You are on page 1of 335

የኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ

የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች


ኢንዱስትሪው ውስጥ የሞተርነት ሚናውን
ከመጫዎት አኳያ ያሉት ተግዳሮቶች፣
ዕድሎችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች

ዶ/ር አማረ ማተቡ


አቶ ካህሳይ ገረዚሄር
ዶ/ር ነፃነት ጆቴ
አቶ ደረጀ ራህመት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
አቶ ዮናስ አብርሀ
ሐምሌ 2009 ዓ.ም አቶ ውባለም ስራው
አቶ አሸናፊ መሀሪ
አቶ አበበ ከበደ
© 2009 ዓ.ም ታተመ
የኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል
የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ

ISBN 978-99944-74-36-3
መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page ii


የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪው
ውስጥ የሞተርነት ሚናውን ከመጫዎት አኳያ ያሉት
ተግዳሮቶች፣ ዕድሎችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች

ሐምሌ 2009 ዓ.ም

በኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page iii


የኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል

የኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል በመጋቢት ወር 2006 ዓ.ም የመንግስት ፖሊሲና
ስትራቴጂ የምርምር ማዕከል ሆኖ ተቋቋመ፡፡ ማዕከሉ የተቋቋመበት ዋና ምክንያት የኢትዮጵያን ፈጣን
የኢኮኖሚ ዕድገት በቀጣይነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ የፖሊሲና ስትራቴጂ ምርምሮችን ለማከናወን
ሲሆን በሀገራችን ቀዳሚው የፖሊሲ ሀሳብ አፍላቂ (Major think tank) እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
ማዕከሉ አምስት የጥናትና ምርምር ዘርፎችን የያዘ ሲሆን ከእነዚህ መካከል አንዱ የኢንዱስትሪ ልማት
ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ነው፡፡ ለተጨማሪ መረጃ እንዲሁም በማዕከሉ የተጠኑ ሌሎች
ምርምሮችን በሚመለከት በዌብሳይታችን www.psrc.gov.et ይመልከቱ፡፡

ኢፌዴሪ - ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል


ፖ. ሳ. ቁ 1072/1110
ስልክ: +251-11-6613767
+251-11-6610462
ፋክስ: +251-11-6621821
ኢ-ሜይል: policy.s120@gmail.com
ዌብሳይት: www.psrc.gov.et

የምርምር ሪፖርት

የኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል በራሱ ተመራማሪዎች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት
ጋር በተለያዩ ወቅታዊ ሀገራዊ የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ጥናትና ምርምሮችን ያከናውናል፡፡ በአምራች
ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ጥናት አንዱ ነው፡፡ በዚህ ጥናት ውስጥ የተካተቱ ጉዳዮችና
አስተያየቶች የተማራማሪዎች አመለካከት ሲሆኑ ሙሉ በሙሉ የማዕከሉን አቋም ላያንፀባርቁ
ይችላሉ፡፡ በዚህ ምርምር ላይ ያላችሁን ማንኛውንም አስተያየት ለኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና
ምርምር ዘርፍ በኢሜይል: amarematebu@yahoo.com ይላኩልን፡፡

የምርምሩ ባለቤት

“የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪው ውስጥ የሞተርነት ሚናውን ከመጫዎት አኳያ
ያሉት ተግዳሮቶች፣ ዕድሎችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች” ምርምር በማዕከሉ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ
ጥናትና ምርምር ዘርፍ ተመራማሪዎች የተከናወነ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page iv


ምስጋና

ጥናቱን በስኬት ለማጠናቀቅ ከመጀመሪያው ጀምሮ የሚመለከታቸው


ተቋማት ያላቸውን የጥናት ሰነዶች፣ የአፈፃፀም ሪፖርቶች፣ መመሪያዎች፣
ደንቦች፣ ዕቅዶችና ሌሎች ጠቃሚ ሰነዶች በመስጠት የተባበሩን
እንዲሁም ለቡድን ውይይቶች አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠትና ጥልቅ
ውይይት በማድረግ ልምዳቸውን ላካፈሉን የፌደራልና የክልል መንግስት
መ/ቤቶች፣ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች፣ የንግድና የዘርፍ
ማህበራት፣ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች እና የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ከፍተኛ ምስጋና እናቀርባለን፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page v


መልዕክት

የኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 311/2006
በመጋቢት ወር 2006 ዓ.ም የመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጂ የምርምር ማዕከል ሆኖ ተቋቋመ፡፡ ማዕከሉ
የተቋቋመበት ዋና ምክንያት የኢትዮጵያን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት በቀጣይነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ
የፖሊሲና ስትራቴጂ ምርምሮችን ለማከናወን ሲሆን በሀገራችን ቀዳሚው የፖሊሲ ሀሳብ አፍላቂ (Major
think tank) እንደሚሆን ታሳቢ ተደርጎ ነው፡፡ የኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል በዋናነት
በስራ ላይ ያሉ ፖሊሲና ስትራቴጂዎችን ከወቅቱ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ የማሻሻያ ስራዎች መስራት
እንዲሁም አዳዲስ የፖሊሲ ሀሳቦች ማመንጨት ነው፡፡ ማዕከሉ አምስት የጥናትና ምርምር ዘርፎችን
የያዘ ሲሆን ከእነዚህ መካከል አንዱ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ነው፡፡ በዚህ
ዘርፍ ውስጥ ምርምር ከሚደረግባቸው ጉዳዮች አንዱ በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብት ተሳትፎና ሚናን የሚመለከት ነው፡፡

በሀገራችን ዘላቂ የኢንዱስትሪ ልማትን ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ግንባር ቀደም ተዋናይ
መሆን እንዳለበት የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂው ያመለክታል (ኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ 1994
ዓ.ም)፡፡ በዚህ ሰነድ ላይ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት እንደዋነኛ ሀይል እንደሚወሰድና ባለሀብቱ
የኢንዱስትሪ ዕድገት ሞተር የመሆን ሚናውን እንዲጫዎት ማስቻል እንዲሁም የባለሀብቱን አቅም
ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ያብራራል፡፡ የግሉ ባለሀብት የኢንዱስትሪ ልማት ሞተር
ይሁን ሲባል የሀገር ውስጥ ባለሀብት ዋነኛው ሀይል የሚሆንበት፣ የውጭው ባለሀብት በሀገር ውስጥ
ባለሀብቱ ላይ በተደራቢነት በሰፊው ተሳታፊ የሚሆንበት፣ በሁለቱም ድምር አቅም የሀገራችን
የኢንዱስትሪ ልማት የሚፋጠንበት ሁኔታ መፍጠር መሆኑንም ይገልፃል፡፡ ሁለቱ ባለሀብቶች
የየራሳቸው የማይተካ ሚና ያላቸው ሲሆን ከሁለቱ አንዱ ብቻውን የምንፈልገውን ፈጣን የኢንዱስትሪና
ኢኮኖሚ ዕድገት ሊያረጋግጥ ስለማይችል አጣምረን መጠቀም እንዳለብን ሰነዱ በሰፊው ያብራራል፡፡
ጥናቱ መነሻ ያደረገው በዚህ በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂው ላይ የተቀመጠውን የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብት ሚና እንዲሁም አሁን ባለሀብቱ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ በማገናዘብ ነው፡፡

መንግስት ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ የአምራች ኢንዱስትሪውን ንዑስ ዘርፍ ለማሳደግ ሰፊ ጥረት እያደረገ
ቢሆንም ነገር ግን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን በአምራች ኢንዱስትሪው ልማት የዋና ተዋናይነት
ድርሻውን እንዲጫዎት ከማድረግ አኳያ የተሰራው ስራ አጥጋቢ ነው ለማለት አያስችልም፡፡ በሀገር
ውስጥ የግሉ ሴክተር በኢንዱስትሪው ዕድገት ላይ በሚፈለገው ደረጃ የሚገባውን ሚና ተጫውቷል
ለማለትም አያስደፍርም፡፡ በአንደኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን የአምራች ንዑስ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page vi


ዘርፉን ለይተን ስንመለከት በ1999 ዓ.ም ከጥቅል የሀገር ውስጥ ምርት (Share in GDP) ከነበረበት
5.5% ድርሻ፣ በ2003 ዓ.ም ወደ 4.9% እንዲሁም በ2007 ዓ.ም 4.6% መውረዱን የብሄራዊ ባንክ
መረጃ ያሳያል። ከዚህ በተጨማሪም ቀላል የማይባል ቁጥር ያለው የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት
በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ ለማሰማራት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ቢወስድም ወደተግባር እንቅስቃሴ
የገቡት ባለሀብቶች ቁጥር ግን እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪው ንዑስ ዘርፍ የውጭ
ምንዛሬ ግኝትም ከታቀደው በታቸ የወረደ ነው፡፡

በአጠቃላይ በሀገራችን የኢንዱስትሪው ልማትና ዕድገት ዋና ተዋናይ እንዲሆን የታሰበው የሀገር ውስጥ
የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ልማት ላይ ሚናውን በታቀደው ልክ እየተጫወተ አለመሆኑና
የኢንቨስትመንት ተሳትፎውም ዝቅተኛ ሆኖ መገኘቱ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ስለዚህ
በአንድ በኩል ቀድመው በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች ያሉባቸውን
ማነቆዎች መፈተሽ፣ አፈፃፀማቸውን ለመገምገምና የሞተርነት ሚናቸውን ከመጫዎት አኳያ ያለውን
ክፍተት በመለየት የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች ለማቅረብ፤ በሌላ በኩል ደግሞ አቅም ያላቸውና በሌሎች
ዘርፎች የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ በስፋት እንዲሰማሩ
የሚያስችል አቅጣጫ የሚያሳዩ የፖሊሲ ምክረ-ሐሳቦች እና መፍትሄዎች በዚህ ጥናት ተካተዋል፡፡
በመሆኑም በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ላይ ሚና ያላቸው ሁሉም አካላት
የጥናቱን ውጤት ግምት ውስጥ በማስገባት ተጨማሪ ዝርዝር የፖሊሲና ስትራቴጂ አፈፃፀም
መመሪያዎችና ደንቦችን በማዘጋጀት ወይም በመከለስ ወደ ተግባር ከገቡ ባለሀብቱንና የአምራች
ኢንዱስትሪ ልማቱን ዕድገት ለማፋጠን እንደሚያግዝ ተስፋ እናደርጋለን፡፡

አማረ ማተቡ ካሳ (ዶ/ር)


የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ

መሪ ተመራማሪ እና የምርምሩ አስተባባሪ

አዲስ አበባ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page vii


ማውጫ

ምስጋና ......................................................................................................................................... V
መልዕክት ..................................................................................................................................... VI
ዝርዝር የሰንጠረዥ ማውጫ.................................................................................................... XIII
ዝርዝር የግራፍ ማውጫ ......................................................................................................... XIV
አህፅሮተ-ማጠቃለያ (Executive Summmary)............................................................................ 1

ክፍል I መግቢያ

ምዕራፍ 1 የጥናቱ አስፈላጊነትና አላማ .................................................................................. 24

1.1 የጥናቱ አስፈላጊነት ............................................................................................................ 24


1.2 የጥናቱ አላማ .................................................................................................................... 26
1.2.1 አጠቃላይ አላማ.............................................................................................................. 26
1.2.2 ዝርዝር አላማዎች ........................................................................................................... 26
1.2.3 በጥናቱ መመለስ ያለባቸው ጥያቄዎች.............................................................................. 26

ምዕራፍ 2 የጥናቱ ዘዴና ተሳታፊዎች ..................................................................................... 28

2.1 የጥናቱ ዓይነት ................................................................................................................... 28


2.2 የመረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴዎችና መሳሪያዎች ............................................................................. 29
2.2.1 የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ (Primary Data) ........................................................................ 29
2.2.2 ሁለተኛ ደረጃ መረጃ (Secondary Data Sources) ........................................................... 31
2.3 ጥናት የተደረገባቸው ቦታዎችና የጥናቱ ተሳታፊዎች ............................................................... 32
2.4 የጥናቱ መረጃ ትንተና፣ ግኝትና ምክረ-ሀሳብ አቀራረብ ............................................................ 33
2.5 የጥናቱ ውስንነት ................................................................................................................. 34

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page viii


ክፍል II የተዛማጅ ጥናቶች ዳሰሳ

ምዕራፍ 3 የተዛማጅ ጥናቶች ዳሰሳ ................................................................................... 35

3.1 በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ኢንቨስትመንት ......................................... 35


3.2 አምራች ኢንዱስትሪን ለማጠናከር የቁጠባ እና መነሻ ካፒታል አስፈላጊነት ............................... 37
3.3 የኢንዱስትሪ ልማት፣ የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ እና የሰው ኃይል ልማት .................................. 40
3.4 ገቢ ምርቶች መተካት እና ለውጭ ገበያ ማምረት .................................................................... 42
3.5 የመንግስት ተነፃፃሪ ነፃነት እና የማስፈፀም ዓቅም ጥንካሬ......................................................... 47
3.6 ለግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት ወሳኝ ሁኔታዎች......................................................................... 49

ክፍል III የጥናቱ ትንተና እና ግኝቶች

ምዕራፍ 4 የአምራች ኢንዱስትሪው ጥቅል ገፅታ................................................................. 53

4.1 አምራች ኢንዱስትሪ እና ሀገራዊ የምጣኔ ሀብት ዕድገት ........................................................... 54


4.2 የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ስብጥር እና አስተዋፅኦ ................................................................ 56
4.3 የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ያለው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ....................... 59
4.4 የፋብሪካዎች ከዓቅም በታች ማምረት (UNDER CAPACITY UTILIZATION)..................................... 60
4.5 የጥንካሬ፣ ድክመት፣ አጋጣሚና ተግዳሮቶች ትንተና ................................................................ 63

ምዕራፍ 5 በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ዋና ዋና ተግዳሮቶች ............ 66

5.1 የኢንዱስትሪ አመራርና አደረጃጀት....................................................................................... 67


5.1.1 በፌደራል ደረጃ የኢንዱስትሪ ልማት አመራርና አደረጃጀት ነባራዊ ሁኔታ ......................... 68
5.1.2 በክልሎች የኢንዱስትሪ ልማት አመራርና አደረጃጀት ነባራዊ ሁኔታ .................................. 69
5.1.3 በኢንዱስትሪ አመራሩ ላይ የተስተዋሉ ዋና ዋና ክፍተቶች ................................................ 72
5.2 የኢንዱስትሪ ማበረታቻና ድጋፍ አቅርቦት ............................................................................. 78
5.2.1 ኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች ......................................................................................... 79
5.2.2 የገቢ ግብር እና የታክስ ማበረታቻዎች ............................................................................. 83

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page ix


5.2.3 የኤክስፖርት ንግድ ማበረታቻዎች.................................................................................... 86
5.2.4 የጉምሩክ ቀረጥ ነፃ አሰራርን ............................................................................................ 87
5.3 የፋይናንስና ብድር አቅርቦት ................................................................................................ 88
5.3.1 የፋይናንስ ተቋማት የማበደር አቅምና የትኩረት አቅጣጫ ................................................. 89
5.3.2 የስራ ማስኬጃ ካፒታል (working capital) አቅርቦት .......................................................... 96
5.3.3 የብድር አቅርቦትና የአገልግሎት አሰጣጥ .......................................................................... 96
5.3.4 የ25/75 የብድር ፖሊሲ አተገባበር .................................................................................... 98
5.3.5 የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ................................................................................................ 100
5.4 የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦት .......................................................................................... 105
5.4.1 ለአምራች ኢንዱስትሪ ከግብርና የሚገኝ የግብአት አቅርቦት ............................................ 107
5.4.2 ለአምራች ኢንዱስትሪ ከውጭ ሀገር የሚገባ የግብአት አቅርቦት ....................................... 116
5.5 የአምራች ኢንዱስትሪ ምርቶች ገበያና የንግዱ ስርአት .......................................................... 121
5.5.1 የአምራች ኢንዱስትሪ ምርት ጥራትና ደረጃ ................................................................... 121
5.5.2 የአምራች ኢንዱስትሪዎች የውድድር ሁኔታ.................................................................... 123
5.5.3 የአለማቀፍ ገበያ እና ንግድ ተፅዕኖ ................................................................................ 126
5.5.4 በአክሲዮን ማህበራት የተደራጁ አምራች ኢንዱስትሪዎች ................................................. 131
5.5.5 የንግድ ፈቃድ እና ስምሪት ............................................................................................ 134
5.5.6 የመንግስት ድጋፍ እና ገበያ ከለላ .................................................................................. 137
5.5.7 የመንግስት የግዥ ስርአት .............................................................................................. 139
5.6 በአምራች ኢንዱስትሪ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት .............................................................. 150
5.6.1 በአምራች ኢንዱስትሪ የቴክኖሎጂ ሽግግር አፈፃፀም ....................................................... 152
5.6.2 በአምራች ኢንዱስትሪ ለቴክኖሎጂ ሽግግር የባለድርሻ አካላት ሚና ................................. 156
5.7 በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ አቅምና ድርሻ ......................................... 162
5.8 ለአምራች ኢንዱስትሪ የመሬትና መሰረተ ልማት አቅርቦት ................................................... 163
5.8.1 ለአምራች ኢንዱስትሪ የመሬት አቅርቦት........................................................................ 164
5.8.2 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ......................................................................................... 169
5.8.3 የመሰረተ ልማት አቅርቦት (የኤሌክትሪክ ሀይል፣ መንገድ፣ ውሀ፣ ኢንተርኔት) ................... 172
የምዕራፉ ማጠቃለያ ............................................................................................................. 175

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page x


ምዕራፍ 6 የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብትና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ ባለሀብቶች ንፅፅር . 178

6.1 የአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብትና የውጭ ባለሀብት ሁኔታ........................... 179
6.2 በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብትና የሌሎች ዘርፎች ባለሀብቶች .................... 181
6.2.1 የሪል እስቴት (Real estate) ንዑስ ዘርፍ ........................................................................ 184

ምዕራፍ 7 በአምራች ኢንዱስትሪው ሊሰማሩ የሚችሉ አዳዲስ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ...... 190

7.1 በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች.......................................................... 190


7.1.1 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት በአምራች ኢንዱስትሪ ያላቸው ስምሪትና ማነቆዎች ........... 191
7.1.2 ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ከመካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ጋር ያላቸው ትስስር ......... 198
7.1.3 በአምራች ዘርፍ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ዕድገትና ሽግግር ......................................... 199
7.2 በገጠር የአርሶአደሩ ምጣኔ ሀብት ........................................................................................ 204
7.3 በንግዱ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ..................................................................................... 213
7.4 በኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ................................................................. 215
7.4.1 የኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፍ አፈፃፀም እና ለሀገር ኢኮኖሚ ያለው ድርሻ .......................... 215

ክፍል IV
የጥናቱ ማጠቃለያና የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦች

ምዕራፍ 8 የጥናቱ ማጠቃለያ እና ምክረ-ሀሳቦች ............................................................... 218

8.1 የጥናቱ ማጠቃለያ ............................................................................................................. 218


8.2 የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦች ........................................................................................................ 231
8.2.1 የኢንዱስትሪ አመራርና አደረጃጀትን ማሻሻል ................................................................. 235
8.2.2 አምራች የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን ለማጠናከር የቀረቡ የማበረታቻ ማሻሻያዎች ........ 239
8.2.3 ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪ የፋይናንስ አቅርቦት ልዩ ትኩረት መስጠት ................ 244
8.2.4 ተገቢ ያልሆነ አለማቀፍ ንግድ ውድድር ለመቆጣጠር የሬጉላቶሪ ስርአት መዘርጋት ......... 245
8.2.5 የመንግስት ግዥ ፓሊሲን ማሻሻል ................................................................................. 247
8.2.6 ያልተማከለ የገጠር ኢንዱስትሪ ልማት አቅጣጫ መከተል ............................................... 254

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page xi


8.3 ለተስተዋሉ ችግሮችና ማነቆዎች የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች............................................ 257
8.3.1 ኢንዱስትሪ ፋይናንስና ብድር አቅርቦት ላይ የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች.................. 257
8.3.2 ኢንዱስትሪ ማበረታቻና ድጋፍ አቅርቦት ላይ የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች ................ 259
8.3.3 ኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦት ላይ የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች ................................ 260
8.3.4 ኢንዱስትሪ ምርቶች ገበያና የንግዱ ስርአት ዙሪያ የቀረቡ መፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች ........... 263
8.3.5 በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ ለተስተዋሉ ችግሮች የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች .............. 266
8.3.6 በአምራች ባለሀብቱ ዙሪያ ለተስተዋሉ ችግሮች የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች ................ 269
8.3.7 መሬትና መሰረተ ልማት አቅርቦት ላይ የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች ......................... 272
8.3.8 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን በብዛትና በስፋት ማጠናከር................................ 274
8.3.9 በንግዱ ዘርፍ የተሰማራውን የሀገር ውስጥ ባለሀብት ወደ አምራች መሳብ ......................... 275
8.3.10 በኮንስትራክሽን የተሰማሩ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ወደ አምራች መሳብ ........................ 275

ዋቢ ምንጮች (REFERENCES) ..................................................................................... 276

አባሪዎች (APPENDIX) ................................................................................................... 280

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page xii


ዝርዝር የሰንጠረዥ ማውጫ

ሰንጠረዥ 2.1 መረጃ የተሰበሰበባቸው ምንጮች.....……………………..………………...….…..........…33

ሰንጠረዥ 4.1 በአምራች ኢንዱስትሪ ወደ ምርት የተሸጋገሩ (1984-2009 ዓ.ም ሩብ አመት)…….... 60

ሰንጠረዥ 4.2 የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ጥንካሬ፣ ውስንነት፣ አጋጣሚና ተግዳሮቶች………..……...64

ሰንጠረዥ 5.1 የኢንቨስትመንት መስኮች ተነፃፃሪ የካፒታል ዓቅም.…………….….…….....…….........95

ሰንጠረዥ 5.2 በክልሎች ለባሀብቶች የተሰጠ እና በስራ ላይ የዋለ የቦታ ስፋት.….………………..….166

ሰንጠረዥ 5.3 በፌደራል ደረጃ የተቋቋሙና በመቋቋም ላይ ያሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች………..…....170

ሰንጠረዥ 5.4 በክልል ደረጃ የሚቋቋሙ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች.….....................................…..171

ሰንጠረዥ 6.1 አምራች ዘርፍ ከንግድ፣ ኮንስተራክሽንና አገልግሎት ዘርፎች ጋር ሲነፃፀር…………...183

ሰንጠረዥ 7.1 በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ብዛት……….......199

ሰንጠረዥ 7.2 በየአመቱ ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች………………..….....201

ሰንጠረዥ 7.3 ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ወደ ታዳጊ መካከለኛ ላለመሸጋገር

የሚያቀርቡት ምክንያት ……………...………………………………………..…….….....203

ሰንጠረዥ 7.4 በአራቱ ክልሎች የሚኖረው ጠቅላላ አርሶአደርና አርብቶአደር ብዛት……...…………207

ሰንጠረዥ 7.5 ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮች ያስመዘገቡት ጥሬ ገንዘብ………………..212

ሰንጠረዥ 7.6 ከ2004/5-2006/7 ኢንዱስትሪ ንዑስ ዘርፎች ከኢንዱስትሪው ያላቸው ድርሻ……......216

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page xiii


ዝርዝር የግራፍ ማውጫ

ግራፍ 3.1 ዓለማቀፍ የኢንቨስትመንት ፍሰት (ሚለዮን USD) 1982-2005 ዓ.ም....................................36

ግራፍ 4.1 የኢንዱስትሪ አንጻራዊ ዕድገት 1999-2006 ዓ.ም ...............................................................54

ግራፍ 4.2 ኢንዱስትሪ ለሀገራዊ ምጣኔ ሀብት ዕድገትያበረከተው አስተዋጽኦ1999-2006 ዓ.ም…….…...55

ግራፍ 4.3 የአምራች ኢንዱስትሪዎች የዘርፍ ስብጥር ……..………………………………….….………..56

ግራፍ 4.4 የኢንዱስትሪ ንኡስ ዘርፎች ተነፃፃሪ ድርሻ.…………………………………………....…..…...57

ግራፍ 4.5 የፋብሪካዎች የማምረት ዓቅም አጠቃቀም በፐርሰንት….…………………………….........…..61

ግራፍ 4.6 ፋብሪካዎች ከዓቅም በታች የሚያመርቱበት ምክንያቶች.……………………….….……...…..62

ግራፍ 5.1 ከውጭ የሚገቡ ምርቶች የዋጋ ድርሻ በተጠቃሚ (በመቶኛ)……………………..........….….92

ግራፍ 5.2 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ 1999-2004 ያሰራጨው ብድር ድርሻ በመቶኛ……….….….........94

ግራፍ 5.3 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የለቀቀው የብድር መጠን (1998 -2007 ዓ.ም…………….…........102

ግራፍ 5.4 የገቢ ሸቀጦች የዋጋ ድርሻ በመቶኛ (ፔትሮሊየምና ማዳበሪያን ሳይጨምር)………..….......118

ግራፍ 5.5 በተለያዩ ዘርፎች በአስመጪነት የተሰማሩ ባለሀብቶች..………………..………..….….........136

ግራፍ 6.1 የሪል እስቴት ኢንቨስትመንት ከሌሎች ዘርፎች ጋር ሲነፃፀር (2007 ዓ.ም).................…..186

ግራፍ 7.1 በየአመቱ የተቋቋሙ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በዘርፍ …….......…..……..…..193

ግራፍ 7.2 ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች (2003-2006 ዓ.ም)………….….….200

ግራፍ 7.3 ጥ/አነስተኛ አንቀሳቃሾች ወደ ታዳጊ መካከለኛ ለመሸጋገር ያላቸው ፍላጎት……..………...201

ግራፍ 7.4 የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት የብድር ስርጭት መጠን የሚያሳይ…………….......…..202

ግራፍ 7.5 በ2007 ዓ.ም ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶአደሮች-(አራት ክልሎች)…………...….…..206

ግራፍ 7.6 በአራቱ ክልሎች የሚኖረው ጠቅላላ አርሶአደርና አርብቶአደር ብዛት………….……….......207

ግራፍ 7.7 በአራቱ ክልሎች ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶአደሮች በ% (ተደራሽነት)……….....….208

ግራፍ 7.8 በየክልሎቹ የተፈጠረው ካፒታል ከባለሀብቶች ቁጥር ጋር ሲወዳደር..……………….………209

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page xiv


አህፅሮተ-ማጠቃለያ (Executive Summary)

መንግስት የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚው ውስጥ ጉልህ ሚና እንዲጫዎት የሚያስችሉ


ሁኔታዎች አመቻችቷል፡፡ የተረጋጋ የማክሮ-ኢኮኖሚ ቀጣይነትን በማረጋገጥ ለልማታዊ
የግል ባለሀብቶች ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ተደርጓል፡፡ በተለያዩ
ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተለይተው የተከለሉ የኢንዱስትሪ ዞኖችና ፓርኮች
በማቋቋምና መሰረተ-ልማታቸው እንዲሟላ በማድረግ ለባለሀብቶች በማቅረብ ላይ
ይገኛል፡፡ ነገር ግን በአንደኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ውስጥ
የተመዘገቡት ውጤቶች ቀደም ሲል ከነበረው የአምስት አመት የዕቅድ ዘመን አማካይ
ጋር ሲነፃፀር የኢንዱስትሪው ዘርፍ እያደገ የመጣ ቢሆንም የአምራች ኢንዱስትሪው
ከጥቅል የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ ግን ከ5% በታች መሆኑ ለዘርፉ ዕድገት
ያለውን አስተዋፅኦ አነስተኛ እንዲሆን አድርጎታል፡፡

በሀገራችን ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪውን ንዑስ ዘርፍ


ለማሳደግ ሰፊ ጥረት እያደረገ ቢሆንም ነገር ግን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን
በአምራች ኢንዱስትሪው ልማት የዋና ተዋናይነት ድርሻውን እንዲወጣ ከማድረግ አኳያ
የተሰራው ስራ አጥጋቢ አይደለም፡፡ በሀገር ውስጥ የግሉ ሴክተር በኢንዱስትሪው
ዕድገት ላይ በሚፈለገው ደረጃ የሚገባውን ሚና ተጫውቷል ለማለትም አያስደፍርም፡፡
የኢንዱስትሪው ዘርፍ በ1999 ዓ.ም ለሀገራዊ ምጣኔ ሀብት ያበረከተው አስተዋፅኦ 8.5%
የነበረ ሲሆን በ2008 ዓ.ም ወደ 38.8% አድጓል፡፡ በ1999 ዓ.ም ከጥቅል የሀገር ውስጥ
ምርት (Share in GDP) የነበረው ድርሻ 14% ሲሆን በ2008 ዓ.ም ወደ 16.7%
አድጓል፡፡ ነገር ግን የአምራች ንዑስ ዘርፉን ለይተን ስንመለከት በ1999 ዓ.ም ለጥቅል
የሀገር ውስጥ ምርት የነበረው ድርሻ ከነበረበት 5.5% በ2003 ዓ.ም ወደ 4.9%
እንዲሁም በ2007 ዓ.ም 4.6% መውረዱን የብሄራዊ ባንክ መረጃ ያሳያል። ከዚህ
በተጨማሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት የኢንቨስትመንት ስምሪትን ስንመለከት
ከ1984-2009 ዓ.ም ሩብ አመት ድረስ 78,348 ፕሮጅክቶች የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ ሲሆን ከዚህ ውስጥ በአምራች ዘርፍ ፈቃድ
የወሰዱት 17,519 ፕሮጀክቶች ብቻ ናቸው፡፡ ከ17,519 ፕሮጀክቶች መካከል ደግሞ
ወደ ማምረት ተግባር የተሸጋገሩት 1837 (10.44%) ፕሮጀክቶች ብቻ ናቸው
(ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ 2009 ዓ.ም)፡፡ እነዚህም ቢሆኑ የማምረት
አቅማቸው (Capacity utilization) በጣም ዝቅተኛ (በአማካይ 58% ብቻ) ነው፡፡
በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች በብዙ ችግሮችና

የኢንዱስትሪ ልማት ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 1


ማነቆዎች ውስጥ ይገኛሉ፡፡ በአጠቃላይ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች
ኢንዱስትሪ ላይ ያለው ተሳትፎ በጣም ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መገንዘብ
ይቻላል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪውን ልማት ለማፋጠን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት፣ የውጭ


ባለሀብትና መንግስት ሁሉም በየፊናቸው የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ይጠበቃል፡፡
በዚህ ጥናት ውስጥ ትኩረት የተደረገው የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች
ኢንዱስትሪው ላይ ያለውን የሞተርነት ወይም የዋና ተዋናይነት ሚና የሚመለከት
ነው፡፡ በሀገራችን የኢንዱስትሪ ፖሊሲ ሰነድ ላይ በግልፅ እንደተቀመጠው የግል
ባለሀብት ለኢንዱስትሪው ልማትና ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር ወይም ዋና ተዋናይ
ነው፡፡ የግሉ ባለሀብት የኢንዱስትሪ ልማት ሞተር ይሁን ሲባል የሀገር ውስጥ ባለሀብት
ዋነኛው ሀይል የሚሆንበት፣ የውጭው ባለሀብት በሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ላይ
በተደራቢነት በሰፊው ተሳታፊ የሚሆንበት፣ በሁለቱም ድምር አቅም የሀገራችን
የኢንዱስትሪ ልማት የሚፋጠንበት ሁኔታ መፈጠር እንዳለበት ሰነዱ ያስረዳል፡፡
ምክንያቱም ከሁለቱ አንዱ ብቻውን የምንፈልገውን ፈጣን ዕድገት ሊያረጋግጥ
ስለማይችል አጣምረን መጠቀም እንዳለብን ይገልፃል፡፡

ምንም እንኳ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለየ ማበረታቻና ድጋፍ


ፓኬጆች አዘጋጅቶ ከጥቂት አመታት በፊት ወደ ስራ የገባ ቢሆንም፤ ነገር ግን አሁን
በተግባር እየታየ ያለው አብዛኛው የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት የመጀመሪያ ምርጫው
አምራች ኢንዱስትሪው ሳይሆን የንግድ፣ ሪል እስቴትና የአገልግሎት ዘርፎች ናቸው፡፡
ይህ የሚያመለክተው የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ከሌሎች ዘርፎች ጋር ሲነፃፀር
የግል ባለሀብቶችን የማይስብና ተመራጭ ያልሆነ መሆኑን ነው፡፡ ከዚህ ጉዳይ ጋር
ተያይዞ ሁለት ምክንያቶችን ማንሳት ይቻላል፡፡ አንደኛው ቀድመው በአምራች
ኢንዱስትሪ የተሰማሩ አብዛኛዎቹ ባለሀብቶች በብዙ ችግሮችና ማነቆዎች ምክንያት
ውጤታማ ባለመሆናቸው ወደ ዘርፉ መግባት ለሚፈልግ ባለሀብት ጥሩ አርአያ
ስላልሆኑት፤ ሁለተኛው ከላይ እንደተጠቀሰው በንግድና አገልግሎት ዘርፎች የሚገኘው
ትርፍ በጣም የተጋነነና ሳቢ በመሆኑ ነው፡፡ የግል ባለሀብቱ የመጀመሪያ ትኩረቱ
ትርፍ እስከሆነ ድረስ ያለብዙ ውጣውረድ ከፍተኛ ትርፍ የሚያስገኝለትን ዘርፍ
መምረጡ የማይቀር ነው፡፡ መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪውንና የሌሎችን ዘርፎች
ባህሪ በማየት የተጋነነ ትርፍ በሚያስገኙት ዘርፎች ገደብ ካላበጀላቸው እንዲሁም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 2


በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ የሚስተዋሉትን መሰረታዊ ችግሮችና ማነቆዎች በመፍታት
ተገቢውን ማበረታቻና ድጋፍ ካላደረግ ክፍተቱ እየሰፋ ሄዶ የአምራች ኢንዱስትሪ
ዘርፉን ማዳከሙ አይቀርም፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማራው ባለሀብት ለዘርፉ ዕድገት የሞተርነት ሚናውን


እንዲጫዎት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅዕኖ ያላቸው ባለድርሻ አካላት ዘርፉን
በተፈለገው ደረጃ ለማሳደግ ሁሉም የየራሳቸው ድርሻ ቢኖራቸውም ድርሻቸውን
በመወጣት በኩል በቂ ትኩረትና የተግባር እንቅስቃሴ እንዳላደረጉ ምዕራፍ አምስት ላይ
በዝርዝር ታይቷል፡፡ የመንግስት አካላት ለባለሀብቱ በቂ ድጋፍና ክትትል አለማድረግ፣
ለባለሀብቱ የተፈቀዱ ማበረታቻዎች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ አለማድረጋቸው፣ የተንዛዛ፣
አድካሚና ውጣውረድ የበዛበት አገልግሎት አሰጣጥ፣ የአመራር ቁርጠኝነትና የማስፈፀም
አቅም ማነስ፣ በቅንጅት አለመስራት እና ሌሎችም በአምራች ኢንዱስትሪ የባለሀብቱን
እንቅስቃሴ የሚገድቡ አሰራሮች ተከስተዋል፡፡

በጥቅሉ በሀገራችን የኢንዱስትሪው ልማትና ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር እንዲሆን


የታሰበው የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ልማት ላይ የዋና
ተዋናይነት ሚናውን እየተጫወተ አለመሆኑና የኢንቨስትመንት ተሳትፎውም ዝቅተኛ
ሆኖ መገኘቱ በሀገራችን ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ስለዚህ በአንድ በኩል
ቀድመው በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች
ያሉባቸውን ማነቆዎች መፈተሽ፣ አፈፃፀማቸውን ለመገምገምና የሞተርነት ሚናቸውን
ከመጫዎት አኳያ ያለውን ክፍተት በመለየት የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች ለማቅረብ ሲሆን
በሌላ በኩል ደግሞ አቅም ያላቸውና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ በስፋት እንዲሰማሩ የሚያስችል አቅጣጫ መለየትና
መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ የፖሊሲ ምክረ-ሐሳቦች ለማቅረብ ጥናቱ
አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

የዚህ ጥናት ዋና አላማ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ውስጥ
የሞተርነት ሚናውን ከመጫወት አኳያ ያሉትን ተግዳቶቶችና መልካም ዕድሎች
በመፈተሽ፣ ባለሀብቱ ተነፃፃሪ የኢንቨስትመንት ምርጫው አምራች ኢንዱስትሪው
እንዲሆን የሚያስችል የፖሊሲ ምክረ-ሀሳብ ማቅረብ ነው፡፡ የጥናቱን ዓላማ ለማሳካት
አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ መረጃዎች ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ በጥናቱ 88 አምራቾች
በናሙናነት ከትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያና ደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል መስተዳደሮች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 3


እንዲሁም የአዲሰ አባባና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮች ተካተዋል፡፡ የመጀመሪያ ደረጃ
መረጃ በፅሁፍ-መጠየቅ (Questionnaire) እና ቃለ-መጠይቅ አማካኝነት ከአምራች
ባለሀብቶች፣ የመንግስት መ/ቤት የስራ ሀላፊዎች መረጃዎች ተሰብስቧል፡፡ በተጨማሪም
በዘርፉ ልምድና ዕውቀት ያላቸው ባለሞያዎች የተሳተፉበት የቡድን ውይይቶች (FGD)
ተካሄደዋል፡፡ በተወሰኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ የአካል ምልከታ (Physical
observation) ተከናውኗል፡፡ ሁለተኛ ደረጃ መረጃም የተለያዩ ሰነዶች፣ የጥናት
ፅሁፎችና ተዛማጅ ፅሁፎች በጥልቀት ታይተዋል፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ዋና ዋና ተግዳሮቶች

የኢትዮጵያን የረጅምና አጭር ጊዜ የኢኮኖሚ ዕድገት ራዕይ ለማሳካት ጠንካራና


ተወዳዳሪ የሆነ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ መገንባት ወሳኝና አስፈላጊ ነው፡፡
መንግስት የሀገራችንን የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴ ተሞክሮ እና የግል ባለሀብቱን
አጠቃላይ ዓቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት ለዘርፉ የተለያዩ የኢንቨስትመንት
ማዕቀፎችን በማዘጋጀት የተሻለ አስቻይ ሁኔታ እንዲፈጠር ጥረት አድርጓል፡፡ ነገር ግን
ባለፉት አስር አመታት በተለይ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የተፈለገውን ያህል
የዕድገት ውጤት አላስመዘገበም፡፡ በአምራች ኢንዱስትሪው ውስጥ የተስተዋሉ ዋና ዋና
ችግሮችና ማነቆዎች 1) የኢንዱስትሪ አመራርና አደረጃጀት ችግር፣ 2) የማበረታቻና
ድጋፍ አቅርቦት ችግር፣ 3) የፋይናንስና ብድር አቅርቦት ችግር፣ 4) የኢንዱስትሪ
ግብአት አቅርቦት ችግር፣ 5) የአምራች ኢንዱስትሪ ምርቶች ገበያና የተሳለጠ የንግድ
ስርአት አለመኖር፣ 6) የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት አለመፋጠን፣ 7) በአምራች
ኢንዱስትሪ ባለሀብቱ በራሱ የተስተዋሉ ችግሮችና ውስንነቶች እና 8) ለአምራች
ኢንዱስትሪ የመሬትና መሰረተ-ልማት በበቂ ሁኔታ አለማቅረብ በመሰረታዊነት
ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው፡፡

1. የኢንዱስትሪ አመራርና አደረጃጀት


በሀገራችን የኢንዱስትሪና ኢኮኖሚ ልማት ውስጥ የግሉ ሴክተር ጠንካራና ተወዳዳሪ
ሆኖ የጎላ ድርሻ እንዲኖረው እና የወና ተዋናይነት ሚናውን እንዲጫዎት የኢንዱስትሪ
አመራሩ አቅምና ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን መገንዘብ ያሻል፡፡ የኢንዱስትሪ አመራርና
አደረጃጀትን በሚመለከት ሶስት መሰረታዊ ችግሮች አሉ፡፡ አንደኛው የኢንዱስትሪ
አመራሩ የማስፈፀም ችግር ነው፡፡ ሁለተኛው አሁን ያለው የኢንዱስትሪ አደረጃጀት
የተሳለጠ አለመሆን እና ኢንዱስትሪውን ለመምራት በሚያስችለው ቁመና ላይ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 4


አለመሆኑ ነው፡፡ ሶስተኛው የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተናበውና ተቀናጅተው
ያለመስራት ችግር ነው፡፡ አመራሩ የኢንዱስትሪ ፖሊሰና ስትራቴጂዎችን በትከክል
ተገንዝቦ በእውቀት ላይ የተመሰረተ አመራር ያለመስጠት ችግር ይታያል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ አመራሩ ስራውን ትኩረት ሰጦ በቁርጠኝነት ያለመስራት ችግር ይታያል፡፡
በተለይ በክልሎች በየደረጃው የኢንዱስትሪውን ዘርፍ በብቃት ለመምራት የሚያስችል
አመራርና አደረጃጀት አለ ለማለት አያስደፍርም፡፡

በሀገራችን በፌደራልም ይሁን በክልሎች የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን አደረጃጀት


ስንመለከት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተናበውና ተቀናጅተው እንዲሰሩ የሚያደርግ
አደረጃጀትና መዋቅር አለ ለማለት አያስደፍርም፡፡ በተለያየ ጊዜ በፌደራልና በክልል
ደረጃ መለስተኛ የአደረጃጀት ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በቅርቡ
መለስተኛ የሚባል የአደረጃጀት ለውጥ ያደረገ መሆኑን ከመ/ቤቱ የተገኙ መረጃዎች
ያመለክታሉ፡፡ ከዚህ በፊት በአንድ ሚኒስትር፣ በሶስት ሚኒስትር ዴኤታዎችና በአስራ
አንድ ተቋማት ይመራ የነበው የኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ በአሁን ወቅት በአንድ
ሚኒስትር፣ በሶስት ሚኒስትር ዴኤታዎችና በሰባት ተቋማት ተጠናክሮ እንደሚመራ
ይገልፃል፡፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብት ትራንስፎርሜሽን ዳይሬክቶሬትም ለሚኒስትሩ
ተጠሪ ሆኖ እንዲቋቋም ተደርጓል፡፡ ይህ ዳይሬክቶሬት በተለይ በአምራች
ኢንዱስትሪው የተሰማራውን የሀገር ውስጥ ባለሀብት ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራ መሆኑ ጥሩ
ነው፡፡ ነገር ግን የሀገር ውስጥ ባለሀብት ልማትን የሚመለከት ጉዳይ በተለይ በክልሎች
ከፍተኛ ሚና መጫዎት የሚገባቸው በመሆኑ ሚኒስቴር መ/ቤቱ በምን የአሰራር ስርአት
ከክልሎች ጋር መስራት እንዳለበት ግልፅ አቅጣጫ ማስቀመጥ የሚኖርበት ይሆናል፡፡

በክልሎችም በተለይ በታችኛው እርከኖች ኢንዱስትሪውን በተሟላ መንገድ ለመምራት


የሚያስችል ጠንካራ አደረጃጀት አልተፈጠረም፤ የልማት ተልዕኮው መወጣት
በሚችልበት ደረጃ ላይ አልደረሰም፡፡ በዚህም አቅም ያላቸውን ባለሀብቶች በሙሉ ልብ
እና በራስ መተማመን አሳምኖ ወደ አምራች ኢንዱስትሪ እንዲቀላቀሉ ማድረግ
አልተቻለም፡፡ ልማታዊ ባለሀብቱን የማጠናከርና ጥገኛ ባለሀብቱን የማክሰም ስራ
መስራት አልቻለም፡፡ ለባለሀብቱ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመለየት የአዋጭነት
ጥናቶችን በማከናወን ተጠቃሚ ማድረግ አልተቻለም፡፡ ባለሙያውም ቢሆን በተመሳሳይ
የግንዛቤ እና የአቅም ክፍተት ስለሚስተዋልበት ለባለሀብቱ ጥራት ያለውና ቀልጣፋ
አገልግሎት መስጠት አልቻለም፡፡ ዘርፉ ራሱን ችሎ አለመደራጀቱ በሀብት አመዳደብና
ስልጣን (power) ላይ አዎንታዊ አስተዋፅኦ እየተጫወተ አይደለም፡፡ በፌደራል ደረጃ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 5


ኢንዱስትሪውን የሚደግፍ መዋቅር ያለ ቢሆንም ይህ መዋቅር ግን በታችኛው
የአስተዳደር እርከን ከሌሎች አስፈጻሚ መ/ቤቶች ጋር እንዲዳበል በመደረጉ የአምራች
ኢንዱስትሪው መዋቅር እንዲዋጥና ትኩረት እንዳያገኝ አድርጎታል፡፡ በተለይ የሀገር
ውስጥ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትና ልማት በአብዛኛው በክልሎች እንዲሰራ ትኩረት
ከመሰጠቱ ጋር ተያይዞ ሴክተሩ ከከተማ ልማትና ንግድ ጋር ተጣምሮ መዋቀሩ
አሁንም ኢንዱስትሪው ተገቢውን የተቀናጀ አመራርና ትኩረት እንዳያገኝ ዕንቅፋት
መሆኑ አይቀርም፡፡ በተጨማሪም ከፌደራል እስከ ክልል እንዲሁም ወረዳ ያለው
የኢንዱስትሪው ሴክተር አወቃቀር ሲታይ ከክልል ክልል ወጥነት የጎደለው እና
በተደጋጋሚ የመበተንና የመደራጀት ችግሮች የሚስተዋልበት ነው፡፡

2. የኢንዱስትሪ ማበረታቻ እና ድጋፍ አቅርቦት


መንግስት ጠንካራ ሀገራዊ ባለሀብት ለመፍጠር የማክሮ-ኢኮኖሚ ማረጋጋት፣ መሰረተ-
ልማት ማስፋፋት፣ የሰለጠነ የሰው ሀይል አቅርቦት፣ የተስማሚ ፋይናስ ስርአት
መዘርጋት፣ ቀልጣፋ የፍትህ ስርአት የመዘርጋት ስራዎችን በመሰራት ላይ ይገኛል፡፡
ሌላው መንግስት ቅድሚያ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ የኢንዱስትሪ ንዑስ ዘርፎችን
በመለየት ድጋፍ እና ማበረታቻ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሰረት የተጠበቀውን
ያህል ባይሆንም የተወሰኑ ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች ለመፍጠር ተችሏል፡፡ ነገር ግን
ለአምራች ኢንዱስትሪ እየቀረበ ያለው ማበረታቻ የዘርፉን ዕድገት እና ተነፃፃሪ
ተመራጭነት በሚፈለገው ርቀት ማሳደግ አልተቻለም፡፡ ማበረታቻዎች በጅምላ
የሚቀርቡና የእያንዳንዱን ንዑስ ዘርፍ ፍላጎት ያላማከሉ እንዲሁም በስብጥርና በመጠን
አነስተኛ የሆኑ ናቸው፡፡ የማበረታቻ ስርአቱ እና አፈፃፀሙ የዘርፉን መዋቅራዊ ለውጥ
በሚያረጋግጥ አቅጣጫ አልተቃኘም፤ የግሉ ባለሀብትም ፊቱን ወደ አገልግሎት፣ ንግድ
እና ሪል እስቴት ዘርፍ ማዞሩን አላቆመም፡፡ በሌላ አገላለፅ የሀገራችን የካፒታል
ክምችት ትንሽ እሴት ወደ ሚጨምረው እና ያለ ድካምና ውጣውረድ በአጭር ጊዜ
ትርፍ ወደሚገኝበት ዘርፍ እንዲሆን እያደረገ ነው፡፡ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ
የሚቀርበው ማበረታቻና ድጋፍ ተወዳዳሪነቱን በሚያጎለብት ሁኔታ ካለመቅረቡ
በተጨማሪ ለጥገኛ ባለሀብቶች መጠቀሚያ የመሆን አዝማሚያ እየታየበት ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ማበረታቻዎች አፈፃፀም ደካማ የሆነበት ዋና ዋና ምክንያቶች ስንመለከት፡
አንደኛ በአምራች ዘርፍ የተሰማራው የግል ባለሀብት ኢንቨስትመንት ሲጀምር፣
ኢንቨስትመንት ሲያስፋፋ፣ ምርት ሲያመርት እና ምርት ለገበያ ሲያቀርብ ከሌላ ዘርፍ
የተሻለ ድጋፍ አለመማግኘቱ፤ ሁለተኛ ማበረታቻው ከተሰጠ በኋላ ለታለመለት አላማ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 6


መዋሉን ክትትልና ቁጥጥር አለመደረጉና አፈፃፀምን መሰረት አድርጎ የማይተገበር
መሆኑ፤ ሶስተኛ መንግስት የፈቀዳቸው ማበረታቻዎች በአብዛኛው ለኪራይ ሰብሳቢው
ባለሀብት የተጋለጡ ወይም የተመቹ መሆናቸው ነው፡፡ በጥቅሉ ዋናው መሰረታዊ ችግር
አገልግሎት ሰጪውና ጥቂት የማይባሉ የግል ባለሀብቶች ኪራይ በመሰብሰብ ላይ
ስለተጠመዱ ማበረታቻዎች በትክክል ተግባራዊ አልተደረጉም፡፡ስለዚህ አመራሩ
ልማታዊ ባለሀብቱን ከጥገኛ ባለሀብቱ ለይቶ ማበረታታት እንዳልቻለ እና ጥገኛ
ባለሀብቱን የማክሰም ስራ በደንብ እንዳልተሰራ ያመላክታል፡፡

3. የፋይናንስና ብድር አቅርቦት


የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ መዋቅር ለማረጋገጥና በቀጣይነት የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት
ፋይናንስ አስፈላጊ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ የሀገራችን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ
በመጠንም ሆነ በጥራት እያደገ የመጣ በመሆኑ ከፍተኛ ካፒታል የሚጠይቁ
ኢንቨስትመንቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ
በሀገራችን የቁጠባ ባህልና የባንኮች የማበደር አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ
መጧል። በሁለተኛው አምስት ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን
በአጠቃላይ ወደ 1.9 ትሪሊዮን ብር እንደሚሰበሰብ እንዲሁም ለኢኮኖሚ ዘርፎች
በአጠቃላይ ወደ 1.68 ትሪሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ታቅዷል፡፡ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ
ከተደረገው የፋይናንስ ድልድል ውስጥ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት
የተሰጠው በመሆኑ በዕቅዱ ዘመን በአጠቃላይ 502.8 ቢሊዮን ብር የተመደበለት ሲሆን
ይህም ከ2007 መነሻ ግምት 30.1 ቢሊዮን ብር በዓመት በአማካይ የ41.4 በመቶ
ዕድገት በማሳየት በ2012 ዓ.ም 156.9 ቢሊዮን ብር እንደሚደርስ ዕቅዱ ያሳያል፡፡
በተጨማሪም ለሀገር ውስጥ ብድር ይውላል ተብሎ ከተቀመጠው በ2008 ዓ.ም 64
በመቶ ለግሉ ዘርፍ ቀሪው 36 በመቶ ለመንግሰት ልማት ድርጅቶች እንደሚውል
ተቀምጧል፡፡

በቅርቡ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ተቋማት ያላቸው የዋስትና ማስያዣ (collateral)


ግምት ውስጥ ያስገባ የሊዝ ፋይናንስ በልማት ባንክ መጀመሩና በም/ፕሬዝዳንት
እንዲመራ መደረጉ ጥሩ ቢሆንም በዚህ የብድር ስርዓት በ2008 ዓ.ም ሊሰጥ ከታቀደው
4.6 ቢሊዮን ብር የተሰጠው 2.24 ሚሊዮን (0.05 በመቶ) ብቻ ነው። ለዚህ አፈፃፀም
አናሳነት ዋናው ምክንያት የሊዝ ፋይናንስ ዘግይቶ በመጀመሩ የዝግጅት ወቅት መሆኑ
የባንኩ ሀላፊዎች ይገልፃሉ፡፡ ሆኖም የባንኩ በ2009 የ9 ወራት የሊዝ ፋይናንስ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 7


አፈፃፀም ስንመለከት ለባንኩ የቀረበለት የብድር ጥያቄ 6.98 ቢሊዮን ሲሆን ተቀብሎ
ያፀደቀው 2.5 (37 በመቶ) ቢሊዮን በተጨባጭ ለተጠቀሚዎች ያሰራጨው ደግሞ 330
ሚሊዮን ወይም ከቀረበለት ጥያቄ ውስጥ 4.7 በመቶ ብቻ ነው፡፡ በልማት ባንክ ባለፉት
አምስት ዓመታት ብድር ለመስጠት ካቀደው ውስጥ በየዓመቱ የሚሰጠው ከ50% በታች
ካፀደቀው ብድር ውስጥ ደግሞ ባለፉት 11 ዓመታት በአማካይ 62% ብቻ ወደ ተጠቃሚ
አድርሷል፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያት የብድር ፍላጎት ባለመኖሩ ሳይሆን የባንኩ
አሰራር እጅግ ውጣወረድ የበዛበት እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያልተደገፈ፣ ወስብስብ እና
ግልፅነት የጎደለው መሆኑን ተጠቃሚዎች ይገልፃሉ፡፡

በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የባለሀብቱ መዋጮ ለአምራች ዘርፍ 25%፣ ለአነስተኛና


መካከለኛ በተለይ ለሊዝ ፋይናንስ 20% እንዲሆን የተደረገው አዲስ ማሻሻያ መልካም
ጅማሮ ቢሆንም የግሉ ዘርፍ የሞተርነት ሚናውን እንዲወጣ ከማስቻል አንፃር
ማሻሻያው በቂ አለመሆኑ እና በአፈፃፀም ላይ ጉድለቶች ያሉበት ነው፡፡ የባንኩ የብድር
ወለድ መጠን 12% እንዲሆን መደረጉ የሀገራችን አምራች ዘርፍ አቅም ያላገናዘበና
በጣም ከፍተኛ መሆኑ ነው፡፡ ምንም እንኳ ባንኩ በተለየ ሁኔታ ምርታቸው ወደ ውጪ
ለሚልኩ፣ እንዲሁም የተመረጡ የውጪ ምርት የሚተኩ እና በjoint venture
የተቋቋሙ የተለየ የወለድ መጠን (9-9.5 በመቶ) የተቀመጠ ቢሆንም፤ ይህም በራሱ
በአምራች ዘርፍ ፈጣን እድገት ካሳዩት የምስራቅ ኤስያ ሀገራት ጋር እና የኢትዮጵያ
ንግድ ባንክ አገልግሎት ጨምሮ ለሁሉም ዘርፍ ከሚያስከፍለው 9.5% የወለድ መጠን
ጋር ሲወዳደር ከፍተኛ ነው፡፡ በአምራች ዘርፍ ስኬታማ የሆኑ የምስራቅ ኤስያ ሀገራት
ተሞክሮ ለምሳሌ በታይዋን በመጀመሪያዎቹ የዕድገት ዘመናት እ.ኤ.አ ከ1963-1973
የአምራች ዘርፍ የነበረው የብድር ወለድ 7.5 የነበረ ሲሆን ለሌሎች ዘርፎች የነበረው
አነስተኛ የወለድ መጠን 14% ነበር፡፡ የታይዋን ኤክስፖርት ከገቢ ንግድ በላይ
በሆነባቸው 1990ዎች ጭምር ለአምራች ዘርፍ በተለይ ለኤክስፖርት የነበረው የብድር
ወለድ መጠን አነስተኛ ነው፡፡ በተመሳሳይ የደቡብ ኮሪያና ሲንጋፖር ለአምራች ዘርፍ
የሚሰጠው የብድር ወለድ ከሌሎች ዘርፎች አንፃር በእጅጉ ያነሰ መሆኑን መረጃዎች
ያሳያሉ፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተነፃፃሪ ለሁሉም ዘርፎች የብድር ወለድ ልማት
ባንክ ከቀረበው የብድር የወለድ ያነሰ 9.5% እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ
ያለው ሌላው የአተገባበር ችግር አምራቾች 12% ወለድ ሲከፍሉ ከቆዩ በኋላ ምርታቸው
ወደ ውጪ ሲልኩ በዓመቱ መጨረሻ የላኩትን ምርት መጠን ካቀረቡ በኋላ ተቀናሹ
እንደሚመለስላቸው አሰራሩ የሚፈቅድ ቢሆንም እንዴት እንደሚመለስ፣ መቸ እና በምን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 8


መልኩ እንደሆነ በግልፅ ያልተቀመጠና በተግባር ያልተጀመረ መሆኑን ባለሀብቶች
ይገልፃሉ፡፡

4. የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦት፡


በሀገራችን የግብርና ውጤቶች በተለይ ለአምራች ኢንዱስትሪው በበቂ አቅርቦት፣
በጥራትና ተወዳዳሪ በሆነ ዋጋ እየቀረበ አለመሆኑን በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ
ባለሀብቶቸ እና የክልል ግብርና ቢሮዎች ይገልፃሉ፡፡ አብዛኞቹ ትኩረት የተሰጣቸው
አምራች ኢንዱስትሪዎች (የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎች፣ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች
ኢንዱስትሪዎች፣ የምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎችና ሌሎችም) በዋናነት የግብርናውን
ምርት በግብአትነት የሚጠቀሙ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ እነዚህ ኢንዱስትሪዎች
ግብአት የሚያገኙባቸውን አማራጮች ስንመለከት በመጀመሪያ አርሶአደሩ በአነስተኛ
ማሳ ከሚያመርተው ምርት፣ አርብቶአደሩና ከፊል አርብቶአደሩ በተለምዶ
ከሚያመርተው የእንሰሳት እርባታ ውጤት (ቆዳና ሌጦ)፣ ከግብርና ሰፋፊ
ኢንቨስትመንት እና ከውጭ የሚገቡ ናቸው፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ሁሉም
አማራጮች ያለውን የአምራች ኢንዱስትሪ የግብአት ፍላጎት ከማሟላት አኳያ ሰፊ
ክፍተት አለባቸው፡፡

በአርሶአደሩ አነስተኛ ማሳ እየተካሄደ ያለው የሰብል ልማት በሀገሪቱ የሚገኙ ጥቂት


አምራች ኢንዱስትሪዎችን እንኳ የሚመግብ የግብአት አቅርቦት ዓቅም አልፈጠረም፡፡
በሀገራችን ጥጥ፣ ቆዳና ለአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ግብአት የሚውሉ የግብርና
ምርቶችን ለማምረት የሚያስችል ዕምቅ ሀብት ያለ ቢሆንም በሚፈለገው ጥራት፣
መጠንና ዋጋ ለአምራች ኢንዱስትሪ ማቅረብ አልተቻለም።የግብርና ምርቶች ለአምራች
ኢንዱስትሪው ተወዳዳሪ በሆነ ዋጋ አለመቅረቡ እንደ አንድ ምክንያት የሚነሳው ጉዳይ
የተዛባ የገበያ ስርአት መኖሩ ነው፡፡ ደላላዎች በሚፈጥሩት አላስፈላጊ፣ ረጅምና እሴት
የማይጨምር የግብይት ሰንሰለት ምክንያት የምርቶች ዋጋ የተጋነነ እንዲሆን እና
የገበያ ስርአቱ በውድድር እንዳይመራ እያደረገው ይገኛል፡፡ ረጅምና እሴት
የማይጨምር የግብይት ሰንሰለት ግብይቱ በውድድር እንዳይመራ ስለሚያደርግ በዋጋ
የሚታይ ችግር በጥራትም ተመሳሳይ ተፅኖ እየፈጠረ መሆኑን አምራቾች ገልፀዋል፡፡
ምርቱ በታሰረ ሰንሰለት በመያዙ አምራቾች አማራጭ እንዳይኖራውና በተሻለ ጥራት
አወዳድረው ማግኘት እንዳይችሉ ያደረጋቸው መሆኑን ይገልፃሉ። በሰፋፊ እርሻዎች
የሚመረቱ የኢንዱስትሪ ግብአቶችን በምናይበት ጊዜ ከ1996 ዓ.ም እስከ 2ዐዐ7 ዓ.ም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 9


አጋማሽ ድረስ ለባለሀብቶች የተሰጠ የመሬት ስፋት 2.45 ሚሊዮን ሄክታር ቢደርስም
ከተሰጠው መሬት እስካሁን የለማው ከ9ዐዐ,ዐዐዐ ሄክታር (37%) የማይበልጥ ነው፡፡
ምክንያቶቹን ስንመለከት፡ 1) ከመንግስት በቂ ክትትልና ድጋፍ አለመደረጉ፣ 2)
ባላለሙ ባለሀብቶች ላይ ተመጣጣኝ እርምጃ አለመወሰዱ እና 3) ጥራት ያለው
ባለሀብት በዘርፉ ባለመሰማራቱ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

አምራች ኢንዱስትሪዎች ከሚጠቀሙት ግብአት በዋጋ 45.23 በመቶ የሚሆነው በሀገር


ውስጥ በሚገኝ ጥሬ ዕቃ የሚሸፈን ሲሆን ቀሪው 54.77 በመቶ የሚሆነው ወጪ ደግሞ
ከውጪ ሀገር የሚገባ ጥሬ ዕቃ ነው (ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ 2006 ዓ.ም)።
የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቱ ከውጭ ሀገር ግብአት ለማሰገባት የውጭ ምንዛሬ
ዕጥረት መኖሩ ትልቅ ችግር እንደሆነባቸው ይገልፃሉ፡፡ የአምራች ባለሀብቱ የውጭ
ምንዛሬ የሚያገኘው ሸቀጣሸቀጥ ከሚያስገቡ አስመጪዎች ጋር እኩል ተሰልፎ ነው፡፡

5. የአምራች ኢንዱስትሪ ምርት ገበያና የንግዱ ስርአት


የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ተወዳዳሪነት እና ምርታማነት በዘላቂነት ለማሳደግ
ቀልጣፋ፣ ውጤታማ እና ፍትሃዊ የገበያ እና የንግድ ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊና
ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው፡፡ ጠንካራ የገበያና የንግድ ስርዓት ለመገንባት ደግሞ
የንግድ አሰራርን ምቹ ማድረግ፣ ለየገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ጥራትና ደረጃ መጠበቅና
ማሻሻል፣ ከአለማቀፍ ንግድ የሚመነጩ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን መቆጣጠር፣ የገቢ-
ምርቶች ስብጥርና መጠን ከልማት ፋላጎት ጋር እንዲጣጣም ማድረግ፣ የኢንዱስትሪ
ተቋማት አደረጃጀት እንደየ ንኡስ ዘርፎቹ ባህሪ ማስተካከል፣ በገበያ ሰንሰለት ላይ ያሉ
ተዋንያን መካከል የተሳለጠ ትስስር መፍጠር፣ ለኢንዱስትሪው አመች የገበያ ዕድል
የሚፈጥር የመንግስት ግዥ ፓሊሲ መቅረፅ፣ በገበያ ሰንሰለቱ ላይ የሚታዩ የመረጃና
የቅንጅት ችግሮን መቅረፍ እና ተያያዥ ተግባራትን ማከናወን አስፈላጊ መሆኑን
መረጃዎች ያሳያሉ። ስለሆነም በጥናቱ የተለዩ ዋና ዋና የንግዱ ስርአት ችግሮች
ያሉበትን ሁኔታ ለማየት ተሞክሯል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪ ምርት ጥራት እና ደረጃ፡ የሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪ


ከተጋረጡበት ዋነኛ ችግሮች አንዱ በአለማቀፍ ወይም በብሄራዊ ደረጃ የተቀመጡ
የጥራት እና ደረጃ መስፈርቶችን የማያሟሉ የሀገር ውስጥ እና ኢንፓርት የተደረጉ
ምርቶች በገበያ ላይ መበራከት ነው፡፡ እነዚህ ጥራትና ደረጃ ያልጠበቁ ምርቶች (sub-
standard products) በገበያ ላይ መገኘት ደግሞ ህግ እና ስርአት ተከትለው ጥራትና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 10


ደረጃውን የጠበቀ ምርት በሚያመርቱ የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች ዕድገት፣
ትርፋማነት እና አለማቀፍ ተወዳዳሪነት ላይ ተፅዕኖ ማሳደራቸው አልቀረም፡፡ በ2008
ዓ.ም አስገዳጅ የጥራት ደረጃ የተዘጋጀላቸውን ምርቶች ጥራት ለመፈተሸ በናሙናነት
ከተወሰድ 134 ፋብሪካዎች ውስጥ 18(13%) የሚሆኑት ደረጃውን ያልጠበቀ ምርት
በማምረት ላይ ነበሩ ፡፡ ሆኖም ከፋብሪካዎች ይልቅ ለገበያ ከቀረቡ ምርቶች
የተሰበሰቡ መረጃዎ የጥራት ችግር ከፍተኛ መሆኑን ይጠቁማሉ፡፡ በ2008 ዓ.ም በ10
ከተሞች የአስገዳጅ ደረጃ ከወጣላቸው የምርት ዓይነቶች (ማለትም ቆርቆሮ፣ አርማታ
ብረት፣ ምስማር፣ የታሸገ ውሀ፣ የምግብ ዘይት፣ ሲሚንቶ፣ ኤሌክትሪክ ገመድ፣ ክብሪት
እና ሳሙና) ላይ ናሙና ተወስዶ በተካሄደ የገበያ ላይ ዳሰሳ ጥናት 55% የሀገር ውስጥ
ምርቶች እና 100% የውጭ ሀገር ምርቶች የጥራት ደረጃ ያላሟሉ መሆናቸው ከንግድ
ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡ ከዚህ መገንዘብ እንደሚቻለው ከውጭ የሚገቡ
ምርቶች የጥራት ችግር ልቆ መገኘቱ ጀማሪ የሀገር ውስጥ አምራቾች እድገት የሚገታ
እና ከገበያ እንዲወጡ የሚያደርግ አዝማሚያ እንዳለ ያሳያል፡፡

የንግድ አሰራር ስርአት፡ የነጻ ገበያ ስርአት ለሚያራምድ ኢኮኖሚ ጤናማ የንግድ
አሰራር ማረጋገጥ የኢንዱሰትሪ ልማት ለማረጋገጥ አይነተኛ ግብአት ተደርጎ
ይወሰዳል፡፡ ደካማ የንግድ አሰራር ባለበት ነባራዊ ሁኔታ ተገቢ ያልሆነ የንግድ
ውድድር (unfair competition)፣ በበላይነት የተያዘ ገበያን ያለአግባብ መጠቀም፣
በቡድን የገበያ ዋጋን እና ምርትን ያላግባብ መወሰን እና ተያያዥ ጉዳዮች
መገለጫዎች ናቸው፡፡ ስለሆነም ፍትሃዊና ቀልጣፋ የንግድ አሰራር ለማስፈን ተገቢ
የሆነ ውድድር መፍጠር፣ በበላይነት የተያዘ ገበያን ያለአግባብ እንዳይጠቀሙ
መቆጣጠር፣ በቡድን በመሆን ዋጋ እና ምርት የሚወስኑ አካላትን መከላከል ጠንካራ
የንግድ ስርአት ለመገንባት አጋዥ ነው፡፡ የሀገራችን የንግድ አሰራር ስርአት ውጤታማ፣
ጠንካራ እና ብቃት ያለው ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡ በመጀመሪያ ተገቢ ያልሆነ
ውድድር (unfair competition) በገበያ ላይ እያጋጠመው እንደሆነ እና ለዚህም ችግሩን
ለመፍታት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች አመርቂ እንዳልሆኑ በባለሀብቱ ይነሳል፡፡
በአስመጭዎች፣ በንግድ እንደራሲዎች እና በንግድ ወኪሎች የሚደረገው የተዛባ የውጭ
ምርት ማስተዋወቅ ስራ በሀገራዊ ምርቶች ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩን ባለሀብቱ እና የዘርፍ
ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ እነዚህ አካላት የተለያዩ የመንግስት እና የግል መገናኛ
ብዙሀንን እንደ መሳሪያ በመጠቀም የውጭ ምርቶች ጥራት የበላይነት እንዲሁም የዋጋ
ተመጣጣኝነት በማጉላት፣ የውጭ ሀገር ምርቶች የተሻሉ እንደሆኑ አድርጎ ለተጠቃሚው

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 11


በማቅረብ እና ሸማቹ ማህበረሰብ ለሀገር ውስጥ ምርት የተዛባ አመለካከት እንዲኖረው
በማድረግ በሀገር ውስጥ ምርት ተቀባይነት እና በሸማቹ ህብረተሰብ የግዥ ፍላጎት ላይ
አሉታዊ ተፅኖ ፈጥሯል፡፡ በዚህ ምክንያት ተፈላጊውን የጥራት እና ዋጋ አሟልተው
የሚያቀርቡ ሀገራዊ አምራች ኢንዱስትሪዎች ተገቢውን ጥቅም ማግኘት እንዳልቻሉ
ይገለፃል፡፡ ሁለተኛው በሀገራችን ተገቢ ያልሆነ የንግድ ውድድር ተግባር ምንጩ
ያልታወቀ፣ ተመሳስሎ የተሰራ እና ደረጃውን ያልጠበቀ ምርት በገበያ ላይ መበራከት
ነው፡፡ ሶስተኛው ተገቢ ያልሆነ የንግድ ውድድር መገለጫ መስመር የለቀቀ
የኮንትሮባንድ ንግድ ሲሆን ኮንትሮባንድን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚደረጉ
ጥረቶች ዘላቂነት የጎደላቸው ናቸው፡፡

ከአለማቀፍ ገበያና ንግድ የሚመነጩ ተፅዕኖዎች፡ ሀገሪቱ የነጻ ገበያና ንግድ


የሚያጎለብቱ ፓሊሲዎች ተግባራዊ እያደረገች ብትገኝም የፓሊሲ ለውጦችን ተከትለው
ከአለማቀፍ ገበያና ንግድ ስርአት የሚመነጩ የጎንዮሽ ጉዳቶችን ለመለየት የሚያስችል
በየጊዜው ተፅኖ አማላካች ጥናት (Impact Assessement) አይካሄድም፡፡ በተጨማሪ
የገበያ ከለላ መቀነሱን ተከትሎ ገቢ-ምርቶች በሀገራችን የአምራች ኢንዱስትሪ ዕድገት
ላይ ሊያስከትሉ የሚችሉትን አሉታዊ ተፅኖ ለመቆጣጠር የሚያስችል ግልፅ ፓሊሲ እና
አደረጃጀት እንደሌለ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡በንፅፅር ለኢንዱስትሪ ልማት ትኩረት የሰጡ
ብዙ ታዳጊ ሀገራት ከገቢ-ምርቶች የሚመነጭ ኢ-ፍትሃዊ ውድድር ለመቆጣጠር
የሚያስችል ፓሊሲ ቀርፀው ተግባራዊ ሲያደርጉ ይታያል፡፡ በሀገራችን የተደረጉ ውስን
ጥናቶች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች እና አምራቾች የተገኘ መረጃ እንደሚጠቁመው የገቢ
ምርቶች የሚፈጥሩት ድንገተኛ ማጥለቅለቅ (sudden import surge)፣ ዝቅተኛ ዋጋ
በገፍ የሚገቡ ምርቶች (dumped products) እና በመንግስታት ተደጉመው የሚገቡ
ምርቶች ኢፍትሃዊ የንግድ ውድድር (effects of subsidized products) እየጨመረ
መምጣቱን ነው፡፡

የአክሲዮን ማህበራት አደረጃጀት፡ የአክስዮን ማህበራት አደረጃጀት ከሌሎች


አደረጃጀቶች በተሻለ ከፍተኛ ዕውቀት፣ ካፒታልና ቴክኖሎጅን የማቀናጀት ሚና
እንዳለው ይታወቃል፡፡ ትንሽ የካፒታል አቅም ያላቸውን ዜጎች በማሰባሰብ የረጅም
ጊዜ ቁጠባ እና ኢንቨስመንት ባህል ያዳብራል፣ የአደረጃጀት ባህሪው ከአክሲዮን
ባለቤቶች ይልቅ በባለሙያዎች (professionals) አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲመሩ
ያስቻላል እንዲሁም ግዙፍ እና ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪዎች እንዲፈጠሩ ያደርጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 12


የሀገራችን የአምራች ኢንዱስትሪ በግል ባለሀብቶች ተመራጭ ያልሆነበት ዋና ምክንያት
የላቀ ካፒታል፣ ቴክኖሎጅና ዕውቀት ስለሚጠይቅ ነው፡፡ አክሲዮን ማህበራት ይህን
ችግር ለመቅረፍ አይነተኛ ሚና አላቸው፡፡ በመሆኑም የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን
በአክስዮን እንዲደራጅ መደገፍ እና መቀስቀስ ከላይ የተገለፁትን ግብአቶች ለማሰባሰብ
በማስቻል የስትራቴጂ ጠቀሜታ ባላቸው ትላልቅ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለማጎልበት
ያስችላል፡፡ ነገር ግን የአክሲዮን ማህበራት ውጤታማ ያልሆኑበት ምክንያቱ፡ 1)
የአክስዮን ማህበራት አስተዳደርና አመራር (corporate governance) ችግር፣ 2)
የአክስዮን ማህበራትን ለመቆጣር የወጡ ህጎች ወቅታዊ ማሻሻያ እና በአግባቡ ተፈጻሚ
ያለመሆንና ህጎችና ደንቦች የማስፈፀሚያ መመሪያ አለመኖር (ለምሳሌ በአይነት
የሚደረጉ መዋጮዎች ዝውውር ጊዜ ገደብ አለመወሰን፣ ከአክሲዮን አባላት ለመውጣት
ለሚፈልጉ ገንዘብ አመላለስ ችግር) እና 3) መንግስት ለአክስዮን ማህበራት ቴክኒካዊ
ድጋፍ ለማድረግ፣ ለመከታተልና መቆጣጠር የሚያስችል የአመራር እና አቅም
ውስንነት መኖር ናቸው፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ምክንያቶች ህብረተሰቡ ለአክስዮን
ማህበራት ያለው አመለካከት የተዛባ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ በመሆኑም የሀገር ውስጥ
ባለሀብቱን በአክስዮ ማህበር በስፋት ማደራጀት አልተቻለም፡፡

የንግድ የፈቃድ ስምሪት፡ የንግድ ፈቃድ ስምሪት ሚዛናዊ በማድረግ የገበያ ውድድርን
ውጤታማ እና ብቃት ያለው ማድረግ ነው፡፡ በገበያ ሰንሰለት ላይ የተጨናነቀ የንግድ
ስምሪት የሚስተዋልበትን ዘርፍ (crowd out sub-sector) በመለየት እና የሳሳ ስምሪት
ወደ አለበት ዘርፍ እንዲሰማራ በማድረግ ቀልጣፋና ውጤታማ የንግድ ስርአት ማዳበር
ይቻላል፡፡ የንግድ ፈቃድ ድልድል ማድረግ ሌላው ፋይዳ ሞኖፓሊ፣ በህብረት መወሰን፣
የገበያ የበላይነትን ያላግባብ መጠቀም እና ጎጅ ውህደት የመሳሰሉ ፀረ-ውድድር
ተግባራትን ለመከላከል ያግዛል፡፡ ነገር ግን በሀገራችን ያለው የንግድ ፈቃድ አሰጣጥ
የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ የሚሰማራበትን ዘርፍ አቅጣጫ ለመወሰን ጥረት ሲያደርግ እና
የኢኮኖሚ ልማት በሚያግዝ መልክ የንግድ ፈቃድ ድልድል ሲደረግ አይስተዋልም፤
ምንም እንኳን በነፃ ኢኮኖሚ ስርአት ባለሀብቱ በሚያዋጣው የንግድ ዘርፍ የመሰማራት
መብት ቢኖረውም፡፡በሌላ አገላለፅ አምራች ኢንዱስትሪው በሚገኝበት የገበያ ሰንሰለት
ላይ የተጨናነቀ የንግድ ስምሪት የሚታይበትን ዘርፍ (crowded sector) በመለየት
የሳሳ ስምሪት ወደ አለበት ዘርፍ እንዲሰማራ ጥረት አይደረግም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 13


የመንግስት ድጋፍ እና ገበያ ከለላ፡ ለውጭ ገበያ የሚያመርቱ እና ገቢ-ምርት ለሚተኩ
ኢንዱስትሪዎች ድጋፍ እና ገበያ ከለላ ለመስጠት በማሰብ መንግስት ቀረጥን እና
ታክስን በመሳሪያት ሲጠቀም ይስተዋላል፡፡ የመንግስት ድጋፍ እና ገበያ ከለላ አላማ
የአምራች ኢንዱስትሪው ጥራት ያለው ግብአት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ እና
ለሚያመርተው ምርት ገበያ ለመፍጠር ነው፡፡ ነገር ግን የመንግስት ድጋፍ እና የገበያ
ከለላ አቅርቦት የአፈፃፀም ብቃትን መሰረት አለማድረጉ እና ጠንካራ ክትትልና ቁጥጥር
አለመኖሩ የልማታዊ የባለሀብቱን ተጠቃሚነት በሚፈለገው ደረጃ አላረጋገጠም፡፡

በአንድ በኩል የገበያ ከለላው የዘርፉን ኢንቨስትመንት እና ምርት ከማሳደግ ይልቅ


የገበያ ውድድሩን በማጥበብ ትርፍ የመሰብሰብ አዝማሚያ (ለምሳሌ በሲሚንቶ ዘርፍ
እና የብረታብረት ግብአት ዘርፍ) ፈጥሯል፡፡ በሌላ በኩል መንግስት ኤክስፓርት ዘርፍ
ቢያበረታታም በሀገር ውስጥ ገበያ የመወሰን አዝማሚያ ይታያል፡፡ ለምሳሌ
የጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪ ላለፍት አራት ዓመታት የውጭ ምንዛሬ ግኝት
እየተቀዛቀዘ ለመሄዱ ከተጠቀሱት ምክንያቶች አንዱ የሀገር ውስጥ የገበያ ዋጋ
ከውጭው ገበያ በልጦ በመገኙቱ ፋብሪካዎች ፊታቸውን ወደ ሀገር ውስጥ ገበያ ማዞር
መጀመራቸው ነው፡፡ ሌላው የቀረጥ ነፃ ተጠቃሚ የሆኑ የአምራች ኢንዱስትሪ እና
ሌሎች ዘርፎች ከውጭ ለሚያስገቧቸው የግንባታ እና የካፒታል እቃዎች ለሚፈለገው
አገልግሎት ሳያውሉ ህጋዊ መብት ለሌለው አካል በማስተላለፍ በገበያ ላይ ኢ-ፍትሃዊ
ውድድር የመፍጠር አዝማሚያ ታይቷል።

የመንግስት ግዥ ስርአት፡ የመንግስት ግዥ ስርአት ለአምራች ዘርፍ ተወዳዳሪነት፣


ምርታማነትና እና የቴክኖሎጅ አቅም ለማጎልበት የሚያግዝ የፓሊሲ መሳሪያ ተደርጎ
ይወሰዳል፡፡ በዚህ ረገድ የበለጸጉት ሀገራት የግዥ ፓሊሲያቸውን ለኢንዱስትሪ ልማት
አሟጠው ከመጠቀም አልፈው ለቴክኖሎጂ ዕድገትና ፈጠራ አቅም ግንባታ
ተጠቅመውበታል፡፡ በተመሳሳይ በፈጣን ዕድገት ላይ የሚገኙት የኤሲያ ሀገራት
የመንግስት ግዥ ፖሊሲያቸውን ለጀማሪ ኢንተርፕራይዞች ከለላ፣ አለማቀፍ
ተወዳዳሪነት እና የስራ ፈጠራ ዕድል ማሳደጊያ ተጠቅመውበታል፡፡ የመንግስት ግዥ
ፓሊሲን ወጭ ቆጣቢ፣ ውጤት ተኮር እና ግልፅ ውድድር መርህን ሳያጓድል አምራች
ኢንዱስትሪውን መደገፍ ከሌሎች ማበረታቻዎች በተሻለ ዘርፉን ውጤታማ ያደርጋል
ተብሎ ይታመናል፡፡ ሀገራችን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገቧን ተከትሎ
የመንግስት የገቢ ምንጭ እና የመግዛት አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ ነው፡፡ ለአብነት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 14


በመንግስት አመታዊ በጀት (government expenditure) ውስጥ የግዥ ወጭ
ከፍተኛውን ድርሻ ሲይዝ በአማካይ 64% ያህሉን አመታዊ በጀት ለግዥ ተግባር
እንደሚጠቀም ይገመታል፡፡ ይህ አቅም የአምራች ዘርፍ ዕድገት ለማፋጠን ፋይዳው
የጎላ ይሆናል፡፡

የግዥ ፓሊሲው የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪን ለማበረታታት ብዙ ማሻሻያዎች


ያስፈልጉታል፡፡ ለምሳሌ በአለማቀፍ ጨረታ ሁለቱም አካላት በተመሳሳይ መንገድ
መመዘን እና በብሄራዊ ጨረታ ግምገማ ወቅት ሀገር በቀል አምራቹን የዋጋ ልዩ ድጎማ
አለመስጠት፣ ለሀገር ውስጥ ምርት አቅራቢዎች ብቃትን መሰረት ያደረገ የልዩ
አስተያየት (preferential qualification requirement) አለማካተት፣ ለሀገር ውስጥ
ባለሀብት አሳሪ የሆነ የብቃት መመዘኛ መስፈርት መጠቀም፣ ወዘተ ይገኙበታል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ በሀገራች የመንግስት መ/ቤቶችና ፕሮጀክቶች አመታዊ የግዥ በጀት
በመጠቀም የሀገር ውስጥ ምርት እንዲገዙ የሚያደርግ አስገዳጅ ስርአት ባለመኖሩ
የሀገር ውስጥ ምርትን ገዝቶ የመጠቀም ዝንባሌ አናሳ ሆኖ ይገኛል፡፡ የፌደራል ግዥ
ፓሊሲ የኢትዮጵያን ይግዙ (Buy Ethiopian) መርህ ባለኖሩ መ/ቤቶች በግዥ ዕቅድ
እና አፈፃፀም ሪፖርት ውስጥ የሀገር ውስጥ ምርት ግዥ ድርሻ በየጊዜው እንዲያድግ
የሚያደርግ ስርአት አላዳበሩም።

6. በአምራች ኢንዱስትሪ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት


ብዙ ፀሀፊዎች ለአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኙ የቴክኖሎጂ ዕድገት መሆኑን
ይስማማሉ፡፡ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት የቴክኖሎጂ አጠቃቀማችን ፈጥኖ
ማደግ አለበት፡፡የሀገራችን ሁለንተናዊ ልማት የሚጠይቀው የቴክኖሎጂ ግብአት በተለይ
ኢንዱስትሪው በማቆጥቆጥ ላይ ያለና ጀማሪ በመሆኑ ቅድሚያ ትኩረት የተሰጠው
የቴክኖሎጂ ኩረጃ ነው፡፡ በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራው የሀገር ውስጥ ባለሀብት
በተሰማራበት የስራ ዘርፍ በአለማቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ከሚያስችሉት ጉዳዮች
አንዱ ተስማሚ የሆነ የቴክኖሎጂ አቅርቦት ማመቻቸት እና ተጠቃሚ ማድረግ ነው፡፡
በሀገራችን በተለይም በአምራች ኢንዱስትሪው የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ቢያንስ
ሁለት ጉዳዮች ላይ ማተኮር ያሻል፡፡ አንደኛው ቴክኖሎጂውን መቅሰም የሚችል ብቁ
የሰው ሀይል እንዲኖር ማድረግና ሁለተኛው ደግሞ አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ
የተሰማራው የሀገር ውስጥ ባለሀብት ለአዳዲስ ቴክኖሎጂዎችና አሰራሮች በሩን ክፍት
እንዲያደርግ ማስቻል ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 15


የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች በየዘርፉ የተቋቋሙ የምርምር ኢንስቲትዩቶች
የሚሰጡት ስልጠና ንድፈ-ሐሳባዊ እንጂ አምራቹን ላጋጠመው ችግር መፍትሄ የሚሆን
በሙያ ክህሎት ስልጠና ላይ ያተኮረ ባለመሆኑ አጋዥ እንዳልሆነ ይገልፃሉ፡፡ ድጋፎች
መሰረታዊ ለውጥ የማያመጡና ተደራሽነታቸውም ጠባብ ነው፡፡ በልማት
ኢንስቲትዮቶች የሚታዩ ሁለት ክፍተቶች፡ 1) ከተቋቋሙበት ተቀዳሚ ዓላማ ወጥተው
የፋሲሊቴሽን ስራ ላይ የተጠመዱ መሆኑ፤ 2) በኢንስቲትዩቶች ያሉት ተመራማሪዎች
አቅምና ተነሳሽነት ማነስ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል የዩኒቨርስቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር
(Industry-University Linkage) ለኢንተርሽፕ ተማሪ መመደብ ባለፈ ኢንዱስትሪዎችን
በቴክሎጂ ሽግግር ከመደገፍ አንጻር የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ አይደለም፡፡ ይህም
የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች በታቀደ ሁኔታ እየተተገበሩ ላለመሆኑ አንዱ ማሳያ ነው፡፡
የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት ስራ ሁሉን አቀፍ የሆነ የፖሊሲ አቅጣጫ ተዘጋጅቶለት
እንዲሁም በባለቤትነት አቀናጅቶ የሚመራው አደረጃጀትና ተቋም ያስፈልገዋል፡፡
በተጨማሪም በየወቅቱ ምን ያህል የቴክኖሎጂ ሽግግር እንደተደረገ የሚለካበትና
የሚገመገምበት የአሰራር ስልት አልተቀየሰም፡፡

7. በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ አቅምና ድርሻ


አብዛኛው በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማራው ባለሀብት በዘልማድ የንግድ ስራ ለበርካታ
ዓመታት የቆየ በመሆኑ ዘርፉን ሲቀላቀል በልምድ እንጂ በተሟላ ዕውቀት ላይ
ተመስርቶ አይደለም፡፡ በመሆኑም የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ የዕውቀት፣ ክህሎትና
የአመራር ውስንነት ይስተዋሉበታል፡፡ የስራ ፈጠራ ችሎታ እንዲሁ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ
የሚገኝ፣ አዳዲስ ፕሮጀክት የመቅረፅ እና የመተግበር ብቃት ያለመኖር እና ባለሙያና
አማካሪ ቀጥሮ የማሰራት ልምድ የለውም፡፡ በመሆኑም በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ትርፍ
በሚያስገኘው የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለመሰማራት ይቸገራል፡፡ በተጨማሪም
የሂሳብ አያያዝ ስልት ደካማነት፣ ገበያን የመተንተን አቅም ማነስ፣ አለማቀፍ የገበያና
የቴክኖሎጂ ሁኔታን በውል ያለመረዳት የግሉ ባለሀብቱ በአምራች ዘርፍ ውጤት
ማምጣት እንዳይችል ማነቆ ሁኖበታል።

ከዕውቀት፣ ክህሎት እና አመራር ጋር ከተያያዙ ችግሮች በተጓዳኝ ሀገራዊ ባለሀብቱ


የአመለካከት ችግር በሰፊው ይንፀባረቅበታል። ለአብነት በሰከነና በቁርጠኝነት
ኢንተርፕራይዞችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ዳተኝነት፣ የመንግስትን ድጋፍና
ማበረታቻ ጠባቂነት፣ በአጭር ጊዜና በአቋራጭ ትርፍ ለመሰብሰብ መዳዳት እና
የመንግስትን ድጋፍ ላልታለመለት አላማ የማዋል ዝንባሌ እና ተያያዥ ችግሮች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 16


ተስተውለዋል፡፡ በሌላ በኩል የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ከግል ባለሀብቱ ጋር
ተቀራርቦ የመስራት፣ ሞዴል ባለሀብት በዘርፉ እንዲፈጠር ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ማድረግ
እና አፈፃፀምን መሰረት ያደረገ የግል ባለሀብት ምልመላ አለመኖር የሀገራዊ ባለሀብቱ
በአምራች ዘርፍ ድርሻው ውስን እንዲሆን ካደረጉት ምክንያቶች ተጠቃሽ ነው፡፡

