Professional Documents
Culture Documents
5
5
ማውጫ
መግቢያ ፡፡
ያዕቆብ በማታልለ ከወንድሙ በኩርነትን ዘርፎ ወስዶ ነበር ፡፡ ኤሳውም ተቆጥቶ ሊገድለው ፈለገ፡፡ በዚህ
ምክንያት ያዕቆብ ከቤት ኮበለለ፡፡ የኸው ኃጢያቱም ከእግዚአብሔር እንዳይለየው ፈርቶ ነበር፡፡ በሌሊቱ
ሊያርፍ ተጋደመ፤ ሕልምም አየ እነሆ አንድ መሰላል በምድር ተተክሎ ጫፉ ሰማይ ደርሶ፡፡ እነሆ
የእግዚአብሔር መላእክትም በርሱ ይወጡና ይወርዱ ነበር ፡፡ ይህም የምድና የሰማይ መጋጠም ገለጠለት ፡፡
ለዚሁ መንገደኛ በዚያ በመሰላሉ ላይ በቆመው በኩል የማፅናናትና የተስፋ ቃል ተነገረለት ፡፡
በሰማይ ያለው አባታችን የሕይወት፤ የጥበብ፤ የደስታም ምንጭ ነው፡፡ እኒህን የሚያምሩና የሚገርሙ
ፍጥረቶች ተመልከት ፡፡ ስለሚገርመው የሚስማማ ነገራቸው ሰው ለሚሻው ነገርና ደስ ለሚያሰኘውም
ጥቅም መሆኑን አስብ፡፡ ደግሞም ሕይወት ላለው ፍጥረት ሁሉ እንጂ ለሰው ብቻ አይደለም፡፡ ምድርን ደስ
የሚያሰኝ የፀሐይ ብርሃንና የሚያለመልም ዝናብም ኮረፍቶችም፤ ባሕሮችም፤ ሜዳዎችም ሁሉ፤ ሁሉ
የፈጣሪን ፍቅር ይነግሩናል፡፡ ፍጥረቱ ሁሉ በየለቱ የሚሻውን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው፡፡ በሚያምረው
በባለ መዝሙሩ በዳዊት ቃል ይላል፤ የሁሉ ዓይን አንተን ደጅ ይፀናል፡፡
አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ፡፡
አንተ እጅህን ትዘረጋለህ፡፡
ሕያዋንንም ሁሉ እንደ በጎ ፈቃድህ ታጸግባለህ፡፡ (መዝ ፩፵፮፣፲፭ -፲፮ ፡፡) እግዚአብሔር ሰውን ፈጽሞ ቅዱስና
ዕድላምም አደረገው፡፡ የተዋበው ምድርም ከእግዚአብሔር እጅ እንደመጣ፤ የመበላሸት ነውር ወይም
የርግማን ጽላ አልነበረበትም፡፡ ወዮታንና ሞትን ያመጣ የእግዚአብሔርን የፍቅር ሕግ መተላለፍ ነው፡፡
ገናም ኃጢአት ባመጣው መከራ ስንሰቃይ ሳለን በዚያ መሀከል የእግዚአብሔር ፍቅር ተገለጠ፡፡ ከሰው ክፋት
የተነሣ እግዚአብሔር ምድርን እንደረገመ ተጽፎአል ፡፡ (ዘፍ ፫፡፲፯)፡፡ በእግዚአብሔር አሳብ ሠራተኛው ሰው
እንደሚሻው ዕድል ኃጢአት ካመጣው መፍረስና ከማዕረግ መዋረድ ርሱን ከፍ ለማድረግ ኑሮውን
የጥረትና የአሳብ ኑሮ የሚያደርጉና እሾሆችና አሜከላዎች ጭንቀትና ፈተናም ስለእርሱ ጥቅም ተደረጉ ፡፡
ዓለም ምንም ቢወድቅ ሁለንተናውን ኃዘንና ጥፋት አይደለም፡፡ በተፈጠረው ፍጥረት በራሱ ላይ ያለኝታና
የመጽናናት መልእክቶች አሉ፡፡ በአሜከላዎች ላይ አበቦች አሉ፡፡ እሾሆችም በጽጌረዳ ተሸፍነዋል፡፡ በሚፈነዳው
ቆባ ሁሉ ላይ በተጎነጎነው ቡቃያ ሣር ሁሉ ላይ እግዚአብሔር ፍቅር ነው የሚል ተጽፎአል፡፡ የተወደዱ ዖፎች
ያማረ ድምጻቸውን ደስ በሚያሰኝ ዜማቸውን እያዜሙ፤ ነጭ የሆኑ አበቦችም በለስላሰነታቸውና
በፍጹምነታቸው ነፋሱን እያሸተቱ ረጃጅሞች የዱር ዛፎችም ሕይወት ካለው ብዙ ከለመለመ ቅጠላቸው
ጋር እሊህ ሁሉ ርኅሩኅ ለሆነ አምላክ ልጆቹን ደስ ለማሰኘት የአባትነት አሳብ ማሰቡን ይመሰክራሉ፡፡
የእግዚአብሔር ቃል የእግዚአብሔርን ባሕርይ ይገልጣል፡፡ እርሱ ራሱ የማያልፈውን ፍቅሩንና ርኅራኄውን
ገልጦአል፡፡ ሙሴ ክብርህን አሳየኝ ብሎ በለመነው ጊዜ ጌታ መለሰለት አለውም፤ እኔ ቸርነቴን ሁሉ በፊትህ
አሳልፋለሁ፡፡ ክብሩ ይህ ነው ፡፡ (ዘፀ ፴፫፡ ፲፰፡ ፲፱ ) ጌታ በሙሴ ፊት አለፈ ጮኸም እንዲህ ሲል፤
እግዚአብሔር እግዚአብሔር መሐሪ ጸጋ ያለው ለቁጣም የዘገየ፡፡ ባለታላቅ ቸርነትና እውነት እስከ ሽሕም
ትውልድ ድረስ ጸጋን የሚጠብቅ ፡፡ ጠማምነትንም መተላለፍንም ኃጢአትንም ይቅር የሚል ርኅሩኅ
አምላክ ነው፡፡ (ዘፀ ፴፬፡ ፮፡ ፯ ) ለቁጣ የዘገየ ቸርነቱም የበዛ ነው፡፡ (ዮና ፬፡፪ ) ምሕረት ይወዳልና (ሚክያስ
፯፡፲፰)፡፡ እግዚአብሔር በሰማይና በምድር ቁጥር በሌላው ምልክት ልባችነን ወደርሱ አሥሮታል፡፡
በፍጥረቶች ነገር በጠለቀና በለሰለሰ ምድራዊ ማሠሪያ፤ እርሱ ራሱን ሊገልጽልን ማሰቡን የሰው ልብ
ያውቀው ዘንድ እንዲችል ምንም እሊህ ሁሉ ምስክሮች ቢሰጡነ፤ እሊህም ገና ፍቅሩን ጥቂት ብቻ ያሳዩናል፡፡
እግዚአብሔር ይቅር የማይል ጨካኝ መስሎአቸው እንዲሁ ወደርሱ በፍርሃት ዓይን እንዲያዩ፤ ያ የበጎ ነገር
ጠላት የሰዎችን ዓይነ ልቡና ዕውር አደረገ ፡፡ ሰይጣን ለእግዚአብሔር የሻከረ ፅኑ ፍርድ መፍረድ ዋና ገንዘቡ
እንደሆነ እንደ ጨካኝ ፈራጅም እንደ ፅኑም አበዳሪ ይመስላቸው ዘንድ ሰዎችን መራ፡፡ የሰዎችም ስህተትና
ያልሆነውንም ሥራ መሥራት ለይቶ ለማወቅ እግዚአብሔር በላያቸው ፍርድ ያመጣባቸው ዘንድ ሰይጣን
ፈጣሪን በምቀኝነት ዓይን እንደሚጠብቅ አስመስለው ፡፡ የሱስ በሰዎች መሀከል ሊኖር የመጣ
ያማያልቀውን የእግዚአብሔርን ፍቅር ለዓለሙ በመግለጥ ይህን የጨለማ ጥላ ለማስወገድ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ አብን ሊገልጽ ከሰማይ መጣ፡፡ «ባባቱ እቅፍ ያለው አንዱ ልጁ ገለጠው እንጅ
በማናቸውም ጊዜ እግዚአብሔርን ያየው ከቶ የለም፡፡» (ዮሐ ፩፡፲፰) «ልጅ ይገለጽለት ዘንድ ከሚሻው በቀር
አንድ ስንኳ አብን አያውቅም፡፡» (ማቲ ፲፩ ፡ ፳፯) ፡፡ አንዱ ከደቀ መዛምርቱ «አብን አሳየን» ብሎ በጠየቀው
ጊዜ የሱስ መለሰ አለውም «ፊልጶስ እኔ ከላንት ጋራ ይህን ያህል ዘመን ስኖር አታውቀኝምን እኔን ያየ አብን
ፈጽሞ አየ ፡፡ እንዴትስ አብን አሳየን ትላለህ» (ዮሐ ፲፬፡ ፰ ፡ ፱) ፡፡ የሱስ የምድራዊ መልዕክቱ ምን እንደሆነ
ሲያስታውቅ አለ «ለድኆች የምስራች እነግር ዘንድ ስለ ቀባኝ የእግዚአብሔር መንፍስ በላዬ ነው፡፡ ልባቸው
የተሰበረውን እፈውስ ዘንድ የተማረኩትንም ልመልስ፤ ዕውሮችም እንዲያዩ የተገፉትም እንዲለቀቁ
እሰብክላቸው ዘንድ ላከኝ፡፡» (ሉቃ ፬ ፡ ፲፰፤) ሥራው ይህ ነበረ፡፡ መልካም እየሠራ፤ ሠይጣን
የተጫናቸውንም እየፈወሰ ይዞር ነበር፡፡ ለመንደሩ ሁሉ በማናቸውም ቤት የበሽታ ልቅሶ፤ ጩኸት
ያልነበረበት አልነበረምና፤ እርሱ ወደነዚያ ሒዶ በሽተኞቻቸውን ሁሉ ፈወሰ፡፡ ሥራውንም ለመለኮታዊ
ቅባቱ መሰከረ፡፡ በምድርም ሳለ በሠራው ሥራ ሁሉ ፍቅርና ምሕረት ቸርነትም ተገልጠው ነበሩ፡፡ ኅዘንን
በርኅራኄ ለመካፈል ልቡ ወደ ሰው ልጆች ዘነበለ፡፡ ሰው የሚሻውን ለማወቅ የሰውን ባሕርይ ገንዘብ አደረገ፡፡
በጣም የደኸዩትና የተዋረዱት ይቀርቡት ዘንድ አልፈሩም ፡፡ ከቶውንም ታናናሾች ልጆች በርሱ ፍቅር
ተስበው መጡ፡፡ ወደ ጉልበቱም ተቆናጠው ሊወጡ ወደዱ፡፡ ከፍቅር የተነሣ ቸር ወደ ሆነ አሳቢ ግምባርም
ተመለከቱ ፡፡ የሱስ አንድ የውነት ቃል ደብቆ አላስቀረም፤ ግን ሁልጊዜ በፍቅር ይናገረው ነበር ፡፡ ከሰዎች ጋር
በንግግሩ የሚበልጠውን ሥራና አሳብ የሞላበትን ጥንቃቄ አስለመደ ፡፡ እርሱ ግብሩ ምንም የሻከረ
አልነበረም፤ በሚያሻውም ነገር እንዲያው ያለ አሳብ የጭከና ቃል አልተናገረም ፡፡ እርሱ ለምታስብ ነፍስ
የማይገባ የሚዋጋ ነገር ምንም አልሰጠም ፡፡ እርሱ ለምታስብ ነፍስ የማይገባ የሚዋጋ ነገር ምንመ
አልሰጠም ፡፡ እርሱ በሰው ድካም ላይ የማይገባ ፍርድ አልፈረደም ፡፡ እርሱ እውነቱን ተናገረ፤ ግን ሁልጊዜ
በፍቅር ነበር፡፡ ግን ገና ጥፋት ሳይመጣ ይመክረው የነበረውን ምክሩን ሲናገር ሳለ እንቦቹ ካይኖቹ ይፈሱ
ነበር ፡፡ ስለ ኢየሩሳሌም ስለሚወዳቱ ከተማ ልትቀበለው እምቢ ስላለችው አለቀሰ፡፡ እርሱን መንገዱን፤
እውነቱን ሕይወቱን፤ አዳኙን፤ ንቀውት ነበር ፡፡ ግን እርሱ በርኅራኄና በቸርነት አያቸው፡፡ ኑሮው ራሱን
የመካድ ኑሮ ለሌሎችም አሳብ የመላበት ጥንቃቄ ነበረ፡፡ ነፍስ ሁሉ በዓይኑ ዘንድ የከበረ ነበረ፡፡ እርሱ ሁል
ጊዜ በመለኮትነት መዓርግ ሳለ ለእግዚአብሔር ቤተሰብ ርኅሩኅ በሆነ ማክበር ራሱን አዋረደ፡፡ እርሱ ለማዳን
ተልኮ በመምጣቱ የሰው ሁሉ ነፍስ የወደቀ መሆኑን አየ፡፡ በኑሮው እንደሚታይ የክርስቶስ ባሕርይ እንዲህ
ነው፡፡ የእግዚአብሔር ባሕርይ ይህ ነው ፡፡ ከአብ ልብ ወጥቶ ወደሰዎች ልጆች የሚፈስ በክርስቶስ
የተገለጠው የመለኮታዊ ርኅራኄ ፈሳሽ ይህ ነው፡፡ የሱስ በሥጋ የተገለጸ ቸር ርኅሩኅ አዳኝ አምላክ ነበር ፡፡ (፩
ጢሞ ፫ ፡ ፲፮) ፡፡ የሱስ በዚህ ዓለም የኖረና መከራ የተቀበለ፤ የሞተም ሊያድነን ነው ፡፡ እኛ የዘለዓለም
ደስታን ተካፋዮች እንሆን ዘንድ እርሱ የኃዘን ሰው ሆነ ፡፡ እግዚአብሔር ጸጋና እውነት የመላበትን የተወደደደ
ልጁን፤ ክብሩ ሊነገር ከማይቻል ዓለም በኃጢአት ወደ ተደመሰሰና ወደተበላሸ፤ በሞት ጥላና በርግማንም
ወደ ጨለመው ዓለም ይመጣ ዘንድ ፈቀደለት፡፡ የፍቅር እቅፉን (ሕፅኑን) የመላእክትንም ስግደት ለመተው
ኃፍረትንም ለመታገሥ፤ ለመሰደብ፤ ውርደትንም፤ መጠላትንም፤ ሞትንም ለመታገሥ ፈቀደለት፡፡
የደህንነታችን ተግሣፅ በርሱ ላይ ሆነ፡፡ በርሱ ቁስልም እኛ ተፈወስነ፡፡ (ኢሳ ፶፫ ፡ ፭)፡፡ በጌቴሴማኒ ዱር
በመስቀል ላይም እዩት፡፡ ነውር የሌለበት የእግዚአብሔር ልጅ የኃጢአትን ሸክም በራሱ ላይ ተሸከመ፡፡
ኃጢአት በሰውና በእግዚአብሔር መሀከል ያደረገው ክፉ መለያየት ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ለነበረው
በነፍሱ ታወቀው፡፡ ይህም በከንፈሮቹ አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ ብሎ የጣረ ሞትን ጩኸት ጮኸ
(ማቴ ፳፯ ፡ ፵፮) የኃጢአት የሚያስፈራ ሸክሙ መታወቁ፤ ነፍስን ከእግዚአብሔር መለየቱ ነበረ፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ ልብ የሰበረ ይህ ነው፡፡ ግን ይህ ትልቅ መሥዋዕት በእግዚአብሔር ልብ ሰውን መውደድ
እንዲፈጥር አልተደረገም፤ ወይም ያድን ዘንድ እንዲወለድ ሊያደርገው አይደለም፡፡ «እግዚአብሔር አንድ
ልጁን እስኪለውጥ ድረስ ዓለሙን ወድዋልና» (ዮሐ ፫ ፡ ፲፮) አብ ስለትልቁ አስታራቂ አልወደደንም፤ ግን ስለ
ወደደነ ማስታረቂያውን አዘጋጀ ፡፡ በዚህ በወደቀ ዓለም ላይ የማያልቅ ፍቅሩን ለማፍሰስ በቻለበት በኩል
መሀከለኛ ሁኖ ያስታረቀ ክርስቶስ ነው፤ «እግዚአብሔር ዓለሙን ከራሱ ጋራ ባስታረቀ ጊዜ በክርስቶስ አድሮ
ነበር፡፡» (፪ ቆሮ ፭ ፡ ፲፱) ፡፡ ለእግዚአብሔር የልጁ መከራ ተሰማው ፡፡ በጌተሴማኒ ፃዕረ ሞት፤ በቀራንዮ ሞት
የማያልቀው የፍቅር ልብ የመዳኛችነን ዋጋ ከፈለ፡፡ የሱስ አለ እኔ «ነፍሴን እሰጣለሁና ዳግመኛም
እወስዳታለሁ ስለዚህ አባቴ ይወደኛል፡፡» (ዮሐ ፲ ፡ ፲፯)) ፡፡ እላንተን ለማዳን ሕይወቴን ስለ ሰጠሁ ከቶውንም
አባቴ እኔን አብልጦ እንደሚወደኝ እላንተን ወደዳችሁ ፡፡ የላንት ቤዛና ዋስ በመሆኔ ራሴንም አሳልፌ
በመስጠቴ የእላንተንም ዕዳ የእላንተንም መተላለፍ በመሸከሜ እኔ ባባቴ ዘንድ የተወደድሁ ነኝ፡፡ በኔ
መሥዋዕትነት እግዚአብሔር የቀና መሆኑ ይገለጻል፡፡ ገናም ደግሞ በየሱስ የሚያምነውን ያጸድቃል ፡፡
መዳናችነን ሊፈጽም የሚችል ከእግዚአብሔር ልጅ በቀር ማንም የለም ፡፡ በአብ እቅፍ (ሕፅን) የነበረው
እርሱ ብቻ ሊገልጸው ችሎአልና፡፡ የእግዚአብሔርን ፍቅር ከፍታውንና ጥልቁን የሚያውቀው፤ እርሱ ብቻ
ሊገልጸው ቻለ፡፡ ስለ ወደቀው ሰው በክርስቶስ ከተደረገው ከማያልቅ መሥዋዕት በቀር፤ ለሰው ፍጥረት
የአብን ፍቅር ሊያስታውቀው የሚችል ሌላ የለም፡፡ እግዚአብሔር አንድ ልጁን እስኪለወጥ ድረስ እንዲሁ
ዓለሙን ወድዋልና ፡፡ ለሞት አሳልፎ የሰጠው ለኒህ ለወደቁ ሕዝብ ኃጢአታቸውን ሊሸከም
መሥዋዕታቸውም ሁኖ ሊሞት ነው እንጂ፤ በሰዎች መሀከል ብቻ ሊኖር አይደለም፡፡ ስለ ሰው ፍቅር
ስለሚሆነው ነገርና ሰው ስለሚሻው ነገር ክርስቶስ ራሱን ከሰው ጋር አስተካከለ ፡፡ እርሱ ከእግዚአብሔር ጋር
አንድ የነበረው፤ ከሰዎች ልጆች ጋር ምንም በማይቆረጥ ማሠሪያ ተቆራኜ ፡፡ የሱስ ወንድሞቼ ብሎ
ሊጠራቸው አላፈረም ፡፡ (ዕብ ፪ ፡ ፲፩ )፡፡ መሥዋዕታችን፤ ጠበቃችን፤ ወንድማችንም እርሱ ነው ፡፡ በአብ
መንበረ መንግሥት ፊት የሰውነታችነን መልክ ወስዶ፤ በዘለዓለሙ ትውልድ ካዳናቸው ወገኖች ጋር የሰው
ልጅ አንድ ሆነ ፡፡ ይህ ሁሉ የሆነ ሰው ከጥፋትና ከኃጢአት ውርደት ከፍ ይል ዘንድ የእግዚአብሔርንም ፍቅር
መልሶ እንዲያሳይና የቅድስና ደስታንም እንዲካፈል ነው፡፡ ስለኛ መዳን የተሰጠው ዋጋ የማያልቀው የሰማዩ
አባታችን መሥዋዕት፤ ልጁን ስለኛ ለሞት አሳልፎ በመስጠቱ፤ በክርስቶስ የምንሆነውን ከፍ ያለ አሳብ
ይሰጠናል ፡፡ መንፈስ ቅዱስ የመላበት ሐዋርያው ዮሐንስ፤ ወደሚጠፉ የሰው ወገን ያለውን የአብ ፍቅር
ከፍታውን፤ ጥልቁን፤ ስፋቱንም ባየ ዚዜ ስግደትና ማክበር መላበት፡፡ የዚህን ፍቅር ትልቅነትና ርኅራኄ
ለማስታወቅ የተስማማ ቃል አጥቶ፤ ዓለሙ እንዲያየው እንዲህ ሲል ጠራ፤ እዩ የእግዚአብሔር ልጆች እንባል
ዘንድ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር ሰጠነ፡፡ (፩ ዮሐ ፫ ፡ ፩)፡፡ ይህ ስፍራ በሰው ዘንድ እንዴት የከበረ ነው፡፡
የሰው ልጆች ትእዛዝን በመተላለፍ ለሰይጣን ተገዦች ሆኑ፡፡ የአዳም ልጆች በሃይማኖት በክርስቶስ
የማስታረቅ መሥዋዕትነት የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ክርስቶስ የሰውን ባሕርይ በመውሰዱ ሰውን
ከፍ አደረገ፡፡ የወደቁ ሰዎች ከክርስቶስ ጋር አንድ በመሆን የእግዚአብሔር ልጆች ለመባል በውነት
ወደሚገባቸው ስፍራ ተቀምጠዋል ፡፡ የሰማያዊ ንጉሥ ልጆች መባል የከበረ ተስፋ፤ እጅግ ለጠለቀው አሳብ
ዋና ነገር፤ እርሱን ለማይወደው ዓለም ምሳሌ የሌለው የእግዚአብሔር ፍቅር እንዲህ ያለው ፍቅር፤ ልክ
የሌለው ነው ፡፡ አሳብ በነፍስ ላይ የሚያስገዛ አሳብንም ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ ማርኮ የሚያወጣ ኃይል
አለው፡፡ የመለኮትን ባሕርይ በመስቀሉ ብርሃን አብዝተን ስንመለከት፤ ከቀና ፍቅር ጋር የተደባለቀውን
የምሕረት ርኅራኄውንና ይቅርታውንም አብዝተን ስናይ ቁጥር የሌለውን የፍቅር ምልክት በጣም አብዝተን
በግልጽ ስናይ እናት ከመንገድ ስለወጣው ልጅዋ ከምታዝነው የሚበልጥ ኀዘን ነው፡፡ እንዲህ ያለው ፍቅርም
ምሳሌ የሌለው የማያልቅ ፍቅር ነው፡፡ የሰው ሁሉ ማሠሪያ ይበጠሳል፡፡
ወዳጆች ወዳጆቻቸውን ይከዳሉ፡፡
የናት ልብም የወለደውን ለማጥባት ይረሳል፡፡
በመጨረሻ ሰማይና ምድር ያልፋሉ፡፡
የአምላክ ፍቅር ግን ፍጥረቱን ሁሉ ያስባል፡፡
ምዕራፍ 2—የኃጢአተኛ ክርስቶስን መፈለግ፡፡
ለሰው በፊት ታላቅ ኃይልና ትክክል ሁኖ የተመዘነ አእምሮ ተሰጥቶት ነበር፡፡ እርሱም ፈጽሞ ደግ ፍጥረት ፤
ከእግዚአብሔር ጋራም ፈጽሞ የተስማማ፤ አሳቡ ሁሉ ንጹሕ፤ አመለካከቱም ቅዱስ ነበረ፡፡ ግን ባለመታዘዙ
ምክንያት ኃይሎቹ ተጣመሙ፡፡ የፍቅርን ስፍራ ብቻ ራስን መውደድ ያዘው፡፡ እንዲሁ ከመተላለፍ የተነሣ
ባሕርዩም የደከመ ሆነ፡፡ የክፉውን ኃይልም ለመቋቋም እርሱው ራሱ አልተቻለውም፡፡ የሰይጣን ምርኮኛ
ሆነ፡፡ እግዚአብሔር በመሀከልም ገብቶ በተለየ ነገር አለያይቶት ባይሆን፤ እንዲሁ ሁኖ ለዘለዓነሙ በኖረ
ነበር፡፡ የፈታኙ አሳብ እግዚአብሔር ሰውን ለመፍጠር ያሰበውን አሳብ ለመቃወም፤ ምድርንም በወዮታና
በጥፋት ለመምላት ነበር፡፡ እግዚአብሔር ሰውን በመፍጠሩ ይህ ክፉ ነገር ከእግዚአብሔር ሥራ እንደወጣ
አስመስሎ ሰይጣን ለሁሉ ባመለከተ ነበር፡፡
ኃጢአቱን የሚሠውር ደኅንነት አያገኝም የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረት ያገኛል፡፡ ምሳሌ ፳፰፡፲፫፡፡
የእግዚአብሔርን ምሕረት የማግኘት መንገድ ለፈለገው ሰው ገር፤ የቀና ሊያተውሉት የማይቸግር ነው፡፡
ይቅርታ ስለማግኘት ብለን የሚያሳዝን ነገር ልናደርግ እግዚአብሔር አይወድልንም፡፡ ነፍሳችነን ለሰማዩ
አምላክ አደራ ለመስጠት፤ ወይም ኃጢአታችነን ለማወገድ ረጅም የሚያደክም የምናኔ መንገድ፤ ወይም
