ ብሎ ኼደ”


(ማቴ ፬፥፲፪) መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን እስር
ሲሰማ ከናዝሬት ወደ ቅፍርናሆም የተሰደደው ‘መከራ መመጣባችኹ ጊዜ ሽሹ እንጂ እንዲኹ
ተዘልላችኹ ወደ ፈተና አትግቡ ለማለት አብነት ለመኾን ነው። ወደ መከራ በገቡ ጊዜ
መከራውን በጽናትና በትግሥት አለመቀበል እንጂ ራስን ወደ መከራ አለማስገባት ወይም
ከመከራ መሸሽ ነውር አይደለም’ ይላል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የማቴዎስን ወንጌል
በተረጎመበት ድርሳኑ ፣ ድርሳን ፲፬

2. መጸሐፍ ቅዱስን ስለ ቊጣ ክፋት ያስተማረንን ትምህርት


በኅሊናችን ደጋግመን ማሰብ/ማስታወስ

8
 “ሐሰትን ተዉአት፤ ኹላችኹም ከወንድሞቻችኹ ጋራ እውነትን ተነጋገሩ፤ እኛ አንድ አካል
ነንና። ተቈጡ፤ አትበድሉም፤ ፀሓይ ሳይገባ ቁጣችኹንም አብርዱ፤ ለሰይጣንም መንገድ
አትስጡት። … ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ፣ የሚጠቅም
ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችኹ ከቶ አይውጣ። ለቤዛ ቀን የታተማችኹበትን
ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ። መራራትና ንዴት፣ ቊጣንም፣ ጩኸትንም፣
መሳደብም ኹሉ ከክፋት ኹሉ ጋራ ከእናንተ ዘንድ ይወገድ” (ኤፌ ፬፥፳፮-፴፩)፤
 “እናንተ ቊጣንና ንዴትን፣ ክፋትንም፣ ስድብን፣ የሚያሳፍርም ንግግር አስወግዱ” (ቈላ
፫፥፰)፤
 “ሰው ኹሉ ለቊጣ የዘገየ ይኹን” (ያዕ ፩፥፲፱)፤
 “ክቊጣ ራቅ” (መዝ ፴፯፥፰)፤
 “ሕይወትን የሚፈቅድ (የዘለዓለም ሕይወት ሊያይ የሚፈልግ) ሰው ማን ነው? በጎንም
ዘመን ለማየት የሚወድ? አንደበትኽን ከክፉ ከልክል፤ ከንፈሮችኽም ሽንገላን እንዳይናገሩ።
ከክፉ ሽሽ መልካምንም አድርግ፤ ሰላምን ሻ፥ ተከተላትም። የእግዚአብሔር ዐይኖች ወደ
ጻድቃን ዦሮዎቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና።” (መዝ ፴፫፥፲፪-፲፭)፤
 “ቊጡ ሰው አይጸድቅም፤ በቊጣ ጊዜ መከራ ይመጣል” (ሲራ ፩፥፳፩-፳፪)፤
 “በአንደበትኽ አድጦኽ ከምትወድቅ በምድር ላይ አድጦኽ ብትወድቅ ይሻላል” (ሲራክ
፳፥፲፰)፤
 “በውስጡ ብዙ ኃጢአት አለና ከአንደበትኽ የመዘባበት ነገር አይዉጣ፤ አባትኽንና እናትኽን
አትስደብ” (ሲራክ ፳፫፥፲፫)፤
 “በአንድበት የማይስት ማንም ቢኖር እርሱ ሥጋውን ኹሉ ደግሞ ሊገታ የሚችል ፍጹም
ሰው ነው። እነሆ፥ ይታዘዙን ዘንድ በፈረሶች በአፋቸው ልጓም እናገባለን፤ አካላቸውንም
ኹሉ ኣንመራለን። እነሆ መርከቦች ደግሞ አካላቸው ይኽን ያኽል ታላቅ ሲኾን በነፋስ
ኀይል ይነዳሉ፤ ይመላለሳሉም፤ ሰውም ይኽን ያኽል ታላሽ በኾነ መቅሰፊያ ይመልሳቸዋል፤
ወደ ወደደው ወደብም ያደርሳቸዋል። እንዲኹ ምላስም ትንሽ አካል ናት፤ ታላላቅ ነገርንም
ታመጣለች፤ እነሆ፥ እጅግ ትንሽ የኾነች እሳትም ይኽን የሚያኽል ጫካ ታቃጥላለች።
ምላስም እሳት ናት፤ እነሆ፥ ትንሽ ምላስ በሰውነታችን ውስጥ ዐመፅ የተመላበት ዓለም
ናት፤ ሥጋችንን ትበለዋለች፤ ውስጣዊ ሰውነታችንንም ትጠብሰዋለች፤ ከገሃምም ይልቅ
9
ታቃጥላለች። የአራዊትና የወፎች፥ የተቀሳቃሾች በባሕር ያለ የፍጥረት ወገን ኹሉ ለሰው
ይገዛል፤ ተአዝዞታልም። የሰው ምላስ ግን መግዛት የሚቻለው የለም፤ ክፉ ናት፤ ዐቅምም
የላትም፤ የሚገድል መርዝንም የተመላች ናት። በእርሷ እግዚአብሔር አብን
እናመሰግንበታለን፤ በእርሷም በአርአያ እግዚአብሔር የተፈጠረው ሰውን እንረግመዋለን።
ከአንድ አፍ በረከትና መርገም ይወጣሉ፤ ወንድሞቻችን ሆይ እንዲኽ አይኹን። ምንጭስ
ከአንድ አፍ የሚጣፍጥና የሚመርን ውኃ ያመነጫልን? ወንድሞቻችን ሆይ በለስ ዘይትን፥
ወይስ ወይን በለስን ሊያፈራ ይችላልን? እንዲኹም መራራ ውኃ ጣፋጭ ውኃ አይኾንም፤
ጣፋጭ ውኃም መራራ አይኾንም።” (ያዕ ፫፥፪-፲፪)

የሚሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ኃይለ ቃሎችን በኅሊናችን ደጋግመን ማሰብ ቊጣን ለሚያነሣሱ
ሐሳቦችና ነገሮች በር እንዳንከፍት ይረዱናል።

3. ወንድምን መውደድና ይቅር ማለትን መለማመድ


“ጠላቶቻችኹን ውደዱ፤ የሚረግሟችኹንም መርቁ፤ ለሚጠሏችኹም መልካም አድርጉ፤
ለሚሰድቧችኹና ለሚያሳድዷችኹ ጸልዩ። በሰማይ ላለው አባታችኹ ልጆች ትኾኑ ዘንድ እርሱ
ለክፉዎችና ለደጎች ፀሓይን ያወጣልና፤ ለጻድቃንና ለኃጥአንም ዝናብን ያዘንባልና።
የሚወዷችኹንማ ብትወዱ ዋጋችኹ ምንድን ነው? እንደዚኽማ ቀራጮችስ ያደርጉ የለምን?
ወንሞቻችኹን ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችኹ? አሕዛብስ ይኽንኑ ያደረጉ
የለምን? እንግዲኽ ሰማያዊ አባታችኹ ፍጹም እንደኾነ እናንተም ፍጹማን ኹኑ” (ማቴ
፭፥፵፬-፵፰)፤ “[በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ!] በደላችንን ይቅር በለን፤ እኛም
የበደሉንን ይቅር እንደምንል፤” (ማቴ ፮፥፲፪)፤ “ሰዎችች ሊያደርጉላችኹ የምትወዱትን ኹሉ
እናንተም እንዲኹ አድርጉላቸው” (ማቴ ፯፥፲፪)፤ “ለራስኽ የምትጠላውን ለማንም
አታድርግ” (ጦቢ ፬፥፲፭)፤ “ባልጀሮቻችኹን ታገሡአቸው፤ እርስ በርሳችኹም ይቅር ተባባሉ፤
ባልጀሮቻችኹን የነቀፋችኹበትን ሥራ ተዉ፤ ክርስቶስ ይቅር እንዳላችኹ እናናተም ኣንዲኹ
አድርጉ። ከዚኹም ጋራ ዘወትር ተፋቀሩ፤ የመጨረሻው ማሰሪያ እርሱ ነውና ” (ቈላ ፫፥፲፫-
፲፬)፤ “እያንዳዳችኹ ከባልጀሮቻችኹ ጋራ እውነትን ተነጋገሩ፤ በበር አደባባያችኹም
የእውነትንና የሰላምን ፍርድ ፍረዱ፤ ኹላችኹም በባልጀሮቻችኹ ላይ በልባችኹ ክፉ ነገር