8. ለአምራች ኢንዱስትሪ የመሬትና መሰረተ ልማት አቅርቦት


የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው በብቃት በአለም ገበያ ተወዳዳሪ
እንዲሆን የመሠረተ ልማት አቅርቦት ወሳኝ ነው፡፡ በሀገራችንም በተለይ ከ1998 ወዲህ
በኢንቨስትመንት የሚሰማራው ባለሀብት ለመሬት የሚያወጣው ወጪ ለፋብሪካው
የሚያወጣውን ኢንቨስትመንት እንዳያዳክመው መሬት በዝቅተኛ ዋጋ እንዲቀርብለት
እየተደረገ ነው፡፡ ነገር ግን አሁንም ቢሆን ለአዳዲስ የአምራች ኢንቨስትመንት ፈታኝ
ከሆኑ ሁኔታዎች አንዱ የመሬት አቅርቦት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው፡፡ ከተሞች
አምራች ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን ያህል የለማ መሬት መስጠት ላይ ክፍተት አለ፡፡
የሀገራችን የግል ባለሀብት ተነፃፃሪ ዓቅሙ ዝቅተኛ በመሆኑ ከዚህ ጋር የሚመጣጠን
የመሬት አቅርቦት የሚያስፈልገው ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አስቸጋሪ እየሆነ
ነው፡፡ በሌላ በኩል በሁሉም ከተሞች ከኢንዱስትሪ መንደር ውጭ መሬት በአምራች
ኢንዱስትሪ ለሚሰማራው ባለሀብት በጨረታ ካልሆነ በስተቀር በምደባ እየተሰጠ
አይደለም፡፡ በዝቅተኛ ሊዝ ዋጋ ተጠቃሚ አይደሉም። አንዳንድ ተነሳሽነቱ ያላቸው
ባለሀብቶች መሬት ለማግኘት ያለውን ወጪና ውጣውረድ በመፍራት የግለሰብ ቤት
ተከራይተው ለምሳሌ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ከፍተው የሚሰሩ ባለሀብቶች አሉ፡፡

በሌላ በኩል በሀገራችን የኢንዱስትሪ ፓርኮች በብዛት እየተስፋፉ ነው፡፡ የኢንዱስትሪ


ፓርኮችን ማልማት በመሬት አጠቃቀም ላይ የሚታዩውን ኪራይ ሰብሳቢነት
ለማስቀረት፣ የሎጅስቲክስና የጉምሩክ አገልግሎት ችግሮችን ለማስወገድ፣ መሰረተ-
ልማቶችን በማሟላት ኢንቨስትመንቶች ያለብዙ ውጣ ውረድ እንዲሰፍሩና በአጭር ጊዜ
ውስጥ ወደ ምርት እንዲሸጋገሩ ለማድረግ፣ በመካከለኛና ትላልቆቹ እና በአነስተኛ
ኢንዱስትሪዎች መካከል ትስስር ለማመቻቸትና ክላስተር ለመፍጠር በዚህም
የቴክኖሎጂ፣ የአመራረትና የስራ አመራር ዘዴን ለማስተላለፍ፣ የሥራ ዕድልን
ለማሳደግ፣ የሀገር ሀብትን በቁጠባና ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመጠቀምና አረንጓዴ
የኢንዱስትሪ ልማት አቅጣጫን ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ ነገር ግን
በእነዚህ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ምን ያህል እና እንዴት
ተጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል በደንብ ማጤን ያሻል። ለምሳሌ በአንደኛው የዕድገትና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 17


ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተገንብቶ ለባለሀብቶች የተላለፈው የቦሌ ለሚ ምዕራፍ አንድ
ኢንዱስትሪ ፓርክ በአቅም ማነስም ይሁን በፍላጎት ማጣት ምክንያት አንድም የሀገር
ውስጥ ባለሀብት አልተሰማራም፡፡ በቅርቡ ወደስራ እየገባ ባለው የሀዋሳ ኢንዱስትሪ
ፓረክም ቢሆን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ተሳትፎ በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ይህ ጉዳይ
በአንድ ወገን በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ተሳትፎ 20 በመቶ
መሆኑ በቂ አይደለም የሚሉ አካላት ቢኖሩም ነገር ግን የተሰጠውን ኮታም ቢሆን
መጠቀም እንዳልተቻለ የተግባር እንቅስቃሴዎች ያስገነዝባሉ፡፡ ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱ
በፌደራል ደረጃ ከሚገነቡ ፓርኮች በተጨማሪ ለወደፊት በክልሎች በሚገነቡ የተቀናጀ
አግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርኮች በሰፊው እንደሚሳተፍ ይጠበቃል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ አሁንም ቢሆን በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ተሟልተው ካልቀረቡ


መሰረተ ልማቶች መካከል የኤሌክትሪክ ሀይል፣ መንገድ፣ ውሀና የኢንተርኔት
አገልግሎቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች በኤሌክትሪክ ሀይል
ማነስና መቆራረጥ ምክንያት በሙሉ አቅማቸው መስራት እንዳልቻሉ እንዲሁም
በሚሊዮኖች ብር ኪሳራ እንዳደረሰባቸው ገልፀዋል፡፡ በሌላ በኩል በየከተሞቹ ያሉት
አብዘኞቹ የኢንዱስትሪ መንደሮች የመንገድ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው
አይደሉም፡፡ ለአምራች ኢንዱስትሪ መንደሮች የመንገድ፣ የውሀ እና የኢንተርኔት
መሰረተ ልማቶች በጥራትና በበቂ ሁኔታ አልተዳረሱም፡፡

የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦች

የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገትና ልማት ላይ የሚኖረው


ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ በሀገራችን የረጅም ጊዜ የኢንዱስትሪ ልማት ዕድገታችን ፍጥነትና
ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ የማይተካ ሚና አለው፡፡በሀገራችን
ዘላቂ የኢንዱስትሪ ልማትን ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ግንባር ቀደም
ተዋናይ መሆን እንዳለበት የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂያችን ያመለክታል
(ኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ 1994 ዓ.ም)፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ጉዞ ውስብስብ እና ተፃራሪ ፍላጎት ያላቸውን በርካታ ባለድርሻ


አካላትን የሚያካትት በመሆኑ የመንግስትን የመምራት አቅምና የመሪነት ሚና
የሚጠይቅ፣ የመንግስት ቁርጠኝነትና ተጠያቂነትን በእጅጉ የሚሻ እንዲሁም
ከተለመደው የአመራር ዘይቤ በመውጣት በትጋት ካልሰራ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ
ልማት የሚደረገውን መዋቅራዊ ሽግግር ለማረጋገጥ አስቸጋሪ እንደሚሆን ብዙ ጥናቶች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 18


ይጠቁማሉ፡፡ በዘርፉ ስኬታማ የሆኑ ሀገራት ተሞክሮ የሚያስተምረን እንደዚህ አይነት
ውስብስብ ዘርፍ ላይ መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት ግልፅ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲና
ስትራቴጂ ከማዘጋጀት በተጨማሪ በየደረጃው ያሉ ሁሉም የመንግስት አመራር አካላት
በፖሊሲው ይዘትና አተገባበር ላይ በቂ ግንዛቤ በመያዝ ከፍተኛ ሚና በመጫወታቸው
እንደነበር ከታሪካቸው ለመረዳት ይቻላል።

የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገትና ልማት ላይ የሚኖረው


ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ በሀገራችን የረጅም ጊዜ የኢንዱስትሪ ልማት ዕድገታችን ፍጥነትና
ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ የማይተካ ሚና አለው፡፡ ከዚህ
አንፃር በተለይ በ2017 ዓ.ም የተቀመጠውን ሀገራዊ ራዕይ ለማሳካት ይቻል ዘንድ
ከሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱና ከአምራች ኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካላት የሚጠበቀው
አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው፡፡ በመሆኑም በአምራች ኢንዱስትው የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብት ተሳትፎ ለማሰዳግና የዋና ተዋናይነት ሚናውን እንዲጫዎት በጥቂቱ በዚህ
ጥናት ውስጥ የተጠቀሱ የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦችን ተግባራዊ ማድረግን ይጠይቃል፡፡
የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦች ዝርዘር ማብራሪያ በክፍል 8.2 ይገኛል፡፡

I. የኢንዱስትሪ አመራርና አደረጃጀትን ማሻሻል

በተለያዩ ሀገራት መካከል የዕድገት ልዩነት የመጣው ሀገራት በሚከተሉት የፖሊሲ


አቅጣጫና የመንግስት የማስፈፃፀም አቅም ነው፡፡ ስኬታማ የሆኑ የምስራቅ ኤስያ
ሀገራት ተሞክሮ የሚያሳየው የፖሊሲ አቅጣጫ ማስቀመጥና የማስፈፀም ዓቅምን ማሳደግ
ላይ ትኩረት ማድረጋቸው ነው፡፡ ሁለቱም ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኞች ናቸው፡፡
የአንድን ሀገር የማስፈፀም አቅም ስንለካ የተቋማትን፣ የአሰራር ስርዓትን እና የሰው
ሀይል አቅም ማየት ያስፈልጋል፡፡ በሀገራችን ኢንዱስትሪውን እንዲደግፉ የተቋቋሙ
አደረጃጀቶችን ስንመለከት ተቋማዊ አደረጃጀቱ ወደ ታችኛው የመንግስት መዋቅር
(ክልል፣ ወረዳ እና ከተሞች) በትኩረት ያልተሰራበት ነው፡፡ በእነዚህ መዋቅሮች ውስጥ
በብዛትና በብቃት የሰው ሀይል አልተመደበም፤ የራሱ በጀትም የለውም፤ ስልጣንና
ሀላፊነት አልተሰጠውም፡፡ በአጠቃላይ የኢንዱስትሪ ልማቱን ሊመራ የሚችል አቅም
አልተፈጠረም፡፡ በተጨማሪም አገልግሎት አሰጣጡ በቴክኖሎጂ ያልታገዘ፣ ቀልጣፋ
አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የአሰራር ስርአት አልተዘረጋለትም። በመሆኑም
ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚው መዋቅራዊ ሽግግር የሚጠበቅበትን ማበርከት እንዲችል

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 19


የሚከተሉትን ዋና ዋና እርምጃዎች ዝርዝር ጥናት ላይ በመመስረት ማከናወን ተገቢ
ይሆናል፡፡

ሀ) የኢንዱስትሪ ልማት አደረጃጀትና ተግባርን ማሻሻል


ለ) ለኢንዱስትሪ አመራሮችና ባለሙያዎች የታቀደ ሰፊ ስልጠና መስጠት
ሐ) ጠንካራ የአመራርና ባለሙያ ምደባ እና ግምገማ ስርዓት መዘርጋት

II. አምራች የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን ለማጠናከር የቀረቡ የማበረታቻ


ማሻሻያዎች

በሀገራችን መንግስት የግሉ ዘርፍ በዋናነት በአምራች ዘርፍ እንዲሰማራ ማበረታቻዎች


እና የድጋፍ ማዕቀፎች አዘጋጅቶ ወደስራ የገባ ቢሆንም፤ ነገር ግን አሁንም የግሉ ዘርፍ
ስምሪት ትኩረት የአግልግሎት ዘርፍ እንደሆነ ቀጥሏል፡፡ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ
የሚቀርበው ማበረታቻና ድጋፍ ተወዳዳሪነቱን በሚያጎለብት ሁኔታ ካለመቅረቡ
በተጨማሪ ለጥገኛ ባለሀብቶች መጠቀሚያ የመሆን አዝማሚያ እየታየበት ነው፡፡ ከላይ
እንደተጠቀሰው የኢንዱስትሪ ማበረታቻዎች አፈፃፀም ደካማ የሆነበት ዋና ዋና
ምክንያቶች በርካታ ቢሆኑም በዋናነት ማበረታቻው ከተሰጠ በኋላ ለታለመለት አላማ
መዋሉን ክትትልና ቁጥጥር አለመደረጉና አፈፃፀምን መሰረት አድርጎ የማይተገበር
መሆኑ፤ እንዲሁም አገልግሎት ሰጪውና ጥቂት የማይባሉ የግል ባለሀብቶች ኪራይ
በመሰብሰብ ላይ ስለተጠመዱ ማበረታቻዎች በትክክል ተግባራዊ አልተደረጉም፡፡
በመሆኑም የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ
እንዲሰማሩ ለማድረግ አሁን በስራ ላይ ያለውን የማበረታቻና ድጋፍ ማዕቀፍ መከለስና
የበለጠ ማጠናከር ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም በዘርፉ የባለሀብቱን ስምሪት ለማስፋፋትና
ለማጠናከር እንዲቻል የሚከተሉት የማበረታቻና ድጋፍ ፖሊሲ ማሻሻያ ሀሳቦች ዝርዘር
በክፍል 8.2 መመልከት ይቻላል፡፡

ሀ) ለአምራች ባለሀብቱ የብድር ወለድ መጠን ከሌላ ዘርፍ ባለሀብት ያነሰ ማድረግ
ለ) በታክስ ህግ የሚቀርቡ ማበረታቻዎችን ማሻሻል (የገቢ ግብርና እርጅና ተቀናሽ)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 20


III. ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪ የፋይናንስ አቅርቦት ልዩ ትኩረት መስጠት

በአምራች ኢንዱስትሪ ስኬታማ የሆኑ ሀገራት ልምድ እንደሚያሳየው ለአምራች ዘርፍ


ብቻ ትኩረት አድርጎ ፋይናንስ የሚያቀርብ SME ባንክ አቋቁመው ውጤታማ ሆነዋል፡፡
ለምሳሌ በታይዋን ለአነስተኛና መካከለኛ ተቋማት ብቻ ፋይናንስ የሚያቀርቡ እና
የብድር ማስያዥያ ችግራቸውን ለመፍታት የሚችሉ ተቋማት አሏቸው፡፡ በሀገራችን
ያለው የልማት ባንክ ለሁሉም ዘርፎች ፋይናንሰ የሚያቀርብ በመሆኑ ለአምራች ዘርፉ
ትኩረት በማድረግ የሚጠበቅበትን ሚና መጫዎት አልቻለም፡፡ የአነስተኛና መካከለኛ
ኢንዱስትሪ ባንክ አሁን ባለንበት ወቅት ራሱን ችሎ ማቋቋም የማያስችሉ ሁኔታዎች
(በቂ የፋይናንስ አቅም አለመኖር) ስላሉ በልማት ባንክ ውስጥ ራሱን ችሎና አንድ
የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ የሚደራጅበትን ሁኔታ መፍጠር ይቻላል፡፡ ይህ አማራጭ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የተሟላ የመሰረተ ልማት ስላለው፣ የተጀመረው የሊዝ
ፋይናንስ የተሟላ ፋይናንስ ለመስጠት ጅምር መኖሩ እና ብዛት ያላቸው ቅርንጫፎች
ስላለውና ወደፊትም ስለሚኖሩት በቀላሉ ተደራሽ ለማደረግ ያስችላል፡፡ ስለዚህ
ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ትኩረት አድርጎ የሚሰራና የዘርፉን የፋይናንስ
ፍላጎት ግምት ውስጥ ያስገባ የተለየ የብድር ፖሊሲ፣ ግልፅ ተልዕኮ፣ አደረጃጀት እና
የሰው ሀይል ያለው እንዲሁም ተደራሽ የሆነ መዋቅር ተዘርግቶለት ቢደራጅ የተሻለ
ይሆናል፡፡ይህ አደረጃጀት አሁን ያለውን የአነስተኛና መካከለኛ ተቋማት ችግር
መፍታት የሚችል እና በቀላሉ ተደራሽ የሚሆን ቢሆንም የአነስተኛና መካከለኛ
ተቋማት ዕድገትን መሸከም የማይችልበት ደረጃ መድረሱ ስለማይቀር በሂደት ራሱን
ችሎ ሊደራጅ ይችላል፡፡ ስለዚህ ልማት ባንክ ለSME በልዩ ሁኔታ በውስጡ ከላይ
እስከታች በማደራጀት ስራ ቢጀምር የተሻለ ይሆናል፡፡ ይህ ክፍል ኢኩፕመንት ሊዝ
ብቻ ሳይሆን የስራ ማስኬጃን ጭምሮ ሌላም ብደር አጠቃሎ የሚሰጥ ቢሆን የተሻለ
ነው፡፡

IV. ተገቢ ያልሆነ የአለማቀፍ ንግድ ውድድር ለመቆጣጠር የሬጉላቶሪ ስርአት


መዘርጋት

ገቢ-ምርቶች የሚፈጥሩት ተገቢ ያልሆነ የንግድ ውድድር የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪን


ተወዳዳሪነትና ምርታማነት ላይ ቀላል የማይባል ተፅዕኖ አለው፡፡ ይህ ኢ-ፍትሃዊ
ውድድር የሀገር ውስጥ ገበያን በድንገት በማጥለቅለቅ (sudden import surge)፣ ገበያን
ለመቆጣጠር ሲባል ተመጣጣኝ ባልሆነ ዝቅተኛ ዋጋ በመሸጥ (dumped products) እና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 21


በመንግስታት ድጎማ አማካኝነት የውድድር የበላይነት በመውሰድ የሀገር ውስጥ
ኢንዱስትሪን ከገበያ በማስወጣት (subsidized products) የሚፈፀም ድርጊት
ነው፡፡የማሻሻያ ሀሳቦችን ዝርዘር በክፍል 8.2 መመልከት ይቻላል፡፡

ሀ) የፀረ-ዳንፒንግ (anti-dumping)፣ ገበያን በድንገት ማጥለቅለቅ (sudden import


surge) እና በድጎማ ገበያን መቆጣጠር (subsidized products) የተመለከተ አንቀፅ
በንግድ አሰራር እና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ እንዲካተት ማድረግ፣
ለ) ሁለተኛው አማራጭ ሶስቱን ጉዳዮች ማለትም የፀረ-ዳንፒንግ መከላከል ማዕቀፍ፣
የገቢ-ምርቶ ቅፅበታዊ ማጥለቅለቅ መከላከል እና ተደጉመው የሚገቡ ምርቶች አሉታዊ
ተፅዕኖ መከላከል የሚያስችል ዘርዘር ያለ የህግ ማዕቀፍ ወይም አዋጅ (ፓሊሲ) መቅረፅ
እና ለንግድ ሚኒስቴር ተጠሪ የሆነ ተቋም ማደራጀች፤

V. የመንግስት ግዥ ፓሊሲን ማሻሻል

የመንግስት ግዥ ለአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነት፣ ተወዳዳሪነት፣ ስራ ፈጠራ እና


ቴክኖሎጅ ሽግግር ለማረጋገጥ የሚያገለግል ቁልፍ የፓሊሲ መሳሪያ መሆኑን የሀገራት
የተግባር ተሞክሮዎች ያረጋግጣሉ፡፡ ልማት ተኮር የግዥ ፓሊሲ አቅጣጫ መከተል
ለጀማሪ ኢንዱስትሪ ከለላ (infant industry protection) ለመስጠት እና ስትራቴጅካዊ
ጠቀሜታ ያላቸውን ኢንዱስትሪዎች ለማነቃቃት አስተዋፅጾው ከፍተኛ ነው፡፡
መንግስት በአንድ ሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ከማንኛውም አካል በላቀ ሁኔታ መጠነ-ሰፊ
ግዥ መፈጸሙ በአምራች ምርት ላይ ገበያ የመፍጠር ተፅዕኖው (demand side
effect) የጎላ እና የግዥ ድጋፍ ከሌሎች የማበረታቻ ስልቶች በበለጠ ውጤታማ መሆኑ
የግዥ ፓሊሲ ለኢንዱስትሪ ልማት ያለውን ቀጥተኛ ፋይዳ ያመለክታል፡፡ ሆኖም
በሀገራችን የፌደራል መንግስት ግዥ ፖሊሲ (ማለትም አዋጅ እና መመሪያ) የአምራች
ኢንዱስትሪ ዘርፍ በመደገፍ በኩል ሰፊ ጉድለቶች ያሉበት ነው፡፡ ከዚህ አንጻር
የመንግስት የግዥ ፓሊሲ የልማታዊ የግዥ መርህ (Developmental Public
Procurment) እንዲላበስ በማድረግ የአምራች ኢንዱስትሪውን ዕድገት ማፋጠን
ተገቢነት አለው፡፡
ሀ) ተስማሚ የዋጋና የብቃት ልዩ አስተያየት ድጋፍ ማዘጋጀት (preferential treatment)
i. የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳግ ማሻሻል (preferential price margin)
ii. ከብቃት መመዘኛ መስፈርት ጋር የተያያዘ የልዩ አስተያየት ድጋፍ መዘርጋት
iii. የስራ ፈጠራ እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልዩ አስተያየት ድጋፍ ማሻሻል

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 22


iv. ጨረታ ሰነድ ማስረከቢያ ጊዜ እና ምርት ማቅረቢያ ጊዜ መከለስ
ለ) ለሀገር ውስጥ ምርት ቅድሚያ የሚሰጥ ስርአት መዘርጋት (Domestic preference)
ሐ) የውጭ ተጫራቾች የሀገር ውስጥ ግብአት በሰፊው እንዲጠቀሙ አቅጣጫ መቀየስ
(Domestic content requirement policy)
መ) የግዥ ቅድመ ክፍያ ምጣኔ ማስተካከል (advance payment)
ሠ) የመንግስት ግዥ ስርአት ከሙስና የፀዳ ብቃት ያለው ባለሙያ አመራር ማደራጀት

VI. ያልተማከለ የገጠር ኢንዲስትሪ ልማት አቅጣጫ መከተል


በግብርና ላይ በተሰማራው አርሶአደርና አርብቶአደር እየተፈጠረ ያለውን የሀብት
ክምችት ቀጣይ የኢንቨስትመንት ስምሪቱን መምራት (የአሰራር ስርአትና አቅጣጫ
ማስቀመጥ) አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ ከፍተኛ ሀብት ወደ ሚፈለገው ዘርፍ በአግባቡ
ባለመመራቱ አብዛኛው የገጠር አረሶአደር ያገኘውን ሀብት በከተማ ቤት መግዛት፣
መኪና መግዛት፣ ወዘተ እየተጠቀመበት ይገኛል፡፡ ስለዚህ የገጠሩን ሀብታም
አርሶአደርና በገጠር የሚኖሩ የተማሩ ወጣቶች በተናጥልም ሆነ በማደራጀት በአነስተኛ
አምራች ኢንዱስትሪ (በተለይ በአግሮ-ፕሮሰሲንግና የኮንስትራክሽን ግብአት ንዑስ-
ዘርፎች) በብዛት ማሰማራት ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ያልተማከለ
የገጠር ኢንዲስትሪ ልማትን ለማረጋገጥ በጥቂቱ የሚከተሉት ሁለት ጉዳዮች ላይ
ትኩረት ማድረግ ያሻል፡፡ የፖሊ ማሻሻያ ምክረ-ሀሳቡን ዝርዝር በክፍል 8.2 ይገኛል፡፡

ሀ) ከከፍተኛ ኢንዱስት ጋር የተቀናጀ ተመጋጋቢ የገጠር ኢንዱስትሪ ማልማት


ለ) በገጠር መሰረተ-ልማትን ማስፋፋት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 23


ክፍል I
መግቢያ

ምዕራፍ 1
የጥናቱ አስፈላጊነትና አላማ

1.1 የጥናቱ አስፈላጊነት

በሀገራችን የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ የግብርናው ምርትና ምርታማነት ይበልጥ


በማሳደግ የኢንዱስትሪውን የግብአት ፍላጎት የሚያሟላ በማድረግ የኢንዱስትሪው ዘርፍ
ልማት በማፋጠን በ2017 ኢንዱስትሪው በሀገራዊ ምጣኔ ሀብት ከፍተኛ ድርሻ
እንዲኖረው ለማድረግ ፈርጀ ብዙ ልማታዊ ጥረቶች ተደርጓል፤ እየተደረገም ነው፡፡
መንግስት ግልፅና አመቺ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ፣ የሕግ ማዕቀፎችና ማበረታቻ
ፓኬጆች አዘጋጅቶ በስራ ላይ እንዲውሉ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡

ለኢኮኖሚው ዕድገት ወሳኝና የመሪነት ሚና ያለው የግብርናው ክፍለ-ኢኮኖሚ ቢሆንም


የኢንዱስትሪው ዘርፍም የበኩሉን አስተዋፅኦ በማበረከት ላይ ነው፡፡ በተለይ በአንደኛው
የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ውስጥ የተመዘገቡት ውጤቶች ቀደም ሲል
ከነበረው የአምስት አመት የዕቅድ ዘመን አማካይ ጋር ሲነፃፀር የኢንዱስትሪው ዘርፍ
እያደገ የመጣ ቢሆንም የአምራች ኢንዱስትሪው የምርት ድርሻ ግን ከ5% በታች
መሆኑ ለዘርፉ ዕድገት ያለው አስተዋፅኦ አነስተኛ መሆኑን ያመለክታል፡፡

ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪውን ንዑስ ዘርፍ ለማሳደግ ሰፊ


ጥረት እያደረገ ቢሆንም ነገር ግን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን በአምራች
ኢንዱስትሪው ልማት የሞተርነት ሚናውን ወይም የዋና ተዋናይነት ድርሻውን
እንዲወጣ ከማድረግ አኳያ የተሰራው ስራ አጥጋቢ አይደለም፡፡ በሀገር ውስጥ የግሉ
ሴክተር በኢንዱስትሪው ዕድገት ላይ በሚፈለገው ደረጃ የሚገባውን ሚና ተጫውቷል
ለማለትም አያስደፍርም፡፡ ለምሳሌ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት የኢንቨስትመንት
ስምሪትን ስንመለከት ከ1984-2009 ዓ.ም ሩብ አመት ድረስ 78,348 ፕሮጅክቶች
የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ ሲሆን ከዚህ ውስጥ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 24


በአምራች ዘርፍ ፈቃድ የወሰዱት 17,519 ፕሮጀክቶች ብቻ ናቸው፡፡ ከ17,519
ፕሮጀክቶች መካከል ደግሞ ወደ ማምረት ተግባር የተሸጋገሩት 1837 (10.44%)
ፕሮጀክቶች ብቻ ናቸው (ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ 2009 ዓ.ም)፡፡ ይህ
አሀዛዊ መረጃ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ እና አጠቃላይ የግሉ ዘርፍ በአምራች ኢንዱስትሪ
ላይ ያለው ተሳትፎ በጣም ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ያሳያል፡፡

ይህ ዝቅተኛ ተሳትፎ የአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ጎልቶ እንዳይታይ አድርጎታል፡፡


በ1994 በጀት ዓመት የአምራች ኢንዱስትሪው ንዑስ ዘርፍ ከጥቅል ሀገራዊ ምርቱ 5.3
በመቶ አስተዋጽኦ የነበረ ሲሆን በ2003 በጀት ዓመት ወደ 4.9 በመቶ እንዲሁም
በ2007 ዓ.ም ወደ 4.6 በመቶ ዝቅ ብሏል፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ በውጭ ሰደድ
(export earning) አስተዋፅኦውም ከአጠቃላይ የውጭ ሰደድ ምርቶች ዋጋ 7.5 በመቶ
ብቻ ነበር (KOICA, 2005 ዓ.ም)፡፡ በዚህ ምክንያት አንደኛው የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ግቦች ከማሳካት አኳያ ሲታይ የግብርና ምርት በግብአትነት
የሚጠቀሙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታቸው 9 ዕጥፍ፣ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት
14 ዕጥፍ፣ የብረታብረት ምርት አምራች ኢንዱስትሪ 3 ዕጥፍ በላይ ማሳደግ
እንደሚጠበቅ የኮሪያ ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ ጥናት ያሳያል፡፡ በመሆኑም
ለአምራች ኢንዱስትሪ ዕድገትና ልማት ዘገምተኝነት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው
የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ልማት ላይ ያለው ተሳትፎ
በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ ምክንያት እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

በአጠቃላይ በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር የሆነው የሀገር


ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪው ልማት ላይ የዋና ተዋናይነት ሚናውን
እየተጫወተ አለመሆኑ እና የኢንቨስትመንት ተሳትፎውም ዝቅተኛ ሆኖ መገኘቱ
በሀገራችን ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ በአንድ በኩል ቀድመው
በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች ያሉባቸውን
ማነቆዎች ለመፈተሽ፣ አፈፃፀማቸውን ለመገምገምና የሞተርነት ሚናቸውን ከመጫዎት
አኳያ ያለውን ክፍተት በመለየት መወሰድ ያለባቸውን የፖሊሲና የመፍትሄ ሀሳቦች
ለማቅረብ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ አቅም ያላቸውና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ የሀገር
ውስጥ የግል ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ በስፋት እንዲሰማሩ የሚያስችል
አቅጣጫ ለማመላከት ጥናቱ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 25


1.2 የጥናቱ አላማ

1.2.1 አጠቃላይ አላማ


የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ውስጥ የሞተርነት ሚናውን
ከመጫወት አኳያ ያሉትን መልካም ዕድሎችና ተግዳሮቶች በመፈተሽ፣ ባለሀብቱ
ተነፃፃሪ የኢንቨስትመንት ምርጫው አምራች ኢንዱስትሪው እንዲሆን የሚያስችል
የፖሊሲ ምክረ-ሀሳብ ማቅረብ ነው፡፡

1.2.2 ዝርዝር አላማዎች


1. የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪው ውስጥ የሞተርነት ሚናውን
ከመጫወት አኳያ ያሉትን ተግዳሮቶች መፈተሽ፤
2. የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ወደ አምራች ኢንዱስትሪው በስፋት ያልተሰማራበትን
ምክንያቶች መለየት ባለሀብቱ በዘርፉ ሰፊ ተሳትፎ የሚያደርግበት አቅጣጫ
ማመላከት፤
3. በአምራች ኢንዱስትሪው ሊሰማሩ የሚችሉ አዳዲስ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶችን
የክፍለ-ኢኮኖሚያዊ መነሻዎችን መለየት፤ በምን ስትራቴጂና ድጋፍ ወደ ዘርፉ
መሳብ እንደሚቻል ማመለካት፤
4. በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች የዋና ተዋናይነት
ሚናቸውን እንዲወጡና ዘርፉ ለአዳዲስ ባለሀብቶች ሳቢ እንዲሆን የሚያስችሉ
የፖሊሲና ስትራቴጂ ምክረ-ሀሳቦችን ማቅረብ፤

1.2.3 በጥናቱ መመለስ ያለባቸው ጥያቄዎች

ከላይ በጥቅል ዓላማው በተቀመጠው መሰረት ዝርዝር ዓላማዎቹ ከግብ ለማድረስ


ትኩረት በመስጠት በዚህ ጥናት በዝርዝር መመለስ የሚገባቸው ገዥ ጥያቄዎች
እንደሚከተለው ተለይተዋል፡፡
1. ቀድመው በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ባለሀብቶችን የሚመለከቱ
ሀ) የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ ያለው ተሳትፎ
በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 26


ለ) በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች ያሉባቸው
መሠረታዊ ችግሮችና ማነቆዎች ምንድናቸው? መሰረታዊ መንስኤዎች
ምንድናቸው?
ሐ) የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪው ውስጥ የሞተርነት
ሚናውን እየተጫወተ ነው ለማለት ይቻላልን?
መ) የኢንዱስትሪ ስትራቴጂዎችና የተለያዩ የድጋፍና ማበረታቻ ማዕቀፎች
አምራች ኢንዱስትሪውን በተፈለገው ደረጃ ውጤታማ ያላደረጉት ምክንያቶች
ምንድናቸው?
2. አዳዲስ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶችን የሚመለከት፡
ሀ) የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪው በስፋት
ያልተሰማሩበት ዋና ዋና ምክንያቶች ምንድናቸው?
ለ) በአምራች ኢንዱስትሪው ሊሰማሩ የሚችሉ አዳዲስ የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብቶችን በዋናነት በየትኛው ክፍለ-ኢኮኖሚ የሚገኙ ናቸው?
3. የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ ውስጥ የሞተርነት ሚናውን
እንዲጫዎት ምን ምን ፖሊሲና ስትራቴጂክ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው?

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 27


ምዕራፍ 2
የጥናቱ ዘዴና ተሳታፊዎች

ከላይ የተጠቀሰውን የጥናቱን አላማ ለማሳካትና መሠረታዊ የሆኑ ዋና ዋና ጥያቄዎችን


ለመመለስ የሚያስችል የጥናት ስልቶችንና መሳሪያዎች ተለይተው ጥቅም ላይ
መዋላቸው የጥናቱን ውጤት የተሻለ ጥራት እንዲኖረው አድርጓል፡፡ ለጥናቱ ግብአት
የሚሆኑ የመጀመሪያ ደረጃ መረጃዎች (Primary data) እና የሁለተኛ ደረጃ መረጃዎችን
(secondary data) ለመሰብሰብ የጥናቱ አይነት ወይም ይዘት፣ አላማ እና የሚጠበቀው
ውጤት ላይ መሠረት ያደረገ የጥናት ዘዴዎችና መሳሪያዎች በተግባር ላይ ውለዋል፡፡

2.1 የጥናቱ ዓይነት

ጥናቶች በግብአትነት ከሚጠቀሙት የመረጃ ዓይነት ሲታይ አሀዝ-ተኮርና


(Quantitative) እና ሐሳብ-ተኮር (Qualitative) በማለት በሁለት ይከፈላሉ፡፡
የመጀመሪያው የጥናት ዓይነት የሚጠቀመው መረጃ በዋናነት አሀዛዊ ሲሆን
ትንታኔውም በአሀዝ የተመሰረተ ከመሆኑ በሻገር ድምዳሜውም በአሀዝ የሚገለጽ
ይሆናል፡፡ በአንጻሩ ሐሳብ-ተኮር ጥናቶች ለምን? እንዴት? በምን ምክንያት ወዘተ
የመሳሰሉ ጥያቄዎች ላይ መልስ በማፈላለግ ላይ ያጠነጥናሉ፡፡ በሁለተኛው ዓይነት
ጥናት በብዛት የሚፈለገው መረጃ አሀዛዊ ሳይሆን ምክንያቶች የሚያቀርብ፣ ሁኔታዎች
የሚያስረዳ እና የሚተነትን ዕውቀት፣ ተሞክሮና ልምድ፣ አመለካከትና አስተያየት አዘል
ነው፡፡ ሆኖም ግን አንድ ጥናት ሙሉውን አሀዝ ላይ ብቻ ወይም ሐሳብ ላይ ብቻ
የተመሰረተ ሊሆን አይችልም፡፡

ለዚህ ጥናት የተጠቀምንበት የጥናት ዓይነትም ሁለቱም የጥናት ዓይነቶች በመቀላቀል


(Mixed Research) ነው፡፡ አሀዛዊ ትንታኔው መሬት ላይ ያለ ሁኔታ ከተቀመጠለት
አመላካች ምን ያህል እየተፈፀመ መሆኑ የሚያመላክት ሲሆን የሐሳብ ትንታኔው እየታየ
ያለውን ነባራዊ ሁኔታ መነሻ ምክንያቱ እና ውጤቱ ምን እንደሚመስል ለማስረዳት
ተጠቅመንበታል፡፡ ይሁን እንጂ የዚህ ጥናት አሀዛዊ ትንታኔው በራሱ ግብ ተደርጎ
የተወሰደ ሳይሆን ነባራዊ ሁኔታው የፈጠሩት ምክንያቶችና ውጤታቸው ምን ያህል
እንደሆነ በደጋፊነት የተጠቀምንበት ነው፡፡ ይህ ማለት ጥናቱ ምን፣ ለምን እና እንዴት
የሚሉትን ጥያቄዎች የሚመልስ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 28


2.2 የመረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴዎችና መሳሪያዎች

የዚህ ጥናት ትኩረት በአንድ በኩል ቀድመው በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ የተሰማሩ


የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች የገጠማቸውን ችግሮችና ማነቆዎች መፈተሽ እና
እንዲሁም የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ያለው
የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ዝቅተኛ የሆነበትን ምክንያቶች ማወቅና ተጨማሪ አዳዲስ
የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶችን ወደ ዘርፉ ለመሳብ ምን ምን ተግባራት መከናወን
እንዳለባቸው ለመለየትና በጥናት ላይ የተመሠረተ ምክረ-ሀሳብ ለማቅረብ ነው፡፡ ስለዚህ
ይህንን የጥናት አላማ ለማሳካት በዋነኛነት ተግባራዊ የተደረጉ የመረጃ ማሰባሰቢያ
ዘዴዎችና መሣሪያዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡

2.2.1 የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ (Primary Data)

ሀ) የጽሑፍ መጠየቅ
በዚህ ጥናት ውስጥ ሁለት የተለያዩ ዘርፎችን የሚመለከቱ መጠይቆች (Questionnaires)
ተዘጋጅተው ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ አንደኛው መጠይቅ በአምራች ኢንዱስትሪው
የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች የሚመለከት ሲሆን ሁለተኛው መጠይቅ ደግሞ
ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርኘራይዝ የተዘጋጀ ነው፡፡ ሁለቱም መቀይቆች ይዘታቸው
አሀዛዊ (Quantitative Data) እና አሀዛዊ ያልሆኑ (Qualitative Data) የተገደቡና (Closed)
ያልተገደቡ (Open ended) መረጃዎችን ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ናቸው፡፡

ለ) ቃለ መጠይቅ (Unstructured Interview)

በተመረጡ ድርጅቶች (አምራቾች መንግስታዊ ያልሆኑ) እና የመንግስት መስሪያ ቤቶች


በከፊል የተደራጁ የጥናት ቃለ መጠይቆች ተግባራዊ ሆነዋል፡፡ በቃለ መጠይቁ
የተካተቱ ጥያቄዎች ጥናቱን በሁለት መንገድ ለማጎልበት አገልግለዋል፡፡ በአንድ በኩል
በፅሑፍ መጠይቆች (Questionaires) የተሰጡ መልሶችን ለማገናዘብና ለማረጋገጥ
ያገለገሉ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ቃለ-መጠይቁ ከሚመለከታቸው ሀላፊዎች
የሚፈለገውን መረጃ በጥልቀት ለማግኘት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ በመሆኑም
በዚህ ጥናት ውስጥ በቃለ መጠይቅ መረጃ የተሰበሰበባቸው መስሪያ ቤቶችና ድርጅቶች
ለናሙና የተመረጡ የአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች፣ አነስተኛ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 29


የብድርና ቁጠባ ተቋማት ሀላፊዎች፣ የግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ሀላፊዎች፣
የኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርኘራይዝ ኤጀንሲ
ሀላፊዎች፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሀላፊዎችና እንዲሁም ንግድ ሚኒስቴር ናቸው፡፡

ሐ) ርዕሰ ጉዳይ ቡድን ውይይት (Focused Group Discussion)

የርዕሰ ጉዳይ ቡድን ውይይት የተመረጠበት ምክንያት አንድን ጉዳይ ከተለያዩ


አቅጣጫዎች ለማየት እንዲያስችል እና በጉዳዩ ላይ የተሻለ ዕውቀት ያላቸው ተወያዮች
በማሳተፍ የጠራ መረጃ ለመሰብሰብ ታስቦ ነው፡፡ በዚህ መሠረት በትኩረት የቡድን
ውይይት ውስጥ በጉዳዩ ዙሪያ በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች የሚሰሩና በጉዳዩ ላይ
የተሻለ ዕውቀትና መረጃ ያላቸው አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡
ተሳታፊዎች የሚያውቁትን መረጃ በግልፅና በባለቤትነት ስሜት ነፃ ሆነው እንዲያቀርቡ
ተደርጓል፡፡ በዚህ ጥናት ውስጥ ለትኩረት የቡድን ውይይት የተመረጡ ዘርፎች
በአስመጪነትና ላኪነት የተሰማሩ ነጋዴዎች እና በየደረጃው የሚገኙ የንግድና የዘርፍ
ማሕበራት አመራሮች ናቸው፡፡

መ) የባለሙያዎች ፓናል ውይይት (Experts Panel Discussion)

የባለሙያዎች ፓናል የተመረጠበት ምክንያት አንዳንድ የጥናት ጉዳዮች


ከሚመለከታቸው ባለሙያዎች የጠለቀ ውይይትና ትንተና ስለሚያስፈልግ ነው፡፡
በዚህም መሠረት በባለሙያዎች የፓናል ውይይት ውስጥ በጉዳዩ ላይ የጠለቀ ዕውቀት
ያላቸው ባለሙያዎች በጥንቃቄ ተመርጠው እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡ በዚህ ጥናት ውስጥ
ለባለሙያዎች ፓናል ውይይት የተመረጡት ዘርፎችና መስሪያ ቤቶች የጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት፣ የንግድ ቢሮዎች፣ የግብርናና ገጠር ልማት
ቢሮዎችና ሚኒስቴር መስሪያቤት፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የኢትዩጵያ
ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ባለሙያዎች ናቸው፡፡

ሠ) የአካል ምልከታ (Physical Observation)

በተለይ ለናሙና በተመረጡ በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል


ባለሀብቶች ፋብሪካዎቻቸው ድረስ በመሄድና የፋብሪካዎቻቸውን ይዘትና የምርት ሂደት
ከተጐበኘ በኋላ ወደ ውይይት ይገባል፡፡ በመሆኑም የፋብሪካ ባለቤቶች በስራቸው ላይ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 30


ያጋጠሟቸውን ችግሮች ለአጥኝዎች ለማስረዳት ችለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ጥቂት
የማይባሉ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተሰማሩ አንቀሳቃሾችን በአካል
በመገኘት የምርት እንቅስቃሴያቸው የተጎበኘ ሲሆን ያሉባቸውን መሰረታዊ ችግሮች
ለአጥኝዎች ለማስረዳት ችለዋል፡፡

2.2.2 ሁለተኛ ደረጃ መረጃ (Secondary Data Sources)

ሌላው ለጥናቱ ግብአት ከመጀመሪያ ደረጃ መረጃ (Primary data) በተጨማሪ የሁለተኛ
ደረጃ መረጃ (secondary data) ማሰባሰብ ነው፡፡ ይህ ተግባር በሁለት አቅጣጫ ወይም
መንገድ ተከፍሎ ተከናውኗል። አንደኛው ከሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶች እና
ድርጅቶች ያሏቸውን ሰነዶች ማሰባሰብ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ተያያዥነት ያላቸውን
የጥናት ፅሁፎች (Related Literature Review) ዳሰሳ በማካሄድ ነው።

ሀ) የሰነድ ምርመራ (Document Analysis)

ከላይ እንደተገለፀው የሁለተኛ ደረጃ መረጃን (secondary data) ለማሰባሰብ መጀመሪያ


የሚመለከታቸውን መስሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ተመርጠዋል፡፡ እነዚህ መስሪያ ቤቶችና
ድርጅቶች ያሉአቸውን አመታዊ ሪፖርቶች፣ አዋጆች፣ መመሪያዎችና ደንቦች፣
የፖሊሲና ስትራቴጂ ሰነዶች፣ የጥናት ሰነዶች፣ ወዘተ ተሰብስበዋል፡፡ ለዚህ ጥናት
ግብአት እንዲሆኑ የተለያዩ ሰነዶችን ከሚከተሉት መ/ቤቶችና ድርጅቶች ለማሰባሰብ
ተችሏል፡፡ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የንግድ ሚኒስቴር፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ
ልማት ትብብር ሚኒስቴር፣ ፕላኒንግ ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣
የከተማ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር፣ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ልማት
ኢንስቲትዩት፣ የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ልማት ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ
ባንክ፣ የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ፣ የኢትዩጵያ ልማት ባንክ፣ የተለያዩ የክልል ቢሮዎችና
መምሪያዎች እና ሌሎችም ናቸው፡፡

ለ) የጥናት ፅሁፎች ዳሰሳ (Literature Review)

የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ ያለውን ተሳትፎ


የሚመለከቱና ተያያዥነት ያላቸው የጥናት ፅሁፎች (Related literature review)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 31


ተዳሰዋል፡፡ በተለይ ኢንቨስትመንት በአንድ ሀገር ውስጥ ከምጣኔ ሀብት ዕድገት ጋር
ያለውን ተዛምዶ፣ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ ኢንቨስት
እንዲያደርግ ለምን እንዳስፈለገ እንዲሁም የባለሀብቱን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ
የሚወስኑ ጉዳዮች (determinant factors) ምን ምን እንደሆኑ መለየት፣ እና ሌሎችም
ጉዳዩች ተዳሰዋል፡፡

2.3 ጥናት የተደረገባቸው ቦታዎችና የጥናቱ ተሳታፊዎች

የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ ያለውን ተሳትፎ እንደ ሀገር
ለማጥናት የታቀደ እንደመሆኑ፤ ጥናቱ በተቻለ መጠን አብዛኛውን የሀገሪቱን የአምራች
ኢንዱስትሪ አካባቢዎች ያካተተ እና የሚዳስስ መሆን እንደሚገባው አያጠራጥርም፡፡
ስለዚህ ጥናቱ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶችና አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚበዙባቸውን
አካባቢዎችና ቦታዎች ለማዳረስ ጥረት ተደርጓል፡፡ በዚህም መሠረት አራት የክልል
መስተዳድሮች (የትግራይ፣ የአማራ፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች እና ኦሮሚያ
እንዲሁም ሁለት የከተማ አስተዳደሮች (የአዲስ አበባና ድሬደዋ) በጥናቱ ተካተዋል፡፡

የመጀመሪያ ደረጃ መረጃን ለማሰባሰብ በተመረጡ የጥናት ቦታዎች የቃለ መጠይቅ፣


የፅሁፍ መጠይቅ፣ የርዕሰ ጉዳይ ቡድን ውይይት፣ የባለሙያዎች ፓናል ውይይትና
የአካል ምልከታ ዘዴዎችና መሣሪያዎች ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ
በሀገሪቱ ባሉ ስድስት ዋና ዋና ከተሞች (አዲስ አበባ፣ ድሬድዋ፣ ባህርዳር፣ መቀሌ፣
ሀዋሣና አዳማ) የሚገኙ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች በጥናቱ
ውስጥ ትኩረት የተሰጣቸው ናቸው፡፡

በሰንጠረዥ 2.1 እንደተገለፀው በዚህ ጥናት ውስጥ የተዳሰሱ መ/ቤቶች ኢንዱስትሪ


ሚኒስቴር፣ የግብርናና ገጠር ልማት፣ ንግድና ኢንዱስትሪ፣ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና
ጽ/ቤቶች፣ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን፣ አስመጪና ላኪ፣ ንግድና ዘርፍ ማህበራት፣
ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን፣ ፌደራል ግዥና ንብረት ኤጀንሲ፣ በአምራች ኢንዱስትሪ
የተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የኢትዮጵያ
ልማት ባንክ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት እና ጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ናቸው፡፡ እነዚህ የተመረጡበት ምክንያት በቀጥታም ሆነ
በተዘዋዋሪ መንገድ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ ያለውን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 32


የዋና ተዋናይነት ሚና እንዲሁም የኢንቨስትመንት ተሳትፎና ውጤታማነት በተገቢው
መንገድ ለማጥናት፣ ለመገምገም፣ ያጋጠሙ ችግሮችና ማነቆዎች ለመለየትና የፖሊሲ
ምክረ ሀሳብ ለማቅረብ የሚያስችሉ በመሆናቸው ነው፡፡

ሰንጠረዥ 2.1 መረጃ የተሰበሰበባቸው ምንጮች

ተ. የመረጃ ምንጭ መለኪያ የተቋም የተሳታፊ መረጃ መሰብሰቢያ ስልት


ቁ ብዛት ብዛት
1 በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ቁጥር 88 88 የፅሑፍ መጠይቅ
ባለሀብቶች 12 12 ቃለ መጠይቅ
2 ኢንቨስትመንት አስፈፃሚ ቁጥር 6 ቃለ መጠይቅ
መስሪያ ቤቶች 2 23 የባለሙያዎች ምክክር
3 የንግድ አስፈፃሚ መስሪያ ቡድን 6 የባለሙያዎች ምክክር
ቤቶች /ፌዴራል-ክልል/ከተሞች/ 3 83 ቃለ መጠይቅ
4 የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ቡድን 1 7 ርዕሰ ጉዳይ የቡድን
ውይይት
5 የግብርና አስፈፃሚ መስሪያ ቡድን 5 ባለሙያዎች ምክክር
ቤቶች /ፌዴራልና ክልሎች/ 41
1 ቃለ መጠይቅና አሀዛዊ
መረጃ
6 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ቁጥር 1 1 ቃለ መጠይቅና አሀዛዊ
7 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር 1 2 ቃለ መጠይቅና አሀዛዊ
8 የንግድና ዘርፍ ማሕበራት ቁጥር 7 ርዕሰ ጉዳይ ቡድን ውይይት
ምክርቤቶች /ሀገር አቀፍ እና 1 ቃለ መጠይቅና ርዕሰ
የከተሞች/ 31 ጉዳይ የቡድን ውይይት
9 የጥቃቅንና አነስተኛ ቁጥር 116 116 የፅሑፍ መጠይቅ
ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች
10 የጥቃቅንና አነስተኛ ቁጥር 2 ቃለ-መጠይቅና አሀዛዊ
ኢንተርፕራይዞች ልማት 45 መረጃ
ኤጀንሲዎች፣ቢሮዎች፣ ጽ/ቤቶች 6 የባለሙያዎች ውይይትና
አሀዛዊ መረጃ
11 አነስተኛ ብድርናቁጠባ ተቋማት ቁጥር 6 7 ቃለ-መጠይቅና አሀዛዊ
መረጃ
12 ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ቁጥር 1 7 አሀዛዊ መረጃ
13 ፌደራል ግዥና ንብረት ኤጀንሲ ቁጥር 1 4 ኢ- አሀዛዊ መረጃ
14 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ቁጥር 1 3 ኢ- አሀዛዊ መረጃ

2.4 የጥናቱ መረጃ ትንተና፣ ግኝትና ምክረ-ሀሳብ አቀራረብ

የጥናቱ አካሄድን ስንመለከት አራት ደረጃ ያለው ነው፡፡ መጀመሪያ በጥናት ርዕሱ ዙሪያ
በሀገራችንና በሌሎች ሀገራት የተጠኑ የጥናት ሰነዶችንና ፅሁፎች ለመነሻነት
ተዳሰዋል፡፡ ከዚህ በመነሳትም ከመስክና ሌሎች ምንጮች የተሰበሰበውን የመጀመሪያ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 33


እና ሁለተኛ ደረጃ መረጃዎች በተገቢው መንገድ በመረዳት ጥቅል ነባራዊ ሁኔታ
ትንተና (Situational Analysis) ተሰርቷል፡፡ በሶስተኛ ደረጃ የጥናቱ ትንተናና ግኝቶችን
ለማመላከት ተሞክሯል፡፡ ችግሮችና ማነቆዎች ከነመንስኤዎቻቸው ተለይተው
ቀርበዋል፡፡ በመጨረሻም የጥናቱን ትንተናና ግኝቶች መሰረት በማድረግ፣
ከተሳታፊዎች የፈለቁ ሀሳቦችን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የጥናት ድርሳናትን በማየት
እንዲሁም አጥኚዎች በእያንዳንዱ ጉዳይ ላይ ውይይትና ክርክር በማድረግ በአምራች
ኢንዱስትሪው የግል ባለሀብቱን ለማጠናከር የቀረቡ የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦችን ለይቶ
ለማስቀመጥ ተሞክሯል፡፡

2.5 የጥናቱ ውስንነት

አንደኛው የዚህ ጥናት ውስንነት በክልልና በፌደራል መስራያ ቤቶች የሚገኘውን መረጃ
ልዩነትና ያለመናበብ ክፍተት መኖሩ እንዲሁም የተሟላ መረጃ ያለመገኘት ችግር
ነው፡፡ በዚህ ምክንያት የሚፈለገው መረጃ በሙሉ ባለመገኘቱ አልፎ አልፎ ሙሉ
ምስሉን ለመረዳት በተወሰነ ደረጃ ክፍተት መፍጠሩ አልቀረም፡፡ ሁለተኛ የጥናቱ
ውጤት ህጋዊ በሆነ መንገድ ይፋ የሆነው መረጃው ከተሰበሰበበት ጊዜ ዘግይቶ በመሆኑ
የተወሰኑ መረጃዎች ጊዜ ያለፈባቸው እንዲሆኑ አድርጎታል፡፡ነገር ግን በቀረቡት
የፖሊሲ አማራጭ ሀሳቦች ላይ ለውጥ አያመጣም፡፡ ሶስተኛው ክፍተት ይህንን የጥናት
ርዕሰ ጉዳይ (ማለትም የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ያለው
ስኬታማነትን የሚመለከት) ከሀገር ውስጥና ከውጭ በሚፈለገው ደረጃ ጠቃሚ የጥናት
ድርሳናት አለመኖራቸው እና ንፅፅራዊ ውድድር (Comparative analysis) ለማድረግ
አለመቻሉ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 34


ክፍል II የተዛማጅ ጥናቶች ዳሰሳ

ምዕራፍ 3
የተዛማጅ ጥናቶች ዳሰሳ

3.1 በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ኢንቨስትመንት

በተለያዩ ሀገራት በኢንዱስትሪ ልማት ዙሪያ የሚጠኑ ጥናቶች እንደ ጥናቱ ዓላማና
መረጃ የተለያየ ድምዳሜ ይዘው ይወጣሉ፤ የሚሰጡት የፖሊሲ ምክረ ሀሳቦችም እንዲሁ
ይለያያል፡፡ በእነዚህ ጥናቶች ከሀገር ውስጥ ባለሀብት ይልቅ የውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት ሰፊ ሽፋን አለው፡፡ በተለይ የምስራቅ ኤስያና ብራዚል የመሳሰሉ
የላቲን አሜሪካ ሀገራት በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እና የገበያ መር የኢኮኖሚ
ለውጦች ላይ የሚያተኩሩ ጥናቶች ቁጥር ከፍተኛ ናቸው፡፡

ብዙ የዘርፉ ተመራማሪዎች ሀገራት ዘላቂ የኢንዱስትሪና ኢኮኖሚ ዕድገታቸውን


ለማረጋገጥ በዋናነት ከውጪ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ይልቅ በሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብት ኢንቨስትመንት ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ይመክራሉ፡፡ ለምሣሌ ምዛ እና
ግሮይድ (በ2ዐዐ3 እ.ኤ.አ) የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት (Foreign Direct
Investment) በማለዥያ የኢኮኖሚ ዕድገትን የበለጠ ለማፋጠን የሚጠቅም ቢሆንም ነገር
ግን በተለይ በረጅም ጊዜ ዕቅድ ውስጥ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ላይ ከሚገባው
በላይ ማተኮርና እምነት መጣል ወይም መተማመን በሁለት ምክንያቶች ለማለዥያ
ተመራጭ ወይም ተመካሪ እንዳልሆነ ይገልፃሉ፡፡ አንደኛው የውጭ ባለሀብቶች
ኢንቨስት ለማድረግ ሲመጡ ትኩረታቸው የገበያ (market-seeking)፣ የሀብት
(resource-seeking) እና የቅልጥፍና (efficiency-seeking) ፍላጐታቸውን ለማሳካት
ሲሆን፤ ማለዥያ ደግሞ እነዚህ ጉዳዮች ላይ በብቃት ባለሀብቶችን መሳብ የሚያስችላት
ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ የመጣ መሆኑ፤ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ እንደ ምዛ
እና ዓይሮድ (2ዐዐ3 እ.ኤ.አ) ጥናት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት (FDI) በሀገሪቱ
መስፋፋቱ የሚጠበቀውን አዎንታዊ ለውጥ ወይም ውጤት ማምጣቱ እርግጠኛ
አለመሆን ወይም ጥያቄ የሚያስነሳ መሆኑ ነው፡፡ ማርሰን፣ ዙካፊሊ እና ሀሰሊንደር
የተባሉ ተመራማሪዎች በበኩላቸው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ጥቂት አዎንታዊ
ለውጥ ቢያመጣም ብዙ አሉታዊ ገፅታዎች (negative effects) ስለሚበዙበት አጠቃላይ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 35


የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውጤት የተጋነነ ነው የሚል መከራከሪያ ያቀርባሉ፡፡
በመሆኑም በአሁኑ ወቅት (በ2ዐ12 እ.ኤ.አ) ማለዥያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት
ላይ ያላት ዕምነት ጫፍ ደርሶ አሁን ትኩረቷ ወደ ሀገር ውስጥ የግሉ ባለሀብት መሆኑን
ገልፀዋል፡፡

በሌላ በኩል ሀገራት ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለማግኘት ያስቀመጡት አላማ


እየተሳካ መሆኑና አለመሆኑ እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቱ የሀገር ውስጥ ዓቅም
እያጠናከረ መሆኑ በየጊዜው እየተፈተሸ ካልሄደ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ከገበያ ውጭ
ሊሆን እንደሚችል በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ዙሪያ የሚጠኑ ጥናቶች ያመለክታሉ
(ፕሪማቻንድራ፣ እ.ኤ.አ 1996)፡፡ በተለይ የመጀመሪያ ዓላማቸው ገበያ ፍለጋ የሆኑት
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶች የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ከጨዋታ ውጭ የማድረግ
ኃይላቸው ከፍተኛ እንደሆነ ግዋንግዝህ፣ ሚካኤል እና ሚንግሁዋይ (እ.ኤ.አ 2015)
እንዲሁም ሚሪያ እና ዌንዥያ (እ.ኤ.አ 2015) ያስረዳሉ፡፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ
በኢንዱስትሪ ልማት ላይ ትኩረት ማድረግ የሚያስፈልግበት አንዱ ምክንያት የውጭ
ቀጥታ ኢንቨስትመንት በሀገራቱ የሚቆየው በኢንቨስተሩ እይታ የተሻለ ተወዳዳሪ ሌላ
አገር እስከሌለ ብቻ ነው (ግዋንግዝህ፣ ሚካኤል እና ሚንግሁዋይ፣ እ.ኤ.አ 2015፤ ሚሪያ
እና ዌንዥያ፣ እ.ኤ.አ 2015፤ ኩዋን እ.ኤ.አ 1991፤ ውኡ፣ እ.ኤ.አ 2011)፡፡

ግራፍ 3.1 አለማቀፍ የኢንቨስትመንት ፍሰት በሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር 1982-2005


(ምንጭ፡ UNCTAD)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 36


የተባበሩት መንግስታት የንግድና ልማት ኮንፈረንስ (United Nations Conference on
Trade and Development) መረጃ እንደሚያሳያው ከፍተኛው የውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት ፍሰት የሚይዘው የአገልግሎት ዘርፉ መሆኑን ያሳያል፡፡ እ.ኤ.አ እስከ
2012 በዓለማችን በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ከተመዘገበ ጠቅላላ ካፒታል
የአገልግሎት ዘርፉ 68.93 በመቶ ድርሻ የነበረው ሲሆን ኢንዱስትሪው 18.75 በመቶ
ብቻ ነው፡፡ ይህ ማለት የኢንዱስትሪ መዋቅሩ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት
የሚቃኙት ሀገራት በተለይ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቱ እንደልብ የማይገኝ
ይልቁንም በከፍተኛ ውድድር የተመሰረተ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሀገራት የራሳቸው
የውስጥ ዓቅም በአምራች ዘርፉ በስፋት ማሰማራት እንዳለባቸው አመላካች ተደርጎ
ሊወሰድ ይችላል፡፡

ከተለያዩ የጥናት ድርሳናት የምናየው ሌላው ተሞክሮ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት


በአስተናጋጅ አገር (Hosting Country) ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ኢንዱስትሪ መዋቅራዊ
ለውጥ የሚያበረክተው ሚና ተጨባጭ ፋይዳ የሚኖረው በሀገራቱ የመቀበል ዓቅም
(Absorbing capcity) ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነው፡፡ አስተናጋጅ ሀገራት የውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት የቴክኖሎጂ ሽግግር (ቴክኒካዊ፣ የገበያ፣ የስራ የኢንዱስትሪ አመራር፣
የኢንዱስትሪ የስራ ባህል፣ ወዘተ) ዕውቀትና ክህሎት ማስቀረት የሚችል ዓቅም የፈጠረ
የኢንዱስትሪ መዋቅር ሊኖር እንደሚገባ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮሩ
ጥናቶች በአፅንኦት ይገልፃሉ፡፡ ለምሳሌ ግዋንግዝህ፣ ሚካኤል እና ሚንግሁዋይ (እ.ኤ.አ
2015) የምስራቅ ኤስያ ሀገራት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በኢንዱስትሪና
በኢኮኖሚያቸው ያስመዘገቡት ስኬት በዚህ ምክንያት መሆኑን ያስረዳሉ፡፡

በአጠቃላይ ከላይ እንደተገለፀው ከሀገር ውስጥ የኢንቨስትመንት ፍላጎትን ከማሟላት ሆነ


ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ማግኘት የሚገባቸው ጥቅም (Spillover effect)
እንዲያገኙ ከተፈለገ መንገዱ የሀገር ውስጥ ዓቅም ተገቢውን ትኩረት መስጠት
እንደሚገባ ነው፡፡

3.2 አምራች ኢንዱስትሪን ለማጠናከር የቁጠባ እና መነሻ ካፒታል አስፈላጊነት

የኢንዱስትሪ የምጣኔ ሃብት ዘርፍን ለማልማት መነሻ ካፒታል፣ በዕውቀትና ክህሎት


የዳበረ የሰው ሀይል ያስፈልጋል፡፡ በንድፈ-ሐሳብ ደረጃ የካፒታል መነሻ አቅም ክምችት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 37


የሚከወነው በዘገምተኛ ኢኮኖሚ በራስ ወይም በተለመደው ሂደት አንደኛው አማራጭ
ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በታቀደ የመንግስት የነቃ ተሳትፎ ነው፡፡

ለኢንዱስትሪ ልማት የሚያስፈልገው ሀብት መከማቸት ያለበት ከሀገር ውስጥ ሀብት


መሆን እንዳለበት አንዳንድ ባለሙያዎች ይገልፃሉ (ዳቪድ፣ እ.ኤ.አ 2004)፡፡ በሀገር
ውስጥ የሀብት ክምችት ለማምጣት የመንግስት የነቃ ተሳትፎ ካልታከለበት በቂ ዓቅም
ለመፍጠር ፈታኝ መሆኑ አይቀርም፡፡ የምጣኔ ሀብት የታሪክ ድርሳናት እንደሚያሳዩት
በራስ ሂደት መነሻ የካፒታል ዓቅም መፍጠር የተቻለው በእንግሊዝ ብቻ ሲሆን ከዚያ
በኋላ የመጡት ጀርመን፣ ሶቭዬት ሕብረት፣ የምስራቅ ኤስያ እና የላቲን አሜሪካ ሀገራት
የካፒታል ስብስብ ዕውን ማድረግ የተቻለው በነቃና በታቀደ የመንግስት እንቅስቃሴ
መንገድ ነው፡፡ በዚህ መሠረት እ.ኤ.አ 2009 ዊልሰን እና አናሊሳ የተለያዩ ዋቢዎች
በመጥቀስ እንደሚሉት ካፒታሉ ከየትም ይገኝ ኢንዱስትሪውን ለማስጀመር የሚያስችል
የሀብት ክምችት ከሀገር ውስጥ ማሰባሰብ የግድ እንደሚል ነው፡፡

ሌላው የመነሻ ካፒታል ማሰባሰቢያ ስልት ቁጠባ ነው፡፡ ቁጠባ ለኢንዱስትሪ ዕድገት
የሚኖረው መስተጋብር በተለያዩ ሞዴሎች ሲጠና የቆየ ቢሆንም ታሪካዊ መረጃዎችም
ረዘም ላለ ጊዜ ከፍተኛ የሀገር ውስጥ ቁጠባ ተግባራዊ ያደረጉ ሀገራት ተከታታይ እና
ፈጣን የምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት ሲያስመዘግቡ ታይተዋል፡፡

ቁጠባ ከአጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ አጀንዳዎች ጋር ተያይዞ የሚታይ ነው፡፡ አምራች


ኢንዱስትሪው በማንኛውም የስፋት መጠን (Scale) ቢጀምርም በቀጣይነት ለማሳደግ
ራሱ ከሚያመነጨው ትርፍ የበለጠ ሰፊ ፋይናንስ ይጠይቃል፡፡ እ.ኤ.አ በ1993
የታተመው የዓለም ባንክ ጥናት ቁጠባ ለኢንዱስትሪ ልማትና ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት
ወሳኝ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎች ደግሞ ቁጠባ የምጣኔ ሀብት
ዕድገት ውጤት መሆኑ ሰፋፊ መረጃዎችን በማቅረብ ከሚከራከሩ ለምሳሌ ጆን ዊስ
(እ.ኤ.አ 2005) ተጠቃሽ ነው፡፡ አሁን በፈጣን ዕድገታቸው የሚታወቁት የምስራቅ
ኤስያ ሀገራት በ1960ዎቹ ፈጣን ዕድገታቸው ሲጀምር አጠቃላይ የሀገር ውስጥ
ቁጠባቸው (Gross Domestic Saving) ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርታቸው (Gross Domestic
Product) የነበረው ድርሻ ከ7%፣ እና 31% (ሆንግኮንግ) ነበር፡፡ በ1993 ግን የቁጠባው
ምጣኔ በጣም ከፍ ብሏል፡፡ ዝቅተኛው አሃዝ 28% (Taipie-Taiwan) ሲደርስ ከፍተኛው
50% (ሲንጋፓር) ተመዝግቧል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 38


የሀገር ውስጥ ቁጠባ ማጠናከር በዓለም የፋይናንስ ገበያ መዋዠቅ ምክንያት ሊደርስ
ከሚችለው መንኮታኮት ሙሉ በሙሉ ባያስቀርም ችግሩን ለመቅረፍ የራሱ ሚና
አለው፡፡ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ባላቸው ዝቅተኛ የሀገር ውስጥ ቁጠባ ምክንያት
ለኢንቨስትመንት የሚያስፈልጋቸውን የካፒታል ዕጥረት ለመፍታት ባለመቻላቸውና
ከውጭ በሚገኘው ፋይናንስ ጥገኛ በመሆናቸው ለኢንዱስትሪ ዕድገታቸው ዝቅተኛነት
ምክንያት ሆኖ እንደ ቀጠለ የተለያዩ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ለምሳሌ የሌኦንስ እ.ኤ.አ 2014
ጥናት አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ከ1970ዎቹ ጀምሮ ከጥቅል ሀገራዊ ምርት ሲሰላ
ሀገራዊ ጥቅል ቁጠባቸው (Domestic Saving to GDP Ratio) በተከታታይ እየቀነሰ
መምጣቱን ያሳያል፡፡ አማካይ የቁጠባ መጠኑ እ.ኤ.አ 1970ዎቹ ከነበረበት 22.8%
እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ ወደ 20% እና እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ ወደ 15.5% አሽቆልቁሏል፡፡

የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማሳደግ እና ዓቅም ለመፍጠር በተግባር ላይ የዋሉት


ስልቶችና የማበረታቻ ፓኬጆች እንደ ካፒታል ማከማቻ ስልት ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡

 አምራች ኢንዱስትሪውን ሊያዳክሙ የሚችሉት የንግድ ዘርፎች የንግድ ፈቃድ


መከልከል፣
 ገቢ ምርቶች የሚተካ ኢንዱስትሪ ማሳደግ ሲፈለግ የሀገር የመገበያያ ገንዘብ ከውጭ
ምንዛሬ ያለው ምጣኔ ማጠናከር (Appreciating value) እና ለውጭ ገበያ የሚያቀርብ
ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ሲፈለግ ደግሞ የሀገር ውስጥ የመገበያያ ገንዘብ የምንዛሬ
ዓቅሙ መቀነስ (Devaluation)፣
 በገቢ ምርቶች ተነፃፃሪ ከፍተኛ ግብር መጣልና የገቢ መጠኑም ኮታ መጣል፣
 የተመረጡ ኢንዱስትሪዎች ብድር እና የውጭ ምንዛሬ ቅድሚያ እንዲያገኙ
ማድረግ፣
 ለተመረጡ ኢንዱስትሪዎች (በፋብሪካ ደረጃም) የተለየ የውጭ ምንዛሬ ተመን
መስጠት፣
 ለቅንጦት ሸቀጦች የፋይናንስ አቅርቦት ገደብ መጣል፣
 የግዴታ ቁጠባ ወዘተ፣

ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ አሜሪካን ጨምሮ ቀድመው በኢንዱስትሪ ያደጉ ሀገራት በስራ ላይ


አውለውታል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ስልቶች በመሣሪያነት ከመጠቀም አኳያ ያስገኙት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 39


ውጤት በተግባር ከመተርጐም ይልቅ በፅንሰ-ሀሳባዊ ክርክር ደረጃ ሰፊ ውይይት
ሲደረግባቸው ይስተዋላል፡፡

በፍጥነት የዕድገት ለውጥ የሚታወቁ የምስራቅ ኤስያ ሃገራት የተከተሏቸው የማክሮ


ኢኮኖሚ መሳሪያዎች ከሞላ ጐደል ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ከሌሎች ታዳጊ ሀገራት
የሚለዩት በቁጠባ የሚከፈለው የወለድ ምጣኔ (Real Interest Rate) ከዜሮ በታች ብዙ
ያልራቀ እንዳይሆን ማድረጋቸው እና የዋጋ ግሽበት ምጣኔ ዝቅተኛ እንዲሆን ያላሰለሰ
ጥረት አድርገው ስኬታማ መሆናቸው ነው፡፡ እነዚህ ጥምር እርምጃዎች ሕብረተሰቡ
በአጠቃላይ በቁጠባ የተሻለ ርቀት እንዲጓዝ አስችሎታል፡፡ በተጨማሪም በፍጆታ
ዕቃዎች በተለይም በቅንጦት ሸቀጦች የፋይናንስ አቅርቦት እንዳይኖረው የተመቻቸ
ስልት ፈጥረው ተጉዘዋል (የዓለም ባንክ እ.ኤ.አ 1993፤ ሃጆው፣ ሆንግጂ እና ቹል እ.እ.አ
1998)፡፡ ሌላው ትልቅ ሚና የተጫወተው የመንግስት ቁጠባ ነው፡፡ ከ1970-1988 በ111
ሀገራት የተጠና ጥናት እንደሚያሳየው ከሌሎች ታዳጊና በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት
ይልቅ የምስራቅ ኤስያ ሀገራት የመንግስት ቁጠባ ከፍተኛ ነበር፡፡ የመንግስት ቁጠባ
በሲንጋፓር በ1974 ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ምጣኔ 5.5% የነበረ ሲሆን በ1980
ወደ18.5% ከፍ ብሏል፡፡ በተመሳሳይ ወቅት በማሌዥያ ከ3.2% ወደ 10.3% አድጓል፡፡
በአንፃሩ በሌሎች ታዳጊ ሀገራት የመንግስት ቁጠባ ዝቅተኛ ነበር፡፡ ለምሳሌ በፊሊፒንስ
ከ10.4% (1980-83 አማካይ) ወደ 1.4% ሲቀንስ በጋናም አሉታዊ ዕድገት አሳይቷል፡፡
እነዚህ በፈጣን ዕድገታቸው የሚታወቁ የምስራቅ ኤስያ ሃገራት የመንግስት ቁጠባቸውን
ከፍ ለማድረግ የተከተሉት ስልት ከፍተኛ ግብርና ታክስ መሰብሰብ ሳይሆን
ትኩረታቸው የመንግስት ወጪን መቀነስ ነበር፡፡

ስለዚህ የመንግስት ሚና በቁጠባ አሰባሰብ እና የተሰባሰበው የፋይናንስ አቅም በተገቢው


መንገድ ለኢንዱስትሪው ፈጣን ዕድገት እንዲውል በማድረግ የምስራቅ ኤስያ ሀገራት
ከሌሎች ሃገራት የተሻለ ተነፃፃሪ የማስፈፀም ብቃት እንደነበራቸው አብዛኛው በምጣኔ
ሀብት ዕድገትና የኢንዱስትሪ ልማትና የፖሊሲ ነክ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡

3.3 የኢንዱስትሪ ልማት፣ የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ እና የሰው ኃይል ልማት

የካፒታል ዓቅም ብቻውን ለኢንዱስትሪ ልማት ስኬት በቂ እንዳልሆነ ከተለያዩ ሀገራት


ተሞክሮዎች መማር ይቻላል፡፡ ለአምራች ኢንዱስትሪው ልማት ከካፒታል በተጨማሪ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 40


ሌላው ወሳኝ ጉዳይ የሰው ሀብት ልማትና የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ መሆናቸው ብዙ
አያከራክርም፡፡

በኢንዱስትሪ ልማት ዕድገትና በኢንቨስትመንት (ቁጠባ) ያለው መስተጋብራዊ


ግንኙነት እንደሚጠና ሁሉ ለሰው ሃይል ልማት እና በኢንዱስትሪ ልማትም ተመሳሳይ
ጥናት ይካሄዳሉ፡፡ የነዚህ ግንኙነት ውጤትም ቀጥተኛ መሆኑ ይታመንበታል፤ ኔልሰን
እና ፓክ (እ.ኤ.አ 1999)፡፡ የደቡብ ምስራቅ ኤስያ ሃገራት ከ1960-1989 ያስመዘገቡት
የኢኮኖሚ ዕድገት በተጨማሪ በኢንቨስትመንትና በቁጠባ ይመጣል ተብሎ ከተገመተው
በላይ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በቴፒ 4.7% እንዲሁም በኮሪያ ደግሞ 3.2% ከተገመተው
ዕድገት በላይ ተመዝግቧል፡፡ ይህ ልዩነት የቴክኖሎጂና የሰው ኃይል ብቃት ውጤት
መሆኑ ይገለፃል፡፡ ሌሎች በርካታ ጥናቶችም በላቲን አሜሪካ፣ ከሰሀራ በታች የሚገኙ
የአፍሪካ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት፣ ወዘተ በንፅፅር ውጤታቸው ሲያቀርቡ የሰው ኃይል
ሙያዊ ብቃትና የቴክኖሎጂ ዓቅም ለኢንዱስትሪ ዕድገት እጅግ ወሳኝ መሆኑን
ያስረዳሉ፡፡

ሀገራት የራሳቸው ቴክኖሎጂ መፍጠር ደረጃ ላይ ካልደረሱ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ


ትምህርት በቂ መሆኑን ነገር ግን ቴክኖሎጂ ማላመድና ማሻሻል ሲጀመር ከፍተኛ
ትምህርት አስፈላጊ መሆኑ ይገለፃል (አሽፎርድ እ.ኤ.አ 2012)፡፡ በፈጣን ዕድገታቸው
የሚታወቁት የምስራቅ ኤስያ ሀገራት ለትምህርት ከሚመደበው በጀት አብዛኛው
ለታችኞቹ የትምህርት እርከኖች (1ኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት) ሲያውሉት የሰው
ኃይላቸውን ከታች ጀምሮ እያበቁ እንዲሄዱ አድርጓቸዋል፡፡ የደቡብ ኤስያ፣ ላቲን
አሜሪካ እና ከሰሃራ በታች የሚገኙት ሀገራት ደግሞ አብዛኛውን ለትምህርት
የሚያወጡት በጀት ለከፍተኛ ትምህርት ማለትም ለዩኒቨርስቲዎች ይውላል፡፡

ሌላው ከደቡብ ምስራቅ ኤስያ ሀገራት የሚወሰድ ልምድ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና


ስልጠና የሚመለከት ነው፡፡ በመደበኛ ትምህርት ዓይነት የሚሰጡት የቴክኒክና ሙያ
ስልጠናዎች የኢንዱስትሪ ልማቱን ፍላጎት የሚመጥን ክህሎትና ዕውቀት የጨበጠ (Firm
level trained) አለመሆኑን በመረዳታቸው በእነዚህ ሀገራት ያሉ ፋብሪካዎች የሰው ኃይል
ከገበያ ከመቅጠር ይልቅ በራሳቸው አሰልጥነው በመቅጠር ከፍተኛ ውጤት
አስመዝግበዋል፡፡ ለምሳሌ በ48,000 የታይዋን አምራች ፋብሪካዎች በተደረገው ጥናት
እንደሚያመላክተው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከተመረቁ ይልቅ በፋብሪካ ደረጃ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 41


የሰለጠኑ ሰራተኞች በምርታማነትና የቴክኖሎጂ ብቃት ውጤታማ ሆነው ተገኝተዋል፡፡
በኮሪያ በመርከብ ኢንዱስትሪ የተደረገ ጥናትም ተመሳሳይ ግኝት አለው፡፡ በዚህ
ምክንያት መንግስት በ1974 ያወጣውን የስድስት ወራት መደበኛ የቴክኒክና ሙያ
የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ብዙዎቹ የኮሪያ ካምፓኒዎች በተቃውሞ አስቀርተውታል
(የዓለም ባንክ እ.ኤ.አ 1993)፡፡

በተለያዩ ጥናቶች የምናየው ሌላው አማራጭ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ጋር


ተያይዞ የሚፈጠር የቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር ነው፡፡ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት
ከሚሰጣቸው ጥቅሞች የፋይናንስ አማራጭ መሆንና የቴክኖሎጂ ሽግግር በግንባር
ቀደምትነት ይጠቀሳሉ፡፡ የቴክኖሎጂ /ዕውቀትና ክህሎት/ ሽግግሩ በሰራተኞች ፍሰት
ምክንያት (Turn over from the foreign firms to local firms) ወይም የውጭ ኢንቨስተሮቹ
ከሀገር ውስጥ የመንግስትም ሆነ የግል ኩባንያዎች በሽርክና የሚሰሩ ከሆነ በግል
ሰራተኛ ፍሰት አማካኝነት ከሚገኝ የበለጠ ዓቅም ለመፍጠር ያስችላል፡፡ ሌላኛው ስልት
የውጭ አምራች ኢንዱስትሪውን እንደ ማስልጠኛ ማዕከል በመጠቀም የሀገር ውስጥ
ኢንዱስትሪዎች የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲያገኙ በታቀደ ሁኔታ መስራት የመሳሰሉት
ናቸው፡፡ ነገር ግን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በስፋት የሳቡ ሀገራት በበቂ ሁኔታ
የዕውቀትና ክህሎት ሽግግር ተጠቃሚ እንዳልሆኑ ይገለፃል (ማኒትራ፣ ሻላ፣ እና
ሚካኤል እ.ኤ.አ 2014፤ እ.ኤ.አ 2014፤ ሌድንስ)፡፡

3.4 ገቢ ምርቶች መተካት እና ለውጭ ገበያ ማምረት

በኢንዱስትሪ ልማት አቅጣጫ በንድፈ ሐሳብና በተግባር ተሞክሮዎች ላይ ተመስርቶ


የሚነሳው አከራካሪ ጉዳይ ገቢ ምርቶች የሚተካ (Import Substitution Industry) እና
ለውጭ ገበያ ማምረት (Export oriented Industry) ትኩረት የመስጠት ጉዳይ ነው፡፡
የክርክሩ ማዕከልም በአስፈላጊነት ሳይሆን በፍጥነት ለማደግ በሚያስመዘግበው ስኬት
እና ለምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት በሚጫወተው ሚና በማነፃፀር ላይ ያተኮረ ነው፡፡

ገቢ ምርቶችን የሚተካ ኢንዱስትሪ ለዕድገት የማይበጅ መሆኑ የሚቀርብለት ትንተና


ከኢንዱስትሪው ባህሪ እና ከፖሊሲ አቅጣጫው ሊታይ ይችላል፡፡ ከፖሊሲ አቅጣጫው
ሲታይ ሀገራት ይህንን ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ሲባል ከድጐማ አንስቶ፣ የፋይናንስ
አቅርቦት፣ ወዘተ የተለያዩ የማበረታቻ ስርዓቶች እስከ ተመሳሳይ ገቢ ምርቶች መገደብ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 42


አልያም ጠቅላላ የገበያ ክልከላ የሚደርሱ የፖሊሲ እርምጃዎች ስለሚወስዱ
ኢንዱስትሪው በሀገር ውስጥ ገበያ ብቻ እንዲወሰን ስለሚያደርገው በብዛት /በስፋት/
ማምረት ስለማይችል የማምረት አማካይ ወጪው ከፍተኛ እንደሚሆን፤ በገቢ ምርቶች
ላይ የሚጣለው ማንኛውም ገደብ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪው ከተለያዩ የቴክኖሎጂ
ውጤቶች እንዳይተዋወቅ እና ወደፊት እንዳይራመድ እንደሚገድብ፤ በምርቶች ጥራት
ተወዳዳሪ እንዳይሆን እንደሚያደርጉት ይገለፃል፡፡ በነዚህ ምክንያት ኢንዱስትሪው ሰፊ
ምርት ባለማምረቱም የገበያ ፍላጐቱ ሙሉ በሙሉ ሟሟላት ካለመቻሉ በላይ
ያልተመጣጠነ የንግድ ሚዛን የወለደው ያልተስተካከለ የክፍያዎች ልውውጥ (Balance of
payments) ያስከትላል የሚሉ ይገኙባቸዋል (ማኒትራ፣ ሻላ፣ እና ሚካኤል እ.ኤ.አ
2014)፡፡ ለምሳሌ እንደ ራኸይስ (እ.ኤ.አ 1991) አባበል ብራዚል እና ሜክሲኮ እስከ
1970ዎች ገቢ ምርቶች ተኪ ኢንዱስትሪዎች ትኩረት ሰጠው ሲሰሩ እንደቆዩና የደቡብ
ምስራቅ ኤስያ ሀገራት ግን ኢንዱስትሪያቸው በውጭ ሰደድ ያተኮረ እንዲሆን
እንዳደረጉት፤ በዚህ ምክንያት የሀገራቱ የምጣኔ ሀብት እድገት ከላቲን አሜሪካ ሀገራት
ዕደገት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ብልጫ አሳይቷል፡፡ በተጨማሪም የላቲን አሜሪካ ሀገራት
የክፍያዎች ልውውጥ ሚዛን (Balance of payment) ጫና ምክንያት በ1970ዎች መጨረሻ
እና በ1980ዎች መጀመሪያ አከባቢ ገቢ ምርት በመተካት የተመሰረተ
ኢንዱስትሪያቸው ለማስቀጠልም ከፍተኛ መንገራገጭ አጋጥሟቸዋል፡፡ ይህ ሁኔታም
ለውጭ ገበያ በማምረት የተቃኘ ስልት ያተኮረ ኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ላይ
ሲታይ የነበረ የተዛባ የልማት አመለካከት እንዲቀረፍ ምክንያት እንደሆነና በውጭ
ገበያ የተመሰረተ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ አዋጭ የልማት ስትራቴጂ ተደርጎ
እንዲወሰድ ምክንያት እንደሆነ ይገለፃል፡፡

ገቢ ምርቶች የሚተካ ኢንዱስትሪ በታዳጊ ሀገራት ማቋቋም ያስፈለገው ወደ ሀገር ውስጥ


የሚገቡ አብዛኞቹ ምርቶች የተወሳሰበ ቴክኖሎጂ እና እውቀት እንዲሁም ቴክኒካዊ
ችሎታ በብዛት የማይጠቀሙ የፍጆታ ዕቃዎች (durable and non-durable consumer goods)
ከመሆናቸው የተነሳ በሀገር ውስጥ የኢንዱስትሪ ልማት ለመከወን እንደ መነሻ መማሪያ
እንዲሆኑ ታሳቢ ተደርጎ ነው (ካናዮ፣ አቼ እና ኢነዌር እ.እአ 2011)፡፡ ይህ ማለት
በግብአት ሰንሰለቱ የመጨረሻው ምርት (Final Product) ብቻ የሚያመርት ዓይነት
ከመሆኑ በተጨማሪ የሚያመርተው ምርትም ለፍጆታ አገልግሎት የሚውሉ ናቸው፡፡
የቴክኖሎጂ ፈጠራና ሽግግር የሚዳብረው በግብአት ካፒታል ዕቃዎች (intermediate
capital goods) ምርት ስራ ነው፡፡ ገቢ ምርቶች የሚተካው ኢንዱስትሪ ግን የመጨረሻው

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 43


ምርት በማምረት ስራ የተሰማራ በመሆኑ ለፈጠራና የቴክኖሎጂ ዕድገት ዕድል
የማይሰጥ ነው፡፡

በአንፃሩ በውጭ ሰደድ ምርት ያተኮረ (Export Oriented) ኢንዱስትሪ ራሱን በፍጥነት
ከማሳደግ እና አጠቃላይ የምጣኔ ሀብት መዋቅራዊ ለውጥ ከማምጣት አኳያ ይበልጥ
ስኬታማ መሆኑ በስፋት ይተነተናል (ፔተር እ.ኤ.አ 2002፤ የጋራ ብልፅግና ሀገራት
ድርጅት እ.ኤ.አ 2002) የዚህ ኢንዱስትሪ የስኬት መገለጫዎች በገቢ ምርቶች ተኪ
ኢንዱስትሪ ውድቀት ምክንያት ናቸው በሚል የሚገልፁት ናቸው፡፡

ይሁንና በንድፈ ሐሳብ ደረጃ በሚገባ መታየት ያለበት ጉዳይ እንዳለና በተግባራዊ
ተሞክሮም ተጨባጭ ልዩነት እንዳለ ግልፅ ነው፡፡ የውጭ ገበያ ዕድል ማስፋት
ለምርታማነት ቅድመ ሁኔታ ተደርጐ መወሰዱ የሚያስኬድ አይመስልም፡፡ ሀገራትም
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የሚፈልጉበት ምክንያት እንዲሁም ድንበር ተሻጋሪ
ኩባንያዎች (MNC) በሌላ ሀገር የሚሰማሩበት ምክንያት በእነዚህ ሀገራት ያልተሸፈነ
ሰፊ ገበያ በመኖሩ መሆኑ ከዋናዎቹ ምክንያቶች አንዱ ነው፡፡ ስለዚህ ሀገራት
የውስጣቸው ገበያ ሳይሸፍኑ የውጭ ገበያ የሚያፈላልጉበት ምክንያት አሳማኝ
አይደለም፡፡ ጆን (እ.ኤ.አ 2005) በደ/ምስራቅ ኤስያ ሀገራት ያደረገው ጥናት ይህንን
ሀሳብ የሚያጠናክር ሆኖ ይታያል፡፡በፋብሪካዎች ደረጃ (Firm level) ያለ መረጃ
በመሰብሰብ ያጠናው ጥናት እንደሚያመለክተው ምርታማነት ሲጨምር ኢንዱስትሪው
ተጨማሪ ገበያ ፍለጋ እንደሚጀምር እንጂ ገበያ ለምርታማነት ቅድመ ሁኔታ አለመሆኑ
ነው፡፡

በዋናነት በገቢ ምርቶች መተካት የተሰማሩ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪ የቴክኖሎጂ


አቅማቸው እና ምርታማነታቸው ለማሳደግ ብሎም ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚያዊ ሽግግር
ወሳኝ ሚና እንዲጫወት የካፒታል ዕቃዎች ገቢ ንግድ ገደብ ሊደረግበት እንደማይገባ
እንደ አማራጭ ብቻ ሳይሆን ወሳኝ መሆኑም በብዙዎቹ የዘርፉን አጥኚዎች ትኩረት
ስቧል፡፡ ይሁንና (ኢቭጊኒ እና ጃውአቶን እ.ኤ.አ 2014) በፋብሪካ ደረጃ እና
በኢንዱስትሪ ደረጃ የሚገለፅ መረጃ በመውሰድ በጋና፣ ታንዛንያ እና ኬንያ ባደረጉት
ጥናት የሀገር ውስጥ መሰረታዊ የሆነ የኢንዱስትሪ ባህል ያላዳበሩ፣ የጥናትና ምርምር
ስራዎች የማይሰሩ እና ዝቅተኛ ቴክኒካዊ ብቃት ያላቸው ኢንዱስትሪዎች ከገቢ
ካፒታል ዕቃው የሚገኘው አዳዲስ ዕውቀት መጠቀም እንዳልቻሉ ያሳያል፡፡ በተመሳሳይ
(ማኒትራ፣ ሻላ፣ እና ሚካኤል እ.ኤ.አ 2014) የኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሞሪሽየስ አምራች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 44