የሚያም ቅጣት ልንቀበል አያሻነም፡፡ ግን ኃጢአቱን የተወና ያስታወቀ ከእግዚአብሔር ይቅርታ ያገኛል፡፡
ሐዋርያው «እንድትፈወሱ ኃጢአታችሁ እርስ በርሳችሁ ተናዘዙ፡፡ አንዱም ላንዱ ይጸልይለት ይላል፡፡» (ያዕ ፭
፡፲፮)፡፡ ኃጢአታችሁን ለእግዚአብሔር ለርሱ ብቻ ይቅር ለሚለው አስታውቁ፡፡ በደላችሁንም እርስ በርሳችሁ
ይቅር ተባባሉ፡፡ ወዳጆቻችሁንም ወይም ጎረቤቶቻችሁን አሳዝናችሁ ቢሆን፤ በደላችሁን ለነዚያ ማታወቅና
ይቅርታ መለመን ይገባችኋል፡፡ እነዚያም ካሣ ሳይፈልጉ እንዲያው ይቅር ሊሉአችሁ ይገባል፡፡ ከዚህ
ቀጥላችሁ የእግዚአብሔርን ይቅርታ ብትሹ ታገኛላችሁ፡፡ ያ ያቆሰላችሁት ወንድማችሁ የእግዚአብሔር
ገንዘብ ስለሆነ፡፡ እርሱንም በመጉዳታችሁ በፈጣሪውና በአዳኙ ላይ ስለበደላችሁ፡፡ ነገሩ ብቻ ባንዱ
እውነተኛ አስታራቂያችን በትልቁ ሊቀ ካህናታችን ተደርጎአል፡፡ «እርሱ በሁሉ እንደኛ የተፈተነ ያለ ኃጢአት
ከመሆኑ በቀር በድካም ከኛ ጋራ የተካከለ፡፡» ዕብ ፱ ፡፲፭፡፡ ከኃጢአት ሁሉ ሊያነጻን የሚችል፡፡ እሊያን
ኃጢአታቸውን በማታወቅ ነፍሳቸውን በእግዚአብሔር ፊት ዝቅ ያላደረጉትን ገና ፈጽሞ ክርስቶስ
አልተቀበላቸውም፡፡ ክፉ ነገርን ጠልተን በውነት በተዋረደች ነፍስና በተሰበረች መንፈስ ኃጢአታችንነ
ካላስታወቅነ፤ የኃጢያትን ይቅርታ ለማገኘት ምንም አላሳብነ፡፡ ወይም አልፈለግነ፡፡ ካልፈለግነም ከቶውንም
የእግዚአብሔርን ሰላም አላገኘንም፡፡ ባለፈው ጊዜ ለኃጢአታችን ይቅርታ አለማግኘታችን፤ ምክንያቱ ስለ
ምን ነው፤ ምክንያቱ ልባነችንን ልናዋርድና ለእውነቱ ቃል ልንታዘዝ እሺ ስላለማለታችን ነው፡፡ ስለዚህ ነገር
የተገለጠ ትምህርት ተሰጥቶናል፡፡ በሰው ሁሉ ፊትም ቢሆን ውይም በሥውር ብቻ በእግዚአብሔር ፊትም
ቢሆን ከልባችን ከገዛ ራሳችን ፈቃድ የተደረገ ሊሆን ይገባዋል፡፡ በነፃነትም ሊነገር ይገባዋል፡፡ ኃጢአተኛውም
የግድ ንስሓ መግባት አይሆንም፡፡ የኃጢአትን ባሕርይ የመጥላት እውነተኛ እውቀት የሌላቸው፤ አሳብ
በሌለው የችኮላ ንግግር የግድ ንስሓ ግባ ሊሉት አይገባም፡፡ ኃጢአትን ማስታወቅ፤ ርኅራኄው
ወደማያልቀው እግዚአብሔር የሚውስደውን መንገድ ለማግኘት በነፍስ ውስጥ ያለውን ጭንቀት አውጥቶ
ማፍሰስ ነው፡፡ ዳዊት በመዝሙሩ፤ «እግዚአብሔር ልባቸው ገር ለሆነ ቅርብ ነው በመንፈሳቸው
የተሰበሩትንም ያድናቸዋል አለ፡፡» (መዝ ፴፬፡፲፰)፡፡ ንስሓ መግባት መጠጠት የተለየውን ኃጢአት
የሚስታውቅ የተለየ ነገር ነው፡፡ ኃጢአትን ለማስታወቅ ልዩ ልዩ መንገድ አለው፡፡ ብቻ በእግዚአብሔር ፊት
ሊነገር የሚገባ ኃጢአት ይኖራል፡፡ እርሱ ኃጢአተኛው እንደ ሠራው ያለ፤ ኃጢአትን በመሥራት ወደተጎዱት
ሰዎች ሂዶ ለያንዳንዳቸው ያነውን ኃጢአት ቢያስታውቃቸው ስሕተት ይሆናል፡፡ ግን በሕዝብ ሁሉ ፊት
የተሠራ ኃጢአት ቢኖር፤ ይቅርታ ስለማግኘት በሕዝቡ ሁሉ ፊት ሊነገር ይገባዋል፡፡ ግን የተወሰነ መሆን
ይገባዋል፡፡ ያነውን የበደላችሁበት ነገር እያታወቃችሁና እያመለከታችሁ መናዘዝ የገባችኋል፡፡ በሳሙኤል
ዘመን የእስራኤል ልጆች ከእግዚአብሔር መንገድ ወጥተው ተቅበዘበዙ፡፡ በእግዚአብሔር ማመናቸውን
ስለተው ሕዝቡን የሚገዛበቱን ኃይሉንና ጥበቡን ባለማወቃቸው፤ ሌላውን ለማዳን የሚችለውን ኃይሉን
መታመናቸውን ስለተዉ፤ ኃጢአት ያከተለውን መከራ ተቀበሉ፡፡ ዓለሙን ሁሉ ከሚገዛው ከትልቁ ገዢ
ፊታቸውን አዙረው በዙሪያቸው እንደነበሩት አሕዛብ ሁነው ሊገዙ ወደዱ፡፡ ገና ሰላም ሳያገኙ የተወሰነ ኑዛኔ
አደረጉ፡፡ እንዲህ ሲሉ፤ «ንጉሥ አንግሥልን ብለን በመለመናችን በኃጢአታችን ሁሉ ላይ ክፋት ጨመርነ፡፡»
(፩ ሳሙ ፲፪ ፡፲፱)፡፡ ያነውን ያመኑትን ኃጢአታቸውን አስታወቁ፡፡ እግዚአብሔርን አለማመስገናቸው
ነፍሳቸውን አስጨነቃት፤ ከእግዚአብሔርም ለያቸው፡፡ በውነት ንስሓ ካልገቡና ካልታደሱ፣ ንስሓን
እግዚአብሔር አይቀበልም፡፡ እግዚአብሔርም የሚስከፋ ነገርን ሁሉ ወዲያ ትቶ ሰው ፈጽሞ መለወጥ
ይገባዋል፡፡ በውነት ስለኃጢአቱ ለሚያዝን ሰው ትርፉ ይህ ነው፡፡ በኛ በኩል የምናደርገው ሥራ በግልጽ በኛ
ፊት ተቀምጦአል፡፡ «ታፀቡ ሰውነታችሁን አንጹ፡፡ ክፉ ሥራችሁን ከፊቴ አስወግዱ ክፉ መሥራታችሁን
ተዉ፣ መልካም ለመሥራት ተማሩ፤ እውነትን ፈልጉ፡፡ ፍርድን እሹየተጨነቀውን ከእስራቱ ፍቱ አባት
ለሌለው ፍረዱለት፡፡ ባልዋ ለሞተባትም ጠበቃ ሁኑአት፡፡» (ኢሳ ፩ ፡፲፮ ፡፲፯ )፡፡ «ያ ኃጢአተኛ ሰው ያኖረበትን
አደራ መልሶ ቢሰጥ የቀማውንም ቢመልስ ክፉ ሥራውን ትቶ በሕይወት ሥራት ቢመላለስ እርሱ ይድናል፡፡
አይሞትም»፡፡ (ሕዝ ፴፫ ፡፲፭ )፤ ጳውሎስ ስለ ንስሐ ሲናገር እንዲህ አለ፤ «እነሆ የልብ ኀዘን እንደ
እግዚአብሔር ፈቃድ የሚሆን ስንት ጥረት እሻችሁ ልመናም ቁጣም ፍርሃትም ናፍቆትም ቅናትም
መበቀልም ይህን ሁሉ ነገር ከማድረግ አቁማችሁ በሁሉ ንጹሐን ሆናችሁ፡፡» (፪ ቆሮ ፯ ፡፲፩ )፡፡ የሰውን
የጨዋነት አካሔድ፤ ዕውቀት ኃጢአት በገደለው ጊዜ በደለኛው የራን ጠባይ ጎደሎነት ለይቶ አያውቅም፡፡
ያደረገውን ክፋትም እውነት ነው አክፍቻለሁ ብሎ አያስታውቅም፡፡ እርሱን ለሚገሥፀው ለመንፈስ ቅዱ
ኃይል ካልታዘዘ በቀር፤ የሠራውን ኃጢአት እንዳያይ ወደ ዕውርነት አድልቶ ይኖራል፡፡ ኃጢአቱን ማታወቁ
የቀና እውነት አይደለም፡፡ ለሔደበት ክፉ መንገድ ይቅርታ ለማገኘት ኃጢአቱን ሁሉ በማታወቁ ላይ
ምክንያት ይጨምርበታል፡፡ ስለተነቀፈበቱ ነገር ስላንድ ምክንያት ባይሆን የህነንም ያነንም ባላደረግሁም
ነበር ይላል፡፡ አዳምና ሔዋን ከተከለከለው የዛፍ ፍሬ ከበሉ በኋላ የኃፍረትና የፍርሃት ዕውቀት ሞላባቸው፡፡
በመጀመርያ አሳባቸው ለኃጢአታቸው ምክንያት መሳይ አምጥተው ከሚያፈራ ከሞት ፍርድ ለማምለጥ
ብቻ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ስለኃጢአታቸው በጠየቃቸው ጊዜ አዳም ኃጢአቱን ከፍሎ በእግዚአብሔር፤
ከፍሎም በባለንጀራው በሔዋን ላይ ጭኖ «ከኔ ጋር ትሆን ዘንድ የሰጠኸኝ ሴት እርስዋ ከዛፊቱ ፍሬ ሰጠችኝ
በላሁ» አለ፡፡ ሴቲቱም ነውሩን በእባቢቱ ላይ አደረገች፤ እንዲህ ስትል፤ «እባቢቱ አታለለችኝ በላሁኝ፡፡» (ዘፍ
፫ ፡፲፫ ፡፲፬ )፡፡ እርስዋም ይህን ማለትዋ ስለምን እባብን ፈጠርህ፤ ስለምን ወደ ገነት ትመጣ ዘንድ
ፈቀድህላት ማለትዋ ነው፡፡ የወደቀችበትን ዕዳ ሁሉ በጌታ ላይ አድርጋ ይህን ጥያቄ መጠየቅዋ ነው፡፡ ራስን
የማጽደቅ መንፈስ እንዲሁ በሐሰት አባት ተጀመረ፡፡ ቀጥሎም በአዳም ወንዶችና ሴቶች ልጆች ሁሉ ተገለጸ፡፡
የእንዲህ ያለ ኑዛዜ ሥርዓት፤ በመለኮታዊ መንፈስ የተገለጸ አይዶለም፡፡ እግዚአብሔርም አይቀበለውም፡፡
እውነተኛ ንስሓ ሰዉን የራን ስሕተት እርሱ ራሱ ይሸከመው ዘንድ ይመራዋል፡፡ ያለማታለልና ያለግብዝና
እንዲያስታውቅ የ እውነቱን መንፈስ ይገልጽለታል፡፡ እንደዚያ ምስኪን ቀራጭ እንዲጮህ እንዲህ ሲል፤
«አቤቱ እኔን ኃጢአተኛውን ይቅር በለኝ፡፡» ዓይኑን ስንኳ ወደ ሰማይ ሊያነሣ ሳይደፍር እንዲሁ ኃጢአቱን
ያስታውቃል፡፡ እነዚያ ስሕተታቸውን የሚስታውቁ ይጸድቃሉ፡፡ ስኃጢአትዋ ተጸጽታ ንስሓ ስለገባች ነፍስ
የሱስ ደሙን ሰላፈሰሰ፡፡ በእግዚአብሔር ቃል የተሰጠው ምሳሌ ምክንያት የሌለበትን ኃጢአት፤ ወይም
ራስን ለማጽደቅ መሞከር የሌለበትን ጥሩ ንስሓን መዋረድን፤ ኃጢአትን የማስታወቅ መንፈስ ይገልጣል፡፡
ጳውሎስ ራሱን ሊመክት አላሻም፡፡ ኃጢአቱን ያሳንስ ዘንድ ሳይፈትን በጥቁር ቀለም ሳለው፡፡ እርሱም
«ከካህናት አለቆች ትዕዛዝ በተቀበልሁ ጊዜ ከቅዱሳን ብዙዎችን ሰዎች በግዞት ጨመርሁአቸው፡፡»
ሲገድሉአቸውም፤ የማፈርድባቸው እኔ ነበርሁ፡፡ በመስጊዱም ሁሉ ብዙ ጊዜ ቀጣኋቸው፡፡ ይሰደቡበትም
ዘንድ የግድ አልኋቸው በላያቸው ተነሥቼ ያለ ለክ ወፈፍ ብዬ ወደእንግዶች አገር ደግሞ አሳዳቸው ነበርሁ
አለ፡፡ (የሐዋ ፳፮ ፡፲ ፡፲፩)፡፡ እኔ መጀመሪያቸው የሆንሁ ኃጢአቶኞችን ሊያድን ክርስቶስ የሱስ ወደ ዓለም
እንደመጣ ያልጥርጥር የታወቀ ነው፡፡ (፩ ጢሞ ፩ ፡፲፭)፡፡ ከጥሩ ንስሓ በታች የሆነ የተዋረደና የተሰበረ ልብ
ከእግዚአብሔር ፍቅር በቃራንዮ ከተከፈለው ዋጋ ጥቂት ነገር አስቦ ያመሰግናል፡፡ ልጅ ለሚወደው አባቱ
እንደሚያስታውቅ እንዲሁ በውነት የተጸጸተ ኃጢአቱን ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ያሳያል፡፡ ተጽፎአልም
እንዲህ ሲል፤ ኃጢአታቸነን ብናስታውቅ ይቅር ይለን ዘንድ ከግፍም ሁሉ ያለጻን ዘንድ እርሱ የታመነና
ጻድቅ ነው፡፡ (፩ ዮሐ ፩ ፡፱)፡፡ ለሰው ሁል ጊዜ የሚታወቀው፡፡
የበረታው ፍቅሩ ታወቀኝ፡፡
የነፍሴን ጠላት ከኔ ሲያርቀው፡፡
ከግራ ሊመራኝ ወደቀኝ፡፡
ሸክሜን በእግሩ በታች እጥላለሁ፡፡
ወደ ሰማይ ደስታ ለመግባት፡፡
እጅግ አጥብቄ እቸኩላለሁ፡፡
የሕይወትን ፍሬ ልመገባት፡፡
ሕሊናችሁ በመንፈስ ቅዱስ ስለነቃ፤ የኃጢአትን ክፋቱን፤ ኃይሉን ነውሩን፤ ወዮታውን ታያላችሁ፡፡
በመጥላት ዓይንም ታያላችሁ፡፡ ኃጢአት ከእግዚአብሔር እንደለያችሁ፤ ለክፉ ኃይልም ባርያ እንደሆናችሁ
ይታወቃችኋል፡፡ ለማምለጥ በጣም ስትጥሩ ረዳት የሌላችሁ መሆናችሁን አብልጣችሁ ታያላችሁ፡፡
አሳባችሁና ልባችሁ ንጹሕ አይደለም፡፡ ኑሮአችሁ ራሳችሁን በመውደድና በኃጢአት ሞልቶ እንደ ነበረ
ታያላችሁ፡፡ ይቅር ልትባሉ፤ ልትነጹም አርነትም ልትወጡ ትናፍቃላችሁ፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር
መስማማትን፤ እርሱን መመሰልን በምንድር ነው የምታገኙ፤ የሰማያዊ ንጉሥን ይቅርታ፤ ሰላምን
ለነፍሳችሁ ስለማግኘት የምትሹት ሰላም ነው፡፡ ገንዘብ ሊገዛው አይችልም፤ እውቀትም ሊያገኘው
አይችልም፡፡ በራችሁ ግድለትም ልታገኙት አትችሉም፡፡ «ዳሩ ግን እግዚአብሔር፤ ያለ ብር ያለ ዋጋ እንዲያው
ሰጣችሁ» (ኢሳ ፶፭ ፡፩)፡፡ ብቻ እጃችሁን ዘርግታችሁ ብትጨብጡት፤ የእላንተ ነው፡፡ እግዚአብሔር አለ፤
ኃጢአታችሁ እንደ ከሰል ቢጠቁር እንደ በረዶ ይነጻል፡፡ እንደ ደምም ቢቀላ እንደ ነጭ ጥጥ ይጸራል፡፡ (ኢሳ ፩
፡፲፰ )፡፡ ደግሞ አዲስ ልብ እሰጣችኋለሁ፡፡ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፡፡ (ሐዝ ፴፮ ፡፳፮)፡፡
በክርስቶስ የሆነ ሁሉ ሰው እርሱ አዲስ ፍጥረት ነው አሮጌው ሥራ ፈጽሞ ሔደ፡፡ እነሆ ሁሉ ታደሰ፡፡ (፪ ቆሮ
፭ ፡፲፯ )፡፡
ሰው ወደ እግዚአብሔር የተለመሰበትን እርግጡን ጊዜ፣ ወይም ሥፍራውን ወይም የሆነውን ነገር በተራ ለማመልከት
አይችልም ይሆናል፡፡ ግብ ወደ እግዚአብሔር ያልተመለሰ ለመሆኑ ይህ ምስክር አይሆንበትም፡፡ ክርስቶስ ኒቆዲሞስን
አለው፤ ነፋስ ወደ ወደደችው ትነፍሳለች ድምፅዋንም ትሰማለህ፡፡ ዳሩ ግን ከወዴት እንድትመጣ ወዴትስ እንድሔድ
አታውቅም፡፡ ከመንፈስ ቅዱስ የሚወለድ ሁሉም እንዲሁ ነው፡፡ (ዮሐ ፫ ፡፰ )፡፡ ነፋስ የማይታይ እንደሆነ ገናም ኃይሉ
ያለ ችግር ለሰውነት የሚታወቅ እንደ ሆነ፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ በሥራው፤ በሰው ልብ ውስጥ እንዲሁ ነው፡፡
ሁለተኛ የመውለድ ኃይል፤ የሰው ዓይን ሊያየው የማይችለውን አዲስ ሕይወት በነፍስ ይወልዳል እንደ እግዚአብሔር
መንፈስ ድምጹአይሰማም፤ ረቂቅ የማይደሰስ ነው፡፡ ግን በሚያደርገው ኃይል ይገለጣል፡፡ልብ በእግዚአብሔር መንፈስ
የታደሰ ከሆነ፤ የሰውዬው አኗኗር ለእውነተኛናቱ ይመሰክርለታል፡፡ ልባችነን ለመለወጥ፤ ወይም ራሳቸነን
ከእግዚአብሔር ጋራ ልናስማማ አንዳች ነገር ልናደርግ ባልቻነን ጊዜ፤ በራሳችንም ፈጽመን ልንታመን የማይገባነ በሆነ
ጊዜ፤ ወይም በመልካም ሥራችን ልንታመን ባልቻልነ ጊዜ የእግዚአብሔር መንፈስ በውሥጣችን አድሮብን እንደሆነ፤
ወይም አላደረብን እንደሆን ኑሮአችን ይገልጠዋል፡፡ የእግዚአብሔር ጸጋ አድሮብን እንደሆን፤ ወይም አላደረብን
እንደሆን ያክፉ ልማድ፤ ክፉ አካሔድ በመለወጡ ይታያል፡፡ የቀድሞውን ሥራችነንና ያሁኑን ሥራችነን
ብናበላልጠውና ብናተያየው የቀድሞውና የዛሬው ልዩ መሆኑ ይገለጣል፡፡ ጠባይ የሚገልጥ ጸንቶ በሚኖር መልካም
ልማድና መልካም ንግግር ነው እንጂ፤ አንዳንድ ጊዜ በሚገለጥ መልካም ሥራ ወይም ክፉ ሥራ አይዶለም፡፡
የመታደስን ኃይል ገና ከክርስቶስ ሳያገኙ፤ በውጭ የታረመ ደኅና አካሔድ የሚያዩ ሰዎች መኖራቸው እውነት ነው፡፡
ሌላዎችን ሰዎች ስለማከበር ኃይል ለማገኘት መውደድና መሻት መልካም ሥራት ያለው ኑሮ ይሰጣል፡፡ ራን ማክበር
ክፉ ነገር ወደማይታይበት ይመራል፡፡ ራን የሚወድ ልብ የልግሥና ሥራን ይፈጽማል፡፡ ግን ወደማናቸው ወገን እንደሆነ
የተቆረጠ አሳባችነን እናሳያለንን፡፡ ልባችን የያዘው ማነው፤ አሳባችንስ ከማን ጋራ ነው፤ ስለማን ልንናገር እንወዳለን፤
የሞቀውን ኃይላችነንና ንራታታችነን የያዘ ማነው፡፡ የክርስቶስ ከሆነ አሳባችን ከርሱ ጋር ነው፡፡ የሚጣፍጠው
አሳባችንም የርሱ ነው፡፡ ያለነው ነገር ሁሉ ለርሱ ተቀድሶ የተሰጠ ነው፡፡ እንደርሱ ለመሆን፤ የርሱን መንፈስ ልንተነፍስ፤
ፈቃዱን ልባደርግ፤ በነገሩ ሁሉም ደስ ልናሰኘው እናንፍቃለን፡፡ እኒያ በክርስቶስ የሱስ አዲስ ፈጥረቶች የሆኑ የመንፈስ
ፍሬዎች፤ «ፍቅርን ደስታን፤ ሰላምን፤ ትዕግሥትን፤ ቸርነትን፤ በጎነትን፤ ሃይማኖትን፤ ገርነትን፤ መሻትን መግዛትን
ያፈራሉ፡፡» (ገላ ፭ ፡፳፪ ፡፳፫ )፡፡ በእግዚአብሔር ልጅ ሃየማኖት፤ ፍለጋውን ወይም ኮቲውን ተከትለው፤ ከቶውንም
«እርሱ ንጹሕ እንደ ሆነ»፡፡ ራሳቸውን አንጽተው፤ የርሱውን ባሕርይ ያሳያሉ እንጂ፤ ሰውነታቸውን ለቀደመው መሻት
ዓይነት አይሰጡም፡፡ አንድ ጊዜ ጠልተውት የነበረውን ነገር አሁን ይወዱታል፤ አንድ ጊዜ ጠልተውት የነበረውን ነገር ዛሬ
ይጠሉታል፡፡ ትዕቢተኞች የነበሩ፤ ራቸውን እውነተኛ ያደርጉ የነበሪ ሰዎች፤ ገሮችና የተዋረዱ ይሆናሉ፡፡ ያ ከንቱ ክብር
የሚወደው መንፈሳዊና ትሑት ይሆናል፡፡ ሰካራምም የማይሰክር፤ ዘማዊም ንጹሕ ይሆናል፡፡ ከንቱ ልማድና የዚህ
ዓለም ሥራ ዓይነት ወዳንድ ወገን ይጣላሉ፡፡ ክርስቲያኖች «በማጥፋት ልብ የተሠወረውን ሰው» ከቶውንም የገርነትና
የጸጥታ ጌጥን ይሻሉ እንጂ፤ ነውጭ የሚታይን ጌጥ አይሹም፡፡ (፩ ጴጥ ፫ ፡፫ ፡፬ )፡፡ የሰው ንስሓ መግባቱ የመታደስ
ሥራን ካልሠራ፤ በውነት ጥሩ ንስሓ ለመግባቱ ምስክር አያገኝም፡፡ ኃጢአተኛ በመያዣ የወሰደውንና የቀማውን
ቢመልስ፤ ኃጢአቱቱንም ቢያስታውቅ እግዚአብሔርንና ሰውን ቢወድ፤ በውነት ከሞት ወደ ሕይወት ይሻገራል፡፡ እኛ
በደለኞች፤ ኃጢአተኞች መሆናችንን አውቀን ወደ ክርስቶስ ስንመጣ፤ የይቅርታ ጸጋውንን ተካፋዮች ስንሆን ፍቅር
ከልብ ተነሥቶ ይዘላል፤ ወይም ይመነጫል፡፡ ክርስቶስ የጫነው ቀምበር ቀላል ስለሆነ፤ ሸክሙ ሁሉ ቀላል ነው፡፡ ሊደረግ
የሚገባው ሥራም በደስታ ይደረጋል፡፡ የሚቀርበው መሥዋዕትም በፍሥሓ የቀርባል፡፡ በጨለማ የተሸፈነ መስሎ
የነበረው መንገድ ከእውነተኛው ጠሐይ በወጣው ጮራ ብርሃን ይሆናል፡፡ የክርስቶስን ባሕርይ መውደድ፤ ከክርስቶስ
በሚከተሉት ሰዎች ይታያል፤ ለክርስቶስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማድረግ ደስታው ነበር፡፡ ለመድኃኔ ዓለም
እግዚአብሔርን መውደድ ስለ እግዚአብሔር ክብር መቅናት፤ በኑሮው አቸናፊ ኃይሉ ነበረ፡፡ ፍቅር ሥራውን ሁሉ
አሳመረለት፤ አከናወነለት፡፡ ፍቅር ከእግዚአብሔር ነው፡፡ ያልተቀደደሰ ልብ ፍቅርን ሊጀምረውና ሊያደርገው
አይችልም፡፡ ፍውር የሚገኝ ብቻ ክርስቶስ በነገሠበት ልብ ነው፡፡ «እርሱ አስቀድሞ ስለወደደን እኛ እንወደዋለን፡፡» (፩
ዮሐ ፬ ፡፲፱ )፡፡ በመለኮታዊ ጸጋ በታደሰ ልብ በኩል ፍቅር ዋና ነገር ነው፡፡ ባሕርይን ይለውጣል፡፡ ኃይልን ይገዛዋል፤
ፃዕርንም ያቸንፈዋል፡፡ ጠላታችነትንም በታች አድርጎ ይገዛዋል፡፡ በጣም የበረታውን ኃይል ያስችለዋል፤ ያስታግሠዋል፡፡