10
አታስቡ፤ የሐሰትንም መሐላ አትውደዱ፤ ይኽን ነገር እጠላለኹና (ዘካ ፰፥፲፮-፲፯)፤ “በብርሃን
አለኹ የሚል ወንድሙንም የሚጠላ እስከ አሁን በጨለማ አለ፤ ወንድሙን የሚወድ በብርሃን
ይኖራል፤ ማሰናከያም የለበትም። ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ ይመላለሳል፤
የሚኼድበትንም አያውቅም፤ ጨለማው [ጥላቻው] ዐይኑን አሳውሮታልና” (፩ዮሐ ፪፥፱-
፲፩፣)፤ “ወንድሙን የማይወድ ኹሉ ከእግዚአብሔር አይደለም። … ወንድሞን የማይወድ
በሞት ይኖራል። ወንድሞን የሚጠላ ነፍሰ ገዳይ ነው። … ማንም እግዚ አብሔርን እወደዋለኹ
እያለ ወንድሞን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚ አብሔርን
ሊወደው እንዴት ይችላል?። እግዚአብሔርን የሚወድ ወንድሙንም ደግሞ እንዲወድ ይችይ
ትእዛዝ ከርሱ [ከእግዚአብሔር] ናት” (፩ዮሐ ፫፥፲-፲፭፣ ፬፥፳-፳፩) በማለት መጽሐፍ ቅዱስ
ወንድምን መውደድ ማለት ምን ማለት እንደኾነ፣ ከእግዚአብሔር የሚያሰጠውን ጸጋ፤
በአንጻሩ ደግሞ ተግባሩን ሳይኾን አድራጊውን ወንድምን መጥላት ከእግዚአብሔር
እንደሚለየን፣ በዓይነ ሥጋችን የምናየውን ወንድማችንን ሳንወድ በዓይነ ልቦችን የምናየውን
እግዚአብሔርን እንወደዋለን ማለት እንደማይገባን ይነግረናል። ስለኾነም በከንቱ መቈጣት
ወንድምን የመጥላት ምልክት ስለኾነ መሠረቱን (የቊጣ መሠረት - ጥላቻን) በፍቅር
ልንተካው ያስፈልጋል።

4. የእግዝአብሔርን ፍቅር ገንዘብ ማድረግ


“አምላክኽን እግዚ አብሔርን በፍጹም ልብኽ፣ በፍጹምም ነፍስኽ፣ በፍጹምም ኃይልኽ ወደድ”
የሚለው ትዕዛዝ የመለገለጸው ትዕዛዙን በጠበቅ ነው (ዘዳ ፮፥፭)። “ከወደዳችኹኝስ ትእዛዜን
ጠብቁ” (ዮሐ ፲፬፥፲፭) እንዲል። የጌታችንን ትዕዛዝ መጠበቅ የመታዘዝ ነጸብራቅ ሳይኾን
ለእግዚአብሔር እና ለጥሩነት ካለን እውነተኛ ፍቅር የሚመነጭ ውጤት ነው። እግዚአብሔር
ከእኛ የሚፈልገው ፍሬ የሚያፈራ መታዘዝን ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ያለ እውነተኛ
ግንኙነት እግዚአብሔርን እንደምንወደውና እንደማንወደው ተለይቶ የሚታወቅበት ነው።
በእግዚአብሔር ላይ ያለን ፍቅር የጸና ከኾነ ምንም ዓይነት ኹኔታዎች፣ ችግሮች ወይም
መከራዎች ቢገጥሙንም ትዕዛዛቱን አንሽርም። ትዕዛዛቱን የምጠብቀው ለርሱ ካለን ንጹኽ
መሻት በመነሣት መኾኑን አለበት።