ኢንዱስትሪዎች ከ1969-1997 የነበራቸውን አፈፃፀም መረጃ ወስደው እንዳጠኑት ከገቢ
ካፒታል ዕቃዎች ይልቅ የሰው ኃይል ልማት (በተለይ በጥናትና ምርምር ዘርፍ እና
ስራ አመራር) የአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነት ለመጨመር የበለጠ አስተዋፅኦ
እንዳለው ይገልፃሉ፡፡

ኮሪያና ቻይና ለብቻ ለይተን ካየን የአምራች ኢንዱስትሪ መዋቅር ዓይነት (Export
Oriented versus Import Substitution) ያን ያህል ልዩነት ፈጣሪ እንዳልሆነ መገንዘብ
ይቻላል፡፡ ልዩነት ሊፈጥር የሚችለው የባለቤትነት ጉዳይ (የውጭ ኩባንያ ወይም የሀገር
ውስጥ ኩባንያ) ይሆናል፡፡ በተግባርም በላቲን አሜሪካ ሀገራት ታይቷል፡፡ አብዛኞቹ
በኢንዱስትሪ ልማትና ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት ጥናት ያካሄዱ የተለያዩ ባለሙያዎችና
ተቋማት የሚከተሏቸው የኢንዱስትሪ ሴክተር ፖሊሲዎች ከልዩነታቸው ይልቅ
ተመሳሳይነታቸው እንደሚያመዝን ያስረዳሉ (ራኸይስ እ.ኤ.አ 1991)፡፡ልዩነቱ የሚታየው
በትግበራውና ተጠቃሚው ሴክተር ልዩነት ነው፡፡

ሌላው መሠረታዊ ጉዳይ ለገበያ ክፍት መሆኑና አለመሆን ይመለከታል፡፡ የላቲን


አሜሪካ ሀገራት በራሳቸው በነፃ ገበያ ክፍት ያደረጉት ቀድመው ከ195ዐዎቹ (ጉይሌርሞ
እ.ኤ.አ 2006፣ ሮበርት እ.ኤ.አ 2006) ጀምሮ ነበር፤ የደቡብ ምስራቅ ኤስያ ሀገራት
ደግሞ የገበያ አክራሪዎች ጫና በመቋቋም የውስጥ ዓቅማቸውን ለውድድር ብቁ መሆኑ
እየመዘኑ ቀስ በቀስ ነበር የተገበሩት፡፡ በራሳቸው ለገበያ ክፍት ያደረጉትም የገበያ
አክራሪዎች ባስቀመጡት ዓይነት አካሄድ ሳይሆን የደቡብ ምስራቅ ኤስያ የራሳቸው
አዲስ ስልት በመቀየስ ነበር (ሮበርት እ.ኤ.አ 2005)፡፡ የደቡብ ምስራቅ ኤስያ ሀገራት
የአምራች ኢንዱስትሪ ስኬት በራሳቸው ለገበያ ክፍት በማድረጋቸው ምክንያት መሆኑን
ለማስረዳት ከሚሞክሩት በርካታ ጥናቶች የዓለም ባንክ ያወጣቸው 1987 እና 1999
የዓለም ዕድገት ሪፖርት (World Development Report) አንዱ ሲሆን ልቅ በሆነ የገበያ
መርህ የሚመሩ ሀገራት ከፍተኛ የምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት (GDP) ሲያስመዘግቡ ለሀገር
ውስጥ ገበያ ምርት ትኩረት የሚሰጡ ደግሞ ዝቅተኛ ወይም አሉታዊ ዕድገት
እንደሚያስመዘግቡ ያሳያል (ፓሃሪይ እ.ኤ.አ 2008)፡፡

በአጠቃላይ ከላይ በዝርዝር ከቀረቡት የሀገራት ተሞክሮዎችና ትምህርቶች


የሚከተሉትን ጠቃሚ ሀሳቦች ግምት ውስጥ ማስገባት ወይም መውስድ ይቻላል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 45


 የመነሻ ካፒታልና የሰው ኃይል ልማትና የቴክኖሎጂ ዓቅም ማሰባሰብን አምራች
ኢንዱስትሪ ለማልማት እኩል አስፈላጊዎች እንጂ አንዱ ሌላውን የማይተካ
መሆናቸው ነው፡፡
 ከውጭ ኩባንያዎች (FDI) እና የካፒታል ዕቃዎች ግዥ (የገበያ አማራጭ) ተገቢውን
የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪው እና የሰው
ኃይሉ ክህሎት ብቃት ሊኖረው እንደሚገባ፤ በቴክኖሎጂ ሽግግሩ የመንግስት
ቀጥተኛ ተሳትፎም ሊታለፍ የማይገባ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም የግሉ ዘርፍ
በታቀደ ሁኔታ የቴክኖሎጂ መቅዳትና ማላመድ እንዲሁም ማሻሻል ከመሰራት
አኳያ ክፍተት ይታይበታል፡፡ ሆኖም ግን የግል ሴክተሩ በጥናትና ምርምር ንቁ
ተሳታፊ ካልሆነ የመንግስት ጥረት ብቻ የሚፈለገውን ስኬት ማስገኘት አይችልም፡፡
 ለምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትና መዋቅራዊ ለውጥ ሁነኛው መፍትሔ በንግድ ላይ
መንጠልጠል ሳይሆን የተቀናጀ የኢንቨስትመንት ውጤት መሆኑ ከላቲን አሜሪካ
እና ደቡብ ምስራቅ ኤስያ ተግባራዊ የፖሊሲ ተሞክሮዎች አስረጂዎች ናቸው፡፡
 የኢንዱስትሪ ዓቅም ከማጐልበት አኳያ እንዲሁም ለምጣኔ ሃብታዊ ዕድገት ለውጭ
ገበያ የሚያመርቱም ሆነ ገቢ ምርቶችን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች
ማማረት ቀዳሚ መፍትሔ አለመሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ በውጭ ሰደድ
ምርት የተሰማሩት ኢንዱስትሪዎች የውጭ ምንዛሬ ሲያስገኙ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ
የሚያመርቱ ደግሞ የውጭ ምንዛሬ ፍላጐት ይቀንሳሉ፡፡ ስለዚህ ውጤታቸው አንድ
ዓይነት ነው፡፡ ምናልባትም መታየት ያለበት እንደ ኮርያና ቻይና የመሳሰሉት
ሀገራት ለውጭ ገበያ የሚያመርት ጠንካራ ኢንዱስትሪ መገንባት የቻሉት ቀደም
ሲል ገቢ ምርት የሚተካ ኢንዱስትሪ ላይ አትኩረው ሲሰሩ በፈጠሩት ዓቅም እንጂ
ከጅምሩ በውጭ ሰደድ ኢንዱስትሪ እንዳልተጓዙ ነው፡፡ በመሆኑም የሀገር ውስጥ
ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ ገበያ መሸፈን እንዲችል ምን ያህል ትኩረት ይሰጠዋል
የሚል ይሆናል፡፡

ስለዚህ ሀገራት በጀመሩት የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ኮቴ ተከትለው (Path


Dependence) የማስፈፀም ዓቅማቸውን በየጊዜው እያሻሻሉ እልህ አስጨራሽ ስራ ከተሰራ
በየትኛውም አቅጣጫ ቢጀመርም አምራች ኢንዱስትሪው ስኬታማ በሆነ መንገድ
ማልማት እንደሚቻል ያሳያል (ውኡ እ.ኤ.አ 2011፣ ሮበርት እ.ኤ.አ 2008)፡፡ ይህ
ማለት የሀገር ውስጥ ባለሀብት በየትኛው ኢንዱስትሪ (Import Substitution or Export

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 46


Oriented) ይሰማራል የሚል መሠረታዊ ጥያቄ እንዳልሆነ ያሳያል (ፓኸና እ.ኤ.አ
2008)።

3.5 የመንግስት ተነፃፃሪ ነፃነት እና የማስፈፀም ዓቅም ጥንካሬ

አብዛኞቹ የጥናት ድርሳናት ለኢንዱስትሪ ልማት ስኬት ልዩነት የፖሊሲ ልዩነት


መሆኑን ይከራከራሉ፡፡ የላቲን አሜሪካና የምስራቅ ኤስያ ሀገራት በማነፃፀር የተጠኑ
ጥናቶች የሚያሳዩት ግን ከፖሊሲው ልዩነት ይልቅ የመንግስታቱ የማስፈጸም ዓቅም
ይበልጥ ወሳኝ መሆኑ ያስረዳሉ፡፡ መንግስታት ፖሊሲውን ለማስፈጸም የሚከተሏቸው
ስትራቴጅዎችና የመንግስት መዋቅር ቢሮክራሲ እጅግ ወሳኝ መሆናቸው አንዳንድ
ጥናቶች በአፅንኦት ይገልፃሉ። የፖሊሲ አቅጣጫውም ቢሆን የመንግስታቱ ጥንካሬ
ውጤት ናቸው የሚል መከራከሪያ ያቀርባሉ።

በላቲን አሜሪካ እና በምስራቅ ኤስያ የኢንዱስትሪ ዕድገት ታሪክ የፖሊሲ ልዩነቱ የጎላ
እንደነበር የሚታወቅ ቢሆንም የተወሰኑ የምስራቅ ኤስያ ሀገራት በውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት ላይ በመመስረት (ሲንጋፖር)፣ ለውጭ ገበያ የሚያመርት የኢንዱስትሪ
ዓይነት ላይ ትኩረት በማድረግ (ከኮሪያና ታይዋን በስተቀር)፣ ነፃ ገበያ መርህ
በመተግበር (ሆንግኮንግ) የላቲን አሜሪካ አቻቸውን ፈለግ የተከተሉም ነበሩ፡፡ ነገር ግን
የምስራቅ ኤስያ ሀገራት ከላቲን አሜሪካ አቻዎቻቸው በተሻለ ሁኔታ ቀድመው ልማት
ያሳኩት ልዩነቱ የፖሊሲ ሳይሆን የመንግስታቱ ጥንካሬ እና ልማትን የመምራት ብቃት
መሆኑ ራይስ የተባለ (እ.ኤ.አ 1991) ይገልፃል፡፡

ራይስ እንደሚለው በአብዛኛው የላቲን አሜሪካ ሀገራት ፖሊሲዎች ከሀገራቱ ከውስጣዊ


ኢኮኖሚያዊ ሁኔታቸው የመነጩ ሳይሆኑ በተለያዩ አካላት ፍላጎት የሚቃኙ ነበሩ፡፡
ከላቲን አሜሪካ ሀገራት ይልቅ የምስራቅ ኤስያ ሀገራት መንግስት ከተለያዩ አካላት
ማለትም የውጭ ባለሀብት፣ የሀገር ውስጥ ባለሃብትና የተለያዩ ተጽዕኖ ፈጣሪ
የሕብረተሰብ ክፍሎችና ቡድኖች ተነፃፃሪ ነፃነት ስለነበረው የፖሊሲ አውጭነት ሚናው
ከሀገሩ አጠቃላይ የልማት አጀንዳ የሚመነጭ ዓላማ ለማሳካት የሚያስችል እንዲሆን
ዕድል ሰጧቸዋል፡፡ በምስራቅ ኤስያ በአንጻሩ የፖሊሲ አቅጣጫው ምን ይሁን ምን
መነሻው ሀገራዊ ሁኔታው ነው ይላል፡፡ለዚም ነው ማንኛውም ዓይነት ፖሊሲ በምስራቅ
ኤስያ ሲሳካ በላቲን አሜሪካ ዘገምተኛ የሆነው የሚል መከራከሪያ ይቀርባል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 47


ከፖሊሲ ማውጣት በዘለለ የመንግስት የአመራር ብቃት በምስራቅ ኤሲያ ሀገራት ከላቲን
አሜሪካ አቻቸው የተለየ ጥንካሬ ነበረው፡፡ የመንግስት መዋቅሩ ልማቱን መምራት
የሚያስችል ውጤታማ ቢሮክራሲ በመገንባታቸው የኢኮኖሚ ስትራቴጂያቸው በተሳካ
መንገድ ለመፈጸም አስችሏቸዋል፡፡ በኢኮኖሚ እና ኢንዱስትሪ ልማት የመንግስት
አመራር ውጤታማ የሚሆነው መንግስት የመሪነት ሚና ስለተሰጠው ብቻ ሳይሆን
ከተለያዩ ኃይሎች ተነፃፃሪ ነፃነት የተጠበቀ ሆኖ የመሪነት ሚናውን መከወን የሚችል
ብቃት ያለው የመንግስት መዋቅር ሲፈጠር፣ እነዚህ የተለያዩ የመንግስት መዋቅሮች
የተሰጣቸውን የስራ ሀላፊነት ሲወጡ፣ ድምር ውጤቱ አጠቃላይ የልማት ዓላማው
በሚያሳካ መልኩ (Successes and achievements of each and either of the government entities
must ensure avoidance of suboptimization over achievement of the entire development
objectives) መናበብና መቀናጀት ወሳኝ ነው ተብሎ ይወሰዳል፡፡ በዚህ ረገድ በመንግስት
ቢሮክራሲ ተቋማዊ ተአማኒነት (corporate loyality) በመፍጠር ኮሪያ የስኬት ምሳሌ
ተደርጋ ትወሰዳለች (ጆን፣ እ.ኤ.አ 2005 እና ሮበርት፣ እ.ኤ.አ 2008)፡፡ ራይስ
እንደሚለው ከሆነ በምስራቅ ኤስያ ሀገራት በተለይ በኮሪያ የመንግስት ሰራተኛው
ከፖለቲካ መዋቅሩ አባልነት ውጭ መደረጉ ቢሮክራሲውን ፈጣን አድርጎታል፤ በአንጻሩ
በላቲን አሜሪካ ሀገራት (አርጀንቲናና ሜክሲኮ) በርካታው የመንግስት ሰራተኛ የፖለቲካ
ሹመኛ በመሆኑ ለመንግስት መዋቅሩ ውጤታማነት በዕንቅፋትነቱ የሚፈረጅ ተሞክሮ
ሰጪ ነው ይላል፡፡

እንደ ጎ-ሺማዳ (እ.ኤ.አ 2013) ደግሞ የመንግስት ቢሮክራሲው በፖሊሲ ማቀድ እና


ፖሊሲ ትግበራ ላይ የሚያደርገው ቀጣይ የመማር ሂደት የማስፈጸም ዓቅሙ
ያጎለብታል፡፡ ይህ ፀሐፊ በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፖሊሲ ያካሄደው ጥናት ላይ
ተመስርቶ በፖሊሲ እቅድ ሰፊ ክፍተት መኖሩ ሲያመላክት ሚኒስትሮችና ሌሎች
ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በተለያዩ መድረኮች የሚያቀርቡት የፖሊሲ
አቅጣጫዎችና የፖሊሲ ሰነዶቹ ልዩነት እንዳላቸው አንደኛው ሲሆን ሁለተኛው
በከፍተኛ አመራሩና በፖሊሲ ፈጻሚ ሲቪል ሰርቫንቱ በፖሊሲዎቹ ዙሪያ የተራራቀ
ዕውቀት መኖሩና ፖሊሲ የመማር ስልቱ ጠባብ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ከዚህ ፀሐፊ
መረዳት የሚቻለው ጠቃሚ ጉዳይ በሀገራችን የኢንዱስትሪ ፖሊሲ ላይ በሁሉም
የመንግስት ቢሮክራሲው በደንብ ያልተጨበጠና በባለቤትነት ያልተያዘ መሆኑን
ያስረዳል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 48


ጎ-ሺማዳ (እ.ኤ.አ 2013) በሁለተኛ እርከን የሚያስቀምጠው የመማር ተግባር የፖሊሲ
ትግበራ ነው፡፡ የመንግስት ፖሊሲ በተሳካ መንገድ የመተግበር ብቃት በቢሮክራሲው
መዋቅር ብቃት ይወሰናል፡፡ በየጊዜው በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርቶ ትምህርት
እየተወሰደ የማስፈጸም አቅሙ ላይ አስፈላጊ ማስተካከያ ሊደረግ ይገባል ይላል፡፡

3.6 ለግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት ወሳኝ ሁኔታዎች

በአጠቃላይ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ባጭር ጊዜ ትርፍ የሚገኝበት ባለመሆኑ


ባለሀብቱ የሀገሪቱ አጠቃላይ ሁኔታ ለረጅም ጊዜ ለኪሳራ የማያጋልጥ መሆኑ መገምገም
እንደሚገባው የምጣኔ ሀብት ምሁራን ያስቀምጣሉ፡፡ ይህንን ግምገማ ለማድረግ
የተለያዩ ሁኔታዎች ከግምት ማስገባቱ የማይቀር ነው፡፡ ለግምገማው ታሳቢ ያደረጋቸው
የግል ባለሀብቱ በኢንቨስትመንት ላይ ያለውን ተሳትፎና እንቅስቃሴ የሚገድቡ ወይም
ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡ ቀጣይነት ያለው የፖለቲካ እና የማክሮ
ኢኮኖሚ መረጋጋት በአንድ ሀገር ውስጥ አስፈላጊ ሲሆኑ፤ ባለሀብቱ በኢንዱስትሪ
ኢንቨስትመንት ለመሰማራት ከሚወስኑት ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ መሆናቸውን
የተለያዩ የፖሊሲ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡

ከአጀንዳዎቹ የሀገሪቱ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ፖሊሲ በተለይ ደግሞ የኢንዱስትሪ ልማት


ፖሊሲ ምናልባት ቀዳሚውን ደረጃ ይዞ ይገኛል፡፡ በተለይ ሀገራት የሚከተሉትና
የሚያራምዱት ርዕዮተ ዓለም የኢንዱስትሪ ፖሊሲው የስሕበት ማዕከል ሆኖ ይገኛል፡፡
ይህንን ለመረዳት የተለያዩ ጥናቶች በላቲን አሜሪካ በምስራቅ ኤስያ እና በአፍሪካ
ሀገራት የፖሊሲ ልዩነት ላይ ተመስርተው የሚሰጡት ትንታኔ በውል ማጤን
ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ የፖሊሲ ቅኝቱ ከርዕዮተ ዓለማዊ ክርክሩ ተዳምሮ ባለሀብቱ
በኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት የመሰማራት ውሳኔው ተፅዕኖ ያሳርፍበታል፡፡ በሌላ
መልኩ የንብረት ዋስትና፤ መንግስት በፋይናንስ ገበያ፣ በመሰረተ ልማት፣ በመሬት፣
የምርቶች ደረጃዎች፣ የአከባቢ ተጽዕኖና ደረጃዎች፣ የንግድ ፖሊሲ፣ የፈጠራ ባለቤትነት
ጉዳይ፣ እና ሌሎች የሚከተላቸው አቅጣጫዎች የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲው አካል
በመሆናቸው ተነጥለው የሚታዩ አይደሉም (ጎ-ሺማዳ፣ እ.ኤ.አ 2013)፡፡

የመንግስት ጥንካሬ እና ፖሊሲው የማስፈጸም ቁርጠኝነት ሌላኛው የግሉ ዘርፍ ከግምት


የሚያስገባው ጉዳይ ነው፡፡ በተለይ የምስራቅ ኤስያ ሀገራት ተመሳሳይ ፖሊሲ ከሚከተሉ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 49


ሌሎች በተመሳሳይ የኢኮኖሚ እድገት ይገኙ የነበሩ ሀገራት በኢንዱስትሪ ልማቱ
ፈጥነው ስኬት ማስመዝገባቸው የመንግስት ጥንካሬ ትኩረት እየሳበ መምጣቱ በርካታ
በዘርፉ ምርምር ያካሄዱ (አምስደን፣ እ.ኤ.አ 2001፤ ጉይሌረሞ፣ እ.ኤ.አ 2006፤ ጆን፣
እ.ኤ.አ 2005 ወዘተ) ያስረዳሉ፡፡ በተለይ የመንግስት ሕጎች ግልጽነትና የመንግስት
መዋቅር ፖሊሲው ለማስፈጸም የሚያሳየው ቆራጥነት ብሎም የሚያስመዘግበው ፋይዳ
ከፍተኛ ትኩረት ይሰጠዋል፡፡

የሀገሪቱ አጠቃላይ የመሰረተ ልማት ደረጃ በኢንዱስትሪ ልማቱ ቁልፍ ሚና ይወጣል፡፡


በወሳኝ መሰረተ ልማት የሚደረግ ኢንቨስትመንት ለባለሀብቱ ትኩረት ይሰጠዋል፡፡
በፊዚካል እና ማሕበራዊ መሰረተ ልማት የሚውል መዋዕለ ንዋይ የኢንዱስትሪው
ተወዳዳሪነትና ትርፋማነት በቀጥታ ይወስናል፡፡ ለዚም ነው በርካታ ጥናቶች የአፍሪካ
የኢንዱስትሪ ስኬት ማነስ ከመሰረተ ልማት የሚያገናኙት፡፡ ለምሳሌ ግዋንግዝህ፣
ሚካኤልና ሚንግሁዋይ (እ.ኤ.አ 2015) ኢትዮጵያ በእንዲህ ዓይነት በቂ የመሰረተ
ልማት ሽፋን፣ ብቁ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ፣ በቂ ክህሎትና ዕውቀት የተላበሰ የሰው
ኃይል ባለመኖሩ ለኢንቨስትመንት ያላት ተመራጭነት እየተፈታተነው መሆኑን
ይገልፃሉ፡፡ የዓለም ባንክ በየዓመቱ የሚያወጣው ሪፖርትም የአፍሪካ ሀገራት ከሌሎች
ሀገራት ጋር ሲነፃፀር በመሰረተ ልማት ምክንያት ለኢንቨስትመንት ተመራጭነታቸው
ጠንካራ እንዳልሆነ ያስገነዝባል (የዓለም ባንክ፣ እ.ኤ.አ 2004፣ 2005፣ 2006)፡፡

በገበያ ቀጣይ ተወዳዳሪና ትርፋማ ለመሆን የማምረቻ ወጪዎች በተለይ በኩባንያ ደረጃ
ትኩረት የሚሰጠው ይሆናል፡፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብት ብቻ ሳይሆን የውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት ትርፉማነቱና ቀጣይነቱ ለማረጋገጥ የማምረቻ ወጪዎች ላይ ከፍተኛ
ጥናት ያካሄዳል፡፡ አብዛኞቹ ወደ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ እየመጡ ያሉት አምራች
ኩባንያዎች ትልቁ ምክንያታቸው ተነፃፃሪ ዝቅተኛ የጉልበት ዋጋ እና መሬት
መሆናቸውን ጥናቶች ያሳያሉ (የኮሪያ ዓለማቀፍ ትብብር ኤጀንሲ እ.ኤ.አ 2013)።

ከላይ የተቀመጡ ገዥ ቅድመ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው የግሉ ዘርፍ የመማር


ሂደትም ለኢንቨስትመንት ውሳኔው እጅግ ወሳኝ መሆኑ በህንድ የግሉ ዘርፍ ተሞክሮ
በመጥቀስ ጎ-ሺማዳ (እ.ኤ.አ 2005) ያብራራል፡፡ ለባለሀብቱ መሰጠት የሚገባቸው
ስልጠናዎች ስትራተጂያዊ የቢዝነስ አመራር (ለኩባንያ ባለቤቶችና ከፍተኛ የስራ
አመራር አካላት)፣ ከምርት ንድፍ ዝግጅት እስከ ጥራት ቁጥጥር የሚደርስ ምርት ስራ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 50


አመራር፣ መሰረታዊ የንግድ/ ቢዝነስ ዕውቀት/ (ለሁሉም አነስተኛ አንቀሳቃሾች) እና
የቴክኖሎጂ ዓቅም ግንባታ እንደሆኑ ያስረዳል፡፡

የተዛማጅ ጥናቶች ዳሰሳ ማጠቃለያ

ልማታዊ መንግስታትም ይሁኑ ሊበራል አስተሳሰብ የሚያራምዱ መንግስታት የግሉ


ዘርፍ ኢንቨስትመንት የኢኮኖሚ ዋና ሞተር መሆኑን ይስማማሉ፡፡ ልዩነታቸው
መንግስት የገበያ ክፍተት ለመሙላት ሊኖረው በሚገባ ሚና ላይ ነው፡፡ የልዩነቱ
መንስኤም አንደኛው ከዓለም አቀፍ ግንኙነቱ አኳያ ሲታይ ሊበራል አስተሳሰብ
የሚያራምዱ ሀገራት በእነሱና በታዳጊ ሀገራት ያለው ነባራዊ የዕድገት ደረጃ ከግምት
ካለማስገባት የመነጨ ሲሆን ሁለተኛው ሊበራል አስተሳሰብ አራማጆች በፍትሀዊ ልማት
ላይ ያላቸው ዕይታ ደካማ መሆኑ ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ ልማታዊ መንግስታት የግሉ
ዘርፍ በኢንዱስትሪ ልማት ስምሪቱ በፖሊሲያቸው በተገቢ ሁኔታ በመምራት የበለፀጉ
ሀገራት ያላሳዩት ፈጣን ስኬት አስመዝግበዋል፡፡

ሁለተኛው ጉዳይ የኢንዱስትሪ ልማት ዘላቂ ስኬት የሚኖረው በዋናነት በሀገር ውስጥ
ባለሀብት ግንባር ቀደም ተዋናይነት ነው፡፡ የውጭ ባለሀብት በአስተናጋጅ ሀገራት
የኢንዱስትሪ ልማቱ የራሱ ሚና ቢኖረውም የሀገር ውስጥ ባለሀብት ሚናን መተካት
አይችልም፡፡ ይህ ከሆነ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን
በተለያየ መልክ ከገበያ እንዳያስወጣ በጥንቃቄ መመራት ያስፈልገዋል፡፡ የውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት ዘላንነት ባህሪ እንደተጠበቀ ሆኖ ፍሰቱ በራሱ ሲታይም አብዛኛው
የአገልግሎት ዘርፍ በመሆኑ አገራት የአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ፍላጎታቸው
በቀጣይ በአገር ውስጥ ባለሀብት የተመሰረተ እንደሚሆን ዓለማቀፍ የኢንቨስትመንት
ፍሰት መረጃ ያመለክታል፡፡

ሶስተኛው ማጠቃለያ ለውጭ ገበያ የሚያመርት ኢንዱስትሪ ወይም ገቢ ምርቶች


የሚተካ የሚያመርት ኢንዱስትሪ ቅድሚያ የመስጠት ጉዳይ በአንድ በኩል የአገር
ውስጥ የገበያ ስፋት መታየት ይኖርበታል፡፡ ከስኬት አኳያ ሲታይ ግን አብዛኞቹ
ሀገራት ገቢ ምርቶች የሚተኩ ኢንዱስትሪዎች በማልማት የተሻለ ዕውቀትና ዓቅም
መፍጠር እንደቻሉና ለውጭ ገበያ የሚያመርት ኢንዱስትሪ መሰረቱ ገቢ ምርቶች
የሚተካ ኢንዱስትሪው ላይ የሰሩት ስራ መሆኑ ይታያል፡፡ በዚህ በኩል በብዙ መልኩ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 51


አሳማኝ ሆኖ የተገኘው መረጃ በየትም ይጀመር የኢንዱስትሪ ልማት ጉዞው ስኬታማ
የሚሆነው የተጀመረው ዘርፍ በጥንካሬ በመምራት ዳር ማድረስ ላይ የመንግስት
የፖሊሲ የማስፈጸም ዓቅም እጅግ ወሳኝ መሆኑ ነው፡፡

በመጨረሻም መንግስት በፖሊሲ ዕቅድና ፖሊሲ ማስፈጸም ላይ በማተኮር በሚያደርገው


የመማር ሂደት የማስፈጸም ዓቅሙ ስለሚያጠናክርለት የግሉ ዘርፍ በመንግስት
የሚኖረው እምነት እንዲጨምር እና በኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት በስፋት እንዲሰማራ
ለመወሰን ዋስትና ይሰጠዋል፡፡ መንግስት ፖሊሲዎቹ ለግሉ ዘርፍ ተደራሽ በማድረግ
እንዲሁም የግሉ ዘርፍ የመማር ሂደት በማቀናጀትና በማፋጠን ተመሳሳይ ውጤት
ያስገኛሉ፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 52


ክፍል III
የጥናቱ ትንተና እና ግኝቶች

ምዕራፍ 4
የአምራች ኢንዱስትሪው ጥቅል ገፅታ

ሀገራችን ግብርና መር የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ (Agricultural Development


Led Industrialization) ትከተላለች፡፡ የግብርናው አቅም የሀገራችን ሁለንተናዊ የምጣኔ
ሀብት ዕድገት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑ የታመነበት እና ላለፉት ሁለት
አስርት አመታት ውጤታማ የሆነ ዘርፍ ነው፡፡ በመሆኑም ግብርናው ለኢንዱስትሪው
ልማት ቢያንስ አራት ዋና ዋና አስተዋፅኦ አለው፡፡ አንደኛው ኢንዱስትሪው ለምርት
የሚያስፈልገውን ግብአት በተለይ ለአግሮፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ፣ ጨርቃ ጨርቅ፣
ቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ እና ለመሳሰሉት ዘርፎች ለማቅረብ ነው፡፡ ሁለተኛው ግብርናው
ለኢንዱስትሪ የመጀመሪያ ካፒታል ክምችት ይፈጥራል፡፡ ሶስተኛው የውጭ ምንዛሬ
ለማግኘት ይረዳል፡፡ የመጨረሻው ደግሞ ግብርናው ለአምራች ኢንዱስትሪ ሰፊ ገበያ
የሚፈጥር መሆኑ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማቱ ዋና ተዋናይ የግሉ ባለሀብት መሆኑ በሀገራችን የኢንዱስትሪ


ልማት ስትራቴጂ በግልፅ የተቀመጠ ጉዳይ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ
ልማት ፖሊሲን እውን ለማድረግ አምስት ዋና ዋና አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡
አንደኛው አቅጣጫ የተቀናጀና ጠንካራ የመንግስት አመራር ሚና እንዲኖር ማድረግ
ነው፡፡ መንግስት እንደ መርህ በኢኮኖሚ ኢንቨስትመንት በስፋት የመሳተፍ ዓላማ
አይኖረውም፡፡ የመንግስት ሚና ኢንዱስትሪውን አቀናጅቶ መምራት እና የገበያ
ጉድለት ማስተካከል ነው፡፡ ኢንዱስትሪውን በፍጥነት ለማሳደግ የዘርፉ ማነቆዎችን
በጥናት መፍታት፣ ዘርፉን ሊመራ የሚችል የተሟላና ጠንካራ መዋቅር መፍጠር፣
ኢንዱስትሪው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን የገበያና ሌሎች መረጃዎችን
በማቅረብ ድጋፍ መስጠት፣ የአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋና ግልፅ እንዲሆን ማድረግ፣
ኢንዱስትሪው የጐንዮሽና በምርት ሰንሰለቱ ግንኙነት (Vertical & Horizontal Linkage)
እንዲጠናከር ማድረግ፣ እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ በተለይ የሀገር ውስጥ የግል
ኢንቨስትመንት ጠንካራና ተወዳዳሪ የሚያደርጉ የመሰረተ ልማትና መሬት አቅርቦት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 53


ትኩረት የተሰጣቸው አጀንዳዎች ናቸው፡፡ ሁለተኛው አቅጣጫ ኢንዱስትሪው ጉልበትን
በሰፊው የሚጠቀም፣ በአንፃሩ ካፒታልን የሚቀንሱ ዘርፎች ላይ ማተኮር ነው፡፡ ሶስተኛ
አቅጣጫ ኢንዱስትሪው በውጭ ገበያ እንዲመራ ማድረግ ነው፡፡ አራተኛው ደግሞ
የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቱን አቀናጅቶ የመጠቀም አቅጣጫ መከተል ነው፡፡
አምስተኛው አቅጣጫ መላው ህብረተሰብ ለኢንዱስትሪ ልማት በጋራ የሚሳተፍበትን
ስልት መከተል ነው፡፡

4.1 አምራች ኢንዱስትሪ እና ሀገራዊ የምጣኔ ሀብት ዕድገት

የሀገራችን አጠቃላይ ምጣኔ ሀብት በ1999 ዓ.ም ከነበረበት 313.9 ቢሊዮን ብር በ2006
በጀት ዓመት ወደ 630.8 ቢሊዮን ብር ከፍ ብሏል (ብሔራዊ ባንክ 2006 ዓ.ም)፡፡
ባለፉት 10 ዓመታት የግብርናው ምጣኔ ከብር 158.5 ቢሊዮን ወደ ብር 251.8 ቢሊዮን፣
የኢንዲስትሪ ምጣኔ ከብር 32.1 ቢሊዮን ወደ ብር 89.6 ቢሊዮን፣ የአገልግሎት ዘርፉም
ከብር 123.3 ቢሊዮን ወደ ብር 289.4 ቢሊዮን አድጓል፡፡

ግራፍ 4.1 የኢንዱስትሪ አንፃራዊ ዕድገት 1999-2007 ዓ.ም


(ምንጭ፡ ብሔራዊ ባንክ 2007 ሪፖርት)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 54


የሶስቱም (ግብርና፣ ኢንዱስትሪና አገልግሎት) ተነፃፃሪ ዘርፎች ዕድገት ስንመለከት
ከ1999 ዓ.ም በኋላ ኢንዱስትሪና አገልግሎት ከግብርናው በላይ ዕድገት
አስመዝግበዋል፡፡ እስከ 2003 ዓ.ም የአገልግሎቱ ዕድገት ከኢንዱስትሪው ዕድገት በጣም
የፈጠነ ሆኖ ይታያል፡፡ ከ2004-2007 ባሉት ዓመታት ግን የኢንዱስትሪው ዕድገት
ፈጣን መሆኑን ያመለክታል፡፡

የኢንዱስትሪ ፈጣን ውስጣዊ ዕድገት ላለፉት ስምንት ዓመታት የቀጠለ ሲሆን


ከአጠቃላይ ሀገራዊ የምጣኔ ሀብት ዕድገት (GDP growth) ያለው አስተዋፅኦም ከጊዜ ወደ
ጊዜ የተሻለ ለውጥ አሳይቷል፡፡ ነገር ግን የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ አስተዋፅኦ
በተቀመጠው ግብና እንዲሁም በሚፈለገው ደረጃ አለመድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡

ግራፍ 4.2 ኢንዱስትሪው ለሀገራዊ ምጣኔ ሀብት ዕድገት ያበረከተው አስተዋፅኦ1999-2008ዓ.ም


(ምንጭ፡ ብሔራዊ ባንክ 2008 ሪፖርት)

ኢንዱስትሪው በ1999 ዓ.ም ለአጠቃላይ የምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት ያበረከተው አስተዋፅኦ


8.5% ሲሆን ለሀገራዊ ምጣኔ ሀብት (GDP) ያለው ድርሻ ደግሞ 10.2% ነበር፡፡ ከዚህ
ጊዜ ጀምሮ እስከ 2003 ዓ.ም ድረስ በጥቂቱም ቢሆን አስተዋፅኦው በተከታታይ
እየጨመረ መሆኑን ያሳያል፡፡ ከ2003-2008 ዓ.ም ደግሞ አስተዋፅኦው ከበፊቱ በተሻለ
ፍጥነት የጨመረ ሲሆን ለGDP ያለው ድርሻም በ2008 ዓ.ም 38.8% መሆኑን
ያመለክታል፡፡ ለኢንዱስትሪው ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ያለው

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 55


የኮንስትራክሽን ንዑስ-ዘርፍ ነው፡፡ ውጤቱ የሚያመላክተው የአምራች ኢንዱስትሪው
ዕድገት ከዚህ በላይ መፍጠን እንዳለበት ነው፡፡

4.2 የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ስብጥር እና አስተዋፅኦ

በሀገራችን ከ1996 ዓ.ም በኋላ ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ዕቅድና


ኘሮግራሞች እንዲሁም የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ መዘጋጀት ጋር ተያይዞ
ዕይታው እየሰፋ በመሄድ በአሁኑ ሰዓት አምራች ኢንዱስትሪ የሚለው ትርጉም
በከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የሚቋቋም ብቻ ሳይሆን በግለሰብ እና ቤተሰብ ደረጃ በቀላል
ቴክኖሎጂ እና ዝቅተኛ ካፒታል የሚሰራ እንዲሁም በምርት ሂደት እሴት የሚጨምር
ሁሉ በአምራች ዘርፍ የሚካተት ነው፡፡ በሀገራችን በ2006 ዓ.ም በአጠቃላይ 2758
መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ነበሩ (CSA, 2006)፡፡

ግራፍ 4.3 የመካከለኛና ትላልቅ አምራች ኢንዱስትሪዎች የዘርፍ ስብጥር


(ምንጭ፡ ማዕከላዊ ስታትስቲክስ አጀንሲ 2ዐዐ6 ዓ.ም)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 56


የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ በግራፍ 4.3 እንደሚያሳየው ከአምራች
ኢንዱስትሪዎች መካከል በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ከፍተኛውን ድርሻ
(27 %) የያዙ ሲሆን ብረት ያልሆኑ የማዕድን ውጤቶችን የሚያመርቱ ደግሞ ተከታዩን
(24%) ድርሻ ይዘዋል፡፡ የእሴት ጭማሪ (Value added) ስንመለከት የምግብና መጠጥ
ኢንዱስትሪዎች 37.9% በመያዝ ከፍተኛውን ድርሻ ሲያበረክት ከዚህ በመቀጠል
18.7% ብረት ያልሆኑ የማዕድን ውጤቶች ኢንዱስትሪ፣ 9% ኬሚካልና የኬሚካል
ውጤቶች ኢንዱስትሪ፣ 7.72% የጎማና ፕላስቲክ ውጤቶች ኢንዱስትሪ፣ 7.53% ደግሞ
ቆዳና የቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ አበርክተዋል፡፡ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ 0.33%
የዕሴት ጭማሪ በማበርከት ዝቅተኛውን ድርሻ ይዟል፡፡

የኢንዱስትሪው ዘርፍ ከድህነት ቅነሳና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ጊዜ ጀምሮ በታቀደለት ልክ


ባይሆንም ቀጣይነት ያለው ዓመታዊ ዕድገት እያስመዘገበ ይገኛል፡፡ የኢንዱስትሪ ዘርፉ
በድምር (ኮንስትራክሽን፣ አምራችና ሌሎች) በ1999 ዓ.ም ለሀገራዊ ምጣኔ ሀብት
ያበረከተው አስተዋፅኦ 8.5% የነበረ ሲሆን በ2008 ዓ.ም ወደ 38.8% አድጓል፡፡ በ1999
ዓ.ም ከጥቅል የሀገር ውስጥ ምርት (Share in GDP) የነበረው ድርሻ 14% ሲሆን
በ2008 ዓ.ም ወደ 16.7% አድጓል፡፡ ነገር ግን የአምራች ኢንዱስትሪ የዕድገት ፍጥነት
በታቀደው ልክ አለመሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለምሳሌ በ2ዐዐ2 ዓ.ም የዘርፉ ዓመታዊ
ዕድገት ከነበረበት 1ዐ.6% በ2ዐዐ7 ዓ.ም ወደ 2ዐ.1% ለማድረስ ታቅዶ ቢሰራም በ2ዐዐ6
ዓ.ም የተመዘገበ ዓመታዊ ዕድገት 18% ነው (ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ 2007)፡፡

ግራፍ 4.4 የኢንዱስትሪ ንዑስ ዘርፎች ተነፃፃሪ ድርሻ (2004 - 2006 ዓ.ም)
(የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 2006 ዓ.ም ሪፖርት)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 57


አምራች ንዑስ ዘርፉን ለይተን ስንመለከት ከኮንስትራክሽንና የኃይል ልማት ያነሰ ሚና
እየተጫወተ ይገኛል፡፡ ይህ ንዑስ ዘርፍ በ1998 ዓ.ም ለጥቅል ሀገራዊ ምርቱ 5.5%
ያህል ያበረከተ ሲሆን በ2ዐዐ2 ዓ.ም ድርሻው ወደ 5.3፣ በ2ዐዐ3 ዓ.ም ወደ 4.9 እና
በ2007 ዓ.ም ደግሞ ወደ 4.6 ወርዷል፡፡ የኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፉ ከአምራች
ኢንዱስትሪ ዘርፍ በላይ ከፍተኛ ዕድገት አስመዝግቧል፡፡ ለምሳሌ የኮንስትራክሽን ንዑስ
ዘርፉ በ2ዐዐ4 ከነበረበት 42.1% ድርሻ በ2ዐዐ6 ወደ 53.1% (31.5-38.7% ዓመታዊ
ዕድገት) ከፍ ሲል የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ግን ድርሻው ከ24% ወደ 22.7%
(13.5-24.2% ዓመታዊ ዕድገት) ወርዷል።

የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ከ2003-2006 በጀት ዓመታት የታየ የውጭ ምንዛሬ


ግኝትም ከዕቅዱ ጋር ሲታይ ዝቅተኛ ነው፡፡ የውጭ ምንዛሬ ግኝቱ በመነሻ ዘመኑ
ከነበረበት 183.7 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወደ 1.82 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ጥረት
ቢደረግም የተከናወነው ግን የዕቅዱን 21.9% (398 ሚሊዮን ዶላር) ያህሉ ብቻ ነው፡፡
ባለፉት አራት አመታት ጨርቃ ጨርቅ ዘርፉ ከዕቅዱ 15%፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች
ዘርፍ የዕቅዱ 27%፣ የምግብ፣ መጠጥና ፋርማሲዩቲካል ዘርፎች የቅዱ 21.3% ያህል
ብቻ አከናውነዋል (ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ 2007)።

የአምራች ዘርፉ በጥቅል ሀገራዊ ምርትና በውጭ ምንዛሬ ግኝት አስተዋፅኦ ዝቅተኛነት
በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ይገለፃል፡፡ አንደኛው ምክንያት አምራች ኢንዱስትሪዎች
ማምረት ከሚችሉት ዓቅም በታች ማምረታቸው ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት በአምራች
ኢንዱስትሪ የሚሰማራ የኢንቨስትመንት መጠን ሰፊና ጠንካራ አለመሆኑ ነው፡፡
አብዛኛው የግል ባለሀብት የኢንቨስትመንት ምርጫው የአገልግሎት ዘርፍ ሆኖ
ቀጥሏል፡፡ የአምራች ዘርፉን ለማጐልበት በመንግስት በኩል ዘርፈ ብዙ ጥረቶች
ቢደረጉም፤ ዘርፉ የተጠበቀውን ያህል ውጤት አላስመዘገበም፡፡ ባለሀብቱ በአምራች
ዘርፍ በስፋት ያልተሳተፈበት ምክንያቶች በዚህ ጥናት ውስጥ ተዳሰዋል። በአምራች
ኢንዱስትሪው ለመሰማራት የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰደው ባለሀብት ቁጥሩ ቀላል
ባይባልም ወደ ማምረት የሚገባው ቁጥር ግን እጅግ ዝቅተኛ ነው።

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 58


4.3 የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ያለው የኢንቨስትመንት
ተሳትፎ

በሀገራችን በ1983 ዓ.ም የፖለቲካ ለውጥ ተከትሎ የምጣኔ ሀብት መዋቅሩ በለውጥ
ሂደት ላይ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ በተለይ የኢንዱስትሪው ዘርፍ ዋነኛ ተዋናይና የንብረት
ባለቤትነት የተረጋገጠለት እና የሀብት መጠን ገደብ ያልተደረገለት በዋናነት የሀገር
ውስጥ የግል ባለሀብት መሆኑ በሀገራችን የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ በግልፅ
ተቀምጧል፡፡ ይህንን ተከትሎ የግሉ ኢንቨስትመንት እያደገ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ
ኢንቨስትመንት ኮሚሽን መረጃ እንደሚያሳየው ከ1984 እስከ 2009 ሩብ በጀት ዓመት
ድረስ 78,348 የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት፣ 5,446 የውጭ ቀጥታ ኢንቨስተሮች እና
212 የመንግስት የልማት ድርጅቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደዋል፡፡ በእነዚህ
ዓመታት በድምሩ 65,202,455,000 ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 7,416 (9.46%) የሀገር
ውስጥ ባለሀብቶች፣ 93,616,526,000 ብር ያስመዘገቡ 2,549 (46.8%) የውጭ ሀገር
ባለሀብቶች እና 18,529,643,000 ብር ያስመዘገቡ 36 (16.98%) የመንግስት የልማት
ድርጅቶች ወደ ምርትና አገልግሎት የተሸጋገሩ ቢሆንም የሀገር ውስጥ ባለሀብት
ተሳትፎ አጥጋቢ እንዳልሆነ ያመለክታል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትም ተመሳሳይ ስርጭት አለው፡፡ ከ1984-2ዐዐ9


ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ በጀት ዓመት ድረስ 20,860 ፕሮጀክቶች በአምራች ዘርፍ
ለመሠማራት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደዋል፡፡ ከነዚህ ፕሮጀክቶች ውስጥ 83.98%
(17,519) የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ሲሆኑ 11.67% (2435) የውጭ ባለሀብቶች፣ 3.6%
(751) ጆይንት ቬንቸር እንዲሁም የተቀሩት 0.4% (83 ፕሮጀክቶች) የመንግስት
የልማት ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡

ባለፋት 25 ዓመታት በአምራች ኢንዱስትሪ ለመሰማራት ፈቃድ ከወሰዱ 17,591


የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ቢኖሩም በተግባር ወደ ማምረት የገቡት ግን 1837 (10.44%)
ብቻ ናቸው፡፡ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ስንመለከት ፈቃድ ከወሰዱት 2435
ባለሀብቶች 1129 (46.37%) ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል፡፡ በአምራች ኢንዱስትሪ
ለመሰማራት ፈቃድ ከወሰዱ 751 ጆይንት ቬንቸር ባለሀብቶች መካከል 353 (88.7%)
ፕሮጀክቶች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 59


ሰንጠረዥ 4.1 በአምራች ኢንዱስትሪ ወደ ማምረት የተሸጋገሩት(1984-2009 ዓ.ም ሩብ አመት)

ተ.ቁ የኢንቨስትመንት አይነት ወደ ማምረት የተሸጋገሩ ወደ ማምረት ያልተሸጋገሩ ጠቅላላ


(Types of Investment) (Operational stage) (Pre-operational stage) ድምር
1 የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት 1837 15,754 17,591
(Domestic Private Investors)
2 (የውጪ ባለሀብት) 1129 1306 2435
Foreign Investors
3 (ጆይንት ቬንቸር) 353 398 751
Joint Venture
4 (የመንግስት ኢንቨስትመንት) 22 61 83
Public Investment

ጠቅላላ ድምር 3341 17,519 20,860

የመረጃ ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን 2009 ዓ.ም

የሀገር ውስጥ ባለሀብትም ሆነ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቱ ወደ ምርት ለመሸጋገር


እጅግ ረጅም ጊዜ እንደሚወስድባቸው ከዚህ መረጃ ለመረዳት ይቻላል፡፡የሀገር ውስጥ
ባለሀብቱ ለየት የሚያደርገው በየዓመቱ እየተሰጠ ካለው የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሲታይ
ወደ ምርት እየተሸጋገረ ያለው ቁጥሩ በጣም ዝቅተኛ መሆኑ ነው፡፡

4.4 ፋብሪካዎች ከዓቅም በታች ማምረት (Under Capacity Utilization)

በዚህ ጥናት ውስጥ በናሙናነት ተወስደው የተዳሰሱት 88 አምራች ኢንዱስትሪዎች


ሲሆኑ በስድስት ዋና ዋና የሀገራችን ከተሞች የሚገኙ ናቸው፡፡ ስርጭታቸውን
ስንመለከት ከመቀሌ ከተማ 11፣ ከባህርዳር 1ዐ ፣ ከድሬዳዋ 12፣ ከሀዋሳ 12፣ ከአዳማ
13 እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማ 30 ኢንዱስትሪዎች ናቸው፡፡ እነዚህ አምራች
ኢንዱስትሪዎች ለዚህ ጥናት በናሙናነት ሲመረጡ አገልግሎታቸው፣ የምርት
አይነታቸው፣ የገበያ ትኩረታቸው እና የመሳሰሉት ግምት ውስጥ ገብቶ ንዑስ ዘርፉን
እንዲወክሉ ተደርጎ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 60


በጥናቱ ናሙና ከተካተቱት 88 ፋብሪካዎች የማምረት አቅማቸው ምን ያህል (Capacity
utilization) እንደሆነ ተጠይቀው ለጥያቄው መልስ የሰጡት 71 ፋብሪካዎች ናቸው፡፡
በዚህ መሰረት ዝቅተኛው የማምረት አቅም ሪፖርት 12% ሲሆን ከፍተኛው ደግሞ
1ዐዐ% ነው፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ ፋብሪካዎች ማምረት ከሚችሉት ዓቅማቸው ከ4ዐ-
6ዐ% ብቻ እያመረቱ ይገኛሉ፡፡ ከአጠቃላይ የማምረት ዓቅማቸው ከ75 በመቶ በላይ
የሚያመርቱ 22.5 በመቶ ፋብሪካዎች ሲሆኑ በድምሩ የ71 ፋብሪካዎች በአማካይ
የማምረት አቅም 58.14% ነው፡፡

ግራፍ 4.5 የፋብሪካዎች የማምረት ዓቅም አጠቃቀም በፐርሰንት


ምንጭ፡ የመስክ ዳሰሳ፣ 2007 ዓ.ም

የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች በቃለ-መጠይቅ እና በተሰጣቸው የጽሑፍ መጠይቅ


እንደገለፁት በሙሉ አቅም ያለማምረት ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ ሳይሆን
እየተባባሰ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ዝቅተኛው የማምረት አቅም የታየው በቆዳና ቆዳ
ውጤት ፋብሪካዎች ሲሆን ከፍተኛ የማምረት ዓቅም ያስመዘገቡት ደግሞ የመጠጥ
ፋብሪካዎች ናቸው፡፡ እንደ ቢራ፣ ለስላሳ፣ እና የታሸገ ውሃ የመሳሰሉ ጥቂት አምራች
ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅማቸው ከ85 በመቶ በላይ የሚያሳይ ቢሆንም የአብዛኛው
አምራች ኢንዱስትሪ የማምረት አቅም ግን በአማካይ 58% ብቻ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 61


ለመሆኑ በዚህ ጥናት በናሙናነት የተወሰዱ አምራች ኢንዱስትሪዎች ከዓቅም በታች
ለማምረት ያስገደዷቸው ችግሮችና ማነቆዎች ምንድናቸው? በአምራች ኢንዱስትሪ
የተሰማሩ ባለሀብቶች ከአቅም በታች እንዲያመርቱ ያስገደዷቸው ችግሮችና
ማነቆዎች፡1) የኤሌክትሪክ ሀይል ማነስና መቆራረጥ፣ 2) የኢንዱስትሪ ግብአት ችግር
(የአቅርቦት ማነስ፣ ከፍተኛ ዋጋ፣ ዝቅተኛ ጥራት) ፣ 3) የውጭ ምንዛሬ ዕጥረት፣ 4)
የፋይናንስና ብድር አቅርቦት ማነስ (በተለይ ለስራ ማስኬጃ)፣ 5) የገበያ ችግር፣ 6)
የሰራተኛ ብቃት ማነስና በገበያ ላይ ብቃት ያለው የሰው ሀይል አለማግኘት እንዲሁም
7) የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ባለሀብቱ በራሱ
በሚፈጥራቸው ችግሮች (ለምሳሌ ብቃት ያለውን የሰው ሀይል በተገቢው ቦታ
አለመመደብ ወይም አለመጠቀም፣ አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን አለመተግበር
ወይም አለመጠቀም፣ ወዘተ እንደምክንያት ይጠቀሳሉ፡፡

ግራፍ 4.6 ፋብሪካዎች ከዓቅም በታች የሚያመርቱበት ምክንያቶች


ምንጭ፡ የመስክ ዳሰሳ፣ 2007 ዓ.ም

ዘላቂ ችግር ባይሆንም የኤሌክትሪክ ሀይል ማነስና መቆራረጥ አሁንም ለአምራች


ኢንዱስትሪው በሙሉ አቅም ላለማምረት የመጀመሪያው ዋና ችግር ሆኖ ይገኛል፡፡
ሌላው በዋጋና በጥራት ተወዳዳሪ ግብአት በበቂ ሁኔታና በቀጣይነት ያለማግኘት ችግር
ነው፡፡ ይህ ችግር በተለይ በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ፣ ቆዳና ቆዳ
ውጤቶች ኢንዱስትሪ እና የምግብና የመጠጥ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ የግብአት
ዕጥረት ይታያል፡፡ ሶስተኛው ችግር በተለይ ግብአት ከውጭ ሀገር ለሚያስመጡ
ኢንዱስትሪዎች የውጭ ምንዛሬ ዕጥረት ነው፡፡ ሌላው ማነቆ ለማስፋፊያ ፕሮጀክትና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 62


ለስራ ማስኬጃ የተጠየቀውን ያህል ብድር በፍጥነት ያለማግኘት ችግር ነው፡፡ በሌላ
በኩል ኢንዱስትሪን የመምራት ብቃት ማነስ እንዲሁም ለተመረተው ምርት ገበያ
ማጣት አምራች ኢንዱስትሪው በሙሉ አቅሙ እንዳይንቀሳቀስ ያላቸው ተፅዕኖ ቀላል
የሚባል አይደለም፡፡ የሰራተኛ ብቃት ማነስና በገበያ ላይ ብቃት ያለው የሰው ሀይል
አለማግኘት እንዲሁም በባለሀብቱ በኩልም በቂ ሰራተኛ አፈላልጎ ያለመቅጠር ችግርም
ተስተውሏል፡፡ ዋና ዋና የመንግስት አገልግሎቶች ተደራሽነትና ቅልጥፍና መጓደልም
ተጨማሪ ችግሮች ናቸው፡፡

4.5 የጥንካሬ፣ ድክመት፣ አጋጣሚና ተግዳሮቶች ትንተና

መንግስት በሀገራችን በተለይ ላለፉት አስር አመታት ለአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት


ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየሰራ ቢገኝም፤ የኢንዱስትሪው ዕድገት አንቀሳቃሽ
ሞተር የሆነው የግሉ ባለሀብት በተለይ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች
ኢንዱስትሪው ልማት ላይ ያለው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ አናሳ እንዲሆን ያደረጉ
በርካታ ውጫዊና ውስጣዊ ምክንያቶች እንዳሉት ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን ወሳኝነት
ያላቸውንና ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ችግሮችን በመለየት አሁን በአምራች
ኢንዱስትሪው ለተሰማራውና ለወደፊት ወደ ዘርፍ ለሚቀላቀለው የግል ባለሀብት
በሚያግዝ መልኩ ስትራቴጅክ ጉዳዮችን ማመላከት ያስፈልጋል፡፡ የጥንካሬ፣ ድክመት፣
መልካም አጋጣሚና ተግዳሮቶችን የመተንተኛ (SLOC Analysis) ዘዴ የአምራች
ኢንዱስትሪውን ውስጣዊ ሁኔታ (internal environment) እንዲሁም የአምራች
ኢንዱስትሪውን ውጫዊ ሁኔታ (external environment) ለመገምገም የሚያስችል ነው፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪውን ውጫዊ ነባራዊ ሁኔታ ስንዳስስ ደግሞ ለኢንዱስትሪው ዘርፍ


ልማት መልካም አጋጣሚ (opportunity) እና ተግዳሮቶች (Challenges) የሚታዩ
ጉዳዮችን ማንሳት ተገቢ ነው፡፡በውጫዊ ነባራዊ ሁኔታ ትንታኔ ወቅት የሀገሪቱ ህግና
ደንብ፣ የመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጅ፣ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ሁኔታ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ
ጉዳዮች፣ ከአምራች ኢንዱስትሪው ውጭ ያሉ ዘርፎች እንደምታ እና አለማቀፍ ነባራዊ
ሁኔታን ያካትታል፡፡የመንግስት ተቋማትም ሁኔታዎቹን በመረዳት የፖሊሲ አቅጣጫ
እንዲያሻሽሉና እንዲቀይሱ ያስችላቸዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 63


ሰንጠረዥ 4.2 የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ጥንካሬ፣ ውስንነት፣ አጋጣሚና ተግዳሮቶች
ጥንካሬዎች (Strengths) መልካም አጋጣሚዎች (Opportunities)
 ልማታዊ ባለሀብትን ለማፍራት የሚጥር ዲሞክራሲያዊ የልማት
 ዘርፉ ከጊዜ ወደ ጊዜ በኢኮኖሚው ያለው ሚና መንግስት መኖሩ፤
እየጨመረ መጥቷል፤  ጠንካራ የመንግስት ቁርጠኝነት መኖሩ፣
 በአምራች ዘርፍ ተሰማርተው ሊሰሩ የሚችሉ  የፖለቲካና ማህበራዊ መረጋጋት (political and social
የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መኖራቸው stability) መኖሩ፤
 ከውጭ ከሚገቡ ሸቀጦች ጋር የመወዳደር  የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት መኖሩ፤
ዓቅም እያደገ መምጣቱ  መሰረታዊ የፖሊሲና ስትራቴጂ አቅጣጫዎች መኖራቸው፤
 በቁርጠኝነት የሚሰሩና አርአያ የሆኑ የሀገር  መንግስት የማበረታቻና ድጋፍ ማዕቀፎችን ማዘጋጀቱ፤
ውስጥ የግል ባለሀብቶች መኖራቸው፤  ሰፊና በርካሽ ዋጋ መስራት የሚችል የሰው ሀይል መኖሩ
 ንፅፅራዊ ብልጫ ባላቸው ምርቶች በውጭ ገበያ እንዲሁም ዝቅተኛ የሰራተኛ መነሻ ደሞወዝ (lower minimum
ተወዳዳሪ እየሆኑ መምጣት፤ wage rate)፤
 የሀገር ውስጥ ገበያው ገና ያልተነካ መሆኑ፤
 ሰፊ የኢንዱስትሪ ግብአት ለማቅረብ የሚያስችል አቅም መኖሩ
 ለሀገር ውስጥ ባለሀብት የተከለለ የስምሪት ዘርፎች መኖራቸው
 ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ልዩ የመሰረተ ልማት አቅርቦት
ለመፍጠር ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱ (መሬት፤ ኢንዱስትሪ
ፓርክ፤ ወዘተ) መኖሩ፣
 የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት እያደገ መምጣቱ በሽርክና
የመስራት እድል ይፈጠራል፤
 በአደጉት ሀገራት ውስጥ ከቀረጥ ነፃ የሆነ የገበያ እድል መኖሩ

ውስንነቶች (Limitations) ተግዳሮቶች (Challenges)


 ግልፅ፤ፍትሀዊና፤ቀልጣፍ አገልግሎት ችግር፤
 የምርታማነትና ጥራት ውስንነት፤  የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር፤
 ገበያን አጥንቶ ያለመስራትና በገበያ ሰንሰለት  የግብአት አቅርቦት ችግር
ላይ ቅንጅት አለመኖር፤  ፍትሀዊ የንግድ ስርአት ለማስፈን አስፈፃሚ ተቋማት
 የመንግስትን ፋይናንስ ድጋፍ ማበረታቻዎችን ቁርጠኝነት ማነስ፤
ለታለመለት አላማ አለማዋል፤  የውጭ ምንዛሬ፤ብድር አቅርቦት እጥረት፤
 የቴክኖሎጂ ፈጠራና የመቀበል አቅም  በቂና ፈጣን የመሬት አቅርቦት ፍላጎትን ማሟላት ያለመቻል፤
ውስንነት፤  ኋላቀር የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አሰራር፤
 ፋይናንስ ተቋማት አሰራር ግለፅነት አለመኖር፤  ሰፊና የተሟላ የመሰረተ ልማት አቅርቦት፤
 የአስፈፃሚና ፈፃሚ አካላት ብቃት ማነስ፤  የሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀም ልምድ አናሳ መሆኑ፤
 የባለሀብቱ የአቅም (አመራር፣ ዕውቀትና  ኢንዱስትሪው በሚፈልገው ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሀይል ማቅረብ
ክህሎት) ውስንነት፤ አለመቻል፤
 የግብርና ቀረጥ ማበረታቻ ፖሊሲዎች በቂ  የቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ ሽግግርና ልማት በሚፈለገው ደረጃ
አለመሆናቸው፤ አለመስፋፋት፤
 ሁለንተናዊ ገፅታው ውጤታማ የሆነ ቢሮክራሲ  የምርምርና ልማት ስርፀትን በሚፈለገው ደረጃ ያለማስፋፋት፤
ያለመኖር፤  በጥራት፣ በብዛትና በተመጣጣኝ ዋጋ የግብአት አቀርቦት
 ማበረታቻዎች ላይ የትግበራ ክፍተት መኖር ያለመኖር፤
 ጠንካራ የፋይናንስ ተቋማት አደረጃጀት  የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን በሚጎዳ አካሄድ፤ የገቢ ምርቶች
አለመኖር ገበያውን ማጥለቅለቅ፣
 ከአለማቀፍ ተቋማት ጋር በዋጋ፤ በጥራት፤ በቴክኖሎጅና
በአመራር ዕውቀት አለመመጣጠን፣
ምንጭ፡ የጥናት ቡድኑ ትንተና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 64


አምራች ኢንዱስትሪው የፈጠረው ጥንካሬ እና የተፈጠረለት መልካም አጋጣሚ አስቻይ
ሁኔታን (enablers) ይፈጥርለታል፡፡ በሌላ በኩል የአምራች ኢንዱስትሪው ድክመቶች
(Limitations) እና ተግዳሮቶች (challenges) ዘርፉ የሚጠበቅበትን ሚና እንዳይጫዎት
ወደኋላ ሊጎትቱት ይችላሉ፡፡ በመሆኑም መንግስትም ሆነ በአምራች ኢንዱስትሪው
የተሰማራው ባለሀብት አስቻይ ሁኔታዎችንና ተግዳሬቶች በማጤን ስትራቴጅካዊ
ጉዳዮች እና አቅጣጫዎች በትክክል እንዲለዩ ያግዛል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 65


ምዕራፍ 5
በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ዋና ዋና
ተግዳሮቶች

የኢትዮጵያን የረጅምና መካከለኛ ጊዜ የኢኮኖሚ ዕድገት ራዕይ ለማሳካት ጠንካራና


ተወዳዳሪ የሆነ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ መገንባት ወሳኝና አስፈላጊ ነው፡፡ ከዚህ
ጋር ተያይዞ የግሉ ሴክተር በተለይ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ለኢንዱስትሪው
ልማትና ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር ወይም ዋና ተዋናይ መሆኑ በሀገራችን የኢንዱስትሪ
ስትራቴጂ በግልፅ ተቀምጧል፡፡ በሚቀጥሉት አስር አመታት የዘርፉ የልማት
አቅጣጫዎች ግብርናን መሰረት ያደረጉና በግሉ ዘርፍ የሚመሩ፣ ኤክስፖርት መር
የሆኑና ጉልበትን በሰፊው የሚጠቀሙ ቀላል ኢንዱስትሪዎች ላይ ትኩረት የሚደረግ
ሲሆን ብረታብረትና ኬሚካል ለመሳሰሉ ኢንዱስትሪዎች ደግሞ መሰረት የሚጣልበት
ጊዜ ነው፡፡

የሀገሪቱን ምጣኔ-ሀብታዊ መዋቅር፣ ተነፃፃሪ ብልጫዎች፣የሀብት ስብጥር፣ አካባቢያዊ


አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የኢንዱስትሪ መዋቅር፣ የገበያ ሁኔታ፣ የቴክኖሎጂ ደረጃ፣ እና
የልማት ዕድሎች ዳሰሳ ላይ በመመስረት የኢንዱስትሪ የልማት አቅጣጫዎች
ተለይተዋል፡፡ የዘርፉ አስተዋፅኦም ለሀገሪቱ ጥቅል ዓመታዊ ምርት እና ለውጭ ምንዛሬ
ግኝት በየጊዜው ምን ያህል ማበርከት እንዳለበት ግብ ተቀምጦ ላለፉት አስር ዓመታት
ያህል ተሰርቶበታል፡፡ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴ ተሞክሮ እና የግል
ባለሀብቱን አጠቃላይ ዓቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት ለዘርፉ የተለያዩ
የኢንቨስትመንት ማዕቀፎችን በማዘጋጀት የተሻለ አስቻይ ሁኔታ እንዲፈጠር ጥረት
ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ ባለፉት አስር አመታት በተለይ የአምራች ኢንዱስትሪው
ዘርፍ የተፈለገውን ያህል የዕድገት ውጤት ያላስመዘገበ ሲሆን ለዚህ ዋናው ምክንያት
የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች በዘርፉ የተጠበቀውን ያህል ሰፊ ኢንቨስትመንት
አለማድረጋቸውና አብዛኛዎቹ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ ባለሀብቶችም ወደ
ማምረት ተግባር ባለመሸጋገራቸው ነው፡፡ በአጠቃላይ በአምራች ኢንዱስትሪው ውስጥ
የተስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮችና ማነቆዎች ስንመለከት 1) የኢንዱስትሪ አመራርና
አደረጃጀት 2) የማበረታቻና ድጋፍ አቅርቦት ችግር፣ 3) የፋይናንስና ብድር አቅርቦት
ችግር፣ 4) የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦት ችግር፣ እና የማስፈፀም ችግር፣ 5) የአምራች
ኢንዱስትሪ ምርቶች ገበያና የተሳለጠ የንግድ ስርአት አለመኖር፣ 6) የቴክኖሎጂ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 66


ሽግግርና ልማት አለመፋጠን፣ 7) በአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቱ በራሱ የተስተዋሉ
ችግሮችና ውስንነቶች፣ እና 8) ለአምራች ኢንዱስትሪ የመሬትና መሰረተ-ልማት በበቂ
ሁኔታ አለመቅረብ፣ በመሰረታዊነት ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው፡፡

5.1 የኢንዱስትሪ አመራርና አደረጃጀት

በሀገራችን የኢኮኖሚ ልማት ውስጥ የግሉ ሴክተር ጠንካራና ተወዳዳሪ ሆኖ የጎላ ድርሻ
እንዲኖረው እና የሞተርነት ሚናውን እንዲጫዎት የኢንዱስትሪ አመራሩ አቅምና
ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን ለመረዳት አያዳግትም፡፡ እስካሁን ያለው ልምድ የሚያሳየው
አመራሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በኢንዱስትሪ ልማቱ ላይ ከፍተኛ ሚና
እንዲጫዎት የሚያስችሉትን የኢንዱስትሪ ግብአቶች፣ የፋይናንስና ብድር፣ የውጭ
ምንዛሬ፣ ማበረታቻዎችና ድጋፎች፣ ብቃት ያለው የሰለጠነ የሰው ሀይል፣ የቴክኖሎጂ
ሽግግር፣ ምርምርና ስርፀት፣ ገበያና የተሳለጠ የንግድ ስርአት፣ መሬትና መሰረተ-ልማት፣
ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ፣ ወዘተ አቅርቦቶች በተሟላ ሁኔታ ከማቅረብ አኳያ
ክፍተቶች ታይተዋል፡፡ በአንደኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመን የኢንዱስትሪ
ልማቱን በተፈለገው ደረጃ ለማሳደግ የመንግስት የማስፈፀም አቅም ጠንካራ
አልነበረም፡፡ ጥቂት የማይባሉ የኢንዱስትሪ አመራሮችና እና ሌሎች የመንግስት
አስፈፃሚ አካላት የኢንዱስትሪ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በትክክልና በተሟላ
መልኩ ተረድቶ እንዲሁም ትኩረት ሰጥቶ ያለመተግበር ችግር ተስተውሏል፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ባለሀብቶች ከሁሉም በላይ በመንግስት የአደረጃጀት


መዋቅር ውስጥ የአሰራር ግልፅነት አለመኖር፣ ቀልጣፋ አገልግሎት አለማግኘት፣
የተጠያቂነት አሰራር አለመኖር፣ እርስ በእርስ አለመናበብ፣ ደንበኛ ተኮር አለመሆን፣
ኋላቀር አሰራር መከተል፣ ወዘተ በተለይ በመሬት አቅርቦት፣ በገቢዎችና ጉምሩክ፣
በባንኮችና በሌሎችም በስፋት ከፍተኛ ቅሬታ የሚቀርቡባቸው ናቸው፡፡ አዳዲስ ወደ
አምራች ኢንዱስትሪው መሰማራት የሚፈልጉት ባለሀብቶችም ቢሆን ያለውን
ውጣውረድና ድካም በመፍራት ለኢንቨስትመንት የማይበረታቱ ብዙዎች ናቸው፡፡
ስለዚህ በአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት የሚሰማራ ባለሀብት በርከት ያሉ
የመንግስት አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች ማለፍ ስለሚጠበቅበት እነዚህ የመንግስት
መዋቅሮች ግልጽ፣ ውጤታማ፣ ፈጣንና፣ በሕግና በአስተዳደራዊ ሂደት ተጠያቂነት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 67


የሰፈነበት አገልግሎት መስጠት ካልተቻለ በኢንቨስትመንቱ ላይ ምን ያህል ጫና
እንደሚያሳድር መገመት አያዳግትም፡፡

5.1.1 በፌደራል ደረጃ የኢንዱስትሪ ልማት አመራርና አደረጃጀት ነባራዊ ሁኔታ

የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በሀገሪቱ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋና


የአምራች ምርት በብዛትና በጥራት በማቅረብ ተወዳዳሪና ውጤታማ በማድረግ
የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ አቅም በመገንባት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ
እንዲሳካ ለማገዝ የተቀመጡትን ግቦች ለውጤት እንዲያበቃ፤ በተለይ የአምራች
ኢንዱስትሪው ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን
ይጠበቅበታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ከክልሎች ጋር በመደጋገፍ
ለመስራት የሚያስችል፣ ለኢንዱስትሪው በሰው ሃይልና ቴክኖሎጂ ልማት አቅርቦት
በትስስር የሚከናወኑ ተግባራት ወጥነት ባለው ሁኔታ ለማከናወን የሚያስችሉ
አሰራሮችን መዘርጋትና መተግበር ይገባዋል፡፡ ሚኒስቴር መ/ቤቱ በሁለተኛው
የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን የዕቅድ ዘመን ለዘርፉ የተጣሉ ግቦችን ለማሳካት መለስተኛ
አዲስ አደረጃጀት አድርጓል። በዚህ መሠረት ቀደም ሲል በአንድ ሚኒስትር፣ በሶስት
ሚኒስትር ዴኤታዎችና በአስራ አንድ ተቋማት ይመራ የነበረው የኢንዱስትሪ ልማት
ዘርፍ በአሁኑ ወቅት በአንድ ሚኒስትር፣ በሶስት ሚኒስትር ዴኤታዎችና በሰባት
ተቋማት እንዲደራጅ ተደርጓል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የሀገር ውስጥ ባለሀብት ትራንስፎርሜሽን ዳይሬክቶሬት ለሚኒስትሩ


ተጠሪ ሆኖ እንዲቋቋም ተደርጓል፡፡ ይህ ዳይሬክቶሬት በተለይ በአምራች
ኢንዱስትሪው የተሰማራውን የሀገር ውስጥ ባለሀብት ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራ ከሆነ
የተሻለ ውጤት ሊያመጣ ይችላል፡፡ ነገር ግን የሀገር ውስጥ ባለሀብት ልማትን
የሚመለከት ጉዳይ በተለይ ክልሎች ከፍተኛ ሚና መጫዎት የሚገባቸው በመሆኑ
ሚኒስቴር መ/ቤቱ በምን የአሰራር ስርአት ከክልሎች ጋር መስራት እንዳለበት ግልፅ
አቅጣጫና አሰራር ማስቀመጥ የሚኖርበት ይሆናል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 68


5.1.2 በክልሎች የኢንዱስትሪ ልማት አመራርና አደረጃጀት ነባራዊ ሁኔታ

በዚህ ጥናት የተሰበሰቡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በክልሎች፣ ዞኖችና ወረዳዎች


የሚገኘው መዋቅር የኢንዱስትሪ ልማት ተልዕኮን ለማሳካት በሚችልበት ደረጃ ላይ
አልደረሰም፡፡ በትግራይ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ ብ/ብ/ሕዝቦች ክልሎች እና ድሬደዋ
ከተማ አስተዳደር የኢንዱስትሪ ቢሮ ከንግድና ከከተማ ልማት በጋራ የተዋቀረ ነው፡፡
በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ኢንቨስትመንትና ልማት በዋናነት
የመምራት ኃላፊነት ለክልሎች የተሰጠ ነው፡፡ ነገር ግን ከላይ እንደተጠቀሰው ይህ
ዘርፍ ከከተማ ልማትና ንግድ ጋር ተጣምሮ መዋቀሩ እንዲሁም በውስጡ ያሉ
አመራሮችና ባለሙያዎች በዋናነት በንግድና ከተማ ልማት ተግባራት ላይ የተጠመዱ
መሆናቸው አሁንም ኢንዱስትሪው ተገቢውን ትኩረት እንዳያገኝ ዕንቅፋት መሆኑ
አልቀረም፡፡

በየደረጃው ያካሄድናቸው ውይይቶች የንግድና የከተማ ልማት ዘርፍ መዋቅሮች (የስራ


ሂደቶች) የተሻለ የማስፈፀም ዓቅም አላቸው፡፡ በአንፃሩ ኢንዱስትሪውን የሚመሩ
(የኢንቨስትመንት እና የአምራች ኢንዱስትሪ ድጋፍ የስራ ሂደቶች) ጥንካሬ በልምድም
ሆነ በተቋማዊ ስልጣን ላይ ክፍተት ያለባቸው ሆነው ይታያሉ፡፡ የኢንቨስትመንት የስራ
ሂደት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከመስጠትና የባለሀብቱ መረጃ ከማጠናከር በዘለለ
የሚሰራው ስራ የለውም፡፡ መረጃው ከተሰበሰበባቸው ሁሉም ክልሎችና ከተሞች ያለው
አመራርም በተግባር በንግድና የከተማ ልማት ስራዎች በተነፃፃሪነት የተሻለ አመራር
እየሰጠ ሲሆን ኢንዱስትሪውን ለመምራት ግን ያን ያህል የተሟላ ቁመና የሌለው
መሆኑን የኢንቨስትመንትና የአምራች ኢንዱስትሪ ድጋፍ ሰጪ ባለሙያዎች
ገልፀዋል፡፡ አምራች ኢንዱስትሪው ለሀገራዊ ምጣኔ ሀብት ልማት የመሪነት ሚና
እንዲጫወት ከሀብት አመዳደብ ጀምሮ የተሰጠው ትኩረት በተግባር ዝቅተኛ ነው፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ ዝቅተኛ እንዲሆን ካደረገው ሌላው


ምክንያት ለሀገር ውስጥ ባለሀብት የተሰጠው ትኩረት ዝቅተኛ መሆኑ ነው፡፡ የኢትዮጵያ
ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከክልሎችና ከተሞች የተሻለ መዋቅርና ስልጣን አለው፡፡
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ዋነኛ ተልዕኮው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት
የመምራትና የማስተባበር ስራ ነው፡፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን ክልሎች እንዲመሩት
ሲደረግ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በዚህ በኩል የተሰጠው ኃላፊነት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 69


ለክልሎችና ከተሞች የምክርና የቴክኒክ ድጋፍ ማድረግ ላይ የተገደበ ነው (አዋጅ ቁጥር
769/2004 አንቀፅ 28/14)፡፡ ይህ በመሆኑ በኮሚሽኑ ውስጥ ለክልል ኢንቨስትመንት
ድጋፍ የሚሰጥ አንድ ዳይሬክቶሬት ቢኖረውም፤ ዳይሬክቶሬቱ አሁን ያለው ቁመና
በሰው ኃይል ያልተጠናከረና በቂ ድጋፍ መስጠት በሚችልበት ደረጃ አይደለም፡፡ በቂ
ስልጠናና ቴክኒካዊ ድጋፍ እየሰጠ እንዳልሆነም በውይይቱ ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡

የሀገር ውስጥ ባለሀብት ለኢንቨስትመንት የማስተዋወቅ፣ የማነቃቃትና በኢንቨስትመንቱ


እንዲሰማራ የማድረግ ስራው ለክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የተሰጠ ኃላፊነት
ቢሆንም ካለው አደረጃጀትና ልምድ የክልልና ዞን አስተዳዳር ኢንቨስትመንት የስራ
ሂደቶች ጠንካራ ስራ እየሰሩ አይደለም፡፡ ቀዳሚ ስራቸው ሆኖ የሚታየው ፈቃድ
መስጠት እና የስታስቲክስ መረጃ ማጠናቀር ብቻ ነው፡፡ በተለያየ መንገድ እና አጋጣሚ
የኢንቨስትመንት አማራጮች ለባለሃብቱ የማስተዋወቅ ስራ ሲሰራም በጅምላ እንጂ
በታቀደ ሁኔታ የማነሳሳት ስራ ሊሰራበት የሚገባውን ባለሀብት ለይተን እየሰራን
አይደለም (It is generic instead of being focused)፡፡ ብዙዎቹ መሰል
እንቅስቃሴዎች የሚካሄዱት በኢንቨስትመንት ፎረሞች በመሆኑ በእነዚያ መድረኮች
የሚገኘው ባለሀብት በኢንቨስትመንት የተሰማራ ብቻ በመሆኑ የኢንቨስትመንት
የማስተዋወቅ ስራችን ተደማሪ ውጤቱ ዝቅተኛ ይሆናል፡፡ በራሪ ፅሑፎችና የተለያዩ
መገናኛ ብዙሀን በመጠቀም የሚካሄደው የማስተዋወቅና ማነቃቃት ስራውም ዕውቀቱ
ላለው ካልሆነ በስተቀር ለአብዛኛው የንግድ ማሕበረሰብ በቂ መረጃ ይሰጣል ተብሎ
አይገመትም፡፡

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ተጠሪ መ/ቤቶች ላይ የተነሳው ቅሬታ


ኢንዱስትሪው እየተጋረጡበት የሚገኙ ወቅታዊ ችግሮችንና ማነቆዎች በተከታታይ
በማጥናት መፍትሔ ያለማስቀመጥ አንዱ ሲሆን ሁለተኛው በኢንቨስትመንት ፎረሞች
ባለሀብቱ የሚያነሳቸውን አጀንዳዎች በሚገባ በመያዝ በፍጥነት እንዲፈቱ ጥረት
አለማድረግ ነው፡፡ በኢንቨስትመንት ፎረሞችም ቢሆን በየደረጃው ያለ ከፍተኛ አመራር
/ከሚኒስቴሩ ጀምሮ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና የከተማ ከንቲባዎች/ ስለማይገኙ
በየደረጃው የሚገኘው አመራር ኢንዱስትሪው ያሉበት ችግሮች በተገቢ ሁኔታ ከመረዳት
እና የችግሩ አጣዳፊነት ስለማይገነዘብ ተገቢ መፍትሔዎች በወቅቱ አይሰጡም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 70


በሌላ በኩል በቅርቡ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለዘርፉ የተጣሉ
ግቦችን ለማሳካት ጊዜው የሚጠይቀውን አደረጃጀት መፍጠር ተገቢ መሆኑን በማመን
በፌደራል መንግስት የተጀመረውን ነባሩን አደረጃጀት የማስተካከል ስራ ክልሎችና
ሁለቱ የፌደራል ከተማ መስተዳደሮች ካላቸው ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ
አደረጃጀታቸውን ለማስተካከል ጅምሮች እንዳሉ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ከፌደራል
አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኤጀንሲ የተገኙ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
በዚህም መሠረት የደ/ብ/ብ/ሕ ክልል አደረጃጀቱን በማስተካከል በክልል ደረጃ ለክልሉ
ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ተጠሪ የሆነ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪ
ልማት ኤጀንሲ ያቋቋመ ሲሆን በአማራ ክልልም ከደቡብ ክልል ጋር ተመሳሳይ የሆነ
አደረጃጀት የማዋቀር ስራ ተሰርቷል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ደግሞ ለክልሉ ከተማ ልማትና
ኢንዱስትሪ ቢሮ ተጠሪ የሆነ የኢንዱስትሪ ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ለማቋቋም
በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ የትግራይ ክልልዊ መንግስትም እንደ ሌሎቹ ክልሎች
አደረጃጀቱን ለማስተካከል የተለያዩ ጥረቶች በማድረግ ላይ ነው፡፡

ይህ አደረጃጀት ከዚህ በፊት ከነበረው አወቃቀር ጋር ሲነፃፀር አምራች ኢንዱስትሪውን


በቅርበት ለመደገፍ የሚያስችል ቢሆንም አሁንም ከዚህ በፊት እንደነበረው የንግድ
መዋቅሩ ስራ የአምራች ኢንዱስትሪ ስራን እንዳይውጠው ስጋት አለ፡፡ ምክንያቱም
ከዚህ በፊት እንደታየው አመራሩ ካለበት የግንዛቤና የአቅም ክፍተት የተነሳ ብዙውን
ጊዜ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው በንግድና ተያያዥ ስራዎች ላይ መሆኑ ስለማይቀር
ነው፡፡ የንግድና ኢንዱስትሪ ጽ/ቤት ስራን ስንመለከት አብዛኛውን ጊዜያቸው
የሚያጠፉት በዕለት ተዕለት ስራ በሆነው የንግድ ስራ ዘርፍ ላይ ነው፡፡

ከላይ እንደተገለፀው የኢንዱስትሪው ሴክተር ከፌደራል እስከ ክልል እንዲሁም ወረዳ


ያለው አደረጃጀት ሲታይ ወጥነት የጎደለው፣ ራሱን ችሎ ያልተዋቀረና በተደጋጋሚ
የመበተንና የመደራጀት ችግሮች የሚስተዋልበት ነው፡፡ ከፍተኛው የኢንዱስትሪ
አመራር ኢንዱስትሪውን ለማልማትና ውጤት ለማምጣት የሚያስችሉ ተልዕኮዎች፣
ፕሮግራሞችና ተግባራትን በተገቢው መንገድ ለይቶ ለሚመለከታቸው ባለድርሻዎች
አልሰጠም፤ የሚደረገው ክትትልና ድጋፍም ዝቅተኛ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 71


5.1.3 በኢንዱስትሪ አመራሩ ላይ የተስተዋሉ ዋና ዋና ክፍተቶች

የልማታዊ ዲሞክራሲ መስመር የሚከተሉ ሀገራት ዋነኛ መገለጫ ባህሪያት ከሆኑት


መካከል መንግስት የልማት ስራዎችን ለመፈጸም እና የታቀዱ እቅዶችን ከግብ
ለማድረስ የአመራሩ ሚና ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡ ደቡብ ኮሪያና ቻይና የመሳሰሉ
የሩቅ ምስራቅ እስያ ሀገራት በአጭር ጊዜ የሚያስደንቅ ውጤት ያስመዘገቡት ብቃትና
ቀጣይነት ያለው የመሪነት ሚና በመፍጠራቸው ነው፡፡ ኢንዱስትሪን ለማልማት የብዙ
ባለድርሻ አካላት ጥረትና ርብርብ የሚጠይቅ ሲሆን ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ
በእውቀት ላይ የተመሰረተ አመራር ያስፈልገዋል፡፡ አሁን ባለው የሀገራችን ነባራዊ
ሁኔታ አምራች ኢንዱስትሪው የተጠበቀውን ያህል እንዳያድግ ካደረጉት ዋነኛ
ምክንያቶች መካከል አንዱ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ አመራሮች ብቃትና ችሎታ
እንዲሁም የማስፈጸም አቅም ማነስ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶችና የሪፖርት ሰነዶች
ያመላክታሉ (የአንደኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ግምገማ ሪፖርት፣
ተስፋሁን አባይ፣ 2007 ዓ.ም)፡፡ በዚህ ጥናትም በኢንዱስትሪ አመራሮችና ባለሙያዎች
ላይ የተስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

1. በኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂዎች ላይ የአመለካከት ብዥታ መኖር


ከፌደራል እስከ ክልል ወረዳዎች ድረስ ያለው የኢንዱስትሪ አመራርና ባለሙያ
በሀገሪቱ የኢንዱስትሪ ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ የጠራ ግንዛቤና ተግባቦት አለው ለማለት
አያስደፍርም፡፡ በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና ፈጻሚ አካላት በኢንዱስትሪ ልማት
ፖሊሲና ስትራቴጂ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ጨብጦ ወደ ስራ ከመግባት አንጻር ሰፊ
ክፍተቶች አሉ፡፡ በተለይም በታችኛው የአስተዳደር እርከን ማለትም በወረዳ እና
በከተሞች ያለው አመራር በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ ያለው ግንዛቤ ዝቅተኛ በመሆኑ
በዋናነት በአገልግሎት እና በሌሎች የስራ ዘርፎች ሰፊ ጊዜና ሀብት በመመደብ
ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው (የአነ/መካ/ኢን/ልማት ኤጀንሲ፣ 2009 ዓ.ም)፡፡ ነገር ግን
በሀገራችን የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ በተለይ አነስተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች
በወረዳዎችና በከተሞች በስፋት ማሰማራት እንደሚያስፈልግ እና አመራሩ ትኩረት
ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ያስገነዝባል፡፡

በሀገራችን የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ ላይ የግሉ ሴክተር በተለይም የሀገር ውስጥ የግል


ባለሀብቱ ለኢንዱስትሪው ልማትና ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር ወይም ዋና ተዋናይ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 72


መሆኑ በግልፅ የተቀመጠ ቢሆንም የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ይህን የሞተርነት ሚና
እንዲጫዎት ከማድረግ አኳያ በአመራሩና በባለሙያው የተሰራው ስራ አጥጋቢ ነው
ማለት አይቻልም፡፡ ይህም የሚያመላክተው በፖሊሲው ላይ በቂ ግንዛቤ ያለመጨበጡና
በአመራሩ ዘንድ አንድ አይነት አቋም ያለመኖሩ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሀገራችን
የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ ሰነድ የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብት አቀናጅቶ የመጠቀም
አቅጣጫ የዕውቀትና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የካፒታል ዕጥረት ከመፍታት አንፃር ያለው
ፋይዳ በግልፅ ያስቀመጠ ቢሆንም እሰካሁን ድረስ የጎላ ተጨባጭ ውጤት ያልታየበት
ከመሆኑም በላይ ሁለቱን ባለሀብቶች አቀናጅቶ ሊያሰራ የሚችል የአሰራር ስርአት
አልተዘረጋለትም፤ ክትትልና ግምገማ አልተደረገበትም፤ ይህን ተግባር የሚያከናወነው
አካልም በግልፅ የሚታወቅ አይመስልም፡፡

በሌላ በኩል በሀገራችን የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ላይ በአመራሩና በባለሙያው


በቂ ውይይት እና ግንዛቤ ሳይፈጠር ፖሊሲና ስትራቴጂውን ለመተግበር በፍጥነት
መገባቱ እቅዶች ውጤታማ እንዳይሆኑ ማድረጉን እ.ኤ.አ. በ2011 በGRIPS እና
በJICA የተጠኑ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በሀገራችን ዘላቂ የኢንዱስትሪ ዕድገትና ልማት ለማረጋገጥ በ1994


ዓ.ም የወጣውን የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ ወደተግባር ለመቀየር
የሚያስችሉ መመሪያዎችና የአሰራር ስርአቶች በተሟላ መልኩ አልተዘጋጁም፡፡ለምሳሌ
ከላይ እንደተጠቀሰው የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብትን አቀናጅቶ ለመጠቀም
የሚያስችል ግልፅ የአሰራር ስርአት ወይም መመሪያ አልተዘጋጀም፡፡ ሌላው
በኢንዱስትሪ ልማት የመንግስትና የሀገር ወስጥ የግል ባለሀብት ቅንጅት በሚመለከትም
ግልፅ የአሰራር ስርአት የለውም፡፡