ይህ በነፍስ ውስጥ ያደገ ፍቅር ኑሮውን ያጣፍጣል፤ በዙርያውን ሁሉ ላይ የማርቀቅን ኃይል ያፈስበታል፡፡ በተለየ አሁን
በእግዚአብሔር ጸጋ ታምነው በሚመጡበት በእግዚአብሔር ልጆች ላይ መጠንቀቅ የሚያፈልጉ ሁለት ስሕተቶች አለ፡፡
የመጀመሪያው ፈጽሞ ያለባቸው ራቸውን ከእግዚአብሔር ጋራ ስለማስማማት ባነዳች ነገር ታምነው ሕግን በመጠበቅ
በገዛጃቸው ቅዱስ ለመሆን የራሳቸውን ሥራ መመልከታቸው ነው፡፡ ሕግን በመጠበቅ በሥራው ቅዱስ እሆናለሁ
የሚል፤ የማይሆን ነገር መፈተኑ ነው፡፡ ሰው ያለ ክርስቶስ የሚያደርገው ሁሉ ነገር፤ ራስን በመውደድና በኃጢአት
የረከሰ ነው፡፡ በሃይማኖት ቅዱ ሊያደርገን የሚችል፤ ብቻ የክስቶስ ጸጋ ነው፡፡ ሁለተኛው የኸን የሚቃወመው ሰው
በክርስቶስ ካመነ የእግዚአብሔርን ሕግ ሊጠብቅ አያሻውም ማት ነው፡፡ በሃይማኖት ብቻ የክስቶስን ጸጋ ተካፋዮች
ከሆነ፤ ሥራችን ለደኅንነታችን ከሚሆን ነገር አንዳች መገናኛ የለውም ይላሉ፡፡ ግን ፈቃደኝነት የፍቅር ማገልገል እንጅ
ብቻ የውጭ እሽታ እንዳይደል በዚህ ተመልከት፡፡ የእግዚአብሔር ሕግ የእግዚአብሔርን እውነተኛ ባሕርይ
የሚያስታውቀው የትልቁ ፍቅር መልክ ነው ይም ለግዛቱ በሰማይና በምድር መሠረት ሁኖታል፡፡ ልባችን እንደ
እግዚአብሔር ልብ ሁኖ ቢታደስ መለኮታዊ ፍቅርም በነፍሳችን ቢተከል፤ የእግዚአብሔርን ሕግ በነፍሳችን፤ በኑሮአችን
አንሸከመውንም፡፡ የፍቅር ዓይነተኛው ነገር በልብ ሲበቅል ሰው እንደፈጣሪው መልክ ሆኖ ሲታደስ፤ የአዲስ ቃል ኪዳን
ይፈጸማል፡፡ «ሕጎቼን በልባቸው አኖራለሁ በሕሊናቸውም እጽፋቸዋለሁ» እንዳለ፡፡ (ዕብ ፲ ፡፲፮ )፡፡ ሕግም በልብ የተጻፈ
ሆነ የሰውን አናኑዋር አያበጀውምን፡፡ ትእዛዝንና የፍቅር አገልግሎት መፈጸም የእውነተኛ ደቀ መዝሙር ምልክት ነው፡፡
መጽሀፍ ቅዱ እንዲህ ይላል፤ «የእግዚአብሔር ፍቅር ይህች ናት እርስዋም ትእዛዙን መጠበቅ» አውቀዋለሁ የሚል
ትእዛዙንም የማይጠብቅ እርሱ አነስተኛ ነው፡፡ እውነትም የለበት፡፡ (፩ ዮሐ ፭ ፡፫ ፡፡ ፪ ፡፬ )፡፡ ሰውን ከመታዘዝ አርነት
በማውጣት ፈንታ የክርስቶስን ጸጋ ተካፋዮች የሚደርገነን ሃይማኖትን መያዝ ይገባናል፡፡ ሃይማኖትም እንታዘዝ ዘንድ
እንድንችል ያደርገናል፡፡ በመታዘዝ መዳንን አናገኝም፡፡ መዳን በሃይማኖት የተገኘ የእግዚአብሔር ስጦታ ነውና፡፡
መታዘዝ ግን የሃይማኖት ፍሬ ነው፡፡ ያ ኃጢአታችነን ሊያስወግድ እንደ ተገለጠ እላንት ታውቃላችሁ፡፡ ኃጢአትም
በርሱ የለበትም፡፡ በርሱ የሚኖር ሁሉ ኃጢአት የለበትም፡፡ ኃጢአት የሚሠራ እሱን አላየውም፤ አላወቀውም፡፡ (፩ ዮሐ
፫ ፡፭ ፡፮)፡፡ እውነተኛ ፈተና በዚህ አለ፡፡ በክርስቶስ አምነን ብንኖር የእግዚአብሔር ፍውር በኛ ቦድር በልባችን
የሚታወቀነው ነገር፤ አሳባችን፣ ሥራችን ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋራ የተስማማ ይሆናል፡፡ በቅዱስ ሕግ እንደ ተናገረ
እንዲህ ሲል፤ «ልጆች ሆይ ማንም አያስታችሁ ጽድቅን የሚደርግ ጻድቅ ነው፡፡ ያ ክርስቶስ ጻድቅ እንደሆነ» (፩ ዮሐ ፫ ፡፯
)፡፡ በደብረ ሲና በተሰጡት በእግዚአብሔር 10 ትእዛዛት ጽድቅ በእግዚአብሔር ሕግ ተወስኖአል፡፡ ለእግዚአብሔር
ከመታዘዝ ሰውን አርነት የሚያወጣ ሃይማኖት ጥርጥር ይባላል እንጂ ሃማኖት አያባልም፡፡ «በጸጋው በሀያማኖት
ድናችኋል»፡፡ ሃይማኖት «ግን ምግባር ከሌላት እርስዋ የሞተች ናት»፡፡ (ኤፌ ፪ ፡፰ ፡፡ ያእ ፪ ፡፲፯)፡፡ የሱስ ወደዚህ ዓለም
ጋነ ሳይመጣ ስለራሱ እንዲህ አለ፤ «አባቴ ሆይ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ፡፡ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው፡፡» (መዝ ፵
፡፰ ) የሱስም ገና ወደ ሰማይ ተመልሶ ሳይወጣ እንዲህ አለ «እኔ ያባቴን ትእዛዝ ጠበቅሁ በውዱም ፀናሁ» (ዮሐ ፲፭፡፲
)፡፡ መጽሃፉ ይላል፤ ትእዛዙን ብንጠብቅ እንድናውቀው በዚህ እናውቃለን እኔ በርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ በሔደበት
መንገድ ሊሔድ ይገባዋል፡፡ (፩ ዮሐ ፪ ፡፫ ፡፮ ) ክርስቶስ ደግሞ ስለኛ ሕማም ተቀብሎአል፡፡ ፍለጋውን እንከተል ዘንድ
ለኛ ምሳሌ ትቶ፡፡ (፩ ጴጥ ፪ ፡፳፩ )፡፡ የዘለዓለም ሕይወት የሚገኝ የመጀመሪያ ወላጆችን ሳይወድቁ በገነት ይደረግ
እንደነበረ ለእግዚአብሔር ሕግ ፈጽሞ መታዘዝ ፍጹም ጽድቅ ማድረግ ነው፡፡ የዘለዓለም ሕይወት በማናቸውን ነገር
ከዘህ ቀደም ብሎ ተሰጥቶ ቢሆን ያን ጊዜ የዓለሙን ሁሉ ደስታ የሚያስፈራ ነገር ባገኘ ነበር፡፡ መንገዱም ለኃጢአት
የተከፈተ በሆነ ነበር፡፡ ከወዮታና ከክፉ ሥራው ጋር የማይሞት በመሆኑ፡፡ ለአዳም ከመውደቅ በፉት ለእግዚአብሔር
ሕግ በመታዘዝ የጽድቅ ስራ ሊሰራ ይቻለው ነበር፡፡ ግን ይህን ማድረግ ተሳነው፡፡ በርሱ ኃጢአትም የኛ ባሕርይ
ስለወደቀ ራሳችነን ልናጸድቅ አንችልም፡፡ እኛም ኃጢአት የሞላብነ ቅዱሳን አይዶለነ ከሆነ፤ ቅዱስ ለሆነ ሕግ ፈጽመን
ልንታዘዝ አንችልም፡፡ የእግዚአብሔርን ሕግ በመፈለግ እኛ በገዛጃችን ጽድቅ አናገኝም፡፡ ግን ክርስቶስ የምናመልጥበት
መንገድ አበጅቶልናል፡፡ በምድር እኛን እንደሚያገኘን፤ እርሱንም መከራና ፈተና አገኘው፡፡ እርሱ ኃጢአት የሌለበት ኑሮ
ኖረ፡፡ እርሱ ስለኛ ሞተ፡፡ ኃጢአታችነን አስወግዶ የርሱን ጽድቅ ይሰጠን ዘንድ፤ ራሱን መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ፡፡
ራችሁን ለርሱ ብትሰጡ፤ አዳኛችን ነው ብላችሁ ብትቀበሉት፤ ያን ጊዜ ምንም ኃጢአት የሞላበት ኑሮ ብትኖሩ ስለርሱ
ከጻድቃን ጋር ትቆጠራላችሁ፡፡ የክርስቶስ ባሕርይ በእላን ባሕርይ ፈንታ ይቆማል፡፡ ያን ጊዜ ኃጢአት እንዳልሠራችሁ
አድርጎ እግዚአብሔር ይቀበላችኋል፡፡ ከዚህም የሚበልጥ ክርስቶስ ልብን ይለውጣል፡፡ እርሱ በሃይማኖት በልባችሁ
ያድራል፡፡ በሃይማኖት ከክርስቶስ ጋራ አንድ መሆንን፤ ሁል ጊዜ ለርሱ እሺ ማለትን ገንዘብ ታደርጋላችሁ፡፡ ይህንንም
ስታደርጉ ሳላችሁ እንደርሱ በጎ ፈቃድ እንድትወዱና እንድታደርጉ እርሱ በእላንት አድሮ ይሠራል፡፡ እንዲህም
ትላላችሁ፤ «አሁን እኔ በሥጋ የምኖረው ኑሮ፤ እኔን በወደደኝ፤ ራሱንም ስለኔ አሳልፎ በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ
ሃይማኖት ነው፡፡» (ገላ 2፡20) እንዲሁ የሱስ ለደቀ መዛሙርቱ አላቸው፤ «በላንት አድ የሚናገር የሰማዩ አባታችሁ
መንፈስ ነው እንጂ እላንት የምትናገሩት አይዶላችሁም፡፡» (ማቴ ፲ ፡፳ )፡፡ እንዲሁ በላንት አድሮ ከላንት ጋራ
በሚሠራው በክርስቶስ ያለውን መንፈስ ትገልጻላችሁ፡፡ እርሱ የሚሠራውን ሥራ የጽድቅ ሥራ፤ የመታዘዝ ሥራ
ትሠራላችሁ፡፡ እንዲሁ በራሳችን የምንኮራበት አንዳች ነገር የለም፡፡ ራሳችነንም ከፍ የምናደርግበት ቦታ የለነም፡፡ ብቻ
እንኮራ ዘንድ ተስፋ የምናደርግበት ነገር፤ ስለኛ ጽድቅ ሆኖ የተቆጠረልን ነው፤ የየሱስ ክስቶስ ጽድቅ ነው፡፡ በኛ አድሮ
እየሠራ በመንፈሱ ያደረገው፡፡ ስለ ሃይማኖት ስንናገር፤ በአእምሮአችን ልንሸከመው የሚገባ ልዩ ነገር አለ፡፡ ፈጽሞ
ከሃይማኖት የተለየ አንድ ዓይነት ሃይማኖት አለ፡፡ ህላዌውንና ወይም መኖሩን የእግዚአብሔርም ኃይል የቃሉ
እውነት፤ እሊህ በእርግጥ እውነት ነገሮች ናቸው፡፡ ሰይጣንና ሠራዊቶቹ ስንኳ በልብ ሊክዱአቸው አይችሉም፡፡ መጽሐፍ
ቅዱስ «ሰይጣናትም ያምናሉ፤ ይንቀጠቀጣሉ ይላል፡፡» (ያዕ ፪ ፡፲፱ )፡፡ ግን ይህ ሃይማኖት አይዶለም፤ የእግዚአብሔርን
ቃል ማመን ብቻ በሌለበት ሥፍራ ግን፤ ለእግዚአብሔር ፈቃድ መታዘዝ ቢኖር የሰውዬውም አሳብ በእግዚአብሔር
በማመኑ ቢፀና፤ በፍቅር የሚሠራ፤ ነፍስንም የሚያነጻ፤ ሃይማኖት ይህ ነው፡፡ በዚህ ሃይማኖት የሰው ልብ እንደ
ለእግዚአብሔር ሕግ ገና ያልተገዛ ልብ፤ ከባለ መዝሙሩ ከዳዊት ጋራ ሁኖ፤ «ኦ እንደ ምን ሕግህን ወደድሁ እርሱ ቀኑን
ሁሉ አሳቤ ነው» እያለ፤ በእግዚአብሔር ቅዱስ ሕግ ደስ ሊለው ይችላል፡፡ (መዝ ፻፡ ፲፱ ፡ ፺፯ ) በመንፈስ እንጂ በሥጋ
በማንመላለስ፤በኛ የሕግ ጽድቅ ተፈጽሞአል፡፡ (ሮሜ ፰ ፡፩ )፡፡ የክርስቶስን የይቅርታ ፍቅር ያወቁ የእግዚአብሔር ልጆች
ለመሆንም በውነት የሚሹ አሉ፡፡ ገና ደግሞ ጠባያቸው ፍጹም አለመሆኑ ኑሮአቸውም በደለኛ መሆኑ፤ በውነት
ይታወቃቸዋል እሊህም ልባቸው በመንፈስ ቅዱ የታደሰ እንደሆነ ወይም ያልታደሰ እንደሆነ፤ ለመጠራጠር የተዘጋጁ
ናቸው፡፡ እንዲህ ላሉት ተስፋ ቆርጣችሁ፤ ወደኋላ አትመለሱ እላቸዋለሁ፡፡ በየሱስ እግሮች ላይ ለመውደቅ ሁል ጊዜ
ወደርሱ ስላልሔድነና ስለ በደልነ አንገታችነን ሰብረን ማልቀስ ይገባናል፡፡ ዳሩ ግን አንፍራ፡፡ በጠላት ስንኋድል የተነሣነ
ብንሆን፤ ወደ ውጭ የተጣልነ፤ በእግዚአብሔር ዘንድም የተረሳነና የተናቅኘ አይደለነም፡፡ ለኛ ደግሞ የሚያማልደነ፤
ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦአል፡፡ የተወደደው ዮሐንስ እንዳለ፤ «ኃጢአት እንዳትሠሩ ይህ ነገር
እጽፍላችኋለሁ፡፡ ከእላንተም ማንም ኃጢአት ቢሠራ፤ ከአብ ዘንድ የሚያማልደነ የሱስ ክርስቶስ፤ ጻድቁ አለነ፡፡» (፩
ዮሐ ፪ ፡፩ )፡፡ አብ ራሱ ይወዳችኋል የሚለውን ክርስቶስ ቃል አትርሱ፡፡ (የሐ ፲፮ ፡፳፯ )፡፡ የርሱም የንጽሕናና የቅድስና
ፀዳለ ብርሃን፤ በእላንት ውሥጥ አልፎ፤ ሲያበራ ለማየት፤ እሱ ወደርሱ ብታዘነብሉ፤ እርሱ ለእላንት መልካም ሥራ
የጀመረው ተሸክሞ፤ ወደፊት ወደ የሱስ ክርስቶስ ቀን ያደርሰዋል፡፡ በጣም ሞቅ ብላችሁ ጸልዩ፡፡ በጣም ሞልታችሁ
እመኑ፡፡ በራችን ኃይል የማንታመን ከሆነ በመድኃኔ ዓለም ኃይል እንታመን፡፡ እርሱን ለኛ ሰውነት ጤና የሆነውን
እናመሰግነው፡፡ በጣም ወደርሱ ስትቀርቡ፤ እጅግ በደለኞች መሆናችሁን፤ በገዛ ዓይኖቻችሁ ታያለችሁ፡፡ ለርሱ ባሕርይ
የማይስማማው፤ የእላንት ፍጹማን አለመሆን፤ ለርሱ ፍጹም ለሆነው ሰፊ ሁኖ፤ በተለየ ይታየዋል፡፡ የሰይጣን የሚስቱ
ነገሮቹ ሁሉ፤ ኃይላቸው እንደጠፋ፤ የሚያነቃ የእግዚአብሔር መንፈስ ኃይልም ሊያስነሳችሁ እንደጀመረ ይህ ምስክር
ነው፡፡ የራሱን ኃጢአት በማያውቅ ሰው ልብ፤ የክርስቶስ ፍውር በጣም ወደ ውስጥ ጠልቆ አያድርበትም፡፡ በክርስቶስ
ጸጋ ከክፉ ወደ በጎ ነገር የተለወጠ መልክ፤ ያላት ነፍስ፤ የክርስቶስን መለኮታዊ ባሕርይ ቃደንቃለች፡፡ የአካሔዳችነን
መልክ መክፋት ልናይ ካልቻልነ፤ ያማረና የከበረ የክርስቶስ መልክ፤ እንደሌለብነ ያለ ጥርጥር እንመሰክራለን፡፡
የራሳችነን ክብ ጥቂት ስናበላልጥና ስናስተካክል፤ የማያልቀውን የመድኃኔ ዓለም ንጽሕናና ፍቅር አብልጠን እናያለን፡፡
ኃጢአት የሞላብነ መሆናችነን ማየታችን፤ ይቅር ሊለን ወደሚችለው ይነዳናል፡፡ ነፍስም ረዳት የሌላት መሆንዋን
አምና፤ ወደ ክርስቶስ ስትደርስ፤ ክርስቶስ ራሱን በኃይል ይገልጽላታል፡፡ እርዳታ እንድንሻ ማወቃችን በጣም ወደ
ክርስቶስና ወደ ቃሉ ሊነዳነ ከርሱ ባሕርይ በጣም ከፍ ያለ ማየት ስናገኝ፤ የርሱን መልክ በጣም አሳልፈን ለሌሎም
ሰውች እናሳያለን፡፡
የእግዚአብሔር ልጆች የምንሆንበት የልብ መለወጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ፤ ዳግመኛ መወለድ ነው ተብሎ
ተነግሮአል፡፡ ዳግመኛም አራሽ ለዘራው መልካም ቡቃያ ምሳሌ ሁኒ በትክክል ተጽፎአል፡፡ እንዲሁ እሊህ
አሁን ወደ ክርስቶስ የተመለሱት «ለማደግ አዲስ እንደ ተወለዱ ሕፃናት» ልጆች ናቸው፡፡ (፩ ፡ ጴጥ ፪ ፪ ኤፌ
፬ ፡፲፭ )፡፡ በክርስቶስ ለዓቅመ አዳምና ለዓቅመ ሔዋን እንዲደርሱ፡፡ ወይም በእርሻ እንደ ተዘራ መልክም ዘር
እንዲያድጉና ፍሬ እንዲሰጡ፡፡ ኢያሳያስ «እግዚአብሔር ይከብርባቸው ዘንድ እግዚአብሔር የተከላቸው
የጽድቅ ዛፎች የእግዚአብሔር አታክልት»፣ ይባላሉ አለ፡፡ (ኢሳ ፷፩ ፡፫ ) እንዲሁ የመንፈሳቂ ኑሮ ምሥጢርን
እንደሚሻል አድርገን እንድናስተውለው ይረዳን ዘንድ ከፍጥረቶች ምሳሌ ተቀድቶአል፡፡
ለትንሾች ፍጥረቶች ስንኳ የሰው ጥበብና ዕውቀት ሁሉ፤ ሕይወት ሊሰጥ አይችልም፡፡ ግን አታክልትም
ቢሁኑ ወይም እንስሶች ሊኖሩ የሚችሉ፣ እግዚአብሔር ባካፈላቸው ሕይወት ነው፡፡ እንዲሁ መንፈሳዊ
ሕይወት በሰው ልብ የሚወለድ ብቻ ከእግዚአብሔር በተገኘው ሕይወት ነው፡፡ ሰው «ከላይ ካልተወለደ»
ክርስቶስ ሊሰጠን ከመጣበቱ ሕይወት ተካፋይ ሊሆን አይችልም (ዮሐ ፫ :፫ )፡፡ በሕይወትም እንደሆነ
በማደግም እንዲሁ ነው፡፡ ቡቃያውንን እንዲያብብ፤ ያበበውንም እንዲያፈራ የሚያደርግ እግዚአብሔር
ነው፡፡ ዘሩም የሚበቅል በእግዚአብሔር ኃይል ነው፡፡ «መጀመሪያ ቆባ ኋላ ዛላ፤ በዛላውም ሥንዴ
ትሆናለች፡፡» (ማር ፬ ፡ ፳፰ )፡፡ ነቢዩ ሆሴዕ ስለ እስራኤል ይላል፤ እንደ ቡቋያ ያድጋል፣ እንደአበባም ያብባል፣
ችራፎች ይዘረጋሉ፣ ክብሩም እንደ ወይራ ሽታውም እንደ ሊባኖስ ወይን ይሆናል፣ (ሆሴዕ ፲፬ ፡፭ ፡፯ ) የሱስ
እንዲህ ብሎ ያዘናል፤ «አበቦችን እንዴት እንዲያድጉ ተመልከቱ፡፡» (ሉቃ ፲፪ ፡፳፯ )፡፡ አበባዎች እግዚአብሔር
ለሕይወታቸው ጥቅም ያዘጋጀውን በመቀበል እንጂ በገዛ አሳባቸው፣ በገዛ ትጋታቸው ወይም በገዛ
ጥረታቸው አያድጉም፡፡ ታናሽልጅ በራሱ ትካዜ ወይም ኃይል በቁመቱ ላ አንዳች ነገር ሊጨምር አይችልም፡፡
እላንተም በራሳችሁ ትካዜ ወይም ጥረት መንፈሳዊ ማደግን አታገኙም፡፡ ተክልም ልጅም በዙሪያቸው
ያለውን ለሕይወታቸው የሚያገለግልን ነፋስን፣ ብርሃነ፣ ፀሐይን፣ ምግብን በመቀበል ያድጋሉ፡፡ እሊህ
የፍጥረቶች ስጦታ ለእንስሶችና ለአትክልት እንደ ተሰጡ ክርስቶስም በርሱ ለሚታመኑ እንዲሁ ነው፡፡
«የዘለዓለሙ ብርሃናቸው» እርሱ ነው፡፡ «ፀሐይም ጋሻም እርሱ ነው፡፡» (ኢሳ ፷ ፡፲፱ ፡፡ መዝ ፹፬ ፡፲፩ )፡፡
ለእስራኤል እርሱ «እንደ ጠል ነው፡፡ እንደ ዝናምም በታጨደ ሣር ላይ ይወርዳል»፡፡ እሱ የሕይወት
ውኃእንጀራ ከሰማይ የወረደ የእግዚአብሔር ሕይወት ለዓለሙ የሚሰጥ ነው፡፡ (የሐ ፮ ፡ ፴፫)፡፡ እግዚአብሔር
ምሳሌ የሌለውን ልጁን ለኛ በመስጠቱ፤ ነፋ በውነት የምድሩን ዙሪያ እንደሚከበው እንዲሁ ዓለሙን ሁሉ
እግዚአብሔር በጸጋ ነፋስ ከቢታል፡፡ ይህነን ሕይወት የሚሰጥ እስትንፋስ ሊተነፍስ የሚወድ ሁሉ፣
በክርስቶስ ለዓቅመ አዳምና ሔዋን እስኪደርስ ሕያው ሆኖ ይኖራል፣ ያድጋል፡፡ አበባ ውበቱን መተካከሉን
ለመፈጸም የብርሃን ፀዳል እንዲረዳው ፊቱን ወደ ፀሐይ እንደሚመልስ፣ እኛም እንዲሁ ወደ እውነተኛው
ፀሐይ እንመልሳለን፡፡ የሰማይ ብርሃን በላያችን እንዲያበራ ባሕርያችንም በክርስቶስ ምሳሌ የወጣ ሆኖ
እንዲታይ፡፡ የሱስም ይህነውን ነገር ያስተምራል እንዲህ ሲል፤ «በኔ ፅ ኑ እኔም በእላንተ»፡፡ ጨፍም በወይኑ
ዛፍ ከሌለ ብቻውን ያፈራ ዘንድ እንዳይችል እንዲሁም እላንተ በኔ ካልጸናችሁ ያለኔ አንዳች ታደርጉ ዘንድ
አትችሉም፡፡ (ዮሐ ፲፭ :፬ ፡፭ )፡፡ ቅርንጫፍ ወይም ዓፅቅ ለማደግና ብዙ ፍሬ ለመስጠት በግንድ ላይ
እንደሚሆን እላንተም በክርስቶስ ላይ እንደተንጠለጠላችሁ ናችሁ፡፡ ከርሱ ከተለያችሁ ሕይወት የላችሁም፡፡
ፈተናን ለመቃወመወ ወይም በጸጋና በቅድስና ለማደግ ለእላንት ኃይል የላችሁም፡፡ በርሱ ስትኖሩ
ታብባላችሁ፡፡ ሕይወታችሁን ከእርሱ ከሕይወቱ ምንጭ ስትቀዱ አትጸወልጉም፤ ፍሬ የሌላችሁም
አትሆኑም፡፡ በወንዝ ውኃ ዳር እንደተተከል ተክል ትሆናለችሁ፡፡ ከሥራው ጥቂት ከፍለው ሊያደርጉ
የሚያስቡ ሰዎች አሉ፡፡ ስለ ኃጢአት ይቅርታም በክርስቶስ ታምነዋል፡፡ አሁን ግን በገዛ ጥረታቸው የቀና ኑሮ
ለመኖር ያሻሉ፡፡ ግን እንደዚህ ያለው ጥረት ሁሉ ከንቱ ነው፡፡ የሱስ አለ፤ «የለኔ አንዳች ልታደርጉ
አትችሉም»፡፡ በጸጋ ማደጋችን፤ ደስታችንም፤ የምንረባ መሆናችንም ሁሉ ከክርስቶስ ጋራ አንድ በመሆናችን
ላይ ነው፡፡ የቀኑ፤ በየሰዓቱ በጸጋ የምናደርግ፤ ከርሱ ጋራ አንድ ሁነን በመኖር ነው፡፡ እርሱ የሃይማኖታችን
