Professional Documents
Culture Documents
ሆሴዕ
ሆሴዕ
ሆሴዕ 6÷3
በዚህ መፅሐፍ (ትንቢተ ሆሴዕ) እግዚአብሔር በወደዳት፣ በጭቃ ከተለወሰችበት መሬት
አንስቶ ደሟን በማጠብ ከኃጢያትዋ ባነጻት፣ አይታ የማታዉቀዉን ደግሞም የማይገባትን ወግ
ማዕረግ ባሳያት፣ ከግልሙትናዋ ባላቀቃት፣ የኃጢያትዋንና የባርነቷን ዋጋ ሁሉ በመክፈል ከባርነት
ባወጣት...፣ ከምንም በላይ ደግሞ ማንም ዳግም ሊያፈቅራት በማይችለዉ ታላቅ ፍቅር ያፈቀራት
እና የሚንሰፈሰፍላት "እስራኤል" ከእርሱ እዉነተኛ ፍቅር ይልቅ ሌላዉን፣ ተድላን፣ ምቾትን፣
በሚገርም ሁኔታ ደግሞ የቀድሞ ግልሙትናዋንም ጭምር በመምረጧ የመጨረሻዉን ፍርድ በእርሷ
ላይ ከማሳለፉ በፊት እና እንዳትጠፋበትም ካለዉ ታላቅ ርህራሄ የተነሣ አንጀቱ እንደሚላወስበት
አባት እና ልቡም እንደሚቃጠልበት አፍቃሪ ፍቅሩን ለማደስ እና እርሷን ወደራሱ ለመመለስ
የሚያደርገዉን በፍቅርና በቁጣ የተሞላዉን የመጨረሻ የሚመስል ትግሉን ያሳየናል፡፡ ይህንንም፡-
“እስራኤል ሆይ! እንዴት እጥልሃለሁ? እንዴትስ አሳልፌ እሰጥሃለሁ? ለአንተ ያለኝ
ፍቅር ይህን ሁሉ እናዳደርግ አይፈቅድልኝም እኔኮ እንደ ሰዉ አይደለሁም!”(11÷8)
በሚል የፍቅር ቃል ይገልፅላታል፡፡ ነገር ግን እስራኤል ይህንን የፍቅር ጥሪ የምትመልሰዉ
“እንወቅ፤ እናዉቀዉም ዘንድ እግዚአብሔርን እንከተል፡፡”(6÷3) በሚል የእዉነት እና
ፍፁም የፀፀት ቃል መሣይ ነገር ግን ከልብ ባልሆነ የስላቅ እና የማስመሰል መልስ ነዉ፡፡
እግዚአብሔርም ለእስራኤል ሕዝብ “አንቺን ማግኘቴ እኮ የወይንን ፍሬ÷በምድረበዳ
የማግኘት ያህል ነበር፤ አባቶቻችሁንም ማግኘቴ አንድ ገበሬ የመጀመሪያዉን የበለስ
ፍሬ ሲያይ የሚሰማዉን አይነት ነበር”(9÷10) እያለ ሲነግራት፣ ሲያባብላት፣ ሊመልሳት
ሲጥር እርሷ ግን ከእርሱ ይልቅ አሁንም ሌላ አምላክን፣ ከክብሯ ይልቅ ዉርደትን፣ ከሕይወት
ይልቅ ሞትን መርጣ ከዳችዉ፤ ሲታይ ተስፋ ሰጪ የሚመስለዉን ለእርሱ ያላትን ፍቅርም
ሲገልጸዉ ማለዳ ላይ ምድርን ሁሉ ሸፍኖ እና ከድኖ እንደሚታይ የማለዳ ጉም
እንዲሁም ምድርን ሁሉ አረስርሶ ጨርሶ ተርፎት የሚተፋ በሚመስለዉ የጠዋት ጤዛ
ነዉ፡፡(6÷4) የእስራኤልማ ክህደት፣ በእግዚአብሔር ላይ ያሳየችዉ ንቀት፣ የኃጢያትዋ ብዛት፣
የድፍረቷ ትልቀት፣ የልብዋ ጥንካሬ፣ በእግዚአብሔር ላይ ላለመታመን ያላት ትልቅ እምነት፣ ኸረ
ምኑ ቅጡ÷ የቱ ተዘርዝሮ የቱ ይተዋል???
ኢሣያስ አያሌዉ
06/10/2010 E.C