2. የትራንስፎርሜሽን አመራር ብቃት መጓደል /Absence of transformational


leadership qualities/

የኢንዱስትሪ ልማትና ዕድገትን ለማረጋገጥ ፖሊሲዎችን፣ የማስፈፀሚያ ፕሮግራሞችን


እና ልዩ ልዩ ስትራቴጂዎችን ከመንደፍ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን
ለማረጋገጥ ራዕይ ያላቸውና ቁርጠኛ የሆኑ አመራሮችና ባለሙያዎች ያስፈልጋሉ፡፡
የትራንስፎርሜሽን አመራር የሚመሩትን መ/ቤት ራዕይ፣ ግብ እና አላማ ከሀገራዊ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 73


ረዕይና ተልዕኮ ጋር በማስተሳሰር በብቃት ወደ ተግባር መቀየርና ፈጣን ለውጥ
ማምጣትን ይጠይቃል፡፡ በተጨማሪም አመራሮች ከራሳቸው ፍላጎትና ስሜት ይልቅ
አጠቃላይ መ/ቤታቸውን ፍላጎት የሚያስቀድሙና የሚመሩት መ/ቤት ላይ ፈጣን፣
ተጨባጭና ተገልጋዩን የሚያረካ ለውጥ ማምጣት የሚችሉ ናቸው (Lewin 1951)፡፡

የኢንዱስትሪ አመራሩንና ባለሙያውን አቅም መገንባት ማለት በአምራች ኢንዱስትሪ


የተሰማራውን የግል ባለሀብት የአቅም ክፍተት (የዕውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት)
መሙላትና መገንባት ማለት ነው፡፡ የባለሀብቱ አቅም በሂደት እየተገነባ ከሄደ ደግሞ
በቢዝነሱ አለም ተወዳዳሪ ይሆናል፡፡ ስለዚህ አዳዲስ ባለሀብቶችን ወደ አምራች
ኢንዱስትሪው ለመሳብ እንዲሁም ቀድመው በዘርፉ የተሰማሩትን ባለሀብቶች አቅም
ለመገንባት ብቃት ያለው አመራርና ባለሙያ በስፋት ማፍራት ቀዳሚ ተግባር
ይሆናል፡፡ የአመራሩና ባለሙያው የማስፈፀም አቅም ከተገነባ የባለሀብቱ የመፈፀም
አቅም ይገነባል፡፡

በሀገራችን የረጅምና የአጭር ጊዜ ራዕይን ለማሳካት ወሳኝ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ


ጠንካራና ተወዳዳሪ የሆነ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ መገንባት ነው፡፡ ነገር ግን በዘርፉ
የተቋማት አመራሮች የማስፈፀም አቅም ውስንነት ጎለቶ ይታያል፡፡

በተለይ በታችኛው የአስተዳደር እርከን (በዞንና/ወረዳ) ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በግልፅ


ያሳያል፡፡ አብዛኛው ጊዜ በታችኛው የአስተዳደር እርከን የሚገኙ አመራሮች ጥቃቅንና
ደራሽ የሆኑ ስራዎች ላይ የተጠመዱ ናቸው፡፡ በአካባቢያቸው የሚገኙ በአንጻራዊ
የተሻሉ ተፈጥሮአዊ እና ሰው ሰራሽ አቅሞችን ለይቶ በዛው ልክ ተወዳዳሪ የሆኑ
አምራች ኢንዱስትሪዎችን እንዲፈጠሩ ሲያደርጉ አይስተዋልም፡፡ ይህ ችግር በወረዳ
ወይም በከተሞች ብቻ ሳይሆን በፌደራል እና በክልል የሚገኙ አመራሮች ዘንድም
ይንጸባረቃል፡፡ አመራሩ ሀገራዊ ራዕዮችን ለማሳካት ከመረባረብ ይልቅ ባሉበት መ/ቤት
የመታጠር ችግሮች ይታያሉ፡፡ አምራች ኢንዱስትሪዎችን መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ
አካል ኃላፊነት እንደሆነ ቢታወቅም ነገር ግን በፌደራልም ሆነ በክልል የሚገኙ ጥቂት
የማይባሉ መ/ቤቶች (ለምሣሌ፡ የገቢዎችና ጉምሩክ፣ የመብራት ሀይል ባለስልጣን፣
ባንኮች፣ ወዘተ…) ለዘርፉ የተለየ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ አይመስሉም፡፡ ምናልባት
ለዚህ ዋናው ምክንያት የሚሆነው በመ/ቤቶቹ በተለያየ ደረጃ ያሉ አመራሮች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 74


በኢንዱስትሪ ልማት ዙሪያ ያላቸው ግንዛቤ አናሳ መሆኑን እና የትራንስፎርሜሽን
የአመራር ብቃት መጓደል እና ሩቅ አሳቢ ያለመሆናቸውን ያሳያል፡፡

በሌላ በኩል ለዚህ ዘርፍ የሚመደቡ አመራሮች (በተለይም በታችኛው የአስተዳደር


እርከን) በቂ አቅምና ልምድ ያላቸው ባለመሆኑ ምክንያት በተገቢው መንገድ እየመሩት
ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡ አቅማቸው ባለሀብቶችን በሙሉ ልብ እና በራስ
መተማመን አሳምኖ ወደ አምራች ኢንዱስትሪ እንዲቀላቀሉ ማድረግ አልተቻለም፡፡
ልማታዊ ባለሀብቱን የማጠናከርና ጥገኛ ባለሀብቱን የማክሰም ስራ መስራት
አልቻሉም፡፡ ለባለሀብቱ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመለየት የአዋጭነት ጥናቶችን
በማከናወን ተጠቃሚ ማድረግ አልተቻለም፡፡ ባለሙያውም ቢሆን በተመሳሳይ የግንዛቤ
እና የአቅም ክፍተት ስለሚስተዋልበት ለባለሀብቱ ጥራት ያለውና ቀልጣፋ አገልግሎት
መስጠት አልቻለም፡፡ የመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ግምገማም
ሪፖርት የሚያመላክተው ይህንኑ ነው፡፡ ለዕቅዱ በታሰበው መልኩ ያለመሳካት እንደ
ምክንያት ከተጠቀሱት መካከል በአመራሩ ዘንድ የሚታየው የማስፈጸም አቅም መጓደል
በዋነኝነት ይጠቀሳል፡፡

ሌላው በአመራሩ ዘንድ በስፋት የሚነሳው ክፍተት አመራሩ ችግር የመፍታት አቅሙ
ዝቅተኛ መሆኑ ነው፡፡ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች ለስራቸው እንቅፋት የሆኑ የተለያዩ
ችግሮችን ለመንግስት አካል በየጊዜው ቢያቀርቡም ችግሮቹን የሚፈታ አካል
አልተገኘም፡፡ የተወሰኑ ችግሮች ቢፈቱም በጣም ዘግይተው ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋነኛ
ተጠያቂ ኢንዱስትሪውን በመምራት ላይ የሚገኙ አመራሮች እንደሆኑ የአምራች
ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች ገልፀዋል፡፡ በተለያዩ ወቅቶች ከባለሀብቱ ጋር በሚደረጉ
የውይይት መድረኮች ተመሳሳይ ችግሮች በተደጋጋሚ መነሳታቸው የአመራሩ ችግር
የመፍታት አቅም ያነሰ መሆኑ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ኢዱስትሪውን
በመምራት ላይ የሚገኙ አመራሮች ለኢንዱስትሪዎች ማነቆ የሆኑ እንቅፋቶችን
በአጭር እና በረዥም ጊዜ እየከፋፈሉ ከመፍታት ይልቅ ጊዜያቸውን በተለያዩ ደራሽ
ስራዎች ተጠምደው ይታያሉ፡፡ ይህም የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ለከፍተኛ ችግርና
ምሬት እንዲዳረግ አድርጎታል፡፡

ቻይና ፈጣን የኢንዱስትሪ ልማት እንድታረጋግጥ ካደረጓት ወሳኝ ምክንያቶች መካከል


መንግስት በሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ከስር ከስር የሚፈታ ጠንካራ አመራር

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 75


በመመደቡ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ሀገሪቷ ምርጥ ፖሊሲዎችን ማውጣት ብቻ ሳይሆን
ብቁ አስፈጻሚ ተቋማትን ለመፍጠር የተለያዩ ስልቶችን ቀይሳ ተንቀሳቅሳለች፡፡ እነዚህ
ተቋማትን በብቃት ለመምራት ደግሞ ውጤት ተኮር የሆነ እንዲሁም በፈጠራና በራስ
መተማመን ላይ የተመሰረተ አመራር ይጠይቅ ነበር፡፡ ያልተሞከረ አዲስ ሀሳብ
ሳይንሳዊነቱን በማመን ብቁ ተቋምና የህግ ማዕቀፍ በመፍጠር፣ አመራሩ ውጤቱን
በቅርበት በመከታተልና በመገምገም፣ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ወዲያሁኑ መፍታት
የሚችል በራሳቸው የሚተማመኑ አመራሮችን መድባ በማሰራት ውጤታማ ሆናለች፡፡

በሌላ በኩል በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ኢንዱስትሪን ማልማት የህልውና (ወይም


በእድገት የመቀጠል ወይም ያለመቀጠል) ጉዳይ አድርጎ ያለማየት ብሎም ከበላይ
አካል ቅስቀሳን የመጠበቅ አዝማሚያ ይታይባቸዋል፡፡ አመራሮችና ባለሙያዎችም
በስራ ገበታቸው ተገኝተው ለባለሀብቱ ተገቢውን ድጋፍ ከመስጠት አንፃር ክፍተት
አለባቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ዘርፉን እየመሩ የሚገኙ አመራሮችና ባለሙያዎች
በስብሰባ እና የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር ከስራ ገበታቸው ስለማይገኙ
ለባለሀብቱ መስጠት ያለባቸውን አገልግሎት በተገቢው መልኩ እየሰጡ አይደለም፡፡
ከዚህም ሌላ ለባለሀብቱ አገልግሎት እንዲሰጡ በየደረጃው የተደራጁ ቢሮዎች ዘመናዊ
አሰራር ስርዓት ስላልተዘረጋላቸው ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ አይደለም፡፡ የመረጃ
ልውውጥ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ አይደለም፡፡ ይህም ባለሀብቱ ቀልጣፋ
አገልግሎት እንዳያገኝ አድርጎታል፡፡

3. በጋራ ተቀናጅቶ ያለመስራት


በፌደራልም ሆነ በክልል ደረጃ ለአምራች ኢንዱስትሪ ድጋፍ እንዲሰጡ የተዋቀሩ
አስፈጻሚ አካላት በቅንጅት ተናበው እየሰሩ አይደለም፡፡ አምራች ኢንዱስትሪ ልዩ ልዩ
አገልግሎቶችን ከተለያ መ/ቤቶች እንደሚያገኝ ይታወቃል፡፡ የጉምሩክ፣ የመብራት፣
የቴሌኮሚኒኬሽን፣ የማምረቻ ቦታ፣ የቴክኖሎጂ ድጋፍ፣ የፋይናንስ አቅርቦት ድጋፍ፣
ወዘተ ከብዙዎቹ ጥቂቶቹ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ተቋማት በጋራ
ተቀናጅተው የማይሰሩ በመሆናቸው ባለሀብቱ ለከፍተኛ እንግልት ሲዳረግ ይስተዋላል፡፡
በተጨማሪም በፌደራልና በክልሎች መካከልም በዕቅድ ዙሪያ ወጥ የሆነ አቋም ይዘውና
ተናበው ለዘርፉ ውጤታማነት በትጋት ከመስራት አኳያ ክፍተቶች ተስተውለዋል፡፡
አብዛኛዎቹ የመንግስት አመራርና ፈፃሚ አካላት በኢንዱስትሪ ፖሊሲዎችንና
ስትራቴጂዎች ላይ የተሟላና የጠራ ግንዛቤ በትክክል ተጨብጦና መግባባት ተደርሶበት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 76


ወደ ዕቅድና ትግበራ ያልተገባበት፣ ባለድርሻዎችም ተናበውና ተቀናጅተውና ትኩረት
ሰጥተው በቁርጠኝነት ያለመተግበር ችግር አለ፡፡

በአጠቃላይ ከላይ የተጠቀሱ ዋና ዋና የኢንዱስትሪ አመራር ችግሮች በአንድም ሆነ


በሌላ መልኩ በአመራሩ ላይ ጎልተው የሚታዩ በመሆኑ አመራሩ አምራች
ኢንዱስትሪውን መደገፍ በሚገባው መልኩ ሳይደግፍ ቀርቷል፡፡ በዚህም ዘርፉ ማደግ
በሚገባው ፍጥነት እንዳያድግ አድርጎታል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱ
ችግሮች በአመራሩ ላይ መኖራቸው እየታወቀ በፌደራልም ሆነ በክልል መንግስታት
ችግሮቹን ለማረም እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ለውጥ የማያመጡ መሆናቸው ትልቁና
አሳሳቢው ችግር ሆኖ ይገኛል፡፡ አመራሩ ያቀደውን ዕቅድ ከማሳካት አንጻር
የሚገመገምበት አሰራር ያለ ቢሆንም ችግሩን ከስር መሰረቱ ለመቅረፍ የሚያስችል
አይደለም፡፡ መንግስትም የአመራሩን አቅም ለማጎልበት የተወሰኑ ጅምር ስራዎችን
የሰራ ቢሆንም ከተቀመጠው ግብ አንጻር በቂ አይደለም፡፡

የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ ከላይ እንደተገለፀው ጠንካራ የመንግስት


አመራር እና ጣልቃገብነት ይፈልጋል፤ እስካሁን እየተሰራበት ከነበረው የአሰራር ዘይቤ
(ከተለመደው አካሄድ) በመውጣት ወይም በተለየ አካሄድ መስራትን ይጠይቃል፤ይህ
ደግሞ ታምራዊ ለውጥ ይፈልጋል፤ በአምራች ኢንዱስትሪው ለተሰማራው የሀገር ውስጥ
ባለሀብት የተለየ ትኩረት መስጠትን ይጠይቃል፡፡

ሌላው ብቁ አመራሮችን መርጦ ለወሳኝ ስራዎች በትክክል ከመመደብ እና በቂ ድጋፍ


ከማድረግ አንጻር በፌደራልም ይሁን በክልል መንግስታት ከፍተኛ ችግር ይስተዋላል፡፡
አመራሩ ለተመደበበት ስራ በቂ ጊዜ ሰጥቶ በሰራው መጠን ልክ ከመገምገም ይልቅ
አመራሩን ገና ሳይሰራ የመቀያየር ችግሮች ይንጸባረቃሉ፡፡ ይህ ደግሞ የባለሀብቱን
ችግር የበለጠ እንዲባባስ አድርጎታል፡፡ የደቡብ ኮሪያን ልምድ በምናይበት ጊዜ፤
በሀገሪቱ ወሳኝ ስራዎች በአግባቡ ተለይተው በውጤት ተኮር ምዘና ውጤታማነቱ
የተረጋገጠና የታመነበት አመራር ከየትም ተመርጦ ይመደብላቸዋል፡፡ የተመደበው
አመራር ስራውን ጠንቅቆ አውቆ አመርቂ ውጤት ያመጣ ዘንድ በቂ ጊዜ እንዲያገኝ
በተመደበበት ስራ ረዘም ያለ ጊዜ እንዲቆይና ተቋሙን ትራንስፎርም ማድረግና ስኬት
ማምጣት ላይ በነጻነትና በራስ መተማመን እንዲመራ ሙሉ እምነት ይጣልበታል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 77


ቀጥሎም ችግር ፈቺና ውጤት አስመዝጋቢ መሆን ያለመሆኑን በጠንካራ ድጋፍና
በሱፐርቪዥን በውጤት ተኮር ምዘና በየጊዜው ይረጋገጣል፡፡

5.2 የኢንዱስትሪ ማበረታቻና ድጋፍ አቅርቦት

መንግስት ጠንካራ ሀገራዊ ባለሀብት ለመፍጠር የማክሮ ኢኮኖሚ ማረጋጋት፣ መሰረተ-


ልማት ማስፋፋት፣ የሰለጠነ የሰው ሀይል አቅርቦት፣ የተስማሚ ፋይናንስ ስርአት
መዘርጋት፣ ቀልጣፋ የፍትህ ስርአት መፍጠር እና ሌሎች ስራዎች ሰርቷል፤
በመስራትም ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሰረት የተጠበቀውን ያህል ባይሆንም የተወሰኑ
ልማታዊ ባለሀብቶች ለመፍጠር ተችሏል፡፡ በተለይ ከአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ
ይልቅ በሪል እስቴት፣ አስመጪ-ላኪ እና በአገልግሎት ዘርፍ በርካታ ባለሀብት
ተፈጥሯል፡፡

ለዚህ እንደ ዋና ምክንያት የሚገለፀው በአምራች ዘርፍ የተሰማራው ባለሀብት


ኢንቨስትመንት ሲጀምር፣ ኢንቨስትመንት ሲያስፋፋ፣ ምርት ሲያመርት እና ምርት
ለገበያ ሲያቀርብ ከሌላ ዘርፍ የተሻለ ድጋፍ አለመማግኘቱ በዋናነት ይጠቀሳል፡፡
ስለሆነም በአምራች ዘርፍ የተሰማራው ባለሀብት ተወዳዳሪነት ለማጠናከርና አዳዲስ
ኢንቨስተሮች ለመሳብ አሁን እየቀረበ ያለውን የማበረታቻ ማዕቀፍ መከለስና
ለተግባራዊነቱ መትጋት ያስፈልጋል፡፡ በተጨማሪም ሀገራዊ ባለሀብቱ በአምራች ዘርፍ
በሚፈለገው መጠን ሚናውን እንዲጫዎት እና አዳዲስ ባለሀብት ለመሳብ እንዲቻል
አሁን ያለውን የማበረታቻ ማዕቀፍ መቃኘት እና ማነቆዎችን መለየት አስፈላጊ ነው፡፡
ይህ ማለት የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለው ሚና ተጠናክሮ
እንዲቀጥል ከተፈለገ የማበረታቻ ስርዐቱ የዘርፉን መዋቅራዊ ለውጥ በሚያረጋግጥ
አቅጣጫ ካልተቃኘ ባለሀብቱ ፊቱን ወደ አገልግሎት፣ ንግድ እና ሪል እስቴት ዘርፍ
ማዞሩን አያቆምም፡፡ በሌላ አገላለጽ የሀገራችን የካፒታል ክምችት ትንሽ እሴት ወደ
ሚጨምረው እና ያለ ድካምና ውጣውረድ ትርፍ ወደሚገኝበት ዘርፍ እንዲሆን
ያደርጋል፡፡

ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚቀርበው ማበረታቻና ድጋፍ ተወዳዳሪነቱን


በሚያጎለብት ሁኔታ ካለመቅረቡ በተጨማሪ ለጥገኛ ባለሀብቶች መጠቀሚያ የመሆን
አዝማሚያ ይታይበታል፡፡ ለዘርፉ የሚቀርበውን ማበረታቻ በሶስት ከፍለን ማየት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 78


እንችላለን፡ የኢንቨስትመንት፣ የኤክስፖርት እና ሌሎች ማበረታቻዎች (ኢንዱስትሪና
ንግድ ሚኒስቴር እና UNDP፣ 2000)፡፡ በተጨማሪ የኢንቨስትመንትና የኤክስፖርት
ማበረታቻ ስርዐቱ በአብዛኛው ከግብር እና ቀረጥ ጋር የተያያዘ ሆኖ ይታያል፡፡ በዚህ
ርዕስ በዋናነት መዳሰስ የተፈለገው ግብር እና ቀረጥ ተመስርተው የሚቀርቡ
ማበረታቻዎች ላይ ይሆናል፡፡

5.2.1 ኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች

በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራው ባለሀብት (የሀገር ውስጥ እና የውጭ)


ለፕሮጀክት ኢንቨስትመንት አስፈላጊ የሆኑ የካፒታል እቃዎች (እስከ 15% ያህል
የካፒታል እቃዎችን ዋጋ የሚገመት መለዋወጫዎችን ለአምስት አመት ከጉምሩክ
ቀረጥ ነፃ ማስገባትን ጨምሮ) ማለትም ማሽነሪና ኢኩፕመንት፣ የወርክሾፕና የላቦራቶሪ
እቃዎችን እና የግንባታ እቃዎችን ከጉምሩክ ቀረጥ እና ታክስ ነፃ በሆነ መንገድ
በማንኛውም ጊዜ ማስመጣት እንዲችል በኢንቨስትመንት ደንብ ተፈቅዶለታል፡፡
በተጨማሪም ለኢንቨስትመንት ፕሮጀክት አስፈላጊ የሆኑ ተሽከርካሪዎችን እንዲሁ፡፡
የጉምሩክ ቀረጥ ነፃ መብት ተጠቃሚ የሆነ ባለሀብት በሀገር ውስጥ የተመረተ የካፒታል
ወይም የግንባታ እቃ ሲገዛ እንዲሁ ማበረታቻው ተፈጻሚ ይሆናል (ደንብ ቁጥር
270/2005 ዓ.ም)፡፡

በሌላ በኩል የልማት ፍላጐት፣ የኢንቨስትመንቱ ክብደት እና ፕሮጀክቱ የተቋቋመበትን


ታሳቢ ያደረገ ከአንድ እስከ አስር አመት ከገቢ ግብር ክፍያ ነፃ የሚያደርግ ማበረታቻ
ያገኛል፡፡ በተጓዳኝ ከአዲስ አበባ ራቅ ባሉ የተለዩ አካባቢዎች (ማለትም በተመረጡ
ታዳጊ ክልሎች ወይም ዞኖች) በኢንቨስትመንት ለሚሰማራ ባለሀብት የገቢ ግብር
እፎይታ ዘመን ከተጠናቀቀ በኋላ ለሶስት ተከታታይ አመታት ከ30% የገቢ ግብር
ቅናሽ ይደረግለታል፡፡ ቢያንስ 60% ምርት ለውጭ ገበያ የሚልክ ባለሀብት ወይም ወደ
ውጭ በምርት ግብአትነት የሚያቀርብ ከሆነ ከተፈቀደለት እፎይታ ዘመን በተጨማሪ
ለሁለት ዓመት ከገቢ ግብር ነፃ ይሆናል (ደንብ ቁጥር 270/2005 ዓ.ም)፡፡ ሌላው
በኢንዱስትሪ ልማት ቀጠና ውስጥ ያለ አምራች ኢንዱስትሪ ቢያንስ 80%
የሚገመተውን ምርት ለውጭ ገበያ ከላከ ወይም ወደ ውጭ ለሚልክ ባለሀብት በምርት
ግብአትነት የሚያቀርብ ከሆነ የተቋቋመበትን ቦታ ወይም ክልል ታሳቢ በማድረግ
ከተፈቀደለት ዕፎይታ ዘመን በተጨማሪ ከ2 እስከ 4 አመት ነፃ የገቢ ግብር ማበረታቻ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 79


ያገኛል፡፡ በሌላ አገላለጽ ለአዲስ አበባ እና አዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን 2
አመት እና በሌላ አካባቢ ባለ የኢንዱስትሪ ልማት ቀጠና ለተቋቋመ ኢንዱስትሪ 4
አመት ከገቢ ግብር ነጻ ማበረታቻ ይቀርባል፡፡ በተጓዳኝ ለአዲስ አበባ እና አዲስ አበባ
ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ለተቋቋመ የኢንዱስትሪ ልማት ቀጠና 10 አመት እና በሌላ
አካባቢ ለተቋቋመ የኢንዱስትሪ ልማት ቀጠና 15 አመት ከገቢ ግብር ነፃ ማበረታቻ
ያገኛል (የኢንቨትመንት ማበረታቻ ማሻሽያ መመሪያ፣ 312/2006 ዓ.ም)፡፡ሌላው
የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ኪሣራ ማስተላለፍን ይመለከታል፡፡ የገቢ ግብር ነፃ
ማበረታቻ በተሰጠበት ዘመን ውስጥ ኪሳራ ያጋጠመው ባለሀብት የገቢ ግብር ነፃ ዘመኑ
ከተጠናቀቀ በኋላ የዚሁ ዘመን ግማሽ ለሚሆን ኪሳራው ይተላለፍለታል፡፡ ነገር ግን
ኪሳራ የደረሰበት ባለሀብት የደረሰበትን ኪሳራ ከአምስት የገቢ ግብር ዘመን በላይ
ማስተላለፍ አይችልም (ደንብ ቁጥር 270/2005 ዓ.ም)፡፡

ለባለሀብቱ የሚቀርበው ኢንቨስትመንት ማበረታቻ (investment incentive) ሁለት


መሰረታዊ ችግሮች እንዳሉበት ከሰነድ እና ከባለሀብቱ የተገኙ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
አንደኛ አስፈፃሚ አካላት አመራር፣ አቅምና አመለካከት ችግር ምክንያት
በኢንቨስትመንት ደንብ የተፈቀደለትን ማበረታቻ በሚፈለገው ደረጃ ተደራሽ
አለመደረጉ ነው፡፡ ሁለተኛው የማበረታቻ አቅርቦት አይነትና መጠን በአምራች
ኢንዱስትሪ የተሰማራውን ባለሀብት ለመደገፍ በቂ አይደለም፡፡

የመጀመሪያውን ችግር ዘርዘር አድርገን ስናይ የተፈቀዱ ማበረታቻዎች ለተፈቀደላቸው


አካላት በትክክል እንዳይደርስና እንዳይተገበር በቀጥታ የሚመለከታቸው ተቋማት
የማስፈጸም አቅም ውስንነት እና የቅንጅት ጉድለት እንደሆነ በአምራች ኢንዱስትሪ
የተሰማራው ባለሀብት እና ባለሙያ ይገልፃል፡፡ ለአብነት በገቢዎች እና ጉምሩክ
ባለስልጣን በኩል ያለው ቅልጥፍና እና ብቃት የጎደለው የአገልግሎት አሰጣጥ በመኖሩ
ማበረታቻ እና ድጋፍ በአግባቡ መሬት ላይ እንዳይወርድ ሆኗል፡፡የካፒታል ዕቃዎች
እና ሌሎች ከቀረጥ ነፃ የተፈቀዱ መብቶች ለማስፈጸም በየክልሎች እና በሌሎች
ከተሞች የሚገኙት አምራቾች አዲስ አበባ ድረስ ተጉዘው ማስፈፀም የግድ ይላቸዋል፡፡
በክልል ዋና ከተሞች የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ቢኖሩም አገልግሎቱን ለባለሀብቱ
በአቅራቢያው እየሰጡት እንዳልሆነ ይታያል፡፡ አምራቹ አዲስ አበባ ድረስ እየመጣ
መሰል ጉዳይ ማስፈፀሙ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በኩል አሰራር ግድፈት እንዳለ
ያመላክታል። ከዚህ በተጨማሪ ቀረጥ ለማስከፈል የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 80


ዘመናዊ ያልሆነ አሰራር ብሎም ወቅታዊ የገበያ መረጃ ላይ ባልተደገፈ አኳኋን
ስለሚሰራ አምራቾች ከውጭ ለሚያስገቡት ግብአት እና መለዋወጫዎች ሊከፈልበት
ከሚገባው ዋጋ በላይ እየከፈሉ መሆኑን ኢንቨስተሮች ይገልፃሉ፡፡

ለምሳሌ በ2007 ዓ.ም በተሰበሰበው መረጃ መሰረት በናሙናነት ከተወሰዱ የአምራች


ኩባንያዎች መካከል 46 ኩባንያዎች (53.5%) መንግስት የፈቀደውን ማበረታቻ
አሟጠው እንደሚጠቀሙበት እና 31 ኩባንያዎች (36%) ደግሞ በከፊል
እንደሚጠቀሙበት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በአዋጅ እና መመሪያ
ለተቀመጡት ማበረታቻዎች በመንግስት በተግባር ለማቅረብ ውስንነት እንዳለበት ጥናቱ
ጠቁሟል፡፡ በዚሁ አመት መንግስት ማበረታቻዎችን በመተግበር በተመለከተ መጠይቅ
ከተደረገላው የአምራች ኩባንያዎች ውስጥ 56 ኩባንያዎች (65.1%) ማበረታቻዎቹ
ተሟልተው እየቀረቡ አለመሆኑን እና 8 ኩባንያዎች (9.3%) በአግባቡ ማበረታቻዎቹ
ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚ እንዳልሆኑ ጠቅሰዋል፡፡ በሌላ አገላለጽ 74.4% ለሚሆኑ
ኩባንያዎች የመንግስት ማበረታቻ ተሟልቶ ወይም መሉ በሙሉ እንደማይደርስ
ያሳያል፡፡

ሁለተኛው ጉዳይ በመንግስት እየቀረበ ያለው ማበረታቻ አነስተኛ መሆኑ ነው፡፡በተለይ


የተፈቀደው የእፎይታ ዘመን (የገቢ ግብር ነፃ ማበረታቻ) በቂ አለመሆኑ በጥናቱ
የተሳተፉ ኩባንያዎች ገልፀዋል፡፡ አብዛኛው የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብት ለዘርፉ
አዲሰ በመሆኑ፣ በሀገራችን ያለው አግልግሎት አሰጣጥ የተንዛዛ እና ውጣ ውረድ
የበዛበት ብሎም አገልግሎት በአንድ ቦታ የማይሰጥ መሆኑ፣ የፋብሪካ ህንፃ ግንባታ
እቃዎች እና ማሽነሪዎች ለመግዛት የውጪ ምንዛሬ ዕጥረት መኖር፤ መሰረተ ልማት
አቅርቦት፣ የሎጂስቲክስ አገልግሎት ውስን መሆኑ እና ሌሎች ማነቆዎች በመኖራቸው
ባለሀብቱ የገቢ ግብር ነፃ ማበረታቻ አሟጦ መጠቀም አይችልም፡፡ ከዚህ የተነሳ አሁን
በስራ ላይ የዋለው የእፎይታ ዘመን አጭርና ባለሀብቱን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ
አይደለም፡፡ በተጨማሪ በክልሎች (በተለይ መሰረተ ልማት እና ሎጀስቲክ ውስን
በሆነባቸው አከባቢዎች) የተሰጠው የእፎይታ ዘመን ማበረታቻ በቂ አለመሆኑን
ከባለሙያዎች እና ኩባንያዎች የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡ ሌላው በክልሎች የሚሰጠው
የነፃ ግብር ዘመን ማበረታቻ ለኢንቨስተሮች ሳቢ የማድረግ ፋይዳ ፍትሃዊ
የአንቨስትመንት ስምሪት እና የሀብት ክፍፍል ለማረጋገጥ ያግዛል፡፡ ለምሳሌ በአዲስ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 81


አበባና አዲስ አበባ አካባቢ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተዘረጋው የእፎይታ ዘመን ከክልሎችና
ሌሎች አካባቢዎች ጋር ሲነጻጸር የጎላ ልዩነት የለውም፡፡

የሌሎች ሀገራት ልምድ ስንመለከት የኤሲያ ሀገራት በልዩ ሁኔታ ለተመረጡ ዘርፎች
ከሚያደርጉት ማበረታቻ ባሻገር በኤክስፓርት ዘርፍ ለተሰማሩ ተጨማሪ ማበረታቻ
ያቀርቡ ነበር፡፡ ማበረታቻዎቹ የኢንዱስትሪ እድገትን እየተከተሉ በየጊዜው የሚሻሻሉ
እንደሆኑ መገንዘብ ያሻል፡፡ ለአብነት የኮሪያ በ1980ዎቹ የነበረው የግብር እፎይታ
ስርአት ሲታይ ለተመረጡ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ከማነኛውም የግብር አይነት
(corporate income tax, dividend income tax, unincorporated units income tax,
property tax, development tax and property acquisition tax) እስከ 5 ዓመት
የሚደርስ እፎይታ እንዲሁም የእፎይታ ዘመን ካለቀ በኋላ ተጨማሪ 50% የታክስ
ቅናሽ ለ 3 አመት ታቀርብ ነበር፡፡ ከተጠቀሰው ማበረታቻ በተጨማሪ የኤክስፓርት
ዘርፍ ከቢዝነስ ታክስ (Business tax) ነፃ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ ማሌዥያ ለተመረጡ
ዘርፎች ከ5-10 አመት የግብር እፎይታ (ኮርፖሬት ገቢ ግብር፣ ዲቪደንድ ገቢ ግብር
እና ደቨሎፕመንት ግብር) እና በጊዜ ያልተገደበ ኪሳራን የማስተላለፍ መብት ትሰጥ
ነበር፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ ማሌዥያ የግብር እፎይታ ለኤክስፖርት ዘርፍ ተጨማሪ ከ4-7
አመት የታክስ እፎይታ ነበራት፡፡ ሌላው ፊሊፒንስ ስትሆን ትኩረት ለተሰጣቸው
ዘርፎች ከማነኛውም ግብር ነፃ (የኮርፖሬት ገቢ ግብር ሳይጨምር) ማበረታቻ ታደርግ
ነበር፡፡ ከዚህ ሌላ ትኩረት የተሰጣቸው ዘርፎች እስከ 10 አመት የሚደርስ የኪሳራ
ማሸጋገር መብት ነበራቸው፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን አንድ አምራች ማምረት ከጀመረበት ጊዜ
አንስቶ በ5 አመታት ጊዜ ውስጥ ገቢው ከ5 ሚሊዮን ዶላር ከበለጠ ኤክስፖርት
ለሚያደርገው ምርት ከኤክስፖርት ታክስ (export tax) ነፃ ይደረጋል፡፡ ታይላንድ
በተመሳሳይ የግብር እፎይታ ለተመረጡ ዘርፎች ከ3-8 አመት የግብር ብሎም የግብር
እፎይታ ዘመን ሲጠናቀቅ ለ5 አመታት 50% የቢዝነስ ግብር እና የኮርፖሬት ገቢግብር
ተቀናሽ ታደርግ ነበር፡፡ በተጨማሪም ኤክስፖርት ለሚያደርጉ አምራቾች ከኤክስፖርት
ግብር እና ቢዝነስ ግብር ነፃ ታደርግ ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር ሲታይ በሀገራችን ባለሀብቱን
ለመሳብ አሁን ያለው ማበረታቻና ድጋፍ በቂ ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 82


5.2.2 የገቢ ግብር እና የታክስ ማበረታቻዎች

እንደሚታወቀው አምራች ኢንዱስትሪው ከፍተኛ እውቀት እና ክህሎት የሚሻ፣ ግዙፍ


የካፒታል ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ፣ የትርፍ ህዳጉ አነስተኛና ረጅም ጊዜ የሚፈልግ
እና ጠንካራ አለማቀፍ ውድድር ያለበት በመሆኑ እልህ አስጨራሽ ጥረት እና
ቁርጠኝነት ይጠይቃል፡፡ ዘርፉ ያሉበትን ፈተናዎች ተቋቁሞ የተፈለገበት ደረጃ
እንዲደርስ በየደረጃው ማበረታቻ ማቅረብ ተቀባይነት ያለው የፓሊሲ አቅጣጫ እንደሆነ
ብዙዎች ይስማማሉ፡፡ ነገር ግን የሀገራችን የግብር ህግ አምራች ኢንዱስትሪውን
ለማበረታታት ታስቦ የተዘጋጀ አይመስልም፡፡ በገቢ ግብር ህግ ውስጥ የገቢ ግብር
ምጣኔ፣ የእርጅና ተቀናሽ፣ ከግብር ተቀናሽ ወጭዎች እና ሌሎች ጉዳዮች በአጠቃላይ
ሲታዩ ለአምራች ኢንዱስትሪውና ሌሎች ዘርፎች ተመሳሳይነት አላቸው፡፡

የገቢ ግብር ምጣኔ


በሀገራች ለኢንዱስትሪ፣ ግብርና እና አገልግሎት ዘርፎች የሚጣለው የገቢ ግብር ምጣኔ
አንድ አይነት ሲሆን አሁን ያለው የገቢ ግብር ምጣኔም ለሁሉም የኢኮኖሚ ዘርፎች
የ30% መጠን ይዟል፡፡ ይህ የግብር ምጣኔ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ነባራዊ ሁኔታ
ያገናዘበ አይመስልም፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እሴት በመጨመር፣ የኢኮኖሚ
ዘርፎችን በማስተሳሰር፣ መጠነ ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠር፣ የውጭ ንግድ በማስፋፋት
እና ብሎም ለአጠቃላይ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን የማይተካ ሚና አለው፤ ነገር ግን
በበርካታ ማነቆዎች እና ችግሮች ተውጦ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል የአገልግሎት፣ ሪል
እስቴት እና ገቢ-ወጭ ንግድ ያሉት ዘርፎች ያለብዙ ድካም ትርፋማ የሚያደርጉ፣
እንዲሁም በእሴት መጨመር እና የስራ ዕድል ፈጠራ ውስን አስተዋፅኦ ያላቸው
ናቸው፡፡ ስለሆነም አንድ አይነት የገቢ ግብር ምጣኔ መኖሩ የአምራች ዘርፍ
በኢንቨስተሩ ተመራጭነት የሚቀንስ እና በዘርፉ የተሰማራውን ባለሀብት ወደ ሌሎች
ዘርፎች እንዲኮበልል ያደርጋል፡፡

በሌላ በኩል ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚቀርበውን የገቢ ግብር ምጣኔ በልዩ ሁኔታ
ዝቅተኛ ማድረግ የግል ባለሀብት በዘርፉ እንዲቆይ፣ አዳዲስ ባለሀብት ለመሳብ እና
ዘርፍን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይረዳል፡፡ ይህን እውነታ ለመረዳት በኢንዱስትሪ ልማት
የገፉ ሀገራትን ተሞክሮ መጥቅስ ተገቢ ነው፡፡ ለምሳሌ ቬትናም ለአምራች ኢንዱስትሪ
እንደ ኢንቨስትመንቱ አይነትና የሚገኝበት ቦታ ከ10-20% እና ለሌሎች ዘርፎች 25%

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 83


የገቢ ግብር ምጣኔ አላት፡፡ እንዲሁም በታይዋን በ1960 ዎቹ የአምራች ዘርፍ የቢዝነስ
ግብር መጠን 18% ሲሆን በንግድ ዘርፍ ለተሰማራው ባለሀብት ደግሞ 32.5% ነበር፡፡
በተመሳሳይ በደቡብ ኮሪያ የፓርክ አስተዳደር ትኩረት ለተሰጣቸው አምራች
ኢንዱስትሪዎች በተለያዩ ጊዜያት የኮርፖሬት (corporate) እና ለግልሰብ የሚጣል ገቢ
ግብር መጠን (private income tax rates) ላይ ቅናሽ ማድረግ ከሌሎች ዘርፎች ያነሰ
ግብር እንዲከፍሉ በማድረግ ዘርፉን ያበረታታ እንደ ነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በአጠቃላይ ሲታይ ከላይ የተጠቀሱት ሀገራት በአምራች ኢንዱስትሪና በሌሎች ዘርፎች
መካከል የዘረጉት የገቢ ግብር ምጣኔ ልዩነት እስከ 17% ይደርሳል፡፡

የሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪ ነባራዊ ሁኔታ እና የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ


የሚያስገነዝበን አሁን ያለውን የገቢ ግብር ምጣኔ ማስተካከል የሚቻልበትን አሰራር
ማጤን እንደሚያስፈልግ ነው፡፡ አንደኛ ከአምራች ዘርፍ የሚሰበሰበው ግብር በንፅፅር
አነስተኛ በመሆኑ በመንግስት የግብር ገቢ ላይ የሚያስከትለው ጉዳት አነስተኛ ሊሆን
እንደሚችል መገመት ይቻላል፡፡ሁለተኛ የአምራች ኢንዱስትሪውን የገቢ ግብር ምጣኔ
ዝቅ በማድረግ በአንጻሩ ትርፋማ የሆነውን የአገልግሎት፣ የሪል እስቴት እና ንግድ
ዘርፍ የገቢ ግብር በመጨመር የመንግስት የግብር ገቢ ማካካስ ይቻላል፡፡ ሶስተኛ
ለኢንዱስትሪ ዘርፍ የገቢ ግብር ምጣኔ ዝቅ ማድረግ እና የሌሎች ዘርፎችን የገቢ ግብር
ምጣኔ ባለበት መተው ይቻላል፡፡ በዚህ እሳቤ ለጊዜው የመንግስት ገቢ መቀነስ
አዝማሚያ ሊታይበት ቢችልም ዘርፉ በዘላቂነት በሚፈጥረው የስራ እድል፣ የውጭ
ምንዛሬ ግኝት፣ ኢንቨስትመንት ወዘተ ፋይዳው ከፍተኛ እንደሚሆን ታሳቢ ማድረግ
ያሻል፡፡

የእርጅና ተቀናሽ ወጪዎች


ከገቢ ግብር ጋር በተያያዘ አምራች ኢንዱስትሪን ለማበረታታት የሚያግዝ የፓሊሲ
መሳሪያ የእርጅና ወጪዎች ከገቢ ተቀናሽ የማድረግ ስልት መቀየስ ነው፡፡ የእርጅና
ተቀናሽ ስልት ወጭ እንዲጨምር በማድረግ አምራች ኢንዱስትሪው የሚከፍለውን
ግብር ዝቅ እንዲል ያግዘዋል፡፡ ስለሆነም የእርጅና ወጭ ተቀናሽ ለዘርፉ ተስማሚ
አድርጎ ማዘጋጀት የባለሀብቱን ኢንቨስትመንት የማስፋፋት ፍላጎት ያሳድጋል፣
የፋይናንስ ችግሩን ለመቀነስ ያግዘዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 84


የሀገራችን የገቢ ግብር ህግ የእርጅና ወጪዎች ከገቢ ግብር ተቀናሽ ማድረጊያ ዘዴ
ያለው ሲሆን ለሁሉም ዘርፎች አንድ አይነት ሆኖ የተዘረጋ አሰራር ነው፡፡ ይህ አሰራር
የአምራች ኢንዱስትሪን ባህሪ እና ሚና ግምት ውስጥ ያስገባ አይመስልም፡፡ በሀገራችን
ያለው ከገቢ ግብር የእርጅና ተቀናሽ የሚደረገው ቀጥተኛ መስመር ዘዴ (straight line
method) እና በፑሊንግ ዘዴ (pooling system) ነው፡፡ከገቢ ግብር የእርጅና ተቀናሽ
ለህንፃ ግንባታዎች 5% እና ለማይዳሰሱ ንብረቶች 10% በቀጥታ መስመር ዘዴ
ይሰላል፡፡ የማምረቻ መሳሪያ እና ሌሎች ንብረቶች በፑሊንግ ዘዴ ይሰላል፡፡ በዚህ
መሰረት ለኮምፒተር እና መረጃ ስርአት 25% እና ሌሎች የማምረቻ መሳሪያዎች 20%
በመጀመሪያው አመት የእርጅና ተቀናሽ ከተደረገ በኋላ ቀሪው መጠን በተመሳሳይ
መቶኛ ለሚቀጥሉት አመታት ተቀናሽ ይሆናል፡፡ ይህ የእርጅና ተቀናሽ ስልት
የአምራች ኢንዱስትሪው የሚስተዋልበትን የሥራ ማስኬጃ ፋይናንስ ችግር የሚያባብስ
ይሆናል፡፡

በአንፃሩ የአንዳንድ ሀገራትን ልምድ ስንመለከት ለአምራች ኢንዱስትሪ የሚያቀርቡት


የካፒታል እቃዎች የእርጅና ተቀናሽ ስልት ከሀገራችን የተለየ ሆኖ እናገኛዋለን፡፡
ሀገራቱ ፈጣን የእርጅና ፈጣን ተቀናሽ (Accelerated depreciation) ስልት
በመጠቀማቸው አምራች ኢንዱስትሪው ከመነሻው የሚያስፈልገውን የስራ ማስኬጃ
ካፒታል ለማሟላት አሰራሩ በእጅጉ ተጠቃሚ እንዲሆን አስችሎታል፡፡ ለምሳሌ
በ1980ዎቹ ኮሪያ የፈጣን እርጅና ተቀናሽ በሀገር ውስጥ የተመረጡ የማምረቻ መሳሪያ
(ኢኩፕመንት) ለሚጠቀሙ ለተመረጡ ኢንዱስትሪዎች ተግብራለች፡፡ በመሆኑም
በሀገር ውስጥ የተመረቱ የማምረቻ መሳሪያዎች (ኢኩፕመንት) ለሚጠቀሙ የእርጅና
ተቀናሽ ፐርሰንት ለሌሎች ዘርፎች ከሚደረገው እስከ 4 እጥፍ ሊደረግ ይችላል፡፡
ማሌዥያ በበኩሏ ለተመረጡ ዘርፎች የፈጣን እርጅና ተቀናሽ ድጋፍ የምታደርገው
ሀገሪቱ ያስቀመጠችውን ቅድመ ሁኔታ አምራቾች ማሟላት ሲችሉ ነው፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ በኤክስፖርት ለሚሳተፉ አምራቾች 40% የካፒታል ንብረት (capital asset)
የእርጅና ተቀናሽ ድጋፍ ያገኛል፡፡ ፊሊፒንስ ለተመረጡ ኢንዱስትሪዎች የምታደርገው
ፈጣን እርጅና ድጋፍ ለሌሎች ዘርፎች ከሚቀርበው የእርጅና ተቀናሽ በሁለት እጥፍ
ይበልጣል፡፡ በመሆኑም የሀገራችን የእርጅና ተቀናሽ ማበረታቻ የአምራች
ኢንዱስትሪውን የስራ ማስኬጃ እጥረት ለመቅረፍ በሚያግዝ መልኩ እንደ አምራች
ኢንዱስትሪው ባህሪ ተጠንቶ ቢሻሻል ለውጥ ያመጣል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 85


የግብር ተቀናሽ ወጭዎች
በተጨማሪ የግብር ተቀናሽ ወጭዎችን (tax deductable) በመጠቀም የአምራች
ኢንዱስትሪ ዘርፍ በልዩ ሁኔታ ማበረታታት ይቻላል፡፡ እንደ ኢንዱስትሪው ንኡስ
ዘርፍ ባህሪ የሚለያይ ቢሆንም ለምርምርና ስርፀት፤ ለገበያ ማፈላለግ፣ ለደንበኛ
መሰተንግዶ፣ ለንግድ ድርድርና ውል፣ ለአለም አቀፍ ንግድ ትርኢት ተሳትፎ፣
ለኢንተርናሽናል ብራንድ ወይም ፓተንት ምዝገባ፣ የሰራተኛ ስልጠና እና የመሳሰሉትን
ሌሎች ወጪዎችን ከታክስ በተወሰነ መጠን ተቀናሽ እንዲሆኑ በማድረግ ባለሀብቱን
ማበረታታት ይቻላል፡፡የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ስናይ የግብር ተቀናሽ ወጭ ለየት
ባለመልክ በማቅረብ የአምራች ዘርፍ ለመደገፍ ይጠቀሙበታል፡፡ ስለዚህ የሀገራችንን
አምራች ኢንዱስትሪ አለማቀፍ ተወዳዳሪነትና ምርታማነት በዘላዊነት ለመገንባት
ስርአቱን መዘርጋት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ወጭዎችን
ከግብር በእጥፍ ተቀናሽ በማድረግ የአምራች ዘርፉን የበለጠ ለማበረታታት እና
ተወዳዳሪነቱን ለማጠናከር ብዙ ሀገራት ሲተገብሩት ይታያል፡፡ ለምሳሌ ማሌዥያ
በ1980ዎቹ ኤክስፖርት የሚያደርጉ አምራቾችን ለማበረታታት ስትል ከግብር በፊት
ከገቢ ላይ ወጭዎችን ተቀናሽ በማድረግ አምራቹ የሚከፍለው የግብር መጠን ዝቅ
እንዲል ተደርጓል፡፡ በዚህ መሰረት ማሌዥያ ለትራንስፖርት፣ በውጭ ሀገር ምርትን
ለማስተዋወቅ እና የኤክስፖርት ማርኬት ጥናት ለማድረግ የሚወጡ ወጭዎችን
አምራቹ ተቀናሽ እንዲያደርግ ይፈቀድለታል፡፡ በተመሳሳይ ፊሊፒንስ የኢንዱስትሪ
አስተዳደር ወጭዎችን ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው ዘርፎች ተቀናሽ እንዲያደርጉ ትፈቅድ
ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኤክስፖርት ለሚያደርጉ አምራቾች ከኤክስፖርት የሚገኝ
ገቢን ታሳቢ ያደረገ የተወሰነ እጅ እንደ ግብር ተቀናሽ ወጭ (tax deductable) ተደርጎ
እንዲሰላ ትፈቅድ ነበር፡፡ እንዲሁም የሀገር ውስጥ ግብአት ለተጠቀሙ ኤክስፖርተሮች
የተወሰነ እጅ ከግብር በፊት ተቀናሽ ወጭ ይደረግ ነበር፡፡ የሀገራችን ታክስ ህግ
ከሌሎች ሀገራት ልምድ አንፃር የአምራች ዘርፉ የበለጠ ለማበረታታት እና ዘርፉ
ተመራጭ የቢዝነስ መስክ ከማድረግ አንፃር የተቃኘ አይደለም፡፡

5.2.3 የኤክስፖርት ንግድ ማበረታቻዎች

የአምራች ዘርፍ ከሚቀርቡ ዋና ዋና ማበርታቻዎች አንዱ የኤክስፖርት ንግድ


ማበረታቻ ፓሊሲ ነው፡፡ የኤክስፖርት ንግድ ለማጠናከር የተቀመጡት ማበረታቻዎች
በዝርዝር በአዋጅ ተቀምጠዋል፡፡ ተጨማሪ እሴት መሰረት ያደረጉ ማበረታቻዎች፣

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 86


ለከፍተኛ ውጤት አስመዝጋቢ የሚሰጥ ማበረታቻ እና ለከፍተኛ ኤክሰፖርት የሚሰጥ
ማበረታቻ ወዘተ መጥቀስ ይቻላል፡፡ እነዚህ ማበረታቻዎች በአዋጅ ደረጃ ቢቀመጡም
የአተገባበር ችግር ጎልቶ ይታይባቸዋል፡፡ ለምሳሌ በየዓመቱ የተደረገ አጠቃላይ ሽያጭ፣
ለውጪ ገበያ የተላከው መጠንና ዕድገት እየተለየ የሚመዘገብበት፣ ዕሴት ጭማሪ
የሚለካበት የመረጃ አያያዝ ስርዓትና በዚህ መሰረት ማበረታቻ የሚቀርብበት አሰራር
ጉድለት እንዳለ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በሀገራችን ላኪዎችና
አምራቾች ወደ አዳዲስ ገበያ መዳረሻ ወይም የነፃ ንግድ ቀጠና እድልን ለማስፋፋት
ያለመ ኤክስፖርትን መሰረት ያደረገ ማበረታቻ አይስተዋልም፡፡ ስለዚህ ዘገምተኛ
የሆነውን የኤክሰፖርት ንግድ ዕድገት ለማሻሻል እንዲቻል ከሌሎች ሀገራት ልምድ
በመውስድ በቀላሉ ሊተገበር የሚያስችል አሰራር መዘርጋት ያስፈልጋል፡

5.2.4 የጉምሩክ ቀረጥ ነፃ አሰራርን

የጉምሩክ ቀረጥ ነጻ አሰራር ጋር ተያይዞ በአምራች ኢንዱስትሪው የሚነሱ መሰረታዊ


ችግሮች አሉ፡፡ አንደኛው የቀረጥ ነፃ መብት ተጠቃሚ ድርጅቶች መብታቸውን ለሌላ
ሲያዘዋውሩ ወይም ሲሸጡ የሚደረገው የክትትል እና ቁጥጥር ስርዓት ይመለከታል፡፡
በርካታ ፕሮጆክቶች የጉምሩክ ስነ-ስርዓት ሳይፈፀሙና የቀረጥ እዳቸውን ሳይከፍሉ
ወይም ሳያወራርዱ የሚያዛውሩና የሚሸጡ እንዳሉ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን
የተደረገው ጥናት ያመለክታል፡፡ ይህ በዋናነት በኮንስትራክሽን ግብዓት በተለይ
በብረታብረት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ዘንድ ጎልቶ የሚታይ ከመሆኑም በላይ በሀገር
ውስጥ በብረታብረት ማምረት ስራ የተሰማራው ባለሃብት በሙሉ አቅሙ እንዳይሰሩ
እና በገበያ እጦት ምክንያት ማምረት ያቆሙ ፋብሪካዎች እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
እንደዚህ አይነት ችግሮች በየወቅቱ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ ፈጣን የማስተካከያ
እርምጃ የሚጠይቅ ቢሆንም ለማስተካከል ዳተኝነት ይታያል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ የቀረበለትን ማበረታቻ ለታለመለት አላማ ያላዋለ አካል ተጠያቂ


ለማድረግ የሚያስች ስርአት ተግባራዊ ሆኖ አይታይም፡፡ በሌላ አገላለፅ ማበረታቻ
ወስደው የውል ግዴታውን ላልተወጣ ባለሀብት ማበረታቻውን እና ተያያዥ ኪሳራዎችን
እንዲከፍል ጥረት ሲደረግ አይስተዋልም፡፡ ስሆነም የተሰጣቸውን ማበረታቻ ወስደው
በስምምነታቸው መሰረት ግዴታቸውን ያልተወጡ አምራች ኢንዱስትሪዎች በርካታ
መሆናቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ለምሳሌ የገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 87


ፈቃድ ሰጭ መ/ቤቶችን የመንግስት ማበረታቻ ተጠቃሚ ሆነው ፈቃዳቸው
የተዘረዘረባቸውን ድርጅቶች ዝርዝር መረጃ በጠየቀው መሰረት ከኢንቨስትመንት
ኮሚሽን 7965 ድርጅቶችን፤ ማዕድን ሚኒስቴር 222 ድርጅቶችን እና የበጎ አድራጎት
ኤጀንሲ 284 ድርጅቶችን በአጠቃላይ 8471 ድርጅቶችን በተለያዩ ምክንያቶች ፈቃድ
መሰረዛቸውን አሳውቀዋል፡፡የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ፈቃዳቸውን ከሰረዘባቸው 7965
ድርጅቶች ውስጥ ከቀረጥ ነፃ መብት ተጠቃሚ መሆናቸውን ለመፈተሸ ከተወሰዱ 53
ድርጅቶች ናሙና 24 ድርጅቶች የነፃ መብት ተጠቃሚ መሆናቸውን አረጋግጧል፡፡
በዚህ ስሌት መሰረት 45.3% ወይም 3606 ድርጅቶች የመንግስት ቀረጥ ነፃ ማበረታቻ
ወስደው ፈቃዳቸው በኢንቨስትመንት ኮሚሽን የተሰረዘባቸው እንደሚሆኑ መገመት
ይቻላል፡፡ ከዚህ የምንረዳው የክትትል እና ቁጥጥር ተግባሩን ቀልጣፋና በቅንጅት
ባለመተግበሩ ማበረታቻው የታለመለትን አላማ አላሳካም፤የሀብት ብክነት አስከትሏል፡፡
በሌላ በኩል የቀረጥ ማበረታቻ ከማቅረብ ጎን ለጎን ማበረታቻው ለታለመለት ዓላማ
ሰለመዋሉ ጠንካራ ክትትል እና ቁጥጥር ማድረግ እንደሚያስፈልግ ያስገነዝበናል፡፡

ስኬታማ የሆኑ ሀገራትን ልምድ ስንመለከት ለምሳሌ በኮሪያ ለተመረጡ አምራች


ኢንዱስትሪዎች የሚገቡ የካፒታል እቃዎች (ጥሬ እቃንም እንደ ካፒታል እቃ
በመቆጠር) ከቀረጥ ነጻ ድጋፍ ይደረግ ነበር። በተመሳሳይ ማሌዥያ በሀገር ውስጥ
የማይመረቱ ከሆነ ጥሬ እቃ እና ማሽነሪ ከቀረጥ ነጻ እንዲያስገቡ ትፈቅድ ነበር፡፡
በሌላ በኩል በፊሊፒንስ ለተመረጡ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት ማምረቻነት
የሚውሉ ነገር ግን በሀገር ውስጥ የማይገኙ ማሽነሪዎች ከሆኑ ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ
ይፈቀዳል፤ በሌላ በኩል ፊሊፒንስ የኢንዱስትሪ ጥሬ እቃ ከቀረጥ ነፃ እንዳይገባ
ትከለክል ነበር፡፡

5.3 የፋይናንስና ብድር አቅርቦት

የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ መዋቅር ለማረጋገጥና በቀጣይነት የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት


ፋይናንስ አስፈላጊ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ የሀገራችን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ
በመጠንም ሆነ በጥራት እያደገ የመጣ በመሆኑ ከፍተኛ ካፒታል የሚጠይቁ
ኢንቨስትመንቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጧል፡፡ በሁለተኛው አምስት ዓመት
የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ከባንክና አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት ቁጠባ
እና ከቦንድና ኮንትራታዊ ቁጠባ ምንጮች በአጠቃላይ 1.9 ትሪሊዮን ብር

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 88


እንደሚሰበሰብ ታቅዷል፡፡ ከዚህ ውስጥ ባንኮችና አነስተኛ የገንዘብ ተቋማት በቁጠባና
ብድር ተመላሽ የሚሰበሰቡት ብር 1.8 ትሪሊዮን (93.7 በመቶ) ድርሻ ያለው ሲሆን፣
የኮንትራታዊ ቁጠባ የቦንድ ሽያጭን ጨምሮ ከሌሎች የፋይናንስ ምንጮች
የሚሰበሰበው ደግሞ 120 ቢሊዮን ብር (6.3 በመቶ) እንደሚሆን ዕቅዱ ያሳያል፡፡

ከበጀት ውጭ የፋይናንስ ድልድል በዘርፍ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ለኢኮኖሚ


ዘርፎች አጠቃላይ የብድር አቅርቦት 1.68 ትሪሊዮን ብር ዕቅድ የተያዘ ሲሆን
ለኢንዱስትሪ 1.0 ትሪሊዮን ብር (59.1 በመቶ) እንደሚውል ዕቅድ ተይዟል፡፡
የፋይናንስ ድልድሉ በተቋማዊ ባለቤት ሲታይ 1.04 ትሪሊዮን ብር (62.0 በመቶ)
የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት ፍላጎት ለማሟላት የሚውል ሲሆን 640.0 ቢሊዮን ብር
(38.0 በመቶ) ደግሞ በመንግስት የሚካሄዱ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ወጪ
ለመሸፈን እንደሚውል በዕቅድ ተይዟል፡፡ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ ከተደረገው የፋይናንስ
ድልድል ውስጥ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ
በዕቅዱ ዘመን በአጠቃላይ 502.8 ቢሊዮን ብር የተመደበለት ሲሆን ይህም ከ2007
መነሻ ግምት 30.1 ቢሊዮን ብር በዓመት በአማካይ የ41.4 በመቶ ዕድገት በማሳየት
በ2012 ዓ.ም 156.9 ቢሊዮን ብር እንደሚደርስ ዕቅዱ ያሳያል፡፡ በተጨማሪም ለሀገር
ውስጥ ብድር ይውላል ተብሎ ከተቀመጠው በ2008 ዓ.ም 64 በመቶ ለግሉ ዘርፍ ቀሪው
36 በመቶ ለመንግሰት ልማት ድርጅቶች እንደሚውል ተቀምጧል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ
ባንክ በዋናነት መንግስት ለመሠረተ ልማት የሚያውለውን የኢንቨስትመንት ብድርና
ለኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚፈለገውን የሥራ ማስኬጃ እንደሚያቀርብ ታሳቢ የተደረገ ሲሆን
ለግብርናና ለኢንዱስትሪ የሚውለው የረጅም እና የመካከለኛ ጊዜ ኢንቨስትመንት
ብድር በዋናነት በኢትዮጵያ ልማት ባንክ እንደሚቀርብ እና ለአገልግሎት ዘርፍ
የሚያስፈልገውን ብድር ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የግል ባንኮች እንደሚያቀርቡ
ታሳቢ ተደርጓል፡፡

5.3.1 የፋይናንስ ተቋማት የማበደር አቅምና የትኩረት አቅጣጫ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገራችን የፋይናንስ ተቋማት ዕድገት ፈጣን ሆኖ ቀጥሏል። ነገር


ግን አጠቃላይ የፋይናንስ አቅሙ የኢንዱስትሪውን ፍላጎት ሊያሟላ በሚችል ቁመና
ላይ አይደለም። የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ጨምሮ በድምሩ 18 የንግድ ባንኮች
በኢኮኖሚው ውስጥ ይንቀሳቀሳሉ። ያሰባሰቡት የገንዘብ መጠን በድምሩ ስንመለከት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 89


በ2ዐዐ1 ዓ.ም ብር 62.9 ቢሊዩን ነበር። ይህ አሀዝ በተከታታይ እያደገ በ2ዐዐ8 በጀት
ዓመት መጨረሻ የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ብቻ ብር 288.5 ቢሊዮን ጠቅላላ ገንዘብ
ሲያሰባስብ የባንኩ ጠቅላላ ሀብት 384 ቢሊዮን ደርሷል፡፡ በሀገራችን ከተሰበሰበው
ገንዘብ 67.1 በመቶ የመንግስት ባንኮች ያሰባሰቡት ሲሆን 32.9 በመቶ 16 የግል
ባንኮች የተሰበሰበ መሆኑ የብሄራዊ ባንክ መረጃ ያሳያል፡፡ ባጭሩ የሀገራችን የቁጠባ
ዓቅም በ2ዐዐ3 በጀት ዓመት ከጥቅል ሀገራዊ ምርቱ ከነበረበት 11 በመቶ
በመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን መጨረሻ ላይ 22.5 በመቶ ደርሷል። ይህ
የቁጠባ አቅም አሁንም ቢሆን ዝቅተኛ በሚባል ደረጃ እንደሚገኝ ሁለት ማሳያዎች
ማቅረብ ይቻላል፡፡ አንደኛው ከፍተኛ መጠን ያለው የቁጠባ መጠን ማህበረሰቡ ለታላቁ
የህዳሴ ግድብ ቦንድ የቆጠበው እና ለኮንደሚንየም ቁጠባ የተሰበሰበ በመሆኑ አሁንም
አስተማማኝ ደረጃ ላይ አለመድረሱን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለተኛ የሀገራችን የቁጠባ
አቅም እያደገ ቢመጣም አሁንም ዝቅተኛ የቁጠባ መጠን ካላቸው ከፊል የሰሃራ አፍሪካ
ሀገራት ያነሰ መሆኑ ነው፡፡

በብድር አቅርቦት በኩል ሲታይ ሁሉም ባንኮች እስከ 2ዐዐ7 ግማሽ በጀት ዓመት
በድምሩ ከብር 166.3 ቢሊዮን በላይ አሰራጭተዋል፡፡ ይሁንና ለአምራች ኢንዱስትሪው
የተሰጠው የብድር አቅርቦት የስራ ማስኬጃ ካፒታልን ጨምሮ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን
በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ይገልፃሉ፡፡ በዚህ ጥናት የተዳሰሱት 88 ናሙና አምራች
ኢንዱስትሪዎች መካከል 35 ኢንዱስትሪዎች ለስራ ማስኬጃ ከንግድ ባንኮች (በተለይ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)፣ 22 ኢንዱስትሪዎች ከራሳቸው የውስጥ ገቢ፣ 11
ኢንዱስትሪዎች አራጣን ጨምሮ ከሌሎች መደበኛ ካልሆኑ የብድር አማራጮች
መጠቀማቸውን ገልፀዋል፡፡ ይህ ደግሞ ከላይ የተጠቀሰውን ሀሳብ የሚያጠናክር ነው፡፡

በዚህ ጥናት የተዳሰሱት አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ የተለያዩ የንግዱ ማሕበረሰብ


አደረጃጀቶች እና የመንግስት አስፈፃሚ አካላት የብድር አቅርቦቱ በቂ እንዳልሆነ
ይስማማሉ። ፈጣን የምጣኔ ሀብት እድገት በተለይ የኢንዱስትሪ ልማት ካሳኩ ሀገራት
ተሞክሮ ሲታይ የፋይናንስ ዕጥረት እንደሚያጋጥም ቀድሞ ይታወቃል። እነዚህ ሀገሮች
ፈጣን የኢንዱስትሪ ልማትና አጠቃላይ የምጣኔ ሀብት ዕድገት ያስመዘገቡት አሁን እኛ
የገጠመንን የፋይናንስ ዕጥረት ተቋቁመው አልፈው መሆኑ ግልፅ ነው። ሀገራቱ ፈጣን
የኢንዱስትሪ ልማት ያስመዘገቡት መጀመሪያ በተጠናና በተመረጠ ጠንካራ የመንግስት
ቀጥታ ኢንቨስትመንት በማካሄድ መሆኑ ይታወቃል። በእነዚህ ሀገራት ውስጥ የግል

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 90


ኢንቨስትመንቱ የተደላደለ ሜዳ የተፈጠረለት በመንግስት ቀጥታ ኢንቨስትመንት
በተፈጠረ ዓቅምና ልምድ ነው። ያላቸውን ትንሽ ካፒታል ለኢኮኖሚው ፈጣን ዕድገት
በሚያመጡ ዘርፎች (አምራች ኢንዱስትሪ) ላይ በስፋት በመጠቀም ውጤታማ ሆነዋል።
በሀገራችን በዋናነት የብድር አገልግሎት የሚያቀርበውን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
ስንመለከት ከ1999 ዓ.ም እስከ 2004 ዓ.ም ለኢንቨስትመንት ካሰራጨው ጠቅላላ ብድር
ከፍተኛው ድርሻ ለአምራች ዘርፉ ቢውልም ዘርፉ እየፈለገው ካለው መጠን ጋር
ሲወዳደር ግን በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ ለግብርና እና ኢንዱስትሪ የሚውለው የረጅምና
መካከለኛ ጊዜ ኢንቨስትመንት በሁለተኛው የእድገት እና ትራንስፎርሜሽን እቅድ 154
ቢሊዮን 838 ሚሊዮን ለአምራች፣ 18 ቢሊዮን 618 ሚሊዮን ለግብርና በአጠቃላይ 173
ቢሊዮን 457 ሚሊዮን እንደሚያስፈልግ በየዓመቱ በአማካይ 34.7 ቢሊዮን መሆኑ ሲሆን
ይህም በዋናነት በኢትዮጵያ ልማት ባንክ እንደሚቀርብ ታቅዷል፡፡ ባለፉት አምስት
ዓመታት በልማት ባንክ ብድር ለመስጠት ከታቀደው ውስጥ በየዓመቱ የሚሰጠው
ከ50% በታች ሲሆን፣ ካፀደቀው ብድር ውስጥ ደግሞ በለፉት 11 ዓመታት በአማካይ
62% ብቻ ወደተጠቃሚ የለቀቀው፡፡ ለዚህም ዋና ምክንያት የብድር ፍላጎት ባለመኖሩ
ሳይሆን የባንኩ አሰራር እጅግ ውጣወረድ የበዛበትና በዘመራዊ ቴክኖሎጂ ያልተደገፈ፣
ወስብስብ እና ግልፅነት የጎደለው መሆኑን ተጠቃሚዎች ይገልፃሉ፡፡

ለካፒታል ኢንቨስትመንቱ ፋይናንስ ለማቅረብ የተቋቋመ ባንክ አንድ ብቻ መሆኑ


እንደችግር የሚታይ ከመሆኑ በተጨማሪ የተደራሽነት አቅሙም ኢንቨስትመንቱ
በሚፈልገው ስፋት በብቃት መመለስ ያልቻለና ሰፊ ውስንነት ያለው በመሆኑ የተወሰኑ
ዘርፎችን በመምረጥ የመደገፍ አቅጣጫ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 91


ግራፍ 5.1፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ 2004-2008 ያሰራጨው ብድር ድርሻ በመቶኛ
ምንጭ ፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ 1999 እና 2004 ሪፖርቶች

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከላይ እንደተቀመጠው ባለፉት አምስት ዓመታት 50-60


በመቶ የሚሆነው ብድር ለአምራች ዘርፍ የተሰጠ ሲሆን ግብርና በአማካይ 33 በመቶ
ድርሻ ወስዷል፡፡ ሀገር ውሰጥ የግሉ ባለሀብት ከፍተኛ ድርሻ የወሰደ ሲሆን የውጪ
ባለሀብት እና የመንግስት ልማት ድርጅቶች ከባንኩ ከፍተኛ ብድር ወስደዋል፡፡
ለምሳሌ በ2005 ዓ.ም 79 በመቶ በተለያዩ ዘርፍ የተሰማሩ የግሉ ዘርፍ (26 በመቶ
ለውጪ ባለሀብት) የተሰጠ ሲሆን ቀሪው 21 በመቶ ለመንግስት ልማት ድርጅቶችና
ማህበራት የተሰጠ ነው፡፡ በ2006 ዓ.ም 52 በመቶ ለሀገር ውስጥ የግል ዘርፍ፣ 28 የውጭ
ባለሀብት፣ 8 በመቶ ለመንግስትና 12 በመቶ ለማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የተሰጠ
ነው፡፡ በ2007 እና 2008 ዓ.ም የግሉ ዘርፍ የሚወስደው ብድር በተነፃፃሪ ከፍተኛ
ቢመስልም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ ተጠቀሚ የሆነው መንግስት እና የውጪ
ባለሀብቱ የሚወስደው ብድር ከፍተኛ መሆኑ ነው፡፡

ሌላው ለአነስተኛ እና መካከለኛ ተቋማት ያላቸው የዋስትና ማስያዣ (collateral) ግምት


ውስጥ ያስገባ የሊዝ ፋይናንስ በልማት ባንክ ተጀምሯል፡፡ ለዚህም በባንኩ ያለው
አደረጃጀት በም/ፕሬዝዳንት እንዲመራ መደረጉ በመልካም ጎኑ የሚነሳ ቢሆንም በዚህ
የብድር ስርዓት በ2008 ሊሰጥ ከታቀደው 4.6 ቢሊዮን ብር የተሰጠው 2,242,730.07
(0.05 በመቶ) ብቻ ነው፡፡ ለዚህ አፈፃፀም አናሳነት ዋናው ምክንያት የሊዝ ፋይናንስ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 92


ዘግይቶ በመጀመሩና የዝግጅት ወቅት መሆኑ የባንኩ ሀላፊዎች ይገልፃሉ፡፡ ሆኖም
የባንኩ በ2009 የ9 ወራት የሊዝ ፋይናንስ አፈፃፀም ስንመለከት ለባንኩ የቀረበለት
ብድር 6.98 ቢሊዮን ሲሆን፤ ተቀብሎ ያፀደቀው 2.5 (37 በመቶ) ቢሊዮን፤ በተጨባጭ
ለተጠቀሚዎች ያሰራጨው ደግሞ 330 ሚሊዮን ወይም ከቀረበለት ጥያቄ ውስጥ 4.7
በመቶ ብቻ በመሆኑ ከላይ በባንኩ ሀላፊዎች የቀረበው ምክንያት ብቻ ሳይሆን አሁንም
ሌሎች ሊፈቱ የሚገባቸው መሰረታዊ እንቅፋቶች እንዳሉ ስለሚያመላክት እንደገና
መፈተሸ ተገቢ ነው፡፡ በልማት ባንክ ባለፉት አምስት ዓመታት በአብዛኛው ለመስጠት
ከሚያቅደው ብድር ውስጥ በአብዛኛው በዓመቱ የሚሰጠው ከ50 በመቶ በታች ሲሆን
ለዚህም ዋና ምክንያት የብድር ፍላጎት ባለመኖሩ ሳይሆን የባንኩ አሰራር እጅግ
ውጣወረድ የበዛበት እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያልተደገፈ፣ ውስብስብ እና ግልፅነት
የጎደለው መሆኑን ተጠቃሚዎች ይገልፃሉ፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተለይ ከሀገሪቱ የልማት ስትራቴጂ
ቅድሚያ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች ውጭ ላሉት የኢንቨስትመንት መስኮች የብድር
አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ባንክ ነው፡፡ በአማራ ክልል ከሚገኙ የተሟላ መረጃ
የተመዘገበላቸው የአምራች ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ለመረዳት እንደሚቻለው
የንግድና አገልግሎት ኢንቨስትመንት ዘርፎች ከመደበኛ የንግድ ባንኮች የተሻለ ብድር
የማግኘት ዕድል አላቸው፡፡ በንግድና አገልግሎት ዘርፎች የተሰማሩ ፕሮጀክቶች
በብድር ለመሸፈን ካቀዱት የኢንቨስትመንት ካፒታል በድምሩ 56.92 በመቶ ያህል
ለማግኘት ችለዋል፡፡ በሆቴልና ቱሪዝም መስክ የተሰማሩም በአማካይ በኢንዱስትሪ
ከተሰማሩ ፕሮጀክቶች በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ሲሆኑ ብድር ለማግኘት ካቀዱት
ካፒታል 17.34% ያህል አሳክተዋል፡፡ በኢንዱስትሪ የተሰማሩ ፕሮጀክቶች በብድር
ለመሸፈን ካቀዱት የኢንቨስትመንት ካፒታል 10.01 ያህሉ ብቻ ነው።

የኢዮጵያ ንግድ ባንክ በአንደኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን የዕቅድ ዘመን (2003-


2007 በጀት ዓመታት) በድምሩ 136,742,000,000 ብር የሚደርስ ካፒታል ለተለያዩ
ሴክተሮች ብድር አቅርቧል፡፡ ከተሰራጨው ጠቅላላ ብድር የኢንዱስትሪው ዘርፍ
በድምር 44.22 በመቶ ያህሉ ሲጠቀም፣ 30.96 በመቶ ያህሉ ለግብርናው ዘርፍ
ተሰራጭቷል፡፡ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ትግበራ ተከትሎ መንግስት
ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን መሰረተ ልማት እና ባለሀብቱ ባልሸፈናቸው የኢንዱስትሪ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 93


መስኮች ላይ ባደረገው ቀጥተኛ የኢንቨስትመት ተሳትፎ ከ68 እስከ 78 በመቶ ያህል
የብድር ተጠቃሚ መንግስት መሆኑ የባንኩ መረጃ ያሳያል፡፡

ግራፍ 5.2 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የለቀቀው የብድር መጠን


(ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)

በተለይ ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ የመንግስት ድርሻ በእጅጉ እየጨመረ የመጣ ሲሆን
በአጠቃላይ ከአንደኛው የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ጊዜ ጀምሮ የተለቀቁት አዳዲስ
ብድሮች የግሉ ዘርፍ (በተለይ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት) ድርሻ በእጅጉ ቀንሷል፡፡
ስለዚህ በሀገራችን የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ አቅርቦት ከመገደቡም በላይ የግሉ ዘርፍ
በአምራች ዘርፍ የሞተርነት ሚናው እንዳይጫወት አድርጎታል፡፡ የሌላ ሀገር ልምድ
ብንወስድ ለምሳሌ ደቡብ ኮሪያ እ.አ.አ 1960-1980ዎች በሀገሪቱ ከሚሰጠው ብድር
ውስጥ ከ40 እስከ 60 በመቶ የሚሆነው ለተመረጡ የግሉ ሴክተሮች ይሰጥ እንደነበር
መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአምራች ኢንዱስትሪም ሆነ በግብርና ዘርፍ


በተቀመጠው አሰራር መሰረት አዋጭ ፕሮጀክቶች አቅርቦ በብድር አቅርቦት ችግር
ምክንያት የቆመ አንድም የግል ባለሀብት ፕሮጀክት እንደሌለ ይገልፃል፡፡ ነገር ግን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 94


ባንኩ የግል ባለሀብቶች በምን ምክንያት ብደር ለመውሰድ እንዳልቻሉ ምክንያቶችን
በዝርዝር ማወቅና የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

ሰንጠረዥ 5.1 የኢንቨስትመንት መስኮች ተነፃፃሪ የካፒታል ዓቅም


2004 2005 2006 ድምር ኣማካይ
የኢንቨስትመንት ካፒታል ካፒታል ካፒታል ካፒታል ካፒታል
መስክ ቁጥር ሚ.ብር ቁጥር ሚ.ብር ቁጥር ሚ.ብር ቁጥር ሚ.ብር ሚ.ብር
አምራች 18 146.1 24 1370.5 38 516.80 80 2033.4 25.42
ግብርና ልማት 6 16.40 0 0.00 13 70.10 19 86.5 4.55
ሪል-እስቴትና
ተያያዥ ቢዝነስ 32 223.20 17 89.00 36.00 2,135.30 85 2447.5 28.79
ሆቴለ 0 0 2 3.10 6 44.10 8 47.2 5.90
ትምህርትና ጤና 2 6.6 4 8.50 3.00 25.60 9 40.7 4.52
ኮንስትራክሽን 4 244.2 3 21.60 58.00 2811.20 65 3077 47.34
ጅምላና ችርቻሮ 1 0.10 0 0.00 1.00 10.90 2 11 5.50
ትራንስፖርት
መጋዘን፣ኮሚኒኬሽን 5 11.2 3 5.20 4.00 12.10 12 28.5 2.38
ማዕድን ልማት 0 0 0 0.00 1.00 11.00 1 11 11.00
ሌላ ማሕበራዊ
አገልግሎቶች 0 0 2 13.80 3 9.10 5 22.9 4.58
ድምር 68 647.8 55 1511.7 163 5646.2 286 7805.7 27.29
መረጃ ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መረጃ እንደሚያሳየው ከአጠቃላይ የሀገሪቱ የፋይናንስ


አቅርቦት ኮንስትራክሽንና ሪል-እስቴት ዘርፎች ከማንም በላይ ተጠቃሚ መሆናቸው
ነው፡፡ባለፉት ሶስት ዓመታት ወደ ትግበራ ከተሸጋገሩ ፕሮጀክቶች በኮንስትራክሽን
ዘርፍ የተሰማሩት አማካይ የፕሮጀክት ካፒታላቸው ብር 47.34 ሚሊዮን ፣ በሪል
እስቴት ልማት የተሰማሩ ብር 28.79 ሚሊዮን ሲሆን በአምራች ዘርፍ የተሰማሩት
ከኮንስትራክሽንንና ሪል እስቴት በታች በአማካይ 25.42 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ስለዚህ
የፋይናንስ አቅርቦቱና ፍሰቱ ከአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ይልቅ ወደ ኮንስትራክሽንና
ሪል-እስቴት ዘርፎች እየተሸጋገረ መሆኑን መመልከት ይቻላል፡፡

ለኢኮኖሚው ፈጣን ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተለይቶ የተቀመጠው


አምራች ኢንዱስትሪው እንደዘርፉ ውስብስብነት የተለየ ትኩረት ካልተሰጠው

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 95


ባለሀብቶችን ወደ ዘርፉ ማምጣት አይቻልም። እስካሁን ያለው ተግባራዊ እንቅስቃሴ
እንደሚያሳየው የንግድ ባንኮች በተለምዶ ከአምራች ኢንዱስትሪ ይልቅ ለንግድ እና
ለኮንስትራክሽን ዘርፎች የተሻለ አገልግሎት እንደሚሰጡ አያጠያይቅም።

5.3.2 የስራ ማስኬጃ ካፒታል (working capital) አቅርቦት

በዚህ ጥናት ውስጥ ሌላው ዋና ችግር ሆኖ የተለየው ለአምራች ዘርፉ ተብሎ የተለየ
የስራ ማስኬጃ (working capital) ብደር አቅርቦት ያልተመደበ መሆኑ ነው። ለካፒታል
ኢንቨስትመንቱ በጥቂቱም ቢሆን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አገልግሎት እየሰጠ ነው።
በፈጣን የኢንዱስትሪ ልማት ስኬታቸው የሚታወቁ የምስራቅ ኤስያ ሀገራት
በኢንዱስትሪ ስኬት ያስመዘገቡት ከፍተኛ የፋይናንስ ዕጥረት ተግዳሮት ውስጥ ሆነው
የተገኘውን ካፒታል በአግባቡ በመጠቀም መሆኑ ለማንም ግልጽ ነው። የአምራች
ኢንዱስትሪው ከፋይናንስ አቅርቦት አኳያ አንዱ የስራ ማስኬጃ (working capital)
በመሆኑ በኢንቨስትመንት በኩል ያለ የፋይናንስ ፍላጐት ቢፈታ እንኳ የተቋቋመው
ኢንዱስትሪ ካላመረተና ምርቱን ገበያ ላይ ካላቀረበ የኢንቨስትመንት ወጪውም ኪሳራ
ይሆናል። ካፒታል ፕሮጀክቱ ተጠናቆ የስራ ማስኬጃ ፋይናንስ ባለማግኘታቸው
ምክንያት ምርት ሳያመርቱ እስከ አንድ ዓመት የቆሙ ኢንዱስትሪዎች እንዳሉ
ከባለቤቶቹና አምራች ዘርፍ ማህበራት ጋር በተካሄዱ ውይይቶች ለመረዳት ተችሏል።

እንደ ኢንቨስትመንት ፋይናንስ ሁሉ የመስሪያ ፋይናንስ አቅርቦትም የሀገር ውስጥ እና


የውጭ ባለሀብት እኩል የሚስተናገድበት ሁኔታ በመኖሩ የተገኘውን ያህል የመስሪያ
ብድር እንደ ኢንቨስትመንት ካፒታሉ የውጭ ባለሀብቱ በተሻለ እየተጠቀመበት መሆኑ
የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ይገልጻሉ፡፡ የውጭ ባለሀብቶች ከሀገራቸው ይዘውት የሚመጡ
ቋሚ ማሽነሪ የተጋነነ የግምት ዋጋ ስለሚያሰሩለት (Over Valued) ከንግድ ባንኮችም ሆነ
ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የተሻለ መጠን የመስሪያ ካፒታል ያገኛሉ፡፡

5.3.3 የብድር አቅርቦትና የአገልግሎት አሰጣጥ

ከላይ እንደተገለፀው የባንኩ ፋይናንስ አቅም ውስንነት እንደተጠበቀ ሆኖ ሌላው


መታየት የሚገባው ጉዳይ የባንኮች የብደር አገልግሎት አሰጣጥ ውስብስብ፣ የተንዛዛና
ውጣውረድ የበዛበት መሆኑ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአፈፃፀም ከሚወቀስባቸው

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 96


አንዱ ያልተሳለጠ የንብረት ግምት አሰራር ተጠቃሽ ነው፡፡ ባንኩ ለፋብሪካዎች የስራ
ማስኬጃ ፋይናንስ ለማበደር የፋብሪካው ካፒታል ዕቃዎች ለብድር አመላለስ መያዥ
ሲባል ዋጋቸው ትመና ላይ ይመሰረታል፡፡ የልማት ባንክ ባለሙያዎች በየጊዜው
የተለያየ ሰው እየተመላለሱ ከሁለት ዓመት በላይ የሚቆይበት ሁኔታ ይታያል፡፡ ባንኩ
ለግምት ዋጋ ዝግጅት የሚጠቀምበት ማሸነሪዎቹ የተገዙበት ደረሰኝ መነሻ አድርጎ
በመሆኑ ደረሰኝ የሌላቸው የፋብሪካ ባለቤቶች ብድር የማግኘት ዕድላቸው ጠባብ
ይሆናል፡፡ ባንኩ ቀደም ብሎ ለፋብሪካዎቹ ያበደረበት ሰነዶች በእጁ እያሉ እነኝህ
ሰነዶች ላይ ተመስርቶ ከመስራት ይልቅ በየጊዜው ደረሰኝ መጠየቅ ለተጓተተ አሰራር
እየዳረገው ነው የሚል ቅሬታ እየቀረበበት ነው፡፡ በእንዲህ ዓይነት ምክንያት የሀዋሳ
ጨርቃ ጨርቅ ብድር ከጠየቀ ከሁለት ዓመታት በላይ ቢሆነውም መልስ አላገኘም፡፡
የአንድ ጊዜ የብድር ጥያቄ ለማስተናገድ የባንኩ ሰራተኞች በርካታ ጊዜ ፋብሪካውን
የሚጎበኙ ሲሆን በየጊዜው የሚመጡ ሰራተኞች የተለያዩ በመሆናቸው የሚጠይቁት
መረጃም በዚያው ልክ ይለያያል፡፡ ፋብሪካው ቀደም ሲል ከባንኩ ብድር ለመውሰድ
የንብረት ግምት (valuation) አሰርቶ የሰጠ ሲሆን ሰነዱ በልማት ባንከ እያለ ይህን
ሰነድ በመነሻነት መጠቀም እየተቻለ፣ ወይም ፋብሪካው በግል የሙያ ተቋም ዝርዝር
ግምት አሰርቶ ለባንኩ አቅርቦ እያለ ባንኩ ግን ከ30 ዓመት በፊት ማሽነሪዎቹ
የተገዙበት ደረሰኝ እንዲቀርብለት ይጠይቃል፡፡

በሌላ በኩል በየዓመቱ ለብድር የሚመደበው ካፒታል የአቅርቦት አፈፃፀሙ ዝቅተኛ


መሆኑን የባንኩ አመራሮች ይገልፃሉ፡፡ ለምሳሌ በ2006 በጀት ዓመት ለማበደር
ካቀደው መጠን ከ50 በመቶ የማይበልጥ ብቻ ማበደሩ ከባንኩ በተደረገው ቃለ-መጠይቅ
ተገልጿል፡፡ በዚህ ሂሳብ ባንኩ የካፒታል ዕጥረት እንደሌለበት ይልቁንስ ተበዳሪ
አለመገኘቱን ይገልፃል፡፡ ነገር ግን የዚህ ዋነኛ ምክንያት በኢኮኖሚው ትኩረት
አግኝተው ባንኩ እንዲደግፋቸው የተለዩ የኢንቨስትመንት መስኮች እና የባለሀብቱ
የኢንቨስትመንት መስክ ምርጫ ያለመጣጣም በአንድ በኩል፤ በሌላ በኩል ደግሞ የሀገር
ውስጥ ባለሀብቱ በኢኮኖሚው ትኩረት በተሰጣቸው ከፍተኛ ፋይናንስ የሚጠይቁ
ፕሮጀክቶች ለመሰማራት ሲፈልግ የባለሀብቱ የካፒታል አስተዋጽኦ ዓቅም ፈታኝ
እንደሆነበት በባንኩ ይገለፃል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 97


5.3.4 የ25/75 የብድር ፖሊሲ አተገባበር

በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የባለሀብቱ መዋጮ ለአምራች ዘርፍ 25 በመቶ፣ ለአነስተኛ