ጀማሪ ብቻ አይደለም፡፡ ግን ፈጻሚም ነው እንጂ፡፡ ክርስቶስ መጀመሪያና መጨረሻ፤ ሁል ጊዜም ነው፡፡
እርሱ ከኛ ጋር የሚሆን በመንገዳችን መጀመሪያና መጨረሻ ብቻ አይ ደለም፤ ግን በየመንገዳችን እርምጃ
ከኛ ጋር ነው፡፡ ዳዊት አለ፤ እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ በፊቱ አየዋለሁ፡፡ በቀኜ ስለ ሆነ፡፡ እንዳልታወክ፡፡ (መዝ ፲
፮ ፡፰ )፡፡ በመጀመሪያ ክርስቶስን በተቀበላችሁ ጊዜ፤ እኔ በክርስቶስ እንዴት እኖራለሁ ብላችሁ ራሳችሁን
«ትጠይቃላችሁ እንግዲህ ጌታችነን የሱስ ክርስቶስን እንደተቀበላችሁት በርሱ ሒዱ፡፡ ጻድቅ በሃይማኖት
ይድናል፡፡» (ቆላ ፪ ፡፮ ፡፡ ዕብ ፲ ፡፴፰ ) ልታገለግሉትና ልትታዘዙት ራሳችሁን ፈጽማችሁ ለእግዚአብሔር
ሰጣችሁ፡፡ ክርስቶስም አዳኛችሁ እንደሆነ አውቃችሁ ተቀበላችሁት፡፡ እላንት ስለ ኃጢአታአችሁ ራሳችሁን
ቤዛ አድርጋችሁ ልትሰጡ ወይም ልትለውጡ አትችሉም፡፡ ግን ራሳችሁን ለእግዚአብሔር ሰጥታችሁ እርሱ
ስለ ክርስቶስ የህን ሁሉ እንዳደረገላችሁ አመናችሁ፡፡ በሃይማኖት የክርስቶች ሆናችሁ፡፡ በሃይማኖት
በመስጠትና በመውሰድ በርሱ ታደርጋላችሁ፡፡ ልባችሁ ሁሉ፤ እርሱ በሚሻው ነገር ሁሉ ለመታዘዝ ልትሰጡ
ናችሁ፡፡ ክርስቶስን ፈጽማችሁ ልትቀበሉት ይገባችኋል፡፡ የበረከቱንም ምላት ልትቀበሉ ይገባችኋል ትታዘዙ
ዘንድ ኃይል እንዲሰጣችሁ፤ ክርስቶስን ኃይላችሁን፤ ጽድቃችሁን የዘለዓለም ረዳታችሁን ልትቀበሉት
የገባችኋል፡፡ በጡዋት ማለዳ ራሳችሁን የተቀደሰ ስጦታ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር ስጡ፡፡ ይህነንም
ለእላንት የመጀመሪያ ሥራ አድርጉት፡፡ ጸሎታችሁም እንዲህ ይሁን፤ ጌታ ሆይ ፈጽመህ ላንተ አድርገኝ፡፡
አሳቤን ሁሉ በእግርህ አኖራለሁ፡፡ ዛሬ ለሥራህ የምባ አድርገኝ፡፡ ከኔ ጋራ ኑር ሥራ ሁሉ ባንተ የተደረገ
ይሁን፡፡ ይህም በየለቱ የሚደረግ ነገር ነው፡፡ ለዚያኛው ቀን ስትል፤ በየቀኑ ራስህን ለእግዚአብሔር ቀድሰህ
ስጥ፡፡ እርሱ እንዳዘጋጀው ሁኖ እንዲደረግልህ አሳብህን ሁሉ ለእግዚአብሔር ስጥ፡፡ እንዲሁ በየቀኑ
ሕይወታችሁን ለእግዚአብሔር እጅ ትሰጣላችሁ፡፡ እንዲሁ ኑሮአችሁ በጣም እንደ ክርስቶስ ይሆናል፡፡
በክርስቶስ መኖር ዕረፍት የሞላበት ኑሮ ነው፡፡ በዚያም ያ ትልቅ ደስታ አይታወቅም ይሆናል፡፡ ግን በዚያ
በሰላምና በመታመን ልትኖር ይሆንልሃል፡፡ ተስፋችሁን ከክርስቶስ እንጂ፤ ከራሳችሁ አታገኙም፡፡ ድካማችሁ
ከርሱ ኃይል ጋራ፤ አለማወቃችሁም ከርሱ ጥበብ ጋራ፤ ኮሳስነታችሁም ፀንቶ ከሚኖረው ኃይሉ ጋራ
ተቀላቅሎአል፡፡ እንዲሁ በራሳችሁ ልትታመኑ አይገባም፡፡ አሳባችሁ በከርስቶስ እንጂ በራሳችሁ አይሁን፡፡
አሳብህ በእርሱ ፍቅር ላይ በእርሱ ውበት ላይ፤ በእርሱ ባሕርይ ፍጹምነት ላይ ይኑር፡፡ ነፍስ በጥንቃቄ
ልታስበው የሚገባት ዋናው ነገር፤ ክርስቶስ ራሱን አሳልፎ ስለ ሰው መስጠቱን፤ ክርስቶስ መዋረዱን፤
የክስቶስን ንጹ ሕና፤ ቅዱስ መሆንን፤ የክርስቶስን ምሳሌ የሌለው ፍቅሩን ነው፡፡ እርሱን መምሰል የሚገኝ
እርሱን በመውደድ፤ ፈጽሞ እርሱን መስሎ በእርሱ ዘንድ ሁኖ በመገኘት ነው፡፡ የሱስ አለ፤ በኔ ኑሩ፡፡ እሊህ
ቃሎች የዕረፍትን ነገር በሃይማኖት ፀንቶ መኖርን፤ መታመንን ያሳያሉ፡፡ ዳግመኛም ወደኔ ኑ እያለ
ይጠራል፡፡ (ማቴ ፲፩ ፡፳፰ ፡፳፱)፡፡ ባለ መዝሙሩ ዳዊትም ይሀነውን አሳብ የገልጻል እንዲህ ብሎ፤
በእግዚአብሔር አርፈህ በትዕግሥት ደጅ ፅና፡፡ ኢሳይያስም የዚህን ነገር እርግጥነት ያስረዳል እንዲህ እያለ፤
ኃይል የምታገኙ በእርጋታና በመታመን ነው፡፡ (መዝ ፴፯ ፡፯ ፡፡ ኢሳ ፴ ፡፲፭ ) ይህ ዕረፍት በሥራ የተገኘ
አይደለም፡፡ የመድኃኔ ዓለም ጠሪት ተስፋም ለሥራ ከመጠራት ጋራ አንድነት የተወሐደ ነውና፡፡ ቀምበሬን
በላያችሁ ተሸከሙ፡፡ ዕረፍትም ለነፍሳችሁ ታገኛላችሁ፡፡ (ማቴ ፲፩ ፡፳፱ )፡፡ በክርስቶስ ላይ ፈጽሞ የሚያርፍ
ልብ ስለ ክርስቶስ ሊሠራ በጣም የሚሻና የሚጥር ይሆናል፡፡ ሰው በገዛ ራሱ አሳብ ላይ ሲኖር ከክርስቶስ
ከኃይልና ከሕይወት ምንጭ ርቆ ወደ ሌላ ይዞራል፡፡ አሳብን ከመድኃኔ ዓለም የሚለይ የሰይጣን ፅኑ ጥረት
ነው፡፡ እንዲሁ ነፍስን ከክርስቶስ ጋራ አንድ እንዳትሆን ይከለክላታል፡፡ የዓለሙ ደስታ ለኑሮ ማሰብ፤
ጭንቀት ኃዘን የሌላዎች ሰዎች በደለወ፤ ወይም በዚህ ሁሉ ነገር የተያዘ ሰው ክስቶስን ከማሰብ ይልቅ፤
አእምሮውን ወደ ሌላ ለማዞር ይሻል፡፡ ሰይጣን ቢያታልልህ በርሱ ተመርተህ ወዳልሆነ መንገድ አትሒድ፡፡
ብዙዎች ኃጢአታቸው በውነት የታወቃቸው ለእግዚአብሔር ሊኖሩ ሲወዱ፤ ደግሞ በስሕተታቸውና
በድካማቸው እንዲኖሩ፤ ሰይጣን ይመራቸዋል፡፡ እንዲሁ እነዚያን ከክርስቶስ በመለየት ድል ሊነሣቸው
ተስፋ ያገርጋል፡፡ እንድናለን ወይስ እንድንም በማለት የውሥጡን አሳባችነን ትጋት በገዛ ራሳችን ማድረግ፤
መጨነቅ፤ ፍርሃት አይገባነም፡፡ ይህ ሁሉ ነፍስን ከኃይላችን ምንጭ ያርቃታልና፡፡ የነፍስህን ጥበቃ
ለእግዚአብሔር ስጥ፡፡ በርሱም ታመን፡፡ ስለ የሱስ ተነጋገርና አስብ፡፡ ጥርጥርን ሁሉ ወዲያ አስወግድ፤
ፍርሃትንም አሰናብት፡፡ ከሐዋርያው ከጳውሎስ ጋራ ሁነህ እንዲህ በል፤ «እኔ ህያው ነኝ፡፡ እኔም አይደለሁ፤
ግን ክርስቶስ በኔ ሐያው ነው፡፡ ይህችንም ሕይወት ዛሬ እኔ በሥጋ ያለሁባት እኔን በወደደኝ ራሱንም ስለኔ
በነወጠው፤ በእግዚአብሔር ልጅ ሃይማኖት የምኖርባት ሕይወት ናት»፡፡ (ገላ ፪ :፳)፡፡ በእግዚአብሔር ዕረፍ
ለርሱ የሰጠኸውን አደራ ሊጠብቅ የሚችል ስለሆነ ራሳችሁን በርሱ እጅ ብትተውለት፤ ድል ከነሣ ይልቅ
በርሱ በወደዳችሁ ያመጣችኋል፡፡ ክስቶስን የሰውን ባሕርይ፤ በራሡ ላይ በተሸከመ ጊዜ፤ ሰው መሆንን
በፍቅር ማሠርያ አሥሮ ተሸከመ፡፡ ይህን የፍቅር ማሠር›ሪያም፤ ሰውየው እርሱው ራሱ ሊቆርጥ አይቻልም፡፡
ሰይጣን ይህን የፍቅር ማሠርያ ቆረጠን፤ ከክርስቶስ እንድንለይ ሊያደርገን ሁል ጊዜ የማጥመጃ ነገር
በመንገዳችን ያኖራል፡፡ ሌላ ጌታ ለመምረጥ፤ አንዳች ነገር እንዳያጸምደን ለመጸለይ የምንተጋበት ጊዜ እንሆ
ይህ ነው፡፡ ይህን ለማድረግ እኛ እንዳንከለከል ነፃ ነን፡፡ ግን ዓይናችነን ተክለን ወደ ክርስቶስ እንመልከት፤
እርሱም ይጠብቀናል፡፡ ወደ ክርስቶስ በማየት እናድናለን፤ ከእጁ ሊያወጣን የሚችል አንዳች ነገር የለም፤
እርሱን አፅንተን በመመለክታችን፤ ከቶውንም በጌታ መንፈስ ከክብር ወደ ክብር ወደ እርሱ መልክ
ተለውጠናል፡፡ (፪ ቆሮ ፫ ፡ ፲፰ )፡፡ የፊተኞች ደቀ መዛሙርት፤ የተወደደውን መድኃኔ ዓለምን መምሰላቸውን
ያገኙት እንዲሁ ነበር፡፡ እሊያ ደቀማዛሙርት ዬሱስን ቃል በሰሙ ጊዜ፤ እርሱን መሻት እንዲያስፈልጋቸው
ታወቃቸው፡፡ ፈለጉት፤ አገኙት፤ ተከተሉት፡፡ በቤት በማዕድ ጊዜ፤ በእልፍኛ፤ በውጭ ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡
ከከንፈሩ የሚወጣውን የተቀደሰውን እውነተኛ ትምህርት፤ በየዕለቱ እየተቀበሉ፤ ተማሮች ከመምህራቸው
ጋር እንዲቀመጡ፤ ከርሱ ጋራ ነበሩ፡፡ ሎሌዎች ያደርጉት ዘንድ የሚገባቸውን ሥራ ለማወቅ፤ ጌታቸውን
እንደሚያዩት፤ ያዩት ነበሩ፡፡ እሊያ ደቀ መዛሙርትም፤ «አንደኛ በድካም የተካከሉነ ሰውች ለበሩ»፡፡
ከኃጢአት ጋራ ለመዋጋት፤ የኸው ጦርነት ነበረባቸው፡፡ የተቀደሰ ኑሮ ለመኖር የህኑ ጸጋ ይሹ ነበሩ፡፡ (ያዕ ፭
፡፲፯ )፡፡ የተወደደው ደቀ መዝሙር ዮሐንስ፤ በጣም ክርስቶስን የመሰለው ስንኳ ያን ፍቅር በባሕርይ
አላገኘውም፡፡ እርሱ ራሱን እውነተኛ አድርጊና ክብር ፈላጊ ብቻ አልነበረም፤ ግን ቀልጥፎ የሚቆጣና
ኃጢአተኛ ነበር፡፡ ግን የመለኮት ባሕርይ በተገለጠለት ጊ\፤ የራሱን ጎደሎነትና የሚያሻውን ነገር አየ፡፡
በእውቀትም ራሱን አዋረደ፡፡ መበርታትን፤ ትእግሥትን፤ ኃይልን፤ ርኅሩኅነትን፤ ግርማ ሞገስን፤
በእግዚአብሔር ልጅ አናኑዋር ባየ ጊዜ፤ በነፍሱ መደነቅና ፍቅር መላበት፡፡ ጌታውን ስለወደደ፤ በገዛ ራሱ
መታመንን እስኪተው ድረስ፤ በየቀኑ ወደ ክርስቶስ ይሳብ ነበረ፡፡ ቁጣ የሞላበት ክብን የሚወድ፤ ጠባዩም፤
ወደ ለስላሳው፤ ወደ ክርስቶስ ጠባይ ተመለሰ፡፡ ዳግመኛ የመወለድ፤ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል፤ ልቡን
አደሰለት፡፡ የክርስቶስ የፍቅሩ ኃይል፤ ጠባዩን ለወጠለት፡፡ ከክርስቶስ ጋራ አንድ በመሆን የሚገኘው
የውነተኛው ነገር ይህ ትርፉ ነው፡፡ ክርስቶስ በልብ ሲያድር ክፉ ጠባይ ሁሉ፤ ወደ መልካም ነገር ይለወጣል፡፡
የክርስቶስ መንፈስና ፍቅር ልብን ያለሰልሳል፡፡ ነፍስንም እንድትገዛ ያደርጋታል፡፡ አሳብንማ ፈቃድንም ወደ
እግዚአብሔርና ወደ ሰማይ ያስነሣል፡፡ ክስቶስ ወደ ሰማይ ኣቡ ያን ጊዜ ከደቀመዛሙርቱ ጋራ ነበረ፡፡ የሱስ
መድኃኒታችን፤ ከነዚያ ጋራ ሲሔድ የነበረው፤ ሲነጋገራቸውም ሲጸልይ፤ ለልባቸው የተስፋና የመፅናናት ነገር
ይነግራቸው የነበረው፤ የሰላሙ መልእክት ገና ከከንፈሩ ሳለ፤ ከነርሳቸው ወደ ሰማይ ተነጠቀ፡፡ ደመኖች
በተቀበሉት ጊዜ፤ የድምጹ ቃና ወደነርሳቸው ተመልሶ መጣ አላቸውም፤ «በዘመኑ ሁሉ፤ እስከ ፍጻሜ
ድረስ፤ ከላንተ ጋራ ነኝ»፡፡ (ማቴ ፳፰ ፡፳)፡፡ በሰውነቱ አካል፤ ወደ ሰማይ ወጣ፡፡ እነዚያም ወዳጃቸውና
አዳኛቸው በአባቱ ዙፋን ቀኝ እንደተቀመጠ፤ ገናም ከነዚያም ጋራ ሁኖ እንደወትሮው፤ ሰው መሆንን
ታግሦ፤ እንዲያዝን አወቁ፡፡ ስላዳነቸው ፍጥረቶች፤ ለከፈለው ዋጋ መታሰቢያ፤ የቆሰሉትን እጆቹንና
እግሮቹን የከነረውን የራሱን ደም ምግባር በአባቱ ፊት አቀረበ፡፡ ለነርሳቸው ቦታ ሊያዘጋጅ ወደ ሰማይ
መውጣቱን ዳግመኛም፤ ለራሱ ወደርሱ ሊወስዳቸው እንመጣ አወቁ፡፡ ሐዋርያትም፤ ከዕርገቱ በኋላ
አንድነት በተገናኙ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር አብ በየሱስ ስም ጸሎታቸውን ያቀርቡ ዘንድ ቀለጠፉ፡፡
እግዚአብሔርን መፍራት ባለበት ሃይማኖት፤ ለጸሎት ተምበረከኩ፡፡ ጌታ የሰጣቸውን የእምነትን ቃል
እየደገሙ፡፡ «በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ አብ ይሰጣችኋል»፡፡ እስከ ዛሬ በስሜ አንዳች አለመናችሁም፡፡
ደስታችሁ እንዲፈጽም ለምኑ ይሰጣችኋል፡፡ (ዮሐ ፲ ፡፮ ፡፳፫ ፡ ፳፬ )፡፡ የለመኑትን ሊያደርግላቸው ወደሚችል
እግዚአብሔር የሃይማኖት እጃቸውን ከፍ ከፍ አደረጉ፡፡ የሞተውም፤ ከሙታን የተነሣው፤ በእግዚአብሔር
ቀኝም የተቀመጠው ክርስቶስ ነው፡፡ እርሱም ያስምረናል፡፡ (ሮሜ ፰ ፡ ፴፬ )፡፡ በጰንጤቆስጤ ቀን በእላንት
ያድርባችኋል ያለውን፤ የሚያፀናውን መንፈስ ቅዱስን ላከላቸው፡፡ ከዚህም የሚበልጥ ብሎአል፤ «ነገር ግን
መሔዴ እንዲሻላችሁ እውነት እላችኋለሁ፡፡ እኔ ባልሔድ ጰራቅሊጦ አይመጣላቹሁምና፡፡ የሔድሁ እንደሆን
ግን እርሱን እልክላችኋለሁ»፡፡ (ዮሐ ፲፬ ፡፲፯ ፡፲፮ ፡፯ )፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ ሁል ጊዜ
በልጆቹ ልብ ለያድር ነው፡፡ ከርሱ ጋራ አንድነታቸው ይልቅ የሚበልጥ ሆነ፡፡ በውሥጣቸው ያደረው
የክርስቶስ ብርሃንና ፍቅር፤ ኃይልም በነዚያ ታይቶአል፡፡ እንዲሁም ይህነውንም ያዩ ሰዎች አደነቁ፡፡ እኒያ ደቀ
መዛሙርትም ከየሱስ ጋራ እንደነበሩ አወቁ (የሐዋ ፱ ፡፲፫ )፡፡ ክርስቶስ ለመጀመሪያ ደቀ መዛሙርቱ
ሁኖላቸው እንደነበረው ሁሉ፤ ለዛሬዎች ልጆቹም፤ ሊሆንላቸው ፈቃዱ ነው፡፡ ከነዚያ ጥቂቶች
ደቀመዛሙርቱ ጋራ ሳለ፤ በመጨረሻ ጸሎቱ ጊዜ አለ፤ ደግሞ በቃላቸው ስለሚያምኑብኝ እንጂ ስለነዚህ
ብቻ አለምንም፡፡ (ዮሐ ፲፯ ፡፳)፡፡ የሱስ እሱ ከአብ ጋራ አንድ እንደሆነ፣ እኛ ደግሞ፤ ከርሱ ጋራ አንድ
እንድንሆን ጸለየ፤ ለመነ፡፡ ያ እንድነት፤ እንዴት ያለ አንድነት፤ እንዴት ያለ አንድነት ነው? መድኃኔ ዓለም
ስለራ እንዲህ አለ፤ ልጅ ከራሱ አንዳች ያደርግ ዘንድ አይችልም፡፡ አብ በኔ ያደረብኝ እርሱ ሥራውን ይሠራል
እንጂ፡፡ (ዮሐ ፭ ፡፲፱ ፡፲፬ ፡፲)፡፡ ክርስቶስ በልባችን ካደረ እንደ በጎ ፈቃዱ እንድንወድም፤ እንድናደርግም፤ በኛ
ውሥጥ አድሮ ይሠራል፡፡ (ፊል ፪ ፡፲፫ )፡፡ እርሱ እንደሠራ እኛም እንሠራለን፡፡ ያነውን መንፈስም
እንገልጣለን፡፡ እንዲሁ እየወደድነው በርሱ እየኖርነ፤ በነገሩ ሁሉ በሆነው በክርስቶስ እናድጋለን፡፡ (ኤፌ ፬ ፡፭
)፡፡
እግዚአብሔር ለዓለሙ፤ የሕይወት፤ የብርሃን የደስታ፤ ምንጭ ነው፡፡ ፀዳለ ብርሃን ከፀሐይ እንደሚወጣ፤
ፈሳሽ ውኃም ሕይወት ካለው ምንጭ ፈልቆ እንደሚጎርፍ፤ በረከት ከእርሱ ወጥቶ፤ ለፍጥረቱ ሁሉ
ይጎርፋል፡፡ ለእግዚአብሔር ሕይወት ያሉበት፤ የሰው ልብ ሁሉ በፍቅርና በበረከት ለሌሎች ሰውች የሕይወት
ውኃ ያጎርፋል፡፡
የመድኃኔ ዓለም ደስታው፤ የወደቀውን ሰው ማንሣትና ማዳን ነበረ፡፡ ስለዚህ ሕይወትን እንደከበረ ነገር
አልቆጠረውም፡፡ ግን የመስቀልን ሕማም፤ መናቅን፤ ኃፍረትን ታሠ፡፡ እንዲሁ መላእክት ሌላዎችን ደስ
ለማሰኘት፤ ሁልጊዜ ይሠራሉ፡፡ ደስታቸው ይህ ነው፡፡ ኃጢአት የሌላቸውን የመላእክትን ሥራ፤ ራሱን ብቻ
የሚወድ የሰው ልብ ይንቀዋል፡፡ ለድሆችና ለተዋረዱ ሰዎች፤ በመዓርግም ዝቅ ላሉ ሁሉ ማገልገልን እንደ
ውርደት ይቆጥረዋል፡፡ ዳሩ ግን ይህ ሥራ ለመላእክት የከበረ ሥራቸው ነው፡፡ ወደ ሰማይ የሚገባ የክርስቶስ
ራሱን መሥዋዕት አድርጎ የመስጠት የፍቅር መንፈስ ነው፡፡ የክርስቶስ ተከታዮች የሚያገኙት መንፈስ
የሚያደርጉትም ሥራ ይህ ነው፡፡ የክርስቶስ መንፈስ እንደ ጣፋጭ መብል በልብ ሲገባ ሊሸሽግ አይችልም፡፡
በምናገኛቸው ሰዎች ዘንድ ሁሉ፤ ቅዱስ የሆነ ኃይሉ ይታወቃል፡፡ የክርስቶስ መንፈስ በሰው ልብ ውሥጥ
ሁሉን ለማለምለም ሊሞቱ የቀረቡትንም ቀልጥፈው ወደ ሕይወት ውኃ እንዲመጡ እያደረገ፤ በበረሀ
እንደሚደፍስ ውኃ ነው፡፡ የሱስን መውደድ የሚገለጥ፤ ስለ ሰው በረከትና ከፍታ እርሱ የሠራውን ሥራ
በመሥራት ነው፡፡ የሰማዩ አባታችን የሚያስብላቸውን ፍጥረቶች ሁሉ፤ እንድንወዳቸው፤ እንድንራራላቸው
ሲያዝኑም አብናቸው እንድናዝን፤ ወደ መልካም አሳብ ይመራናል፡፡ የመድኃኔ ዓለም ኑሮ በምድር ላይ
ራሱን ለማከበርና ስለ መቀደስ የተደረገ ገር ኑሮ አልነበረም፡፡ ግን የጠፋውን የሰው ወገን ስለማዳን፤
የማይደክም የእውነተኛ ጥረት ሥራውን በጠና ሠራ፡፡ ከበረከቱ ወይም ከጋጣው አንሥቶ እስከ ቀራንዮ
ድረስ ራስን የመካድ መንገድ ሔደ ከሚያስጨንቅ ሥራም ሊፈታ አልወደደም፤ የሚያሳምም ጣር የሞላበት
ኖሮ ኖረ፤ ፍጹም አሳብና ሥራም ነበረበት፡፡ እርሱ አለ፤ የሰው ልጅ ነፍሱን ለብ ዙዎች ቤዛ ሊሰጥና
ሊያገለግል እንጂ ሊያገለግሉት አልመጣም፡፡ (ማቴ ፳፡፳፰ )፡፡ በምድር ሳለ የሠራው ትልቁ ሥራው ይህ
ነበረ፡፡ ሌላው ሁሉ ሥራው ከዚህ ዝቅ ያለ ነበረ፡፡ የእርሱ መብሉና መጠጡ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ
ማድረግና ሥራውን መፈጸም ነበር፡፡ ራስንና የራን ጥቅም መውደድ በርሱ ሥራ ውስጥ ክፍል
አልነበረውም፡፡ እንዲሁ እነዚያ የክርስቶስ ጸጋ ተካፋዮች የሆኑት፤ ሌሎች ስለነዚያ ክርስቶስ የሞተላቸው፤
የሰማዩን ስጦታ ተካፋዮች ይሆኑ ዘንድ፤ በማናቸውም መሥዋዕት ሊያቀርቡ የተዘጋጁ ይሆናሉ፡፡ በዓለም
በመቀመጣቸው ዓለሙን የተሸለ ለማድረግ የሚቻላቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡ ይህ መንፈስ በውነት
የተመሰለችን ነፍስ ማደግ ያሳየናል፡፡ በየሱስ ክስቶስ እንዴት የከበረ ወዳጅ እንዳገኘ ለሌላዎች ይነግር ዘንድ፤
ፈቃድ ካለው ሰው በቀር እንዱን ስንኳ ወደ ክርስቶስ እንዲመጣ ሊያደርግ የሚችል የለም፡፡ የማዳንና
የመቀደስ እውነት በልቡ ውሥጥ ተዘግቶ ሊቀመጥ አይችልም፡፡ የክስቶስን ጽድቅ ከለበስነ፤ በውሥጥ
የሚያድረው መንፈስ፤ ደስታም በልባችን ከሞላብነ ዝም ልንል አንችልም፡፡ ጌታ ለኛ ቸር እንደሆነ