11
ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር የጸና ሲኾን የእግዚአብሔር ህልውና ኹሌም በፊታችን እናዳለን፤
የምንሠራውንም ማናቸውንም ነገር መልካምም ይኹን መጥፉ እንደሚያየን፤ በምንኼድበት
ኹሉ በመንገዳችን አብሮ እንዳለን፣ ዓይኖቹ ዘወትር እኛን እንደሚመለከቱን ይሰማናል። በፊቱ
እንድቆምን፣ ኹሌም እንደምንመለከተው ይረዳናል። ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር የጸና
ሲኾንሥራችንን ከእግዚአብሔር አንለይም፤ በምንሠራው ሥራ ኹሉ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር
መኾኑን እርግጠኛ እንኾናለን፤ ሥራንንም በእግዚአብሔር ስም እንከውናለን። ፩ነገ ፲፯፥፩፣
መዝ ፲፭፥፰።

ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር ልባዊ፣ እውነተኛና ከልብ የመነጨ ከኾነ ትዕዛዙን የምንጠብቀው
ባንጠብቀው የሚመጣብንን ቅጣት አይኾንም። መልካምነት ከመውደድ የተነሣ ይኾናል እንጂ።
ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር ጽኑ ኾነ ማለት ዲያብሎስ እኛን ከመዋጋት ይከለከለዋል ማለት
አይደለም። ስለዚኽ በጽናት ይጠበቅብናል ማለት ነው።

5. ቊጣ የሚያስከትለውን ጉዳት አለመዘንጋት - ሲዖልን መፍራት


ቊጣ ኃጢአት መኾኑን መገንዘብ፤ የኃጢአትም ደመወዟም ሞት (ከእግዚአብሔር መንግሥት
መለየት) መኾኑን ማወቅ ማስተዋል ከቊጣ ድርጊት እድንታቀብ ይረዳናል (ሮሜ ፮፥፳-፳፫፤)።
“[እግዚአብሔርን] የማይፈሩ፣ የማያምኑ ፥ የርኩሳንም [ስንቊጣ አንደበታችን እያረከስን ልብ
ይሏል]፣ የነፍስ ገዳዮችም፣ የሴሰኛዎችም፣ የአስማተኞችም፣ ጣዖትንም የሚያመልኩ፣
የሐሰተኞችም ኹሉ ዕድላቸው በዲን እና በእሳት በሚቃጠል በባሕር ነው፤ ይኸውም ኹለተኛ
ሞት ነው” (ራዕ ፳፩፥፰)።

“በከንቱ ወንድሙን የሚቈጣ የገሃነም ፍርድ ይገባዋል”(ማቴ ፭፥፳፪)፤ “ሰዎች ስለሚናገሩት


ከንቱ ነገር ኹሉ በፍርድ ቀን ስለ እርሱ መልስ ይሰጡበታል። “ከአነጋገርኽ የተነሣ ትጸድቃለኽ፤
ከአነጋገርኽም የተነሣ ይፈረድብኸል” (ማቴ ፲፪፥፴፯)፤ “የሚቊጣ፣ የሚሳደብ
የእግዚአብሔርን መንግሥት አያያትም” (ገላ ፭፥፲፱-፳፪፤ ፩ቆሮ ፮፥፱-፲፤ ኤፌ ፭፥፫-፭)
በማለት ቊጣ የሚያመጣብንን ፍዳና መከራ ይነግረናል። ይኽ ክፉ ፍርድ - ከመንግሥተ
እግዚአብሔር መለየት - ነገ ይሻሻላል የማንለው የዘለዓለም ስቃይ ያለበት የሚያስፈራ ፍርድ
ነው።