እና መካከለኛ በተለይ ለሊዝ ፋይናንስ 20 በመቶ እንዲሆን የተደረገው አዲስ ማሻሻያ
መልካም ጅማሮ ቢሆንም የሀገራችን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በአምራች ዘርፍ
ያለው ተሳትፎ እንዲጠናከር እና በኢንዱስትሪ ስትራቴጂው በተቀመጠው መሰረት
የግሉ ዘርፍ የሞተርነት ሚናውን እንዲወጣ ከማስቻል አንፃር ማሻሻያው በቂ አለመሆኑ
እና በአፈፃፀም ላይ ጉድለቶች ያሉበት ይመስላል፡፡ አንደኛው የተቀመጠው የሀገር
ውስጥ ባለሀብቱ መዋጮ ከላይ የተቀመጡት ሃሳቦች አንፃር አሁንም ከፍተኛ መሆኑ
ነው፡፡ ሁለተኛ የማስፋፊያ ብድርን በሚመለከት በማምረት ላይ ያሉ ቅድሚያ
የሚሰጣቸውን ፕሮጀክቶች ለማስፋፋት የሚሹ ባለሀብቶች ፕሮጅቶቻቸው በሌላ ብድር
ዋስትና ያልተያዘና አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ሀብት ግምት የፕሮጀክቱን ወጭ 40%
የሚሸፍን ከሆነ የማስፋፊያውን ወጭ 100% ባንኩ ፋይናንስ ሊያደርገው እንደሚችል
አስቀምጠዋል፡፡ ይህም የባንኩን ብድርና የተበዳሪውን 60፡40 እንዲሚያደርግ
የተቀመጠ ቢሆንም ባለሀብቱ የተበደረው ብድር በተገቢው መልሶ ካጠናቀቀ በኋላ
ለማስፋፊያ የሚጠይቀው ብድር የሚጠየቀው መዋጮ (40 በመቶ) ከፍተኛ መሆኑ
ነው፡፡ ሌላው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የብድር ወለድ መጠን 12 በመቶ እንዲሆን
መደረጉ የሀገራችን አምራች ዘርፍ ሁኔታ ያላገናዘበና እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ነው፡፡
ምንም እንኳ ባንኩ በተለየ ሁኔታ ከ80 በመቶ በላይ ምርታቸው ወደ ውጪ የሚልኩ
ከቦንድ ሽያጭ ወለድ 3 በመቶ (9 በመቶ)፣ 60-80 በመቶ ምርታቸው ወደውጪ
የሚልኩ ተጨማሪ 3.5 በመቶ (9.5 በመቶ) እንዲሁም የተመረጡ የውጪ ምርት
የሚተኩ እና በአሽሙር ንግድ የተቋቋሙና ከ40-60 በመቶ ምርታቸው ወደ ውጪ
ለሚልኩ በተመሳሳይ ከቦንድ ወለድ መጠን ላይ 3.5 በመቶ ተጨምሮ ማለትም 9.5
በመቶ ወለድ እንዲከፍሉ የተደረገ ቢሆንም፤ ይህም በራሱ በአምራች ዘርፍ ፈጣን
እድገት ካሳዩት የምስራቅ ኤስያ ሀገራት ጋር ሲወዳደር እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ ከዚህ ጋር
ተያይዞ ያለው ሌላው የአተገባበር ችግር አምራቾች 12 በመቶ ወለድ ሲከፍሉ ከቆዩ
በኋላ ምርታቸው ወደ ውጪ ሲልኩ በዓመቱ መጨረሻ የላኩትን ምርት መጠን ካቀረቡ
በኋላ ተቀናሹ እንደሚመለስላቸው አሰራሩ የሚፈቅድ ቢሆንም እንዴት እንደሚመለስ፣
መቸ እና በምን መልኩ እንደሆነ በግልፅ ያልተቀመጠና በተግባር ያልተጀመረ መሆኑን
ባለሀብቶች ይገልፃሉ፡፡ በአምራች ዘርፍ የተሳካላቸው የምስራቅ ኤስያ ሀገራት ተሞክሮ
እንደሚያሳየው የአምራች ዘርፍ በተለይ የኤክስፖርት ዘርፍ ማገዝ እንደሚያስፈልግ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 98


ያሳያል፡፡ ለምሳሌ በታይዋን በመጀመሪያዎቹ የእድገት ዘመን እ.አ.አ ከ1963-1973
የአምራች ዘርፍ የነበረው የብድር ወለድ 7.5 የነበረ ሲሆን ለሌሎች ዘርፎች የነበረው
አነስተኛ የወለድ መጠን 14 በመቶ ነበር፡፡ የታይዋን ኤክስፖርት ከገቢ ንግድ በላይ
በሆነባቸው 1990ዎች ጭምር ለአምራች ዘርፍ በተለይ ለኤክስፖርት የነበረው የብድር
ወለድ መጠን አነስተኛ ነው፡፡ በተመሳሳይ የደቡብ ኮሪያና ሲንጋፖር ለአምራች ዘርፍ
የሚሰጠው የብድር ወለድ ከሌሎች ዘርፎች አንፃር በእጅጉ ያነሰ መሆኑን መረጃዎች
ያሳያሉ፡፡ በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በዋናነት ከፍተኛውን ብድር
ለመንግሰት የልማት ተቋማት እንዲሰጥ እና ለግሉ ዘርፍ ደግሞ የስራ ማስኬጃ ብድር
ብቻ እንዲያቀርብ ተልዕኮ የተሰጠው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተነፃፃሪ ለሁሉም
ዘርፎች የብድር ወለዱ ከልማት ባንክ ያነሰ 9.5 በመቶ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ስለዚህ
ለአምራች ዘርፍ በዋናነት ፋይናንስ እንዲያቀርብ የተመደበው የልማት ባንክ ከቀረበው
የወለድ መጠን ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ መሆኑን
ያመላክታል፡፡

ሌላው ባለሀብቱ በቁስ፣ በግንባታ፣ በማሽነሪ እንዲሁም በመሬት ሊዝ ዋጋ ያወጣው ወጪ


እንዲታሰብለት መደረጉ መልካም ቢሆንም የተግባር አፈፃፀሙ ሲታይ ግን የዋጋ
ትመናው በተለይ ተሸከርካሪ፣ ማሽነሪ እና ሌሎች የባለሙያዎች ስነምግባር ችግር፣
አሰራሩ የቆዩ እቃዎች ዋጋ ደረሰኝ እንዲያቀርቡ የመጠየቅ እና ረጅም ጊዜ እና ውጣ
ውረድ የበዛበት መሆኑ ባለሀብቶች ይገልፃሉ፡፡

በናሙናነት ከተወሰዱ 88 አምራች ፋብሪካዎች 23 ፋብሪካዎች በአማካይ 26.14%


የኢንቨስትመንት ወጪ ፍላጐታቸው ከባንክ ብድር ያሟሉ ሲሆን 63 ፋብሪካዎች
በአማካይ 71.55% ያህሉ ከራሳቸው ሀብት እንዳሟሉ ገልፀዋል፡፡ 2 ፋብሪካዎች ደግሞ
በአማካይ 2.27% ያህል የኢንቨስትመንት ካፒታል ፍላጐታቸው ከሌላ አማራጭ
እንደተጠቀሙ ገልፀዋል፡፡ በአጭር አገላለፅ የናሙና ፋብሪካዎች መረጃ የሚያሳየው
በኢንቨስትመንት ካፒታል አቅርቦት በኩል የባንክ ድርሻ 26.14 በመቶ ብቻ ሲሆን
71.55 በመቶ ያህሉ ከባለሀብቱ ከራሱ የሚሸፈን መሆኑ ነው፡፡

ባንኩ ብድር ከለቀቀ በኋላ ብድሩ ለአምራች ዘርፍ እንደ መሆኑ መጠን ከሌሎች
ዘርፎች ወደምርት ለመግባት የሚወሰደው ጊዜ ይኖራል፡፡ ልማት ባንክ ብድር ከለቀቀ
በኋላ ለተበዳሪዎች የሚሰጠው ዋናው ብድር የማይከፈልበት ጊዜ (Grace Period) ላይ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 99


የሚከፈለው የአንድ ወይም ሁለት ዓመት ወለድ ባለሃብቶች በዝግ ሂሳብ
እንዲያስቀምጡ ያደርጋል፡፡ የባለሀብቶች መዋጮ ካስቀመጡት ገንዘብ መጠን ማለትም
25 በመቶ በተጨማሪ ይህን ወለድ በአንድ ጊዜ ገና ከመጀመሪያው እንዲከፍሉ ማድረግ
የባለሀብቶችን አቅም ያላገናዘበ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ዙሮ ዙሮ የተሻሻለው የመዋጮ ቅናሽ
መጠን ትርጉም አልባ (ቢያንስ 25% + 9.5% = 34.5%) ከማድረጉም በላይ ባላቸው
ከፍተኛ የስራ ማስኬጃ እጥረት ላይ ተጨማሪ ማነቆ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡

በሌላ በኩል የውጭ ባለሀብቶች በዋናነት ለውጭ ገበያ በሚያመርቱ የኢንቨስትመንት


ፕሮጀክቶች የሚሰማሩ በመሆናቸው፣ በኢንዱስትሪ መንደሮች ቅድሚያ ስለሚሰጣቸውና
ለፋብሪካ ሼድ መገንባት ስለማይጠበቅባቸው 5ዐ በመቶ መዋጮ በተለያዩ መልክ
(የውጪ ብድር፣ አሮጊ ማሽነሪዎች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በማስገመት ወዘተ)
የኢንቨስትመንት ብድር ለማግኘት ከሀገር ውስጥ ባለሀብቱ የተሻለ ዕድል አላቸው፡፡
ስለዚህ የልማት ባንክ የፋይናንስ አቅርቦት ግንባር ቀደም ተጠቃሚ የሀገር ውስጥ
ባለሀብቱ ሳይሆን የውጭ ባለሀብት ነው የሚለውን አስተያየት የበለጠ ያጎላዋል፡፡

5.3.5 የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት

የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ችግር በአምራች ኢንዱስትሪው በሙሉ አቅሙ እንዳይሰራ


ካደረጉት መሰረታዊ ችግሮች መካከል አንዱ ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሁሉም
የኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች ስራቸውን ለማከናወን የውጭ ምንዛሬ ያስፈልጋቸዋል።
ነገር ግን የምንጠቀመው የውጭ ምንዛሬ ከምናስገኘው መጠን በብዙ ዕጥፍ የላቀ
በመሆኑ ትኩረት የሚያሻው ጉዳይ ሆኗል፡፡ ከውጭ ምንዛሬ ከማስገኘት አኳያ ሲታይ
የግብርናው ሴክተር የተሻለ ሲሆን የኢንዱስትሪው ምርት ተከታዩን ደረጃ ይዞ ይገኛል።
በግብርናው በኩል የተሻለ ትርፍ በማምረት ለውጭ ገበያ በስፋት በማቅረብ በየጊዜው
እያደገ ያለው የሀገሪቱ ምጣኔ-ሀብትና ልማት የሚጠይቀውን የውጭ ምንዛሬ ከማስገኘት
አኳያ በሚፈለገው ደረጃ አልደረሰም፡፡ በሌላ በኩል የአገልግሎት ዘርፉ በዋናነት ለውጭ
ምንዛሬ ግኝት ያለው ፋይዳ ጎልቶ የሚታይ አይደለም። ስለዚህ ሀገራችን ወደ ውጭ
የምትልከው የሀገር ውስጥ ምርት ወደ ሀገራችን ከሚገባው ምርት ጋር ሲወዳደር በጣም
አነስተኛ በመሆኑ የንግድ ሚዛኑ በአሉታዊ መልኩ እየሰፋ በመሄድ ላይ ነው። የንግድ
ሚዛኑ በ1980 ዓ.ም ከነበረበት ብር -1.5 ቢሊዮን ልዩነቱ እየጨመረ መጥቶ በ2006
ዓ.ም ብር -199.7 ቢሊዮን ደርሷል። በሌላ በኩል የወጪ ንግድ ግኝት ከብር 773.6

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 100


ሚሊዮን ወደ ብር 62.084 ቢሊዮን ብቻ አድጓል። ከዚህ በተጨማሪ ወደሀገራችን
የሚገባው ሸቀጥ በዓይነትና በዋጋ የአንበሳውን ድርሻ የያዘ ሲሆን ለአምራች ኢንዱስትሪ
ግብአት የማይውል መሆኑ ይታያል። የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የንግድ ሚኒስቴር የ2006 ዓ.ም
መረጃ እንደሚያሳየው ከጠቅላላ 41,685 የንግድ ፍቃዶች 4,969 በላኪነት፣ ከ29,908
በላይ የንግድ ፈቃዶች ደግሞ በአስመጪነት ተሰማርተዋል። በአስመጪነት ከተመዘገቡ
የንግድ ፈቃዶች ውስጥ ለኢንዱስትሪው ግብአት የሚያቀርቡ አስመጪዎች ከ1,565
እና ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መለዋወጫ የሚያስመጡ ደግሞ ከ1,013 አይበልጡም።
9339 የንግድ ፈቃድ አላቂ የፍጆታ ዕቃዎች አስመጪ ናቸው።ሌላኛው መሰረታዊ
ችግር በሀገራችን በተለያዩ ዘርፍ የተሰማሩ የሀገር ውስጥ እና የውጪ ባለሀብቶች
ምርታቸው ወደ ውጪ ለመላክ ከፍተኛ ማበረታቻዎች በተለያየ መንገድ
የሚወስዱ/የሚሰጣቸው ቢሆንም ባለሀብቶች በገቡት ቃል መሰረት ምርታቸው ወደውጪ
የሚልኩት ግን እጅግ አነስተኛ በመሆናቸው ሊገኝ የታሰበው የውጪ ምንዛሬ እጅግ
አነስተኛ ሊሆን ችሏል፡፡ ይህ ተግባር በውጪ ባለሀብቶች የበለጠ ጎልቶ የሚታይ መሆኑ
ደግሞ የበለጠ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ከሀገራችን ወደ ውጪ የሚወጣ የውጪ ምንዛሬ
የሚደረገው ቁጥጥር የላላ መሆኑ የሀገራችን የውጪ ምንዛሬ ፍላጎት ለሟሟላት አዳጋች
ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ ነው፡፡

የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት


ባለፉት አስር አመታት የኢንዱስትሪው ኢንቨስትመንት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ
በመምጣቱ ምክንያት ለካፒታል ዕቃዎች ኢንቨስትመንት ግዥ የሚውል የውጭ ምንዛሬ
ፍላጎት በየጊዜው እየጨመረ ነው። በሌላ በኩል አብዛኛዎቹ አምራች ኢንዱስትሪዎች
(በተለይ አግሮ-ፕሮሰሲንግ) ግብአት በዋናነት ከሀገር ውስጥ በተለይ ከግብርናው
እንደሚያገኙ ታሳቢ ያደረገ ቢሆንም ከላይ እንደተጠቀሰው ግብርናው ከምግብ ፍጆታ
ያለፈ ሰፊ ትርፍ ማምረት የሚችልበት ደረጃ ባለመድረሱ ኢንዱስትሪዎቹ ግብአት
ከውጭ ለማስገባት ሌላ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ ያስፈልጋቸዋል። የግብርና ምርቶች
በቀጥታ ግብአት የሚጠቀሙ አምራቾች እንደገለፁት አሁንም ቢሆን በሀገር ውስጥ
የተወሰነ ግብአት ቢኖርም ጥራቱ አምራቾች በሚፈልጉት መልኩ እየተመረተ እና
እየቀረበ ባለመሆኑ ከውጭ ለማምጣት እየተገደዱ ነው። ሌሎች ፋብሪካዎችም ቢሆን
የሚጠቀሙት ጥሬ ዕቃ በሀገር ውስጥ ስለማይመረት ያለው አማራጭ በቀጥታም ሆነ
በተዘዋዋሪ ግብአቱን ከውጭ ለማምጣት የውጪ ምንዛሬ ያስፈልጋቸዋል።

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 101


በሀገራችን እየተካሄዱ የሚገኙት ከፍተኛ የኮንስትራክሽን ልማቶች ማለትም መንገድ፣
የኃይል ማመንጫ ግድቦች፣ የኃይል ማስተላለፊያና ማሰራጫ መስመሮች፣ የምድር
ባቡር መስመሮች ወዘተ አብዛኞቹ በውጭ ኮንትራክተሮችና አማካሪዎች ስለሚሰሩ
ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይጠቀማሉ። በፌደራል መንግስት ፋይናንስ የሚሰራ መንገድ
ብቻ እንኳን ስንመለከት በ1997 ዓ.ም ብር 2.85 ቢሊዮን የነበረ ሲሆን፣ በ2001 ዓ.ም
ወደ ብር 9.81 ቢሊዮን፣ በ2006 ዓ.ም ደግሞ ወደ ብር 29.7 ቢሊዮን ደርሷል
(የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 2003-2006)።

ግራፍ 5.3 የገቢ ሸቀጦች የዋጋ ድርሻ በመቶኛ (ፔትሮሊየምና ማዳበሪያን ሳይጨምር)
ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ 2006 ዓ.ም

ሌላው የውጭ ምንዛሬ በስፋት የሚጠቀሙት ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡት አዳዲስና


ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች እንዲሁም መለዋወጫቸው ናቸው። በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የንግድ
ሚኒስቴር መረጃ መሰረት በሀገራችን 211 ንግድ ፈቃዶች አዳዲስ ተሽከርካሪዎች፣ 3636
ንግድ ፈቃዶች ደግሞ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች፣ ከዚህ ጋር ተያይዞም 778 ንግድ ፈቃዶች

የተሽከርካሪዎች መለዋወጫዎች አስመጪዎች መሆናቸውን ያሳያል። ወደ ሀገሪቱ


የሚገባ የተሽከርካሪዎች ዋጋ አጠቃላይ የገቢ ሸቀጦች ዋጋ በ2001 በጀት ዓመት 6.87

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 102


በመቶ የነበረ ሲሆን በ2006 በጀት ዓመት ወደ 12.7 በመቶ ከፍ ብሏል። ስለዚህ
ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንደሚጠቀሙ መገንዘብ ይቻላል።

የውጭ ምንዛሬ አጠቃቀም


ሌላው ትኩረት የሚሻው ጉዳይ የውጭ ምንዛሬ በቁጠባና በአግባቡ የመጠቀም
ልምዳችን ዝቅተኛ መሆኑ ነው፡፡ ከውጭ የምናስገባቸው ብዙ ዕቃዎችና ሸቀጦች
በሀገራችን በጥቂቱም ቢሆን እየተመረቱ ነው፡፡ ነገር ግን በሀገር ውስጥ የሚመረቱ
ዕቃዎችንና ሸቀጦች የመጠቀም ፍላጎታችንና ልምዳችን በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ ለምሳሌ
በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሆነ መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ዘርፍ
ደረጃውን የጠበቀ የቤትና የቢሮ ዕቃዎች በሀገራችን እየተመረተ ይገኛል፡፡ በዚህ ዘርፍ
መልካም የሚባል ስምና ዝና ያተረፉ አምራቾች እንዳሉም ይታወቃል፡፡ ነገር ግን
በግሉ ዘርፍም ሆነ በመንግስት ግዥ የሀገር ውስጥ ምርት ከመጠቀምና የውጭ ምንዛሬን
ከማዳን አንፃር በታቀደ ሁኔታ እየተሰራበት አይደለም፡፡

በዚህ ጥናት ውስጥ የታየው ሌላው ጉዳይ የመንግስት የግዥ አካሄድ የውጭ ምንዛሬን
አላግባብ መጠቀም ነው፡፡ መንግስት ለተለያየ ልማት የሚውሉ ምርቶች ከውጭ
መግዛት የግድ መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም በአንድ በጀት ዓመት የሚገዛ ንብረት ከአንድ
ዓመት ፍጆታ በላይ የሚሆንበት ክስተት የተለመደ መሆኑ በፌደራል መስሪያ ቤቶች
ያወያየናቸው የዚህ ጥናት ተሳታፊዎች ገልፀዋል፡፡ ለዚህ ማሳያ ለቤቶች ልማት
ፕሮጀክት የሚገዙ እንደ አርማታ ብረት ያሉ ግብአቶች ናቸው፡፡ እንደዚህ ዓይነት
ግዥዎች ሲፈጸሙ ከአንድ ዓመት ፍጆታ በላይ የሆነውን ምርት አምራቹ ሊጠቀምበት
ይችል የነበረ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይይዛል፡፡

አብዛኛዎቹ አምራች ኢንዱስትሪዎች በግብአት ዕጥረት ምክንያት በአማካይ በ58%


የማምረት ዓቅማቸው ብቻ እያመረቱ ባሉበት ወቅት በንግዱ በኩል ወደ ሀገር ውስጥ
እየገቡ ያሉት ሸቀጣሸቀጦች በአብዛኛው ከኢንዱስትሪው ፍላጐት ውጭ የሆኑ የፍጆታ
ዕቃዎች ናቸው፡፡ ጥቂት የማይባሉ የፍጆታ ሸቀጦችም ቢሆኑ በሀገራችን ያሉት
ፋብሪካዎች ሊያመርቷቸው የሚችሏቸው ተመሳሳይ ምርቶች ናቸው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 103


የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ቅደምተከተል እና ትኩረት
የውጭ ምንዛሬ አቅማችን ለማጠናከርና የተገኘውንም በአግባቡ መጠቀም እንዲቻል
በቅደም ተከተል እንዲሰራ እንደመርህ ቢቀመጥም የተግባር አፈጻጸሙ ሲታይ ግን
ውስንነቶች አሉበት፡፡

አምራች ዘርፉ ተጠናክሮ እንዲወጣ የተገኘውን ያህል የውጭ ምንዛሬ ቅድሚያ


ለካፒታል ዕቃዎች መግዣና ለአምራቹ ለስራ ማስኬጃ እንዲሰጥ በኢንቨስትመንት
ማበረታቻ ማዕቀፍ ተቀምጧል፡፡ አመዳደቡ በተግባር ሲታይ ግን በአስመጪነት
የተሰማራ የንግዱ ማሕበረሰብና በአምራቹ የተሰማራ አኩል እየተስተናገዱ እንደሆነ
አምራቾች ይገልጻሉ፡፡ በዚህ ጥናት በቃለ-መጠይቅና በቡድን ውይይት የተሳተፉ
አምራቾችና የንግዱ ማሕበረሰብ አደረጃጀቶች እንደገለፁት የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት
ቢያንስ ስድስት ወር ጊዜ መጠበቅ የግድ ይላል፡፡ በመሆኑም በአዳዲስና ማስፋፊያ
ፕሮጀክቶች ለካፒታል ኢንቨስትመንትና በማምረት የሚገኙትም ለስራ ማስኬጃ የውጭ
ምንዛሬ ቅድሚያ ዕድል ባለማግኘታቸው ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን ገልፀዋል፡፡
ለምሳሌ በድሬድዋ ከተማ የሚገኝና በብረታብረት ስራ ላይ የተሰማራ አንድ አምራች
ኩባንያ 48,000 የአሜሪካን ዶላር ማሽነሪ ለመግዛት ከስድስት ወር በላይ ወረፋ ይዞ
እየጠበቀ ነበር፤ ሀዋሳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካም መለዋወጫ ለመግዛት የውጭ ምንዛሬ
ባለማግኘቱ በሕዳር ወር 2007 ዓ.ም ለሁለት ሳምንታት ስራ ለማቆም መገደዱን
አስረድቷል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች በግብአት አቅርቦት ዕጥረት ምክንያት በሙሉ


ዓቅማቸው ማምረት እንዳልቻሉ እና አዳዲስ ባለሀብቶች ዘርፉን እየተቀላቀሉ መሆኑ
እየታወቀ አምራቹና በአስመጪነት የተሰማራው ነጋዴ ለውጭ ምንዛሬ እኩል
ይሰለፋሉ፡፡ እኩል መሠለፋቸው ብቻ ሳይሆን አስመጪው ከአንድ በላይ የንግድ ፈቃድ
ስለሚኖረው ከአምራቹ ቀድሞ የውጭ ምንዛሬ የማግኘት ዕድል እንዳለው ይገለፃል፡፡
ስለዚህ አምራቾች ከመነሻው ለካፒታል ኢንቨስትመንት የሚሆን የውጭ ምንዛሬ በቀላሉ
ማግኘት እንደማይችሉ ሲገነዘቡ በዘርፉ ለመሰማራት ያላቸው ፍላጎት ይቀንሳል፡፡
አስመጪው የውጭ ምንዛሬ በተሻለ ሁኔታ ማግኘቱ አንድ ጉዳይ ሆኖ ነገር ግን ወደ
ሀገር የሚያስገባው ሸቀጥ ለኢንዱስትሪ ግብአት የማይውል እንዲሁም በገበያ ከለላው
ምክንያት በሀገር ውስጥ ገበያ የተሻለ ትርፍ የሚያስገኝለት ዓይነት መሆኑ ከብሔራዊ
ባንክና ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 104


ሌላው ጉዳይ የውጭ ምንዛሬ አሰራር ግልፅነት የጎደለውና ክፍተቶች ያሉበት መሆኑ
ነው፡፡ የንግድ ባንኮች ሆነ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ብድር ሲጠየቅም ሆነ የውጭ
ምንዛሬ መጠይቅ ሰነድ (Letter of Credit) ሲከፍት አመልካቹ ምንያህል ወረፋ እንዳለና
መቼ እንደሚደርሰው የሚያውቅበት ስልት እንደሌለ የንግዱ ማሕበረሰብ እና አምራቾች
ይገልፃሉ፡፡ ይህንን ግልፅነት የሌለውና የተወሳሰበ የባንኮች አሰራር ለሀገራዊ የኢኮኖሚ
ዕድገት የሚያበረክተውን የአምራች ኢንዱስትሪ ዕድገት የሚያቀጭጭና ለግለስቦች
ወይም ጥቂት ቡድኖች ከፍተኛ የሀብት ማካበቻ መሳሪያ እየሆነ መሆኑን የጥናቱ
ተሳታፊዎች ገልፀዋል፡፡

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቃለ-መጠይቅ የተደረጉ


ውይይቶች ለመረዳት የተቻለው የውጭ ምንዛሬ አመዳደብ ክፍተት በሴክቶሮች
መካከል ብቻ ሳይሆን በኢንዱስትሪው ሴክተር ውስጥም በስፋት እንዳለ ተጠቁሟል፡፡
በአጠቃላይ በመንግስት የልማት ድርጅቶም ሆነ በግሉ ዘርፍ የውጭ ምንዛሬ አመዳደቡ
የፕሮጀክቶችና የምርት ስራ አፈጻጸም መሰረት ያደረገ እንዳልሆነና የቅንጅት ጉድለት
እንደሚታይበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

5.4 የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦት

በብዙ ጥናቶች እንደተረጋገጠው ሀገራችን ኢትዮጵያ በግብርና፣ በእንስሳት ሀብት እና


በደን ልማት በአንፃራዊነት የተሻለችና ከፍተኛ የመወዳደር አቅም እንዳላት
ይታወቃል፡፡ ስለሆነም እነዚህ ሴክተሮች በሰፊው ማልማትና በተለይ ለአነስተኛ እና
መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ግብአት በበቂ ሁኔታ ማቅረብ ለኢንዱስትሪው ዕድገትና
ተወዳዳሪነት ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡ ለኢንዱስትሪ የሚሆኑ የግብርና ግብአቶችን
ተወዳዳሪ በሆነ ዋጋ፣ በጥራት እና ኢንዱስትሪዎቹ በሚፈልጉት መጠንና ጊዜ
አስተማማኝ አቅርቦት ከሌለ አምራች ኢንዱስትሪዎች በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ሊሆኑ
አይችሉም፡፡ ምክንያቱም የአነስተኛና መካከለኛ ወይም የቀላል ኢንዱስትሪዎች (light
manufacturing) አጠቃላይ ወጪ ሲታይ 70 በመቶ የሚሆነው ለጥሬ ዕቃ ግብአት
ስለሚውል ለግብአት አቅርቦት ትኩረት መስጠትና ጥቂት የዋጋ ልዩነት መፍጠር
በታዳጊ ሀገራት ያለውን ተነፃፃሪ ዝቅተኛ የጉልበት ዋጋ በአግባቡ ለመጠቀምና በዓለም
ገበያ የመወዳደር አቅማቸውንም በዛው ልክ እንዲሻሻል ያደርገዋል (የዓለም ባንክ፤
2012)፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 105


በ2006 ዓ.ም የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ሪፖርት መሰረት በአምራች ኢንዱስትሪ
የተሰማሩ ባለሀብቶች ማምረት ከሚችሉት አቅም በታች እንዲያመርቱ ካደረጓቸው
ምክንያቶች ዋነኛው የግብአት ችግር መሆኑን አስቀምጧል፡፡ በዚህ ጥናትም
የተሰበሰበው መረጃ ይህን የሚያጠናክር ነው፡፡ ጥናቱ መረጃ ከሰበሰበባቸው 71 የሀገር
ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች ውስጥ 60.5 በመቶ የሚሆኑት ከአቅም በታች
እንዲያመርቱ ካደረጓቸው ምክንያቶች ውስጥ የግብአት አቅርቦት ችግር መሆኑን
ገልፀዋል፡፡ በተለይም ችግሩ በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ፣ ቆዳና ቆዳ
ውጤቶች ኢንዱስትሪ እና የምግብና የመጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ጎልቶ
ታይቷል፡፡የግብርና ምርቶችን በማቀነባበር፣ በጨርቃጨርቅና ልብስ ስፌት፣ የእንጨት
ውጤቶችን በማምረት፣ በቆዳ ውጤቶች ማምረት እና በብረታ ብረት ስራ የተሰማሩ
አምራች ኢንዱስትሪዎች በግብአት ችግር ምክንያት የመወዳደር አቅማቸውን መጠቀም
አልቻሉም፡፡

በሀገራችን አብዛኞቹ ትኩረት የተሰጣቸው አምራች ኢንዱስትሪዎች (የጨርቃጨርቅ


ኢንዱስትሪዎች፣ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪዎች፣ የምግብና መጠጥ
ኢንዱስትሪዎች እና ሌሎችም ኢንዱስትሪዎች) በዋናነት የግብርናውን ምርት
በግብአትነት የሚጠቀሙ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ እነዚህ ኢንዱስትሪዎች ግብአት
የሚያገኙባቸውን አማራጮች ስንመለከት በመጀመሪያ አርሶአደሩ በአነስተኛ ማሳ
ከሚያመርተው ምርት፣ አርብቶአደሩና ከፊል አርብቶ አደሩ በተለምዶ ከሚያመርተው
የእንሰሳት እርባታ ውጤት (ቆዳና ሌጦ)፣ ከግብርና ሰፋፊ ኢንቨስትመንት እና ከውጭ
የሚገቡ ናቸው፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ሁሉም አማራጮች ያለውን የአምራች
ኢንዱስትሪ የግብአት ፍላጎት ከማሟላት አኳያ ሰፊ ክፍተት አለባቸው፡፡

በግብርናው በኩል ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራበት የቆየው በአርሶአደር እጅ የሚገኝ መሬት


ላይ የሚለማ ሰብል ምርታማነት ማሳደግ ነው፡፡ ትርፍ አምራች አርሶአደርና ከፊል
አርብቶአደር ትርፍ ምርቱ በጥሬ ገንዘብ መልክ እና በሌላ ኢንቨስትመንት እያከማቸ
እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ በዚህ ጥናት በተዳሰሱት የአራት ክልሎች ግብርና ቢሮዎችና
ግብርና ሚኒስቴር ጋር በተደረገው ውይይት ለመረዳት እንደተቻለው እንደሀገር
እየተመረተ ያለው የግብርና ምርት ከሀገራዊ የምግብ ፍጆታ ያልዘለለ መሆኑን ነው፡፡
ስለዚህ በአርሶአደሩ አነስተኛ ማሳ እየተካሄደ ያለው የሰብል ልማት በሀገሪቱ ለሚገኙ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 106


ጥቂት አምራች ኢንዱስትሪዎችን እንኳ የሚመግብ የግብአት አቅርቦት ዓቅም
አልፈጠረም፡፡

በተደጋጋሚ እንደሚገለፀው በሀገራችን ጥጥ፣ ቆዳና ለአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ


ግብአት የሚውሉ የግብርና ምርቶችን ለማምረት የሚያስችል ዕምቅ ሀብት ያለን
ቢሆንም በሚፈለገው ጥራት፣ መጠንና ዋጋ ለአምራች ኢንዱስትሪው ማቅረብ
አልተቻለም፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ መንግስት በቅርቡ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ
ግብዓቶች ልማት ድርጅት አቋቁሟል፡፡ ከድርጅቱ ዋና ዋና አላማዎች መካከል
ለመጥቀስ ያህል፡ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን አቅርቦት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ
ድርጅቶችን መገንባትና ማስተዳደር፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የኢንዱስትሪ
ግብአቶችን በማምረት ማቅረብ፣ የኢንዱስትሪ ግብአቶችን ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር
በመግዛት ማቅረብ እንዲሁም የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት እና ጥሬ ዕቃ በማቅረብ
ከተሰማሩ ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት ይገኙበታል፡፡ ይህ ተቋም በቅርቡ
የተቋቋመና በአደረጃጀት ላይ የሚገኝ ሲሆን የኢንዱስትሪ ግብአት ችግርን ለመፍታት
በሚያስችል ሁኔታ የተዋቀረ መሆኑን ከወዲሁ መገምገም አይቻልም፡፡ነገር ግን ድርጅቱ
መቋቋሙ አስፈላጊ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡

በዚህ ጥናት ውስጥ የኢንዱስትሪ ግብአትን በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ለይቶ ማየት


ይቻላል፡፡ እነርሱም አንደኛ ከሀገር ውስጥ በተለይ ከግብርና የሚገኙ የኢንዱስትሪ
ግብአቶች፣ ሁለተኛ ከውጭ ሀገር የሚገቡ ግብአቶች ናቸው፡፡

5.4.1 ለአምራች ኢንዱስትሪ ከግብርና የሚገኝ የግብአት አቅርቦት

በሀገራችን የግብርና ውጤቶች በተለይ ለአምራች ኢንዱስትሪው በበቂ አቅርቦት፣


በጥራትና ተወዳዳሪ በሆነ ዋጋ እየቀረበ አለመሆኑ በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ
ባለሀብቶቸ ይገልፃሉ፡፡ የግብርና ምርቶች ለአብዛኛዎቹ ቀላል ኢንዱስትሪዎች ዋነኛው
ግብአት ሆነው ያገለግላሉ፡፡ በመሆኑም በሀገራችን ቀላል አምራች ኢንዱስትሪዎችን
ማስፋፋትና ተወዳዳሪ ለማድረግ የግብርና ምርቶች በብዛትና በጥራት የሚመረቱበትና
ለገበያ የሚቀርቡበት ሁኔታ ማመቻቸት ትኩረት የሚያሻው ጉዳይ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 107


ሀ. የሰብል ምርቶች አቅርቦት ችግር

ከሰብል ምርቶች መካከል አንዱና ዋነኛው የሆነው ስንዴ በእስያ ሀገራት በአንድ ቶን ከ
200 USD እስከ 250 USD ሲሸጥ በሀገራችን ደግሞ ከ300 USD እስከ 350 USD
ይሸጣል (የአለም ባንክ 2012)፡፡ ይህ ደግሞ የስንዴን ምርት በዋናነት እንደ ግብአት
ለሚጠቀሙት ዱቄት ፋብሪካዎች ተወዳዳሪነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ፈጥሯል፡፡ የስንዴ
ግብአት 80 በመቶ የሚሆነው የዱቄት ዋጋ ስለሚሸፍን የዱቄቱ መሸጫ ዋጋ ላይ
ከፍተኛ ጭማሪ እንዲኖር ያደርጋል፡፡ በሀገራችን በአንድ ሄክታር ከአንድ ቶን ያነሰ
ስንዴ ሲመረት በቻይና እስከ 6 ቶን በቬትናም ደግሞ እስከ 4 ቶን ይመረታል (የአለም
ባንክ፣ 2012)፡፡ ይህ የሚያሳየው የሀገራችን የሰብል ምርታማነት ደረጃ ዝቅተኛ መሆኑን
ነው፡፡ በሀገራችን እየተመረተ ያለው ስንዴ በምርታማነት እና በጥራት መወዳደር
ካላስቻሉት ምክንያቶች ለመጥቀስ ያህል ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ ማምረት
ያለመቻል፣ ኋላቀር አስተራረስ መከተል፣ ከፍተኛ ምርት ሊሰጡ የሚችሉ ምርጥ ዘርና
ማዳበሪያ በስፋት መጠቀም ያለመቻል፣ የምርት አያያዝና አጠባበቅ ኋላቀር በመሆኑ፣
ቀልጣፋና አስተማማኝ ገበያ ያለመኖሩ በዋናነት ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡

በአርሶአደሩ ማሳ ላይ የሚካሄደው የሰብል ልማትና በተለይ የግብርና ኢንቨስትመንቱ


ሰፊ ምርት ማምረት ደረጃ አለመድረሱ በሰብል ምርቶች ከሀገራዊ የምግብና ተያያዥ
ፍጆታዎች የዘለለ ባለመሆኑ የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪዎች እንደሌሎች የአምራች
ዘርፎች በግብአት አቅርቦት ዕጥረት ምክንያት በዝቅተኛ የማምረት ዓቅማቸው
እንዲያመርቱ ተገደዋል፡፡ ለምሳሌ የዱቄት፣ ፖስታና ማካሮኒ ኢንዱስትሪዎች ተጠቃሽ
ናቸው፡፡ በሌላ በኩል የግብርና ምርቶች ለአምራች ኢንዱስትሪው ተወዳዳሪ በሆነ ዋጋ
አለመቅረቡ እና የተዛባ የገበያ ስርአት መፈጠሩ ነው፡፡ የገበያ ደላላዎች በሚፈጥሩት
አላስፈላጊ፣ ረጅምና እሴት የማይጨምር የግብይት ሰንሰለት ምክንያት የምርቶች ዋጋ
የተጋነነ እንዲሆን እና የገበያ ስርአቱ በውድድር እንዳይመራ እያደረገው ይገኛል፡፡

የግብርናው ዘርፍ ከሀገራዊ መሰረታዊ ፍጀታ እና የተወሰነ ለውጭ ገበያ (በዋናነት ቡና፣
ሰሊጥ፣ ቁም እንስሳት፣ ጥራጥሬ፣ ወዘተ) ከማምረት የዘለለ እያቆጠቆጠ ላለው የሀገሪቱ
አግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ በቂ ግብአት የማቅረብ ዓቅሙ ውሱን ከመሆኑ ባሻገር
የሀገራችን የገበያ ነባራዊ ሁኔታም የተሟላ ጤናማ ሂደት የማይታይበት እንደሆነ
ግብርና፣ ኢንዱስትሪ እና ንግድን የሚመሩ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አስፈጻሚ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 108


አካላትና የንግድና ዘርፍ ማሕበራት ይገልፃሉ፡፡ የግብርናው ምርት ወደ አምራች
ኢንዱስትሪው የሚደርሰው በቀጥታ ከአምራቹ እጅ ሳይሆን እጅግ ረጅም የድለላ
ሰንሰለት አልፎ ነው፡፡ በዚህ ጥናት ውይይት የተሳተፉ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ
ባለሙያዎች ቢሮው በ2ዐዐ6 ዓ.ም ባስጠናው ጥናት ላይ ተመስርተው እንደሚሉት
በተለይ የግብርና ምርቶች ከአምራቹ ወደ ኢንዱስትሪው እና ሸማቹ የሚደርሰው ብዙ
የድለላ ቅብብሎሽ ሰንሰለት አልፎ ነው፡፡ይህ ዓይነቱ ረጅም እሴት የማይጨምር
ቅብብሎሽ ውጤት የግብይቱ ፍጥነት መጓተት ብቻ አይደለም፤ ዋናው ችግሩ በአምራቹ
ላይ ምንም እሴት ሳይጨመርበት የዋጋ ንረት ማስከተሉ ነው፡፡

ከውጭ የሚገባው ስንዴ የገቢ ቀረጥ ተከፍሎበት እንኳ ከሀገር ውስጥ ከሚገዛው በዋጋ
የተሻለ አዋጭ መሆኑ አምራቾች ይናገራሉ፡፡ ለምሳሌ የዱቄት፡ ፓስታና ማኮሮኒ
አምራች ፋብሪካዎች መረጃ እንደሚያሳየው በሀገር ውስጥ አማካይ የስንዴ ዋጋ
በኩንታል ከብር 1200 በላይ ሲሆን ከኖርወይና ከአውስትራሊያ የሚገባ የስንዴ ዋጋ
የገቢ ቀረጥን ጨምሮ ከብር 900 በላይ አይደለም፡፡ ረጅምና እሴት የማይጨምር
የግብይት ሰንሰለት ግብይቱ በውድድር እንዳይመራ ስለሚያደርግ በዋጋ የሚታይ ችግር
በጥራትም ተመሳሳይ ተጽኖ እየፈጠረ መሆኑን አምራቾች ገልፀዋል፡፡ ምርቱ በታሰረ
ሰንሰለት በመያዙ አምራቹ አማራጭ እንዳይኖረውና የተሻለ ጥራት ያለው ግብአት
አወዳድሮ ማግኘት እንዳይችሉ ያደረጋቸው መሆኑን ይገልፃሉ።

የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት መንግስት የሰፋፊ እርሻዎች ልማት


(Commercial Agriculture) እንደ ሁለተኛ አማራጭ በመያዝ እንቅስቃሴ ከጀመረ
ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ ግብርና ኢንቨስትመንትና መሬት
አስተዳደር ኤጀንሲ መረጃ እንደሚያሳየው ከ1996 ዓ.ም እስከ 2ዐዐ5 ዓ.ም ለ5ዐ52
ባለሀብቶች በግብርና ኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ 21ዐ,213.88 ሄክታር መሬት
ተሰጧቸዋል፡፡ እስከ 2ዐዐ7 ግማሽ ዓመት የተሰጠ የመሬት ስፋት 2.45 ሚሊዮን
ሄክታር ቢደርስም ከተሰጠው መሬት እስካሁን የለማው ከ9ዐዐ,ዐዐዐ ሄክታር (37%)
የማይበልጥ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በግብርና ኢንቨስትመንቱ በ1ዐ ዓመታት ውስጥ ከ37% የማይበልጥ መሬት ማልማት


ዝቅተኛ ከመሆኑም በላይ በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች
ምርታማነታቸው ከአርሶ አደሩ በጣም ያነሰ መሆኑን ከግብርና ቢሮዎችና ሚኒስቴር

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 109


መ/ቤቱ ጋር በተደረጉ ውይይቶች የተሳተፉ ባለሙያዎችና አመራሮች ገልፀዋል፡፡
የግብርናው ኢንቨስትመንት በቴክኖሎጂ የአካባቢውን አርሶአደርና አርብቶአደር
ለመደገፍ አቅጣጫ ተቀምጦ በኢንቨስትመንት ውል እንዲካተት ቢደረግም ውጤታማ
እንዳልሆነ በየደረጃው የሚገኙ የሚመለከታቸው የመንግስት አስፈጻሚ አካላት
ይገልጻሉ፡፡ የግብርና ስራችን ትኩረት በአነስተኛ ማሳ የሚካሄድ የሰብል ልማት ብቻ
ከመሆኑ ባሻገር የግብርናው ኢንቨስትመንት በባለሀብቱ ውሳኔ የተመሰረተ ነው ማለት
ይቻላል፡፡ በዘርፉ ለሚሰማራ ባለሀብት የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት የሚሰጥበት
ዕድል አልተመቻቸም፡፡ በግብርና ኢንቨስትመንት ተሰማርተው ውጤታማ ያልሆኑ
ባለሀብቶች ላይ የሚወሰድ እርምጃ አጥጋቢ እንዳልሆነና ትልቁ እርምጃ
የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከመሰረዝ የዘለለ አለመሆኑን የውይይቱ ተሳታፊዎች
ገልፀዋል፡፡

ለ) የጥጥ አቅርቦት ችግር

የጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪ በመንግስት ትልቅ ትኩረት ከተሰጣቸው


ኢንዱስትሪዎች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ይሁን እንጂ በእስካሁኑ ሂደት ንዑስ ዘርፉ
በተፈለገው ደረጃ ያላደገ እና እንዲሁም ለኢኮኖሚው ዕድገት ያለው አስተዋጽኦ
ዝቅተኛ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ለዚህ ደግሞ እንደ ዋና ምክንያት የሚጠቀሰው ለንዑስ ዘርፉ
እድገት አስፈላጊ የሆነው ዋና የግብአት (ጥጥ) አቅርቦት በተፈለገው ጥራትና ዋጋ
ቀጣይነት ባለው መልኩ አለመቅረቡ በተለያዩ አካላት የተጠኑ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡

በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ከ100 በላይ የሚሆኑ መካከለኛና ከፍተኛ የጨርቃጨርቅና


አልባሳት ኢንዱስትሪዎች በስራ ላይ ይገኛሉ (ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ 2006 ዓ.ም)፡፡
በተጨማሪም በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መጀመሪያ ዓመታት 10
ተጨማሪ ኢንዱስትሪዎች ወደ ዘርፉ ይገባሉ ተብሎ ይታሰባል፡፡ በሌላ በኩል በአሁኑ
ወቅት ሀገራችን በሰፊው የኢንዱስትሪ ፓርኮች በመገንባት ለባለሀብቶች በኪራይ መልክ
የማስተላለፍ ስራ በማከናወን ላይ ሰለምትገኝ አቅም ያላቸውንና በአለም ላይ የታወቁ
ግዙፍ የጨርቃጨርቅ አምራች ኢንደስትሪዎችን በመሳብ ላይ ትገኛለች፡፡ በመሆኑም
የንዑስ ዘርፉ ፈጣን እድገትና መስፋፋት ተከትሎ ከፍተኛ የጥጥ ፍላጎት በመጨመር
ላይ ይገኛል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 110


በዚህ ጥናት የተሰበሰቡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ በመመረት
ላይ ያለው የጥጥ ምርት በብዛትም ይሁን በጥራት የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎችን
ፍላጎት በማሟላት ላይ አይደለም፡፡ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪዎች ልማት
ኢንስቲትዩት መረጃ እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ. በ2013/14 በሀገራችን በሰፋፊ እርሻዎች
በ60,000 ሄክታር መሬት የተመረተው የጥጥ ምርት 35,000 ቶን አካባቢ ብቻ ነው፡፡
ይህ አሀዝ ከዓመት በኋላ በ100,000 ሄክታር ላይ ወደ 60,000 ቶን ማድረስ ተችሏል፡፡
በሌላ በኩል በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ የጥጥ ፍላጎቱ ከ90,000 ቶን ወደ 100,000 ቶን
አድጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2015/16 በሰፋፊ እርሻዎች ብቻ 100,000 ቶን የጥጥ ምርት
ይመረታል ተብሎ ይጠበቃል (TIDI, 2016)።

ባለፉት ዓመታት እነዚህ ፋብሪካዎች ያጋጠማቸውን የጥጥ እጥረት ለመፍታት ከውጭ


የጥጥ ምርት ለማስገባት ተገደዋል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2014/15 ብቻ ወደ 45,000 ኩንታል
የሚጠጋ ጥጥ አዲስ በተቋቋመው በኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦት ድርጅት በኩል
ከውጭ እንዲገባ ተደርጓል (TIDI, 2016): እ.ኤ.አ. በ2013/14 ከውጭ የገባው የጥጥ
መጠን 6,000 ቶን ደርሶ ነበር (International Cotton Advisory Committee, 2014
cited in PSRC & EDRI, 2016)፡፡ በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ
አፈጻጸም ወቅት ሀገሪቱ ከጨርቃጨርቅ እና አልባሳት ልታገኝ ያቀደችውን የውጭ
ምንዛሬ ግኝት እንዳታሳካ ካደረጓት ምክንያቶች መካከል በጥጥ አቅርቦት ላይ የነበረው
የብዛት እና የጥራት ችግር እንዲሁም በእሴት ሰንሰለቱ የነበሩ የተለያዩ ክፍተቶች
እንደነበሩ በእቅድ አፈጻጸም ግምገማው በግልፅ ተቀምጧል፡፡ በቀጣዩ የእድገትና
ትራንስፎርሜሽን እቅድ ይህን ችግር ለመፍታት አሁን በአንድ ሄክታር ይመረት
የነበረውን 15 ኩንታል እ.ኤ.አ. በ2020 ወደ 28 ኩንታል ለማድረስ አቅዷል፡፡ ይሁን
እንጂ ትልቁ ችግር የምርታማነት ብቻ ሳይሆን ጥጥ አምራቾችን ሊያበረታታ
የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ባለመዘርጋቱ ነው፡፡

የጨርቃጨርቅ እና አልባሳት ልማት ኢንስቲትዩት መረጃ እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ


በ2009 ሀገሪቱ ባጋጠማት ከፍተኛ የሆነ የጥጥ እጥረት ምክንያት በ2010 የወጣው የጥጥ
ምርት ወደ ውጭ እንዳይላክ መታገዱ ጥጥ አምራቹን በከፍተኛ ሁኔታ እንዳዳከመው
ይገልፃል፡፡ ለዚህ ማሳያ እንዲሆን እ.ኤ.አ በ2011/12 በሀገሪቱ ከፋብሪካዎች ፍላጎት
በላይ 79,400 ቶን የጥጥ ምርት በመመረቱ ምክንያት 29,710 ቶን ጥጥ ገዢ በማጣቱ
(አማራጭ ገበያ በማጣቱ) ጥጥ አምራች አርሶአደር ወይም ባለሀብቱ በዝቅተኛ ዋጋ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 111


እንዲሸጥ ተገዷል፡፡ በዚህም ምክንያት ጥጥ አምራቹ ፊቱን አስተማማኝ ገበያ
ወዳላቸው ሌሎች የቅባት እና የቅመማ ቅመም እህሎች ለማዞር ተገዷል፡፡ በዚህም
ምክንያት ከጊዜ ወደ ጊዜ በጥጥ ምርት የሚሸፈን የመሬት መጠን እና እየተመረተ
ያለው የጥጥ መጠን እየቀነሰ መጥቷል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2012/13 በሀገራችን የታቀደውን
95,287 ቶን የጥጥ ፍላጎት በከፊል ለማሟላት በማሰብ 125,000 ሄክታር መሬትን በጥጥ
በመሸፈን 80,000 ቶን ጥጥ ለማምረት ቢታቀድም ማሳካት የተቻለው 81,000 ሄክታር
በማልማት 45,000 ቶን ጥጥ ብቻ ሆኗል፡፡ አሁን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት (2007
ዓ.ም) 219,451 ሄክታር በጥጥ ምርት ለመሸፈን ቢታቀድም ማልማት የተቻለው ሩብ
ያህሉን ብቻ ነው፡፡ በዚህም መሰብሰብ የተቻለው 35,000 ቶን ጥጥ ነው፡፡ ይህ ደግሞ
ለመሰብሰብ ከታቀደው 16 በመቶ ብቻ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ የሚያሳየው በሀገራችን
እየተመረተ ያለው የጥጥ ምርት በመጠኑም ሆነ በሚታረሰው የመሬት ስፋት ከጊዜ ወደ
ጊዜ እየቀነሰ መሆኑና ችግሩ እየተባባሰ መምጣቱን ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት መንግስት ወደ
ውጭ እንዳይላክ የተጣለውን እገዳ ያነሳ ቢሆንም የአቅርቦት ክፍተቱን መሙላት ግን
አልተቻለም፡፡ ጥጥ አምራቹንም ፊቱን ካዞረበት የካሽ ክሮፕ ምርት እንዲመልስ
ማድረግ አልተቻለም፡፡ ይህ በጥጥ ምርት ላይ የሚስተዋለው የዋጋና የምርት መጠን
ያለመረጋጋት ችግር በዋናነት ከሚታረሰው የመሬት ስፋት ጋር ይያያዛል፡፡ ችግሩም
ጎልቶ መታየት የጀመረው ከፍተኛ የሆነ ትርፍ ምርት ከተመረተበት እ.ኤ.አ.
ከ2011/12 ጀምሮ እንደሆነ ይገለፃል (TIDI, 2016)፡፡

በሀገራችን ከጥጥ ማምረት ጋር ተያይዞ ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች ብቻ ሳይሆን


የማዳበሪያና የፀረ-አረም አቅርቦት ችግሮችም ይጠቀሳሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በዘመናዊ
አስተራረስ ላይ ያለው ክፍተት፣ በተሻሻለ ዘር አጠቃቀም የሚስተዋለው ችግር፣ በዘርፉ
እየተካሄዱ ያሉ ምርምርና ጥናቶች ውስን መሆናቸው እና በዓለም ገበያ የምርቱ ዋጋ
መዋዠቅ በዘርፉ ካጋጠሙ ችግሮች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ሐ) የቆዳ እና ሌጦ አቅርቦት ችግር


ከእንስሳት ውጤቶች ጋር ተያይዞ ያለውን ሁኔታ ስናይ ደግሞ የእንስሳት ሀብት ልማት
በአገራችን ኢኮኖሚ እድገት ውስጥ እየተጫወተ ያለው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ለውጭ
ምንዛሬ ግኝትም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ ከእንስሳት ውጤቶች መካከል
ለኢንዱስትሪው እንደ ግብአት ከሚያገለግሉት ውስጥ ቆዳና ሌጦ በግንባር ቀደምትነት
መጥቀስ ይቻላል፡፡ በቀደሙት ዓመታት (እ.ኤ.አ. ከ2008 በፊት) አገራችን በየዓመቱ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 112


ከፍተኛ ቁጥር ያለው ቆዳና ሌጦ ለውጭ ገበያ ታቀርብ ነበር፡፡ በተለይም በዓለም ላይ
ተፈላጊ የሆኑ ጥራት ያለውን ቆዳ በጥሬውና በክፊል በማጠናቀቅ ወደ ተመረጡ
የአውሮፓ ገበያዎች አክስፖርት ታደርግ ነበር፡፡ ከዚህ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር የሚይዘው
የበግና የፍየል ቆዳ ነበር፡፡

ሀገራችን 55.03 ሚሊዮን ከብት፣ 27.35 ሚሊዮን በግ፣ እና 28.16 ሚሊዮን ፍየል
እንዳላት ይገመታል (CSA, 2014)፡፡ ይህ የሚያሳየው ሀገራችን ከእንስሳት ሀብት
አንጻር ከፍተኛ አቅም ያላት ቢሆንም የከብት፣ የበግ እና የፍየል ቆዳ እና ሌጦ
ዓመታዊ የማምረት አቅም በምናይበት ጊዜ እ.ኤ.አ. በ2012/13 ብቻ 3.78 ሚሊዮን
ሌጦ፣ 8.41 ሚሊዮን የበግ ቆዳ እና 8.42 ሚሊዮን የፍየል ቆዳ ብቻ ነው (CSA,
እ.ኤ.አ. 2013)፡፡ ይህም የሚያሳየው ሀገራችን በየዓመቱ እስከ 20 ሚሊዮን ቆዳና ሌጦ
ለሀገር ውስጥ ቆዳ ፋብሪካዎች/አልፊዎች የማቅረብ አቅም እንዳላት ነው፡፡ይሁን እንጂ
በአሁኑ ወቅት የቆዳ ፋብሪካዎችን ነባራዊ ሁኔታ በምናይበት ጊዜ 1 ሚሊዮን ሌጦ፣ 7.5
ሚሊዮን የበግ እና 4.5 ሚሊዮን የፍየል ቆዳ በየዓመቱ በማልፋት ላይ ይገኛሉ፡፡
በመሆኑም ቆዳና ሌጦ የመሰብሰብ አቅማችን በቅደም ተከተል በ80 እና በ40 በመቶ
ላይ ተገድቦ ይገኛል፡፡ ለዚህ ደግሞ በዋነኛ ምክንያትነት ከሚጠቀሱት መካከል
በተጠቃሚዎች እና በስጋ አቅራቢዎች የሚስተዋል ኋላቀር የሆነ አስተራረድና የቆዳ
አያያዝ ሲሆን ቆዳ ገዢዎች የሚያቀርቡትም ዝቅተኛ ዋጋም እንደ አንድ ምክንያት
ይታያል፡፡ በኢትዮጵያ የሚገኙ የቆዳ ፋብሪካዎች በየቀኑ 4000 ሌጦ እና 30,000
ቆዳዎችን የማልፋት አቅም አላቸው (Danniel, 2010፣ Ethiopian Investment Agency,
2012)፡፡ ቆዳን ከማልፋት አንጻር ስናያቸው አብዛኛዎቹ ፋብሪካዎች በከፊል
ያለቀላቸው ምርቶችን ማምረት ላይ የተሰማሩ ሲሆን ከአጠቃላዩ ከሚመረቱት ምርቶች
14 በመቶ የሚሆነው ብቻ ነው ወዳለቀለት የቆዳ የምርት ደረጃ ማድረስ የተቻለው
(International Livestock Research Institute፣ 2013)፡፡ መንግስት በሀገር ውስጥ
የሚገኙ ቆዳ አልፊ ፋብሪካዎችን ያለቀለት ቆዳ ወደ ውጭ እንዲልኩ ለማበረታታት
በማሰብ እ.ኤ.አ. ከ2008 ጀምሮ ጥሬ ቆዳን ወደ ውጭ በሚልኩ አካላት ላይ እስከ
150% የሚደርስ ታክስ እንዲከፍሉ የሚያስገድድ ህግ አውጥቶ ተግባራዊ
አድርጓል፡፡ይህ ብቻ ሳይሆን በየጊዜው ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት
ቆዳ አምራች ፋብሪካዎች ያለቀለት ቆዳ አምርተው ለገበያ ማቅረብ የሚያስችላቸው
አሰራር ተግባራዊ አድርገዋል፡፡ውጤቱ ግን የተጠበቀውን ያህል ለውጥ አላመጣም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 113


ባለፉት ጥቂት ዓመታት ባለድርሻ አካላት በጋራ በመረባረባቸው ጥራቱን የጠበቀ ጥሬ
ቆዳ እና ሌጦ ለገበያ ለማቅረብ ጥረት ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ የገበያ ስርዓቱ ላይ ይህ
ነው የሚባል ለውጥ ማምጣት ባለመቻሉ አሁንም አቅርቦቱ ላይ ችግሮች በስፋት
ይታያሉ፡፡ የገበያ ሰንሰለቱ ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ እና ሰፊ አካባቢዎችን የማይሸፍን
ነው፡፡ ከእርድ አንስቶ ቆዳው ፋብሪካ እስኪደርስ ድረስ እሴት የማይጨምሩ ብዙ
አካላት ይሳተፉበታል፡፡ አቅርቦቱ ረጅም የድለላ ሰንሰለት ማለፍ ይጠበቅበታል፡፡ ይህም
በምርቱ ጥራት እና ዋጋ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አለው፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ እ.ኤ.አ.
በ2013 ላይ መንግስት የጥሬ ቆዳና ሌጦ ግብይት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 814/2006)
አውጥቶ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ይህ አዋጅ በይዘቱ ከዚህ በፊት ከወጡት የተሻለ ነው፡፡
ይህን አዋጅም ተግባራዊ ለማድረግ በሚኒስቴሮች ም/ቤት የጸደቀ ሲሆን ንግድ
ሚኒስቴርም ደንቡን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል መመሪያ አውጥቷል፡፡ አዋጁም
ሆነ እሱን ለመተግብር የወጡ ደንቦች በጥሬ ቆዳ እና ሌጦ ግብይት እና አያያዝ
እንዲሁም አጓጓዝ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማስተካከል ታስቦ የጸደቀ ቢሆንም
አሁንም በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው ባለመስራታቸው ችግሩን ከስር
መሠረቱ አልቀረፈውም፡፡

በአብዛኛው ቆዳ የሚሰበሰበው ገጠር ውስጥ ካሉ አራጆች፣ በየአካባቢው ያሉ ስጋ ቤቶች፣


በከተማ ከሚኖሩ ነዋሪዎች፣ እና ከቄራ ድርጅቶች ነው፡፡ ከዚህ በመቀጠል የተለያዩ
አካላት ማለትም በየቤቱ እና በየመንደሩ የሚገኙ ቆዳ ሰብሳቢዎች /collectors/፣
አቅራቢዎች /suppliers/፣ ባህላዊ ቆዳ አልፊዎች /traditional tanners/፣ ቆዳ ላኪዎች
/Exporters/፣ ቆዳ ፋብሪካዎች እና የትራንስፖርት ድርጅቶች ይሳተፋሉ፡፡ የእርድ
ቦታዎቹ የተሰበጣጠሩና የተራራቁ በመሆናቸው እንዲሁም የአስተራረድ ዘይቤው ኋላቀር
በመሆኑ ለመደበኛው ገበያ በሚቀርበው የቆዳ እና ሌጦ ብዛት እና ጥራት ላይ የራሱ
የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፡፡ በዚህም ምክንያት ሊሰበሰብ የሚገባውን ያህል መሰብሰብ
አልተቻለም፡፡ የተሰበሰበውም ቢሆን በተለያዩ እንከኖች እና የአያያዝ ችግሮች
ምክንያት ፋብሪካ ከመድረሱ በፊት እና ፋብሪካ ከደረሱ በኋላ ከጥቅም ውጪ የሚሆነው
ቆዳ ቀላል አይደለም፡፡ እ.ኤ.አ. በ2012 በተደረገ ጥናት በፋብሪካ ደረጃ በሚደረግ
ጥራቱን የጠበቀ የቆዳ እና ሌጦ መረጣ ወቅት 65 በመቶ የሚሆነው ከጥቅም ውጪ ሆኖ
(reject grades) መሆኑ ታውቋል (Kebede and Fetene 2012)፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 114


ሌላው ትልቅ ክፍተት ከእርድ በፊት ያለው የከብቶች አረባብ እና አያያዝ ችግር ነው፡፡
አርሶአደሩ በአብዛኛው ከብቶቹን የሚያረባው በባህላዊ መንገድ በመሆኑ ለምልክት
በሚል እና በተለያዩ ባህላዊ አስተሳሰቦች የተነሳ በከብቶች ቆዳ ላይ የተለያዩ ጠባሳዎች
ይኖራል፡፡ ሌላው መታየት ያለበት ከከብቶች ቆዳ በሽታ ጋር ተያይዞ ያለው ችግር
ነው፡፡ በሀገራችን ያሉ ከብቶች ኤክቶፓራሳይት በሚባል በሽታ ስለሚጠቁ ይህም
በቆዳው ጥራት ላይ ትልቅ ችግር ይፈጥራል፡፡ ነገር ግን ይህን በሽታ በቀላሉ መከላከል
እንደሚቻል የአለም ባንክ እ.ኤ.አ. በ2012 ባስጠናው ጥናት ለመጠቆም ሞክሯል፡፡

እነዚህ ከእርድ በፊት የሚስተዋሉ ችግሮች ከእርድ በኋላ ለሚመጣ የቆዳ ጥራት ማነስ
ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ አላቸው፡፡ በመሆኑም ጥራቱን የጠበቀ ቆዳ እና ሌጦ
ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያዎች ማቅረብ የሚቻለው በእርባታ፣ በእርድ፣ በቆዳ
አሰባሰብ፣ አያያዝ፣ በቆዳ ማከማቸት፣ በቆዳ አለፋፍ፣ በማጓጓዝ እና በፋብሪካ ደረጃ
በሚደረግ የቆዳ ፕሮሰሲንግ ሂደት በሚደረጉ ጥንቃቄዎች ነው፡፡ በዚህ ረገድ በቆዳ
ሻጮቹ እና አቅራቢዎቹ ዘንድ በምርቱ አያያዝ ዙሪያ ትልቅ የእውቀትና የግንዛቤ
ክፍተት እንዳለ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡የቆዳ ኢንዱስትሪውን ሊያሳድግ የሚችል እና
በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚችል ሰፊ የሆነ የሪሶርስ አቅም ያለ ቢሆንም
ከእርድ በፊት እና ከእርድ በኋላ በሚደረጉ የጥንቃቄ ጉድለቶች፣ ኋላቀር የሆነ አሰባሰብ
እና የግብይት ሰንሰለት በመኖሩ ዘርፉ ማደግ ያለበትን ያህል ሳያድግ ቆይቷል፡፡
በችግሮቹም ምክንያት ቆዳ አቅራቢ ነጋዴዎች፣ ከብት አራጆች፣ ቆዳ አልፊዎች፣ ቆዳ
ላኪዎችና ሌሎች በግብይቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት መጠቀም ያለባቸውን ያህል
እየተጠቀሙ አይደለም፡፡ ለሀገራችንም ኢኮኖሚያዊ እድገት ማበርከት ያለበትን
አስተዋጽኦ እንዳያበረክት አድርጎታል፡፡

እነዚህ ከላይ የተጠቀሱ የአምራች ኢንዱስትሪው የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግሮችን


ለማስወገድ መንግስት የተለያዩ እርምጃዎችን የወሰደ ሲሆን ችግሩን ግን በታሰበው
መልኩ ሊፈታ አልቻለም፡፡ ከተወሰዱት እርምጃዎች መካከል ጥሬ ቆዳና ሌጦ፣ የጥጥ
ምርት፣ እና አንዳንድ የሰብል ምርቶች ወደ ውጭ እንዳይላኩ ያገደ ሲሆን፣ አቅርቦቱም
ከገበሬው በቀጥታ ወደ ፋብሪካ ለማድረስ በማሰብ ልዩ ልዩ የአርሶ አደር አደረጃጀቶችን
ለማደራጀት ሞክሯል፡፡ ይሁን እንጂ መሰረታዊ ሕብረት ስራ ማሕበራት፣ ዩኒዮኖችና
ፌደሬሽኖች የአርሶ አደሩ ምርት ከገበያ በማገናኘትና የግብርና-ኢንዱስትሪ ትስስር
ከማፋጠን አኳያ ጠንካራ ስራ እየሰሩ እንዳልሆነ በየክልሉ በተካሄዱ ውይይቶች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 115


ለመረዳት ተችሏል። በተጨማሪም የሀገር ውስጥ የግብርና ምርት እና አምራች
ኢንዱስትሪው ለማበረታታት ሲባል ገበያው በታሪፍና ኮታ ከለላ በመሰጠቱ ምክንያት
ተጠቃሚው በፖሊሲው እንደታሰበው አርሶአደሩና አምራቹ ሳይሆን የገበያ ከለላውን
ላልተገባ ትርፍ እያዋለ ያለው በድለላ የታጠረው የንግዱ ዘርፍ መሆኑን መረዳት
ይቻላል።

ይህ የላይኛው የእሴት ሰንሰለት በተፈለገው ፍጥነት አለማደግ አምራች ኢንዱስትሪውን


ሊመግብ የሚችል የጥሬ ዕቃ አቅርቦት እንዳይሳካ አድርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም
በጣም የሚያሳስበው ጉዳይ እነዚህ በሀገራችን እየተመረቱ የሚገኙት የኢንዱስትሪ ጥሬ
ዕቃዎች (ቆዳ፣ ጥጥ፣ ስንዴ፣ ወዘተ) ከጥራት አንጻር የሚፈለገው ደረጃ ላይ የሚገኙ
ባይሆንም ዋጋቸው ግን ከዓለም ገበያ ከፍ ያለ መሆኑ ነው፡፡

5.4.2 ለአምራች ኢንዱስትሪ ከውጭ ሀገር የሚገባ የግብአት አቅርቦት

በዚህ ጥናት የተካተቱ አምራቾች ሁሉም በከፊል ያለቀለት ግብአት ከሀገር ውስጥ
አምራቾች ከመግዛት ይልቅ የገቢ ቀረጥ ከፍለውም ቢሆን ከውጭ ማስገባት በዋጋና
በጥራት የተሻለ አዋጭ ነው ይላሉ። ለምሳሌ ለምስማር ምርት ግብአት የሚውለው
የስታፋ ብረት የገቢ ቀረጡ ከ5% ወደ 20% ከፍ እንዲል ቢደረግም የገቢ ቀረጥ
ተከፍሎበት ከውጭ የሚገባው ከሀገር ውስጥ አምራቾች የመሸጫ ዋጋ በኪሎ ቢያንስ
ብር 1.30 ይቀንሳል። የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎችም በተመሳሳይ የገቢ ቀረጥ ከፍለው
ከውጭ ጥጥ ሲያስገቡ ከሀገር ውስጥ ገበያው በኪሎ እስከ ብር 1.40 ይቀንስላቸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከውጭ የሚገባው ግብአት ጥራቱ እጅግ የተሻለ ነው ይላሉ። ለምሳሌ
የጥጥ ግብአት ለተወሰነ ጊዜ በድለላ እጅ ተይዞ በመጋዘን ስለሚከማች ከፍተኛ የጥራት
መጓደል እንደሚከሰትበት በጨርቃ ጨርቅ የተሰማሩ አምራቾች ይገልፃሉ።

እንደ ብረታብረት፣ ኬሚካል፣ መድሀኒትና የህክምና መገልገያ ወዘተ ያሉ የተወሰኑ


አምራች ዘርፎች ከአጭርና መካከለኛ ጊዜ አኳያ ከሚጠቀሙት ግብአት ከፍተኛው
የዋጋ ድርሻ የሚሸፍነው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከውጭ የሚገባ ግብአት ነው።
ኬሚካል አምራቾች ከሚጠቀሙት ግብአት ጠቅላላ ዋጋ 70%፣ ፕላስቲክና መሰል
አምራቾች 92%፣ መሰረታዊ ብረት አምራቾች 80%፣ የተፈበረኩ ብረት የሚጠቀሙ
አምራቾች 85% እንዲሁም ወረቀትና የወረቀት ውጤቶች አምራቾች 60% ያህል

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 116


የግብአት ዋጋ የሚያገኙት ከውጭ ገበያ ነው (የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር 2007)። እነዚህ
ኢንዱስትሪዎች ዕጣ ፈንታቸው በዋናነት በዓለም ገበያ ዋጋ እና በሀገራችን የንግድ
ባህሪ የሚወሰን ነው። እነዚህ አምራች ኢንዱስትሪዎች ከአግሮ ፕሮሰሲንግ
ኢንዱስትሪዎች በባሰ ጤናማ ላልሆነ የገበያ ተጽኖ የተጋለጡ ናቸው። ይህንን ከግምት
በማስገባት የሀገራችን የንግድ ሂደት ግልፀኝነት የሰፈነበትና የሸማቹና የአምራቹ መብት
ለማስጠበቅ ብሎም የንግዱ ስራ በውድድር ሲመራ ለአምራች ኢንዱስትሪው ተጨማሪ
ዓቅም እንዲፈጥር በንግድ ስርዓቱ የተለያዩ ለውጦች የተደረጉ ቢሆኑም በተግባር
ያስገኙት ውጤት አመርቂ እንዳልሆነ የንግዱ ማህበረሰብ፣ አምራቾችና የመንግስት
አካላት ይገልፃሉ።

በአግሮ-ፕሮሰሲንግ፣ ቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ ጨርቃ ጨርቅ አምራች ኢንዱስትሪዎች


የግብአት ፍላጎታቸው በሀገር ውስጥ በግብርናው ዘርፍ ከሚመረተው ምርት ማሟላት
ካልቻሉ አማራጫቸው እንደሌሎች አምራች ዘርፎች ከውጭ ሀገር ማስመጣት ይሆናል።
ይህ ደግሞ የውጭ ምንዛሬን ከማባከን በተጨማሪ የሀገር ውስጥ ምርቶች
እንዳይበረታቱና በቂ ገበያ እንዳያገኙ ያደርጋል።

ከላይ እንደተገለፀው አብዛኛዎቹ አምራች ኢንዱስትሪዎች ግብአት ከውጭ ለማምጣት


ተገደዋል። አምራች ኢንዱስትሪዎች ከሚጠቀሙት ግብአት በዋጋ 45.23 በመቶ
የሚሆነው በሀገር ውስጥ በሚገኝ ጥሬ ዕቃ የሚሸፈን ሲሆን ቀሪው 54.77 በመቶ
የሚሆነው ወጪ ደግሞ ከውጪ ሀገር የሚገባ ጥሬ ዕቃ ነው (ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ
ኤጀንሲ 2006 ዓ.ም)። ነገር ግን ብዙ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ዕቃ ለፋብሪካ ግብአት
እንዲውል የሚያደርግ ስርአት የለም። ንግድናኢን ዱስትሪው ለማስተሳሰር የተደረገ
ጥረትም ጠንካራ አይደለም። በሀገራችን የአስመጪነት የንግድ ስምሪት ምንም ዓይነት
ገደብ አይደረግበትም። የንግድ ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያመለክተው እስከ 2006 በጀት
ዓመት 1,065 የውጭ ሀገራት ዜጎች የሚገኙባቸው ከ29,908 በላይ የንግድ ፈቃዶች
በአስመጪነት ተመዝግበዋል። የዚህ ስምሪት ውጤትም ወደሀገር ውስጥ ከሚገቡ
ሸቀጦች ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው ለፍጆታ የሚውል እንዲሆን አድርጎታል።
ለኢንዱስትሪው ግብአት የሚውል ጥሬ ዕቃ የሚያቀርቡ 2,578 የንግድ ፈቃዶች ብቻ
ከመሆናቸው ተያይዞ ወደ ሀገር እየገባ ያለ የጥሬ ዕቃ ግብአት ድርሻው ከአጠቃላይ
ወደሀገር የሚገባው ሸቀጥ ጠቅላላ ዋጋ ከ 1.01% እስከ 4.43% ያህል ብቻ ነው፤
ምጣኔውም ከ2001 ዓም በኋላ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ይገኛል። ይህ መረጃ የሚያሳየው

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 117


ወደሀገር ውስጥ የሚገባው ሸቀጥ በአብዛኛው ካለን የልማት ቅኝት ጋር የሚመጋገብ ነው
ለማለት አያስደፍርም።

ከገቢ ቀረጥ ጋር ተያይዞ የሚደረግ ማሻሻያ ሲታሰብ ግብአቱ የሚጠቀም አምራች ምን


ዓይነት ተጽዕኖ ሊደርስበት እንደሚችል የማገናዘብ ጉድለት ይታያል። በሀገር ውስጥ
እየተመረተ ያለ ተመሳሳይ ምርት ቢያንስ መጠኑ በቂ መሆኑ እና ይህንን ምርት
እንዴት ለቀጣይ እሴት አምራቾች መድረስ እንዳለበት ካልሆነም የተሻለ የአቅርቦት
ውድድር መኖሩ ሳይረጋገጥ ስለሚሆን ይህን ግብአት የሚጠቀሙ በርካታ ፋብሪካዎች
የሚጎዱበት እና ግብአቱ የሚያመርቱ ያለአግባብ የሚጠቀሙበት ሁኔታ እየታየ ነው።
በ2007 በጀት ዓመት ለሚስማር ግብአት የሚውል ስታፋ ብረት ከታሪፍ ምድብ አንድ
ወጥቶ በምድብ ሁለት ሲካተት ግብአቱ በሀገር ውስጥ በበቂ ሁኔታ እየቀረበ መሆኑ እና
ለቀጣይ እሴት አምራቾች እንዴት መድረስ እንዳለበት በቂ ጥናት ሳይካሄድበት የገቢ
ቀረጡ ወደ 20% ከፍ እንዲል በመደረጉ ምክንያት ምስማር አምራቾቹ ለበርካታ
ኪሳራዎች እንደዳረጋቸው ገልፀዋል።

ግራፍ 5.4 ከውጭ የሚገቡ ምርቶች የዋጋ ድርሻ በተጠቀሚ (በመቶኛ)


ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 2006 ሪፖርት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 118


ከውጭ ለሚገቡ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ትልቅ ማነቆ የሆነው የሀገራችን የሎጂስቲክና
የጉምሩክ አሰራር እንዲሁም የትራንስፖርት ቅልጥፍና ችግር ነው፡፡ እንደሚታወቀው
የሎጂስቲክስ እና የጉምሩክ ስራ መቀላጠፍ ለአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት መፋጠን
ትልቅ ድርሻ አለው፡፡ በሀገራችን መንግስት ይህንን በመረዳት በአሁኑ ወቅት
የሎጅስቲክስና የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ እንዲሆንና መጫወት
የሚገባውን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ነገር
ግን አሁንም ቢሆን ችግሩ እንዳልተቃለለ እና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንዳሉ ማየት
ተገቢ ነው፡፡

በተለያዩ አካላት በሀገራችን የተደረጉ ጥናቶች ሪፖርት እንደሚያሳየው የሀገራችን


የሎጅስቲክስ አገልግሎት አሰጣጥ ደረጃና ብቃት የሚገኝበትን ሁኔታ ስንመለከት፡
 የገቢ እቃ ይሁን ወጪ ከጅቡቲ ወደብ ሀገር ውስጥ ወይም ከሀገር ውስጥ ጅቡቲ
ወደብ የትራንዚት ጊዜ 44 ቀናት እንደሚወሰድ፤
 የታንዛኒያና የኬንያ ወደቦች ተጠቃሚ የሆነችው ሩዋንዳ (በቅደም ተከተል 1380
እና 2000 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች)፡፡ የሚጠይቀውን የትራንዚት ጊዜ ግን
በአማካይ ከ28 እስከ 26 ቀናት ያልበለጠ ነው፡፡ እ.አ.አ በ2010 በዚህ በኩል
የነበራት ደረጃ ከኢትዮጵያ ያነሰ የነበረ ቢሆንም አሁን ደረጃዋ ከፍ እንዲል
አድርጋለች፡፡

በሀገራችን አንድ ባለ 20 feet ኮንቴነር ከቻይና ጅቡቲ ለማድረስ በአማካይ USD


1,500 የሚጠይቅ ሲሆን ከጅቡቲ አዲስ አበባ ለማድረስ ግን USD 2,400 ይጠይቃል
(EDRI, 2015)፡፡ የመጋዘንና የመርከቡ ማጓጓዣ ዋጋ እንዲሁም ገቢ ዕቃ በወደብ
የዘገየበት ቅጣት ሲጨመርበት ቻይና በUSD 5,000 የተገዛው እቃ አዲስ አበባ ሲደርስ
ዋጋው USD 9,400 እንደሚደርስ ተመልክቷል፡፡ ይሁንና የሎጀስቲክስ ስርዓቱና
የትራንስፖርት ማኔጅሜንቱን በማስተካከል መጋዘንና ወደብ ቅጣት በማስቀረት
ከጅቡቲ አዲስ አበባ ያለው ክፍያ ወደ 850 USD በማውረድ ጠቅላላ ዋጋው 5850
USD ማድረስ እንደሚቻል ጥናቱ ጨምሮ አመልክቷል፡፡ ሊሰመርበት የሚገባው
ኢትዮጵያ እና ሩዋንዳ ከወደብ ያላቸው ርቀት ብቻ አይደለም፡፡ የሩዋንዳ ትራንዚት
በአብዛኛው በሌሎች ሀገራት የሚደረግ ሲሆን የኢትዮጵያ ግን ከ80% በላይ በራሷ ሀገር
ውስጥ መሆኑ ጭምር ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 119


የኢትዮጵያ የባህር መርከብ ትራንዚትና ደረቅ ወደብ አንድ ላይ ተዋህደው መልቲ-
ሞዳልን እንደሚተገብሩ በአዋጅ ተደንግጓል፡፡ ደረቅ ወደቡም ቢሆን ወደቡን በዘመናዊ
ቴክኖሎጂ ታግዞ እየሰራ አይደለም፡፡ በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ጉምሩክ መ/ቤቶች ያለው
ግንኙነት አሁንም በICT የተደገፈ አይደለም (EDRI, 2015)፡፡ የአስመጪዎች ለጭነት
Waiver ጥያቄ ሰልፍ መያዝ የተለመደ እንደሆነ ተገልጋዮች ይገልፃሉ፡፡ ባለድርሻ
አካላት እንደሚያረጋግጡት የአምራች ግብአቶች ከሚገባው በላይ በትራንዚት
ይዘገያሉ፡፡ የተቋሙ የስራ ዘርፎቹ ማለትም የመርከብ፣ የማሪታይም፣ የደረቅ ወደብና
የኦፕሬሽን ክፍሉ በአጠቃላይ በICT ተገናኝተው መረጃውን ከምንጩ በቀጥታ እያገኙ
ባለመሆኑ ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን በአግባቡ ለመለየትና ተገቢው እርምጃ ለመውሰድ
አዳጋች እንዳደረገው ይነገራል፡፡

የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦቱ እንዳይሳለጥ ያደረጉት ምክንያቶች


ከላይ የተጠቀሱት አምራች ኢንዱስትሪዎች ግብአት በበቂ አቅርቦት፣ በጥራትና
በተወዳዳሪ ዋጋ ማግኘት ያልተቻለበት ምክንያቶች ምንድናቸው? ጥቂቶችን ለመጥቀስ
ያህል፡
 አርሶአደሩ ባለችው ጠባብ ማሳ ላይ ገበያ ተኮር ሆኖ፣ ዘመናዊ የግብርና
ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ ባለማምረቱና ምርታማነቱም በሚፈለገው ደረጃ
ባለመጨመሩ ምክንያት፤
 አርሶአደሩ ከኢንዱስትሪ ባለሀብቶች ጋር በጋራ ተሳስሮ እንዲሰራ አለመደረጉ፤
 ባለሀብቶች በሰፋፊ እርሻዎች በስፋት አለመሰማራታቸውና የተሰማሩትም በቂ
ምርት ባለማምረታቸውና ምርታማነታቸውም ከአርሶአደሩ ማሳ ምርታማነት
የተሻለ አለመሆኑ፤
 ረጅምና እሴት የማይጨምር የግብይት ሰንሰለት (በደላላዎች ምክንያት
የሚፈጠር) መፈጠሩ እና የገበያ ስርአቱ በውድድር እንዳይመራ ማድረጉ፤
 ለኢንዱስትሪ ግብአቶች (Pershible & seasonal items) ባህሪ የሚመጥን
የሎጂስቲክስ መሰረተ-ልማት (ማቆያ፣ ማጓጓዣ፣ ማሽግ፣ ማውረድና መጫን፣
ወዘተ) አለመኖር፤
 አርሶአደሩ ወይም በግብርና የተሰማራው ባለሀብት ላመረተው ምርት ተገቢ የሆነ
ዋጋ እና ቀጣይነት ያለው እንዲሁም አስተማማኝ ገበያ ያለማግኘቱ፤

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 120


5.5 የአምራች ኢንዱስትሪ ምርቶች ገበያና የንግዱ ስርአት

የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ምርታማ ለማድረግ ጠንካራ የገበያ እና


የንግድ ስርዓት በአስተማማኝ ደረጃ መዘርጋት የማይተካ ሚና አለው፡፡ ጠንካራ የገበያ
እና የንግድ ስርዓት ለመገንባት ደግሞ ተገቢ የሆነ የንግድ ውድድር (fair competition)
ማስፈን፣ የምርት ጥራትና ደረጃ መጠበቅ፣ የአለም ንግድ አሉታዊ ተጽኖ መቀነስ፣
የንግድ ተቋማትን አደረጃጀት ማመጣጠን እና በግብይት ሂደት ያሉ ጉድለቶችን
መሙላት ያስፈልጋል፡፡

የንግድ ዘርፍ ከሁሉም የኢኮኖሚ ዘርፎች ጋር ባለው ጥብቅ ቁርኝት ምክንያት ለሀገሪቱ
እድገት እና ልማት ጉልህ ድርሻ ያለው በመሆኑ የተረጋጋ ገበያ እና ፍትሃዊ የንግድ
ስርአት መገንባት ልዩ ትኩረት በመስጠት ርብርብ የሚሻ ጉዳይ መሆኑ ተሰምሮበታል
(የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን፣ 2008 ዓ.ም)፡፡ ነገር ግን በዚህ ጥናት ከተለዩ እና በንግዱ
ስርአት የሚስተዋሉ ችግሮች ውስጥ የጥራት እና ደረጃ የጎደለው ምርት በገበያ በሰፊው
መሰራጨት፣ ተገቢ ላልሆነ የንግድ ውድድር ተጋላጭ መሆን፣ የገቢ-ምርቶች ኢ-ፍትሃዊ
ውድድር ተፅዕኖ፣ የኢንዱስትሪ አደረጃጀት የተዛነፈ መሆን፣ ንግድ ስምሪቱ ዕሴት ወደ
ሚጨምሩ ዘርፎች አለማተኮሩ እና የመንግስት የግዥ ስርአት ለሀገራዊ አምራች
ኢንዱስትሪ ገበያ ለመፍጠር የሚያስችል ቁመና ላይ አለመገኘቱ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡

5.5.1 የአምራች ኢንዱስትሪ ምርት ጥራትና ደረጃ

የሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪ ካሉበት ዋነኛ ችግሮች አንዱ በአለማቀፍ ወይም


በብሄራዊ ደረጃ የተቀመጡ የጥራት እና ደረጃ መስፈርቶችን የማያሟሉ የሀገር ውስጥ
እና ኢምፖርት የተደረጉ ምርቶች በገበያ ላይ መበራከቱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
ለአብነት ከንግድ ሚኒስቴር የተሰበሰበ መረጃ ይሄንኑ ሀሳብ የሚያጠናክር ነው፡፡ በ2008
ዓ.ም የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት አስገዳጅ የጥራት ደረጃ ያላቸውን
ምርቶች በሚያመርቱ 134 ፋብሪካዎች በናሙናነት ወስዶ ባጠናው ጥናት መሰረት 18
(13%) የሚሆኑት ፋብሪካዎች ደረጃ ሳያሟሉ ተገኝተዋል፡፡ በተመሳሳይ ገበያ ላይ
የሚሸጡ የአምራች ምርቶችን ጥራት እና ደረጃ ለመፈተሸ የተደረገ ጥናት የችግሩን
ግዝፈት ለመገመት ያስችላል፡፡ በ10 ከተሞች በ9 የአስገዳጅ ደረጃ በወጣላቸው የምርት
ዓይነቶች (ቆርቆሮ፣ አርማታ ብረት፣ ሚስማር፣ የታሸጉ ውሀዎች፣ የምግብ ዘይት፣

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 121


ሲሚንቶ፣ ኤሌክትሪክ ገመድ፣ ክብሪት እና ሳሙና) ማለትም ከ29 የሀገር ውስጥ
ምርቶች እና ከ14 ገቢ-ምርቶች (በጠቅላላው 43) ናሙና ተወስዶ በተካሄደ የእይታና
የላቦራቶሪ ፍተሻ 16(55%) የሀገር ውስጥ ምርቶች እና 14 (100%) የውጭ ሀገር
ምርቶች የጥራት ደረጃ ሳያሟሉ ተገኝተዋል፡፡ ከዚህ አሀዝ መረዳት የሚቻለው በገበያ
ላይ የሚሸጡ የአምራች ምርቶች ላይ የጥራት እና ደረጃ ችግር መኖሩን ነው፡፡ በተለይ
ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ጥራትና ደረጃ ጉድለት በሀገር ውስጥ ከሚመረቱ የከፋ
መሆኑን ከመረጃው መረዳት ይቻላል፡፡

ሌላው የንግድ አሰራር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን (2007 ዓ.ም) በምግብ፣


ኤሌክትሮኒክስ፣ አልባሳት እና መድሀኒት ምርቶች ላይ በማተኮር ያጠናው ጥናት
እንዲሁ የጥራት እና ደረጃ ችግር በሰፊው እንደሚስተዋል ያስገነዝበናል፡፡ በዚህ
መሰረት ጥራትና ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶች ወደ ሀገራችን ከሚገቡበት መንገድ
ውስጥ ዋነኛው የኮንትሮባንድ ንግድ እንደሆነ ነው፡፡ ሌላው መንገድ ደግሞ ህጋዊ
የጉምሩክ ስነ-ስርአት ተከትሎ ወደ ሀገር የሚገባ ጥራትና ደረጃው ያልጠበቀ ምርት
መሆኑ ነው፡፡ ህጋዊ አሰራርን ሽፋን አድርጎም ሆነ በቀጥታ በህገ ወጥ መንገድ ወደ
ሀገር የሚገባ ጥራት እና ደረጃ ያልጠበቀ ምርት መስፋፋት በመንስኤነት ከሚጠቀሱት
ምክንያቶች ውስጥ ጥራትን እና ደረጃ የሚቆጣጠር በቂ የህግ ማዕቀፍ አለመኖር፣
በመንግስት አስፈጻሚ አካላት ሃላፊነት የጎደለው አሰራር እና የኪራይ ሰብሳቢነት
አመለካከት፣ የፍትህ አካላት ወቅቱን የጠበቀና አስተማሪ እርምጃ ያለመውሰድ፣ የንግዱ
ማህበረሰብ ግንዛቤ ዝቅተኛ መሆን እና አንዳንድ ነጋዴዎች በአጭር ጊዜ ሀብት
ለማካበት መሯሯጥ ናቸው፡፡

በአጠቃላይ ጥራትና ደረጃ ሳያሟሉ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ እና ወደ ሀገር የሚገቡ


ምርቶች በሀገር ኢኮኖሚ እና በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ተፅኖ እያሳደሩ
ይገኛሉ፡፡ጥራት እና ደረጃ በማያሟሉ ምርቶች ምክንያት በህጋዊ መንገድ ጥራት እና
ደረጃውን የጠበቀ ምርት የሚያቀርቡ አምራቾች ለኪሳራ መጋለጥ ብሎም አጠቃላይ
የዘርፉን ምርታማነት እና ተወዳዳሪነት እየጎዳው መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 122