ከቀመስንና ካየነ የምንናገረው አንዳች ነገር አለነ፡፡ ፊልጶስ መድኃኔ ዓለምን ባገኘው ጊዜ እንዳደረገው፤
ሌሎችን ጠርተን ወደ ክርስቶስ ፊት እናቀርባለን፡፡ ወደ ክርስቶስ ልንስባቸው እንሻለን የማይታየውን
እውነተኛ ነገርም ስለሚመጣው ዓለም እንነግራቸዋለን፡፡ በዚያም የሱ በረገጠው መንገድ ለመሔድ፤
ፈቃዳችን በጣም የበረታ ይሆናል፡፡ በዙሪያችን ያሉትም የዓለሙን ኃጢአት የሚያስወግደው
የእግዚአብሔርን በግ ለማየት ይናፍቃሉ፡፡ ሌሎ ሰዎች እንዲባረኩ የምንጥረው ጥረት ተመልሶ ለራሳችን
በረከት ይሆናል፡፡ ከመዳን አሳብ ሥራ አንድ ክፍል ሥራ እንድንሠራ ያደረገነ የእግዚአብሔር አሳብ ምክንያቱ
ይሀ ነው፡፡ የመለኮትን ባሕርይ ተካፋይነት እግዚአብሔር ለሰዎች በሥልጣኑ ሰጥቶአቸዋል፡፡ እነዚያም
በራሳቸው የፈሰሰውን የእግዚአብሔርን መንፈስ በረከት፤ ለሌሎች ሰውች ሊያካፍሉ ይገባቸዋል፡፡ ይሀነንም
በረከት፤ እግዚአብሔር በሰው ላይ ማፍሰሱ ትልቅ ደስታና ክብ ነው፡፡ እነዚያ እንዲሁ የፍቅር ሥራ ተካፋዮች
የሆኑት ወደ ፈጣሪያቸው ይቀርባሉ፡፡ እግዚአብሔር የወንጌልን መልእክትና የፍቅርን ማገልገል ሁሉ ለሰማይ
መላእክት በሰጠ ነበር፡፡ አሳቡን ለመጨረስም ሌላ ነገር ባላደረገ ነበር፡፡ ግን ራሱን ብቻ ከማይወድ ማገልገል
የሚመጣውን በረከቱን፤ ደስታውን፤ መንፈሳዊ ከፍታውን፤ እንድነካፈል ከርሱ ከክርስቶስ፤ ከመላእክት
ጋራ ሠራተኞች ሊያደርገን በማያልቀው ፍቅሩ መረጠነ፡፡ በመከራው ባልንጀሮች በመሆናችን የክርስቶስን
ኃዘን እንካፈላለን፡፡ ለሌሎችም መልካም እንዲሆንላቸው ራነ ቁርባን አድርጎ የመስጠት ሥራ፤ የመስጠትን
ጥቅም በሰጩ ልብ ያበረታል፡፡ «በእርሱ ድኅነት እላንት ሀብታሞች እንድትሆኑ» ስለ እላንት ድኃ ከሆነው፤
ከዚያ ሀብታም ከነበረው፤ ከመድኃኔ ዓለም ጋራ በጣም አቅርቦ ይዛመደዋል፡፡ ያ ኑሮ ለኛ የተባረከ ኑሮ
የሚሆንልን የመለኮትን አሳብ፤ እንዲሁ በፍጥረታችን ስንፈጽም ብቻ ነው፡፡ ክርስቶስ የርሱን
ደቀመዛሙርት፤ ነፍሶችን ወደርሲ እንዲመልሱ እንዳዘዛቸው፤ ነፍሶችን ልትመልሱና ልትሠሩ ብትሔዱ
የጠለቀ ፈተና፤ ትልቅ መንፈሳዊ እውቀት እንዲያሻችሁ ይታወቃችኋል፡፡ ጽድቅም እንደ እንጀራና እንደ ውኃ
ይርባችኋል፤ ይጠማችኋል፡፡ ከእግዚአብሔር ጋራ ትነጋገራላችሁ፤ ሃይማኖታችሁም የበረታ ይሆናል፡፡
ነፍሳችሁም ትልቅ ከሆነ ከሕይወት ውሀ ትጠጣለች፤ የሚቋቋም ነገርና ፈተናም ወደ መጽሐፍ ቅዱስ
ይመራችኋል፡፡ ወደጸሎትም ይወስዳችኋል፡፡ በጸጋና ክርስቶስን በማወቅ ታድጋላችሁ፡፡ ብዙ የተፈተነ
እውቀትም ታገኛላችሁ፡፡ ራሱን ብቻ የሚወድ መንፈስ የሌለባት ሰው ሥራ፤ ሌሎችን ሰዎች በክርስቶስ
ፀንተው እንዲኖሩ ያደርጋቸዋል፡፡ ክርስቶስ የሚወደውን ፍቅርም ለባሕርያቸው ይሰጠዋል፡፡ መንፈሳዊነትም
ከፍ እያለ ይሔዳል፡፡ ለስንፍናና ራስን ብቻ ለመውደድ በዚያ ሰው ዘንድ ስፍራ የላቸውም፡፡
እሊያየክስቲያንን ጸጋ እየቀደመ የሚያሰፉ እግዚአብሔርን በማገልገል እየበረቱና እያደጉ ይሔዳሉ፡፡
መንፈሳዊ ዕውቀትም ያገኛሉ፡፡ የፀና የሚያድግ ሃይማኖትም በጸሎትም የበዛ ኃይል ያገኛሉ፡፡ ነፍስን
መንፈሳዊ ነገር ስለዳሰሳት የእግዚአብሔር መንፈስ መንፈሳቸውን እያንቀሳቀሰ ነፍስን ከእግዚአብሔር ጋር
የተቀደሰ መስማማት እንድታገኝ ይጠራታል፡፡ ነፍስም ምላሽ ትሰጣለች፡፡ ለሌላዎች መልካም
እንዲሆንላቸው እነዚያ ራን መውደድ በሌለበት ጠረት ራቸውን ለሌሎች እንዲበጅ ቀድሰው የሰጡ፤
ለራሳቸው መዳኛ እጅግ በውነት ይሠራሉ፡፡ በጸጋ የምናድግበት መንገድ ብቻ የራችነን ጥቅም ብቻ
ሳንፈልግ፤ ክርስቶስ በኛ ላይ የጣለውን ሥራ ማድረግ ነው፡፡ ሥራውን ለመዘርጋት እንደሚቻለነ መጠን
የኛን እዳታ ለሚፈልጉት መርዳት ይገበናል፡፡ ኃይል ሥራን በመልመድ ይገኛል፡፡ ሥራ ለሕይወት ዋና ነገር
ነው፡፡ ለክርስቶስ አንዳች ሥራ ሳይሠሩ ከጸጋው የሚመጣውን በረከት በመቀበል የክስቲያንን ሕይወት
ለማግኘት የሚጥሩ፤ ሳይደክሙና ሳይጥሩ በመብላት ሊኖሩ የሚፈትኑ ናቸው፡፡ በፍጥረተ ዓለም
እንደሚደረግ በመንፈሳዊ ዓለምም ይህ ሁሉ ጊዜ ውርደትና ጥፋት ያመጣል፡፡ የፍጥረትንም ባሕርይ
ይለውጣል፡፡ አካሎቹን ሥራ ለማልመድ እምቢ የሚል ሰው፤ በቶሎ ኃይል ያጣል፡፡ የክርስቶስ ቤተ ክስቲያን፤
ሰውን ስለማዳን እግዚአብሔር የሾመው ምስለኔ ነው፡፡ መልእክቱም ወንጌልን ወደ ዓለሙ ስለማድረስ
ነው፡፡ ይህም ለክርስቲያን የግድ ሥራው ነው፡፡ ሁሉ እያንዳንዱ፤ የመድኃኔ ዓለምን ሥራ ለመፈጸም
የተቀበለውን ለክሊተ ወርቅ ለማብዛትና ይህን የተመቸ ጊዜ በከንቱ አለማሳለፍ ይገባዋል፡፡ ለኛ የተገለጸውን
የክርስቶስን ፍቅር እርሱን ለማያውቁ ሰዎች የሰጠነው መብራት ለኛ ብቻ አይዶለም፤ ግን በሌሎች ሰዎች
ላይ ደግሞ ልናፈሰው ነው፡፡ የክርስቶስ ተከታዮች የሚገባቸውን ሥራ ለማድረግ ነቅተው ቢሆኑ፤ ዛሬ
የወንጌልን አዋጅ የሚነግር አንድ ሰው ባለበቱ፤ በአረመኔ አገር ሽህ ሰዎች በተገኙ ነበር፡፡ እነዚያም ራሳቸው
ሥራውን ሊወሩ የማይችሉና በገንዘባቸው፤ በማስተዛዘናቸው፤ በጸሎታቸው ሊረዱ ይችላሉ፡፡ ነፍሶችን ስለ
መመለስ በክርስቲያኖች አገር፤ በጣም የበለጠ ሥራ በተደረገ ነበር፡፡ ክርስቶስን ለማገልገል ወደ አረመኔዎች
አገር ለመሔድ፤ ወይም አገራችነን ጠባብ ዙሪያን ልንተወው አያሻነም፡፡ ክርስቶስን ለማገልገል ሥራችን
ባገራችን ቢሆን፤ በዚያው ባገራችን ዙሪያ፤ በቤተ ክርስቲያን አብረናቸው ከምንቀመጠው ሰዎች ጋራ፤
አብረናቸው ከምንሠራው ጋራ ልናደርገው እንችላለን፡፡ ከመድኃኔ ዓለም ኑሮ በምድር ሳለ የሚበልጠው
ክፍል በናዝሬት በነበረው ሐናፂ ቤት፤ በትዕግስሥት እየሠራ ያሳለፈው ኑሮው ነው፡፡ የሕይወት ጌታን፤
ከገበሬዎችና ከሠራተኞች ጋራ ጎድን ለጎድን ሲሔድ ሳለ፤ ሳይታወቅና ሳይከበር አገልጋዮች መላእክት ደጅ
ፀኑት፡፡ የታመመሙትን እየፈወሰ፤ ዓውሎ ነፋስ በነዳው በገሊላ ባሕር ላይ እየተመላለሰ፤ በትሕትና እየሠራ
መልእክቱን የታመነ ሁኖ ፈጸመ፡፡ እንዲሁ በትሑት ሥራ፤ በተዋረደ ኑሮ ከየሱስ ጋረ ልንመላለስና ልንሠራ
ይገባናል፡፡ ሐዋርያው አለ «ወንድሞቼ ሆይ ሁሉ እያንዳንዱ በእግዚአብሔር ዘንድ በተጸራበት ይቀመጥ»፡፡
(፩ ቆሮ ፯ ፡፳፬ )፡፡ ሠራተኛ ሰው የታመነ ስለ ሆነ፤ ጌታው በሚመሰገንበት መንገድ በሥራው ፊት ለፊት
እየመራ ይሔዳል፡፡ እውነተኛ የክርስቶስ ተከታይ ከሆነ በሚያደርገው ነገር ሁሉ ሃይማኖቱን ያሳያል፡፡
የክርስቶስንም መንፈስ ለሰዎች ይገልጻል፡፡ ባለመኪና በገሊላ ኮረፍቶች መሀከል፤ በተዋረደ የኑሮ መንገድ
በሠራው በየሱስ ፊት፤ የተጋና የታመነ ምስለኔ ይሆናል የክርስቶስን ስም የሚጠራ ሁሉ፤ እንዲሁ ሊሠራ
ይገባዋል፡፡ ሌሎች ሰዎች የርሱን መልካም ሥራ በማየት እየተመሩ፤ እርሱን ተከትለው እንዲሔዱ፤
ፈጣሪያቸውንና አዳኛቸውን እንዲያመሰግኑ ምሳሌ ይሆናል፡፡ ብዙዎች ለክርስቶስ ሥራ ስጦታቸውን
እንዳይሰጡ ለራሳቸው ምክንያት አብጅተዋል፡፡ ሌሎች የዋነኝነትንና የመሠልጠንን ሥራ፤ የቤተ ክርስቲያንን
አለቅነት ስላገኙ፡፡ እሊያ በተለየ (የመክሊት) ገንዘብ ያላቸው ብቻ፤ የሚቻለውን ነገር የተቀደሰ አድርገው
ለእግዚአብሔር ሥራ እንዲሰጡ አሳቡ አቸንፎአል፡፡ እሊህ (መክሊቶች) ወርቆች፤ የድካሙን ዋጋ ሊካፈሉ
ያልተጠሩትን ከልክሎ፤ በተለየ ሞገስ ላገኙት ሰውች የተሰጡ ይመስላቸዋል፡፡ ግን ወንጌሉ በምሳሌው የቤቱ
ባለቤት ሎሌዎቹን በጠራ ጊዜ፤ ለሁሉ እነያንዳንዱ እንደ ሥራው መጠን ሰጠው ይላል እንጂ፤ እንዲህ
አይልም፡፡ ባለንበት ዘመን ሁሉ፤ የሚገባነን ሥራችንነን በፍቅር መንፈስ ለጌታቸን እንሠራለን፡፡ (ቆላ፫ ፡፳፫
)፡፡ የእግዚአብሔር ፍቅር በልብ መኖሩ በሰውየው ኑሮ ይታወቃል፡፡ ያማረ የክርስቶስ ሽታ ይከበናል፡፡
ኃይላችንም በዙሪያችን ከፍ ያለና የተባረከ ይሆናል፡፡ ወደ ክርስቶስ ሥራ ለመሔድ፤ ትልቅ ችሎታና በጣም
የተመቸ ጊዜ እስክታገኝ አትቆይ፡፡ ይህ ዓለም ምን ይለኝ ይሆን ብለህ አታስብ፡፡ የዕለት የዕለቱ ኑሮህ
ለሃይማኖትህ ንጽሕናና መታመን ምስክር ከሆነ ሌሎች ሰዎችም ልትጠቅማቸው መውደድህ በውነት
በልባቸው ከታወቃቸው፤ ጥረትህ ጨርሶ አይጠፋም፡፡ በጣም የተዋረደውን ምስኪን የሆነው የየሱስ ደቀ
መዝሙር፤ ለሌሎች ሰውች በረከት ይሆናል፡፡ ዬሱስ ደቀ መዛሙርት አንዳች ታላቅ ነገር በማድረጋቸው
አይቃወቃቸውም፡፡ ግን እነዚያ በማያውቁት ኃይላቸው፤ የበረከት ማዕበልያስነሳሉ፡፡ የዚያን በረከት ስፋትና
ጥልቀት፤ ከዚያም የሚገኘውን በጎ ነገር እስከ መጨረሻው የዋጋ መቀበያ ቀን ድረስ አያውቁትም፡፡ አንዳች
ትልቅ ነገር ሲያደርጉ አይታወቃቸውም፡፡ ወይም አይሰማቸውም፡፡ ሥራቸው እንዲከናወነወንላቸው፤
ራቸውን ሊያደክሙ አልታዘዙም ነበር፡፡ ብቻ እግዚአብሔር ያመለከታቸውንና፤ ያዘጋጀውን ነገር እየሠሩ
ዝም ብለው በሃይማኖት ወደፊት መሔድ አለባቸው፡፡ ይህን ካደረጉ፤ ሕይወታቸው ከንቱ አይሆንም፡፡ በዚህ
ዓለም ኑሮ ከርሱ፤ ከክርስቶስ ጋራ አብረው ሠራተኞች ናቸው፡፡ ከፍ ላለው ጨለማ ለሌለበት ሥራ
ለሚመጣው ሕይወት የተገቡ ናቸው፡፡
Previous
Next
እግዚአብሔር ራሱን ለኛ ለማታወቂያና ከርሱ ጋራ እኛን አንድ ለማድረግ የሚሻቸውን መንገዶች ብዙዎች
ናቸው፡፡ ለተከፈተ ልብ፤ በእግዚአብሔር እጅ ሥራ እንደ ተገለጸ የእግዚአብሔር ፍቅርና ክብር ይታወቃል፡፡
አድማጭ ጆሮ የተፈጠረውን ፍጥረት በመስማትና በማድመፅ ከእግዚአብሔር ጋራ አንድ መሆንን ሊሰማና
ሊያስተውል ይችላል፡፡ የለመለሙት መስኮች ረጅሞች ዛፎች፤ ቡቃያዎች፤ አበባዎች የሚያልፉት ደመናዎች፤
የሚዘንሙት ዝናሞች፤ ፈሳሾ ውኆች፤ የሰማዮች ክብር ለልቦቻችን ይነግሩዋቸዋል፡፡ እሊህን ሁሉ ከፈጠረ
ጋራ ለማስተዋወቅ እኛንም የጠሩናል፡፡
መድኃኔ ዓለም የከበረውን ትምሕርቱን በፈጠረው ፍጥረት አሠረ፡፡ ዛፎቹ፤ ዖፎቹ በቆላ ያሉት አበቦች፤ ኮረብታዎች፤
ባሕሮች፤ ኩሬዎች፤ የሚያምሩት ሰማዮች፤ ከበውነ ያሉት በእግዚአብሔር ቃል የተፈጠሩት ፍጥረቶች ሁሉ እንዲሁ
የእግዚአብሔር ሥራ ትምህርት በአእምሮዋችን እንዲታሰብ ከቶውንም ስለሕይወታቸው ለመጣር የሥራ አሳብ
ባለባቸው ሰዎች መሀከል እንዲታወቅ በውነቱ ቃል ተቆራኝቶአል፡፡ እግዚአብሔር ምድራዊ ቤታችነን ጸጥ ባለ ውበት
ያስጌጠበትን ሥራውን ልጆቹ ያመሰግኑለት ዘንድ ይወዳል፤ ደስም ይለዋል፡፡ እርሱ ያማረ ነገር ወዳጅ ነው፡፡ በውጭ
ከሚታየው ነገር ሁሉ በላይ ያማረ ባሕርይን፤ ንጽሕናን፤ ገርነትን ጸጥ ያለ ያበባዎችን ሞገሥ ልናገኝ ይወዳል፡፡ ብቻ
እግዚአብሔር የፈጠረውን ሥራ ብናዳምጥ፤ የከበረ የፈቃደኝነትና የመታመን ትምሕርት ያስተምረናል፡፡ ደግሞ
ከከዋብት እንማራለን፤ ኮቲ ወይም ፍለጋ በሌላው መንገዳቸው በሚያልፉበት ስፍራ ይታወቃል፡፡ ይህም ከትውልድ
እንከ ትውልድ የተመለከተው መንገዳቸው፤ እየተመለከተ መጥቶአል፡፡ በጣም ትንሽ እስከሆነው ፍጥረት ድረስ
ለፈጣሪ ፈቃድ ይታዘዛል፡፡ እግዚአብሔር ለሁሉ ያስባል፡፡ የፈጠረውን ሁሉ ይመግባል፡፡ እርሱ በማይሰፈር ኃይሉ፤
ቁጥር የሌላቸውን ዓለሞች የሚይዝ ሁሉን ይረዳል፡፡ በዚያን ጊዜም ያለ ፍርሃት ትሑት ዜማውን የሚያዜመው ትንሹ
ጉራማይሌ ዖፍ ለሚሻው ነገር ያስባል፡፡ ሰዎች ለዕለቱ ሥራቸው ወጥተው ወደ ውቭ ሲሔዱ፤ ሲጸልዩም፤ በሌሊትም
ተኝተው ሳሉ፤ ጥዋትም ሲነሡ ሀብታሙ ሰውም ሲበላ ሲጠጣ ድሀውም ሰው በትንሹ ገበታው ዙሪያ ልጆቹን
ሲሰበስብ፤ ይህ ሁሉ እያንዳንዱ በርኅራኄ በሰማያዊው አባት ዘንድ ተጠብቆአል፡፡ እግዚአብሔር የማያውቀው እንባ
የለም፡፡ እግዚአብሔር የማያውቀው ሳቅም የለም፡፡ ይህም ሁሉ በሙሉው ብናምን የማየገባ አሳብ ሁሉ ከኛ ይርቃል፡፡
ሕይወታችንም እንዳሁኑ ተስፋ መቁረጥ አይሞላበትም፤ ነገርን ሁሉ፤ ትንሽም ቢሆን ትልቅም ቢሆን ለእግዚአብሔር
እጅ መስጠት ይገባናል፡፡ ለርሱ ከብዙ አሳብና ከሚዛኑ ብዛት የተነሣ ለማይቸግረውና ለማይከብደው፡፡ ከዚያ ቀጥለን
ብዙዎች ሰዎች እንግዶች ሆነው ከረጅም ዘመን ጀምረው ያላገኙትን የነፍስ ዕረፍት በማገኘት ደስ ይለናል፡፡ ሳቢ በሆነ
ምድራዊ ፍቅር አእምሮህ ደስ እንደሚለው፤ የኃጢአት በሽታና ሞት የሌለበትን የተፈጠረው ፍጥረት መልክም፤
የእርግማንን ጥላ ዳግመኛ የማይለስበትን የሚመጣውን ዓለም አስብ፡፡ በአሳብህ ሥዕል የምታየውን የዳኑትን ሰውች
ቤት ትተህ ብርሃን የሆነው አሳብህ የሚሥለው ይልቅ፤ በጣም የከበረውን ቤት አስብ፡፡ በእግዚአብሔር ልዩ ስጦታ፤
በተፈጠሩት ፍጥረቶች ከክብሩ ብልጭታ ትንሽ እናያለን፡፡ «እግዚአብሔር ለወዳጆቹ ያዘጋጀው፤ ዓይን ያላየው፤ ጀሮ
ያልሰማው፤ በሰው ልብ ያልተሰበ» መሆኑ ተጽፎአል፡፡ (፩ ቆሮ ፪ ፡፱ )፡፡ ባለ ቅኔውችና የፍጥረቶችን ነገር የተማሩት
የሚሉት ብዙ ነገር አላቸው፡፡ ክርስቲያን ግን የምድርን ማማር፤ የሰማያዊ አባቱን እጅ ሠራ እያሰበበ የእግዚአብሔርን
ፍቅር በአበቦች፤ በአታክልት፤ በዛፎች አስተውሎ ከፍ ያለ ምስጋና ለእግዚአብሔር እየሰጠ ደስ ይለዋል፡፡ በተራሮችና
በወንዞች፤ በባሕሮች ያሉት ምልክቶች እግዚአብሔር ሰውን እንደወደደው ለማስታወቅ እንደተፈጠሩ አውቆ
ከሚመለከታቸው በቀር ለእግዚአብሔር ምስጋና ሊሰጥ የሚችል ስንኳ የለም፡፡ እግዚአብሔር በተከናወነ ሥራው
በልባችን የሚያድረው በመንፈሱ ኃይል ከኛ ጋራ ይነጋገራል፡፡ በዙሪያችን ያለውን ነገር ሁሉ፤ በየቀኑ የሚሆነውን
መለወጥ ሁሉ ልባችን ያስተውለው ዘንድ ቢከፍት፤ የከበረ ትምህርት ባገኘነ ነበር፡፡ ባለመዝሙሩ ዳዊት አስቀድሞ
የተዘጋጀውን የእግዚአብሔር ሥራ ተከትሎ ይላል፤ ምድር ከእግዚአብሔር ዘንድ ከመጣው በጉነት ሞልታለች፡፡ (መዝ
፴፫ ፡፭ )፡፡ አዋቂ የሆነ ይህነን ይጠብቅ የእግዚአብሔርንም ምሕረት ያስተውላል፡፡ (መዝ ፻፯ ፡ ፵፫ )፡፡ እግዚአብሔር
ባሕርዩም መገለጽ፤ ከሰው ጋራ የሚሠራው ሥራው፤ ትልቁ የማዳን ሥራው በዚያ እንዳለ በቃሉ ይነግረናል፡፡ የአባቶች፤
የነቢያት፤ የሌሎች የቀደሙት ቅዱሳን ሰዎች ታሪክ ይኸው በፊታችን ተገልጾአል፡፡ እነዚያም በድካም የተካከሉነ
ከሕማም በታች የሆኑ እንደኛ ሰዎች ነበሩ፡፡ (ያዕ ፭ ፡፲፯ )፡፡ ከፍርሃት የተነሣ ከፈተና በታች እንደኛ እየተጣጣሩ፤
እንደወደቁ እናለን፡፡ ከዚህም ጋራ እንደገና ዳግመኛ ልብ እንዳደረጉ፤ በእግዚአብሔር ጸጋም ድል እንደነሱ እናውቃለን፡፡
እኛም ይህን አይተን በጥረታችን ጽድቅን ለማገኘት ተደፋፈርነ፡፡ ስለ ተሰጣቸው የከበረ ፈተና፤ ስለ ብሃንና ስለ ፍቅር
ደስ ይላቸው ዘንድ ስላገኙት በረከት፤ በተሰጣቸው ጸጋም ስለ ሠሩት ሥራ ስናስብ፤ እነዚያን ምንፈሳውያን ያደረጋቸው
መንፈስ፤ የተቀደሰ የቅናት ነበልባል በልባችን ውስጥ ያቃጥላል፡፡ እንደነዚያ ከእግዚአብሔር ጋራ እንድንሔድ፤ በባሕርይ
እንደነዚያ ለመሆን እንድንወድ ያደርገናል፡፡ የሱስ ስለ ብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ተናገረ፡፡ ይልቅስ ስለ ሐዲስ ኪዳን
በውነት እንዴት ብዙ ይናገር፡፡ «እነርሳቸውም ስነለኔ የሚመሰክሩ ናቸው»፡፡ ይላል፡፡ (ዮሐ ፭ ፡፴፱ )፡፡ የዘለዓለም
ሕይወት ተስፋችን የሚገኝበት አዳኛችን እርሱ ነው፡፡ አዎን ቅዱሳት መጸሕፍት ሁሉ ከኦሪት ዘፍጥረት ጀምረው ስለ
ክርስቶስ ይናገራሉ፡፡ ከተደረገው ሁሉ ያለርሱ የተደረገ አልነበረምና፡፡ (ዮሐ ፩ ፡፫ )፡፡ ለመጨረሻው ቃል ኪዳን «እነሆ
ቀልጥፌ እመጣለሁ» ይላል (ራእይ ፳፪ ፡፲፪ )፡፡ እኛ ስለርሱ ሥራ ማንበብ ይዘናል፡፡ ድምጹንም ማድመጥ ይዘናል፡፡
ከመድኃኔ ዓለም ጋራ እንድ ልትሆኑ ብትወዱ ቅዱሳት መጻሕፍትን ተማሩ፡፡ ልባችሁን ሁሉ በእግዚአብሔር ቃል
ሙሉት፡፡ የሚቃጠለውን ጥማታችሁን የሚያጠፋው የሕይወት ውኃ እርሱ ነውና፡፡ ከሰማይ የወረደው የሕይወት
እንጀራ እርሱ ነውና፡፡ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ ሕይወት የላችሁም ብሎ የሱስ ነግሮናል፡፡
«እኔ የምነግራችሁ ነገር መንፈስ ነው፤ ሕይወትም ነው» ፣ በማለቱ እርሱ ራሱ ይተረጉማል፡፡ (ዮሐ ፮ ፡፶፫ ፡፺፫ )፡፡