12
ስለዚኽ ቊጣን መውደድ የሚያመጣውን ክፉ ነገር - ሲዖልን ካወቅንና ከፈራን ቊጣን
እንድንርቅ፣ እና እዳንለማመድ ያደርገናል። ማለትም ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር ከመጨመር
በተጨማሪ ቊጣን ለመራቅ ሲዖልን መፍራት ሌላው መድኅኒት ነው። ሲዖልን መፍራት ክፉ
ምኞታችንን ማራቅ ሳይኾን በጎ ምግባራትም እጀግ ፈጥነው ወደ እኛ እንዲመጡ ያደርጋል።
ፍርሐት ባለበት ቅንአት፣ ፍቅረ ነዋይ፣ ስግግብነት፣ ቊጣ የለም፤ በምትኩ ምጽዋት፣ ጸሎት፣
ትኩስ ዕንባ፣ ራስን መውቀስ አለ እንጂ።

6. ጸሎት
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “መጋደላችን ከሥጋና ከደም ጋር አይደለምና፤ ከአለቆችና
ከሥልጣናት ጋራ፣ ከዚኽም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር፣ በሰማያዊም ሥፍራ ካለ ከክፋት
መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር እንጂ። ስለዚኽ በክፉ ቀን ለመቃወም ኹሉንም ፈጽማችኹ
ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ጋሻ ጦር ኹሉ አንሡ” (ኤፌ ፮፥፲፪-፲፫) በማለት
መንፈሳዊውን ውጊያ በመንፈሳዊ መሣሪያ እንጂ በሌላ ማሸነፍ እንደማይቻል ያስረዳናል።
የእግዚአብሔር የጦር ዕቃ/ጋሻ የተባሉት ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደት እና የመሳሰሉት የትሩፋት ሥራ
ናቸው። እነዚኽን ትሩፋት ለመሥራት የመጀመሪያው ተግባር ደግሞ በፍጹም እምነትና
በመልካም ምግባር ጸንቶ በእግዚአብሔር መደገፍ ነው።

መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ “ወደ ፈተና እንድትገቡ ትጉና ጸልዩ” (ሉቃ፳፪፥፵፮)፣
ሐዋርያው ያዕቆብም “ከእናንተ መከራ የሚቀበል ማንም ቢኖር ይጸልይ” (ያዕ ፭፥፲፫) በማለት
እንዳስተማሩን ከማንኛውም ፈተና ለመዳን ጸሎት አስፈላጊ መሣሪያ ነው።

ስለኾነም ለክርስቲያኖች የችግር ኹሉ መፍትሔ የሚገኘው እግዚአብሔርን በጸሎት በመጠየቅ


ስለኾነ፥ ቊጣን ከእኛ ነቅሎ በምትኩ ፍቅርንና ትዕግስትን፣ ይቅር መባባልን ይተክልልን ዘንድ
እግዚአብሔርን “አቤቱ ወደ አንተ ጮኽኹ፤ ስማኝ። ወደ አንተ ስጮኽም የልመናዬን ቃል
አድምጥ፤ ጸሎቴን በፊትኽ እንደ ዕጣን ተቀበልልኝ፥ እጅ መንሳቴንም እንደ ሠርክ መሥዋዕት
ትኹን። [አንደበት ኹለ ለአንተ ይገዛልና] አቤቱ ለአፌ ጠባቂ አኑር፤ የከንፈሮቼንም መዝጊያ
ጠብቅ፤ ልቤን ወደ ክፉ ነገር አትመልሰው፤ ዐመፃን ከሚያደርጉ ሰዎች ጋራ ለኀጢአት ምክንያት
እንዳልሰጥ ከምርጦቻቸውም ጋራ አልተባበር”፤ “አቤቱ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ የቀናውን