5.5.2 የአምራች ኢንዱስትሪዎች የውድድር ሁኔታ

በአንድ ሀገር ፍትሃዊ እና ጤናማ የንግድ ውድድር መኖር ለአምራች ኢንዱስትሪው


ምርታማነት እና ተወዳዳሪነት እውን ለማድረግ ያስችላል፡፡ ፍትሃዊ የንግድ ውድድር
ተግባር ስንል ተገቢ የሆነ የንግድ ውድድር (faire competition) መፍጠር፣ በአንድ
ወይም ጥቂት ነጋዴዎች በበላይነት የተያዘ ገበያን ያለአግባብ እንዳይጠቀሚሙ
መቆጣጠር፣ በቡድን ወይም በማህበር በመሆን የገበያ ዋጋን እና ምርትን ኢፍትሃዊ
በሆነ መንገድ እንዳይወስኑ መከላከል እና ተያያዥ ጉዳዮች ይመለከታል፡፡

ሆኖም የሀገራችን የንግድ ውድድር ተግባር ውጤታማ፣ ጠንካራ እና ብቃት ያለው ነው


ለማለት አያስደፍርም፡፡ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከተሰማራው ባለሀብት የተገኘው
መረጃ እንደሚያሳየው ተገቢ ያልሆነ የንግድ ውድድር ለዘርፍ ማነቆ እንደሆነ ነው፡፡
ጥራቱን ያልጠበቀ ምርት መሸጥ፣ ምርትን አመሳስሎ መስራት፣ መልካም ዝና ያላቸውን
አምራቾች ስም ማጥፋት፣ በተጋነነ ሁኔታ ምርትን ማስተዋወቅ፣ ኮንትሮባንድ ንግድ እና
መሰል ተግባራት በሀገር ውስጥ ገበያ በርከት ብሎ ይገኛል ምንም እንኳን ችግሩን
ለመከላከልና ለመቆጣጠር መንግስት ፓሊሲ ቀርፆ ቢንቀሳቀስም፡፡

በሀገራዊ አምራቹ ከሚነሱ ችግሮች አንዱ የተጋነነ ይዘት ያለው የውጭ ምርት
ማስታወቂያ ጋር ተያይዞ የሚታየው ተገቢ ያልሆነ የውድድር ተግባር (unfair
competition) ነው፡፡ በአስመጭዎች፣ በንግድ እንደራሲዎች እና በንግድ ወኪሎች
የሚደረገው የተዛባ የውጭ ምርት ማስተዋወቅ ስራ በሀገር ውስጥ አምራቾች ምርት ላይ
ተፅዕኖ እያሳደረ መምጣቱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ እነዚህ አካላት የተለያዩ የመንግስት
እና የግል መገናኛ ብዙሀንን እንደ መሳሪያ በመጠቀም የውጭ ምርቶች ጥራት
የበላይነት እንዲሁም የዋጋ ተመጣጣኝነት በማጉላት የማስተዋወቅ ስራ ሲሰሩ
ይታያል፡፡ የውጭ ሀገር ምርቶች የተሻሉ እንደሆኑ አድርጎ ለተጠቃሚው በማቅረብ
የሀገር ውስጥ ምርቶች ተመራጭ እንዳይሆኑ እያዳደረጋቸው ይገኛል፡፡ በተጨማሪም
ሸማቹ ማህበረሰብ ለሀገር ውስጥ ምርት የተዛባ አመለካከት እንዲያዳብር በማድረግ
በሸማቹ የግዥ ፍላጎት ላይ አሉታዊ ተፅኖ ሲፈጥር ይታያል፡፡ በዚህ ምክንያት
ተፈላጊውን የጥራት እና ዋጋ አሟልተው የሚያቀርቡ የሀገር ውስጥ አምራች
ኢንዱስትሪዎች ተገቢውን ጥቅም ማግኘት አልቻሉም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 123


ሌላው ተገቢ ያልሆነ የንግድ ውድድር ተግባር ምንጩ ያልታወቀ፣ ተመሳስሎ የተሰራ
እና ደረጃውን ያልጠበቀ ምርት ወደ ገበያ በማቅረብ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት
የሚሰሩ እንዳሉ በባለሀብቱ ይገለፃል፡፡ ይህ ችግር ለመከላከል የሚመለከታቸው
የመንግስት ተቋማት (በተለይ የንግድ አሰራር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን) ተገቢውን
ትኩረት ባለመስጠታቸው ባለሀብቱ በራሱ ተነሳሽነት ሚዲያዎችን በመጠቀም
ከምርታቸው ጋር ተመሳስለው የተሰሩ ምርቶች በገበያ ላይ እንዳሉ እና ደንበኞች
ለይተው እንዲገዙ ሲማፀኑ ይስተዋላል፡፡ ሌላው የአምራች ኢንዱስትሪው እድገት ፈተና
እየሆነ ያለው የኮንትሮባንድ ንግድ ጉዳይ ነው፡፡ ኮንትሮባንድ ንግድ ለመከላከል እና
ለመቆጣጠር የሚደረጉ ጥረቶች ዘላቂነት የጎደለው ሆኖ ይገኛል፡፡ ለዚህ ዋነኛ ምክንያት
ደግሞ የቁጥጥር ስራ ለመሥራት የሚመደብ አካል ከኮንትሮባንድ አስመጪዎች ጋር
የመላመድ ወይም በቀላሉ በጥቅም የመደለል አዝማሚያ መንሰራፋቱ ነው፡፡
የሚመለከታቸው አካላት (ንግድ ሚኒስቴር፣ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን፣ ኢንዱስትሪ
ሚኒስቴር፣ የክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮዎች፣ የፌደራልና የክልል የፍትህ አካላት)
በርቀት በመሆን ሃላፊነታቸውን የመግፋት ዝንባሌ ይታያል፡፡ ስለሆነም ችግሩን
ከምንጩ ለማድረቅ በቁርጠኝነት ባለመሰራቱ የሀገር ውስጥ ምርት በዋጋ ተወዳዳሪ
እንዳይሆን እያደረገው ይገኛል፡፡ የኮንትሮባንድ እቃ በባህሪው ቀረጥ የማይከፈልበት፣
የጥራት ደረጃ የማያሟላ እና በኢ-መደበኛ ንግድ የተሰማሩ አካላት ለገበያ የሚቀርብ
በመሆኑ ለአምራች ኢንዱስትሪው እድገት እንቅፋት መሆኑ አያጠያይቅም፡፡ ለምሳሌ
የአለም ባንክ 1997፣ 2003 እና 2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ አምራች ዘርፍ ላይ ባደረገው
ተከታታይ ጥናት የኢ-መደበኛ ንግድ በአምራች ኢንዱስትሪ ለተሰማራው ባለብት
ከዋነኛ ማነቆዎች አንዱ እንደሆነ ያሳያል፡፡ በሌላ በኩል ከንግድ ሚኒስቴር የተገኘው
መረጃ እንደሚሳየው ህገወጥ ንግድ/ ኮንትሮባንድ ሁለንተናዊ ጉዳት ለመቀነስ ከፌደራል
ጀምሮ በተዋረድ የኮንተሮባንድ እና ህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ግብረ ሀይልና ኮማንድ
ፖስት አደረጃጀቶችን በመፍጠር የክትትል እና ድጋፍ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በዚህም
መሰረት የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የተገኙበት ሀገራዊ የንቅናቄ መድረክ
እና የፀረ-ኮንትሮባንድ ልዩ እቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ እንደተገባ ያመለክታል፡ በዚህ
እቅድ በፌደራልና በክልል አካላት መሰራት ያለባቸው ሥራዎች፣ አስፈላጊ የፌደራልና
የክልል ግብረ ሐይልና ኮማንድ ፖስት አደረጃጀት እና የግንኙነት ስርአት እንደተፈጠረ
ይገልፃል፡፡ በተጨማሪም በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሰብሳቢነት ከጠቅላይ
ሚኒስቴር ጽ/ቤት ንግድ ሚኒስቴር፣ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት፣ ማእድን ሚኒስቴር፣
እንስሳትና አሳ ሀብት፣ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና የፌደራል ፖሊስን ያካተተ በ15 ቀናት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 124


እየተገናኘ የክልሎችን ኤክስፖርት ምርት አቅርቦትን እና የሚመለከታቸው ተቋማትን
ኮንትሮባንድ (ህገ-ወጥ ንግድ) የመከላከል ዕቅድ አፈፃፀም እየገመገመ እና እየተከታተለ
እንደሚገኝ ነው፡፡ ነገር ግን ነባራዊ ሁኔታው እንደሚያሳየው ኮንትሮባንድ ችግር ከጊዜ
ወደ ጊዜ እየገዘፈ መሄዱን ነው፡፡ በመሆኑም የኮንትሮባንድ ንግድ የምርታማነት እና
የተወዳዳሪነት አቅማቸው ገና በጅምር ላይ ያሉ በርካታ ሀገር በቀል አምራች
ኢንዱስትሪዎች ላይ አሉታዊ ተፅኖ እየፈጠረ መሆኑን ያመለክታል፡፡

ተገቢ ያልሆነ የንግድ ውድድርን (unfair competition) ለመከታተል እና መቆጣጠር


የሚያግዙ አንቀፆች በፍታብሄር ህግ፣ ንግድ ህግ፣ ንግድ አሰራርና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ
እና ማስተወቂያ አዋጅ ወዘተ ተግባራዊ ቢሆኑም ተመሳስሎ የሚመረት ምርት፣ የተጋነነ
ማስታወቂያ እና ምንጩ ያልታወቀ ምርት ከጊዜ ወደ ጊዜ በገበያ ላይ መበራከት
እንዳለ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ለዚህ ደግሞ ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ወጥነት ያለው
ማስፈፀሚያ ፓሊሲ እና ቅንጅታዊ አሰራር ለመዘርጋት አለመቻሉ ነው፡፡ በተለይ
ደግሞ የንግድ አሰራር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት
ለመስራት የሚያስችለውን ዝርዝር ደንብ (directive) እና የማስፈፀሚያ መመሪያ
(implementation guideline) አዘጋጅቶ ወደስራ አለመግባቱ ችግሩን ለመከላከል እና
ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡

ሌላው አንድ ወይም ጥቂት አምራቾች ወይም ነጋዴዎች ገበያን በበላይነት በመያዝ
አላግባብ የመጠቀም (abuse of market dominance) ችግር ነው፡፡ ገበያ በጥቂት
አካላት በበላይነት በመያዝ አላግባብ መጠቀም ምርትን ከማምረቻ ዋጋ በታች በመሸጥ
ተወዳዳሪን ማሸነፍ ወይም አዳዲስ ኢንቨስተሮች እንዳይፈጠሩ ማድረግ፣ ምርትን
መደበቅና ማከማቸት፣ ምርትን ለተወሰኑ አካላት ብቻ በማቅረብ እና መሰል ድርጊቶች
ሊፈጥር ይቻላል፡፡ በሀገራችን ያለውን ሁኔታ ስናይ ደግሞ በገበያ ላይ ያላቸውን
የበላይት በመጠቀም ምርት የመደበቅ ብሎም እቃዎቹ በመደበኛ የንግድ መስመር
እንዳይወጡ የማድረግ ተግባራት እንዳለ ጥናቱ ያሳያል፡፡ ለአብነት አምራቾች
ለግብአትነት የሚያገለግሉ ወሳኝ ጥሬ እቃዎች፣ በከፊል ያለቁ ጥሬ እቃዎች እና
የካፒታል እቃዎች በጥቂት አስመጭዎች አልፎ አልፎ የመያዝ ሁኔታ በመኖሩ
የአምራች ኢንዱስትሪው ስራው ሲስተጓጎል ይታያል፡፡ በተጨማሪም በሀገር ውስጥ እና
ገቢ-ምርቶች የሚያቀርቡ ነጋዴዎች በየፊናቸው ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር የዋጋ
ንረት ይፈጥራሉ፡፡ ሌላው በህብረት በሚፈፀም ስምምነት የሚፈጠር ፀረ- ውድድር

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 125


ተግባር ሲሆን ችግሩ በጉልህ እንደማይስተዋል ከባለሀብቱ የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡
ሆኖም አልፎ አልፎ ወደ-ጎን ወይም ከላይ ወደታች ግንኙነት ባላቸው ነጋዴዎች
መካካከል ውድድርን ለመገደብ እና ያለአግባብ ትርፍ ለማግኘት መመሳጠር እንዳለ
መረጃው ያሳያል፡፡

5.5.3 የአለማቀፍ ገበያ እና ንግድ ተፅዕኖ

በሀገራችን የነፃ ገበያ ስርአት ለማስፈን ላለፉት 25 አመታት የኢኮኖሚ ፓሊሲ


ለውጦች እና ማሻሻያዎች መደረጋቸው በአለማቀፍ ንግድ ውድድር ጠንካራ ተሳታፊ
እና ተጠቃሚ ለመሆን የተያዘውን አቅጣጫ ያመለክታል፡፡ ለምሳሌ መንግስት
በወሰደው የፓሊሲ ለውጥ የአማካይ ቀረጥ መጠን በ1980 ዓ.ም ከነበረበት 41.6%
በ1995 ዓ.ም ወደ 17.3% ዝቅ ያለ ሲሆን (MIT፣ 2008 GC) በ2008 ዓ.ም ወደ 13%
ቀንሷል (Global Competitivness Index,2016)፡፡ በተያያዘ የአለም ንግድ ድርጅት
(WTO) የአባልነት ጥያቄ እንዲሁ ሀገሪቱ የገበያ ከለላ በመቀነስ ጉዞ ወይም ለአለማቀፍ
ንግድ በሯን ክፍት በማድረግ ጉዞ ላይ መሆኗን አመላካች ነው፡፡ ያም ሆኖ የገበያ ከለላ
ማንሳት ገቢ ምርቶች አማካኝነት የሚፈጠር በድንገት መጥለቅለቅ (sudden import
surge)፣ ኢ-ፍትሃዊ በሆነ ዝቅተኛ ዋጋ በገፍ የሚገቡ ምርቶች (dumped products)
እና በመንግስታት ተደጉመው የሚገቡ ምርቶች የሚፈጥሩት ተገቢ ያልሆነ የንግድ
ውድድር (effects of subsidized products) እና ለሌሎች አደጋዎች የአምራች
ኢንዱስትሪውን የማጋለጥ ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ ነገር ግን የገበያ ከለላ መቀነሱን
ተከትሎ ገቢ-ምርቶች በሀገራችን የአምራች ኢንዱስትሪ ዕድገት ላይ ሊያስከትሉ
የሚችሉትን አሉታዊ ተፅኖ ለመቆጣጠር የሚያስችል ግልጽ ፓሊሲ እና አደረጃጀት
የለም፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪው ከገቢ-ምርቶች ጋር ፍትሃዊ
ውድድር እያደረገ ስለመሆኑ በየጊዜው ተፅኖ አመላካች ጥናት (Impact Assessement)
አይካሄድም፡፡ በዚህ የተነሳ ገቢ-ምርቶች ለሚያስከትሉት ተገቢ ያልሆነ የንግድ
ውድድር በባለሀብቱ በግልፅ ቅሬታ ሲቀርብ ወይም በመንግስት እርምጃ ሲወሰድ
አይታይም፡፡ በንፅፅር ለኢንዱስትሪ ልማት ትኩረት የሰጡ ብዙ ታዳጊ ሀገራት ከገቢ-
ምርቶች የሚመነጭ ኢ-ፍትሃዊ ውድድር ለመቆጣጠር የሚያስችል ፓሊሲ ቀርፀው
ተግባራዊ ያደርጋሉ፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 126


የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪ እና ዳንፒንግ
ዳንፒንግ ስንል የሌላን ሀገር ገበያ ለመቆጣጠር እና የሌላ ሀገር አምራች ከገበያ
ለማስወጣት በማሰብ የውጭ አምራች ተቋማት ኢ-ፍትሃዊ በሆነ ዝቅተኛ ዋጋ ወይም
ተመጣጣኝነት በጎደለው ዝቅተኛ ዋጋ ምርትን በሌላ ሀገር ገበያ ሲሸጡ ነው፡፡
በሀገራችን የንግድ አሰራር አዋጅ (1995 ዓ.ም) ዳንፒንግ ጋር የተያያዘ ሀሳብ "ተገቢ
ያልሆነ የንግድ ውድድር" በሚለው አንቀጽ ስር ተጠቅሶ ይገኝ ነበር፡፡ ነገር ግን በ2002
ዓ.ም እና በ2006 ዓ.ም በተሻሻሉት የንግድ አሰራር እና ሸማቾች ጥበቃ አዋጆች ውስጥ
ከዳንፒንግ ጋር የተያያዘ ሃሳብ አልተካተተም፡፡ እንደ ባለሙያዎች አስተያየት ከሆነ
የዳንፒንግ ፅንሰ ሃሳብ ከአዋጆቹ ለመሰረዙ ዋና ምክንያት ሀሳቡ ውስብስብ እና
ለአፈፃፀም አስቸጋሪ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡

በሀራችን ያለው የዳንፒንግ ሁኔታ በጥልቀት ለመተንተን የመረጃ ውስንነት ያለ


ቢሆንም ከባለሙያዎች፣ ከግል ባለሀብቱ፣ በአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ጽ/ቤት
በ2007 ዓ.ም በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ የተደረገ የዳሰሳ ጥናት፣ የንግድና ኢንዱስትሪ
ሚኒስቴር በተባበሩት መንግስታት ልማት ፕሮግራም (UNDP) ድጋፍ በ2000 ዓ.ም
ያስጠናው ጥናት እና ተዛማጅ ሰነዶች በመጠቀም ዳንፒንግ በሀገር ውስጥ አምራች
ኢንዱስትሪ ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

ከዚህ በመነሳት በሀገራችን ዳንፕ የሚደረጉ ምርቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረሩ


መምጣታቸው እና አምራች ዘርፍ ላይ ችግሩ እንደሚከፋ ለመረዳት አያዳግትም፡፡
ለምሳሌ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተባበሩት መንግስታት ልማት ፕሮግራም
(UNDP) ድጋፍ በ2000 ዓ.ም ያስጠናው ጥናት እንደሚያሳየው ዳንፒንግ በኢንዱስትሪ
ልማት ስትራቴጅ ልዩ ትኩረት በተሰጣቸው የአምራች ኢንዱስትሪ ንኡስ ዘርፎች ላይ
አሉታዊ ተፅኖ እንደነበረው አመላክቷል፡፡ነገር ግን የአምራች ኢንዱስትሪው ለሀገር
ኢኮኖሚ ያለው ድርሻ አነስተኛ በመሆኑ (ማለትም 5%) ምክንያት ዳንፒንግ
በአጠቃላይ የሀገር ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅኖ ፈጥሯል ተብሎ አይታሰብም፡፡ በ2000
ዓ.ም ዳንፒንግ የታየባቸው የገቢ ምርቶች መጠን 4.1 ቢሊዮን ብር ሲገመት ከዚህ
ውስጥ 1.3 ቢሊዮን ብር (ወይም 32%) የሚገመተው በቀጥታ ዳንፕ መደረጉን ጥናቱ
ጠቅሷል፡፡ በወቅቱ ሀገራችን ኢምፖርት ካደረገቻቸው ምርቶች ጋር ሲነፃፀር ደግሞ
3.3% ሊሆን እንደሚችል ሲገመት ዳንፕ የተደረጉ ምርቶች ከአጠቃላይ የሀገራችን
አምራች ኢንዱስትሪ ምርት መጠን ከ10% ይልቃል፡፡ በጥናቱ መሰረት ዳንፕ የተደረጉ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 127


ዋና ዋና የአምራች ምርቶች ውስጥ መሰረታዊ ብረታብረት (85%)፣ የብረታብረት
ምርቶች (65%)፣ ጎማ እና የፕላስቲክ ውጤቶች (12%-15%) እና የጫማ ምርቶች
(10%) ዳንፕ እንደተደረጉ ይገመታል፡፡ በአጠቃላይ ዳንፒንግ የተስተዋለባቸው
ምርቶች እንደ ብረታብረት፣ ኬሚካል፣ ስትራክቸራል ሜታል፣ ጎማ (በተለይ የመኪና
ጎማ)፣ የጫማ ምርቶች እና ጨርቃ ጨርቅ ናቸው፡፡የሀገር ውስጥ ምርትን የመሸጫ ዋጋ
ጋር ሲነፃፀር የገቢ -ምርቶች የመሸጫ ዋጋ በአማካይ ከ35-47% (የዳንፒንግ ህዳግ) ዝቅ
ያለ መሆኑን ጥናቱ ገምቷል፡፡ በተያያዥ በአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ጽ/ቤት
የ2007 ዓ.ም ባስጠናው ጥናት መሰረት ለምርት እድገት ማነቆ (Production
Performance Constraints) ከሆኑ ምክንያቶች አንዱ ዳንፒንግ መሆኑን መጠይቅ
ከተደረገላቸው ኢንዱስትሪዎች መካከል 24% ያህሉ ገልፀዋል፡፡

በሌላ በኩል ከባለሙያዎች እና አንዳንድ የግል ባለሀብት የተገኘ መረጃ


እንደሚጠቁመው አንዳንድ የብረታብረት፣ የጫማ ምርት የእና ጨርቃ ጨርቅ አምራች
ኢንዱስትሪዎች ለኪሳራ እና ለመዘጋት ከዳረጋቸው ምክንያቶች አንዱ የዳንፒንግ
ችግር መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አሁን ካለው የኢኮኖሚ ነባራዊ ሁኔታ
መረዳት እንደሚቻለው የዳንፒንግ መጠን እና ስጋት ከፍተኛ መሆኑን ነው፡፡ አንደኛ
ሀገራችን የነፃ ገበያ ፓሊሲ ተግባራዊነት እየሰራች መሆኗ እና የገበያ ከለላ እየቀነሰ
መሄድ አምራች ኢንዱስትሪ ለዳንፒንግ የበለጠ ተጋላጭ እየሆነ መምጣቱ አይቀርም፡፡
ሁለተኛ ውስን የውጭ ምንዛሬ ቢኖርም የሀገራችን በፈጣን እድገት ላይ የምትገኝ
በመሆኗ የገቢ እቃ ፍላጎትና መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ በዝቅተኛ
ዋጋ ኢምፖርት የማድረግ ዝንባሌ እያደገ መጥቷል፡፡ ለምሳሌ 2007 ዓ.ም የኢምፖርት
መጠን ግምት 25% ያህሉን የሀገሪቱን አጠቃላይ ምርት ሲይዝ ከዚህ ውስጥ ከ70-80%
በላይ የሚሆነው የአምራች ኢንዱስትሪ ምርት ነው፡፡ ሶስተኛ ዳንፕ በማድረግ በብዙ
ሀገራት ቅሬታ ከሚያቀርቡባቸው ጥቂት የኤሲያ ሀገራት የገቢ-ምርቶች ግዥ
የአንበሳውን ድርሻ መያዙ ተጠቃሽ ነው፡፡ ለአብነት በ2007 ዓ.ም ኢምፖርት ከተደረጉ
እቃዎች ውስጥ 70.3% ያህሉ ከኤሲያ ሲሆን ቻይና 38.3% እና ህንድ 6.7% ድርሻ
ነበራቸው፡፡ ከቻይና ኢምፖርት የተደረጉ ምርቶች ውስጥ ኤሌክትሮኒክስ፣ መሰረታዊ
ብረታብረት፣ የብረታብረት ምርቶች፣ ማሽነሪ፣ ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ ጎማ ምርቶች
እና ተሸከርካሪዎች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ አራተኛ የበለፀጉ ሀገራት የገበያ ድርሻቸውን
ለማሳደግ እያደረጉት ባለው እሽቅድድም የህዝብ ብዛት እና አነስተኛ የመግዛት አቅም
ባላቸው ታዳጊ ሀገራት በዝቅተኛ ዋጋ ምርትን የመሸጥ ስትራቴጅ መከተላቸው ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 128


እንዲሁም በበለፀጉ ሀገራት ስትራቴጅካዊ ፋይዳ ባላቸው አንዳንድ የአምራች ዘርፎች
(ለምሳሌ የብረታብረት እና ኬሚካል ኢንዱስትሪ) ዘንድ የምርት መትረፍረፍ (over
capacity) መኖሩ ዋጋ ሰብሮ በአለም ገበያ የመወዳደር ሁኔታ ይስተዋላል፡፡ በአጠቃላይ
ስትራቴጃዊ አምራች ኢንዱስትሪ ንኡስ ዘርፎች ሊፈታተን በሚችል ደረጃ ገቢ-ምርቶች
የዳንፒንግ አዝማሚያ መታየቱ በጉዳዩ ዙሪያ ሰፊ እና ጥልቀት ያለው ምርምር
በማድረግ ፓሊሲ መቅረጽ አስፈላጊ እንደሆነ ያሳያል፡፡

አምራች ኢንዱስትሪው እና በመንግስታት የሚደጎሙ ገቢ-ምርቶች (subsidized


products)
መንግስታት ለሀገራዊ ኢንዱስትሪዎች በሚያደርጉት ድጎማ ገቢ-ምርቶ ተወዳዳሪነት
ከፍ በማድረግ ኢፍትሃዊ ውድድር ሊፈጥር ይቻላል፡፡ በአንፃሩ ድጋፍ እና ድጎማ
በአስተማማኝ ደረጃ የማያገኙ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች በጥራት፣ ዋጋ እና
አቅርቦት መጠን ብቁ ተወዳዳሪ ስለማይሆኑ የኪሳራ እና የመዝጋት አደጋ
ይጨምራል፡፡ ከበርካታ ታዳጊ እና የበለፀጉ ሀገራት ጋር ስናነፃፀር የሀገራችን አምራች
ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚደረግለት ድጋፍ እና ድጎማ አነስተኛ ነው፡፡ አሁን ባለው
የመንግስት ድጋፍና ማበረታቻ ፓሊሲ መሰረት ኤክስፖርት ተኮር ወይም ገቢ-
ምርቶችን የሚተኩ ኢንዱስትሪዎች በተናጠል (case by case) እና በበቂ ሁኔታ ድጎማ
ይቀርባል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ለምሳሌ ኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂው የድጋፍ
ትኩረት አቅጣጫ በሁለት ጉዳዮች ላይ ያጠነጠነ ሲሆን አንድ አምራች ኢንዱስትሪ
መሰረተ ልማት ማቅረብ ሲሆን ሌላው ደግሞ ለተመረጡ የኢንዱስትሪ ንኡስ-ዘርፎችን
ቅድሚያ ሰጥቶ መደገፍ ነው፡፡ ስለሆነም የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጅው ኤክስፖርት
ተኮር ወይም ገቢ-ምርት የሚተካ ንኡስ ዘርፍ እንደየ ባህሪያቸው እና ባበረከቱት
አስተዋጾ በተናጠል ድጎማ የሚያቀርብ አይደለም፡፡ የሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪ
በጥቅሉ ሶስት አይነት የማበረታቻ ፓኬጆች የሚቀርብለት ነው፡ የኢንቨስትመንት
ማበረታቻ፣ የኤክስፖርት ማበረታቻ እና ሌሎች ማበረታቻዎች ናቸው (MIT,2008b)::
እነዚህ ማበረታቻዎች በአብዛኛው ከቀረጥ እና ግብር ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡

በተባበሩት መንግስታት ልማት ፕሮግራም (UNDP) ድጋፍ የንግድና ኢንዱስትሪ


ሚኒስቴር በ2000 ዓ.ም ባስጠናው ጥናት መሰረት የድጎማ ድጋፍ የተደረገባቸው ገቢ-
ምርቶች መጠን 284 ሚሊዮን ብር እንደሚገመት ይገልጻል፡፡ ይህም ሀገራችን
ኢመፖርት ካደረገቻቸው አንድ አይነት ምርቶች ውስጥ ድጎማ የተደረገባቸው

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 129


ምርቶች12% ድርሻ አላቸው፡፡ የድጎማ ድጋፍ ኖሯቸው ኢምፖርት ከተደረጉ ምርቶች
ውስጥ የተቀነባበሩ ምግብ ነክ ምርቶች፣ የተፈበረኩ የብረታብረት ምርቶች፣ ፈርኒቸርና
ተያያዥ ምርቶች፣ የህክምና መሳሪያዎች እና መሰረታዊ ብረታብረት በዋናነት
ይጠቀሳሉ፡፡ በተያያዥ የንኡስ ዘርፍ የአማካኝ ድጎማ ህዳግ (subsidy margin 16%)
ሊሆን እንደሚችል ጥናቱ ያመለክታል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሀገራችን አምራች
ኢንዱስትሪ የእሴት ጭማሬ ድርሻ አነስተኛ በመሆኑ ድጎማ ተደርጎባቸው ኢምፖርት
የሚደረጉ ምርቶች በአጠቃላይ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅኖ ይፈጥራሉ ተብሎ
አይታሰብም፡፡ ሆኖም ከረጅም ጊዜ እይታ (long run perspective) ድጎማ
የተደረገባቸው ገቢ ምርቶች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅኖ እንደሚፈጥሩ እሙን
ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ ተደጉመው የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ የአምራች ኢንዱስትሪ
ዕድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እየፈጠሩ እንደሚገኝ መረዳት ይቻላል፡፡

ሌላው ከባለሙያዎች የተገኘ መረጃ እንደሚጠቁመው ከ90% በላይ የሚሆነው የሀገራችን


ገቢ-ምርት ከአንዱስትሪ የዳበሩ ሀገራት የሚመጣ በመሆኑ በአንድ በኩል የተመቻቸ
የንግድ ስርአትና መሰረተ ልማት ተጠቃሚ ሲሆኑ በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራቱ
ኤክስፖርት ለሚያደርጉ አምራች ኢንዱስትሪዎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ልዩ ልዩ
ድጎማ ማድረጋቸው የማይቀር ነው፡፡ ሁሉም ድጎማዎች ጎጅ ናቸው ለማለት
ባያስደፍርም በሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪ ላይ አልፎ አልፎ ጉዳት የሚያደርሱበት
አጋጣሚ ይኖራል፡፡ በተጨማሪ ድጎማ ተጠቃሚ ገቢ-ምርቶች ባልተመጣጠነ ዝቅተኛ
ዋጋ በመሸጥ በሀገር በቀል ኢንዱስትሪዎች ላይ አደጋ ያመጣሉ፡፡ ለዚህ ደግሞ
ምክንያቱ ድጎማው የገቢ-ምርቶችን የኪሳራ ወጭ በመሸፈን በቀላሉ ውድድራዊ ብልጫ
እንዲይዙ ስለሚረዳቸው ነው፡፡ በአንድ በኩል የተደጎሙ ገቢ-ምርቶን መግዛት ሸማቹ
ማኅበረሰብ በአነስተኛ ዋጋ እንዲገዛ እና የመንግስትን ቀረጥ ገቢ እንዲያድግ ጊዜያዊ
ጥቅም ሊፈጥር ይችላል፡፡ በሌላ በኩል አምራች ኢንዱስሪው ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት
ያለውን አስተዋፅኦ በመገደብ ዘላቂ ልማትን ሊያሰናክል ይችላል፡፡

አምራች ኢንዱስትሪ እና የገቢ- ምርቶች ድንገተኛ መትረፍረፍ (import surges)


የነፃ ገበያ ስርዐት ውስጥ ከፍትሃዊ ውድድር በማፈንገጥ በዝቅተኛ ዋጋ በድንገት ገበያን
የሚያጥለቀልቁ ገቢ-ምርቶች (import surges) ይስተዋላሉ፡፡ የገቢ-ምርት በድንገት
የሀገር ውስጥ ገበያን ማጥለቅለቅ የሚከሰተው የሀገራት የኢኮኖሚ ዘርፎች የማዋቀር
ለውጥ ሲያመጡ፣ የወቅታዊ አየር ሁኔታ ለውጥ ሲኖር እና የአለም ገበያ ሁኔታ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 130


መቀያየር (ለምሳሌ በአለም ገበያ ላይ የዕቃ ዋጋ መውረድ፣ የንግድ ፓሊሲ መቀየር
ወዘተ) እና በመሳሰሉት ምክንያቶች ሊሆን ይችላል፡፡ ሀገራት ቅፅበታዊ የገቢ-ምርት
ማጥለቅለቅ መከሰቱን ለማረጋገጥ የሶስት አመታት ገቢ ምርቶችን መጠን በተንቀሳቃሽ
አማካይ (Moving Average) በመለካት የገቢ ምርት የመጥለቅለቅ ስጋት በተፈጠረበት
አመት በ30% ከፍ ብሎ ሲገኝ ችግሩ መከሰቱን ሊያመላክት ይችላል፡፡ እንደሌሎቹ
ሁሉ የድንገተኛ ገቢ-ምርት መትረፍረፍ (import surges) አሉታዊ ጎን በሀገራችን በቂ
ትኩረት ያልተሰጠው እና የተዘነጋ ይመስላል፡፡ በመሆኑም ጉዳዩን ለመከታተል እና
ለመቆጣጠር የሚያስችል በግልፅ የተቀመጠ የፓሊሲ ማዕቀፍ አልተዘጋጀም፡፡ በአንጻሩ
ለኢንዱስትሪ ልማት ልዩ ትኩረት የሰጡ በርካታ ሀገራት በአንፃሩ የኢንዱስትሪ እና
የንግድ ፓሊሲያቸው አካል በማድረግ ችግሩን ለመቆጣጠር እየሰሩ ይገኛሉ፡፡

እንደ ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር (የ2000 ዓ.ም) ጥናት፣ የግል ባለሀብቱ አስተያት፣
የፓሊሲ ባለሙያዎች እይታ እና ሌሎች ተዛማጅ ሰነዶች መረጃ ከሆነ ድንገተኛ የገቢ-
ምርቶች ማጥለቅለቅ አልፎ አልፎ የሚስተዋል ችግር መሆኑን ይገልፃሉ፡፡ ለምሳሌ
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር (በ2000 ዓ.ም) ያስጠናው ጥናት መሰረት ድንገተኛ
የገቢ ምርቶች መጥለቅለቅ (import surges) ችግር እንደነበረ ድምዳሜ ላይ ደርሷል፡፡
ድንገተኛ የገቢ-ምርቶች ማጥለቅለቅ አሉታዊ ተፅዕኖ በአብዛኛው በአምራች ኢንዱስትሪ
ምርቶች ላይ ተከስቶ እንደ ነበር ያሳያል፡፡ ሆኖም ድንገተኛ የገቢ-ምርቶች ማጥለቅለቅ
መከሰቱ በሀገሪቱ አጠቃላይ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ላይ በጊዜያዊነት የጎላ
ችግር እንዳልፈጠረ ቢገልፅም በዘላቂ ልማት ላይ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል መረዳት
ያስፈልጋል፡፡

5.5.4 በአክሲዮን ማህበራት የተደራጁ አምራች ኢንዱስትሪዎች

የአክስዮን ማህበራት አደረጃጀት ከሌሎች አደረጃጀቶች በተሻለ ከፍተኛ እውቀት፣


ካፒታልና ቴክኖሎጅን የማቀናጀት ሚና እንዳለው ይታወቃል፡፡ ትንሽ የካፒታል አቅም
ያላቸውን ዜጎች በማሰባሰብ የረጅም ጊዜ ቁጠባ እና ኢንቨስመንት ባህል ያካብታል፣
የአደረጃጀት ባህሪው ከአክሲዮን ባለቤቶች ይልቅ በባለሙያዎች (professionals)
አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲመሩ ያስችላል እንዲሁም ግዙፍ እና ተወዳዳሪ
ኢንዱስትሪዎች እንዲፈጠሩ ያደርጋል፡፡ የሀገራችን የአምራች ኢንዱስትሪ ደግሞ
በግል ባለሀብቶች ተመራጭ ያልሆነበት ዋና ምክያት የላቀ ካፒታል፣ ቴክኖሎጅና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 131


እውቀት ስለሚጠይቅ ነው፡፡ አክሲዮን ማህበራት ይህን ችግር ለመቅረፍ አይነተኛ ሚና
አላቸው፡፡ በመሆኑም የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን በአክስዮን እንዲደራጅ መደገፍ እና
መቀስቀስ ከላይ የተገለፁትን ግብአቶች ለማሰባሰብ በማስቻል የስትራቴጂ ጠቀሜታ
ባላቸው ትላልቅ አምራች ኢንዱስትሪዎችን (ለምሳሌ ኬሚካል እና ብረታ ብረት)
ለማጎልበት እንደሚያስችል መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሚስተዋለው የካፒታል፣ እውቀት፣ ቴክኖሎጅ፣


አመራር፣ ዘመናዊ አደረጃጀት፣ ወዘተ ክፍተቶችን ለመሙላት ባለሀብቱን በአክሲዮን
በማቀናጀት ለመስራት የተሄደበት እርቀት በቂ አይደለም፡፡ የአክስዮን ማህበራትን
ለመደገፍ እና ለመቆጣጠር በማሰብ የንግድ ሚኒስቴር የአክሲዮን ማህበራት እና የንግድ
ዘርፍ ማህበራት ጉዳይ ዳይሬክቶሬት አደራጅቶ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ነገር ግን
የግል ባለሀብቱ በበቂ ደረጃ በአክስዮን ማህበራት ተደራጅቶ እንዲሰራ የመቀስቀስ እና
ድጋፍ የማድረግ ጥረት ውስን ሆኖ ይገኛል፤ እንዲሁም በአክስዮን ማህበራት
አደረጃጀት ውስጥ የሚፈጠሩ ማነቆዎችን በወቅቱ ለመፍታት የተሰራው ተጨባጭ ስራ
እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ በአክስዮን ማህበራት ተደራጅተው የሚሰሩ የአምራች
ኢንዱስትሪዎች ያለመጠናከር በምክንያትነት የሚቀርቡ ማነቆዎች፡1) የአክስዮን
ማህበራት አስተዳደር እና አመራር (corporate governance) ችግሮች፣ 2) የአክስዮን
ማህበራቱን ለመቆጣር የወጡ ህጎች ወቅታዊ እና በአግባቡ ተፈጻሚ አለመሆን እና 3)
መንግስት ለአክስዮን ማህበራት የሚያደርገው ድጋፍ እና ቁጥጥር ደካማ መሆን
ናቸው፡፡

አንደኛው ችግር የአክስዮን ማክበራት መልካም አስተዳደር ዕጦት ጎልቶ የሚታይበት


አደረጃጀት መሆኑ ነው፡፡ በአክስዮን ማህበራት ቁልፍ ባለድርሻ አካላት መካከል
የሚፈጠረው ንትርክ እና ትርምስ ሲሆን የአክስዮን ማህበር ቦርድ አባላት፣ አመራር እና
አክስዮን አባላትን ሚዛናዊ በሆነ መንገድ ለማስተናገድ የሚያስችል አክስዮን ማህበራት
ውስጥ መልካም አስተዳደር እጦት ነው፡፡ ለአክስዮን ምስረታ የሚያስፈልጉ ዝርዘር
ህጋዊ ጉዳዮችን አለመረዳት፣ የመስራች አባላት እና የቦርድ ጥቅማጥቅሞች የተጋነነ
መሆን፣ አነስተኛ ድርሻ ያላቸውን አባላት ውክልና አልባ መሆን፣ አንዳንድ ቦርድ
አባላት ማህበሩን ስራ ከግል ስራ ጋር መያያዝ ማህበሩን መበዝበዝ፣ በአመራር እና
በቦርድ መካከል የጥቅም ግጭት መስተዋል፣ ጉባኤዎች ወቅቱን ጠብቆ ያለመከናወን
እና የመሳሰሉት ችግሮች ይታያሉ፡፡ አልፎ ተርፎም በአክስዮን ማህበራት አመራሮች፣

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 132


ቦርድ አባላት እና የአክስዮን ባለቤቶች መካከል በሚፈጠር አለመግባባት ምክንያት
የሀገር ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዳይውል አድርጎታል፡፡

በሁለተኛ ደረጃ አክስዮን ማህበራትን ለመቆጣጠር የወጡት ህጎች ክፍተት


ስለሚስተዋልባቸው ለማህበራቱ መጠናከር ምቹ ሁኔታ መፍጠር አልተቻለም፡፡ ንግድ
ሚኒሰቴር ከንግድ ህጉ ወይም ከምዝገባ እና ፈቃድ አዋጅ ጋር የተያያዙ ክፍተቶችን
ለመሙላት ማሻሻያዎች አለማድረጉ ጎልቶ የሚታይ ችግር ነው፡፡ ለአብነት በንግድ ህጉ
ለአክስዮን ማህበራት በአይነት የሚደረጉ መዋጮዎች ወደ ማህበሩ የዝውውር ጊዜ ገደብ
አለመኖር፣ በህጉ ውስጥ የሚስተዋሉ የሕግ ክፍተቶችን ለመድፈን ደንብና መመሪያ
የማውጣት አግባብነት አለመደንገጉ እና አክሲዮን ገዥዎች ገንዘቤ ይመለስልኝ
ጭቅጭቅ ለመቅረፍ የሚያስችሉ ድንጋጌዎች አለመካተታቸው እና ሌሎችም
ይገኙበታል፡፡

ሌላው ንግድ ሚኒስቴር የአክስዮን ማህበራትን የስራ እንቀስቃሴ በተመለከተ ግንዛቤ


መፍጠር፣ መደገፍ፣ መከታተል፣ መቆጣጠር እና አስፈላጊ ርምጃዎችን የመውሰድ
ስልጣን እና ሀላፊነት እንዳለው ይታወቃል፡፡ ነገር ግን የአክስዮን ማህበራት አሰራር
እና ፋይዳ በተመለከተ ለህብረተሰቡም ሆነ ለአክስዮን ማህበር አባሎች በቂ የሆነ
ግንዛቤ እና ስልጠና ያለመስጠት፣ በቂ አዋጭነት ጥናት አጥንተው አክስዮን መጀመር
የሚያስችል ቴክኒክ ድጋፍ አናሳነት፣ ስራ ለመግባት ዳተኝነት የሚያሳዩትን ማህበራት
ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ሆኖ እርምጃ ያለመውሰድ፣ የአክስዮን ማህበራት ምዝገባ
ስርአቱ በክልሎች መካከል ወጥነት እንዲኖር ያለማድረግ እና ከጅምሩ ጥራት ያለው
ማህበር እንዲመሰረት የሚደረገው ጥረት አናሳ መሆን፣ የአክስዮን ማህበራት አሰራር
በህጋዊ አግባብ መፈፀማቸውን ክትትል እና ቁጥጥር የማድረግ አፋጣኝ እርምጃ
ለመውሰድ የአቅም ችግር መስተዋል ናቸው፡፡

በተጨማሪም በየደረጃው ካሉ የመንግስት አካላት ክትትል እና ቁጥጥር ማነስ የተነሳ


የሀሰት አክስዮን ማህበር አቋቁመናል በማለት ገንዘብ ሰብስቦ መሰወር ይስተዋላል፤
የተቋቋሙትም በፍጥነት ወደ ስራ ያለመግባት እና በአባላት መካከል ግጭት እና
ንትርክ በስፋት መስተዋሉ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ አክስዮን ማህበራት
እንዲጠናከሩ የማህበራቱን ፋይዳ የማስተዋወቅ እና የመደገፍ ስራ አናሳ መሆኑ እና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 133


ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት አለመሰራቱ አክስዮን ማህበራት ለአምራች ኢንዱስትሪ
ዕድገት መጫዎት የነበረበትን ሚና ዘገምተኛ እንዲሆን አድርጎታል፡፡

በአጠቃላይ ከላይ የተዘረዘሩት ችግሮች ዜጎች በአክስዮን ማህበራት ተደራጅተው


ለሀገራቸው አምራች ኢንዱስትሪ እድገት ትልቅ አስተዋፆ እንዳያበረክቱ የበኩሉን
አስተዋጾ አበርክቷል፡፡

5.5.5 የንግድ ፈቃድ እና ስምሪት

በመጀመሪያ ደረጃ የምዝገባ እና ፈቃድ አገልገሎት ስርአትን ቀልጣፋና ፍትሃዊ


ማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብት የሚጠበቅበትን ቅድመ ሁኔታ
አሟልቶ ምርት ማምረት እንዲችል፣ ብሎም ባለሀብቱን በመቆጣጠር እና በመደገፍ
ለኢኮኖሚ ልማት ምቹ የሆነ የንግድ ሰርአት ለመገንባት ያስችላል፡፡ ከዚህ አኳያ
የንግድ ሚኒስቴር እና ንግድ ቢሮዎች በዋናነት የንግድ ምዝገባና ፈቃድ የመስጠት፣
የማደስ፣ የማሻሻል እና የመሰረዝ ተግባራትን ይከውናሉ፡፡ እንዲሁም ከዚህ ተግባር ጋር
በተያያዘ ስልጣን የተሰጣቸው የሚኒስቴር እና ሌሎች መ/ቤቶች የንግድ ፈቃድ
በመስጠት እና በመሰረዝ ስራ ይሰራሉ፡፡ ቀልጣፋ እና ፈጣን የንግድ ምዝገባ እና
ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት እንዲሁም ከተገልጋዮች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት
በርካታ ማሻሻያዎች በንግድ ሚኒስቴር እና ክልል ቢሮዎች ተደርገዋል፡፡ ለአብነት
የክፍያ ስርአትን መቀየር፣ ዘመናዊ የወረፋ ስርአት መዘርጋት፣ የንግድ ስም ምዝገባ
ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ማውረድና የምዝገባና ፈቃድ አሰጣጡ ለበርካታ
ተጋልጋዮች ተደራሽ የማድረግ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡

ነገር ግን የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ ለማውጣት፣ ለማሳደስ እና ለመሰረዝ በተመለከተ


ያለው አገልግሎት አሰጣጥ ዘገምተኛ እና ተደራሽነቱም ውስን እንደሆነ ባለሀብቱ
ይገልፃል፡፡ በተጨማሪም ከቁጥጥር እና ክትትል ማነስ የተነሳ አስፈላጊውን መስፈርት
ሳያሟሉ የንግድ ፈቃድ ማውጣት፣ ንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው ምርት ማምረት እና
ንግድ ፈቃድ ባወጡበት ዘርፍ ያለመሰማራት ችግሮች ይታያሉ፡፡ይህ ችግር በተለይ
በክልሎች አካባቢ ጎልቶ የሚታይ ችግር ሆኗል፡፡ ሌላው በህገ ወጥ መንገድ የንግድ
ፈቃድን ለውጭ ሀገር ዜጎች የማከራየት እና የንግድ ፈቃድ መስጠት ችግር መኖር
ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 134


የሀገራችን ንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ ለመረዳት እንዲቻል
የሀገራትን የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ ቅልጥፍና የአለም ባንክ ያነፃፀረበት ጥናታዊ
ሪፓርት (Doing Business Report 2016) ለመቃኘት ተሞክሯል፡፡ በጥናቱ ሪፓርቱ
ንግድ ለመጀመር የሚያስፈልጉ ቅደም ተከተሎች (procedures)፣ የሚወስደው ጊዜ፣
ለምዝገባና ፈቃድ ወጭ እና ንግድ የመጀመሪያ መነሻ ካፒታል በመለኪያነት
በመውሰድ ንፅፅር አድርጓል፡፡ በዚህ መሰረት በ2008 ሀገራችን ከ189 ሀገራት 176ኛ
ደረጃ ሲሰጣት ይህ ደረጃ ከ2007 ካላት ደረጀ (ከ189 ሀገራት 170ኛ ደረጃ) ያነሰ
መሆኑን ያሳያል፡፡ በተጓዳኝ በሀገራችን የሚገኝ አንድ አነስተኛ እና መካከለኛ
ኢንተርፕራይዝ (ማለትም ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር) የንግድን ምዝገባና ፈቃድ
ለማውጣት በአማካይ 19 ቀናት ይወስድበታል፤ ለንግድ ምዝገባና ፈቃድ አንድ ተቋም
የሚያወጣው ወጭ ደግሞ 76% የሀገሪቱን ነፍስ ወከፍ ገቢ ይገመታል፡፡ አንድ የሀገር
ውስጥ ባለሀብት ንግድ ፈቃድ ወስዶ ለመሰማራት የንግድ ሚኒስቴር፣ የሰነዶች
ማረጋገጫና ምዝገባ ቢሮ፣ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን (እንደየ አስፈላጊነቱ ለቫት
ለመመዝገብ እንደገና ጉምሩክ መሄድን ይጠይቃል)፣ ንግድ ምዝገባ (ንግድ ሚኒስቴር)፣
ባንኮች፣ ማህተም የሚያዘጋጅ አካላት፣ ካሽ ሪጅስተር ማሽን አቅራቢ፣ ሶፍቴዊር አቅራቢ
እና የመሳሰሉትን ተቋማት መጎብኘት ይኖርበታል፡፡ በአለም ባንክ መስፈርት ንግድ
ምዝገባና ፈቃድ ማውጣት፣ ንግድ ፈቃድ ማሳደስ እና ማሻሻል፣ ንግድ ፈቃድ መሰረዝ
እና ንግድ ስም አሰጣጥ ወዘተ አሰራር ከሌሎች ሀገራት ጋር ሲነፃፀር ኋላ-ቀር እና ብዙ
መሻሻል የሚያስፈልገው መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ በጥቅሉ በንግድ ምዝገባ እና
ፈቃድ አገልግሎት የሚስተዋለው ችግር በአገልግሎት ሰጭ ተቋማት ሰራተኞች ወይም
በባለሙያዎች ዘንድ ያለ ቁርጠኝነት እና አቅም ማነስ፣ ለንግድ ማህበረሰብ በቂ መረጃ
እና ስልጠና ተደራሽ አለመሆን፣ የሚመለከታቸው መ/ቤቶች የቅንጅት ጉድለት
በዋቢነት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ሌላው ጉዳይ የንግድ የፈቃድ ስምሪት ሚዛናዊ በማድረግ የገበያ ውድድርን ውጤታማ
እና ብቃት ያለው ማድረግ ነው፡፡ በገበያ ሰንሰለት ላይ የተጨናነቀ የንግድ ስምሪት
የሚስተዋልበትን ዘርፍ (crowd out sub-sector) በመለየት እና የሳሳ ስምሪት ወዳለበት
ዘርፍ እንዲሰማራ በማድረግ ቀልጣፋና ውጤታማ የንግድ ስርአት ማዳበር ይቻላል፡፡
የንግድ ፈቃድ ድልድል ማድረግ ሌላው ፋይዳ ሞኖፖሊ፣ በህብረት መወሰን፣ የገበያ
የበላይነትን ያላግባብ መጠቀም እና ጎጅ ውህደት የመሳሰሉ ፀረ-ውድድር ተግባራትን
ለመከላከል ያግዛል፡፡ ነገር ግን በሀገራች ያለው የንግድ ፈቃድ አሰጣጥ የሀገር ውስጥ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 135


ባለሀብቱ የሚሰማራበትን ዘርፍ አቅጣጫ ለመወሰን ጥረት ሲያደርግ እና የኢኮኖሚ
ልማት በሚያግዝ መልክ የንግድ ፈቃድ ድልድል ሲደረግ አይስተዋልም፤ ምንም
እንኳን በነፃ ኢኮኖሚ ስርአት ባለሀብቱ በሚያዋጣው የንግድ ዘርፍ የመሰማራት መብት
ቢኖረውም፡፡ በተለይ በገበያ ሰንሰለት ላይ ከአምራች ኢንዱስትሪ ጋር ቀጥተኛ ትስስር
ያላቸው ዘርፎች የንግድ ስምሪት ሚዛናዊነት ተዘንግቶ ይገኛል፡፡ ለምሳሌ በአስመጭነት
ንግድ ዘርፍ ፈቃድ ወስዶ የሚንቀሳቀውን ባለሀብት ስምሪት መቃኘት ይቻላል፡፡ ከታች
በግራፉ እንደሚታየው አምስት የአስመጭነት ንግድ ዘርፎች (ማለትም ፈርኒቸር፣
የግንባታ ግብአት፣ ተሸከርካሪ፣ የአምራች ኢንዱስትሪ ጥሬ እቃ እና የኢንዱስትሪ
መለዋወጫ እቃ) የተሰማራው ባለብት ብዛት ላይ ንፅፅር ተደርጓል፡፡

ግራፍ 5.5 በበተለያዩ ንግድ ዘርፎች በአስመጪነት የተሰማሩ ባለሀብቶች ብዛት

የተሽከርካሪ እና የኮንስትራክሽን ግብአት አስመጭዎች ስምሪት ላቅ ያለ ቁጥር ይዞ


እናገኛዋለን፡፡ በመቀጠል የፈርኒቸር አስመጭዎች ቁጥር በርከት ብሎ ይገኛል፡፡
ሆኖም ለአምራች ኢንዱስትሪው ጥሬ እቃ እና መለዋወጫ የሚያገለግሎ ግብአቶችን
አስመጭ አካላት አሃዝ አነስተኛ ሆኖ ይገኛል፡፡ ከዚህ አሃዝ የምንረዳው በአንድ በኩል
የአምራች ኢንዱስትሪ ቁጥር ትንሽ በመሆኑ ከዘርፉ የግብአት ፍላጎት አንጻር አነስተኛ
ቁጥር ያላቸው አቅራቢዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ በሌላ በኩል አስመጭዎች በፍጆታ
እቃዎች እና ዳጎስ ያለ ትርፍ በሚያስገኙ ዘርፎች ላይ ማዘንበሉን ያሳያል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 136


5.5.6 የመንግስት ድጋፍ እና ገበያ ከለላ

በአምራች ኢንዱስትሪ ለተሰማራው ባለሀብት የኢንቨስትመንት፣ የኤክስታርት እና


ሌሎች ማበረታቻዎች ከሞላ ጎደል ይቀርባሉ፡፡ የመንግስት ማበረታቻዎች የኤክስፖርት
እና ገቢ-ምርት የሚተኩ ዘርፎችን ለማስፋፋት እና ለማሳደግ ያለሙ መሆናቸው እሙን
ነው፡፡ ሆኖም ግን አንደኛ በመንግስት የሚቀርቡ ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች የአምራች
ኢንዱስትሪ እሴት ሰንሰለት ላይ በማይጣረስ ወይም በየማይጋጭ ሁኔታ ተመጋጋቢ እና
የታለመለትን አላማ ከመምታ አንፃር የጎላ ክፍተት ይስተዋላል፡፡ ይህ ችግር
በኤክስፖርትም ሆነ ገቢ ምርትን በሚተኩ ምርቶች ላይ የሚስተዋል ነው፡፡

አንደኛ የኤክስፖርት ዘርፍን ስንመለከት በተለያዩ ተቋማት የሚቀርቡ የኤክስፖርት


ማበረታቻዎች በተቀናጀ ሁኔታ የተሟላ ማበረታቻ ማቅረብ፣ ተግባራዊነቱን መከታተል
እና ማስተካክያ እርምጃ ሲወስዱ አይስተዋልም፡፡ ለምሳሌ የኤክስፖርት ዘርፍን
ለማበረታታት ከውጭ ለሚገቡ ጥሬ ዕቃዎች እና የካፒታል እቃዎች በየደረጃው
የታክስና ቀረጥ ነፃ እንዲሁም የፋይናንስ ድጋፍ ያደረጋል፡፡በተጨማሪ ለአንዳንድ
የአምራች ንኡስ ዘርፎች በቂ የግብአት አቅርቦት ለማረጋገጥ ወደ ውጭ በሚላክ ጥሬ
እቃዎች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ ተጥሏል፡፡ ሆኖም መንግስት የውጭ ንግድ ለማበረታታት
የሚያደርገውን ድጋፍ እንደ ገበያ ከለላ በመጠቀም ምርትን ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ
በሀገር ውስጥ ገበያ መሸጥ አዋጭ ሆኖ ስለሚያገኘው በሀገር ውስጥ ገበያ ተወስኖ
የመቅረት አዝማሚያ ይታያል፡፡ ለምሳሌ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪ
ላለፉት አራት ዓመታት የውጭ ምንዛሬ ግኝት እየተቀዛቀዘ ለመሄዱ ከተጠቀሱት
ምክንያቶች አንዱ የሀገር ውስጥ የገበያ ዋጋ ከውጭው ገበያ በልጦ በመገኙቱ
ፋብሪካዎች ፊታቸው ወደ ሀገር ውስጥ ገበያ ማዞር መጀመራቸው ነው (ጨርቃ ጨርቅ
ልማት ኢንስቲትዮት 2003-2006)፡፡ በተያያዘ ለአምራቹ በቂ በግብአት ለማግኝት ጥሬ
እቃዎች ኤክስፖርት ቀረጥ መጣል ተገቢ ቢሆንም ጥሬ እቃ አቅራቢው በፍትሃዊ ዋጋ
ለአምራቹ እንዲያቀርብ ስርአት መዘርጋት ካልተቻለ የጥሬ እቃ ጥራትና መጓደል
ብሎም አቅራቢው ከገበያ የመውጣት አደጋ ያጋጥመዋል፡፡ ለምሳሌ የአምራቹን ጥሬ
እቃ ፍላጎት ለማሟላት መንግስት ያደረገው የፓሊሲ ለውጥ ቀደም ሲል በጥሬ ጥጥ እና
ቆዳና ሌጦ አቅራቢዎች ላይ አሉታዊ ተጽኖ ፈጥሮ እንደነበር አይዘነጋም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 137


ሁለተኛ ገቢ-ምርትን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች ድጋፍ በተመሳሳይ
በኢንዱስትሪው እሴት ሰንሰለት ላይ የተመጋጋቢነት እና የቅንጅት ችግር የሚስተዋል
በመሆኑ ኢ-ፍትሃዊ የገበያና ንግድ ውድድር እንዲፈጠር ያደረገበት አጋጣሚዎች
አሉ፡፡ ለምሳሌ ከውጭ የሚገቡ በከፊል ያለቁ እቃዎችን ለምርት በግብአትነት
የሚጠቀሙ ፋብሪካዎች (የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች) እና በቀጥታ ለመኪና
መለዋወጫነት የሚያቀርቡ አስመጭዎች ተቀራራቢ ቀረጥ እንዲከፍሉ ስለሚደረጉ
የማምረቻ ወጭያቸው እንዲያሻቅብ ማድረጉ ደንበኞች (በተለይ ከቀረጥ ነጻ የማስገባት
መብት ያላቸው) ቀጥታ ከውጭ ማስመጣትን ምርጫቸው መሆኑን ይናገራሉ፡፡
ሌላው የስታፋ ብረት ግብአት አቅራቢዎችን ለመደገፍ (ማለትም የገበያ ከለላ
ለመስጠት) መንግስት በገቢ- የስታፋ ብረት ጥሬ እቃ ላይ ቀረጥ በመጣሉ የተነሳ
በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ እቃ አቅራቢዎች ጥራትና ስታንዳርዱን ያልጠበቀ ጥሬ እቃ
በማቅረባቸው ለስታፋ ብረት አምራች ፋብሪካዎች ለከፍተኛ ወጭና ኪሳራ
መዳረጋቸውን እንዲሁም በጥራትና ዋጋ ችግር ከውጭ ከሚገቡ ምርቶች ጋር መወዳደር
እንዳልቻሉ ይገልጻሉ፡፡

በሌላ በኩል የገቢ-ምርቶች ቁጥጥር ፓሊሲ በዋናነት ያተኮረው የመንግስትን የውጭ


ምንዛሬ እጥረት እና የቀረጥ ገቢ ከፍ ከማድረግ አንጻር ነው ማለት ይቻላል፡፡
ምክንያቱም በልዩ ሁኔታ ገቢ-ምርቶች የሚተኩ ወሳኝ ንኡስ ዘርፎችን የገበያ ከለላ
ለመስጠት በማሰብ የሚጣል ቀረጥ ውስን መሆኑ ነው፡፡ ሌላው ቀረጥ ነክ ያልሆኑ የገበያ
ከለላ ፓሊሲዎች በውል ተለይተው ተግባራዊ የሚደረጉ አይደሉም፡፡ ለአብነት ቀረጥ
ነክ ያልሆኑ የገበያ ከለላ ፓሊሲዎችን (በገቢ ምርቶች ላይ መጠን መወሰን፣
በመንግስት ግዥ ያለማካተት፣ ልዩ ደረጃና ጥራት መስፈርት ማስቀመጥ፣ አስገዳጅ ሀገር
ውስጥ ግብአት መጠቀም፣ ፀረ-ዳንፒንግ እርምጃ፣ ከተወሰኑ አምራቾች ብቻ ማስመጣት፣
ወዘተ) በመጠቀም በተቀናጀ ሁኔታ ከለላ ለሚሹ የሀገር ውስጥ ምርቶች ድጋፍ አቅርቦት
ውስን ሆኖ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ የመንግስት ማበረታቻ እና የገበያ ከለላ አፈፃፀም በቅንጅት መቆጣጠርና


መከታተል ካልተቻለ ፍትሃዊ ላልሆነ ውድድር የሚዳርግ እና የንግድ ስርአቱን ሊያዛባ
እንደሚችል ያስረዳናል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 138


5.5.7 የመንግስት የግዥ ስርአት

የአንድ ሀገር የግዥ ፖሊሲ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ ካላቸው


የመንግስት ተግባራት (functions of government) አንድ ነው፡፡ የመንግስት ግዥ
ስርዐት ለአምራች ዘርፍ ተወዳዳሪነት፣ ምርታማነትና እና የቴክኖሎጅ አቅም
ለማጎልበት አጋዥ የፓሊሲ መሳሪያ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ስኬታማ የሆኑ ሀገራት የግዥ
ፓሊሲያቸውን ለኢንዱስትሪ ልማት አሟጠው ከመጠቀም አልፈው ለቴክኖሎጂ
እድገትና ፈጠራ አቅም ግንባታ በቀጥታ ተጠቅመውበታል፡፡ በተመሳሳይ በፈጣን
እድገት ላይ የሚገኙት የኤሲያ ሀገራት የመንግስት ግዥ ፖሊሲያቸውን ለጀማሪ
ኢንተርፕራይዞች ከለላ፣ አለማቀፍ ተወዳዳሪነት እና የስራ ፈጠራ ዕድል ማሳደጊያ
እየተጠቀሙበት ይገኛል፡፡

የግዥ ፓሊሲ ድጋፍ ለፈጣን ኢንዱስትሪ እድገት ከሌሎች ድጋፎች በተሻለ ውጤታማ
እንደሆነ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ለምሳሌ የመንግስት ጣልቃ ገብነት ላይ ምርምር ያደረጉ
ባለሙያዎች እንደሚሉት የኢንዱስትሪ ልማት ለማፋጠን የግዥ ድጋፍ ከሌሎች
የድጋፍ ማእቀፎች (ማለትም የግብር እፎይታ፣ብድር፣ ቀረጥ ነፃ ድጋፍ፣ ስልጠና ወዘተ)
ተመራጭ ነው፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ መንግስት ከማንኛውም አካል በላቀ ሁኔታ
መጠነ-ሰፊ ግዥ ስለሚፈፅም በምርት ገበያ በኩል (demand side effect) ቀጥተኛ
ተፅኖ መፍጠር መቻሉ ሲሆን የሌሎች ማበረታቻና ድጋፍ ተፅኖ ከሞላ ጎደል በምርት
ግብአት በኩል (supply-side effect) በመሆኑ ነው በማለት ይከራከራሉ፡፡ ሌላው ወጭ
ቆጣቢ፣ ውጤት ተኮር፣ ውድድርና ግልፅ አሰራርን ሳያጓድል አምራች ኢንዱስትሪውን
ለመደገፍ መጠቀም ከፍተኛ ቱርፋት አለው፡፡ የመንግስት ግዥ የኢንዱስትሪ ዘርፍን
አመታዊ እድገት እስከ 5% ከፍ ሊያደርገው እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በግዥ ፓሊሲ ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ሂደቶች ማለትም በጨረታና ውል ማስከበሪያ፣


በጨረታ ሰነድ ግምገማ መስፈርት፣ በቅድመ ክፍያ እና ውል አስተዳደር እና
በመሳሰሉት ልዩ ድጋፍ ስልት በማካተት የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪውን
ተወዳዳሪና ምርታማ ማድረግ ይቻላል፡፡ ለአብነት 1) በዋጋ እና በብቃት መስፈርቶች
ልዩ አስተያየት (preferential treatment) በማድረግ የሀገር ውስጥ ምርትን መደጎም፤ 2)
የሀገር ውስጥ ምርትን መንግስታዊ ተቋማት እንዲገዙ ሬጉላቶሪ ማዐቀፍ በመደንገግ
(Domestic preference)፤ 3) የውጭ ሀገር ጨረታ አሸናፊዎች በፕሮጀክት ትግበራ ጊዜ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 139


የተወሰነ እጅ በሀገር ውስጥ ካፒታል እቃ እንዲያመርቱ እና ከሀገር ውስጥ ግብአት
እንዲጠቀሙ ማድረግ (Domestic content requirement)፣ 4) የግዥ ፍላጎትን እና
መጠን አመላካች ዕቅድ ቀድሞ መረጃ ተደራሽ ማድረግ (planned and pre-
announced public procurement) ሀገራዊ ባለሀብቱ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርግ
ሁኔታዎችን ማመቻቸት፣ 5)ለሀገራዊ ባለብቱ የመጨረታ ሰነድ ዝግጅት ቴክኒካዊ
ድጋፍ፣ የገበያ መረጃ እና ቴክኒካዊ ስልጠና ተደራሽ ማድረግ እና የመሳሰሉትን
ይይዛል፡፡

የፌደራል መንግስት ግዥ ፓሊሲ


ከ1997 ዓ.ም ቀደም ባሉት ጊዚያት በሀገር አቀፍ ደረጃ እራሱን የቻለ የመንግስት ግዥ
ፓሊሲ አልነበረም፡፡ ከሞላ ጎደል የመንግስት ግዥ የሚፈጸመው በፍትሃብሄር ህግ እና
በገንዘብ ሚኒስቴር አዋጅና መመሪያ መሰረት ነበር፡፡ በ1997 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ
የፊደራል መንግስት ግዥ ፓሊሲ የተቀረፀ ሲሆን የግዥ ስርአቱን የሚወስን እና
የሚቆጣጠር የግዥ ኤጀንሲ እንዲቋቋም አስችሏል፡፡ በ2001 ዓ.ም የኤጀንሲውን ስልጣን
እና ሃላፊነት በማስፋት አዲስ የግዥ ፓሊሲ "የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር
አዋጅ" ተነድፏል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በ2002 ዓ.ም የግዥ መመሪያ፣ በ2003 ዓ.ም
ማኑዋል እና መደበኛ የጨረታ ሰነዶች ተዘጋጅተው በተግባር ውለዋል፡፡ በተጨማሪም
በ2008 ዓ.ም የግዥ አፈፃፀም መመሪያ ላይ ማሻሽያ ተደርጎ እየተሰራበት ይገኛል፡፡
ይህ የሚጠቁመን የፊደራል የግዥ ፓሊሲ ይዘት በሂደት እየተሻሻለ እና ኤጀንሲው
ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀት እየፈጠረ መምጣቱን ነው፡፡

ሆኖም ግን የግዥ ፖሊሲው በአግባቡ የኢንዱስትሪ ልማት መቆጣጠያ መሳሪያ ሆኖ


እንዲያገለግል ጠንካራ እና ደካማ ጎኑን መፈተሸ አስፈላጊ ነው፡፡ በመጀመሪያ ሀገራችን
መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለመቀላቀል የኢንዱስትሪ ልማት (በተለይ ደግሞ
የአምራች ኢንዱስትሪ) የህልውና ጉዳይ መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ የግዥ ፓሊሲ
ተልዕኮውን ለማሳካት ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ ማገልገል ይጠበቅበታል፡፡ ሁለተኛ እንደ
ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት የግዥ ፓሊሲ አውጭዎች እና ባለሙያዎች የግዥ
ስርአቱ ወጭ ቆጣቢ፣ ውጤት ተኮር፣ ፍትሃዊ፣ ግልፅ እና ነፃ-ውድድር የሰፈነበት
እንዲሆን ቢጥሩም ፓሊሲው የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪውን ለመደገፍ የሚያደርጉት
ርብርብ ውስንነት ይታይበታል፡፡ ምክንያቱም ሀገራቱ መልካም አስተዳደርን እና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 140


ኢንዱስትሪ የመደገፍ መርህን በግዥ ስርዐት ውስጥ አመጣጥኖ ለመስራት መቸገራቸው
በዋናነት ይጠቀሳል::

ስለዚህ የኢትዮጵያ የፌደራል መንግስት ግዥ ፓሊሲ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ


ለተሰማራው የሀገር ውስጥ ባለሀብት ከመደገፍ አኳያ ያሉ ጠንካራ እና ደካማ ጎን
ለማወቅ እንዲቻል የግዥ አዋጆችን፣ መመሪያዎችን፣ ማኑዋሎችን፣ የእቃ ጨረታ
ሰነዶች እና ሌሎች ሰነዶችን ይዘት መፈተሸ ተገቢ ነው፡፡ እንደሚታወቀው የፌደራል
መንግስት ከፍተኛ አመታዊ በጀት በመመደብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረተ
ልማቶችን በመዘርጋት ላይ ይገኛል፡፡ በተጓዳኝ ሀገራችን ላለፉት አስር አመታት ፈጣን
የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገቧን ተከትሎ የመንግስት የገቢ ምንጭ ከጊዜ ወደ ጊዜ
እያደገ ሄዷል፡፡ ለምሳሌ ከግብርና ግብር-ነክ ካልሆኑ የገቢ ምንጮች የሀገር ውስጥ ገቢ
ግኝት በ2004 ዓ.ም 124.1 ቢሊዮን ነበር፡፡ ይህ አሃዝ በ2007 ዓ.ም ወደ 186.6 ቢሊዮን
ብር ሲያድግ በ2009 ዓ.ም 279.5 ቢሊዮን ብር ከፍ ይላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በተመሳሳይ በ2004 ዓ.ም 137.2 ቢሊዮን ብር መንግስት አጠቃላይ በጀት (ከሀገር
ውስጥ የተገኘ ገቢ እና የለጋሽ ሀገራት ድጋፍ በማጣመር) መድቦ እንደ ነበር
ይታወቃል፡፡ በ2007 ዓ.ም የመንግስት አጠቃላይ በጀት 230.5 ቢሊዩን ብር ከፍ ብሎ
ነበር፡፡ ሌላው መንግስት ከሚመድበው አመታዊ በጀት (government expenditure)
ውስጥ የግዥ ወጭ ከፍተኛውን ድርሻ ይዞ ይገኛል፡፡ በመሆኑም መንግስት በአማካኝ
64% ያህሉን አመታዊ በጀት ለግዥ ተግባር ፈሰስ እንደሚያደርግ ይገመታል፡፡
በልማት ድርጅቶች በኩል ለግዥ የሚውለው ገንዘብ ሲካተት ደግሞ የመንግስት ግዥ
መጠን ከተጠቀሰው በላይ ላቅ ያለ እንደሚሆን መረዳት ይቻላል፡፡ በአጠቃላይ
የሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ የሚነግረን የመንግስት ተቋማት ለዕቃ፣ ለግንባታ ስራ እና
አገልግሎት ለመግዛት የሚያፈሱት ገንዘብ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ነው፡፡
ስለዚህ ፓሊሲው አላማ የግዥ መልካም አስተዳደር ማስፈን እና አምራች ኢንዱስትሪ
ተኮር ድጋፍን አጣምሮ ከተነደፈ የመንግስት የግዥ አቅም ማደግ ለኢንዱስትሪ ልማት
እንደ መልካም አጋጣሚ የሚወስድ ነው፡፡

የፊደራል መንግስት ግዥ ፖሊሲ በሀገር ውስጥ የተመረቱ ምርቶችን፣ ጥቃቅንና


አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን፣ በግንባታ ዘርፍ ስራ እና በምክክርና ሌሎች አገልግሎቶች
የተሰማሩ ሀገራዊ ኩባንያዎች ለመደገፍ እና ለማሳደግ የልዩ አስተያየት (preferential
treatment) ማዕቀፍ አስቀምጧል፡፡ ፓሊሲው የመንግስት መስሪያ ቤቶች ጨረታ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 141


በሚያወጡበት ወቅት የሀገር ውስጥ የተመረተ ምርት አቅራቢ ወይም አገልግሎት ሰጭ
ተቋም በቂ ተሳትፎና ውድድር ማድረጋቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው ይጠቁማል፡፡
በተጨማሪ በግልፅ ጨረታ ግዥ፤ በመወዳደሪያ ሀሳብ መጠየቂያ የሚፈፀም ግዥ፣
በሁለት ደረጃ የሚፈፀም ግዥ እና በውስን ጨረታ ግዥ ዘዴዎች አማካኝነት ግዥ
ሲከናወን የልዩ አስተያየት (preferential treatment) ተግባራዊ እንደሚሆን ይገልፃል፡፡
የልዩ አስተያየቱ በዋናነት በዋጋ (price) ላይ የተመሰረት ድጎማ ሆኖ እናገኛዋለን፡፡
በምርት (products) አቅራቢዎች የልዩ አስተያየት ተጠቃሚ የሚሆኑት ከ35% በላይ
በሀገር ውስጥ እሴት የተጨመረባቸው ከሆነ ነው፡፡ ስለሆነም ከ35% በላይ ዕሴት
ጨምረው በሀገር ውስጥ ከተመረቱ ምርቶች ውስጥ የመድሀኒት ምርቶች እና
የፋርማኩቲካል ኢኪዩፕመንት የ25% የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳጌ በአለም አቀፍ
ጨረታ (international bidding) ወቅት ይደረግላቸዋል፡፡ ነገር ግን ተፈላጊውን የእሴት
መስፈርት ያሟሉ ሌሎች በሀገር ውስጥ የተመረቱ እቃዎች የ15% የዋጋ ልዩ
አስተያየት ህዳጌ ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ በሌላ በኩል በግንባታ ሥራ (contarct works)
እና በማማከር አገልግሎት (consultancy services) የተሰማራ ድርጅት በዋጋ የልዩ
አስተያየት ተጠቃሚ ለመሆን ድርጅቱ ኢትዮጵያ ውስጥ የተቋቋመ ሆኖ ከ50% በላይ
የካፒታል ባለቤትነት ድርሻ፤ ከ50% በላይ የቦርድ አባላቱ እና ቢያንስ 50% የሚሆኑት
ቁልፍ የድርጅቱ ሰራተኞች ኢትዮጵያዊ ዜግነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ይህን
መስፈርት የሚያሟሉ በግንባታ ሥራ ወይም በማማከር አገልግሎት የተሰማራ ድርጅት
የ7.5% የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳጌ በአለማቀፍ ጨርታ ጊዜ ታሳቢ ይደረግላቸዋል፡፡
በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ጨረታ (national bidding) ወቅት ጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፐራይዞች ከሌሎች ሀገራዊ አቅራቢዎች ጋር ሲወዳደሩ የ3% በዋጋ የልዩ
አስተያየት ህዳጌ ይቀርብላቸዋል፡፡ ሆኖም በአለማቀፍ ጨረታ ጊዜ መካከለኛና ከፍተኛ
ተቋማት ከሚያገኙት የዋጋ ልዩ አስተያየት ጋር ተመሳሳይ የሆነ ህዳጌ ይኖራቸዋል፡፡
ሌላው ጉዳይ ከዋጋ ልዩ አስተያየት በተጨማሪ ብቃትን (performance) ታሳቢ ያደረገ
የልዩ አስተያየት ድጋፍ በግንባታ ስራ ዘርፍ ለተሰማራው የሀገር ውስጥ ባለሀብት
በ2008 ዓ.ም በተሻሻለው የመንግስት ግዥ ደንብ ላይ በዝርዝር ተሰጥቷል፡፡ ነገር ግን
ብቃትን መሰረት ያደረገ ልዩ አስተያየት በሌሎች የግዥ አይነቶች ላይ ጎልቶ
አይስተዋልም፡፡

በፌደራል የግዥ ፖሊሲ መሰረት የአለማቀፍ ግልፅ ጨረታ ለመፈፀም የግዥ መጠን
ለእቃዎች 50 ሚሊዮን ብር በላይ፣ ለግንባታ ስራ 150 ሚሊዮን ብር በላይ፣ ለማማከር

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 142


አገልግሎት 7.5 ሚሊዮን ብር በላይ እና ለሌሎች አገልግሎቶች 21 ሚሊዮን ብር በላይ
መሆን አለበት፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በሀገር ውስጥ ተፈላጊው ጥራት፣መጠን እና
ውድድር መኖሩ ከተረጋገጠ ከተጠቀስ የገንዘብ መጠን በላይ ቢሆንም ከሀገር ውስጥ
ምርቱ ወይም አገልግሎቱ ሊገዛ እንደሚችል ፓሊሲው ይገልፃል፡፡

የመንግስት ግዥ ስርአት እና አምራች ኢንዱስትሪው

የሀገራችን ግዥ ስርዐት በእቃዎች፣ ግንባታ ስራዎች፣ ምክር አግልግሎትና አገልግሎት


ግዥን ያካተተ ቢሆንም ይህ ጥናት ትኩረት የግዥ ፓሊሲው በሀገር ውስጥ የአምራች
ኢንዱስትሪ ለተመረቱ ምርቶች ላይ ያለውን ተፅኖ መፈተሸ ነው፡፡ በመሆኑም ጥናቱ
የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪ ምርት ግዥ ሂደት፣ የልዩ ድጋፍ ማዕቀፎች፣
በመንግስት መ/ቤቶች እና ምርት አቅራቢዎች በኩል ያሉ ችግሮች ይዳስሳል፡፡ ከግዥ
ፖሊሲው መርሆች አንዱ የሀገር ውስጥ የተመረቱ ምርቶችን ማበረታታትና መደገፍ
ሲሆን የፓሊሲው የአምራች ኢንዱስትሪውን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት ተረድቶ የዘርፉን
ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝርዝር ይዘት አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡

የመጀመሪያው ጉዳይ የግዥ ፖሊሲው መንግስት በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጅው


ውስጥ ቅድሚያ የሰጣቸውን የአምራች ኢንዱስትሪ ንኡስ ዘርፎች እንደየ እሴት ጭማሪ
ባህሪያቸው ድጋፍ ለመስጠት የሚያስችል ቁመና ላይ አይገኝም ማለት ይቻላል፡፡ የገቢ
ምርትን የሚተኩ (import substitution) እና የውጭ ምርት ተኮር (potentially export
sector) አምራች ኢንዱስትሪዎችን ባህሪ እና እሴት የመጨመር አቅም በማገናዘብ
ዘርዘር ያለ የልዩ አስተያየት ማእቀፍ በግዥ ፓሊሲው ውስጥ አልተካተተም፡፡
ማናቸውም የአምራች ኢንዱስትሪ ምርት በሀገር ውስጥ እንደተመረተ የሚቆጠረው
ከዋጋው 35% በላይ በኢትዮጵያ ከታከለ (value-added) ወይም በሀገር ውስጥ እሴት
ከተጨመረበት መሆኑን ፓሊሲው ይገልፃል፡፡ በዚህ መሰረት ከ35% በላይ በሀገር ውስጥ
እሴት የታከለበት የአምራች ኢንዱስትሪ ምርት በአለማቀፍ ጨረታ ጊዜ የዋጋ ልዩ
አስተያየት ያገኛል ማለት ነው፡፡ ሆኖም በማደግ ላይ ያሉ እና ስትራቴጃዊ ጠቀሜታ
ያላቸው ከባድ ኢንዱስትሪዎችን የተጠቀሰው የእሴት ጣራ ተጠቃሚ አያደርጋቸውም፡፡
ለምሳሌ ብረታብረትና ኢንጅነሪንግ፣ ኬሚካል፣ መድሀኒት እና ፋርማሲዩቲካል
ኢኩፕመንት አምራች ኢንዱስትሪዎች በዝቅተኛ ደረጃ ዕሴት የሚጨመርባቸው ንኡስ
ዘርፎች ሆነው ይገኛሉ፡፡ በሌላ በኩል የአግሮ ፐሮሲሰንግ፣ የቆዳ እና ጨርቃጨርቅ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 143


ኢንዱስትሪዎች ላቅ ያለ እሴት የመጨመር አቅም አላቸው፡፡ የዕሴት ምጣኔ ጣራ
እንደየ ንኡስ ዘርፍ አቅም በለመዘጋጀቱ ለወደፊት ለሀገሪቱ ኢንዱስትሪ እድገት
መሰረት የሚሆኑ ንኡስ ዘርፎች የገበያ እድል ያጣሉ ብሎም ውስን የሆነውን የውጭ
ምንዛሬ ሀብት ለብክነት ይዳርጋል፡፡ በተያያዥ ከ35% እና በታች እሴት ጨምረው
በሀገር ውስጥ የተመረቱ ምርቶች (ለምሳሌ 20% ወይም 15%) ምንም እሴት
ሳይጨመርባቸው ከውጭ ቀጥታ ከሚገቡ ምርቶች በአንድ አይነት ሁኔታ መጫረታቸው
በሂደት እሴት መጨመር የሚችሉ ኢንዱስትሪዎች ተወዳዳሪነት የሚጎዳ መሆኑን
መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ በመነሳት በሀገር ውስጥ እሴት የመጨመር ጣራ እንደየ
ንኡስ-ዘርፍ አቅም እና ስትራቴጂ ጠቀሚታ በየደረጃው እንዲለያይ ወይም ዝቅ ማድረግ
ይጠይቃል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ተፈላጊውን እሴት በሀገር ውስጥ እስካሟሉ ድረስ ሀገር በቀል
ኢንዱስትሪ ሆነ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስተር ከውጭ ተጫራቾች በተሻለ የዋጋ ልዩ
አስተያየት ተጠቃሚ ማድረግ አስፈላጊነቱ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ሆኖም ፓሊሲው
የሀገር ወስጥ ባለሀብቱ ያለውን የተወዳዳሪነት አቅም እና ዘላቂ የልማት ፋይዳ ከግምት
ወስጥ በማስገባት ለሀገር በቀል ኢንዱስትሪዎች ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስተሮች የተሻለ
ተጠቃሚ የሚያደርግ የዋጋ ልዩ አስተያየት አላዘጋጀም፡፡ ስለሆነም በፊደራል የግዥ
ፓሊሲ መሰረት ማንኛውም በሀገር ውስጥ የተመረተ ምርት ከ35% በላይ እሴት እስከ
ጨመረ ድረስ በአለማቀፍ ጨረታ ውድድር የዋጋ ልዩ አስተያየት ተጠቃሚ ይሆናል፡፡
በተመሳሳይ በብሄራዊ ጨረታ ጊዜ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች እና የውጭ ቀጥታ
ኢንቨስተሮች (FDI) ያለ ምንም የዋጋ ልዩ አስተያየት እንዲወዳደሩ ያደርጋል፡፡ ይህ
አሰራር የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን ከግዥ ፓሊሲ ተጠቃሚነት ሊያሳጣው ይችላል፡፡
አንደኛ በውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት በሀገር ውስጥ የሚያመርተው ባለሀብት
በልምድ፣ በቴክኖሎጂ፣ በአመራር፣ ካፒታል እና ገበያ ትስስር ከፍተኛ አቅም ያለው
በመሆኑ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን በጨረታ ውድድር በቀላሉ ማሸነፍ ይችላል፡፡ሁለተኛ
በውጭ ንግድ እንዲሳተፍ ታሳቢ ተደርጎ የመጣው ባለሀብት በሀገር ውስጥ ገበያ
እንዲወሰን ሊያደርገው ይችላል፡፡ ሶስተኛ የውጭ ቀጥታ በልዩ ሁኔታ በግዥ ስርአቱ
በማስተናገድ የግዥ ፓሊሲው የውጭ ባለሀብቱ የቴክኖሎጅ ሽግግር እና የኢንዱስትሪ
ትስስርን እንዲፈጥር ማበረታቻ ማእቀፍ አድርጎ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም
የውጭ ባለሀብቱ ቢያንስ በብሄራዊ ጨረታ ወቅት ከሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በልዩ ሁኔታ
የሚስተናገድበት ስልት ቢኖር ይመረጣል፡፡ በአንጻሩ ቻይና የግዥ ፓሊሲ ተሞክሮ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 144


ያልተጻፈ ልዩ አስተያየት ድጎማ ለሀገር በቀል ኢንዱስትሪ እንደሚሰጥ ያስተምረናል፡፡
ቻይና በግዥ ፓሊሲዋ ውስጥ የሀገር በቀል አምራችን ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስር የተሻለ
ተጠቃሚ የሚያደርግ አንቀጽ በግልጽ አላካተተችም፡፡ ነገር ግን በውስጥ ሰርኩላር
አማካኝነት ተፈላጊውን እሴት የጨመሩ ሀገር በቀል አምራቾች ከውጭ ኢንቨስተሩ
በተሻለ ልዩ ተጠቃሚ የሚያደርግ አሰራር እንዳላት ይገልፃሉ፡፡

ሌላው የኢንዱስትሪ ምርት ለማቅረብ ከሚጫረቱ አካላት ውስጥ አሸናፊውን ለመለየት


የጨረታ መመዘኛ መስፈርቶች መጠቀም እንደሚገባ ፓሊሲው ይገልፃል፡፡ የመመዘኛ
መስፈርቶቹ እንደ ግዥው አይነትና ዘዴ የሚለያይ ቢሆንም የዋጋ ልዩ አስተያየት
ድጋፍ በጨረታ ግምገማ ወቅት ለማበላለጫ በጥቅም ላይ ይውላል፡፡ ተፈላጊውን የዕሴት
መጠን ላከሉ የሀገር ውስጥ ምርቶች የልዩ አስተያየት ህዳግ ተጠቃሚነታቸው በዋናነት
የተመረኮዘው ከዋጋ (price) ጋር በተያያዘ እንደሆነ ፓሊሲው ያሳየናል፡፡ ከመድሃኒትና
የህክምና ምርቶች (25% የዋጋ ህዳግ) በስተቀር ሌሎች ምርቶች 15% የዋጋ ልዩ
አስተያየቱ ህዳግ በጨረታ ግምገማ ጊዜ ይሰጣቸዋል፡፡ ሆኖም በጨረታ ግምገማ ወቅት
የዋጋ ልዩ አስተያየት ማመጣጠን (normalized price) ስልቱ የልዩ አስተያየቱን
የማበላለጥ አቅም አነስተኛ ያደርገዋል፡፡ ሌላው ከውጭ ተጫራቾች በትንሽ ወጭ እና
በብዛት አምርቶ የማቅረብ (economies of scale) አቅም በመኖሩ ዝቅተኛ ዋጋ
የመተመን አቅም ስለሚፈጥርላቻው የሀገር ውስጥ ምርትን በቀላሉ ማሸነፍ ይችላሉ፡፡

የግዥ ፓሊሲው ለሀገር ውስጥ ምርት አቅራቢዎች ብቃትን መሰረት ያደረገ የልዩ
አስተያየት (preferential qualification requirement) ያላካተተ ነው፡፡ ነገር ግን ብቃት
ተኮር መመዘኛ መስፈርቶችን ማሟላት በግዥ ፓሊሲው ውስጥ በጨረታ ለመሳተፍ
እንደ ቅድመ ሁኔታ የተቀመጠ ስለሆነ የብቃት መስፈርቶችን የማያሟሉ አምራቾች
በቀጥታ ከውድድሩ እንዲቀነሱ ይደረጋል፡፡ ስለሆነም በርካታ የሀገር ውስጥ አቅራቢዎች
አሳሪ የሆነውን የብቃት መመዘኛ መስፈርት ለማሟላት ይቸገራሉ፡፡ የብቃት መመዘኛ
መስፈርቱ አጠቃላይ ልምድ፣ ተዛማጅ የስራ ልምድ፣ የፋይናንስ አቅም፣ የካፒታል
መጠን፣ የባለሙያዎች የትምህርት ዝግጅትና ብቃት፣ የማምረቻ መሳሪያ ሁኔታ፣
የማምረት አቅም እና ሌሎችንም ይይዛል፡፡ ከዚህ መረዳት የምንችለው ከዋጋ ልዩ
አስተያየት ይልቅ የብቃት መመዘኛ መስፈርት ለጨረታ መወዳደር እና ማሸነፍ
ከፍተኛ አስተዋፆ እንዳለው ነው፡፡ ለምሳሌ በገበያ እጦት ምክንያት ኪሳራ ያጋጠማቸው
ኢንዱስትሪዎች (ስትራቴጂካዊ ጠቀሚታ ይኑራቸው አይኑራቸውም) የፋይናንስ ብቃት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 145