አካሎቻችን በምንበላውና በምንጠጣው ነገር ተሰርተዋል፤ ሥጋዊ አካላችን ምግብ እንደሚፈልግ እንዲሁ መንፈሳዊ
አካላችንም ምግብ ይፈልጋል፡፡ ለመንፈሳዊ ባሕርያችን ኃይልን ብርታትን የሚሰጠውን ነገር እናስባለን፡፡ መላእክት
ሊዘምሩት የሚወዱት የማዳን ዜማ አንዱ እርሱ ነው፡፡ የዳኑት ማስተዋልና ዜማ፤ ማለቂያ በሌለው የዘለዓለም
ቅውልድ ይሆናል፡፡ ጥንቁቅ ለሆነ ኣብና ትምህርት፤ ጊዜው አሁን አይዶለምን፡፡ ዬሱስ ክርስቶስ ማለቂያ የሌለው
ምሕረትና ፍቅር ስለኛ የተደረገው መሥዋዕት፤ ስለ ዋናው አምልኮና ብርሃን ይጠራል፡፡ በተወደደው አዳኛችንና
አስታራቂያችን ባሕርይ መኖር ይገባናል፡፡ ወገኖቹን ከኃጢአታቸውን ሊያድን የመጣውን ዬሱስን መልእክት ማሰብ
ይገባላል፡፡ እንዲሁ ሰማያዊዉን ዜማ ስልመለክት ሃይማኖታችን፤ ፍቅራችን እየበረታ ይሔዳል፡፡ ጸሎታችን
ከሃይማኖትና ከፍቅር ጋራ በጣም የተደባለቀ ስለሆነ፤ እግዚአብሔር ይቀ በለዋል፡፡ ጸሎታችንም መንፈሳዊ ቅናትና
ዕውቀት ያለበት ይሆናል፡፡ በየሱስ ኃይል እስከ ምድር ዳርቻ ያሉትን ሁሉ፤ በርሱም ወደ እግዚአብሔር የመጡትን ሁሉ
ለማዳን በየሱስ የጸና መታመን፤ በየቀኑ ሕይወት ያለው ዕውቀት ይሆንልናል፡፡ የመድኃኔ ዓለምን ፍጹምነትን ስናስብ
እንደርሱ ያለ የንጽሕና መልክ ልናገኝ፤ ልንለወጥና በርሱ መልክ ልንታደስ እንወዳለን እንደርሱ እንደምናመልከው
እንደፈጣሪያችን ለመሆን ነፍሳችን የተራበችና የተጠማች ትሆናለች፡፡ ስለ ክርስቶስ አብዝተን ለሌላዎች ስንናገር፤
ለዓለሙም ስናስታውቀው አሳባችን በጣም በክርስቶስ ላይ ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ተማሩ ሰዎች ብቻ
አልተጻፈም፡፡ ግን ለማንሙ ሕዝብ ደግሞ ተጽፎአል፡፡ ስለማዳን የሚፈልጉት ትልቆች እውነተኞች ነገሮች፤ እንደ እኩል
ቀን የተገለጡ ሁነዋል በተገለጠው በእግዚአብሔር መንገድ ያለ ችግር በመሔድ ፈንታ በራሳቸው መንገድ ለመሔድ
የራሳቸውን ፈቃድ ከሚከተሉ ሰዎች በቀር፤ የቅዱሳት መጻሕፍትን መንገድ የሚያስትና የሚያጠፋ የለም፡፡
የማናቸውንም ሰው ምስክርነት እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ቃል አድርገን ልንቀበለው አይገባነም፡፡ ግን የእግዚአብሔርን ቃል
ለራሳችን መማር ይገባናል፡፡ ሌላዎችን ሰዎች ለኛ እንደሚመስለን አድርጉ ብንላቸው፤ ያነከሰና የማይስማማ ኃይል
ያለነ እንሆናልን የከበረው የአእምሮ ኃይል በማጣት፤ እንደ ድንክ አጭር ይሆናል፡፡ ሰው የመጽሐፍ ቅዱስን ዋና ነገር
ፍለጋውን ተከትሎ መጸሕፍትን ለመጻሕፍት ጋራ፤ መንፈሳዊ ነገርንም፤ ከመንፈሳዊ ነገር ጋራ እያስታያየ ቢሠራ፤
አእምሮው ይሰፋል፡፡ ዕውቀትን ለማበርታት መጽሀፍ ቅዱስን ከመማር በቀር ሌላ የሚበልጥ ነገር የለም፡፡ ከፍ
ከሚያደርግ ሰፊ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት በቀር፤ አሳብን ከፍ ለማድረግ ሌላ የበረታ ኃይል እንዲሁ ሌላ ትልቅ
መጽሐፍ የለም፡፡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሚገባ ሁኖ ተጠንቶ፤ ወይም ታውቆ ቢሆን ሰዎች የአእምሮ ስፋት፤ የጠባይ
ጥልቀትና፤ የፀና አሳብ ባገኙ ነበር፡፡ በዚህ ወራት ጥቂት ሁኖ የሚታየው ዕውቀትም በበዛ ነበር፡፡ ግን መጽሐፍ ቅዱስ
በችኮላ በማንበብ የሚገኘውን ጥቅም ጥቂት ነው፡፡ አንዱ መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ እስከ መጨረሻው ዘልቆት
ይሆናል፡፡ ከዚሁም ጋራ ውበቱን ለማየት ወይም የጠለቀውንና የተሰወረውን ትርጓሜ ለማገኘት ይቸግረው ይሆናል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ የሚያመለክተነው ነገር ለአእምሮ የተገለጠ እስኪሆን ድረስ፤ ከእርሱም የተገኘው ዕውቀት ለማዳን
አሳብ የተገ ለጠ እስኪሆን ድረስ፤ የተናጠ አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ አምድ ወይም ገጽ ከቶውንም በጥንቃቄ ከተነበበ
ከብዙ ምዕራፍ ይልቅ ብዙ የከበረና የተሻለ እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስህን ካንተ አትለይ፡፡ ጊዜ ካገኘህ
አንብበው፡፡ ጥቅሱንና ዋናውን ነገር በልብህ አኑረው፡፡ ከቶውንም በመንገድ ስትሔድ እንዳትረሳው ጥቂት ክፍል
ልታነብ ትችላለህ፡፡ እንዲሁ በአእምሮህ አጥተኸው ታስበዋለህ፡፡ በጣም የጠለቀ አሳብና ጸሎት ከሌለነ፤ ጥበብን ልናገኝ
አንችልም፡፡ አንዳንድ የመጽሐድ ቅዱስ ክፍሎች ሊያስተውሏቸው የማያስቸግሩ ገሮች ናቸው፡፡ ግን ያንዳንዱ ክፍሎች
ትርጓሜ ለማስተዋል በቶሎ ብልጭ ብሎ አይታይም፡፡ መጻሕፍት ቅዱሳትን ከመጻሕፍት ቅዱሳት ጋር ማስተያት
ይገባል እንዲህ ያለው ትምህርት ተመልሶ ይጠናል፡፡ በጥንቃቄ እየደጋገሙ መመርመር ይገባል፡፡ በፊት ያነበቡትን
ክፍል ደግሞ ወደኋላ ተመልሶ በጸሎት ማንበብ ይገባል፡፡ እንዲህ አድርጎ ያጠኑት ትምህርት ይጠቅማል፡፡ በምድር
ውስጥ የተሠወሩትን የወርቅ ሚትቃሎች ሥር ወርቅ አውጭ እንደሚያወጣ፤ እንዲሁ የእግዚአብሔርን ቃል ሁልጊዜ
እንደራሱ ገንዘብ አድርጎ የሚፈልግ ያነን ዋጋው የከበረ እውነት አሳብ ከሌላቸው ፈላጎች የተሠወረውን ያገኛል፡፡ ከልብ
የተመዘኑ መንፈሳውያን ቃሎች ከሕይወት ምንጭ ፈልቆ እንደሚመነጭ ምንጭ ወይም ፈሳሽ ውኃ ይሆናሉ፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ያለጸሎት አይጠናም፡፡ ገጹን ከመግለጽ በፊት መንፈስ ቅዱ እንዲገልጽልን መለመን ይገባናል፡፡
የለመነውንም እናገኛለን፡፡ ናትናኤል ወደርሱ በመጣ ጊዜ መድኃኔ ዓለም እንዲህ ሲል ጮኸ፤ «እነሆ የእስራኤል ወገን
ሰው በውነት ተንኮል የሌለበት»፡፡ «ናትናኤልም አለው ከወዴት ታውቀኛለህ»፡፡ የሱስም መለሰ አለውም፤ ፊልጶስ
ሳይጠራህ በበልስ በታች አየሁህ፡፡ (ዮሐ ፩ ፡፵፯ ፡፵፰ )፡፡ እውነት ምን እንደሆነ ለማወቅ ብርሃን ለማገኘት ብንለምነው፤
የሱስ እንዲሁ በተሠወረ የጸሎት ቦታ ያየናል፡፡ ብርሃን በሞላበት ዓለም የሚኖሩ መላእክት፤ በትሑት ልብ መንፈስ ቅዱ
ወደመራቸው ከሚሔዱት ሰዎች ጋራ አብረው ይሆናሉ፡፡ መንፈስ ቅዱስ መድኃኔ ዓለምን ከፍ ያደርገዋል፤
ያከብረውማል፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ሥራው፤ በክርስቶስ ፈንታ ሆኖ ሥራ መሥራት፤ የክርስቶስ ጽድቅ፤ ንጽሕና፤
በከርስቶስ የምናገኘውን ትልቁን ማዳን ማስታወቅ ነው፡፡ የሱስም አለ፤ «ያም ከኔ ይወስዳል፤ ይነግራችሁማል»፡፡ (ዮሐ
፲፮ ፡፲፬ )፡፡ አምላካዊ እውነት ፍሬ ያለው መምህር፤ የእውነት መንፈስ ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔር የሰውን ወገን ብዙ
ስላከበረው፤ አንዱን ልጁን ስለነርሳቸው ሊሞት አሳልፎ ሰጠው፡፡ መንፈሱንም የሰው አስተማሪና የዘለዓለም መሪ
ሊሆን ሾመው፡፡
በተፈጠረው ፍጥረትና በሚታይ ነገር ሁሉ እርሱ ባዘጋጀው ነገር በመንፈሱ ኃይል እግዚአብሔር ይነግረናል፡፡
ግን እሊህ አይበቁነም፡፡ የልባችነን አሳብ ወደርሱ ልናፈስ ይገባናል፡፡ መንፈሳዊ ኃይል፤ መንፈሳዊ ኑሮ
ለማግኘት ከሰማያዊ አባታችን ጋራ አንድነት ማግኘት ይገባናል፡፡ አሳባችን ወደርሱ ተስቦ ይሆናል፡፡
የእርሱንም ሥራ ምሕረቱንም በረከቱንም እናስብ ይሆናል፡፡ ግን ይህ በሙሉ ዕውቀት ከእርሱ ጋራ
መገናኘት አይደለም፡፡ ከእግዚአብሔር ጋራ አንድ ለመሆን ስለ እውነቱ ኑሮአችን አንዳች ነገር ልንነግረው
ይገባናል፡፡
ጸሎት ማለት በልብ ያለውንነገር ላንድ ወዳጅ እንደምንገልጠው ለእግዚአብሔር መግለጥ ነው፡፡ እኛ ምን እንደ ሆነ
እግዚአብሔር እንዲያውቅ አይደለም፡፡ ግን እርሱን እንቀበለው ዘንድ እንድንችል እንዲያደርገን ነው፡፡ ጸሎት
እግዚአብሔር ወደኛ አያወርደውም፡፡ ግን እኛን ወደርሱ ያወጣናል፡፡ የሱስ በምድር ሳለ ደቀ መዛሙርቱን እንዴት
እንደጸልዩ አስተማራቸው፡፡ ለዕለቱ የሚሹትን ነገር ለእግዚአብሔር እንዲያስታውቁ አሳባቸውን ሁሉም በእርሱ ላይ
እንዲጥሉ መራቸው፡፡ ልመናቸውን እንዲሰማ እርግጥ መሆኑን ለነዚያ እንዳስታወቃቸው ይህም ለኛ የታወቀ እርግጥ
ነገር ነው፡፡ የሱስ ራሱ በሰዎች መሀከል ሲኖር ሳለ ሁልጊዜ ይጸልይ ነበር፡፡ አዳኛችን የሱስ እኛ በምንሻው ነገርና
በድካማችን ሊረዳን ከኃጢአት በቀር ራሱን እንደኛ አደረገ፡፡ ስለዚህም በሚገባው ከኃጢአት በቀር ራሱን እንደኛ
አደረገ፡፡ ስለዚህም በሚገባው ሥራውና በመከራው የታሠረ ለመሆን ከአባቱ ዘንድ አዲስ ኃይል ለማግኘት ለመነ፡፡
እርሱ በነገሩ ሁሉ ለኛ ምሳሌያችን ነው፡፡ በድካማችን እርሱ ወንድማችን ነው፡፡ ከኃጢአት በቀር እንደኛ በሁሉ ተፈተነ፡፡
ባሕርዩ ከክፉ ሽሽቶ ወደኋላ ተመለሰ፡፡ እርሱ በዚህ ኃጢአተኛ ዓለም መከራንና ሥቃይን በትዕግሥት ተቀበለ፡፡
በሰውነቱ ጸሎትን በሚገባ ዋና ነገር አድርጎ ያዘ፡፡ ከአባቱ ጋራ በጸሎት በመገናኘቱ መጽናናትና ደስታ አገኘ፡፡
ለእግዚአብሔር ልጅ ለመድኃኔ ዓለም ጸሎት የሚያሻ ዋና ነገር መሆኑ ከታወቀው ይልቁን ኃጢአት ለሞላበት ለሙዋች
ሰው ምን ያህል ብዙ የተቃጠለ የጸና ጸሎት እንዲያስፈልገው ይታወቀው ይሆን፡፡ የሰማዩ አባታችን የበረከቱን ምላት
በኛ ላይ ሊያፈስ ሲጠብቅ ይቄያል፡፡ ወሰን ከሌለው የፍቅር ምንጭ በብዙው ልንጠጣ ይገባናል፡፡ ጸሎታችን ጥቂት
መሆኑ እጅግ ይገርማል፡፡ ራሳቸውን በጣም ያዋረዱትን የቀናውን የልጆቹን ጸሎት ለመስማት እግዚአብሔር የተዘጋጀ
ነው፡፡ ገናም የምንሻውን ለእግዚአብሔር እናስታውቅ እምቢ ማለታችን የተገለጸ ነው፡፡ መጨረሻ የሌለው
የእግዚአብሐር የልብ ፍቅር ለድኆች በራሳቸው ረድኤት ለሌላቸው ከፈተና በታች ላሉ ለሰው ፍጥረቶች ሲያዝንላቸው
እለዚያ ከሚለምኑትም አብልጦ ሊሰጣቸው የተዘጋጀ ሲሆን ገናም የእነዚያ ለመናቸው ጥቂት ሲሆን የሰማይ መላእክት
ምን ይመስላቸው ይሆን? መላእክት ለእግዚአብሔር ሊሰግዱ ይወዳሉ፤ በእርሱ አጠገብ ሊሆኑ ይወዳሉ፡፡
ከእግዚአብሐር ጋራ አብሮ መኖርን እንደ ትልቅ ደስታ ይቆጥሩታል፡፡ እግዚአብሔር ብቻ ሊሰጠው የሚችለው እርዳታ
የሚያሻቸው የምድር ልጆች የመንፈሱን ብርሃን ሳያገኙ ፤ የርሱን ባልንጀርነትም ሳያገኙ እንዲያው ሲመላለሱ ደስ
ያላቸው ይመስላሉ ፤ ያለ መንፈሱ ብርሃን ሲሔዱ፡፡ እሊያን ይጸልዩ ዘንድ ችላ የሚሉትን የዚ የክፉው ጨለማ
ይሸፍናቸዋል፡፡ ጠላት በጀሮዋቸው አሾክሹኮ የነገራቸው ፈተና ወደ ኃጢአት ያጸምዳቸዋል፡፡ ይህ ሁሉም የሆነ
እግዚአብሔር የሰጣቸውን የመለኮታዊ ጸሎት ኃይል ቁም ነገር አላደረጉትምና ነው፤ ጸሎት በሃይማኖት እጅ ወሰን
የሌለው የእርዳታ ምንጭ የተሰበሰበበትን የሰማይ ዕቃ ቤት መዝጊያ የሚከፍት ሲሆን የእግዚአብሔር ወንዶችና ሴቶች
ልጆች ስለምንድር ሊጸልዩ እምቢ ይላሉ፡፡ የማያቋርጥ ትጋትና ጸሎት አሳብም የሌለነ መሆናችን በውነት ነገር
ማደጋችነንና የቀናውን መንገዳችነን ትተን ከመሔድ የሚያደርስ እጅግ የሚያስፈራ ነገር ነው፡፡ በብዙ ልመናና
ሃይማኖት ፈተናን ለማቋቋም ጸጋና ኃይል እንዳናገኝ ጠላታችን ወደ ምሕረቱ ዙፋን በሚወስደው መንገድ እንዳንሔድ
ይከለክለናል፡፡ እግዚአብሔር ጸሎታችነን ሰምቶ ምላሽ ይሰጠናል ብለን ተስፋ የምናደርግበት አንድ ነገር አለ፡፡ ከዚህም
አንዱ ከእርሱ እርዳታ የምንሻ ደካሞች መሆናችንን ማወቅ ነው፡፡ እርሱን ቃል ኪዳን ሰጥቶናል እንዲህ ሲል ፤ «በተጸማ
ላይ ውኃ አፈሳለሁ በደረቅ ምድርም ፈሳሽ ውኃ አጐርፋለሁ» (ኢሳ. ፵፬፡፫፡፡) እሊያጽድቅ እንደ እንጀራ የሚገባቸው
እንደ ውኃም የሚጠማቸው እንዲጸግቡ በውነት ይወቁ፡፡ የሰው ልብ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንደያድርበት መክፈት
ይገባዋል፡፡ ያለዚያስ የእግዚአብሔርን መንፈስ ሊቀበል አይሆንለትም፡፡ ያ እኛ የምንሻው ትልቅ ነገር እርሱ ራሱ
ምክንያቱን ይነግረናል፡፡ እንደ ነገር አዋቂ ጠበቃ ሁኖ ስለኛ ይሞአገታል፡፡ ግን እሊህን ነገሮች እግዚአብሔር ለኛ
እንዲያደርግ መለመን ይገባዋል፡፡ እርሱ ብሎአልና ለምኑ ይሰጣችኋል፡፡ ያለልጁ ስለሁላችን አሳልፎ የሰጠው እንጂ
ያልራራለት ከርሱ ጋራ በከንቱ ሁሉን እንዴት አይሰጠን? (ማቴ፡ ፯ ፯፡ ሮሜ ፰፡ ፴፪፡፡) በልባችን ክፉ ነገር ብናኖር
ወደማናቸውም ወደ ታወቀ ኃጢአት ብንጠጋ ጌታ አይሰማንም ፤ ግን የተጸጸተን የልብ ቅን ጸሎት ሁልጊዜ
እግዚአብሔር ይቀበላታል፡፡ ጠማማው ሁሉ ነገራችን ሲቀና እግዚአብሔር ለልመናችን ምላሽ እንዲሰጠን እና ምናለን
የኛው ምግባር በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስ ለማግኘትና ለእግዚአብሔር አደራ ይሰጠን ዘንድ አይበቃም፡፡ ግን
የሚያድነን የሚያነጻን የየሱስ ክርስቶስ ምግባር የርሱ ደም ነው፡፡ ገናም እግዚአብሔር እሽ በማለት ይቀበለን ዘንድ
የምናደርገው ሥራ አለን፡፡ ደግሞ ዋናው አቸናፊ ጸሎት ሃይማኖት ነው፡፡ ወደ እግዚአብሔር የሚመጣ ሰው ለነዚያ
በትጋት እግዚአብሔርን ለሚሹት ዋጋቸውን የሚሰጥ እግዚአብሔር እንደሆነ ማመን ይገባዋል፡፡ (ዕብ፡ ፲፩፡፮) የሱስ
ለደቀመዛሙርቱ አላቸው በጸሎት የትለምኑትን ሁሉ እንድታገኙት እመኑ ይሆንላችሁማል» (ማርቆ ፲፩፡ ፳፬፡፡) በገዛ
ቃሉ አንይዘውምን፡፡ እርሱ የሰጠነው የታመነ ተስፋ ሰፊ ወሰን የሌለው ነው፡፡ እርሱ ተስፋውን የሰጠነው የታመነ ነው፡፡
ያነውን የለመነውን ነገር በለመነ ጊዜ ባናገኘው፤ እግዚአብሔር ጸሎታችንን ገና እንዲሰማ ምላሽም እንዲሰጠን ማመን
ይገባናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ለኛ ያልተባረከውን ነገር በመለመናችንና ባለማስተዋላችን እንስታለን፡፡ የሰማዩ አባታችን ለኛ
በጣም የምንሻውን ነገር በመስጠት ለጸሎታችን ምላሽ ይሰጠናል እኛ ራሳችን የምንሻው ነገር በመንፈሳዊ ራዕይ
ተገልጦልን ቢሆን ነገሩን ሁሉ በውነት እናየው ነበር፡፡ ጸሎታችን ያልተሰማን በመሰለን ጊዜ የተሰጠነውን ቃል ኪዳን
ተጠማጥመን መያዝ ይገባናል፡፡ ምላሽ የምናገኝበት ጊዜ በውነት ይመጣልና በጣም የምንሻውን መባረክም
እናገኛለን፡፡ ግን እኛ እንደምንሻው ሁኖ ጸሎታችን በተለየ ነገር ሁል ጊዜ ይሰማናል ማለት ድፍረት ነው፡፡ እግዚአብሔር
በጣም ቸር ነውና በቀና መንገድ ለሚሔዱት ሰዎች መልካሙን ነገር ለመስጠት አይከለክላቸውም፡፡ ያን ጊዜ በርሱ
ለመታመን አትፍራ፡፡ ለጸሎትህ የቀለጠፈ ምላሽ እንኳ ባታገኝ በውነተኛው ቃል ኪዳኑ ታመን «ለምኑ ይሰጣችኋል»
የሚለውን፡፡ (ማቴ፡ ፯፡፯)፡፡ ከጥርጥራችንና ከፍርሃታችን ጋራ ብንመካከር ወይም ነገሩን ሁሉ አጥርተን ልንተረጉመው
አንችልም ብለን ብንፈትን ፤ ሃይማኖት የሌለው ብቻ የበዛና የጠለቀ ጭንቀት ያገኘናል፡፡ ግን ረዳት እንደሌለን ከርሱ
በታች እንደሆነ አውቀን ወደ እግዚአብሔር ብንመጣ በውነት እንዲሁ እንዳለን ሁነን በትሕትና ራሳችንን ዝቅ አድርገን
በሃይማኖት ፀንተን የምንሻውን ለርሱ እያስታወቅን ለእርሱ ለዕውቀቱ ፍጻሜ ለሌለው በፈጠረው ፍጥረት ውስጥ
ያለውን ነገር ሁሉ ለሚያየው፤ በፈቃዱና በቃሉ ሁሉን ለሚገዛው ጩኸታችንንም ሊሰማ ለሚችል በልባችንም
መብራት እንዲበራ ወደሚያደርገው ወደ እግዚአብሔር ብንመጣ እርሱ ጩኸታችንን ሊሰማ ይችላል ፤ በልባችንም
መብራት እንዲበራ ያደርጋል፡፡ በእውነተኛ ጸሎት ፍጻሜ የሌለው ዕውቀት እናገኛለን፡፡ የመድኃኔዓለም ፊት በርኅራኄና
በፍቅር ወደኛ በተመለሰ ጊዜ በግልጽ አይታወቀንም፡፡ ግን ነገሩ ከቶውን እንዲሁ ነው፡፡ የሚታየው መዳሰሱ
አይታወቀንም ይሆናል፡፡ ግን የቸርነትና የርኅራኄ እጁ በላያችን ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ምህረትና በረከት ለመለመን
በመጣን ጊዜ በልባችን የፍቅርና የይቅርታ መንፈስ ሊኖርብን ይገባል፡፡ እንዴት አድርገን ነው ልንጸልይ የምንችል?
«የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፡፡» (ማቴ ፮፡ ፲፪፡፡) ገናም ይቅር የማይል መንፈስ አለብን
ጸሎታችን ሊሰማልን ብንወድ እኛ ይቅር ልንባል ተስፋ እንደምናደርግ እኛ ደግሞ የበደሉንን ይቅር ልንል ይገባናል፡፡
በጸሎት ጸንቶ መኖር የፈለጉትን ነገር የሚያስገኝ ሁኖአል፡፡ በሃይማኖትና በዕውቀት እያደግን ለመሔድ ብንወድ
ሁልጊዜ መጸለይ ይገባናል፡፡ ለጸሎት የማናርፍ ልንሆን ይገባናል፡፡ «ጸሎትንም የምናዘወትር በርስዋም ተግተን
ማመስገን ይገባናል»፡፡ (ሮሜ ፲፪፡ ፲፪፡፡ ቆላ፡ ፬፡፪፡፡) ጴጥሮስ ያመኑትን ክርስቲያኖች ያስተዋሉ እንዲሆኑ በጸሎትም
እንዲተጉ ይመክራል፡፡ (፩፡ ጴጥ፡ ፬፡፯፡፡) ጳውሎስ እንዲህ ብሎ ይመራል፡፡ «በነገሩ ሁሉ በጸሎትና በምህላ ከምስጋና ጋራ
መሻታችሁ በእግዚአብሔር ዘንድ ትታወቅ» ፤ (ፊል ፬፡ ፮፡፡) ይሁዳ እንዲህ አለ፤ «እላንት ግን ወዳጆቼ ሆይ በመንፈስ
ቅዱስ እየጸለያችሁ በእግዚአብሔር ፍቅር ተጠበቁ» ፡፡ (ይሁዳ ፳፩፡ ፩፪፡፡ እንዲሁ ከእግዚአብሔር የሚወጣ ሕይወት
ወደ ሕይወታችን እንዲመነጭ ከእኛም ሕይወት ንጽሕና ቅድስና ተመልሶ ወደ እግዚአብሐር እንዲመነጭ የማያቋርጥ
ጸሎት በእግዚአብሔርና በነፍስ መሀከል በማይበጠስ ያንድነት ገመድ ነው፡፡ በጸሎት መትጋት የሚያሻ ነገር ነው፡፡
ማናቸውም ነገር አይከልክላችሁ፡፡ የሚቻላችሁን ሁሉ ጥረት ጣሩ፡፡ ድካማችሁ በየሱስና በነፍሳችሁ መሀከል ያለውን
አንድነት እንዲገልጽ ጸሎት ሊደረግበት ወደ ተለመደው ስፍራ ለመሔድ የሚመቸውን ጊዜ ሁሉ እሹ፡፡ እሊያ
ከእግዚአብሔር በውነት አንድነትን ለማግኘት የሚሹት ፤ ተግባራቸውን ለማድረግ የታመኑ ሁነው ራሳቸውን
አዋርደው ፤ እጅግ በመሻት የሚችሉትን ጥቅም ሁሉ ለማጨድና ለማግኘት በማኅበሩ በጸሎት ጊዜ ይታያሉ፡፡ ከሰማይ
የመጣውን ፀዳለ ብርሃን ለማግኘት ራሳቸውን ወደሚያስቀምጡበት ስፍራ የሚመቸውን ጊዜያት ሁሉ ለማግኘት
እየለመዱ ይሄዳሉ፡፡ ቤተሰቦቻችን ከበውን ልንጸልይ ይገባናል፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ በሥውር የምናደርገውን ጸሎታችንን
ችላ ማለት አይገባንም፡፡ የነፍስ ሕይወትዋ ይህ ነውና፡፡ ጸሎት ችላ በተባለ ጊዜ ነፍስ ልትለመልም አይቻላትምና፡፡
ከቤተሰቦችና ከብዙ ሰዎች ጋራ ብቻ መጸለይ አይበቃንም፤ ሁሉን ወደሚያየው ወደ እግዚአብሔር ዓይን ነፍስ ዓይነ
ልቡናዋን ሰቅላ ወደ እግዚአብሔር ብቻ የተመራች ትሁን፡፡ በሥውር የሚደረግ ጸሎት ፤ ጸሎትን በሚሰማው
በእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ይሰማል፡፡ እንዲህ ያለው የጸሎት ሸክም ለመስማት በእግዚአብሔር ዘንድ የከበደ እንግዳ
ነገር አይደለም፡፡ በሥውር ጸሎት ጊዜ ነፍስ በዙሪያዋ ካለ ነገር ሁሉ ከድንጋፄም ነፃ መሆን ይገባታል ፤ በጸጥታ በጣም
የተቃጠለች ሁና ወደ እግዚአብሔር ትደርሳለች፡፡ በሥውር ከሚያየው ከልብ የሚደረገው ጸሎት ለመስማት ጆሮው
ከተከፈተው ከእግዚአብሔር የሚጣፍጥና ፀንቶ የሚኖር በኃይል ይመነጫል፡፡ ነፍስ ከሰይጣን ጋራ ስትዋጋ ሳለች
እንዲያበረታትና እንዲረዳት ጸጥ ባለ ገር ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋራ አንድ መሆንን የመለኮትን ፀዳለ ብርሃን ለራስዋ
ታገኛለች፡፡ የኃይል አምባችን እግዚአብሔር ነው፡፡ በእልፍኝህ ሁነህ ጸልይ ለየለቱ ሥራህ በምትሔድበት ስፍራ ሁሉ ወደ
እግዚአብሔር ልበህን አንሣ፡፡ ሄኖክ ከእግዚአብሔር ጋራ በሔደ ጊዜ እንዲሁ ነበር፡፡ ይህ በቀስታ የሚደረግ ጸሎት
በእግዚአብሔር የጸጋ ዙፋን ፊት መዓዛው እንዳማረ ዕጣን ወደ ላይ ይወጣል፡፡ ልቡ እንዲህ በእግዚአብሔር
የታመነውን ሰው ሰይጣን ሊያቸንፈው አይችልም፡፡ ለእግዚአብሔር ጸሎት የምናቀርብበት የተለየ ጊዜ የለም፡፡
በውነተኛ የጸሎት መንፈስ ልባችንን ወደ እግዚአብሔር ለማንሣት የሚከለክለን ነገር የለም፡፡ በመንገድ በተሰበሰቡት
በብዙዎች ሰዎች መሀከልም ቢሆን ለሥራው በተሰበሰቡት ሰዎች መሀከልም ቢሆን የመለኮትን ኃይል ወደ ቀናው
መንገድ እንዲመራን እርዳታ ለማግኘት በንጉሡ በአርጠቅሲስ ፊት ነህምያ ልመናውን ባቀረበ ጊዜ እንዳደረገው
ጩኸታችንን ወደ እግዚአብሔር እንልካለን፡፡ ባለንበት ሥፍራ ሁሉ አንድነት የምንገናኝበት እልፍኝ ልናገኝ ይገባናል፡፡
የሱስን የመጥራታችን ድምፅ ወደ ላይ እንዲሰማና የሱስ እንደ ሰማይ እንግዳ መጥቶ በነፍሳችን እንዲያድር ፤ የልባችን
በር ሁል ጊዜ የተከፈተ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ይህም ሳይቀር የተበላሸ ንጹሕ ያይደለ ነፍስ አየር በዙሪያችን ይኖር ይሆናል፡፡
እኛም የተበላሸውን ነፋስ ልንተነፍስ አንወድም፡፡ ግን በንጹሑ የሰማይ ነፋስ እንኖራለን፡፡ ንጹሕና ቅዱስ ያይዶለ አሳብ
በልባችን አንዳይገባ በቀና ጸሎት ነፍስን ወደ እግዚአብሔር ፊት ከፍ በማድረግ መዝጊያን ሁሉ እንዘጋለን፡፡ እሊያ
የእግዚአብሔርን እርዳታና በረከት ለመቀበል ልባቸውን የከፈቱት ከምድሩ ነፋስ ይልቅ ቅዱስ በሆነ ነፋስ ይመላለሳሉ፡፡
በሰማይ ካለው አባታቸው ጋራም ፀንቶ የሚኖር አንድነት ያገኛል፡፡ የሱስን በጣም በተለየ ማየት ሙሉ የሆነ የዘለዓለም
የእውነት ክብርን ማስተዋልን ይሰጠናል፡፡ የሱስን የተለየ በማየታችን የእግዚአብሔርን ልጆች ለሆነው ሁሉ በልባችን
የቅድስናን ውበት ይሞላበታል፡፡ ይህም እንዲፈጸም የሰማዩ ነገር መለመን ይገባናል፡፡ እግዚአብሔር ሰማያዊ ነፋስ
እንዲሰጠን ነፍሳችን ወደላይ ልትወጣ ይገባታል፡፡ አበባ በተፈጥሮ ባሕርዩ ወደ ፀሐይ እንደሚመለስ ያልታሰበ ፈተና
በመጣብን ጊዜ አሳባችን ወደ እግዚአብሔር እንደመለስ ሁልጊዜ ወደርሱ መቅረብ ይገባናል፡፡ የምትሹትን ነገር ሁሉ
ደስታችሁንም ኅዘናችሁንም አሳባችሁንም ፤ፍርሃታችሁንም ሁልጊዜ በእግዚአብሔር ፊት አኑሩት የላንት የከበደ
ሸክማችሁ እርሱን አይከብደውም አያደክመውም፡፡ እርሱ የራሳችሁን ጠጉር ቁጥር የሚያውቀው ልጆቹ የሚሹትን
ነገር ያውቃል፡፡ እግዚአብሔር ምሕረቱ የበዛ የሚራራም ነው፡፡ (ያዕ ፭፡፲፡፩፡፡) የፍቅር ልቡ በኅዘናችን ተዳስሶአል፡፡
ከቶውንም ይህን የምንናገረውን ነገር ያውቃል፡፡ በአሳባችን የሚያስጨንቀነን ሁሉ ነገር ወደርሱ መውሰድ ይገባናል፡፡
ይሸከመው ዘንድ ለርሱ የሚከብደው ነገር የለም፡፡ እርሱ ዓለሙን ሁሉ ተሸክሞአልና፡፡ እርሱ በዓለሙ ያለውን ሁሉ
ይገዛልና፡፡ ለደኅንነታችን የሚሆነውን ነገር ታናሽ ስንኳ ቢሆን ችላ ሳይል ያደርግልናል፡፡ በፈተናችን ውስጥ ያለውን
ምዕራፍ ያነበው ዘንድ ለርሱ አይጨልምበትም፡፡ እርሱ ሊገልጸውና ሊተረጉመው የሚያደናግረው ነገር የለም፡፡
ለታናሾቹ ልጆቹ ስንኳ መከራ አያገኛቸውም፡፡ ነፍስንም የቸገረ አሳብ አያገኛትም፡፡ ፍሥሓንም ደስታንም የሚሰጥ
የሰማዩ አባታችን ነው፡፡ የታመነው ጸሎት የሰማዩ አባታችን ሳይሰማው ተከንፈር አምልጦ አይሔድም፡፡ በለመነው ጊዜ
ለኛ ጥቅም የሚሆነውን ነገር እርሱ ወዲያው በቶሎ ይሰጠናል፡፡ «ልባቸው የተሰበረውን ሰዎች እርሱ ይፈውሳል፡፡
ቁስላቸውንም ይጠግናል፡፡ (መዝ፡ ፻፵፯፡ ፫፡፡) እግዚአብሔር የሚወደውን ልጁን አሳልፎ የሰጠላቸው ሌሎች ነፍሶች ስለ
አልኖሩ በእግዚአብሔርና በኢያንዳንዱ ነፍስ መሐከል ያለው ዝምድና በሙሉ የተለየና የታወቀ ነው፡፡ የሱስ አለ
«በስሜ ትለምናላችሁ አብን ስለ እላንት እለምናለሁ አልላችሁም፡፡ አብ እርሱ እራሱ ይወዳችኋልና፡፡ በስሜ
የለመናችሁትን ሁሉ አብ ይሰጣችሁ ዘንድ እኔ መረጥኋችሁ» ፡፡ (ዮሐ፡ ፲፮፡ ፳፮፡ ፳፯፡፡ ፲፭፡፲፮፡፡) ግን በጸለይን ጊዜ
የየሱስን ስም ብቻ በጸሎታችን መጀመርያና መጨረሻ ከማንሣት ይልቅ አብልጠን ልናነሣው ይገባናል፡፡ በሰጠን ቃል
ኪዳን በጸጋውም ከታመነ የርሱን ሥራም ከሠራን በየሱስ ክርስቶስ አእምሮና መንፈስ መጸለያችን ነው፡፡
እግዚአብሔር ከኛ ማናችንንም ቢሆን ባሕታውያን መናኞች ወይም መነኰሳት ሁኑ አላለንም፡፡ ከዓለሙም ወጥተን
ለራሳችን እግዚአብሔርን ልናመልክ ራሳችንን ቀድሰን ለእግዚአብሔር ልንሰጠ አይወድልንም፡፡ ኑሮአችን እንደ ክርስቶስ
ኑሮ በተራሮችና በሕዝቡ መሀከል መሆን ይገባዋል፡፡ ከጸሎት በቀር ሌላ ሥራ የማይሠራ ሰው ከጥቂት ቀን በኋላ ጸሎት
ለመጸለይ ይሰለቻል፡፡ ወይም ጸሎቱ እንዲያው በልማድ ከሰዎች ጋራ አብሮ ከመኖር አስወግደው ክርስቲያን ዓለም
ተግባር ፈትተው በዓለም ሁነው እንደ ክርስቶስ መከራ መስቀልን ከመሸከም ወጥተው እጅግ ያገለገላቸውን ጌታ
ከማገልገል ሲያቋርጡ ዋናው የአምላካዊ ጸሎት ነገር ይቀርባቸዋል፡፡ ማለት ያልታዘዘ ጸሎት ይሆናል፡፡ ጸሎታቸው
ለራሳቸው ብቻና ራሳቸውን ስለመውደድ ይሆናል፡፡ ሌሎች ስለሚሹት ነገር አይጸልዩም፡፡ ስለ ክርስቶስ መንግሥት
አይጥሩም፡፡ በሚሠሩበት ስፍራም ኃይል ለማግኘት አይለምኑም፡፡ እግዚአብሔርን ስናገለግል እርስበርሳችን
ለመፅናናትና አይዞህ አይዞህ ለመባባል አንድነት የመሰብሰብን ሥርዓት ብንንቀው በራሳችን ላይ ጥፋት እናመጣለን፡፡
የእግዚአብሔር የቃሉ እውነቶች ዋናው ነገራቸውና ብርሃናቸው ከአእምሮዋችን ይጠፋል፡፡ ልባችን ብርሃን ከመሆን
በሚቀድስ ኃይላቸው ከፍ ከማለት ያቋርጣል፡፡ ከመንፈሳዊ ነገርም ወደ ሥጋዊ ነገር ይዘነብላል፡፡ እንደ ክርስቲያኖችም
ብነሰበሰብ እርስ በርሳችን ካልተዛዘነ ብዙ ነገር ይጐድልብናል፡፡ እርሱ ራሱን በገዛጁ የሚዘጋ ሰው እግዚአብሔር ሁንበት
ብሎ ያመለክተውን ሥራ አይፈጽምም፡፡ የተዘጋጁ ትልቆች የባልንጀርነትን ሥራዎች በባሕርያችን ከሌሎች ሰዎች ጋራ
እንድንተዛዘን ያደርጉናል፡፡ በእግዚአብሔር ሥራም እያደግንና እየበረታን ለመሔድ ምክንያት ይሆኑናል፡፡ ክርስቲያኖች
ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ስለከበረውም የማዳን እውነት እርስ በርሳቸው እየተነጋገሩ አንድነት ቢሰበሰቡ የገዛ ልባቸው
ይታደሳል፡፡ እርስ በርሳቸውም ይታደሳሉ፡፡ ስለ ሰ ማዩ አባታችን ከጸጋው አዲስ ዕውቀት እያገኘን በየቀኑ አብልጠን
እንማራለን፡፡ ከዚያ ቀጥለን ስለ ፍቅሩ ልንነጋገር እንወዳለን፡፡ ይህን ስናደርግ ሳለን የገዛ ልባችን የሞቀና የሚደፍር
ይሆናል፡፡ ከራሳችን ይልቅ ስለ የሱስ አስበንና ተነጋግረን ቢሆን በጣም አብልጠን ፊቱን ባየነው ነበር፡፡ ብቻ
እግዚአብሔር ስለኛ ማሰቡን እንደምንመሰክር እርሱን ብናስበው እርሱን በአሳባችን በልባችን ባኖርነው ነበር፡፡
ስለእርሱም ልንነጋገርና ልናመሰግነው ደስ ባለን ነበር፡፡ ለጊዜያቱ ስለሚሆኑት ነገሮች ለራሳችን ጥቅም ስለሆኑ ሁልጊዜ
እንነጋገራለን፡፡ ወዳጆቻችንንም ስለወደድናቸው ስለርሳቸው እንነጋገራለን፡፡ ደስታቸው ደስታችን ነው፡፡ ኅዘናቸውም
ኅዘናችን ነው፡፡ ዳሩ ግን የምድር ወዳጆቻችንን ከመውደድ ይልቅ እግዚአብሔርን ለመውደድ ፈጽሞ ትልቅ ምክንያት
አለን፡፡ እግዚአብሔርን ስለ ቸርነቱና ስለ ኃይሉ ከሁሉ በፊት ልናስበውና ለናመሰግነው በዚህ ዓለም የባሕርያችን ነገር
ነው፡፡ በኛ ላይ ያፈሰሰው ብዙ ጸጋው እኛ ለርሱ መልሰን አንዳችን ነገር እንዳንሰጥ የኛን አሳብና ፍቅር ለመዋጥ
አልታሰበም ነበር፡፡ እሊህም ነገሮች ሁልጊዜ እርሱን ያሳስቡናል፡፡ በፍቅር ማሠሪያም ያሥሩናል፡፡ በጎ የሠራልንን
ሰማያዊ አባታችንንም እንድናመሰግነው ያደርረጉናል፡፡ እኛም በታችኛው ምድራዊ አገር ለመቀመጥ በየም ቀርበናል፡፡
ከምድር ዳርቻ በርሱ ወደ እግዚአብሔር የመጡትን ሊያድን በሚችለው በክርስቶስ ፊት የእግዚአብሔር ክብር ወደ
ሚያበራበቱ ወደተከከፈተው ወደላይኛው መቅደስ በር ዓይኖቻችንን እናንሣ፡፡ (ዕብ ፯፡፳፭) ፡፡ እግዚአብሔር ለሰው
ልጆች ስለሠራው በጐነትና ድንቅ ሥራው በኛ አፍ ሊመሰገን ይገባዋል፡፡ (መዝ. ፻፰፡ ፰፡፡) የተቀደሰው ሥራችን ጨርሶ
መለመንና መቀበለ ሊሆን አይገባውም፡፡ ስለምንሻው ነገር ወይም ስለምንቀበለው ነገር ጥቅም ሁልጊዜ የምናስብ
አንሁን፡፡ ብዙ ጸሎት አያስፈልገንም፡፡ ግን ብዙ ማመስገን ይገባናል፡፡ እኛ ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ምሕረት ተቀባዮች
ነን፡፡ ገናም እንዴት ጥቂት ምስጋና እንሰጠዋለን፡፡ ለኛ ስላደረገልነው ቸርነትስ እንዴት ጥቂት ጥቂት እናመሰግነዋለን፡፡
በድሮው ዘመን ጌታ እስራኤልን ያገለግሉት ዘንድ አዘዛቸው እንዲህ ሲል ፤ አንድነት በተሰበሰባችሁ ጊዜ እላንት
የቤታችሁ ሰዎች መብላችሁን ብሉ፡፡ በእግዚአብሔር ባምላካችሁ ፊት እጃችሁን በምትዘረጉበት ነገር ሁሉ ደስም
አይበላችሁ፡፡ እግዚአብሔር አምላካችሁ ስለ ባረካችሁ፡፡ (ዘዳ ፲፪፡ ፯፡፡) ስለ እግዚአብሔር ክብር የሚደረግ ነገር ሁሉ
በደስታ በምስጋና በዝማሬ በውዳሴ እንጂ በኅዘን ፊትን በማጥቆር ሊደረግ አይገባውም፡፡ አምላካችን ርኅሩኅ ምሕረት
የሞላበት አባት ነው፡፡ ኅዘንና ትካዜ በሞላበት ልብ ልናገለግለው አይገባንም፡፡ ጌታን ለማምለክና ለማገልገል ክፍል
ባገኘን ጊዜ ደስታ ማድረግ ይገባናል፡፡ እግዚአብሔር ትልቅ መዳን የተዘጋጀላቸውን ልጆቹን እንደ ጨካኝ ጌታ ሁኖ በግድ
ሊያሠራቸው አይወድም፡፡ እርሱ ከሁሉ ይልቅ የተሻለ ወዳጃቸው ነው፡፡ ለርሱ በሰገዱለት ጊዜም ሊባርካቸውና
ሊያፀናቸው ልባቸውን በደስታና በፍቅር እየሞላ ከነዚያ ጋራ ለመሆን ሲጠብቃቸው ይቆያል፡፡ እግዚአብሔር ልጆቹ
በሥራው ከጭንቅ ነገር ይልቅ ደስታ ሊያገኙ ሊፅናኑ ይወዳል፡፡ እግዚአብሔር እርሱን ለማምለክ የሚመጡት እርሱ
ስለጠበቃቸውና ስለወደዳቸው ደስ እንዲለቸው በየለቱ በሚሠሩት ሥራቸው ሁሉ ሞገስና ጸጋ እንዲያገኙ በነገሩ ሁሉ
እውነትና ሃይማኖት የሞላባቸው እንዲሆኑ መልካም የከበረ አሳብ ይዘው ሊመጡ ይወዳል፡፡ በመስቀሉ ዙሪያ
ልንሰበሰብ ይገባናል፡፡ በጣም ደስ የሚያሰኝ ነው የልባችን መናወጥም ዋናው ነገራችንም የተሰቀለው ክርስቶስ ሊሆን
ይገባዋል፡፡ ከእግዚአብሔር የምንቀበለውን በረከት ሁሉ በልባችን ልናኖረው ይገባናል፡፡ ትልቁን ፍቅሩን በእውነት
ስናውቀው ነገሩን ሁሉ ስለኛ በመስቀል ለተቸነከረው እጅ አደራ መስጠት ይገባናል፡፡ ነፍስ በምስጋና ክንፍ ወደ ሰማይ
አጠገብ ወደ ላይ ትወጣለች፡፤ ለእግዚአብሔር በላይኛው አደባባይ በሙዚቃ ይሰግድለታል፡፡ ምሥጋናችንን
ስግድታችንን ወይም አምልኮአችንን ለእግዚአብሔር ስናስታውቅ አምልኮአችን እንደ መላእክት አምልኮና ስግደት
ወደመሆን ይቀርባል፡፡ ምስጋና የሚያቀርብ ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል፡፡ (መዝ፡ ፶፩ ፡፫)
ምዕራፍ 12—በጥርጥር ጊዜ እንዴት ለማድረግ፡፡
ብዙዎች ሰዎች ይልቁን ገና ወጣቶች ጐበዞች ወጥም ልጃገረዶች፤ በጥርጥር የተነሣ በክርስቲያን ኑሮ
በጭንቀት ቸናው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እነዚያ ሉተረጐሙዋቸው ወይም ሊያስተውሉአቸው
የማይችሎ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ሰይጣን በመፍሐፍ ቅዱስ አይሊህን ሃይማኖት ለማናወጥ፤ ከእግዚአብሔር
የተገለጠ አስመስሎ ሥራውን ይሠራል፡፡ እነዚያም የቀናውን መንገድ እንዴት አድርገን እናውቃለን እያሉ
ይጠይቃሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በእውነት የእግዚአብሔር ቃል ከሆነ ከዚህ የጥርጥር ጭንቀት እንዴት አድርገን
ነው ነፃ የምነሆን ይላሉ፡፡
Previous
Next
ክርስቲያኖች ለሰማዩ መንገድ መብራት አብራዎች ሁነው ቁመዋል፡ ከክርስቶስ ያገኙትን በነዚያ ላይ
የሚያበራውን ብርሃን ለዓለሙ መልሰው ሊያሳዩ ይገባቸዋል፡፡ የነዚያን ላይ የሚያበራውን ብርሃን ለዓለሙ
መልሰው ሊያሳዩ ይገባቸዋል፡፡ የነዚያን አናኑአርና ባሕርይ ሌሎች አይተው ክርስቶስን እንዲያስቡትና
እንዲያገለግሉት፤ መልካም ምሳሌዎች መሆን ይገባቸዋል፡፡ የክርስቶስ እንደ ራሴዎች ከሆነ ሥራው በውነት
የተገለጸ ሁኖ እንዲቀርብ ማድረግ ይገባናል፡፡ ለራሳቸው ጨለማና ኅዘን የሚሰበስቡ የሚያጐረመርሙም፤
የሚከሱም ክርስቱያኖች የእግዚአብሐር ሐሰተኞች እንደራሴዎች መሆናቸውንና ሐሰተኛ የክርስቲያን ኑሮ
መኖራቸውን ለሌሎች ያሳያሉ፡፡ እግዚአብሔርንም ልጆቹን የማይወድ ያስመስሉታል፡፡ በዚህም ነገር በሰማዩ
አባታችን ላይ ሐሰተኛ ምስክር ይመሰክራሉ፡፡ ሰይጣን የእግዚአብሔርን ልጆች ወደ ክህደትና ተስፋ ወደ
መቁረጥ ሊመራቸው በቻለ ጊዜ በደስታ እልል ይላል፡፡ እግዚአብሔር ያድነን ዘንድ መቻሉን ተጠራጥረን
መታመናችን ትተን ባየነ ጊዜ እጅግ ደስ ይለዋል፡፡ ሰይጣን እግዚአብሔር በግዛቱ ክፉ ሊያደርግብን የሚወድ
እንዲመስለን ያደርጋል፡፡ የእግዚአብሔርን እውነት በሐሰት ይወውጣል፡፡ በእግዚአብሐር ወገን አሳባችንን
በሐሰት ይሞላዋል፤ይወውጠውማል፡፡ ስለ ሰማዩ አባታችን በውነቱ በመኖር ፈንታ እኛ ደግሞ እውነተኛ
ባይዶለ የሰይጣን እንደራሴነት ሁል ጊዜ አሳባችንን እናጸናለን፡፡ በእግዚአብሔር ባለመታመናትንና በእርሱ
ላይ በመጐረምረማችን እግዚአብሔርን እናዋርዳለን፡፡ ሰይጣን የሃይማኖትን ኑሮ ሁል ጊዜ ጨለማ
የሚያዳክምና የሚያስቸግር ሁኖ እንዲታይ ሊያደርገው ይወዳል፡፡ ይህንንም የሃይማኖት መልክ ክርስቲያን
በራሱ አናኑዋር ሲያሳይና ሲያቀርብ፤ የሰይጣንን ሐሰት ደግሞ በመጨመሩ ባለማመን መኖሩን ያሳያል፡፡
ብዙዎች ሰዎች በዚህ ዓለም ኑሮ ሲመላለሱ የተሰጣቸውን ተስፋ አናገኘውም ብለው በመቁረጣቸው
በልባቸው ኀዘንና ትካዜ ሞልቶበታል፡፡ በኤውሮጳ ሳለሁ ይህን እያደረገች በጠለቀ ኀዘን በፍረሃትም የነበረች
አንዲት እኅት እባክሽ ጥቂት የሚያጽናና የሚያደፋፍር ቃል ላቂልኝ ብላ ላከችብኝ፡፡ ያን ጊዜ ደብዳቤዋን
ካነበብሁ በኋላ በዚያው ሌሊት ሕልም አለምሁኝ በታክልት ቦታ ያለሁ ይመስለኛል አንዱ ያታክልቱ ጌታ
በመንገዱ የሚመራኝ ይምስለኛል አንዱ የታክልቱ ጌታ በመንገዱ የሚመራኝ ይመስለኛል፡፡ አንዱ ያታክልቱ
ጌታ በመንገዱ የሚመራኝ ይመስለኛል፡፡ እኔም አበባዎችን እሰበስብ ነበር፡፡ በአበባዎች ሽታም እጅግ ደስ
አለኝ፡፡ ያችም እኅት በባጠገቤ ስትሔድ ነበረች፡፡ እርስዋም መንገድዋን ከልክለዋትወደ ነበሩት የዱር አበቦች
አይ ዘንድ አመለከተችኝ፡፡ እሊያም የዱር አበባዎች በጣም አይታዩም ነበር፡፡ በዚያም እርስዋ ስታለቅስና