13
መንፈስ በውስጤ ዐድስ” በማለት በጸሎት መጠየቅ ያስፈልጋል (መዝ ፻፵፥፩-፬፤ ፶፥፲፣ ኤፌ
፬፥፴፩፣ ቈላ ፫፥፲፪-፲፫)። ይኽም ማለት ቊጣን አስወግደን ትዕግሥተኛ ለመኾን [ትግሥትን
ገንዘብ ለማድረግ] የእኛን ፈቃድ፣ ጥረት፣ ቅንነት ይጠይቃል ማለት ነው። ቊጣን ከእኛ
ለማራቅ የእኛን ጥረት ካልጨመርንበት ፥ የእርሱን ክፉነት ማወቅ ብቻውን ምንም ጥቅም
የለውም። ለዚኽ ሐሳብ ማጠናከሪያ ይኾነን ዘንድ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን ሐሳብ
እንዋሳለን። “[ቊጣ ክፉ ግብር መኾኑን] ፣ ትዕግሥት ደግሞ በጎ ነገር መኾኑን ኹላችንም ያለ
ምንም ችግር እናውቃለን፤ ዐዋቂነት ተፈጥሯዊ ነውና። ትግሥተኛ ለመኾን ግን ያለምንም
ችግር፣ ይኽን የማድረግ ፍላጎታችን ሳይገደብና ብዙ ጥረትን ሳናደርግ ማከናወን አይቻለንም፤
ይኽ ፈቃደኛ ልብንና ቅንነትን የሚፈልግ እንጂ ልክ እንደ ዐዋቂነት ተፈጥሯዊ ኾኖ የተሰጠን
አይደለም” ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት ፲፫፥፱።

ራሳችንን እንደደካማ ከመቊጠር ይልቅ እግዚአብሔር አምላክ በአምሳሉና በአርአያው


የፈጠረን ክቡር ፍጡር መኾናችንን ተረድተን ለዘለዓለማዊ ሕይወት በጸሎት፣ በጾም፣ በስግደት
እየተጋን በሃይማኖት ጸንተን ልንኖር ይገባል፡፡

ይኽን ጽሑፍ በጠቢቡ ቃል እንደምድመው፤ ቃሉም እንዲኽ ይላል፥ “በገና እና ከመሰንቆ


ሰውነትን ደስ ያሰኛታል፤ ከኹለቱም ይልቁንም ልዝብ አንደበት ደስ ያሰኛል” ሲራክ ፵፥፳

የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር አብ ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስ ኅብረት


ከኹላችኹን ጋራ ይኹን፤ አሜን። ፪ቆሮ ፲፫፥፲፬

ዋቤ መጽሐፍት

1. መጽሐፍ ቅዱስ 2000 ዓ.ም ዕትምና (እና በስስ ቅጅ (Geez Amharic Bible Pro Version
6.1.1, በብራና አፕስ )
2. ትርጋሜ ኤፌሶን በቅዱስ ዮሐንስ አፈወቅር (ተርጓሜ ኃይለ ኢየሱስ መርሻ፣ 2013
ዓ.ም)
3. ትርጓሜ ማቴዎስ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወቅር (ተርጓሜ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ፣ 2011
ዓ.ም)

14
4. ትምህርት ምክንያተ በእንተ ሐውልታት በቅዱስ ዮሐንስ አፈወቅር (ተርጓሜ ገብረ
እግዚአብሔር ኪደ፣ 2008 ዓ.ም)
5. የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት (የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፣ 2008 ዓ.ም)
6. የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት ትርጓሜ /ማብራሪያ ክፍል ኹለት (ከኤፌሶን እስከ
ዕብራውያን) መ/ር ስቡሕ አዳምጤ፣ 2013 ዓ.ም
7. ሕግጋተ ወንጌል፣ ብዙነኽ ሺበሺ እና ደምሴ ተፈራ ፣ 2010 ዓ.ም
8. https://eotcmk.org/a ‹‹ተቈጡ፤ አትበድሉም›› (ኤፌ. ፬፥፳፮) ፣ መጋቢት ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም
9. ነፍሴ የወደደችውን አያችኹትን? በአቡነ ሲኖዳ ሣልሳዊ (ትርጉም ዘኤልያስ ወልደ
ሚካኤል፣ 2014 ዓ.ም)

ክፍል ኹለት መሐላ

ከቶ አትማሉ ማቴ ፭፥፴፬

15
16

You might also like