ስትዝን ነበር፡፡ መሪውን ተከትላ በደኅናው መንገድ መሔድዋን ትታ እሾህ በሞላባቸው በቀናዎችና
በአጋሞች መሀከል ስትሔድ ነበረች እርስዋም ‹ዎ ይህ ያማረ የአታክልት ቦታ በእሾሆች መበላሸቱ
አያሳዝንምን ብላ አለቀሰች› ያን ጊዜ መሪው እሾሆች መበላሸቱ አያሳዝንምን ብላ አለቀሰች ያን ጊዜ መሪው
እሾሆች ከማቁሰል በቀር ሌላው አያደርጉልሽና እጆሆቹን ወዲያ ትተሽ ጽጌረዳትንና ሌሎችን መልካም
መልካም አበቦች ሰብስቢ ይልቅ አላት፡፡ ለእግዚአብሔር መንፈስ ምላሽ ለመስጠት ልብሽ ከደስታ የተነሳ
ዱጭ ዱጭ ሲል በፈተናሽ ጊዜ ብርሃን የሆኑ ጥቂቶች ስፍራዎች የተወደዱ ጥቂቶች ወራቶች አልነበሩሽምን፡፡
ወደ ኑሮሽ ፈተና ምዕራፍ ወደ ኋላ ተመልሰሽ ስትመለከች ደስ የሚያሰኙ ጥቂቶች ገጾች አታገኝምን፤
የእግዚአብሔር ቃል ኪዳኖች በምትልፊበት መንገድ ግራና ቀኝ ሁነው እንደሚየድጉ ሽታቸው እንደሚያምር
አበቦች አይደሉምን ውቡታቸውና ያማረ ሽታቸው ልብሽን በደስታ ይሞላው ዘንድ አትወጅምን? ቀጋዋችና
አጋሞች ከመውጋትና ከማሳዘን በቀር ሌላ አዳረሱሽም ብቻ እሊህን እሾሆች ብትሰበስቢና ለሌሎች ሰዎች
በዙሪያሽም ላሉት ሁሉ ሰዎች ብትሰጫቸው በሕይወት መንገድ እንዳይሔዱም ብትከለክያቸው አንቺ
የእግዚአብሔርን ቃል ከማቅለል በቀር ምን ልታደርጊ ትችያለሽ፡፡ ያለፈውን ኑሮ ማሰብ ብልሃት የለውም
ፍርሃት እስኪሞላብን ድረስም ያለፈውን ነገር ብንናገው እጅግ ያሰከፋል፡፡ ተስፋም የስቆረጣል፡፡ ፍርሃት
የሞላበት ነፍስ ጨለማ የሞላበት የእግዚአብሔርን ብርሃን እንዳታይ ራስዋን ወደ ውጭ አውጥታ የዘጋች
ናት፡፡ ሌሎችም በሚያልፉበት መንገድ ላይ የጨለማ ጥላ የጣለች ናት፡፡ እግዚአብሔርን ስለ ሰጠነው
የብርሃን ምሳለዎች እናመሰግነዋለን የተባረከውን የፍቅሩን እውነተኞች ነገሮች ሁል ጊዜ
እንድንመለከታቸው አንድነት እንሰብስባቸው የእግዚአብሔር ልጅ የባቱን መንበረ መንግሥት ትቶ
የመለኮትን ባሕርይ ከሰው ባሕርይ ጋራ ለብሶ ሰውን ከሰይጣን ኃይል አዳነ፡፡ በእልልታም የሰማይን በር
ከፍቶ የመገናኛውን የእልፍኝ መጋረጃ ገልጾ የአምላክን ከብርለሰው አሳየ፡፡ የወደቀውን የሰው ፍጥረት
ከኃጢአት ጉድጓድ አውጥቶ በኃጢአት ባሕር ውሥጥ የዘገጠውን ሰውንም ዘለዓለም ከሚኖር አምላክ ጋር
አንድ አደረገው፡፡ መለኮታዊ ፈተናን በሃይማኖት በአደኛችን በኢየሱስ ታግሠን የክርስቶስን ጽድቅ ለብሰን
ወደ እርሱ ዙፋን ከፍ እንደንል አደረገን፡ እግዚአብሐር እንመለከታቸው ዘንድ የሰጠነ ምሳሌዎች እሊህ
ናቸው፡፡ የእግዚአብሔርን ፍቅር ወደ መጠራጠሩ ስንሆን የሰጠነውን ቃል ኪዳንም የማንታመን ስንሆን
እርሱን እናዋርደዋልን መንፈሱንም እናሳዝነዋለን፡፡ አንዲት እናት ለልጆችዋ ሁል ጊዜ የኑሮዋ ጥረት አሳቡዋ
ሁሉ ስለነዚያ ደኀንነት ስለነዚያ ጥቅም ለነዚያ ዕረፍት ለመስጠት ሲሆን ምናልባት እርስዋ የማትወዳቸው
መስሎአቸው ቢጠሉአትና ቢያሳጡአት ምን ይምስላት ይሆን እንዲህ ቢያደርጉአቸው ምን ይምስላቸው
ይሆን የሰማዩ አባታችንም እኛ ሕይወት እንድናገኝ አንዱን ልጁን አሳልፎ ወደመስጠት የመራውን ፍቅሩን
አንታመንም ስንል እንዴት አድርጎ ሊያከብረን ይችላል፡፡ ሐዋርያው እንዲህ ሲል ይጽፋል፡፡ ‹ምንም ሳይራራ
ልጁን ስ ለሁላችን አሳልፎ የሰጠው እግዚአብሔር እንዴትስ ሁሉን ከርሱ ጋር አይሰጠን› ፡፡ (ሮሜ. ፰፦፴፪)፡፡
ገናም ምንም በቃላቸው ባይናገሩ በሥራቸው ይህን ለሌሎችንም ነው እንጂ ምናልባት እኔን አይወደኝም
የሚሉ ስንት ናቸው፡፡ ይህ ሁሉ የገዛ ነፍስህን አጉዳትህ ነው፡፡ የምትናገረው የጥርጥር ነገር ሁሉ የሰይጣንን
ፈተናን ናልኝ ብሎ መጥራት ነው፡ ጥርጥርም ባንተ ዘንድ እየበረታ ይሔዳል፡፡ አገልጋዮችን መላእክትም
ታሳዝናቸዋለህ፡፡ ሰይጣን በፈተነህ ጊዜ የጥርጥርና የጨለመ ነገር አትተነፍስ፡፡ ለሰይጣን አሳብ መዝጊያውን
ልትከፍለት ብትወድ አእምሮህ አለመታመንና ዓመፀኝነት የሞላበት ይሆናል፡፡ የሚታወቅህን የጥርጥር ነገር
ሁሉ ብታሳይ ራስህን ብቻ አትቃወምም፡፡ ግን በሌሎች ሰዎች ልብ ክፉ የሚናገረውን የቃልህን ኃይል
ልታቸንፈው አትችልም፡፡ አንተ ራስህ ከፈተና ወራትና ከሰይጣን ወጽመድ ትድን ይሆናል፡ ግን ባንተ ኃይል
የተወነጨፉት ሌላዎች ሰዎች አንተ አስበኸው ከነበረው ያለማመን አሳብ ሊያመልጡ አይችሉም፡፡ እሊያን
መንፈሳዊ ኃይልና ሕይወት የሚሰጡትን ነገሮች ብቻ መናገር እንዴት ያለ ዋና ነገር ነው፡፡ ስለ ሰማያዊ
ጌታችሁ ለዓለሙ ምን ዓይነት ወሬ እንድታወሩ መላእክት ያደምጣሉ ተው ንግግራችሁ በአብ ፊት እላንተን
ምልጃ ለማማለድ ስለሚኖረው ስለ የሱስ ይሁን ሰላምታ ለመስጠት ያንዱን ወዳጃችሁን እጅ በጨበጣችሁ
ጊዜ የእግዚአብሔር ምስጋና በከንፈራችሁና በልባችሁ ይሁን፡፡ ይህ ነገር አሳብን ወደ የሱስ ያቀርባል፡፡ ሰዎች
ሁሉ ፈተና የከበደ ኀዘን መከራም አለባቸው፡ መከራችሁን እንደ እላንት ለሚሞት ሰው አትንገሩ፡፡ ነገር ግን
ችግራችሁን ሁሉ በጸሎት ተሸክማችሁ ወደ እግዚአብሔር ውሰዱት የጥርጥርና የፍርሃት ነገረን አለመናገርን
አንድ ሥርዓት አድርጉት የተስፋና ቅዱስ የሆነ ቃል በናገር የሌላዎችን ሕይወት ጥረታቸውንም ለመበርታት
በብዙ ትችላላችሁ፡፡ ከገዛ ራሳቸውና ከክፉ ኃይል ጋር በመጋደል እንደ መድከም ያሉ ፈተና ተጭኖ
ያቆሰላቸው ብዙ ደፋሮች ነፍሶች አሉ፡፡ እንዲህ ያለውን ሰው ብዙ ግድለት ይዞ ሳለ አታስፈሩት፡፡
በሚሔድበት መንገድ የግድ በማያጽናናው ድፍረትና ተስፋ የሞላበት ቃል አይዞህ እያላችሁ ደስ አሰኙት፡፡
እንዲሁም በእላንት ያለውን የክርስቶስን ብርሃን ለሌሎች ሰዎች ታሳያላችሁ፡፡ ‹ከኛ ሕይወቱ ለራስ የሆነ
ሰው የለም›፡፡ (ሮሜ ፲፬፦፯)፡፡ ዕውቁት በሌለው መንገዳችን ወይም ኃይላችን ሌላዎች ይደፍሩ ወይም
አይደፍሩ የሆናል፡፡ ከክርስቶስና ከእውነቱ ወደ ኋላ ሸሽተው ይርቁ ይሆናል፡፡ ስለ ክርስቶስ ኑሮና ባሕርይ
የስሕተት አሳብ ያላቸው ብዙዎች አሉ፡፡ ሙቀትና ፀሐይነት የሌለው ይመስላቸዋል፡፡ ሽካራና ጨካኝ ደስታም
የሌለው ይመስላቸዋል፡፡ እንዲሁ በብዙ ነገር የሃይማኖት ፈተና ሁሉ በዚህ ቁጥር ቀለም መልክ ተቀብቶ
ነበር፡፡ የሱስ ሁል ጊዜ ያለቅስ እንደነበረ ሰምተናል፡፡ ግን እንኳን ሳቅ ፍግግ ስንኳ አለ ተብሎ አያውቅም፡፡ የኛ
አዳኝ የኀዘንና የትካዜ ሰው ነበረ፡፡ ስለ ሰዎች ወዮታና ኀዘን ሁሉ ልቡ ያዝን ነበረ፡፡ ከዚህም ጋር ኑሮው ከራሱ
ይልቅ ሰውን መውደድ ነበረ የውጋትና የአሳብ ጽላ የወደቀበት መንፈሱ ያልተደቆሰ ነበረ፡፡ መልኩ የኀዘንና
የትካዜ መልክ አለመበሰም ግን ሲያዩት ሁልጊዜ ደስ የሚያሰኝ የሰላም ጸጥታ ነበረበት፡፡ ልቡም የሕይወት
ምንጭ ነበረ፡፡ ወደሚሔድበት ሁሉም ዕረፍት ሰላም ተድላ ይዞ ይሔድ ነበረ፡፡ መድኃኔ ዓለም እጅግ በጣም
እውነተኛ ነበረ፡፡ ግን ከቶጭልም ያለ ድምን ያለ አልነበረም፡፡ እርሱን የሚመስሉት ሰዎች ኑሮአቸው
እውነተኛ አሳብ ያለበት ይሆናል፡፡ ራሳቸው ለሚያልፉበት ነበር የጠለቀ ዕውቀት ያገኛሉ፡፡ ቅለት ይቀራል፡፡
ጭኸት የበዛበት ደስታ የሻከረ ዋዛ ጨዋታም የለ፡፡ ግን የየሱስ ሃይማኖት እንደ ፈሳሽ ውኃ ሰላም ይሰጣል፡፡
የደስታንም መብራት አያጠፋም፡፡ ደስታንም አይከለክልም፡፡ እግግ ፍግግ የሚልን ፀሐይን የሚመስልን
ፊቱንም አያጠቁርም፡፡ ክርስቶስ ሰዎችን ሊያገለግል መጣ እንጂ እርሱን ሰዎች ሊያገለግሉት አልመጣም፡፡
የርሱ ፍቅር ልባችን ሲገዛው እርሱን ምሳሌ አድርገን በጎ በመሥራት እርሱን እንከተለዋለን፡፡ የሌሎችን
ሰዎች ያልቀና ሥራና ፍርድ በጣም ደኅና አድርገን ብንመለከተው ከርስቶስ እንደወደደን አድርገን
እንዳልወደድናቸው ይታወቀናል፡፡ ክርስቶስ ለኛ ያደረገውን የሚገርም ፍቅሩንና ርኅራኄውን ሁል ጊዜ
ብናስበው እኛም ይህን የፍቅር መንፈስ በሌላዎች ሰዎች ላይ እናፈሳለን፡፡ እርስ በራሳችን መፈቃቀርና
መከባበር ይገባናል፡፡ ከዚሁም ጋሪ ስሕተትና ፍጹም አለመሆን እንዳለብን የግድ እናያለን፡፡ ትሐትና ራስን
አብልጦ አለመውደድ ሊገኙብን ይገባል፡፡ ሌሎች ሰዎችም ባጠፉ ጊዜ የትዕግሥተ ርኅራኄ ልናደርግላቸው
ይገባናል፡፡ ይህም ልበ ጠባቦች የሚያደርገነው ራሳችንን አብልጠን መውደድን ይገድለዋል፡፡ እኛንም ለጋሶች
ቸሮች ያደርገናል፡፡ ባለመዝሙሩ ዳዊት እንዲህ ይላል፡፡ ‹በምድር እንድትኖር በእግዚአብሔር ታመን በጎም
አድርግ እርግጥ እርሱ ይመግብሀል፡፡› (መዝ. ፴፯፦፫)፡፡ በእግዚአብሔር ታመን ቀኑ ሁሉ ለራሱ እያንዳንዱ
የራሱ ሸክም የራሱ አሳብ የራሱ ጭንቀት አለው፡፡ በተገናኘነም ጊዜ ስለ ጭንቀታችንና ስለ አገኘነው ፈተና
ልነነጋገር እንዴት የተዘጋጀነ ነን፡ እንዲሁ የተበደረ ብዙ መከራ በግድ ገብቶአል፡፡ እንዲሁ ብዙ ፍርሃትም
የሚያሻ ሁኑአል፡፡ በቸገረን ጊዜ ሁሉ ሊረዳን ቶሎ የሚደርስልን ጸሎታችን ሊሰማ የተዘጋጀ አዛኝ ወዳጅ አዳኝ
የሌለን እስኪመስለን ድረስ እንዲህ ያለ ሚዛኑ የአበደ አሳብ እንደተጨነነ ታውቆናል፡፡ አንዳንድ ሰዎችም
ሁል ጊዜ መከራን እየተበደሩ ይፈራሉ፡፡ ግን ሁል ጊዜ በእግዚአብሔር የፍቅር ምልክት ተከበዋል፡፡ ሁልጊዜም
እግዚአብሔር ባዘጋጀው የልግስና ስጦተ ደስ ይላቸዋል፡፡ ግን ያሁኑን በረከት ይመለከታሉ፡፡ አእምሮአቸው
ይመጣብን ይሆናል ብለው ከሚፈሩት ጥቂት መከራ የተነሣ ሁል ጊዜ ባንድ በማይስማማ ነገር ሲያስብ
ይኖራል፡፡ ወይም የቸርነትን ስጦታ ለማግኘት እስከሚያሻ ብዙ ነገር እስኪደርሱ ድረስ በውነት ጥቂት
መከራ ይመጣባቸው ይሆናል፡፡ ይኸውም ዓይኖቻቸውን ያውራል፡፡ የህ ጭንቀታቸው የእርዳታ ምንጭ ወደ
ሆነው ወደ እግዚአብሐር በመቅረት ፈንታ ከእርሱ ይለያቸዋል፡፡ ከዚህም የተነሣ ያለ ዕረፍት እያዘኑ ይነቃሉ፤
ያፍሩማል፡፡ እንዲሁ ያለመነ በመሆናችን መልካም እናደርለንን ምስጋናም መታመንም የሌለብን መሆናችን
ስለምን ነው የሱስ ወዳጃችን ነው፡፡ በሰማይ ያሉት ሁሉም ስለኛ ደኅንነት ደስ ይላቸዋል፡ ለልባችን በየቀኑ
ጭንቀት ፍርሃት ለአሳባችን ጥርጥር ለፊታችንም ጥቁረት ልንሰጠው አይገባንም፡፡ ሁል ጊዜ እንዲህ
ብናደርግ ቁጣና ብስጭት ያገኘናል፡፡ ብቻ የሚያስፈራንና የሚያደክምን ጸሎት አያሻነም፡፡ ይህ ፈተና
በመጣብን ጊዜ ለመታገሥ አይረዳንምና፡፡ በሥራህ ትቸገር ይሆናል፡፡ ወደ ፊት የምታየው ማየት
እየጨለመብህ ይሔዳ፡፡ ጥፋት አግኝቶህ ይሆናል ዳሩ ግን አትፍራ፡፡ አሳብህን በእግዚአብሔር ላይ ጥለህ ጸጥ
ብለህ በደስታ ኑር፡፡ ሥራህን ለማድረግ ጥበብ እንድታገኝ በጥንቃቄ ጸልይ፡ ይህን በማድረግህ በጥፋትና
ከመከራ ትድናለህ፡፡ መልካም ነገር ለማድረግ ባንተ ወገን የሚቻልህን ሁሉ አድርግ፡፡ የሱስ ሊረዳነ ቃል
ኪዳን ሰጥቶናል፡፡ ደግሞም ልናገኘው የምንጥርበት ነገር ሁሉን ይሰጠናል እንጂ ከፍሎ አይሰጠንም፡፡
በረዳትህ ላይ ስትታመን የሚቻልህን ሁሉ ማድረግህ ነው፡፡ ከእርሱ የምታገኘውን ሁሉ በደስታ ተቀበል፡፡
እግዚአብሔር ወገኖቹን ሚዛኑ የቀበደ አሳብ ሊጫናቸው አይወድም፡፡ ግን ጌታችን አያታልለንም፡፡ እርሱ
አትፍሩ በመንገዳችሁም የሚያስፈራ ነገር የለም አላለንም፡፡ ፈተና የሚያስፈራም ነገር እንዳለ እርሱ
ያውቃልና እርሱ ነገሩን ሁሉ በገልጽ ነግሮናል፡፡ እርሱ ወገኖቹ ኃጢአትና ክፋት ከሞላበት ዓለም ሊያ
ወጣቸው አላሰበም፡፡ ግን ዘለዓለም ፀንቶ ወደሚኖር አምባ መጠጊያ መራቸው፡፡ ጸሎቱ ስለ ደቀመዛሙርቱ
እንዲህ ነበር ከዓለም ታወጣቸው ዘንድ አለምንም ‹ከክፉ ትጠብቃቸው ዘንድ እንጂ ከዓለም ተወጣቸው
ዘንድ አለምንም፡፡› ደግሞ በዓለም መከራ ያገኛችኋል፡፡ ነገር ግን ፅኑ አላቸው ‹እኔ ዓለምን አሸነፍሁ፡፡› (ዮሐ
፲፯፥፲፭ ምዕ ፲፮፥፴፫)፡፡ ክርስቶስ በተራራ ላይ ሲሰብክ ለደቀመዛሙርቱ በእግዚአብሔር ላይ መታመን
በጣም የሚያሻ እንደ ሆነ እጅግ የከበረ ትምህርት አስተማረ፡፡ እሊህ ትምህርቶች በትውልዱ ሁሉ
የእግዚአብሔርን ልጆች ለማደፋፈር ማመልከቻ ሁነዋል፡፡ ለብዙ ትምህርትና ማጽናትም እስከኛ ጊዜ ድረስ
አሉ፡ መድኃኔ ዓለም ተከታዮቹን የምስጋና መዝሙራቸውን ወደሚዘምሩ የሰማይ ወፎች አመለከታቸው፡፡
ደግሞም ‹እንዳይዘሩና እንዳያጭዱ› ምን እንበላለን ብለውም እንዳያስቡ፡፡ በሰማይ ያለው ትልቁ አባት
ምግባቸውን የሚያዘጋጅላቸው ስለሆነ፡፡ አዳኛችን ‹ከእለዚያ እላንት እጅግ አትሻሉምን› ብሎ ጠየቀ፡፡ ማቴ
፮፥፳፮፡፡ ለሰውና ለእነስሳ ምግባቸውን የሚያዘጋጀው ጌታ እጁን ይዘረጋል፡፡ ፈጥረቶቹን ሁሉ ይመግባል፡፡
የሰማይም ወፎች ከሰቡ በታች ናቸው፡፡ እርሱ ጥሬውን በእጁ ወደ አፋቸው አያፈስላቸውም፡፡ ግን
ለመሸታቸው የማሆን ምግብ ያዘጋጀት ይገባቸዋል፡፡ ታናናሾችን ልጆቻቸውንም መመገብ ይገባቸዋል፡፡
‹እላንት ከነርሳቸው እጅግ አትሻሉምን ከሰማይ ወፎች ይልቅ በጣም የከበራችሁ ብልሆች መንፈሳውያን
ሰጋጆች አይደላችሁምን ብቻ በርሱ ብንታመን የፍጥረታችን ፈጣሪ ሕይወታችንን የሚጠብቀው
በመለኮታዊ መልኩ የፈጠረነው ስለምንሻው ነገር ሁሉ አያዘጋጅልንምን፡፡ ክርስቶስ ደቀመዝሙርቱን
ፍቅሩን ለሰው ስለማሳየት የሰማዩ አባት በሰጣቸው የማማር በልጭልጭታ እየብለጨለጩ በብዛት
ወደሚያድጉት ወደ ዱር አበባዎችን እንዴት እንዲያድጉ ተመልከቱ አለ፡፡ ከሰሎሞን ይልቅ ወደ አጌጡና ወደ
አማሩ አበባዎች እዩ አላቸው፡፡ በጣም ያማሩ በሰው ጥበብ የተሠሩ የጌጥ ልብሶች በፍጥረታቸው ጸጋና
የሚያበራ ውበት ያላቸውን እግዚአብሔር የፈጠራቸውን አበቦች አይተካከሉአቸውም፡፡ የሱስም ጠየቃቸው
እንዲህ ብሎ የምድረ በዳንም እሣር ዛሬ የሚገኝ ነገም ወደ እሳት የሚጣል ‹እግዚአብሔር እንዲሁ
የሚያለብሰው ከሆነ እላንተን ይልቅ አያለብሳችሁምን እላንት ሃይማኖት የጎደላችሁ› ማቴ ፮፥፳፷፥፴፡፡
መለኮታዊ ጥበብ ያለው እግዚአብሔር ለእሊህ አበቦች ስንኳ ልምላ ሜና ያማረ ልዩ ልዩ መልክ የሚሰጥ
ከሆነ ይልቁን በርሱ መልክ ለተፈጠሩት እንዴት አብልጦ ያስብለቸው፡፡ ይህ የክርስቶስ ትምህርት በጣም
የሚያስበውን በጣም የሚጨነቀውን የሚጠራጠረውን ሃይማኖት የሌለውን ልብ ለመገሠፅ ነው፡፡ ጌታ
ወንዶቹና ሴቶቹ ልጆቹ ሁሉ ደስ ሊላቸው ሰላም ሊያገኙ ፈቀደኞች ሊሆኑ ይወዳል፡፡ የሱስ አለ ሰላሜን
እተውላችኃለሁ ሰላሜን የምሰጣችሁ ዓለም እንደማሰጥ አይዶለም፡ ልባችሁ አይደንግጥ አይፍራም፡፡
ደስታዬ በእላንት እንዲፀና እንዲፈጸም ይህን ነገርኋችሁ ዮሐ ፲፬፦፳፯ ማቴ ፲፭፦፲፩፡፡ ከሚገባው ሥራ
መንገድ ወጥቶ ራሱን ብቻ ከሚወድ አእምሮ የታሰበ ደስታ የማይስማማ ደኅና ሁኖ ያልተመዘነ ነገር ነው፡፡
ከልኩም አልፎ ሒዶ ወዲያ ይጠፋል፡፡ ነፍስም ብቻዋን እንደ ሆነችና ኀዘን እን ደሞላበት ይታወቃታል፡፡
እግዚአብሔርን በማገልገል ደስታና ጽጋብ ይገኛል፡፡ ክርስቲያን እርግጥነቱ ባልታወቀ መንገድ ሊሔድ
አልተተወም ለከንቱ ኀዘንና ተስፋ በመቁረጥም አልተተወም፡፡ በዚህ ምድራዊ ኑሮ ደስጸ ብናጣ ገናም ወዲያ
ማዶ ያለውን ኑሮ አሻግረን እያደነ ደስ ይለናል፡፡ ግን በዚህ ዓለምም ቢሆን ክርስቲያኖች ከክርስቶስ ጋር
አንድ የመሆንን ደስታ ያገኛሉ፡፡ የፍቅሩን ብርሃን ከፊት የሚገኘውን የማያልቀውን መፅናናት ያገኛሉ፡፡
የሕይወት እርምጃ እያንዳንዱ ወደ ክርስቶስ ያደርሰናል፡፡ የጠለቀውን የፍቅሩን አውቀትም ይሰጠናል፡፡ ወደ
ተባረከው የሰላም ቤት አንድ መድረክ ቀረብ እንድንል የደርገናል፡፡ አሁን በክርስቶስ መታመናችንን
አንጣል፡፡ ግን ወትሮ ሱሆን ከነበረው ይልቅ የፀና እውነተኛ ነገር ያለነ እንሁን፡ ‹በዚህም እግዚአብሔር
ረድቶናል፡1 (፩ ሳሙ ፯ ፲፪) › እስከ መጨረሻውም ይረዳናል፡፡ ከአጥፊው እጅ ሉያድነንና ሊያፅናናን ጌታ
ወዳቆማቸው የመታሰቢያ አምዶች ወይም ሐውልቶች እንመልከት፡፡ እግዚአብሔር ያሳየነን የርኅራሔ
ምሕረቱን ሁሉ በአእምሮአችንና በአሳባችን አዲስ አድርገን እንያዘው፡፡ እንደባችነን አብሶልናል፤ ውጋታችንን
አቅልሎልናል፡፡ ጭንቀታችንንም አስወግዶልናል፡፡ ፍርሃታችንንም ከኛ አርቆልናል፡፡ የምንሻውነ ነገር
ሰጥቶናል በረከቱንም አፍሶልናል፡፡ እንዲሁ በዚህ በተጀመረው ምናኔአችን በስተ ፊታችን ስላለው ነገር
ራሳችንን እናበርታ ፡፡ ስለ አዲሱ ጭንቀት ወደ ፊት ብቻ አናይም፡፡ ግን በሚመጣው ክርክር ደግሞ እንደ
መጭው ወዳለፈው እናያለን፡፡ «በዚህም ደግሞ ጌታ ረድቶናል እንላለን፡፡» ኃይልህ በቀንህ ልክ ይሆናል፡፡
(ዘዳ፡ ፴፫፡፳፭ ፡፡) እንሸከመው ዘንድ የሚመጣብን መከራ እግዚአብሔር ከሚሰጠን ኃይል አይበልጥም፡፡
አሁንም ስለሚሆነው ሁሉ ነገር ለፈተናው እኩል ወይም የተካከለ ኃይል ክፍል እንዲሰጠን አምነን ሥራችንን
እንሥራ፡፡ ጥቂት በጥቂት የሰማይ በር ለእግዚአብሔር ልጆች ይከፈታል፡፡ ከክቡር ንጉሥም ከንፈሮች የወጣ
ቃል ሲባርካቸው እንደብዙ ሙዚቃ ድምፅ በጆሮአቸው ይሰማሉ፡፡ እንዲህ ሲላቸው እላንት የአባቴ ቡሩካን፡
ኑ፡፡ ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ፡፡ ማቴ፡ ፳፭፡፴፬፡፡ ያን ጊዜ የዳኑት የሱስ
ወዳዘጋጀላቸው ቤት ይገባሉ፡፡ በዚያም የምድር ግፈኞች ሐሰተኞች ፣ አመንዝሮች ፣ ርኩሶች የማያምኑ
ባልንጀሮቻቸው አይሆኑም፡፡ ግን ሰይጣንን ድል ከነሡት ጋራ ባልንጀሮቻቸው አይሆኑም፡፡ ግን ሰይጣንን
ድል ከነሡት ጋራ ባልንጀሮች ይሆናሉ፡፡ በመለኮት ጸጋም ፍጹም የሆነ ባሕርይ ያገኛሉ፡፡ በዚህ ዓለም መከራ
ያሳያቸው የነበረ፤ የኃጢአት አሳብ ሁሉ ፍጹማን አለመሆናቸውም በክርስቶስ ደም ወግዶ ከፀሐይ ብርሃን
በጣም የሚበልጠውን የክርስቶስን የክብሩ ትልቅ ብርሃን ተካፋዮች በሆኑ ጊዜ ያማረ መንፈሳዊ አካሔድና
የርሱ ባሕርይ ፍጹምነት በነዚያ ላይ በውጭ አምሮ ከሚታየው ክብር የበለጠ ሁኖ ያበራል፡፡ በዚያም
የመላእክትን ሥልጣንና መዓርግ ተካፋዮች ሁነው በዚያ በትልቁ ነጭ በሆነው መንበረ መንግሥት ፊት ያለ
ነውር ይኖራል፡፡ ለርሱ የሚሆነውን የከበረ ርስት በማየት፡፡ «ሰው በነፍሱ ፈንታ ምን ይሰጣል፡፡» (ማቴ፡
፲፮፡፳፮፡፡) ሰው ድሀ ይሆን ይሆናል፤ ከዚሁም ጋራ ዓለሙ ሊሰጠው ከሚችለው የሚበልጥ ሀብትና መዓረግ
አለው፡፡ የዳነች ነፍስ ከኃጢአትም የነጻች የከበረ ኃይሉ፡፡ እግዚአብሔርን ለማገልገል ራሱዋን ቀድሳ የሰጠች
የበለጠ ክብር አላት፡፡ በእግዚአብሔርና በቅዱሳን መላእክት ፊት በዳነች ነፍስ ላይ በሰማይ በተቀደሰ ዕልልታ
ደስታ ይሆናል፡፡
Previous
Next