መስፈርት ካላሟሉ በጨረታ እንዳይሳተፍ ይደረጋል፡፡ ስለሆነም የኪሳራ ወይም የገንዘብ
ችግር ላጋጠማቸው የሀገር ውስጥ ተቋማት በመንግስት ግዥ ስርአት ውስጥ ታሳቢ
ተደርገው ከችግራቸው እንዲያገግሙ የሚያስችል አይደለም፡፡

የግዥ ፓሊሲው ለሥራ ዕድል ፈጠራና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከሌሎች በሀገር


ውስጥ ከሚገኑ ተቋማት ጋር በብሄራዊ ጨረታ ሲወዳደሩ የ3% ተጨማሪ የዋጋ ልዩ
አስተያየት ይሰጣል፡፡ ውድድራቸው ከአለማቀፍ ተጫራቾች ጋር ከሆነ ደግሞ እንደ
ሌሎች በሀገር ውስጥ የተመረቱ ምርቶች ጋር ተመሳሳይ የዋጋ ልዩ አስተያየት በጨረታ
ግምገማ ጊዜ እንዲያገኙ ይደረጋል፡፡ የተጠቀሰው የዋጋ ልዩ አስተያየት አነስተኛ
በመሆኑ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ይደግፋል ተብሎ አይታሰብም፡፡
እንዲሁም የመንግስት መ/ቤቶች የሚፈልጉት የእቃ መጠን ብዛት ስለሚኖረው
ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ይልቅ ለመካከለኛና ከፍተኛ አምራች
ኢንዱስትሪዎች ምቹ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ 50 ሚሊዮን እና በላይ ግዥ ለሚቀርብበት
አለማቀፍ ጨረታ ውድድር ላይ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በተናጠል
ይሳተፋሉ ማለት ፈጽሞ አይቻልም፡፡ በጥቅሉ የዘርፉን የአቅም ውስንነት በጥልቅ
በመረዳት ፓሊሲው ልዩ ልዩ ስልቶችን ነድፎ ድጋፍ መስጠት አልቻለም፡፡

የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ ስንቃኝ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና አነስተኛ


ኢንተርፕራይዞችን በበቂ ሁኔታ ከግዥ ስርአቱ ተጠቃሚ እንደሆኑ መረጃዎች
ያሳያሉ፡፡ ለአብነት በሩሲያ የግዥ ፓሊሲ ውስጥ የመንግስታዊ ተቋማት ከአመታዊ
ግዥያቸው ቢያንስ 15% ያህሉ ከአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መሆን እንዳለበት
ይደነግጋል፡፡ በ2004 ዓ.ም የህንድ መንግስት የሥራ ዕድል ፈጠራ እና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞችን ለማበረታታት በቀረፀው የግዥ ፓሊሲ ውስጥ የመንግስት መ/ቤቶች
ወይም ፕሮጀክቶች በሶስት አመታት ጊዜ ውስጥ ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
የሚገዙትን ምርት እና አገልግሎት ከአጠቃላይ ግዥ መጠን 20% ለማድረስ ግብ
እንዲያስቀምጡ ያስገድዳል፡፡ እንዲሁም የመንግስት መ/ቤቶች ከጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች የፈፀሙትን ግዥ በአመታዊ ሪፓርት ማሳወቅ አለባቸው፡፡ የሥራ
ዕድል ፈጠራ እና አነስተኛ ተቋማት ከፍተኛ መጠን ያለው እቃ ማቅረብ ስለማይችሉ
በጨረታ ከሚቀርበው እቃ 20% እንዲያቀርቡ እድል ይሰጣቸዋል፡፡ በርካታ
ኢንተርፕራይዞች በጨረታ ውድድሩ ብቁ ከሆኑ ደግሞ የተፈቀደውን ኮታ (20%) እኩል
ተከፋፍለው እንዲያቀርቡ ይደረጋል፡፡ ሌላው ጠቃሚ ጉዳይ የህንድ ግዥ ፓሊሲ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 146


ከሥራ ዕድል ፈጠራ እና አነስተኛ ተቋማት ብቻ መግዛት ያለባቸውን ምርቶች በዝርዘር
አስቀምጧል፡፡ እንዲሁም የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት አቅራቢዎች አቅም ግንባታ፣
ከመደበኛው ስርአት የተለየ የአቅራቢዎች ምዝገባ፣ ተመሳሳይ እቃ አቅራቢዎችን
በአንድ ጋር ማደራጀት (consortia formation)፣ በግዥ ሄደት ወጭና የተንዛዛ አሰራርን
መቀነስ፣ ልዩ የቅሬታ ስርአት መዘርጋት ወዘተ ያካትታል፡፡

ሌላው የሀገራችን የፌደራል የግዥ ፓሊሲ ልክ እንደ ሌሎች ኢንዱስትሪዎች ሁሉ


ለጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፐራይዞች የብቃት ልዩ አስተያየት አያደርግላቸውም፡፡
ስለዚህ ከዋጋ ልዩ አስተያየት በተጓዳኝ የብቃት መስፈርት ልዩ አስተያየት ማቅረብ
ጥቃቅና አነስተኛ ተቋማት በንቃት እንዲሳተፍ ያደርጋቸዋል፡፡ ሌላው ለጥቃቅን እና
አነስተኛ ተቋማትን በንኡስ ተቋራጭነት ለሚያሰሩ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች
ልዩ ማበረታቻ መስፈርት በማካተት የገበያ ትስስርና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያግዛል፡፡

በአለማቀፍ ግልፅ ጨረታ ውድድር ስልት ለሚፈፀም ግዥ መነሻ ገንዘብ መጠን


ለእቃዎች 50 ሚሊዮን ብር በላይ ተደርጓል (በ2008 ዓ.ም በተሻሻለው የግዥ
መመሪያ)፡፡ ነገር ግን አንድ የሀገር ውስጥ ምርት ተፈላጊውን ጥራት፣ መጠን እና ዋጋ
ካሟላ፣ እንዲሁም በቂ ውድድር መኖሩ ከተረጋገጠ በብሄራዊ የጨረታ ውድድር ግዥው
ሊፈፀም እንደሚችል ይጠቅሳል፡፡ በብሄራዊ የጨረታ ውድድር ግዥ ሊፈፀም ይችላል
የሚለው ሃሳብ የአስገዳጅነት ባህሪ የለውም፡፡ በተጨማሪ የአምራች ኢንዱስትሪው
ምርት መጠን እና ስብጥር በተመለከተ በግዥ የሚሳተፉ ተቋማት በቂ መረጃ የማያገኙ
መሆናቸው ይገለጻል፡፡ ስለሆነም ተቋማቱ በአብዛኛው በአለማቀፍ ግልፅ ጨረታ
አማካኝነት ግዥ ሲፈፅሙ ይታያል፡፡

የፌደራል ግዥ ፓሊሲ ከሆነ የመንግስት መ/ቤቶች የሀገር ውስጥ ምርትን በስፋት


እንዲገዙ ለማስቻል አስገዳጅነት ያለው የአሰራር ስርአት አልዘረጋም፡፡ በሌላ አገላለጽ
የፌደራል ግዥ ፓሊሲ የኢትዮጵያን ይግዙ (Buy Ethiopian) በሚል መርህ ለመንግስት
መ/ቤቶች አስገዳጅ ስርአት የለውም፡፡ ሌላው ቀርቶ በግዥ ፓሊሲው ላይ ለሀገር ውስጥ
ምርት ለመደገፍ የቀረበውን የልዩ አስተያየት በአግባቡ ሲጠቀም አይታይም፡፡
በመሆኑም ለመንግስት መ/ቤቶች አስገዳጅ ማእቀፍ በማዘጋጀት ቢያንስ የተወሰኑ የሀገር
ውስጥ ምርቶች ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስፈልጋል ወይም የመንግስት መ/ቤቶች
ከአመታዊ ግዥ እቅድ የተወሰነ እጅ (percentage) የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለመግዛት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 147


እንዲያውሉ አስገዳጅ አሰራር ማዳበር ይቻላል፡፡ በሂደት ደግሞ የኢንዱስትሪው ዕድገት
እየጎለበተ ስለሚመጣ በርከት ያሉ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ወይም ከግዥ በጀት ከፍተኛ
እጅ የሀገር ውስጥ ምርቶች እንዲሆኑ በኢትዮጵያን ይግዙ ፓሊሲ ማዕቀፍ ውስጥ
ሊካተት ይችላል፡፡ በዚህ አሰራር የሀገር ውስጥ ምርትን መግዛት አስገዳጅ
የማይሆንባቸውን ልዩ ሁኔታዎች በግልፅ መለየት ያስፈልጋል ማለት ነው፡፡ ለአብነት
ለሀገር ጥቅም እና ደህንት አስፈላጊ ለሆኑ እቃዎች፣ ፍትሃዊ ያልሆነ ጥራት እና ዋጋ፣
ከሀገር ውጭ ጥቅም ላይ ለሚውሉ ምርቶች፣ ንፅፅራዊ ብልጫ ላይ ተመስርተው ለውጭ
ንግድ የታለሙ ምርቶች፣ በሀገር ውስጥ የምርት አቅርቦት ችግር ያለባቸው ምርቶች
እና ለመሳሰሉት ልዩ ሁኔታዎች ፓሊሲው ተፈፃሚ እንዳይሆን መወሰን እንደሚቻል
የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ያስረዳናል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በፌደራል ግዥ ፓሊሲ የተወሰነው የጨረታ ጊዜ (floating period of


bids) እና ምርት የሚቀርብበት ጊዜ (lead time) ለሀገር ውስጥ ምርት አቅራቢ እና
ለውጭ ምርት አቅራቢ/ተጫራች/ ተመሳሳይ ሆኖ ይገኛል፡፡ እንደሚታወቀው የውጭ
ተጫራች በጨረታ ሰነድ ዝግጅት፣ የጨረታ አዋጭነት ትንተና፣ በማምረት አቅርቦትና
ጥራት፣ በገበያ አመራር እና ቀልጣፋ ሎጀስቲክ አገልግሎት፣ ወዘተ የተሻለ ልምድ
አለው፡፡ በተቃራኒው የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ከሰነድ ዝግጅት እስከ ውል መፈጸም
ብሎም ምርትን በታቀደው ጊዜና ቦታ ለማቅረብ በርካታ ውጣ ውረድ ይገጥመዋል፣
የልምድ ችግርም እንዲሁ አለበት፡፡ በዚህ ረገድ የጨረታ ጊዜ (floating period of
bids) እና ምርት የሚቀርብበት ጊዜ (lead time) ለሀገር ውስጥ ምርት አቅራቢው
ምንም አይነት ልዩ አስተያየት አለመኖሩ ለጭረታ ውድድር የሚጠቅሙ ሰነዶችን
በወቅቱ ለማዘጋጀት የመቸገር እንዲሁም በውል መሰረት ምርትን የማቅረብ ችግር
እያጋጠመው መሆኑ ይገለፃል፡፡

በፌደራል ግዥ ፓሊሲ መሰረት ጨረታ አሸናፊው አካል አብዛኛውን ጊዜ በጥሬ ገንዘብ፣


ቸክ ወይም ከታወቀ ባንክ ማረጋገጫ በመጠቀም የውል ማስከበሪያ ወይም ቅድመ ክፍያ
ማስከበሪያ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ ለውል እና ለቅድመ ክፍያ ማስከበሪያ በሚል
በገንዘብ ወይም በማይንቀሳቀስ የባንክ አካውንት ግዥ በሚፈጽመው መንግስታዊ ተቋም
በዋስትና ስለሚያዝ የስራ ማስኬጃ ፋይናንስ ችግር ይፈጥርበታል፡፡ በሌላ በኩል ጨረታ
ላሸነፈ አካል የሚሰጠው ቅድመ ክፍያ ከአጠቃላይ የውል ዋጋ ከ30% መብለጥ
እንደሌለበት በግዥ ፓሊሲው ተደንግጓል፡፡ የቅድመ ክፍያ ምጣኔ የባለብቱን ካለበት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 148


ስር የሰደደ የፋይናንስ ችግር አኳያ ሲታይ ዝቅተኛ ሆኖ ይገኛል፡፡ በጥቅል ሲታይ
የቅድመ ክፍያ ዋጋ መጠን፣ የቅድመ ክፍያ ማስከበሪያ እና የውል ማስከበሪያ ዋስትና
የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን ስራ ማስኬጃ ፋይናንስ ፍላጎት እና የፋይናንስ አስተዳደር
ልምድ ከግምት ውስጥ ያላስገባ ነው፡፡

ቀልጣፋ፣ ወጭ ቆጣቢ፣ ፍትሃዊ እና በውድድር መርህ የሚተገበር የግዥ ፓሊሲ


ለማዳበር የባለሀብቱ እና የግዥ ባለሙያው እውቀት፣ ክህሎት እና አመለካከት ከፍተኛ
ድርሻ አለው፡፡ በአንድ በኩል የመንግስት ግዥ ለአምራች ኢንዱስትሪው እድገት ጉልህ
አስተዋጾ እንዳይኖረው ካደረጉ ማነቆዎች አንደኛው የባለሀብቱ ግንዛቤ እና አመለካከት
ነው፡፡ የግል ባለሀብቱ የግዥ ፓሊሲውን በተመለከተ የእውቀትና ግንዛቤ እጥረት
ይታይበታል፣ እንዲሁም የጨረታ ሂደቱ ውስብስብ እና ውጣ ውረድ የበዛበት መሆኑን
በማሰብ በጨረታ ለመወዳዳር ያለው ፍላጎት ይቀንሳል፡፡ በተለይ ጥቃቅንና አነስተኛ
ዘርፍ የተሰማራው የግል ባለሀብት ችግሩ በስፋት ይንፀባረቃል፡፡ ከዚህ የተነሳ ጨረታ
አሸናፊ የሆኑ ግለሰቦች በውሉ መሰረት ምርት ለማቅረብ ፈቃደኝነት ይጎላቸዋል፡፡
ለምሳሌ ውል ከፈፀሙ በኋላ ዋጋ ይጨመርልኝ ብሎ መጠየቅ፤ እቃ የማቅረቢያ ጊዜ
ይራዘምልኝ፣ ምርት ማቅረብ ከጀመሩ በኋላ ማቋረጥ፣ የውል ማስረከቢያ ማቅረብ
አለመቻል፣ በውል ከተጠቀሰው እቃ ውጭ ማቅረብ፣ ደረጃውን ያልጠበቀ እቃ ማቅረብ
እና የመሳሰሉት ችግሮች አሉበት፡፡

በሌላ በኩል በበርካታ የመንግስት የግዥ ባለሙያዎች ዘንድ የእውቀት፣ የክህሎት እና


የአመለካከት ችግር በመኖሩ ባለሀብቱ እና መንግስት ከግዥ ፓሊሲው ተጠቃሚ
እንዳይሆኑ አድርጓቸዋል፡፡ የግዥ ባለሙያው የግዥ ዝርዝር ሂደት እና ተግባር
(ማለትም የግዥ እቅድ፣ ጨረታ ሰነድ ዝግጅት፣ ጨረታ ግምገማና መረጣ መስፈርት፣
ውል ስምምነት፣ ውል አስተዳደር፣ ድርድር፣ ቅሬታ አስተዳደር፣ ፋይናንስ አጠቃቀም
ወዘተ) በተመለከተ በቂ እውቀት እና ክህሎት የለውም፡፡ በተጨማሪ ባለሙያው ከጥቂት
መካከለኛ እና ከፍተኛ አቅራቢ ድርጅቶች ብቻ ግዥ መፈጸም፣ ጥቃቅንና አነስተኛ
ተቋማት ተደራሽ ያልሆነ የጨረታ ዋጋ መመደብ፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት
እምነት ማጣት፣ ለሀገር ውስጥ ምርት የተዛባ አመለካከት መያዝ እና የመሳሰሉ ችግሮች
አሉበት፡፡ በተጓዳኝ የስነ-ምግባር ጉድለት እና አድሏዊ አሰራር ከሰፈነባቸው የመንግስት
ስራ ዘርፎች ውስጥ የግዥ ስርአቱ በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል፡፡ ከተጫራቾች ቅሬታ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 149


እና አስተያየት ለመረዳት እንደተቻለው የግዥ ባለሙያዎች (የመንግስት ግዥና
ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ፣2008 ዓ.ም)
 ለተወሰኑ ተጫራቾች የሚጠቅም ስፔስፊኬሽን ማዘጋጀት፤
 ጨረታ ሰነድ ላይ በሌለ መስፈርት መገምገም፤
 የጨረታ ሰነድ ከተከፈተ በኋላ የግምገማ መስፈርት መቀየር፣
 ከተጫራቾች ጋር በመመሳጠር አድሏዊ የጨረታ ግምገማ ማድረግ፣
 የብቃት ማስረጃ ያልያዙ ተጫራቾችን አሸናፊ ማድረግ እና
 በጨረታ መክፈቻ ወቅት መደበኛ የብቃት መስፈርት ይዞ ያልመጣ (የዘገየ)
ተጫራችን ከውድድር ማስወጣት

ሌላው በመንግስት መ/ቤቶች በሰፊው የሚታይ ግድፈት ደካማ የግዥ እቅድና አፈፃፀም
ነው፡፡ የመንግስት መ/ቤቶች በዕቅዳቸው መሰረት በየጊዜው ግዥ ከመፈፀም ይልቅ
በበጀት አመት መጨረሻ ላይ ሲሯሯጡ ይታያል፡፡ በዚህ ወቅት የመንግስት ግዥ
ፍላጎት እና የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪው የማቅረብ አቅም አለመመጣጠን
ይታይበታል፡፡ በዚህ ምክንያት ለውጭ ተጫራቾች ወይም የውጭ ምርት አስመጭዎች
ምቹ አጋጣሚ በመፍጠር የሀገር ውስጥ አምራቹን ከመንግስት ግዥ ሊያገኝ የሚችለውን
ድጎማ እና ገበያ በማሳጣት ላይ ይገኛል፡፡

ከላይ እንደተገለፀው የዚህ ጥናት ወሰን የፌደራል ግዥ ፓሊሲ አምራች ኢንዱስትሪውን


ከመደገፍ አኳያ ያሉበትን ውስንነቶች መፈተሸ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ በፌደራል
የግዥ ፓሊሲ የተስተዋለው ችግር በክልል መንግስታት ግዥ ፓሊሲ፣ በመንግስት
ልማት ተቋማት ግዥ ስርአት፣ ለሀገር ደህንነትና መከላከያ አስመልክቶ የሚፈፀም
ግዥና በውጭ መንግስታት /ተቋማት/ ድጋፍ በተገኘ ገንዘብ በሚደረግ ግዥ ወቅት
እንዲሁ እንደሚንፀባረቅ መረዳት ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር የፌደራል ግዥ ፓሊሲ
ተግባራዊ ለማይሆንባቸው ሌሎች መንግስታዊ ግዥዎች የአምራች ኢንዱስትሪውን
ተጠቃሚነት ማረጋገጥና አለማረጋገጣቸውን በመፈተሸ ማሻሻያ ማድረግም ተገቢ ነው፡፡

5.6 በአምራች ኢንዱስትሪ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት

ብዙ ፀሀፊዎች ለአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኙ የቴክኖሎጂ ዕድገት መሆኑን


ይገልፃሉ፡፡ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት የቴክኖሎጂ አጠቃቀማችን ፈጥኖ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 150


ማደግ አለበት፡፡ በመሆኑም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለኢንዱስትሪና ኢኮኖሚክ ዕድገት
አይነተኛ መሳሪያ መሆኑን (Science & Technology as a tool for Industrialization
and Economic growth of South Korea) ሁሉም ባለድርሻ አካላት በሚገባ መረዳትና
ለዘርፉ ዕድገት ከፍተኛና የማያቋርጥ አስተዋፅኦ ማድረግ ይጠበቃል፡፡ የሀገሪቱ
ኢኮኖሚ ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ለማሸጋገር መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት
ያስፈልጋል፡፡በዚህ መዋቅራዊ ለውጥ ውስጥ የሀገራችን ኢኮኖሚ ዕድገት ዘላቂነት
ለማረጋገጥ በዋናነት ሀገራዊ የቴክኖሎጂ አቅም መገንባት ወሳኝ ነው።

መንግስት ለሀገራችን ኢኮኖሚ ዘላቂ ዕድገት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን


አስፈላጊነት ላይ ጠንካራ እምነት ስላለው አስራ አንድ (የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የሰው
ሀብት ልማት፣ ምርምር፣ የማምረቻና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ የፋይናንስ ድጋፍ
ማበረታቻ ስርአት፣ የጥራት መሰረተ-ልማት፣ ትምህርትና ምርምር ተቋማት፣ የአዕምሯዊ
ንብረት ስርአት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ፣ የአካባቢ ልማትና ጥበቃ፣ እና አለማቀፍ
ትብብር) ወሳኝ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን አዘጋጅቶ ለመተግበር በእንቅስቃሴ ላይ
ይገኛል፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራው የሀገር ውስጥ ባለሀብት በተሰማራበት የስራ ዘርፍ


በአለማቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ከሚያስችሉት ጉዳዮች አንዱ ተስማሚ የሆነ
የቴክኖሎጂ አቅርቦት ማመቻቸት እና ተጠቃሚ ማድረግ ነው፡፡ በዚህ ረገድ ባለሀብቱ
የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች በማከናወንና በመደገፍ ተግባሮች ላይ ሰፊ
ርብርብ እንዲያደርግ ይጠበቃል፡፡ በሌላ በኩል በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራው
ባለሀብት ከዩኒቨርስቲዎች፣ ምርምር ተቋማት፣ ቴክኒክና ሙያ እንዲሁም ትምህርትና
ስልጠና ተቋማት ጋር በቅርበትና በአጋርነት መስራት ይጠበቅበታል፡፡

ቴክኖሎጂን ከሰጪ ወደ ተቀባይ ለማሸጋገር የሰጪው ፍቃድና ፍላጎት ብቻ ሳይሆን


የተቀባዩ ዝግጁነትም ወሳኝ ነው፡፡ የተቀባዩ ዝግጁነት ሲባል በሚሸጋገረው ቴክኖሎጂ
ላይ ያለውን ዕውቀትና ክህሎት የሚመለከት ነው፡፡ በሀገራችን በተለይም በአምራች
ኢንዱስትሪው የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ቢያንስ ሁለት ጉዳዮች ላይ ማተኮር
ያሻል፡፡ አንደኛው ብቁ የሰው ሀይል እንዲኖር ማድረግና ሁለተኛው ደግሞ
በመካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ የተሰማራው የሀገር ውስጥ ባለሀብት
ለአዳዲስ ቴክኖሎጂዎችና አሰራሮች በሩን ክፍት እንዲያደርግ ማስቻል ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 151


5.6.1 በአምራች ኢንዱስትሪ የቴክኖሎጂ ሽግግር አፈፃፀም

የሀገራችን ሁለንተናዊ ልማት የሚጠይቀው የቴክኖሎጂ ግብአት በተለይ ኢንዱስትሪው


በማቆጥቆጥ ላይ ያለና ጀማሪ በመሆኑ ቅድሚያ ትኩረት የተሰጠው የቴክኖሎጂ ኩረጃ
ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን የፈጠራ ስራዎች ትኩረት አይሰጣቸውም ማለት አይደለም፡፡
የካፒታል ዕቃዎች ምርት ልማት በግዥ (Licensing) ወይም መልሶ መፈብረክ
(reverse engineering) እንደሚሰራ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ ይህንን ለመፈፀም
በተመረጡ የመንግስት የልማት ድርጅቶችና የግል ባለሀብቶች እንዲሳተፉበት አቅጣጫ
ተቀምጦ እየተሰራ ነው፡፡ የኢንዱስትሪ አመራር (industrial management)፣ የምርት
ዲዛይን ማበልጸግና የምርት ቴክኒሽያን ማብቃት፣ የገበያ ጥናትና አመራር፣ እና
ሌሎችም የጥናትና ምርምር ስራዎች ደግሞ በግሉ ባለሀብት እና በአምራች
ኢንዱስትሪው የተቀጠረው ሰራተኛ በቅንጅት የሚፈፀሙት ሲሆን የዚህ ዓይነት
የቴክኖሎጂ ሽግግር ምንጩ የሽርክና (Joint venture) ኢንቨስትመንት፣ የውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት፣ የወሳኝ ፕሮጀክቶች ኮንትራክት እና የማኔጅመንት ኮንትራት እንደሆኑ
ተለይተዋል፡፡ በዚህ መሰረት ከአጭርና መካከለኛ ጊዜ የግሉ ዘርፍ ቅድሚያ ትኩረት
የሚሰጠው የቴክኖሎጂ ሽግግር ከካፒታል ዕቃ ማምረት ባሻገር ያለውን ነው፡፡ ነገር ግን
የቴክኖሎጂ ሽግግር እንቅስቃሴው አጥጋቢ ያልሆነ እንዲሁም አሁን ያለበትን ሁኔታ
በሚገባ ገምግሞ ያላስቀመጠና በትክክል ወደ ተግባር መግባቱም ያልተረጋገጠ እንደሆነ
በየደረጃው የሚገኙ ኢንቨስትመንትንና አምራቹን ዘርፍ የሚመሩ የመንግስት
አስፈፃሚና ፈፃሚዎች እንዲሁም በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ይገልፃሉ፡፡ ከላይ በዚህ
ርእስ ውስጥ እንደተጠቀሰው ቴክኖሎጂን ለማሸጋገር ብዙ ዓይነት መንገዶች ያሉ
ቢሆንም አብዛኛው ጊዜ የሚነሳው እና በታዳጊ ሀገራት ሽግግሩም የጎላ ሆኖ የሚታየው
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ነው፡፡

የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትና የቴክኖሎጂ ሽግግር


ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ቴክኖሎጂን ለማሸጋገር ከሚጠቅሙ ዘዴዎች አንዱና ዋነኛው
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት /FDI/ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2000 በሀገራችን 500 ሚሊዮን
የአሜሪካ ዶላር የነበረው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መጠን በ2014 ወደ 5 ቢሊዮን
ዶላር አድጓል (የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን)፡፡ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች
እንደሚያሳዩትም መጠኑ እየጨመረ መሆኑ ነው፡፡ በኢነርጂና በማዕድን ልማት ብዙ
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በመሳብ ከሚታወቁት ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በተለየ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 152


ሁኔታ (ለመጥቀስ ያህል ሞዛቢክ፣ ታንዛኒያ እና ኡጋንዳ) በኢትዮጵያ የውጭ ባለሀብት
በብዛት በመሰማራት ላይ ያለው በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2014
ዘርፉ ከአጠቃላይ የውጭ ኢንቨስትመንት 72.3 በመቶ የሚሆነውን ለመሳብ ችሏል
(EIC፣ 2015)፡፡ ነገር ግን የውጭ ባለሀብቱ በብዛት የተሰማራው በአዲስ አበባ እና አዲስ
አበባ ዙሪያ ባሉ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ውስጥ ነው፡፡ 80 በመቶ የሚሆነው የውጭ
ኢንቨስትመንት በእነዚህ ቦታዎች እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ (PSRC & EDRI,
2016)፡፡

በሀገራችን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ስናይ በውጭ ባለሀብት የተያዙ ድርጅቶች ከሀገር
ውስጥ ድርጅቶች በተሻለ ሁኔታ ቴክኖሎጂዎችን ይጠቀማሉ፡፡ በሌላ አባባል
አመራረታቸውና የስራ አመራር ዘይቤያቸውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ
ነው (PSRC & EDRI, 2016)፡፡ በሀገራችን ከሚገኙ የውጭ ኢንቨስትመንት ውስጥ 11
በመቶ የሚሆኑት የምርት አመራረት ሂደታቸውን ለማሻሻል በማሰብ የጥናትና ምርምር
(R&D) ስራ የሚሰሩ ሲሆን በአንጻሩ ይህን ተግባር የሚፈጽሙ የሀገር ውስጥ አምራቾች
ከ6 በመቶ አይበልጡም፡፡ በተመሳሳይ የFDI ድርጅቶች ከሀገር ውስጥ አምራች
ድርጅቶች በተሻለ ሁኔታ በዓለማቀፍ ደረጃ እውቅና ያገኙ ፓተንቶችን ይጠቀማሉ፡፡
ከሌላ FDI ቴክኖሎጂን በማስፈቀድ ከመጠቀም አንጻርም የተሻሉ ናቸው (PSRC &
EDRI, 2016)፡፡ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱ መረጃዎች የሚያሳዩት ምንም እንኳን እስካሁን
ወደ ሀገራችን የገቡት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶች ከጥራታቸው አንጻር በሚፈለገው
ደረጃ ባይሆኑም አሁንም ቢሆን ካላቸው ቴክኖሎጂና ከሚጠቀሙት የስራ አመራር
ዘይቤ አንጻር ከሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪዎች የተሻሉ ናቸው፡፡

በፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል እና በኢትዮጵያ የልማት ምርምር ኢንስቲትዩት


በቅርቡ በጋራ የተጠናው ጥናት እንደሚያመላክተው በሀገር ውስጥ ባለሀብቱና በውጭ
ባለሀብቱ መካከል ያለው ትስስር በጣም ደካማ እንደሆነ ነው፡፡ ከሀገር ውስጥ ባለሀብቱ
ውስጥ 7.5 በመቶ የሚሆኑት ብቻ ከFDI ጋር በአቅርቦት የተሳሰሩ ሲሆን 7 በመቶ
የሚሆኑት የሀገር ውስጥ ድርጅቶች በFDI ድርጅቶች ተቀጥሮ ይሰራ የነበረ ሰራተኛ1
ቀጥረው በማሰራት ላይ ናቸው፡፡ በዚህም ምርታማነታቸውን እንዲያሻሽሉና ልዩ ልዩ

1
በቅርቡ የሀገር ውስጥ ባለሀብትና የውጭ ባለሀብት ቁርኝት አስመልክቶ በተደረገ ጥናት ከዚህ በፊት
በውጭ ባለሀብቶች ተቀጥሮ ይሰራ የነበረን ሰራተኛ ከቀጠሩ የአገር ወስጥ ባለሀብቶች መካከል 78 በመቶ
የሚሆኑት ከምርታማነት ማሻሻል፣ ከአመራረት ዘይቤና ቴክኒክ አንጻር ትልቅ ለውጥ ማስመዝገባቸውን
ጥናቱ ያመላክታል (Abebe and Gebreyessus, 2013፤ በPSRC & EDRI, 2016 ላይ
እንደተመለከተው)፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 153


የምርት ሂደት ቴክኒኮችን እንዲቀስሙ እና እንዲተገብሩ ረድቷቸዋል፡፡ ነገር ግን ከላይ
የተጠቀሱት መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ትስስሩ እጅግ ዝቅተኛ በሚባል ደረጃ ላይ
እንደሆነ ነው፡፡ ለዚህ ደካማ ቁርኝት መፈጠር ብዙ ምክንያቶችን ማስቀመጥ የሚቻል
ቢሆንም፣ እንደ መንግስት ከFDI ሊገኝ የሚታሰበው የቴክኖሎጂ ሽግግር አሳንሶ የማየት
በዚህም በማቆራኘቱ ላይ አቅዶ ያለመስራት ችግር ይታያል፡፡ ለምሳሌ ከዓመት በፊት
ወደ ስራ በገባው የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ አንድም የሀገር ውስጥ ባለሀብት
እንዲሳተፍ ያለመደረጉ መንግስት ከFDI ሊገኝ ስለታቀደው ቴክኖሎጂዎች የሰጠውን
አነስተኛ ግምት ያሳያል፡፡

የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቱ በዋናነት የቴክኖሎጂ ሽግግርን እንዲያመጣ


እንደአቅጣጫ የተቀመጠ ቢሆንም ተግባራዊ እንቅስቃሴው ግን በጣም ደካማ ነው፡፡
መንግስት የውጭ ባለሀብቱ ከሀገር ውስጥ ባለሀብት በሽርክና እንዲሰራ የሚያደርግ
የተወሰነ አስገዳጅ ስልት ሊኖረው ይገባል፡፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብት እና የውጭ
ባለሀብት በተለይ በሽርክና እንዲሰሩ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ጠንካራ እንዳልሆነ
በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ይገልፃሉ፡፡

ባለቤትነታቸው ሙሉ በሙሉ የውጭ የሆኑ ፋብሪካዎች በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ


ቴክኖሎጂውን ለኢትዮጵያዊያን ባለሀብቶች ማስተላለፍ የሚጠበቅባቸው ቢሆንም
በተግባር እየተፈፀመ አይደለም፡፡ በእርግጥ የውጭ ፋብሪካዎች የቴክኖሎጂ ሽግግሩ
እንዲፈጸም ፍላጎት የላቸውም፤ እንዲኖራቸውም አይጠበቅም፡፡ነገር ግን ቴክኖሎጂዎችን
ከእጃቸው ፈልቅቆ ለማስቀረት ጥረት ማድረግ ያለባቸው የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብትና
መንግስት ናቸው፡፡ የውጭ ባለሀብቶች ሽግግሩ ገና እንዳልተፈፀመ በመጥቀስ ከውጭ
ይዘዋቸው የመጡ ሠራተኞች የስራ ፈቃድ በማሳደስ ጊዜ እያራዘሙ ነው፡፡ አንዳንዶቹ
ደግሞ የስራ ፈቃዳቸው ሳያሳድሱም እየኖሩ መሆኑ ያገኘናቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
እነዚህ የውጭ ሰራተኞች በዚህ መልክ ለዓመታት ሲኖሩ የቴክኖሎጂ ሽግግሩ ፈጣን
እንዳይሆን ከማድረጉ ባሻገር የሚከፈላቸው በውጭ ምንዛሬ በመሆኑ ተፅዕኖው ቀላል
አይሆንም፡፡

ከውጭ ባለሀብቱ ልናገኘው የሚገባን የቴክኖሎጂ ሽግግር ስልቶች በንድፈ-ሐሳብ ደረጃ


የተቀየሱ ቢሆንም የተጠናከረ የማስተግበሪያ አሰራር ባለመዘርጋቱ ከውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት ሊገኝ የሚገባ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት እየተገኘ አይደለም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 154


ስለሆነም አንዳንድ አምራቾች የተወሰኑ ሰራተኞች ውጭ ልከው ማሰልጠን የግድ
እንደሆነባቸው በተግባር ይታያል፡፡ እንደ መቀሌ ብረታ ብረት፣ ባህርዳር ቆዳ ፋብሪካ
ያሉ በርካታ የብረታ ብረት፣ ምግብ ማቀነባበሪያ፣ ጨርቃ ጨርቅ እና ቆዳ ፋብሪካ
ባለሙያዎች እስከ 3000 ዶላር በወር እየከፈሉ ከውጭ ባለሙያ በመቅጠር ከስድስት
ወር እስከ አንድ ዓመት የሚደርስ ስልጠናዎች ለሰራተኞቻቸው መስጠታቸውን
ገልፀዋል፡፡እነዚህ ፋብሪካዎች ለቴክኖሎጂ ሽግግር የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማድረጋቸው
ለሌሎች መሰል ፋብሪካዎች እንደጥሩ ምሳሌ የሚወሰድ ነው፡፡ ለምሳሌ ባህርዳር ቆዳ
ፋብሪካ በውጭ ሀገር ሰራተኛ ልኮ በማሰልጠን እንዲሁም በሀገር ውስጥ የውጭ ዜጋ
በመቅጠር ያሰለጠናቸው ባለሙያዎቹ በመጠቀም ለሌሎች መሰል የቆዳ ፋብሪካዎች
ስልጠና ይሰጣል፡፡ ሌላው ከአሰራር ክፍተት የሚታየው የሀገር ውስጥና የውጭ
ባለሀብቶች በሽርክና በሚሰሩበት አምራች ፋብሪካዎች ላይ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ
ቴክኖሎጂን ለማሸጋገር ምን ያህል እየተማረበት መሆኑና እንዲሁም በውጭ ቀጥታ
ኢንቨስትመንት ተቀጥሮ እየሰራ ያለ ሰራተኛ ምን ያህል ቴክኖሎጂውን እየኮረጀ መሆኑ
የሚገመገምበት ስልት የለም፡፡ ስለዚህ የኢንዲስትሪ ልማት ኢንስቲትዮቶች እና
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቴክኖሎጂ ሽግግር በሚፈለገው ደረጃ መከናወኑንና የታሰበው
ግብ መሳካቱን እርግጠኛ የሚሆኑበት አካሄድ አለ ለማለት ያስቸግራል፡፡

ሌላው ከቴክኖሎጂ ሽግግር ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ የአምራች ኢንዱስትሪው


ቴክኖሎጂ የመቀበል አቅምና ፍላጎት ነው፡፡ ቴክኖሎጂ የመቀበል አቅም ሰፊ ጽንሰ
ሀሳብ ቢሆንም በዚህ ርእስ በፋብሪካ ደረጃ ስለሚኖረው ቴክኖሎጂ የመቀበል አቅም ብቻ
ይመለከታል፡፡ ብዙ የጥናት ግኝቶች እንሚያመላክቱት የተቋማት ቴክኖሎጂ የመቀበል
አቅም በዋናነት በተቋሙ የሰው ሀይል አቅም ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ነው፡፡ ይህ
ጥናት መረጃ የሰበሰበባቸው የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች እንደሚሉት ቀጥረው
የሚያሰሯቸው አብዛኛዎቹ ሰራተኞች በቂ የሙያ ክህሎትና የፋብሪካ የስራ ባህል
ያልተላበሱ መሆናቸውን ነው፡፡ ሰራተኛው በምርት ሂደት በተሰማራበት ስራ ላይ
በመማርና በፈጠራ ላይ የተመሰረተ መሻሻል ያለባቸው ሂደቶችና በምርት
የሚጨምረው የፈጠራ ውጤት ያለመኖሩ ነው፡፡ በምርት ንድፍ ዝግጅትም ተመሳሳይ
ሰፊ የዓቅም ውስንነት በመኖሩ ምክንያት ምርት የተሟላ ጥራት ኑሮት እንዳይመረት
ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ መሆኑን ይገልፃሉ፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 155


የሳይንስ ኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እ.ኤ.አ በ2015 ባወጣው መረጃ አብዛኛዎቹ
በሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪ ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች የትምህርት
ደረጃቸው 10ኛ እና ከዛ በታች ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው እነዚህ ቀላል አምራች
ኢንዱስትሪዎች አብዛኛዎቹ የሚጠቀሙት ቀላል እና ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን
ነው፡፡ በተጨማሪም በ13 ኢንዱስትሪዎች ውስጥ አንድ PhD ያለው ሰው እንደሚኖርና
ቀሪው TVET፣ BA/BSC እና MA/MSC በቅደም ተከተል 24%፣ 6.7% እና 0.5%
እንደሆነ መረጃው ያሳያል (Science Technology Information center, 2015)፡፡ ይህም
የሚያሳየው በቀላል አምራች ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ተቀጥረው እየሰሩ ያሉ አብዛኛዎቹ
ሰራተኞች ዝቅተኛ የሆነ የትምህርት ደረጃ እንዳላቸው ነው፡፡ ይህም በመሆኑ አዳዲስ
ቴክኖሎጂዎችን ፈጥኖ የመገንዘብ፣ አንብቦ ስለ አጠቃቀማቸው የመረዳት፣ ስለ
ቴክኖሎጂው ምንነት እና አስፈላጊነት ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች የማፈላለግ እና
የመረዳት፣ ወዘተ ሊኖራቸው የሚችለው አቅም ዝቅተኛ ነው፡፡ ለዚህም ነው በብዙ
ጥናቶች በታዳጊ ሀገራት የሚገኙና ባደጉ ሀገራት የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች እኩል
ቴክኖሎጂን የመቀበል አቅም እንደሌላቸው የሚገለፀው፡፡

5.6.2 በአምራች ኢንዱስትሪ ለቴክኖሎጂ ሽግግር የባለድርሻ አካላት ሚና

ለሀገራችን ቴክኖሎጂዎችን የማስገባት፣ የመማር፣ የማላመድና የመጠቀም እንቅስቃሴ


ውጤታማ የሚሆነው የተጠናከረ የምርምር ስርአት ሲኖርና የሚመለከታቸው ተዋንያን
የሚጠበቅባቸውን ሚና ሲጫወቱ ነው፡፡ ዩኒቨርስቲዎች፣ የምርምር ተቋማት፣ የቴክኒክና
ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ እንዲሁም ኢንዱስትሪዎች ለሳይንስና ቴክኖሎጂ
መስፋፋት ዋነኛ ተዋናዮች ናቸው፡፡

በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ላይ እንደተገለፀው በመጀመሪያው


የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን የዕቅድ ዓመታት የኢንዱስትሪ ልማቱ ዋናው አቅጣጫ
የዘርፉን ምርታማነት አሟጦ መጠቀም የነበረ ቢሆንም በዕቅድ ዓመቱ መጨረሻ
የቅልጥፍና ችግር እንደ ዋነኛ ማነቆ ለመለየት ተችሏል፡፡ ይህን ችግር ለመፍታትም
መፍትሄው ተስማሚ ቴክኖሎጂን የመኮረጅ፣ የማላመድና ለሌላ የማስተላለፍ፣
ፋብሪካዎችን የመፈብረክ እና የመገንባት፣ ኮምፖነንቶችንና መለዋወጫዎችን
የመፈብረክ አቅም መፍጠር እንደሆነ፣ ይህ ከተሳካ የአቅም አጠቃቀምንና ምርታማነት
ችግርን ለመፍታት፣ ገቢ ምርቶችን በመተካት የውጭ ምንዛሬን ለማዳንና ቴክኖሎጂን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 156


በውጭ ምንዛሬ የማምጣት ማነቆን በማስወገድ ለተፋጠነና ዘላቂ ለሆነ
ኢንዱስትሪያላይዜሽን የሚሆን መሠረት መጣል እንደሚቻል ተቀምጧል፡፡ ይህን ሁኔታ
ግምት ውስጥ በማስገባት መንግስት የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ድርጅት
ያቋቋመ ሲሆን ባለሙያዎችን ከውጭ በማምጣትና ድርጅቱን ከግል ዘርፍ ጋር
በማስተሳሰር የሰው ሀይሉንና የኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪውን አቅም በአገርአቀፍ ደረጃ
መገንባት የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ በአጭር ጊዜ ሊሳኩ
የሚችሉ የኤሌትሪክ ሽቦዎችን፣ የውሃ ፓምፖችን፣ ትራንስፎርመሮችን ሀገር ውስጥ
ማምረት የተቻለ ሲሆን ማሽነሪዎችንና ኮምፖነንቶችንም ሀገር ውስጥ ለማምረት
የሚያስችል አቅም በመገንባት ላይ እንደሚገኝ መንግስት ይገልፃል፡፡ የተፈጠረው
አቅም ግን ምርት በብዛት በማምረት ስፋት ላለው ገበያ ወደማቅረብ ያልተሸጋገረ ሲሆን
በትስስር ለሀገር ውስጥ አምራቾች የሚሰጡ የምርት ትዕዛዞችም ለውጭ ኩባንያዎች
ተላልፈው የሚሰጡበት፣ የስኳር ልማትና የማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክቶችም በጣም
የተጓተቱበት ሁኔታ ይታያል፡፡ ይህ ጅማሮ ቢኖርም የኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪው
የቅልጥፍና እና የክህሎት ችግር በወሳኝነት አለመፈታቱን ያሳያል፡፡

ከዚህ ሌላ በመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን የዕቅድ ዘመን የተቀመጡትን


የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ግቦችን ለማሳካት በማሰብ የዘርፉ ዋና ተዋናይ የሆነው
የግሉ ዘርፍ ያለበትን የቴክኖሎጂ አመራረጥና አጠቃቀም፣ የአሰራርና የአመራረት ዘዴ፣
የሰለጠነ የሰው ሀይልና የገበያ ትስስር ችግሮች ለመፍታትና ድጋፍ ለመስጠት የዘርፉን
ምርታማነትና ኤክስፖርት ለማሳደግ ቅድሚያ ትኩረት በተሰጣቸው የኢንዱስትሪ
ዘርፎች ስድስት የሚሆኑ የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩቶች እንዲደራጁ ተደርጓል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ከአመራር እስከ ሰራተኛው ልማታዊ አስተሳሰብ ለማስረጽ፣
ቀጣይነት ያለው ምርትና ምርታማነት፣ የምርት ጥራትን ለማሳደግ የሚያስችለውን
የካይዘን ፍልስፍና የሚያስፋፋ ኢንስቲትዩት ተደራጅተዋል፡፡

እነዚህ ኢንስቲትዩቶች ከሚሰሯቸው ዋና ዋና ተግባራት አንዱ በአምራች ኢንዱስትሪው


የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠንና ዓቅም ለመገንባት ቢሆንም የተግባር
እንቅስቃሲያቸው ግን ይህን አያመለክትም፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶችም
ኢንስቲትዩቶቹ የሚሰጡት ስልጠና ንድፈ-ሐሳባዊ እንጂ አምራች ኢንዱስትሪው
ለገጠመው ችግር መፍትሄ የሚሆንና በሙያ ክህሎት ስልጠና ላይ ያተኮረ ባለመሆኑ
አጋዥ እንዳልሆነ ይገልፃሉ፡፡ የንድፈ-ሐሳብ ስልጠናውም ቢሆን አዳዲስ ዕውቀቶች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 157


ሳይሆን ሰራተኛውና ፋብሪካው የሚያውቀው እንደሆነ በዘርፉ የአምራች ባለሀብቶች
ገልፀዋል፡፡ የሚሰጠው ስልጠናና ሌሎች ድጋፎች መሰረታዊ ለውጥ የማያመጡ
ከመሆናቸውም በላይ ተደራሽነታቸውም ጠባብ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ በየዘርፉ
የተቋቋሙት የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩቶች በየዘርፋቸው የሚሰጡት ድጋፍ
በድምሩ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች የግምገማ ውጤት ሲታይ፡ 14 ፋብሪካዎች
(16.3%) የሚሰጠውን ድጋፍ ጥሩ መሆኑን፣ 18 ፋብሪካዎች (20.9%) መካከለኛ
መሆኑን፣ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት (62.8%) ኩባንያዎች ደግሞ ዝቅተኛ መሆኑን
ገልፀዋል፡፡

ከስልጠና ውጭ በፋብሪካ ደረጃ (Firm Level) የሚሰጡት ሌሎች ድጋፎችም


በተመሳሳይ ሁኔታ ውጤታቸው ጎልቶ የሚታይ አለመሆኑን ገልፀዋል፡፡ በአጠቃላይ
የአምራች ኢንዱስትሪ ባለቤቶች የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩቶች ክትትልና ድጋፍ
ትርጉም ያለው ለውጥ አላመጣም የሚል ነው፡፡ ተቋማቱ አስፈላጊውን ጊዜ መድበው
በፋብሪካዎች ያለውን ክፍተት ከባለሀብቶች እና ከአመራሩ ጋር በመሆን ችግሮቹን
የመለየትና መፍትሄ ማቅረብ አይታይባቸውም፡፡ ለምሳሌ አንድ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ
ጥጥ ከህንድ ግዥ ለመፈፀም ውል ገብቶ ናሙና እንዲፈተሽለት ለጨርቃ ጨርቅ
ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዮት ከሰጠ በኋላ ውጤቱ ሳይላክለት ከሁለት ወር በላይ
የዘገየ እንደነበር ገልፀዋል፡፡

ከኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዮቶች ባለሙያዎች ጋር የተካሄደው ውይይት ሁለት


መሠረታዊ ክፍተቶችን ለመለየት አስችሏል፡፡ አንደኛው እነዚህ የኢንዱስትሪ ልማት
ኢንስቲትዩቶች ከተቋቋሙበት ተቀዳሚ ዓላማ (ጥናትና ምርምር) ወጥተው
የኢንቨስትመንት ኮሚሽንና ሌሎች በየደረጃው ያሉ ተቋማት በሚሰሩት የመንግስት
አገልግሎት ድጋፍ (Facilitaton) ስራ ላይ የተጠመዱ መሆኑ ነው፡፡ የዚህ ዋነኛ
ምክንያት ተደርጐ የሚቀርበው የኢንስቲትዩቶች አመራር ትኩረታቸው የዕለት ተዕለት
ስራዎች ላይ የተንጠለጠለ በመሆኑ ባለሙያው ለጥናትና ምርምር ሊያውሉት የሚገባ
ጊዜ መሠረታዊ ለውጥ በማያመጣ ስራ ላይ እንዲባክን እያደረገው ይገኛል፡፡ ሁለተኛው
የተነሳሽነት እና የአቅም ችግር ነው፡፡ በኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩቶች ያለው
የምርምር ሀይል የአቅም ውስንነት ያለበት ከመሆኑ በተጨማሪ ተነሳሽነትን ወስዶ
የምርታማነትና የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚፋጠንበት መፍትሔ ከማፈላለግ አኳያ ሰፊ
ክፍተት ያለበት መሆኑ ይገለፃል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 158


ኢንስቲትዩቶቹ ያሉበት ደረጃ ሲታይ በቅርቡ የተቋቋሙትን ጨምሮ ነባሮቹም ቢሆኑ
ብቃት ያለው የሰው ሀይል ያልያዙና የጥራትና የአመራር ችግር ያለባቸው በመሆኑ
በዓለም አቀፍ ደረጃ በተመሳሳይ ተቋማት ከሚሰጡ አገልግሎቶች ሊመጣጠን የሚችል
ድጋፍ የመስጠት አቅም አልገነቡም፡፡ በዚህም ምክንያት የኢንዱስትሪዎቹን
ምርታማነት በማሳደግ፣ እሴት የመጨመር አቅማቸው ተጠናክሮ ያለቀለት ምርት
ለውጭ ገበያ እንዲያቀርቡ በማድረግ፣ የውጭ ገበያ መረጃዎችን በማቅረብ ኩባንያዎች
ምርታቸውን በተወዳዳሪ ዋጋ እንዲሸጡ በማገዝ፣ ወቅታዊ ቴክኖሎጂ በማፈላለግ፣
በማላመድና በማሰራጨት፣ በምርምርና ስርፀት፣ በኢንዱስትሪዎች መካከል ትስስር
በመፍጠር፣ የኩባንያዎች አመራርና አደረጃጀት ዘመናዊና አለማቀፍ ደረጃ እንዲይዝ
በማድረግ የኢንዱስትሪውን መሰረት በማስፋት ረገድ ያስገኙት ውጤት ሲመዘን ደካማ
ነው፡፡

ከነባሮቹ ኢንስቲትዩቶች ውስጥ የቆዳ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ከውጭ


ተመሳሳይ ተቋም ጋር በተፈጠረለት የቤንችማርኪንግ እና የቁርኝት ትስስር የተሻለ
አቅም የፈጠረና በፒ.ኤች.ዲ እና በማስተርስ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሀይል ማፍራት
የተቻለ ቢሆንም የቴክኖሎ ሽግግር በማስረጽና በማስፋፋት ረገድ የተወሰኑ ሞዴል
ኩባንያዎችን ከመፍጠር አልፎ በዘርፍ ደረጃ ለውጥ ለማምጣት ከዚህ የበለጠ መስራት
ይጠበቅበታል፡፡ ይሁን እንጂ የተፈጠሩ ጥቂት የሚባሉ ሞዴል ኩባንያዎች ያስገኙት
ውጤት ሲመዘን የሚያበረታታ ነው፡፡ ለመጥቀስ ያህል ኢንስቲትዩቱ ከህንድ የጫማ
ዲዛይንና ልማት ኢንስቲትዩት ጋር ጥምረት በመፍጠር ለሰባት የአገር ውስጥ ጫማ
አምራች ፋብሪካዎች በጫማ ዲዛይን አወጣጥ፣ በቴክኒካል ክህሎት፣ በጥራት አጠባበቅ፣
በምርታማነት ማሻሻል እና በናሙና ሙከራ ዙሪያ ቴክኒካል ድጋፍ ማድረግ ችሏል፡፡
በዚህም በራምሴ ጫማ ፋብሪካ ብቻ የጫማ ቶማይ ቆረጣ በቀን ከ2000 ጥንድ ወደ
2400 ጥንድ ሲያድግ፣ የምርት ጥራት ችግር መጠን ከ3 በመቶ ወደ 1 በመቶ
ወርዷል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ድርጅቱ ይህ ድጋፍ ከተደረገለት በኋላ ጥሩ ስም ካለው
የጣሊያን ጫማ አምራች ድርጅት ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለው ስምምነት ፈርሞ
በወር እስከ 60,000 ጥንድ ጫማዎችን በማምረት ወደ ጣሊያን በመላክ ተጠቃሚ ሆኗል
(PSRC & EDRI, 2016)፡፡ ይህም የሚያሳየው አምራቾች ክፍተቶቻቸውን ሊሞላ
የሚችል በቂ የቴክኖሎጂ ድጋፍ ከተደረገላቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ
ማምጣት እንደሚችሉ ነው፡፡ ስለዚህ ይህ የቆዳ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 159


ተልዕኮውን ለማሳካት የሚያደርገው እንቅስቃሴ ጥሩ ቢሆንም ከዚህ የበለጠ አለማቀፍ
ደረጃውን የጠበቀ ኢንስቲትዩት ለመሆን አቅሙን ከዚህ የበለጠ ማሳደግ ይገባዋል፡፡

የጨርቃጨርቅ ልማት ኢንስቲትዩት ብቃት ካለው የውጭ ተቋም ጋር በማስተሳሰር


አቅሙን የመገንባት ስራ የተጀመረው በቅርብ ጊዜ ሲሆን የብረታብረት ኢንዱስትሪ
ልማት ኢንስቲትዩት ቁርኝት ገና የተቋሙን የአቅም ክፍተት በመለየት ደረጃ ላይ
የሚገኝ ነው፡፡ በቅርቡ የተቋቋሙት የምግብ፣ የመጠጥና ፋርማሲዩቲካል፣ የኬሚካልና
ኮንስትራክሽን ግብአቶች፣ የስጋና ወተት ኢንስቲትዩቶች ደግሞ የቁርኝት ስራ
ያልተጀመረባቸው ከመሆኑ በተጨማሪ መሠረተ ልማት ያልተሟላላቸው በመሆኑ
ከፋሲሊቴሽን የዘለለ ድጋፍ መስጠት አልቻሉም፡፡

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከቴክኖሎጂ ሽግግርና እድገት አንጻር ቁልፍ ሚና


መጫወት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከዚህ አንጻር እያበረከቱ ያለውን አስተዋጽኦ በምናይበት
ጊዜ ጎልቶ የሚታይ ስራ አልተሰራም፡፡ እ.ኤ.አ በ2012 የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
ያጠናው ጥናት ይህን ሀሳብ የሚያጠናክር ነው፡፡ ቴክኖሎጂን ከመቅሰም እና ከማሳደግ
እንዲሁም ከማሸጋገር አንጻር ዩኒቨርስቲዎች ሚናቸውን አልተወጡም፡፡ ከዚህ ይልቅ
ዩኒቨርስቲዎች ከኢንዱስትሪዎች አንጻር ወደኋላ የቀሩ ይመስላል (MoST, 2012)፡፡
የዩኒቨርስቲ ኢንዱስትሪ ትስስር በምናይበት ጊዜ ትስስሩ የላላ ስለመሆኑ በተለያዩ
አካላት የተጠኑ ጥናቶች (Science Technology Information center, 2015) እና በዚህ
ጥናት የተሰበሰቡ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ መካከለኛ እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት
የኢንዱስትሪውን የክህሎትና ዕውቀት ፍላጎት ከማሟላት አኳያ ክፍተት እንዳለባቸው
የአምራች ባለሀብቶች ይገልፃሉ፡፡ ኢንዱስትሪው የሚፈልገው የሰው ኃይል ለማፍራት
በመጀመሪያ ዲግሪ በዩኒቨርስቲዎች ከሚገባ የተማሪ ቁጥር 70 በመቶ ያህሉ በተፈጥሮ
ሳይንስና ምህንድስና የትምህርት መስክ እንዲማር እየተደረገ ነው፡፡ በቴክኒክና ሙያ
የሚሰለጥን መካከለኛ ዕውቀትና ክህሎት ያለው ተማሪም በአብዛኛው በኢንዱስትሪው
የሚፈለግ ሙያ እንዲማር እየተደረገ እና በብዛትም እየተመረቀ ይገኛል፡፡ ነገር ግን
ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚመረቀው አብዛኛው በንድፈ ሐሳብ ክህሎት ላይ
የዳበረ ዕውቀት የሌለው እና በተግባር ክህሎትም ዝቅተኛ መሆኑን በአምራች
ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ባለሀብቶች ይገለፃሉ፡፡ ለምሳሌ ከዩኒቨርስቲዎች በጨርቃጨርቅ
ምህንድስና ተመርቀው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ፅ/ቤቶች ተመድበው በዘርፉ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 160


ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች በሙያቸው መደገፍ እንዳልቻሉ የየክልሉ የጥቃቅንና
አነስተኛ ልማት ኤጀንሲዎችና ቢሮዎች ይገልፃሉ፡፡

የዩኒቨርስቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር (Industry-University Linkage) ዓላማ ኢንዱስትሪዎችና


ዩኒቨርስቲዎች ተደጋግፈው እንዲሰሩና ብቃት ያለው የሰው ኃይል ማፍራት ላይ
የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ነው፡፡ ነገር ግን በመካከላቸው ጠንካራ የሚባል ግንኙነት
አልመሰረቱም፡፡ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸው በተወሰነ ጊዜ በአምራች ኢንዱስትሪዎች
ለተግባር ልምምድ ያሰማራሉ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ተማሪዎች ለማስተባበር የሚመደቡ
ሱፐርቫይዘሮች በቂ ድጋፍና ክትትል ስለማይደረግላቸው በተግባር ስልጠና በቂ ክህሎት
አያገኙም፡፡ ይህም ሆኖ ፋብሪካዎች ፈቃደኛ ሆነው ሲያስተናግዱ አብዛኛው ሰልጣኝ
ተማሪ የስራ ስነምግባር እንደማይታይበትና ክህሎት ለመጨበጥ የማይጓጓ እንደሆነ
በሰፊው ይገለፃል፡፡ በዚህ አካሄድ ነገ ኢንዱስትሪውን የሚቀላቀለው ኃይል ሙያውን
በደንብ ያልጨበጠ እና በስነ ምግባር ያልታነፀ እንደሚሆን አሁንም በተግባር እየታየ
ያለ ተጨባጭ ጉዳይ ነው፡፡

ዩኒቨርስቲ-ኢንዱስትሪ ግንኙነት ሌላው ዋናው የተልዕኮ ጉዳይ ዩኒቨርስቲዎች


ኢንዱስትሪውን ችግር-ፈቺ የሆነ ምርምር በማድረግ ድርሻቸውን እንዲወጡ
ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለምሳሌ አምራች ኢንዱስትሪው እያጋጠመው ያለ የቴክሎጂ ልማትና
ሽግግር ዓቅም ውስንነት ዩኒቨርስቲዎች በጥናትና ምርምር ሊፈቱት ይገባል፡፡ ነገር ግን
ይህን በተግባር ለማስፈፀም የሚያስችል ግልፅና ዝርዝር አሰራር የለም ማለት ይቻላል፡፡
ዩኒቨርስቲዎች የጥናትና ምርምር ማዕከላት ቢኖራቸውም በኢንዱስትሪው ዙሪያ የሚታዩ
ችግሮችን ያለማየትና ትኩረት ሰጥቶ መስራት ላይ ክፍተቶች አሉባቸው፡፡ በእርግጥ
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጥቂት የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በኢንዱስትሪው እና ሌሎች
መስኮች ዙሪያ ጥናት በማድረግ አስተዋፅኦ እያደረጉ ነው፡፡ በሌላ በኩል ከፍተኛ
የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸው በአምራች ኢንዱስትሪ ልምምድ ሲያደርጉ
በፋብሪካው ችግሮች ላይ መሰረት አድርገው ለችግሮቹ መፍትሄ ማቅረብ
ይጠበቅባቸዋል፡፡ አንዳንድ ተማሪዎች በተግባር ልምምድ ሂደት በግላቸው የተወሰነ
ጥናት የማካሄድና ለተግባር ልምምድ የተመደቡበት ፋብሪካ የመፍትሔ ሐሳብ
የማቅረብ ጅምር መታየት ጀምሯል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሙከራ ያላቸው ተማሪዎች
ፋብሪካው ቀጥታ በምልመላ ቅጥር እያገኙም ይገኛሉ፡፡ ሌላው መልካም ጅምር
አንዳንድ የዩኒቨርስቲ አስተማሪዎች አዳዲስ ምርቶች የመፍጠርና የማልማት ሂደት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 161


ጅምር መኖሩ ነው፡፡ እነዚህ ጅማሮዎች የሚበረታቱ ቢሆንም ነገር ግን በቂ
አይደሉም፡፡ በአጠቃላይ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አምራች ኢንዱስትሪውን
በምርምር በሚፈለገው ደረጃ እያገዙት አለመሆኑን ለመረዳት አያዳግትም፡፡

5.7 በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ አቅምና ድርሻ

በአምራች ኢንዱስትሪ ስምሪት ባለሀብቱም ሆነ ዘርፉን የሚመራ የመንግስት መዋቅር


ገና ጀማሪዎች እንደመሆናቸው በመማር ሂደት ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡ አብዛኛው
በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማራ ባለሀብት ዘመናዊነት ባልተላበሰ የንግድ ስራ ለበርካታ
ዓመታት የቆየ በመሆኑ አምራች ዘርፉን ሲቀላቀል በልምድ እንጂ በተሟላ ዕውቀት ላይ
ተመስርቶ እንዳልሆነ የአምራች ዘርፉ እና የንግደ ዘርፍ ማህበራትና አደረጃጀቶች
ይገልፃሉ፡፡ በአምራች አንዱስትሪ የተሰማሩ ባለሀብቶችም ከልምዳቸው ተነስተው
ተመሳሳይ አስተያየት አላቸው፡፡

ለባለሀብቱ ትልቁ ፈተና ቴክኒሻን ሆኖ ምርት ማምረት ሳይሆን ኢንዱስትሪውን


ሳይንሳዊና ዘመናዊ በሆነ የአመራር ስልት አለመምራት ነው፡፡ ይህ ችግር ከዘርፍ
መረጣና የአዋጭነት ጥናት ይጀምራል፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ የአመራር ልምድና
ሁኔታን ስንመለከት በአብዛኛው ፋብሪካውን የሚመራው ባለቤቱ ወይም የቅርብ ዘመድ
ስራ አስኪያጅ ወይም ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሆኖ ይታያል፡፡ ስለዚህ ፋብሪካው በተሟላ
ዕውቀትና ክህሎት ከመምራትና ውጤታማ ከማድረግ አኳያ ሰፊ ክፍተት
እንደሚታይበት አምራቾች ከልምዳቸው በመነሳት ማረጋገጫ ሰጠዋል፡፡

ይህ በግልፅ የሚያሳየን የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ የስራ ፈጠራ ችሎታ (entrepreneurial


skill) ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ደፍሮ ውጣ ውረድ በበዛበት የአምራች
ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለመሰማራት አይፈልግም፡፡ እንዲሁም የግል ባለሀብቱ አመጣጥ ኢ-
መደበኛ ከሆነ ዘርፍ (informal sector) ስለሚሆን መደበኛ የሆነ አካሄድ መላመድ
ሲቸገሩ ይስተዋላል፡፡ በተጨማሪም የሀገር ውስጥ ባለሀብት ባህሪ፣ በጥቃቅንና አነስተኛ
አምራች ዘርፍ ላይ ለረጅም ጊዜ በመወሰኑ ወደ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዝ
የማደግ ፍላጎቱ ተገድቦ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ወደ ከፍተኛ
ኢንተርፕራይዝ ባለቤትነት የመሸጋገር ሂደቱን አዝጋሚ አድርጎታል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 162


በሌላ በኩል የስትራቴጅክ እቅድ ወይም የንግድ እቅድ (business plan) ማዘጋጀት
አለመቻል፣ የሂሳብ አያያዝ ስልት ደካማነት፣ ገበያን የመተንተን አቅም ማነስ፣
አለማቀፍ የገበያና የቴክኖሎጅ ሁኔታን በውል ያለመረዳትና የመሳሰሉት የእውቀት እና
ክህሎት ውስንነቶች የግል ባለሀብቱ የረጅም ጊዜ ራዕይ ሰንቆ እንዳይንቀሳቀስ
አድርጎታል፡፡

የግል ባለሀብቱ ችግር፣ በእሴት ሰንሰለት ላይ በሚገኙ ኢንተርፕራይዞች መካከል


ቅንጅት (inter firm linkage) አለመኖሩ ቀጣይነት ያለው የግብአትና የምርት አቅርቦት
እንዳይኖር በማድረጉ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ የምርታማነት እና ተወዳዳሪነት ውስን
እንዲሆን አድርጎታል፡፡

የሀገር ውስጥ ባለሀብት የንግድ አደረጃጀት (ownership structure) ስንመለከት፣


አብዛኛውን ጊዜ በግለሰብ (sole proprietorship) እና ኀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር
(PLC) የተደራጁ ናቸው፡፡ አልፎ አልፎ በሽርክና (partnership) ተደራጅተው ይገኛሉ፡፡
የእነዚህ አደረጃደት ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ቢታወቅም በአንፃሩ ለአምራች
ኢንዱስትሪው የማይመቹ አሉታዊ ጎኖች አሏቸው፡፡ ካፒታል የማሰባሰብ አቅማቸው
ቢሆን ዝቀተኛ ሆኖ ይገኛል፣ የእነዚህ ኢንተርፐራይዞች ባለቤቶች ቁጥራቸው አናሳ
በመሆኑ በግለሰብ ወይም በቤተሰብ የሚተዳደሩና የሚመሩ በመሆናቸው ስራው
በሠለጠነ ባለሙያ እየተመራ አይደለም፣ የኢንተርፐራይዞቹ ዘለቄታ እንዲሁ በባለቤቶቹ
ህልውና ላይ የተንጠለጠለ ይሆናል፡፡ በመሆኑም የግል ባለሀብቱ የተያዘው በአምራች
ኢንዱስትሪ (በተለይ ደግሞ የመካከለኛና የከፍተኛ የሆኑትን) ለካፒታል፣ በቀጣይነት፣
እና ለሰለጠነ የሰው ሀይል ችግሮች የተጋለጠ ሆኖ እናገኛዋለን፡፡

5.8 ለአምራች ኢንዱስትሪ የመሬትና መሰረተ ልማት አቅርቦት

የሀገራችን ኢንዱስትሪ በውጪ ገበያ መመራት አለበት ሲባል በዓለም ገበያ በጥራት፣
በዋጋ እና በአቅርቦት ዓቅም ተወዳዳሪ ምርት ማቅረብ መቻል ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት
ዓቅም ለመፍጠር ከሚያስችሉ ጉዳዮች አንዱ ጥራት ያለው የመሰረተ ልማት አቅርቦት
ነው፡፡ በአለም ላይ ብዙ ሀገራት የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው
በብቃት በአለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆን እንዲሁም የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 163


ለመሳብ በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ከፍተኛ ውድድር እያካሄዱ መሆናቸውን
ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡

5.8.1 ለአምራች ኢንዱስትሪ የመሬት አቅርቦት

ለተፋጠነ የኢንዱስትሪ ልማት አገራችን ካላት አመቺ ሁኔታዎች መካከል አንዱ


በመንግሥት እጅ ያለና በቀላሉ ለአልሚ ባለሀብት በአነስተኛ ዋጋ ሊተላለፍ የሚችል
ሰፊ የመሬት ሀብት ነው፡፡ በሀገራችንም በተለይ ከ1998 ወዲህ በኢንቨስትመንት
የሚሰማራው ባለሀብት ለመሬት የሚያወጣው ወጪ ለፋብሪካው የሚያወጣውን
ኢንቨስትመንት እንዳያዳክመው መሬት በዝቅተኛ ዋጋ እንዲቀርብለት እየተደረገ ነው፡፡
ለአምራች ኢንዱስትሪው በተለየ ዞን /የኢንዱስትሪ መንደር/ እንዲቋቋምና ዓቅም
የፈቀደውን ያህል መሰረተ ልማት እንዲሟላለት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ በተለይ
የክልሎች ዋና ከተሞችና ሌሎች ትላልቅ ከተሞች ለኢንዱስትሪ የሚሆን መሬት
በማዘጋጀት በተነፃፃሪነት የተሻለ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ በፌደራልና ክልል መንግስታት
ከሚደረገው ጥረት በተጨማሪ ዞኖችና ከተሞች የኢንዱስትሪ መንደር ለማቋቋም መሬት
ለይተው እየከለሉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡በሂደትም መሰረተ ልማት ለማሟላት ጥረት
እያደረጉ መሆኑን በውይይቶችና ቃለ መጠይቆች ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

ባለሀብቱን ለመሳብና በተፋጠነ መልኩ ወደ ልማት/ምርት ለማሸጋገር የሚያስችሉ


መሰረተ-ልማቶችን (መንገድ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የፋብሪካ ህንፃዎች (sheds)፣ ውሀ፣
ወዘተ) ለማሟላት ጥረት እየተደረገ ቢሆንም በአፈፃፀም ላይ የሚታዩ ክፍተቶች
ይስተዋላሉ፡፡ በፌዴራልና በክልል አስፈፃሚ አካላት መካከል በቅንጅት ባለመሰራቱ
የተዘጋጀው የመሬት ሀብት በተፈለገው መጠን ጥቅም ላይ ሊውል አልቻለም፡፡
በክልሎች እና በከተማ መስተዳድሮች 11,559.18 ሄክታር መሬት ለኢንዱስትሪ ዞን
የሚውል መሬት ቢከለልም ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በየካቲት እና መጋቢት ወር 2007
ዓ.ም ባደረገው የዳሰሳ ጥናት እስከ መጋቢት 2007 ዓ.ም 4,863.62 ሄክታር መሬት
ብቻ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን ቀሪው 7,300.94 ሄክታር መሬት (63.16 በመቶ)
ባለሃብቶችን እየጠበቀ ይገኛል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት በፌዴራል እና በክልል
ቅንጅት ማነስ፣ በመሰረተ ልማት ውስንነት፣ ባለሃብቱ በአዲስ አበባ እና ዙሪያ መሬት
የመጠይቅ ፍላጎት የተነሳ ነው (ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ 2007 ዓ.ም)፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 164


ከታች በሰንጠረዡ እንደተመለከተው ለናሙና ከተወሰዱት አምስት ክልሎች እና ሁለት
የከተማ መስተዳድሮች መካከል ኦሮሚያ ክልል ትልቁን የተከለለ የቦታ ስፋት ድርሻ
ይዟል፡፡ ክልሉ ለባለሀብቱ መሬት በማሰራጨት ከፍተኛውን ቁጥርም እንዲሁ ይዟል፡፡
ይሁንና አሁንም በክልሉ ከተለለው መሬት ውስጥ 67.42% የሚሆነው ስራ ላይ ያልዋለ
መሬት ነው፡፡ ደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/ መንግስት ከአማራ እና ከትግራይ ክልል ቀጥሎ በአራተኛ
ደረጃ ላይ የሚገኝ ከፍተኛውን ለባለሀብቶች የተዘጋጀ መሬት የያዘ እና በስርጭት
ከኦሮሚያ እና ከአማራ ክልል ቀጥሎ ተጠቃሽ ሲሆን ከአራቱ ክልሎች ዝቅተኛውን
በስራ ላይ ያልዋለ መሬት ቁጥር አስመዝግቧል፡፡

በአሁኑ ወቅት ለአዳዲስ የአምራች ኢንቨስትመንት ፈታኝ ከሆኑ ሁኔታዎች አንዱ


የመሬት አቅርቦት ችግር ነው፡፡ ከተሞች አምራች ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን ያህል
መሬት እያቀረቡ አለመሆኑን ይገልፃሉ፡፡ በቂ መሬት ካሳ ተከፍሎበት ለኢንዱስትሪ
ለማዘጋጀት ዓቅም አልፈቅድ ብሎ እንደቆሙ ይገልፃሉ፡፡ የሀገር ውስጥ አምራቹ ገና
ያልዳበረና በፍጥነት ወደ ዓለም ገበያ ያልገባ በመሆኑ መንግስት በተሻለ ሁኔታ
ያደራጃቸው የኢንዱስትሪ መንደሮች ለመግባት ያለው ዕድል ጠባብ ሆኗል፡፡ ሌላው
ማነቆ የባለሀብቱን አቅም ያላገናዘበ የኢንቨስትመንት መስፈርት ነው፡፡ የመሬት ሊዝ
አዋጁ (አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 12/ሠ) የሀገር ውስጥ አምራቹ መሬት በቀላሉ
እንዲያገኝ መሬት በምደባ እንዲሰጥ ሲደነገግ የኢንቨስትመንት መስፈርቱ የሀገር ውስጥ
ባለሀብቱ መሬት የማግኘት ዕድሉ እንዲዳከም እያደረገው ይገኛል፡፡ ክልሎች
በኢንቨስትመንት ፕሮጀክቱ አይነት መሰረት ዝቅተኛና ከፍተኛ የመሬት ስፋት
ማሰቀመጣቸው እንደ መርህ ትክክል ነው፡፡ የዚህ ክፍተት የመሬት መስፈርቱ
የሀገራችንን ባለሀብት ዓቅም ያላገናዘበ መሆኑ ነው፡፡ ከተለያዩ የንግዱ ማሕበረሰብ
ተወካዮች እንዲሁም አምራቾች ጋር በተደረጉ ውይይቶች ለማወቅ እንደተቻለው
በቅርብ ጊዜ አምራች ዘርፉን እየተቀላቀለ ያለው ባለሀብት በተነፃፃሪ መካከለኛ እና
አነስተኛ የካፒታል ዓቅም ያለው ነው፡፡

በአንድ በኩል መስፈርት /standard/ መኖሩ አግባብነት ያለው ነው፡፡ ምክንያቱም በስመ
ኢንቨስትመንት መሬት እየተወሰደ የሚቸበቸብበት ወይም ታጥሮ የሚቀመጥበት
አካሄድ ሊያስቀር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡ በሌላ በኩል ግን ማልማት ለሚፈለግ ነገር
ግን ተነፃፃሪ ዓቅሙ ዝቅተኛ የሆነ የሀገራችንን የግል ባለሀብት የሚያበረታታ
አይደለም፡፡ አሁን በተግባር በተለያዩ ከተሞች እየታየ ያለው ወደዘርፉ ሊቀላቀል

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 165


የሚፈልግ ባለሀብት ቁጥሩ ቀላል እንዳልሆነ ነገር ግን ይህ ችግር መሰናክል
እንደሆነባቸው በተደረጉ ውይይቶች ተገልጿል፡፡ ጥቂት ተነሳሽነቱ ያላቸው ባለሀብቶች
የግለሰብ ቤት ተከራይተው ፋብሪካ አቋቁመው ምርት እያመረቱ እንደሚገኙም ለማወቅ
ተችሏል፡፡ ለምሳሌ በአዳማ ከተማ አንድ የልብስ ስፌት ፋብሪካ በብር 6,000,000
ካፒታል የግለሰብ መኖሪያ ቤት ተከራይቶ በማምረት ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ባለሀብት
ለተከራየው ቤት ዕድሳት ብር 300,000 የከፈለ ሲሆን በየወሩ ብር 30,000 ለቤት ኪራይ
እየከፈለ ይገኛል፡፡ ይህ እንደ ምሳሌ ቢቀርብም በሌሎች ከተሞችም (ለምሳሌ መቀሌ፣
ሀዋሳ፣ ወዘተ) የግለሰብ ቤት ተከራይተው የሚሰሩ የመካከለኛና አነስተኛ አምራች
ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች እንዳሉ ተጠቁሟል፡፡

ሰንጠረዥ 5.2 በክልሎች ለባሀብቶች የተሰጠ እና በስራ ላይ የዋለ የቦታ ስፋት


ተ.ቁ ክልል ጠ.የቦታ ስፋት ለባለሀብቶች የተሰጠ በስራ ላይ በስራ ላይ
በሄክታር ቦታ በሄክታር ያልዋለ በሄክታር ያልዋለ(%)
1 ትግራይ ክልል 1050.56 380.98 669.58 63.74
2 አማራ ክልል 1276.05 613.11 662.94 51.95
3 ደ/ብ/ብ/ሕ ክልል 1020.94 539.03 471.71 46.20

4 ኦሮሚያ ክልል 7782.73 3157.31 5247.73 67.43


5 ሀረሪ ክልል 65.2 18.008 47.192 72.38
7 አዲስ አበባ 156.7 69.18 80.79 51.56
ከተማ
መስተዳደር
8 ድሬዳዋ ከተማ 207 86 121 58.45
መስተዳደር
ድምር 11,559.18 4,863.618 7,300.942 63.16
ምንጭ፡ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር (2007 ዓ.ም)

ሌላው ጉዳይ ከኢንዱስትሪ ዞን ውጭ ያለ መሬት በኢንዱስትሪ መንደር መስተናገድ


ለማይችሉ ባለሀብቶች እንደ አማራጭ በምደባ አለመሰጠቱ ነው፡፡ በእርግጥ
ኢንዱስትሪው የሚፈልገው መሬት በቀላሉ ለማዘጋጀት ኢንዱስትሪው እርስ በራሱ
በግብአትና ውጤት የምርት ሰንሰለቱን መሰረት አድርጐ ተደጋግፎ እንዲያድግ፣
የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግሩ እንዲፋጠን እንዲሁም ለኢንዱስትሪው ቀልጣፋ
አገልግሎት ለመስጠትና ለመደገፍ የኢንዱስትሪ መንደሮችን ማቋቋም አስፈላጊ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 166


በሌላ በኩል የከተማው ፕላን እስከፈቀደ ድረስ ፋብሪካዎች ከኢንዱስትሪ መንደር
ውጭም ሊቋቋሙ እንደሚችሉ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በሁሉም ከተሞች ከኢንዱስትሪ
መንደር ውጭ መሬት በአምራች ኢንዱስትሪ ለሚሰማራው ባለሀብት በጨረታ ካልሆነ
በስተቀር በምደባ እየተሰጠ አይደለም፡፡ በኢንዱስትሪ መንደሮች ምርታቸውን ለውጭ
ገበያ የሚያቀርቡ የፋብሪካ ባለሀብቶች ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ ይህ በአንድ በኩል
ተገቢ ነው፡፡ ነገር ግን ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚተካ ምርት (Import
subsititution) የሚያመርት ባለሀብትም ተገቢውን ትኩረት ማግኘት አለበት፡፡

ሌላው ከመሬት አቅርቦቱ ጋር ተያይዞ መታየት ያለበት አሁን ባለንበት ወቅት ቅድሚያ
ትኩረት እንዲደረግባቸው የተለዩት የአምራች ኢንዱስትሪዎችና ከእነዚህ ውጪ ያሉት
አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚመለከት ነው፡፡ ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብት ፈጣን ዕድገት
ባላቸው ጠቀሜታና ሌሎች መመዘኛዎች መሠረት መንግስት የተወሰኑ አምራች ዘርፎች
ላይ ትኩረት በመስጠት የሀገር ውስጥና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እንዲሳተፉበት
ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ እንደ ሲሚንቶ፣ ብረታብረትና ኬሚካል የመሳሰሉ
ትላልቅ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ደግሞ ከውጭ የሚገባ ምርት የሚተኩ በመሆናቸው
ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲለሙ እየተደረገ ነው፡፡ ይህ አሰራር ለተወሰነ ጊዜም
ቢሆን ትክክለኛ አቅጣጫ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ነገር ግን ከእነዚህ ኢንዱስትሪዎች
ውጭ ያሉት ሌሎች የአምራች ኢንዱስትሪዎች በዝቅተኛ ሊዝ በሚቀርበው የመሬት
አቅርቦት ተጠቃሚ መሆን አልቻሉም፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ መሠረተ ጠባብ
ስለሆነ ዘርፉን ሊቀላቀሉ የሚመጡ ኢንቨስትመንቶችን አሟጠን ለመጠቀም ለእነዚህ
ባለሀብቶችም ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

በሌላ በኩል የመሬት አስተዳደር ብቃት ማነስና ተጠያቂነት ያለመኖር በመሬት


አቅርቦት የሚታየው ሌላ ተጨማሪ ተግዳሮት ነው፡፡ ምን ያህል መሬት
ለኢንቨስትመንት እንደተሰጠና ምን ያህሉ እንደለማ በየክልሉ የተጠናቀረ መረጃ
ባይገኝም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰደ ባለሀብት ቁጥር እና በ2007 ዓ.ም በድምሩ
በማምረት ሂደት ላይ ካሉት ጋር በማነፃፀር ሲታይ ሰፊ መሬት ሳይለማ በግለሰቦች እጅ
እንደሚገኝ ማየት ይቻላል፡፡ ለምሳሌ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በመጀመሪያው
የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ለ381 ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ መንደርና
ከኢንዱስትሪ መንደር ውጭ 165.39 ሂክታር መሬት ለኢንቨስትመንት ሰጥቷል፡፡
አፈፃፀማቸውን ስንመለከት 122 ምርት ማምረትና አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 167


37 ባለሀብቶች አጥር ገንብተው ቁመዋል፤ 66 በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛሉ፤ 77
መጋዘን ገንብተው ቁመዋል፤ 64 መሬት ተረክበው ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ያላደረጉ
ሲሆኑ 15 የወሰዱት 33.88 ሄክታር መሬት አለአግባብ ላልታለመለት ተግባር
አውለዋል፡፡ ይህም ሆኖ ግን የከተማው አስተዳደር ሕጋዊም ሆነ አስተዳደራዊ
የማስተካከያ እርምጃ አልወሰደም፡፡ በሁሉም ክልሎች መሬት ሳያለሙ የተቀመጡ
ብዙዎች ናቸው፡፡ ለፋብሪካ መሬት ወስደው መጋዘን ገንብተው ቁጭ ብለው ኪራይ
የሚሰበስቡም (ለምሳሌ አዳማና ድሬዳዋ ከተሞች) ቁጥራቸው ቀላል አይደለም፡፡
ለሶስተኛ ወገን ያስተላለፉ እንዳሉም ይነገራል፡፡ ስለዚህ ለኢንቨስትመንት መሬት
የወሰደ አካል ካላለማው በኢንቨስትመንት አዋጁ መሠረት አመራሩ እያስመለሰ
በትክክል ለሚያለማ መስጠት ስላልቻለ እንጂ የመሬት ዕጥረት ስላለ አለመሆኑ
ሊሰመርበት ይገባል፡፡

የመሬት አስተዳደር በአግባቡ እየተመራ አለመሆኑን ባለሙያውና አመራሩ


የሚስማሙበት ቢሆንም በችግሮች ምክንያት ላይ ግን የተለያየ አቋም አላቸው፡፡
አመራሩ መሬት ያላለማውን ከመንጠቅ ይልቅ ባለሀብቱን እያበረታቱ ወደ ስራው
እንዲገባ ማድረግን ይመርጣል፤ ካልሆነ ግን ቀጣይ የሚመጣም በፍጥነት ወደተግባር
የመግባቱ ሁኔታ እርግጠኛ አይደለንም የሚል በአንድ በኩል በሌላ በኩል ደግሞ
መንግስት መሰረተ ልማት የማሟላት ኃላፊነቱን በጊዜው ስለማይወጣ ባለሀብቱ
የወሰደውን መሬት እንዲመለስ ማድረግ አግባብ አለመሆኑን ይከራከራሉ፡፡ ከመሠረተ
ልማት አቅርቦት መጓተት በኩል ሲታይ የአመራሩ አባባል ትክክል ሊሆን ይችላል፤
ነገር ግን መሠረተ ልማት የማሟላት ኃላፊነት የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮችም
ጭምር በመሆኑ ከክልሎችና ከተማ አስተዳደሮቹ አልፎ ለማንም የሚቀርብ ወቀሳ
አይሆንም፡፡ በአጠቃላይ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ያለው አመራር መሬት በገሀድ
ለሶስተኛ ወገን ሲተላለፍ እና ለሌላ አገልግሎት ሲውል እያየ የማስተካከያ እርምጃ
አለመውሰዱ ለህገወጥነት መባባስ በር መክፈቱ አልቀረም፡፡

በሌላ በኩል ከባለሙያውና ከንግዱ ማሕበረሰብ የሚቀርበው ምክንያት ከዚህ በጥቂቱም


ቢሆን ይለያል፡፡ መሬት ከኢንቨስትመንት የአንድ ማዕከል አገልግሎት መውጣቱ ሕጋዊ
ላልሆነ ስራ መስፋፋት የተመቸ ሆኗል፡፡ መሬት በቀረበው የቢዝነስ ፕላን ሳይሆን
በእጅ ካልሆነም በሰው ተሂዶ ስለሚገኝ አመራሩ እርምጃ መውሰድ አይችልም የሚል
ነው፡፡ ህዝቡ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ በየደረጃው ከሚገኙ የምክር ቤት መድረኮች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 168


ጀምሮ ባገኘው አጋጣሚ አቤቱታና የሰላ ትችት እያቀረበ፤ ነገር ግን አመራሩ
ለዓመታት ማስተካከያ እርምጃ መወሰድ አልቻለም፡፡ ሌላው ከባለሙያው የቀረበው
ጠንካራ ትችት መሬት በየደረጃው ያለ ከፍተኛ አመራር ያለበት ኮሚቴ ስለሚሰጥ
እርምጃ ለመውሰድ የሚደፍር ባለሙያም ሆነ ኃላፊ ከፍተኛ ስጋት አለበት፡፡ ርምጃ
በሚወስድ ባለሙያ እና ሌላ የሚመለከተው አካል ወይም ሀላፊ በቀጥታም ሆነ
በተዘዋዋሪ በየደረጃው ከሚገኝ ከፍተኛ አመራር የተለያዩ ተፅዕኖና ጥቃት
እንደሚደርስበት ገልፀዋል፡፡ ለኢንቨስትመንት መሬት የሚፈቅደው የየክልሉ
የኢንቨስትመንት ቦርድ ነው፡፡ ይህንን ታሳቢ የተደረገው ቀደም ሲል ይታይ የነበረ
የመሬት አሰጣጥ ክፍተት ለማጥበብ ብሎም በኢንቨስትመንት ስም ለኪራይ ሰብሳቢነት
ይጋለጥ የነበረ አሰራር ለማስወገድ ነው፡፡ አሁንም ቢሆን ግን መሬት አሰጣጡ ችግር
አለበት፡፡ ከመደበኛው የግንኙት መስመር ውጭ የሚሰራውን የድለላ ስራ አላስቆመም፡፡
መጀመሪያ በኢንቨስትመንት ቦርድ ከዚያ የከተማ ከንቲባ ጽ/ቤትና የከተማ ፕላን
ወይም የቅየሳ ባለሙያ ረጅም ውጣውረድና በየደረጃው ደጅ መጥናት ተባብሷል፡፡
በአጠቃላይ ሲታይ ለኢንቨስትመንት የሚሰጥ መሬት በቦርድ እየተወሰነ በከተሞች ካብኔ
መሬት የመስጠቱ የተሻለ አሰራር ከማምጣት ይልቅ ረጅም ቢሮክራሲ በመፍጠር
የባለሀብቱን ውጣውረድና ድካም የጨመረ ሆኗል፡፡

5.8.2 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት

የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ማልማት ዋነኛው ዓላማው ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ


በመፍጠር የውጭ እና የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንትን በስፋት መሳብ ነው፡፡ በዚህም
ለዜጎች በርካታ የስራ ዕድል በመፍጠር፣ በዋነኛነት የውጭ ንግድን በማስፋፋት፣ ከውጭ
የሚገቡ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት፣ የውጭ ምንዛሬ ገቢያችን
በማሳደግ፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ በማስቻል፣ ዘመናዊ የስራ
አመራር ልምድ እንዲጎለብትና በሙያ እና እውቀት የተካነ በርካታ የሰው ሀይል
በማፍራት በአጠቃላይ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገታችን ለማፋጠን የሚያስችል
ዋነኛ የልማት መሳሪያ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ማልማት በመሬት አጠቃቀም ላይ የሚታዩውን ኪራይ


ሰብሳቢነት ለማስቀረት፣ የሎጅስቲክስና የጉምሩክ አገልግሎት ችግሮችን ለማስወገድ፣
መሰረተ-ልማቶችን በማሟላት ኢንቨስትመንቶች ያለብዙ ውጣ ውረድ እንዲሰፍሩና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 169


በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ምርት እንዲሸጋገሩ ለማድረግ፣ በመካከለኛና ትላልቆቹ እና
በአነስተኛ ኢንዱስትሪዎች መካከል ትስስር ለማመቻቸትና ክላስተር ለመፍጠር በዚህም
የቴክኖሎጂ፣ የአመራረትና የስራ አመራር ዘዴን ለማስተላለፍ፣ የሥራ ዕድልን
ለማሳደግ፣ የሀገር ሀብትን በቁጠባና ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመጠቀምና አረንጓዴ
የኢንዱስትሪ ልማት አቅጣጫን ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡

ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በፌዴራል ደረጃ ለ11


ኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚውል 7,687.7 ሄክታር መሬት ተከልሎ ወደ ስራ ተገብቷል፡፡
ፓርኮቹ በዋናነት ኤክስፖርትን ታሳቢ አድርገው የሚለሙ ሲሆን በዚህ መሰረት 20
በመቶ ለሀገር ውስጥ ባለሃብቶች እና 80 በመቶ ለውጭ ባለሃብቶች አገልግሎት
እንደሚውል ታሳቢ ተደርጓል፡፡ ፓርኮቹ በአሁኑ ወቅት በተለያየ የትግበራ ደረጃ
ማለትም በመሬት ክለላ፣ በዲዛይን፣ ግንባታ እና ግንባታቸው የተጠናቀቁ እና ስራ
የጀመሩ ናቸው፡፡

ሰንጠረዥ 5.3 በፌደራል ደረጃ የተቋቋሙና በመቋቋም ላይ ያሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች


ተ. የሚገኝበት ከአዲስ አበባ ከጅቡቲ የተከለለ ምዕራፍ I ምዕራፍ I
የፓርኩ
ቁ ቦታ ያለው ርቀት ወደብ ያለው መሬት (ሄክታር) የሚጠናቀቅበት ጊዜ
ስም
(ኪ.ሜ) ቅርበት (ሄክታር)
1 አዲስ አዲስ አበባ አዲስ አበባ 863 8.7 8.7 በስራ ላይ ያለ
ኢንዱስትሪ
መንደር
2 ቦሌ ለሚ I አዲስ አበባ አዲስ አበባ 863 156 156 በስራ ላይ ያለ
3 ቦሌ ለሚ II አዲስ አበባ አዲስ አበባ 863 186 186 2017

4 ቂሊንጦ አዲስ አበባ አዲስ አበባ 863 337 337 2017


5 ሐዋሳ ደቡብ 275 998 300 100 ተጠናቆ ለባለሀብቶች
መተላለፍ ጀምሯል፡፡
6 ድሬዳዋ ምስራቅ 473 380 1500 150 2016
7 ኮምቦልቻ ሰሜን-ምስራቅ 380 480 700 50 2016
8 መቀሌ ሰሜን 760 750 1000 50 2016
9 አዳማ ደቡብ-ምስራቅ 74 678 2000 100 2016
10 ባህር ዳር ሰሜን-ምዕራብ 578 985 1000 50 2016/2017
11 ጅማ ደቡብ-ምዕራብ 346 1098 500 50 2016/2017
ምንጭ፡ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር (2007 ዓ.ም)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 170


ከዚህ በተጨማሪም በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አራት የተቀናጁ
የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ፓይለት ፕሮጀክቶችን በአራት ክልሎች 1000 ሄክታር
መሬት ተዘጋጅቷል፡፡ እነዚህን ፓርኮች በማልማት በሚሊዮን የሚቆጠሩ አርሶአደሮች
ምርት ከኢንዱስትሪ ጋር ትስስር እንዲፈጥሩ በማድረግ በግብርና ምርቶች ላይ እሴት
በመጨመር የአግሮ ኢንዱስትሪ ምርቶች የኤክስፖርት እና የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻ
እንዲጨምር በማድረግ የገጠር ትራንስፎርሜሽን እና የግብርና እና ኢንዱስትሪ ትስስር
ለማሳለጥ በመንግስት ደረጃ በዕቅድ ተይዞ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡

ሰንጠረዥ 5.4 በክልል ደረጃ የሚቋቋሙ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች

ተ.ቁ ክልል እና ልዩ ስሙ የተከለለው ሄክታር


1 ኦሮሚያ፣ግንደ-በረት 250 ሄክታር
2 አማራ፣ቡሬ 250 ሄክታር
3 ደቡብ ብሄር ፣ብሄረሰቦችና ህዝቦች 250 ሄክታር
4 ትግራይ 250 ሄክታር
ድምር 1000 ሄክታር
ምንጭ፡ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር (2007 ዓ.ም)

ነገር ግን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ግንባታ እና አስተዳደር ጋር ተያይዞ ችግሮች


እያጋጠሙ እንደሆነ በተለያየ ደረጃ ያሉ ዘርፉን የሚመሩ አካላት ይገልፃሉ፡፡
በመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ግምገማ ወቅትም ከኢንዱስትሪ
ፓርኮች ማስፋፋት ጋር ተያይዞ ስድስት ቁልፍ ችግሮች ተለይተዋል፡፡ እነሱም፡
የተሟላ የስትራቴጂ ፍሬም ወርክ፣ የህግ ማዕቀፍ እና እይታ አለመኖር፣ የመፈፀም
አቅም ውስንነት፣ የንዑስ-ዘርፎች ተኮር ኢንዱስትሪ ዞኖች አለመኖራቸው፣ የፋይናንስ፣
የመሬት እና የማበረታቻ ውስንነት፣ የመሰረተ ልማትና ሌሎች አገልግሎት አቅራቢ
ተቋማት የአቅም ውስንነት እና የቅንጅት ጉድለት እና የተቀናጀ የማስተዋወቅ እና
የባለሀብት መሳብ ክፍተቶች ናቸው፡፡

በተለይ በሀገር ውስጥ ያለው የግንባታ አቅም ደካማ መሆን ፓርኮቹ በተያዘላቸው ጊዜ
እና የጥራት ደረጃ እንዳይጠናቀቁ አድርጓቸዋል፡፡ ይህንንም በማሰብ በአሁኑ ወቅት
መንግስት የግንባታ ስራውን በውጭ ተቋራጮች በማስገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ሌላው
ከፓርኮች ጋር ተያይዞ የሚነሳው ችግር ፓርኮቹን በባለቤትነት ከማስተዳደር ጋር

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 171


ተያይዞ ያሉ ችግሮች ናቸው፡፡ በቅርቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን
እራሱን ችሎ እንዲዋቀር የተደረገ ቢሆንም ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በፓርኮቹ
ልማት እና ማስተዳደር ጋር ተያይዞ እንዴት እንደሚሰሩ በግልፅ የተቀመጠ አሰራር
እንደሌለ ገልፀዋል፡፡ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በኩል እንደተገለፀው ኢንዱስትሪ
ፓርኮችን ማን በባለቤትነት እንደሚያስተዳድራቸው በግልፅ የተቀመጠ መመሪያ
የለም፡፡ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ላይ የተሰጠው ዋነኛው
ሀላፊነት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የሰለጠነ የሰው ሀይል ማቅረብ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ እነዚህ በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ የሀገር


ውስጥ ባለሀብቱ ምን ያህል ተጠቃሚ ሊሆን ይችላል የሚለው ነው፡፡ ለምሳሌ
በአንደኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተገንብቶ ለባለሀብቶች የተላለፈው የቦሌ
ለሚ ምዕራፍ አንድ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአቅም ማነስም ይሁን በፍላጎት ማጣት
ምክንያት አንድም የሀገር ውስጥ ባለሀብት አልተሰማራም፡፡ በቅርቡ ወደስራ እየገባ
ባለው የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓረክም ቢሆን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ተሳትፎ በጣም
ዝቅተኛ ነው፡፡ይህ ጉዳይ በአንድ ወገን በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብቱ ተሳትፎ 20 በመቶ መሆኑ በቂ አይደለም የሚሉ አካላት ቢኖሩም ነገር ግን
የተሰጠውን ኮታም ቢሆን መጠቀም እንዳልተቻለ የተግባር እንቅስቃሴዎች
ያስገነዝባሉ፡፡ ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በፌደራል ደረጃ ከሚገነቡ ፓርኮች በተጨማሪ
ለወደፊቱ በክልሎች በሚገነቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል
ይገልጻሉ፡፡ ክልሎች እና ከተሞች ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ ኢንዱስትሪ ለሚሸጋገሩ
የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች ደረጃቸውን የጠበቁ የኢንዱስትሪ ክላስተሮችና
ፓርኮች እንደሚለሙ በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ላይ ሰፍሮ
ይገኛል፡፡

5.8.3 የመሰረተ ልማት አቅርቦት (የኤሌክትሪክ ሀይል፣ መንገድ፣ ውሀ፣ ኢንተርኔት)

የመሠረተ ልማት ግንባታ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ትልቅ ሚና አለው፡፡


በሀገራችን በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ተሟልተው ካለቀረቡ መሰረተ ልማቶች
መካከል የኤሌክትሪክ ሀይል፣ መንገድ፣ ውሀና የኢንተርኔት አገልግሎቶች ናቸው፡፡
በተለይ እንደ ጊዜያዊ ችግር የሚታይ ቢሆንም የኤሌክትሪክ ሀይል ማነስና መቆራረጥ
ለአምራች ኢንዱስትሪው ፈታኝ ማነቆ ሆኗል፡፡ በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የሚገኝ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 172


አንድ የብረታ ብረት ኢንጅነሪንግ ፋብሪካ በየካቲት ወር 2007 ዓ.ም ብቻ 31 የስራ
ሰዓት በጀነሬተር ለመስራት ተገዷል፡፡ በዚህ ከተማ አስተዳደር የሚገኝ ሌላ የምግብ
ኮምፕሌክስ ፋብሪካ ደግሞ በተመሳሳይ ሁኔታ ከ2004 - 2006 ዓ.ም በኤሌክትሪክ
ማነስና ሀይል መቆራረጥ ምክንያት በምርት ብክነት ብቻ 1.9 ሚሊዮን ብር ኪሳራ
እንደደረሰበት አስረድቷል፡፡ በዚህ ፋብሪካ ለ10 ደቂቃ ኃይል ሲቋረጥ ብር 200,000
እስከ ብር 250,000 ኪሳራ እንደሚደርስበት የስራ ኃላፊዎች ገልፀዋል፡፡ ሰራተኛው
ላልሰራበት ሰዓት የተከፈለውን ክፍያ ሳያካትት በ2006 በጀት ዓመት ብቻ ፋብሪካው
ብር 6,846,954.00 በግብአትና ምርት እንዲሁም ብር 158,880 በማሽነሪ ብልሽት
በድምሩ ብር 7,005,825.00 ኪሳራ አጋጥሞታል፡፡ በተጨማሪም ከዓለም የምግብ
ድርጅት ከፍተኛ የገበያ ትስስር ያለው በህፃናት አልሚ ምግብ ማምረት የተሰማራ
በሀዋሳ ከተማ የሚገኝ አንድ የአግሮ ኢንዱስትሪ በ2006 ዓ.ም የበጀት ዓመት
መጀመሪያ አጋማሸ በኃይል መቆራረጥ ምክንያት በጊዜው ምርቱ ማድረስ ባለመቻሉ
በሚሊዮኖች የአሜሪካን ዶላር የሚገመት የገበያ ዕድል ያጣ መሆኑን የፋብሪካው
ሀላፊዎች ገልፀዋል፡፡ ያለበቂ ምክንያት የሚቆራረጠው የኤሌክትሪክ ኃይል
የሚያደርሰውን ኪሳራ በሚመለከት የተወሰኑ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች
ለመብራት ኃይል ካሳ ሲጠይቁ አስተዳደሩ ወቅታዊ መልስ ስለማይሰጣቸው ለኪሳራው
ካሳ እንደማይጠይቁ ገልፀዋል፡፡እንደ አሰራርም የመ/ቤቱ ግለሰቦች ጥፋት ሲያደርሱ
ተጠያቂ የሚሆኑበት አግባብ የለም፡፡ በአጠቃላይ በመብራት ኃይል መዋቅር ውስጥ
ተጠያቂነት አለመኖሩ ሌላ ተጨማሪ ችግር መሆኑን ተገልጋዮች ገልፀዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የሀይል አቅርቦት በተመለከተ መንግስት በመጀመሪያው የዕድገትና


ትራንስፎርሜሽን ያጋጠሙ ጉድለቶችን መሰረት በማድረግ ለአምራች ኢንዱስትሪ
ቅድሚያ ለመስጠት በተለይም የኢንዱስትሪ ፓርኮችና መንደሮችን በማማከል የከፍተኛ
ሃይል አስተላላፊ መስመሮች እንዲያልፉ ተደረጎ እንደሚሰራ የታቀደ ሲሆን የግል
ባለሃብቱም ኃይል አመንጭቶ እንዲሸጥ ተፈቅዶለታል፡፡ በዚህም መሠረት፡-
 ኢንዱስትሪዎች የራሳቸውን ሰብስቴሽን በመገንባት ከብሄራዊ ግሪድ ሃይል
እንዲወስዱ፤
 ኢንዱስትሪዎች ከ5 ሜጋ ዋት ጀምሮ በማመንጨት እንዲጠቀሙ ማድረግ፣
ትርፉንም እንዲሸጡ መፍቀድ፤
 ባለሃብቶች በሃይል ማመንጨት ኢንቨስትመንት እንዲገቡ ማበረታታት የመሳሰሉ
አቅጣጫዎች በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 173


በዚህም መሰረት ለአምራች ኢንዱስትሪ ከመጀመሪያው የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን በተሻለ ሁኔታ ሃይል እንደሚያገኙ ይጠበቃል፡፡

በሌላ በኩል የተነሳው የመሰረተ-ልማት ችግር የመንገድ ልማትን የሚመለከት ነው፡፡


በተለይ በየከተሞቹ ያሉት አብዛኛዎቹ የኢንዱስትሪ መንደሮች የመንገድ መሠረተ
ልማት የተሟላላቸው አይደሉም፡፡ አብዛኞቹ የኢንዱስትሪ መንደሮች በከተማው ውስጥ
በስፋት የተዳረሰው መንገድ አልደረሳቸውም፡፡ በተለያዩ ከተሞች አዳዲስ የተመሰረቱ
የመኖሪያ መንደሮች ሳይቀር ቢያንስ የጠጠር መንገድ ሲሰራላቸው የኢንዱስትሪ
መንደሮች ግን የጥርጊያ መንገድ እንኳ እየተሰራላቸው አለመሆኑን በአካል በመስክ
ምልከታ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ መንገዱ የተሰራላቸውም ከተሰራ በኋላ ለጥገናው ዞር
ብሎ የሚያይላቸው አካል የለም፡፡ ወደ ኢንዱስትሪ መንደሮች የሚገቡ መንገዶች
እጅጉን የተጐዱ ወይም ለመግባት ጭራሽ የሚያስቸግሩ ናቸው፡፡ በባህርዳር እና ሃዋሳ
ከተሞች ውስጥ ያሉ የኢንዱስትሪ መንደሮች ለዚህ እንደማሳያ ሊሆኑ የሚችሉ ናቸው፡፡
በእነዚህ ከተሞች የሚገኙ የኢንዱስትሪ መንደሮች ሌላ ከተማ ያሉ እስኪመስሉ ድረስ
የጠጠር መንገድ እንኳ በአግባቡ የተገነባላቸው አይደሉም፡፡ በአዳማ ከተማም አንደኛው
የኢንዱስትሪ መንደር ተመሳሳይ ችግር ሲኖረው ሁለተኛው የኢንዱስትሪ መንደር
ደግሞ ጭራሽ መንገድ አልተሰራለትም፡፡

መንግስት ከመንገድ ጋር ተያይዞ ያሉ ማነቆዎችን በውል ለመለየት የሞከረ ሲሆን


በአለማቀፍ ደረጃ በኤክስፖርት ተወዳዳሪ ለመሆን ተወደዳዳሪ የሆነ የትራንስፖርት ዋጋ
እንሚያስፈለግ በማመኑ በአሁኑ ወቅት የባቡር ትራንስፖርት መሰረተ ልማት በተለያዩ
የሀገሪቱ ቀጠናዎች እየለሙ ይገኛሉ፡፡ እየለሙ ካሉ የባቡር ኮሪደሮች መካካል የአዲስ
አበባ ጅቡቲ ኮሪደር በ2009 በጀት አመት ስራ የሚጀምር በመሆኑ የትራንፖርት ዋጋ
በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ተብሎ ይታሰባል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን በአምራች ኢንዱስትሪ
ለተሰማሩ ድርጅቶች ለማበረታት ልዩ የየብስ ትራንስፖርት ታሪፍ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ
እየተደረገ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንግድ የካርጎ አገልግሎትም ኤክስፖርትን
ለማበረታታ ልዩ የካርጎ ታሪፍ በማውጣት ኤክስፖርተሮችን እየደገፈ ይገኛል፡፡ ነገር
ግን መንግስት በቀጣይ አስር ዓመታት ሊያሳካ ካስቀመጣቸው የተለጠጡ የኢንዱስትሪ
ልማት ግቦች አንፃር አሁን እየተኬደበት ያለው ፍጥነት ብዙም የሚያረካ አይደለም፡፡
ከዚህ በበለጠ ማስፋፋትና ማጠናከር ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 174


እንደ ኤሌክትሪክ ሀይልና ሌሎች መሰረተ-ልማቶች የተጋነነ ባይሆንም የውሀ አቅርቦት
ችግርም ሌላው በአምራች ኢንዱስትሪው የሚነሳ ጉዳይ ነው፡፡ አብዛኛዎቹ
ኢንዱስትሪዎች በትላልቅ ከተሞች የተሰባሰቡ ናቸው፡፡ እነዚህ ከተሞች የውሃ
አቅርቦታቸው እንኳንስ ለፋብሪካዎች የሚፈልጉት ያህል ሊሆን ለነዋሪዎቻቸው እንኳ
የሚበቃ አይደለም፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም መቀሌ ከተማ የሚገኙ የምግብ
ማቀነባበርያዎችና ድሬዳዋ የሚገኙ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች የውሃ አቅርቦት ችግር
እንዳለባቸው ይገልፃሉ፡፡ የመቐለ ከተማ ውሃ አቅርቦት ከማንም ከተማ በላይ ከፍተኛ
እጥረት ያለበት ነው፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ ውሃው ጨዋማ በመሆኑ የምግብ ማቀነባበሪያ
ፋብሪካዎች ተጨማሪ የማጣሪያ ወጪ ጠይቋቸዋል፡፡

በሌላ በኩል አምራቾች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችና ምርቶች፣ ገበያ፣ የምርት ዲዛይን፣


የኢንቨስትመንት ሸሪክ ወዘተ ለማፈላለግ እና ከነባር የገበያ እና ኢንቨስትመንት
እንዲሁም አማካሪዎች ለመገናኘትና ወሳኝ ስራዎች ከመስራት አኳያ የኢንተርኔት
መሰረተ-ልማቱ ተኪ የሌለው ሚና ያለው መሆኑን የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች
ይገልፃሉ፡፡ ሆኖም ግን የአገልግሎቱ ተደራሽነትና ጥራት የተጠቃሚዎችን ፍላጎት
የሚመልስ አለመሆኑን ይገልፃሉ፡፡

የምዕራፉ ማጠቃለያ

የኢንዱስትሪ ልማትን በዘላቂነት ለማሳካት ልማታዊ ባለሀብት የኢንዱስትሪ ልማት


ሞተር ሆኖ ሊያንቀሳቅሰውና መንግስት ደግሞ ብቃት ያለው አመራር ሊሰጥ ይገባል፡፡
ከላይ በዝርዝር እንደቀረበው በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ጥቂት የማይባሉ
ባለሀብቶች በብዙ ችግሮችና ማነቆዎች ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የማምራት አቅማቸውም በጣም
ዝቅተኛ (በአማካይ 58%) ነው፡፡ በጥቅሉ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በንዑስ ዘርፉ
ልማት ላይ የሞተርነት ሚናውን በሚፈለገው ደረጃ እየተጫወተ አይደለም፤ መንግስትም
የሚጠበቅበትን የአመራር ሚና ከመጫዎት አኳያ ክፍተቶች ያሉበት መሆኑን
ለመረዳት አያዳግትም፡፡ ከላይ በዝርዝር የታዩት መሰረታዊ ችግሮችና ማነቆዎች ዋና
ዋና መንስኤዎቻቸው፡ የአፈፃፀም ክፍተት ወይም ድክመት፣ የአቅም ችግርና በቂ
ትኩረት ያለመስጠት፣ ተናቦና ተቀናጅቶ ያለመስራት ወይም የአሰራር ክፍተት፣
የአሰራር ስርአት አለመኖር የመሳሰሉት ናቸው፡፡ በሀገራችን የአምራች ኢንዱስትሪ
ባለሀብቱን የሚያግዙ ስትራቴጂዎች፣ አዋጆች፣ መመሪያዎች፣ ህጎች፣ ደንቦችና ሌሎች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 175


ሪፎርሞች ቢዘጋጁም አፈፃፀማቸውን ስንመለከት በንግድ፣ በአገልግሎትና በሪል እስቴት
ዘርፎች ለተሰማሩ ኪራይ ሰብሳቢ ባለሀብቶች የተመቹ ከመሆን አልዘለሉም፡፡ልማታዊ
ባለሀብቱን ከጥገኛው ባለሀብት ነጥሎ የሚያጠናክርና የሚያበረታታ ስራ አልተሰራም፡፡
በጥቅሉ ሁሉም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ
የግል ባለሀብቱን በሚመለከት የተሰጣቸውን ድርሻ በትክክል ወደ መሬት አውርዶ
ከመፈፀም አኳያ ሰፊ ክፍተቶች እንዳሉባቸው መገንዘብ ይቻላል፡፡

አመራሩና ባለሙያው በኢንዱስትሪ ስትራቴጂውና በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ


የግል ባለሀብት ሚና ላይ የጠራ አመለካከትና ተግባቦት አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡
በተለይ በክልሎች ያለው የኢንዱስትሪ አመራር የኢንዱስትሪ ስትራቴጂውን
ለመተግበር የሚያስችለው አቅም የሚጎድለውና ብዥታ ያለበት ይመስላል፡፡ ለአምራች
ኢንዱስትሪ ባለሀብት የተፈቀዱ ማበረታቻዎችም ሙሉ በሙሉ በትክክለኛው አቅጣጫ
መተግበር አልተቻለም፤ በትክክል ለታለመላቸው አላማ መዋል አለመዋላቸውም
ክትትልና ቁጥጥር አይደረግም፡፡ አዳዲስ ባለሀብቶችን በቅስቀሳና ግንዛቤ በመፍጠር
ወደ አምራች ኢንዱስትሪ ለመሳብ የተደረገው ጥረት ዝቅተኛ ነው፡፡ በአምራች
ኢንዱስትሪ የውጭ ባለሀብቱንና የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን አቀናጅቶ ለመጠቀም
የሚያስችል የአሰራር ስርአት ተዘርግቶ በስፋት ወደ ተግባር አልተገባም፡፡

በሌላ በኩል በአምራች ዘርፍ ተሰማርቶ የሚገኘው አብዛኛው ባለሀብት የኢንዱስትሪ


ስትራቴጂዎችን፣ ማበረታቻዎችንና ድጋፎችን ከመረዳት አኳያ ሰፊ ክፍተት አለበት፡፡
በሀገራዊ የልማት አቅጣጫዎችና በዓለማቀፍ ገበያና የምጣኔ-ሀበት ሁኔታ ላይ ያለው
ዕውቀት ውስን ነው፡፡ ጥቂት የማይባሉ ባለሀብቶች ከዕውቀት፣ ክህሎት እና የአመራር
ችግሮች በተጨማሪ የአመለካከትና የግንዛቤ ችግሮች ይንፀባረቁበታል፡፡ ከነዚህም ውስጥ
ዋና ዋናዎቹን ለመጥቀስ፡ በአጭር ጊዜ ትርፋማ ለመሆን መዳዳት እና የኪራይ
ሰብሳቢነት ዝንባሌ (የመንግስትን ድጋፍ ላልታለመለት አላማ መጠቀም)፣
የሚያጋጥሙአቸውን ችግሮች ተቋቁሞ በሰከነ መንገድ ኢንዱስትሪዎች ወደ ተሻለ ደረጃ
ለማድረስ በትጋት አለመስራት፣ በሰንካላ ምክንያት የመንግስትን ድጋፍ መጠበቅ፣
ወዘተ ጎልተው የሚታዩ ችግሮች ናቸው፡፡

በአጠቃላይ የአምራች ኢንዱስትሪው የግል ባለሀብት የሞተርነት ሚናውን


እንዳይጫዎት ያደረጉትን ከላይ የተጠቀሱ መሰረታዊ ችግሮችና ማነቆዎች በዘላቂነት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 176


መፍታት የሚያስችል አቅጣጫ መከተልና በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ
የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማራውን የሀገር ውስጥ
የግል ባለሀብት በሚመለከት የየድርሻቸውን ቀሪ ስራዎች ቆጥሮ በመውስድ ለተስተዋሉ
መሰረታዊ ችግሮች ዘላቂና ስር-ነቀል መፍትሄ ለማምጣት በቁርጠኝነት መስራት
እንደሚጠበቅባቸው መገንዘብ ይቻላል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 177


ምዕራፍ 6
የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብትና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ ባለሀብቶች
ንፅፅር

በሀገራችን የግሉን ባለሀብት ኢንቨስትመንት ለማሰፋፋትና ለማሳደግ ወሳኝ ከሆኑ


ጉዳዮች መካከል በዋናነት ሊጠቀሱ የሚችሉት ገበያ-መር ኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና
ማህበራዊ መረጋጋት፣ የሰራተኛ ክፍያ መጠንና ምርታማነት፣ መሰረተ-ልማት፣ የገበያ
ስፋት እንዲሁም የተለያዩ ከመንግስት የሚቀርቡ ማበረታቻዎችና ድጋፎች ናቸው፡፡
እነዚህ ጉዳዮች በአብዛኛው ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታንና
ዕድልን የፈጠሩ ቢሆንም በተለያዩ ውስጣዊና ውጫዊ ምክንያቶች የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብቱ በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ በሚፈለገው ደረጃ የሚጠበቀውን
ያህል ውጤታማ እንዳልሆነ የሚታወቅ ነው፡፡

በመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ስንመለከት የአምራች ኢንዱስትሪው


ዘርፍ በጥቅል ሀገራዊ ምርትና በውጭ ምንዛሬ ግኝት አስተዋፅኦ ዝቅተኛ ነው፡፡
ዝቅተኛ ውጤት እንዲመዘገብ ምክንያት የሆኑ ብዙ ዝርዝር ችግሮችና ማነቆዎችን
ማንሳት ይቻላል፡፡ ነገር ግን ጥቅል ዋና ዋና ችግሮችን ለማንሳት ያህል፡ ብዙ አምራች
ኢንዱስትሪዎች ማምረት ከሚችሉት አቅም በታች (Under Capacity Utilization- on
Average 58.14%) በተለያዩ ምክንያቶች (ምዕራፍ 4 ላይ ተዘርዝረዋል) ለማምረት
መገደዳቸው፣ ጥቂት የማይባሉ ባለሀብቶች በዘርፉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው
ነገር ግን በፍጥነት ወደ ማምረት ተግባር አለመግባታቸው፣ አብዛኛው የሀገር ውስጥ
ባለሀብት የኢንቨስትመንት ምርጫው የአገልግሎት ዘርፍ መሆኑና የአምራች
ኢንዱስትሪው ኢንቨስትመንት ሰፊ፣ ጠንካራና ጥራት ያለው አለመሆኑና የመሳሰሉት
ይገኙበታል፡፡ በጥቅሉ ሲታይ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው
ውስጥ የዋና ተዋናይነት ሚናውን በሚገባ እንዲጫወት የሚያስችለው ምቹ ሁኔታ
አልተፈጠረለትም፡፡

በአጠቃላይ ለአምራች ኢንዱስትሪው የግብአት አቅርቦት፣ በቂ የፋይናንስና ብድር


አቅርቦት፣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት፣ የተፈቀዱ ማበረታቻዎችን በተግባር ከመፈፀምና
በቂ ድጋፍ ከመስጠት አኳያ፣ የተሳለጠ የንግድ ስርአትና ገበያ ከመፍጠር፣ የአምራቹን
ምርታማነትና እሴት የመጨመር አቅማቸውን በማሳደግ ያለቀለት ምርት ለውጭ ገበያ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 178


እንዲያቀርቡ ከማድረግ አንፃር፣ ወቅታዊ ቴክኖሎጂ በማፈላለግ፣ በማላመድና
በማሰራጨት ተግባር፣ በምርምርና ስርፀት ከመደገፍ አኳያ፣ በኢንዱስትሪዎች መካከል
ትስስር ከመፍጠር አንፃር፣ አመራራቸውና አደረጃጀታቸው ዘመናዊና አለማቀፍ ደረጃ
እንዲይዝ ከማደረግ አኳያ እንዲሁም ጥራት ያላቸውን ኢንቨስትመንቶች በመሳብ
የኢንዱስትሪውን መሰረት ከማስፋት አንፃር በመንግስትም ሆነ በግል ባለሀብቱ
የተደረገው ጥረት ዝቅተኛ ነው፡፡

6.1 የአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብትና የውጭ ባለሀብት ሁኔታ

በሀገራችን የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ ሰነዶች ላይ እንደተቀመጠው የሀገር ውስጥ የግል


ባለሀብቱ እና የውጪ ባለሀብቱ ሁለቱም ለኢንዱስትሪው ልማትና ዕድገት የማይተካ
የየራሳቸው ሚና አላቸው፡፡ አንዱ የሌላውን ሚና ሊተካ አይችልም፡፡ የውጭ ባለሀብቱ
ወደ ሀገራችን ሲገባ የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን፣ የማናጅመንት ክህሎትን
በማስተላለፍ፣ የገበያ ኔትወርክ በመፍጠር፣ የኢንዱስትሪ የስራ ባህል በማስፋፋት፣ ከሀገር
ውስጥ ባለሀብቱ ጋር በጆይንት ቬንቸር (Joint venture) እንዲሰራ በማድረግ፣ ወዘተ
የመሳሰሉትን ጥቅሞች ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱና ለኢኮኖሚው ዕድገት እንዲያበረክት
ይጠበቃል፡፡ በሌላ በኩል የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ከላይ እንደተገለፀው በኢንዱስትሪው
ዘላቂ ልማትና ዕድገት ላይ የራሱን ከፍተኛ ሚና እንዲጫወትና ዋናው አንቀሳቃሽ
ሞተር እንዲሆን ይጠበቃል፡፡ስለዚህ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በዘርፉ ዘላቂ ዕድገት
ላይ ያለው ሚና በዋና ተዋናይነት የሚታይ እንጂ በደጋፊነት የሚታይ አይሆንም፡፡ነገር
ግን የውጪ ባለሀብቱ በዘርፉ ልማት ላይ የደጋፊነት ሚና ይኖረዋል፡፡

የግሉ ባለሀብት የኢንዱስትሪ ልማት ሞተር ይሁን ሲባል የሀገር ውስጥ ባለሀብት
ዋነኛው ሀይል የሚሆንበት፣ የውጭው ባለሀብት በሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ላይ
በተደራቢነት በሰፊው ተሳታፊ የሚሆንበት፣ በሁለቱም ድምር አቅም የሀገራችን
የኢንዱስትሪ ልማት የሚፋጠንበት ሁኔታ መፍጠር ማለት እንደሆነ የሀገራችን
የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ያስረዳል፡፡ ከሁለቱ አንዱ ብቻውን የምንፈልገው ፈጣን
ዕድገት ሊያረጋግጥ ስለማይችል አጣምረን መጠቀም አለብን ማለት ነው፡፡ የሁለቱንም
አቅም አጣምረን በምንጠቀምበት ጊዜ ግን ሁለቱም እኩል ሚና ሊኖራቸው
እንደማይችል ተገንዝበን የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ዋነኛው፣ የውጭው ደግሞ የማይተካ
ሚና ቢኖረውም አጠናካሪ ሀይል መሆኑን መገንዘብ ያሻል፡፡ በሀገራችን በተጨባጭ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 179


እየሆነ ያለው ግን ከዚህ በተቃራኒ ስለመሆኑ የተወስኑ ማሳያዎች በማቅረብ ስንመለከት
በሀገራችን አሁን እየተሰሩ ያሉት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለምሳሌ የሃዋሳ ኢንዱስትሪ
ፓርክ ለሀገር ውስጥ ባለሀብት የተሰጡ ማበረታቻዎች የሚደገፉ ቢሆኑም በፓርኮች
መግባት የሚችሉት የሀገር ውስጥ ባለሀበት ብዛት ከ20 በመቶ እንደማይበልጥ
የኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን አሳውቋል፡፡ በፓርኩ የሚገቡት የሀገር ውስጥ
ባለሀብቶች ቁጥራቸው ውስን መሆኑ ለሀገር ውስጥ ባለብት የሞተርነት ሚናው
እንዳይጫወትና የውጪ በለሀብቱ ባለበት አከባቢ በማምረት ሂደት ውስጥ ያለውን
የአመራርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዕውቀት እንዳይማር እንቅፋት ይሆነዋል፡፡ ሌላው
የፋይናንስ አቅረቦት ጉዳይ ነው፡፡ ውጪ ባለሀብቱ በተነፃፃሪ የተሻለ የካፒታል አቅም
ቢኖረውም ከሀገር ውስጥ ፋይናንስ ዋነኛ ተጠቃሚ መሆኑ ነው፡፡

ሌላው የውጪ ባለሀብት መሰማራት የነበረበት ከፍተኛ እሴት በሚጨምሩ ዘርፎችና


የሀገር ውስጥ የግሉ ዘርፍ ሊሰማራባቸው የማይችሉ መሆን ሲገባቸው በተጨባጭ
በሀገራችን ከፍተኛ ቅጥር ያላቸው የውጪ ባለሀብቶች ከሀገሪቱ የተለያዩ ማበረታቸዎች
ወስደው የሚጨምሩት እሴት ግን በጣም አነስተኛ መሆኑ ነው፡፡ ምንም እንኳ
በሀገራችን የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብት አቀናጅቶ
የመጠቀም አቅጣጫ የዕውቀትና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የካፒታል ዕጥረት ከመፍታት
አንፃር ያለው ፋይዳ የተቀመጠ ቢሆንም እሰካሁን የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብት
አቀናጅተ የመጠቀም ስራ ጠንከር ያለ ስራ ያልተሰራበት መሆኑን መገንዘብ
አያዳግትም፡፡

ሌላው የውጪ ባለሀብት ከፍተኛ ማበረታቻና ድጋፍ ወስዶ ምርቱ በውጪ ገበያ
እንደሚያቀርብ ውል ገብቶ ጥሬ ዕቃ ከቀረጥና ሌሎች ማበረታቻዎች እየተጠቀመ ነገር
ግን ከ84% በላይ የውጪ ባለሀብቶች ምርታቸው ወደ ውጪ አለመላካቸው የቅርብ ጊዜ
መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ በአንድ በኩል የቁጥጥርና ድጋፍ አለመኖሩ በሌላ በኩል ደግሞ
ባለሀብቶች ምርታቸውን ወደ ውጪ ሳይልኩ ሲገኙ ተጠያቂ የሚሆኑበት የህግ ማዕቀፍ
አለመኖሩን ያመለክታል፡፡ የውጪ ባለሀብት በአለም ገበያ ተወዳዳሪ የሆነ ሸቀጥና
አገልግሎት በማምረት ተጨማሪ ሀብትና ልማት በመፍጠር ከመከበር ይልቅ ያለችውን
በገበያ ከለላና ማበረታቻ ምክንያት የተፈጠረች ኪራይ በመቀራማት ላይ
ተሰማርተዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 180


6.2 በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብትና የሌሎች ዘርፎች
ባለሀብቶች

በዚህ ጥናት ውስጥ ለማየት የተሞከረው በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በአምራች


ኢንዱስትሪ የተሰማራውን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ከሌሎች ዘርፎች (በተለይ
ከንግድ፣ ኮንስትራክሽንና አገልግሎት) ባለሀብቶች ጋር ሲወዳደር ያለውን ሚና እና
ጥቅል ሁኔታ በጥቂቱ ለማሳየት ነው፡፡

እንደሚታወቀው በአለም ላይ በፈጣን ዕድገታቸው ስኬታማ የሆኑ ብዙ ሀገሮች የዕድገት


አቅጣጫዎቻቸውን ስንመለከት መጀመሪያ በግብርና ላይ ከፍተኛ ትኩረት ሰጠው ከሰሩ
በኋላ እና የተወሰነ ካፒታል ከፈጠሩ በኋላ ፊታቸውን ወደ አምራች ኢንዱስትሪ
አዙረዋል፡፡ አምራች ኢንዱስትሪውን ተጠቅመው ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ካስመዘገቡ
በኋላ እንዲሁም የንዑስ ዘርፉ ዕድገት ጣራ ላይ ሲደርስ ደግሞ ወደ አገልግሎት ዘርፎች
ተሸጋግረዋል፡፡ ቻይና፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ጃፓን፣ ታይዋን የመሳሰሉ የምስራቅ ኤስያ ሀገሮች
እንደምሳሌ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ጆ ስቱድዌል የተባለ ፀሀፊ በኢኮኖሚ ዕድገት ስኬታማ የሆኑ ሀገራት ከግብርናው


ዕድገት ቀጥሎ ከአገልግሎት ሰጪ ሴክተሮች ይልቅ ለአምራች ኢንዱስትሪ ከፍተኛ
ትኩረት በመስጠት መስራታቸው በጥቂቱ ሁለት ዋና ዋና ጠቀሜታዎች እንዳሉት
ይገልፃል፡፡ የመጀመሪያው አምራች ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ዕሴት በመጨመር ለታዳጊ
ሀገሮች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፈጣን ዕድገት ትልቅ አስተዋፅኦ ስላለው ነው፡፡
ሁለተኛው ጠቀሜታ የአምራች ኢንዱስትሪ ምርቶች ተፈላጊውን የጥራት ደረጃ
እስካሟሉ ድረስ በየትኛውም የአለም ክፍል በነፃነትና በቀላሉ ገበያ ውስጥ ይገባሉ፡፡
በሌላ አገላለፅ አምራች ኢንዱስትሪ አለማቀፍ ንግድን ያስፋፋል፤ ንግድ ደግሞ ለፈጣን
ኢኮኖሚ ዕድገት አስፈላጊ ነው፡፡

ወደ ሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ስንመለከት ቢያንስ ላለፉት አምስት አመታት መንግስት


ለኢንዱስትሪው በተለይም ለአምራች ኢንዱስትሪው ንዑስ ዘርፍ ከሌሎች ዘርፎች
የተለየ ትኩረት በመስጠት የተለያዩ ስራዎችን ለማከናወን ቢሞክርም ውጤቱ
የተፈለገውን ያህል ደረጃ እንዳልደረሰ ይታወቃል፡፡ የንግድ (በተለይ አስመጪና ላኪ)፣
ኮንስትራክሽን (በተለይ ሪል እስቴት)፣ እና አገልግሎት ዘርፎች ያለብዙ ውጣውረድና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 181


ድካም በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ትርፍ ስለሚያስገኙ አብዛኛው የሀገር ውስጥ የግል
ባለሀብት ወደ እነዚህ ዘርፎች እየጎረፈ ነው፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከእነዚህ ዘርፎች ጋር ሲወዳደር ትልቅና በቀላሉ ሊመለስ


የማይችል (Return of investment) ካፒታልን ማፍሰስ የሚጠይቅ፣ የረጅም ጊዜ
ዕይታንና ቁርጠኝነትን እንዲሁም ዘመናዊ አደረጃጀትን የሚፈልግ፣ የዳበረ ክህሎትና
ዕውቀት የሚፈልግ፣ ከፍተኛ ተወዳዳሪነትና የኪሳራ ተጋላጭነት ያለበት፣ የትርፍ
ህዳጌው አነስተኛ እና ከረጅም ጊዜ በኋላ የሚገኝ ነው፡፡ በሌላ በኩል የንግድና
አገልግሎት እንዲሁም የኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፎች ያለብዙ ውጣውረድ በአጭር ጊዜ
ከፍተኛ ትርፍ የሚገኝባቸውና ለኪሳራ ተጋላጭ ያልሆኑ፣ ቢሮክራሲውም ሆነ የፋይናንስ
ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት የሚሽቀዳደሙባቸው ናቸው፡፡ ሰንጠረዥ 6.1 የአምራች
ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ከንግድ፣ ኮንስትራክሽንና አገልግሎት ዘርፎች ጋር ያላቸውን
ተነፃፃሪ ልዩነት የሚሳይ ነው፡፡

ስለዚህ አሁን በሀገራችን ያለው ገፅታ የሚያመለክተው ምንም እንኳ መንግስት


ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለየ ማበረታቻና ድጋፍ ፓኬጆች አዘጋጅቶ ወደ ስራ
የገባ ቢሆንም ነገር ግን በተግባር እየታየ ያለው አብዛኛው የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት
አሁንም የመጀመሪያ ምርጫው አምራች ኢንዱስትሪው ሳይሆን የንግድና አገልግሎት
ዘርፎች ናቸው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 182


ሰንጠረዥ 6.1 አምራች ኢንዱስትሪ ከንግድ፣ ኮንስትራክሽንና አገልግሎት ዘርፎችጋር ሲነፃፀር

ተ.ቁ የአምራች ኢንዱስትሪ ንዑስ ዘርፍ የንግድ፣ ኮንስትራክሽንና አገልግሎት ዘርፎች


1 የካፒታል ወጪው ትልቅ ከመሆኑ በላይ የካፒታል ወጪው ትንሽ ከመሆኑ በተጨማሪ
ወጪውን ለመመለስ ረጅም ጊዜ ይጠይቃል፤ ወጪውን በአጨር ጊዜ መመለስ ይችላሉ፤
2 የረጅም ጊዜ ዕይታንና ቁርጠኝነትን አብዛኛዎቹ የአጭር ጊዜ ዕይታና ትርፍን
ይጠይቃል፤ ኢላማ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ናቸው፤
3 የትርፍ ህዳጌው አነስተኛና ከረጅም ጊዜ የትርፍ ህዳጌው ከፍተኛና በአጭር ጊዜ ውስጥ
በኋላ የሚገኝ ነው፤ የሚገኝ ነው፤
4 የኪሳራ ተጋላጭነት አደጋው (Exposing to የኪሳራ ተጋላጭነት አደጋው (Exposing to
risks) ከፍተኛ ነው፤ risks) ዝቅተኛ ነው፤
5 ዘመናዊና ከፍተኛ ቴክኖሎጂን፣ የተወሳሰበና ከፍተኛ ቴክኖሎጂና ዕውቀት
አደረጃጀትንና ማኔጅመንትን ይጠይቃል፤ የማይጠይቅና በቀላሉ መምራት ይቻላል፤
6 ከሌሎች ንዑስ ዘርፎች ጋር ሲወዳደር ብዙ ከአምራች ኢንዱሰትሪው ጋር ሲወዳደሩ ብዙ
ውጣውረድና ድካም አለው፣ ውጣውረድና ድካም የላቸውም፡
7 የኢንቨስትመንት ካፒታልና የስራ ማስኬጃ አነስተኛ የኢንቨስትመንትና የስራ ማስኬጃ
ካፒታል ወጪው ከፍተኛ ነው፡ ካፒታል ወጪ ይጠይቃል፡
8 አምራች ኢንዱስትሪ ላይ የተሰማራ ባለሀብት ንግድና አገልግሎት ከተሰማሩበት ዘርፍ በቀላሉ
በቀላሉ ከዘርፉ መግባትና መውጣት መውጣትና መግባት የሚያስችል ሁኔታ
አያስችለውም፤ አላቸው፤
9 የአምራች ኢንዱስትሪ ከፍተኛ የሆነ የሀገር ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር ሲነፃፀር እነዚህ
ውስጥና የውጭ ውድድር ያለበት ዘርፍ ነው፤ ዘርፎች ከፍተኛ ውድድር የለባቸውም፤
10 የግብአት አቅርቦቱ በአይነትና በመጠን ከፊሎቹ ብዙ ወይም ጥቂት ጥሬ ዕቃ የሚፈልጉ
ከፍተኛ ከመሆኑ በተጨማሪ በሀገር ውስጥ ቢሆኑም በሀገር ውስጥ እንደልብ ያገኛሉ፤
በቀላሉ አይገኝም፤ ሌሎች ጥሬ ዕቃ አያስፈልጋቸውም፡፡
11 የአምራች ዘርፍ ከትራንስፖርትና ንግድ፣ አገልግሎትና ኮንስትራክሽን በተለይ
ሎጂስቲክስ፣ የብደር አገልግሎት፣ የውጭ የብደር አገልግሎትና የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት
ምንዛሬ አቅርቦት አንፃር የሚያጋጥመው ላይ የተሸለ ተጠቃሚዎች ናቸው፤
ማነቆ ከፍተኛ ነው፤
12 የአምራች ኢንዱስትሪው ልማት ዕሴት የሌሎች ዘርፎች ልማት ዕሴት በመጨመር፣
በመጨመር፣ የስራ ዕድል በመፍጠር፣ የውጭ የስራ ዕድል በመፍጠር፣ የውጭ ምንዛሬ
ምንዛሬ በማስገኘት፣ እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ከማስገኘት እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት
ዕድገት ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው፤ ያላቸው አስተዋፅኦ መጠነኛ/ አነስተኛ ነው፡፡
13 አምራች ኢንዱስትሪው ለግብር ስወራና ንግድ፣ አገልግሎትና ኮንስትራክሽን ለግብር
ማጭበርበር የተጋለጠ አይደለም፤ ስወራና ማጭበርበር የተጋለጡ ናቸው፤
14 ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል ከመፍጠር አንፃር ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል ከመፍጠር አንፃር
የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው፤ የሚጫወቱት ሚና ዝቅተኛ ነው፤

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 183


ይህ የሚያመለክተው የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ከሌሎች ዘርፎች ጋር ሲነፃፀር
የግል ባለሀብቶችን የማይስብና ተመራጭ ያልሆነ መሆኑን ነው፡፡ ከዚህ ጉዳይ ጋር
ተያይዞ ሁለት ምክንያቶችን ማንሳት ይቻላል፡፡ አንደኛው ቀድመው በአምራች
ኢንዱስትሪ የተሰማሩ አብዛኛዎቹ ባለሀብቶች በብዙ ችግሮችና ማነቆዎች ምክንያት
ውጤታማ ባለመሆናቸው ወደ ዘርፉ መግባት ለሚፈልግ ባለሀብት ጥሩ አርአያ
ስላልሆኑት፤ ሁለተኛው ከላይ እንደተጠቀሰው በንግድና አገልግሎት ዘርፎች የሚገኘው
ትርፍ በጣም የተጋነነ በመሆኑ ነው፡፡ የግል ባለሀብቱ የመጀመሪያ ትኩረቱ ትርፍ
እስከሆነ ድረስ ያለብዙ ውጣውረድ ከፍተኛ ትርፍ የሚያስገኝለትን ዘርፍ መምረጡ
የማይቀር ነው፡፡ መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪውንና የሌሎችን ዘርፎች ባህሪ
በማየት የተጋነነ ትርፍ በሚያስገኙት ዘርፎች ገደብ ካላበጀላቸው እና በአምራች
ኢንዱስትሪ ላይ የሚስተዋሉትን መሰረታዊ ችግሮችና ማነቆዎች በመፍታት ተገቢውን
ማበረታቻና ድጋፍ ካላደረግ ክፍተቱ እየሰፋ ሄዶ አምራች የኢንዱስትሪ ዘርፍን
ማዳከሙ አይቀርም፡፡

6.2.1 የሪል እስቴት (Real estate) ንዑስ ዘርፍ

የሪል እስቴት ዘርፍ እንደ መሬት ማልማት፤ ግዥ እና ሽያጭ፤ ማከራየት፤ ድለላ ስራ


እና የሪል እስቴት ንብረትን ማስተዳደር የሚያካትት አንድ የአገልግሎት ዘርፍ ክፍል
ነው፡፡ ዘርፉ በሀገራችን ከ1983 ዓ.ም በኋላ ላለፉት ሁለት አስርተ አመታት እያቆጠቆጠ
እንደመጣ ይታወቃል፡፡ ምንም እንኳን በሪል እስቴት በተሰማራው የግል ባለሀብት
(private real estate developer) የተገነቡ ቤቶች አሀዝ በትክክል የሚያሳይ መረጃ
ባይኖርም፤ ዘርፉ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ቤቶች በመገንባት የተወሰነውን የህብረተሰብ
ክፍል ፍላጎት ለማሟላት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ከከተማና ቤቶች ልማት
ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡

ለሪል እስቴት ስራ መሰረቱ መሬት በመሆኑ መሬትና የሪል እስቴት ልማት


የማይነጣጠሉ ጉዳዮች ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ የሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ስናይ ደግሞ
በሪል እስቴት ልማት ዘርፍ ውስጥ መሬት ቁልፍ ሚና ይዞ ይገኛል፡፡ በእርግጥ
በሀገራችን ብዙ ባለሀብት ሪል እስቴት ላይ ለመሰማራት የሚሽቀዳደመው አንዱ ዋና
ምክንያት የመሬት ዋጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ እና በሪል እስቴት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 184


የተሰማሩ ባለሀብቶች መሬት ከመንግስት በርካሽ ዋጋ ወይም በነፃ ወስደው የተወሰነ
ጊዜ በማቆየት ያለምንም ወጪ ብዙ ትርፍ ስለሚያስገኝ ነው፡፡

ለአምራች ኢንዱስትሪው ከተደረገለት ድጋፍ ጋር ሲወዳደር መንግስት የሪል እስቴት


ኢንቨስትመንት ለማበረታታት ሰፋፊ የግንባታ መሬት በዝቅተኛ ዋጋ ያቀርብ እንደ
ነበር ይታወቃል፡፡ ቀደም ሲል በሪል እስቴት የተሰማራው ባለሀብት መሬትን ከጨረታ
(tender) ይልቅ በአብዛኛው በድርድር (negotiation) እንደሚቀበል ጥናቶች ያሳያሉ፡፡
ለአብነት በከሪ የሱፍና ጓደኞቹ (2009 እ.ኤ.አ) በአዲስ አበባ ከተማ ያጠኑት ጥናት
እንደሚያሳየው ለሪል እስቴት ንዑስ ዘርፍ የሚሰጠው የሊዝ መሬት ዋጋ በአማካኝ
ከኢንዱስሪው ዘርፍ ያነሰ እንደነበር ነው፡፡ እንዲሁም በየአመቱ ለሪል እስቴት ልማት
የሚውለው የመሬት ስፋት (በሄክታር) ከኢንዱስትሪው እንደሚልቅ ጥናቱ ያሳያል፡፡
እ.ኤ.አ በ 2011 የከተማ መሬት በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅን ተከትሎ መሬት
ለሪል እስቴት ባለሀብቱ የሚተላለፈው ጨረታን መሰረት ባደረገ የሊዝ ስርአት እንደሆነ
ይደነግጋል፡፡ በተጨማሪም ለሜጋ ሪል እስቴት ልማት የከተማ አስተዳደሩ ቀድሞ
ባዘጋጀው ቦታ በሊዝ ጨረታ እንደሚተላለፍ ይደነግጋል፡፡ ነገር ግን በሜጋ ሪል እስቴት
ልማት በሚዘጋጀው መሬት ላይ የተጫራቾ ብዛት ብሎም ውድድር አናሳ በመሆኑ
ተመጣጣኝ የሊዝ ገቢ እንደማያስገኝ ያሳያል፡፡

በሪል እስቴት የሚሰማራው ባለሀብት ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መምጣቱን መረጃዎች


ያሳያሉ፡፡ የሪል እስቴት ዘርፍ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ብዛት (የሪል እስቴት፤
ኪራይና ተያያዥ ስራዎች) ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በተነፃፃሪ ከአመት አመት
ዕድገት እያሳየ መሆኑን እንዲሁ መረዳት ይቻላል፡፡ለምሳሌ በ2007 የኢንቨስትመንት
ፈቃድ ከወሰዱ ባለሀብቶች ውስጥ 48.8% የሚሆነው በሪል እስቴትና የንግድ ስራዎች
ለመሰማራት ሲሆን 9.6% ያህሉ ደግሞ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለመሰማራት
የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ ናቸው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 185


ግራፍ 6.1 የሪል እስቴት፣ኪራይና ሌሎች የማማከር ስራዎች ከሌሎች ዘርፎች ጋር ሲነፃፀር (2007 ዓ.ም)
ምንጭ፡ የብሄራዊ ባንክ አመታዊ ሪፖርት 2007 ዓ.ም

በተጨማሪም በሪል እስቴት እና የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፎች መካከል የካፒታል


መጠን ፍላጎት ልዩነት ይስተዋላል፡፡ የሪል እስቴት ዘርፍ በትንሸ ኢንቨስትመንት
ካፒታል መጀመር እንደሚቻል ያሳያል፡፡ ለምሳሌ በ2006/2007 ዓ.ም በሀገሪቱ
አጠቃላይ ከተመዘገበ ፕሮጀክት ውስጥ የሪል እስቴትና የንግድ ስራዎች የካፒታል
ድርሻ 13.6% ሲይዝ የዘርፍ የፕሮጀክት ድርሻ ከአጠቃላይ ከተመዘገቡት
ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 48.8% ያህሉን ይይዛል፡፡ ነገር ግን በአምራች
ኢንዱስትሪው ዘርፍ ፍቃድ የወሰደው ባለሀብት የፕሮጀክት ብዛት 9.6% ድርሻ
ቢይዝም ያስመዘገበው ካፒታል ግን 65.5% ድርሻ ይዟል፡፡ቀደም ያሉ ጥናቶች
በኤልሳቤጥ ቻኩና ፐተር ገብረ (2009 እ.ኤ.አ) እንደሚያሳዩት ከ1992 እስከ 2008
(እ.ኤ.አ) በሪል እስቴት ኢንቨስትመንት የዲያስፖራው ድርሻ 68% ይይዝ እንደነበረ
ነው፡፡ከላይ የተጠቀሱት መረጃዎች የሚያመላክቱት የሪል እስቴት ዘርፍ ልማት
ከአምራች ኢንዱስትሪው በተሻለ በሀገራዊ ባለሀብቱ ተመራጭ መሆኑን ነው፡፡ ሪል
እስቴት ከሌሎች ዘርፎች በተሻለ መንገድ ተመራጭ የሆነበት ምክንያቶች በርካታ
እንደሆኑ ጥናቶች ቢገልፁም በዋናነት መሰረታዊ የሚባሉት ሶስት ናቸው፡፡

በመጀመሪያ ባለሀብቱ በሪል እስቴት ውስጥ የመሳተፍ ፍላጎት ማደጉ ምክንያት የዘርፉ
ንፅፅራዊ አዋጭነት እና በቀላሉ ትርፋማ መሆን ከመሬት ጋር መያያዙ ነው፡፡ ባለሀብቱ
በርካሽ ዋጋ ሰፊ የሊዝ መሬት እንዲያገኝ መቻሉ እና የሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ የመሬትና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 186


ንብረት ዋጋ (land and property values) በፍጥነት እየጨመረ በመሄዱ እንዲሁም
ባለሀብቱ በዚህ ዘርፍ ቢሰማራ መፃኢ ትርፋማነቱ ከፍተኛ እንደሚሆን በማመን ወደ
ዘርፍ ለመቀላቀል እንዲወስን አስችሎታል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የትርፍ ህዳጌ መጠን
ከኢንቨስትመንት ካፒታል መጠን ጋር ሲወዳደር ከፍተኛ ሆኖ እናገኛዋለን፡፡ በሌላ
በኩል የአምራች ኢንዱስትሪው በአጭር ጊዜ ትርፍ የማያስገኝ ብሎም በባህሪው
ከፍተኛ ካፒታልና ክህሎት የሚጠይቅ ዘርፍ ስለሆነ በባለሀብቱ እንዳይመረጥ
አድርጎታል፡፡ለምሳሌ የሪል እስቴት ኩባንያዎች ለልማት የተረከቡትን የሊዝ መሬት
ምንም አይነት እሴት ሳይጨምሩ አጥሮ ወይም ጅምር ህንፃዎችን በማስቀመጥ
የመሬትና ተያያዥ ንብረቶች በሚጨምሩበት ጊዜ ለሌላ አካል በማስተላለፍ ሀብት ያለ
ውጣ ውረድ ማካበት እንደሚችሉ ጥናቶች ይመሰክራሉ፡፡ በአጠቃላይ የባለሀብቱ ወደ
ሪል ስቴት ዘርፍ መሳብ አንድ መገለጫ ባለሀብቱ ሰፊ መሬት በመያዝ እና መሬቱን
ሳያለማ በማቆየት ብቻ ትርፍ እንደሚያዝቀው በመተንበይ (speculation) ኢንቨስት
ስለሚያደርግ ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ታዳጊ ሀገራት በሪል እስቴት ዘርፍ
የተሰማራው ባለሀብት መሬት ከአክስዮን እና ከቦንድ የተሻለ ጥቅም እንዳለው
ይገመታል፡፡ ከሌሎች ኢንቨስትመንት አይነቶች ጋር ሲነፃፀር የሪል እስቴት ዘርፍ
ዋልታ መሬት በመሆኑ ሲሆን መሬት በባህሬው በዋጋ ግሽበት የማይጠቃ ካፒታል
መሆኑ፤ ለብድር ማስያዣነት ተመራጭ እና ያገልግሎት ዘመን ቅናሽ (asset
depreciation) አነስተኛ መሆኑ ዘርፉን ተመራጭ እንዲሆን አስችሎታል፡፡በተቃራኒው
የአምራች ኢንዱስትሪው በስፔኩሌሽን (speculation) እና መሬት ላይ ጥገኛ ሆኖ ትርፍ
የማግኘት ባህሪ የተላበሰ አይደለም፡፡

ሪል እስቴትን ተመራጭ ያደረው ሁለተኛው ምክንያት ዘርፍ በፋይናንስ እና ካፒታል


አጠቃቀሙ ከአምራች ኢንዱስትሪው ለየት ያለ ባህሪ በመላበሱ እንደሆነ ይገለፃል፡፡
ቀደም ብሎ በኮንስትራክሽን እና ቢዝነስ ባንክ በኩል የረጅም ጊዜ የብድር ድጋፍ
(mortgage finance) የሪል እስቴትን ዘርፍ ድጋፍ ይደረግለት እንደነበር ይታወቃል2፡፡
በአሁኑ ወቅት ዘርፉ የፍይናንስ ድጋፍ ከቢዝነስ እና ኮንስትራክሽን ባንክ ማግኘት
ባይችልም የግል ባለሀብቱን የመሳብ አቅሙ ግን አለመገታቱን ይስተዋላል፡፡ የሪል
እስቴት ልማት (real estate development) እራሱን-በራሱ ፋይናንስ የማድረግ ስልት
መከተሉ በባለሀብቱ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ የሪል እስቴት ኩባንያዎች ከመንግስት

2
በአሁኑ ወቅት ግን ዘርፍ በራሱ የፍይናንስ ምንጭ መንቀሳቀስ እንዳለበት መንግስት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
ለበለጠ መረጃ የከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እና የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ (2007ዓ.ም) ጥናት
ማየት ይቻላል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 187


የተረከቡትን መሬት ብቻ በማሳየት ከደንበኛቻቸው (ማለትም ቤት ገዥዎች) ቅድመ
ክፍያ በማስከፈል እንደሚዋዋሉ እና ደንበኞች ከመጀመሪያ ጀምሮ በየወቅቱ
ክፍያዎችን እንዲከፍሉ ይዋዋላሉ፡፡ በዚህ ስልት ባለሀብቱ ትንሽ ካፒታል ቢኖረውም
ከደንበኛ በሚያገኘው ገንዘብ ሪል እስቴት ልማት እያለማ እንደሆነ እና ትርፍማ
እንደሚዝቅ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ነገር ግን የከተማ መሬት በሊዝ ስለመያዝ የወጣው
አዋጅ (2004 ዓ.ም) እንደሚገልፀው ባለሀብቱ የሊዝ መብቱን በተመጣጣኝ ዋጋ ብቻ
እንደ ካፒታል አስተዋፆ መጠቀም እንደሚችል ነው፡፡በተግባር የሚስተዋለው ግን
ባለሀብቱ በተዘዋዋሪ በሊዝ ያገኘውን መሬት የመጠቀም መብት ከመብት ዋጋው
በሚበልጥ አኳኋን ከደንበኞች ብር በማሰባሰብ እንደ ዋስትና እየተጠቀመበት መሆኑን
ነው፡፡ በተጨማሪ የሪል እስቴት ኩባንያዎች ደንበኞቻቸው በብዛት ዲያስፖራዎች ሲሆኑ
ቅድመ ክፍያ የመክፈል አቅም ያላቸው ናቸው፡፡ እነዚህ ደንበኞች የሪል እስቴት
ኩባንያዎችን የቤት ግንባታውን እንዲያከናውኑላቸው ከመዋዋል ባሻገር ውክልናም
ጭምር ለባለሀብቱ እንደሚሰጧቸው ጥናቶች ያሣያሉ፡፡ በመሆኑም የሪል እስቴት
ኩባንያዎች በቤት ገዥዎች እና የግንባታ ኮንትራክተሮች መካከል የድለላ (brokers)፤
የሻጭና ገዥ ስራ እና ሪል እስቴት የማስተዳደር ስራዎችን በዋናነት እንሚሰሩ
ይገለፃል፡፡

ሶስተኛው ምክንያት ደግሞ የሪል እስቴት ዘርፍ ለጥቁር ገበያና ለኪራይ ሰብሳቢነት
ምቹ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡ ዘርፍ እንደባህሪ የተላበስው ነገር ደንበኞችን ያለአግባብ
ቅድመ ክፍያ እንዲከፍሉ መጠየቅ፣ ከተቀመጠው ውል ውጭ የቤቶችን ዋጋ መጨመር፣
የውል ግዴታ ሳይፈፅሙ የሪል እስቴት ኩባንያዎችን መዝጋት ወይም ማፍረስ እና
በዝቅተኛ ዋጋ ከመንግስት የተረከቡትን ሰፊ መሬት እየሽነሸኑ ለሌላ ወገን መሸጥ
ተጠቃሽ ችግሮች እንደሆኑ ይገለፃል፡፡ ሌላው የመኖሪያ ቤት ያላቸውን የልማት
ተነሺዎች ጋር በመደራደር መንግስት ለተነሺዎች ከሚከፍለው ዋጋ ከፍተኛ ግምት
ያለው ገንዘብ በመክፈል መሬት በሊዝ ጨረታ ወደ ልማተዊ ባለሀብቱ እንዳይተላለፍ
በአቋራጭ መንግስት ማግኘት ያለበትን ገቢ በማሰቀረት እና አነስተኛ ዋጋ መሬትን
ጠቅልሎ የመያዝ ዝንባሌዎች አልፎ አልፎ ይስተዋላል፡፡ እንዲሁም የሚመለከታቸው
የመንግስት ተቋማት የሪል እስቴት መሬት እና ንብረትን ያለመመዝገብ፣ ቁጥጥር እና
ክትትል ያለማድረጋቸው ዘርፉ መክፈል የሚገባውን ግብርና ቀረጥ ለመንግስት
እንዳላስገኘ ይገለጻል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ሪል እስቴት ዘርፍ በእነዚህ እና ሌሎች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 188


ችግሮች በመተብተቡ ባለሀብቱ ባቋራጭ ትርፍ ወደ ሚገኝበት ሪል እስቴት ዘርፍ
ትኩረት እንዲያደርግ አድርጎታል፡፡

ሪል እስቴት (በህንፃ ግንባታ) የተሰማራው ባለሀብት ዋነኛ የትርፍ ምንጭ ከገነባው ህንፃ
በላይ መሬትን አቆይቶ በመሸጥ በአጭር ግዜ መበልፀግ መቻሉ፤ በሊዝ ምደባ
የተረከቡትን መሬት እንደ ዋስትና በመጠቀም ለሪል እስቴት ኢንቨስትመንት ፋይናንስ
ምንጭ እራሱ በዘርፍ የተሰማራው ባለሀብት ሳይሆን በአቋራጭ ከደንበኞች የሚሰበስብ
ገንዘብ መሆኑ እና የሪል እስቴት ዘርፍ ለጥቁር ገበያ ወይም ለኪራይ ስብሰባ (ለአብነት
ተገቢውን ግብር አለመክፈል፤ ከውል ውጭ በደንበኛች ላይ የቤቶችን ዋጋ መጨመር፤
የውል ግዴታን ሳይፈፅሙ የሪል እስቴት ኩባንያዎችን ማፍረስ እና የተረከቡትን
መሬት እየሽነሸኑ ለሌላ ወገን መሸጥ) ተጋላጭ በመሆኑ ከዘርፍ ልማት ፍትሃዊ
ተጠቃሚነትን ለማስፈን ተግዳሮት ሆኗል፡፡ ሀገራዊ ባለሀብቱ የኢንቨስትመንት ስምሪት
ስንመለከት ደግሞ ከአምራች ኢንዱስትሪ እና ሌሎች ዘርፎች ወደ ሪል እስቴት ዘርፍ
እየኮበለለ መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ ስለዚህ ዘርፍን ለመቆጣጠር እና ለማልማት ያስችል
ዘንድ የሪል እስቴት ደንብ እና መመሪያ አዘጋጅቶ በተቀናጀ መንገድ ዘርፉን መምራት
ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 189


ምዕራፍ 7
በአምራች ኢንዱስትሪው ሊሰማሩ የሚችሉ አዳዲስ የሀገር ውስጥ
ባለሀብቶች

አዳዲስ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ወደ አምራች ኢንዱስትሪው ለመሳብ አስቸጋሪ


የሚሆነው በሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሆነ የእሰካሁኑ ልምዳችን ያስተምረናል፡፡
አንደኛው የተሰማሩባቸው ዘርፎች ያለብዙ ድካም ከፍተኛ የሚባል ትርፍ ስለሚያገኙ
ሲሆን ሁለተኛው ቀድመው በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ባለሀብቶች ጥሩ አርአያ
ስላልሆኗቸው እና በሶስተኛ ደረጃ ባለሀብቱ በዘርፉ በቂ ዕውቀትና ግንዛቤ ስለሌለውና
ሪስክ መወስድ ስለማይፈልግ ነው፡፡ ስለዚህ በእነዚህ ችግሮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ
በመስራትና በማስተካከል ወደ አምራች ኢንዱስትሪ ሊሰማሩ የሚችሉ አዳዲስ
ባለሀብቶችን ለመሳብ ጥረት መደረግ አለበት፡፡ በሀገራችን አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ
መሰረት አዳዲስ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን በሚከተሉት አራት ዘርፎች ውስጥ ማለትም
በጥቃቅንና አነስተኛ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች፣ በገጠር የአርሶአደሩ ምጣኔ ሀብት፣
በንግዱ ዘርፍና በኮንሰትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ወደ አምራች ኢንዱስትሪ
ማሰማራት ይቻላል፡፡ ስለዚህ እነዚህ ዘርፎች ያሉባቸውን ክፍተቶች በመሙላት ወደ
አምራች ዘርፍ ሊሰማሩ የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ያስፈልጋል፡፡

7.1 በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች

ከዚህ በፊት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በሚል የሚታወቀው አደረጃጀት


በአሁኑ ወቅት በሁለት ተከፍሎ አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ወደ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
እንዲሁም ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ወደ ከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር በአዲስ
መልክ እንደተደራጁ የሚታወቅ ነው፡፡ ነገር ግን ለዚህ ጥናት መረጃ በሚሰበሰብበት
ወቅት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት በሚል የሚታወቅ ስለነበር
በጥናታችንም በዚህ አደረጃጀት የታየ መሆኑን እያሳሰብን ለአዳዲስ ባለሀብቶች
መፍለቂያ ከመሆኑ አንፃር ልዩነት ስለማያመጣ ይህንኑ ተጠቅመንበታል፡፡

የሀገር ውስጥ ባለሀብት ምንጭ ከጥቃቅንና አነስተኛ የሚያድጉ ኢንተርፕይዞች


እንዲሁም ወጣት ኢንተርፕርነርስ መሆናቸው እሙን ነው፡፡በስትራቴጂውም
ከተቀመጡት አምስት ዘርፎች ውስጥ የአምራች ዘርፉን በዕድገት ተኮር ንዑስ ዘርፎች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 190


ከፍሎ ያስቀምጠዋል፡፡ እነርሱም ጨርቃጨርቅና ስፌት (Textile and Garment)፣ ቆዳና
የቆዳ ውጤቶች (Leather and Leather Products)፣ የምግብና መጠጥ ዝግጅት (Food
Processing and beverage)፣ የብረታ ብርትና የኢንጂነሪንግ ምርቶች (Metal Work and
Engineering)፣ የእንጨት ሥራዎች (Wood Work including Furniture)፣ ባህላዊ የዕደ
ጥበብና የጌጣጌጥ ሥራዎች፣ አግሮ ፕሮሰሲንግ ናቸው፡፡ የኢኮኖሚ ልማት በተለይም
የኢንዱስትሪ ልማት ዋና ሞተር የግል ባለሀብቱ መሆኑ ጥያቄ ውስጥ የሚገባ
አይደለም፡፡ በመሆኑም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራዞች በአምራች ኢንዱስትሪ
ተሰማርተው በዘርፉ ልማት ዋና ተዋናይ እና ውጤታማ እንደሆኑ በስትራቴጂው በግልፅ
የተቀመጠ ነው፡፡

7.1.1 የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት በአምራች ኢንዱስትሪ ያላቸው ስምሪትና


ማነቆዎች

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕይዞች የስራ ስምሪታቸው ስብጥርና የተከሰቱ ማነቆዎችን


ለመዳሰስ በጥቅሉ በአራት ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ 116
ኢንተርፕይዞች ናሙና ተወስዶ በፅሁፍ መጠይቅ በተሰበሰበ መረጃ ተመስርቶ
እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ሀ) የፋይናንስና ብድር አቅርቦት

ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አንዱ መሰረታዊ ችግራቸው በቂ የፋይናንስና


ብድር አቅርቦት አለማግኘታቸው ነው፡፡ በተግባር አሁን ኢንተርፕራይዞቹ በብዛት
እየተሰማሩበት ያሉት በብረታ ብረትና እንጨት ስራዎች ዘርፍ ነው፡፡ እነዚህ ስራዎች
ደግሞ በአንጻራዊነት ከፍተኛ ካፒታል የሚጠይቁ መሆናቸው ግልጽ ነው፡፡ ለምሳሌ
በመቀሌ ከተማ የሚገኙ 26 ኢንተርፕራይዞች የጠየቋቸው 33 ማሽነሪዎች ዋጋ ብር
18,870,000 ይደርሳል፡፡ ይህን ካፒታል አንድ አነስተኛ ፋብሪካ ማቋቋም የሚችል
ነው፡፡

ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ፋይናንስ የሚያቀርቡ በየክልሉና በከተማ


አስተዳደሩ የሚገኙ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ናቸው፡፡ ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስ
በስተቀር እነዚህ ተቋማት ያላቸው የፋይናንስ ዓቅም ካለው ፍላጎት ጭራሽ የማይጣጣም
ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በአንድ በኩል ኢንተርፕራይዞቹ ለብድር አመላለስ መያዣ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 191


ስለማይኖራቸው በሌላ በኩል ደግሞ ፋይናንስ ተቋማቱ የማበደር ዓቅም ዝቅተኛ መሆኑ
ተጠቃሚ አልሆኑም፡፡

ለአምራች ዘርፎቹ የሚቀርብ የብድር መጠንም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ ይገኛል፡፡


በትግራይ ክልል ለአንድ ኢንተርፕራይዝ እስከ 200,000 ብር፣ በአዲስ አበባ ከተማ
እስከ 1,500,000 ማበደር ተጀምሯል፡፡ ሆኖም በአንድ በኩል ይህንን መጠን ያህል
ብድር ለሁሉም ኢንተርፕራይዞች ተደራሽ አለመሆኑና በሌላ በኩል ኢንተርፕራይዞቹ
እየጠየቁት ያለው የብድር መጠን ከዚህ በላይ በመሆኑ የፋይናንስ ዓቅሙ ጥያቄዎች
ለመመለስ የሚችል አልሆነም፡፡ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ሁሉም ክልሎችና የከተማ
አስተዳደሮች የዋስትና ፈንድ አቋቁመው በተግባር ወደ ስራ ተገብቷል፡፡ ይሁንና
የዋስትና ፈንዱ አዋጭ ለሆኑ ሁሉም ፕሮጀክቶች የሚያቅፍ በመሆኑ በአምራች ዘርፉ
የሚሰማራውን ብቻ ተጠቀሚ የሚያደርግ አይደለም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 192


ግራፍ 7.1 የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት የብድር ስርጭት መጠን የሚያሳይ
ምንጭ፡ (ደደቢት፣ አብቁተ፣ ኦሮሚያ፣ ኦሞ፣ ድሬ እና አዲስ ማይክሮ ፋናንስ ተቋማት፣ 2007ዓ.ም)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 193


በሌላ በኩል በፋይናንስ አቅርቦትና ተደራሽነት የታየው ችግር የብድር መመለሻ ጊዜው
አጭር መሆኑ ነው፡፡በተለይ ለአምራቹ የሚፈቀደው የብድር መጠን በተቻለ ዓቅም
እያደገ ቢሆንም የመመለሻ ጊዜው አጭር (ከ3-5 ዓመት) በመሆኑ በተለይ ጀማሪ
ኢንተርፕራይዞች ስራውን መልመድ ሲጀምሩ ገንዘቡ ስለሚመለስ ስራው እስከማቆም
ይደርሳሉ፡፡

በግራፍ 7.1 እንደተገለፀው ለኢንዱስትሪው የተሰራጨው የብድር መጠን ዝቅተኛ


መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት መካከል ለኢንዱስትሪው ዘርፍ
ያበደሩት መጠን ላይ ሰፊ ልዩነት ይታያል፡፡ ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ ካሰራጨው
ጠቅላላ ብድር 15.3% ለኢንዱስትሪው ዘርፍ በመመደብ ቀዳሚውን ደረጃ ሲይዝ አዲስ
ብድርና ቁጠባ ተቋም 13%፣ ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ 10%፤ የአማራ ብድርና ቁጠባ
ተቋም 5.7%፤ ኦሮሚያ ብድርና ቁጠባ ተቋም 2.7%፤ ኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ 1.6%
ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘው ይገኛሉ፡፡

ከዚህ መረዳት የሚቻለው አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ለኢንዱስትሪው ዘርፍ


በተለይም ለማኑፋክቸሪግ ዘርፍ ሰፊ ትኩረት ከመስጠት ይልቅ ለሌሎች ዘርፍ ቅድሚያ
ሰጥተው እያስተናገዱ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚቀርበው
በአንድ በኩል የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚጠየቀው የብድር መጠን ከሌሎች አንፃር
ሲታይ ከፍተኛ ስለሆነ በሌላ በኩል ብዙ የብድር ተጠቃሚ ህብረተሰብ በተሰማሩበት
ዘርፎች ላይ ትኩረት ሰጥተው ማስተናገድን መሰረት በማድረግ እየሰሩ መሆኑን
ይገልፃሉ፡፡ በሁሉም ክልሎች ለእያንዳንዱ ዘርፍ በተለይም ለአምራች ዘርፉ ምን ያህል
ካፒታል መመደብ እንዳለበት ተለይቶ የተቀመጠ መጠን የለም፡፡

በየጊዜው ዘርፉን እየተቀላቀለ ያለ ኃይል ለማስተናገድ ሲባል ክልሎች በአነስተኛ


ብድርና ቁጠባ የፋይናንስ ተቋማት በኩል ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
አቅርቦት የሚውል የብድር አቅርቦት ለማሻሻል ጥረት እያደረጉ ቆይተዋል፤ አሁንም
እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሁሉም ክልሎች የብድርና ቁጠባ ተቋማት ከኢትዮጵያ
ልማት ባንክ እንዲበደሩ በማድረግ አቅርቦታቸው እንዲያሻሻሉ ማድረግ እንደ አማራጭ
እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ አንዳንድ ክልሎች በውስጥ ገቢ የሚተዳደሩት እንደ ማዘጋጃ
ቤቶች፣ የከተሞች ውኃ አገልግሎት ፅሕፈት ቤቶች ወዘተ የመሳሰሉት መንግስታዊ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 194


ተቋማት ገንዘባቸውን በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት እንዲያስቀምጡ በማድረግ የተሻለ
አቅም ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ ነው፡፡

መደበኛ የንግድ ባንኮች እስከ ገጠር ወረዳ ከተሞች ሳይቀር ቅርንጫፎቻቸውን በፍጥነት
እያሰፋ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ባንኮች በአነስተኛ ደረጀ የሚፈረጀው የገንዘብ መጠንም
በመሰባሰብ ሰፊ ስራ መስራታቸው ግልፅ ሆኖ በብድር አቅርቦቱ ግን ቋሚ የብድር
ዋስትና መያዣ ላለው ካልሆነ በስተቀር ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተደራሽ
አይደሉም፡፡ በአጠቃላይ ከቀረበው ትንታኔ መረዳት የሚቻለው ሁሉም የአነስተኛ
ብድርና ቁጠባ ተቋማት በሚያስብል ሁኔታ የማበደር አቅም አነስተኛ በመሆኑ ከዘርፉ
የብድር ፍላጎት ጋር ሊጣጣም አለመቻሉን ያመላክታል፡፡

ለ) የዕውቀት፣ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግር

የአምራች ዘርፉ በእርግጥም ከንግድና አገልግሎቱ ዘርፎች በተለየ መልኩ ዕውቀት፡


ክህሎትና የቴክኖሎጂ ግብዓት የሚፈልግ ዘርፍ ነው፡፡ የዘርፉ ልማት ስትራተጂ ጨርቃ
ጨርቅና ስፌት፣ ቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ ምግብና መጠጥ ዝግጅት፣ ሌሎች አግሮ
ፕሮሰሲንግ ስራዎች፣ የእንጨት ውጤቶችና የብረታ ብረት ስራዎች እንዲሁም ዕደ-
ጥበብና ጌጣጌጥ በአምራችነት ተመድበው ትኩረት የሰጣቸው ቢሆንም አብዛኛው ወደ
ብረታ ብረትና የእንጨት ስራዎች ማዘንበሉ አልቀረም፡፡ በተለይ ወደ አግሮ
ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ የሚሰማሩት አንቀሳቃሾች በጣም ጥቂት ናቸው፡፡ በጨርቃ
ጨርቅና አልባሳት እንዲሁም ቆዳና ቆዳ ውጤቶች ላይ የተሰማሩም በብዛት በባህላዊ
አልባሳት የተሰማሩ ሲሆን በዚህ ንዑስ ዘርፍም በበቂ ሁኔታ አልተሰማሩም፡፡ ስለዚህ
ለጀማሪ ኢንተርፕራይዞች በሁሉም አምራች ዘርፎች የክህሎትና ዕውቀት ክፍተቱ ሰፊ
መሆኑ የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የተከታተሉ ይቅርና
ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋም የሚመረቁትም በተለይ የክህሎት
አቅማቸው በአምራች ለመሰማራት በቂ አለመሆኑን በአምራች የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞችና በየደረጃው የሚገኙ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት
የሚመሩ ጽ/ቤቶች ይገልፃሉ፡፡

የቴክኖሎጂ ዓቅም ግንባታ ስራው ለቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆች


የተሰጠ ቢሆንም ተቋማቱ የቴክኖሎጂ ዓቅም ግንባታው የተሰጣቸው ኃላፊነት
የሚወጡበት ደረጃ አለመሆናቸው በሁሉም ክልሎችና ከተሞች በተደረጉ ውይይቶች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 195


ለማወቅ ተችሏል፡፡ የተቋማቱ ውስንነት ቴክኖሎጂ በመፍጠሩ በኩል ብቻ ሳይሆን
በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተፈጠሩትና የተሻሻሉት ቴክኖሎጂዎች
የማሰባሰብና የማባዛት ስራም እየሰሩ አይደለም፡፡ ከዚህ በባሰም የኢንዱስትሪያል
ኤክስቴንሽን ድጋፍ የሚሰጡ ባለሙያዎች በተግባራዊ ዕውቀትና ክህሎት ከአንቀሳቃሾች
የተሻለ ዕውቀት የሌላቸው በመሆኑ በተግባር እየሰጡት ያለው ድጋፍ በቂ አለመሆኑንና
ከስራ አመራር /ቢዝነስ ደቬሎፕመንት ሰርቪስ/ ያልዘለለ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪም በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤቶች ያለው መዋቅርም
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሸን ድጋፍ የሚሰጡ የስራ መደቦች ከብረታ ብረትና ጨርቃ
ጨርቅ የዘለለ አይደለም፡፡

በአጠቃላይ ጥናቱ በተከናወነባቸው የክልልና የከተማ አስተዳደር ከተሞች


ከአንቀሳቃሾች በተሰበሰበው መረጃ መሰረት የቴክኒክና ሙያ የስልጠና ተቋማት
በአምራች ኢንዱስትሪው ለተሰማሩት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በተግባር
የሚሰጡት ድጋፍ ሲታይ 13.7% ያህሉ የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር፣ 39.7% ሙያዊ
የክህሎት ስልጠና፣ 22.1% የስራ ፈጠራ እና 24.4% መልስ ያልሰጡ እንደ ሆነ ሲጠቀስ
ቴሙስተ በስፋት የክህሎት ስልጠና ላይ ማተኮራቸው ለቴክኖሎጂ ልማት ሽግግር
የሰጡት ትኩረት አነስተኛ መሆኑን ያመለክታል፡፡ በሌላ በኩል በአንቀሳቃሾች በኩል
ያለው የሽግግር ፍላጎት ሲታይ ደግሞ ከ116 አንቀሳቃሾች የተሰበሰበው መረጃ
እንደሚያመለክተው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የዕድገት ሽግግር
ፍላጎታቸው ዝቅተኛ የሆነበት ከሚጠቀሱት ዋነኛ ምክንያት 34.5% ያህሉ ለሽግግር
የሚያበቃ ዓቅም ስለሌላቸው፣ 7.6% ከተሸጋገሩ የሚጣልባቸው የግብር መጠን ከፍተኛ
ይሆናል የሚል ስጋት፣ 19.1% የተለያዩ የመንግስት ድጋፎች ስለሚቋረጡ፣ 18.3%
ከሽግግር በኃላ ለዕድገቱ የሚመጥን ድጋፍ ስለማይሰጥባቸው፣ 1.5% ትክክለኛ ባልሆነ
አስተሳሰብ ፣ 2.3% በአንቀሳቃሾች ድክመት፣ 8% የመንግስት ድጋፍ ተደራሽነት ማነስ
ነው ሲሉ፣ 1.5% ያህሉ በምክንያትነት በተጠቀሱት ሁሉ ይስማማሉ፡፡

ሐ) የመስሪያና መሸጫ ቦታ ዝግጅት አቅምና መሰረተ ልማት


የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የልማት ስትራቴጂ ኢንተርፕራይዞች
የሚሰሩባቸውና ለምርት ማሳያና መሸጫ የሚሆኑ ቦታዎች ተለይተው እንዲዘጋጁና
ደረጃውን የጠበቀ ሼዶች መገንባት እንዳለባቸው አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ በዚህ
መልኩም በሁሉም ክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ቢሆንም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 196


ፍላጎቱን ከማሟላት አንጻር ሲታይ ግን ዝቅተኛ መሆኑን በየክልሉ ከተካሄዱ
ውይይቶችና ቃለ-መጠይቆች ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከተሞቹ ለእያንዳንዱ አምራች
ኢንተርፕራይዝ የሚሆን መሬት ማዘጋጀት ትልቅ ችግር እየሆነባቸው ነው፡፡ ምክንያቱ
ደግሞ ከካሳና ተያያዥ ወጪዎች የመክፈል አቅም አለመኖሩን ይገልፃሉ፡፡ ለጥቃቅንና
አነስተኛ የሚሰጥ ቦታም በጊዚያዊነት በመሆኑ ኢንተርፕራይዞቹ ተረጋግተው እንዲሰሩ
የሚያስችል አይደለም፡፡ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች መንደሮችን ለመገንባት
የፋይናንስ አቅርቦት ችግርም አለባቸው፡፡ በአምራች ዘርፍ እየተሰማሩ ያሉት
ኢንተርፕራይዞች ከሌሎች ዘርፎች አንፃር ሲታይ ቁጥሩ ጥቂት ቢሆንም አሀዙ በራሱ
ሲታይ ግን በየዓመቱ እየተቀላቀለ ያለ አንቀሳቃሽ ቁጥሩ እየጨመረ ይገኛል፡፡ ስለዚህ
ወደፊት የሚጨምረውን ቁጥር ግምት ውስጥ ስናስገባው አሁንም ከተሞች መሬት
ማቅረብ እንዲሁም ሼዶች ለመገንባት የሚጠይቀው ወጪን ለመሸፈን ፈታኝ
እንደሚሆኑባቸው መገመት ይቻላል፡፡

መ) ገበያ
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችም ከላይ በመደበኛ አምራች ኢንቨስትመንት
እንዳየነው የገበያ ችግር እንዳለባቸው ይገልጻሉ፡፡ ከገበያ እጦት እየተነሱ ያሉት
ሁኔታዎች ሶስት መልክ አላቸው፡፡ የመጀመሪያው አነስተኛ አምራቾች ከአጭር ጊዜ
አኳያ እራሳቸው ከንግድና አገልግሎት በማወዳደር በፍጥነት ሃብት ለማካበት ፍላጎት
ይንፀባረቅባቸዋል፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ ትርፋማ ቢሆኑም ገበያው በየቀኑና በየሳምንቱ
የማያቋርጥ ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት እንዳለበት የማሰብ ሁኔታ ይታያል፡፡ ሁለተኛው
ከምርት ጥራት መጓደል ተያይዞ የሚከሰት ችግር ነው፡፡ በዘርፉ ልማት ስትራቴጂ
ማንኛውም ምርት ተገቢውን ዋጋ እንዲያገኝ ተወዳደሪ ጥራት ሊኖረው እንደሚገባ እና
ዘርፉን የሚመሩ ሴክተሮች ለኢንተርፕራይዙ የሚመጥን ደረጃ ተግባራዊ እንዲደረግ
በግል ቢያሰቀምጥም በተግባር የደረጃ ምደባ እየተተገበረ አይደለም፡፡

ሶስተኛው ምክንያት ከመንግስት የግዥ ፖሊሲ ጋር ይያያዛል፡፡ ክልሎችና የከተማ


አስተዳደሮች ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር እንዲያገኙ የተለያዩ
ጥረቶች እያደረጉ ነው፡፡ በደ/ብ/ብ/ህዝቦችና ትግራይ ክልሎች የጥቃቅን አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች ከሌላ አቅራቢ ጋር በመንግስት ግዥ ሲጫረቱ 3% ተጨማሪ ነጥብ
ይጨመርለታል፡፡ በኮንስትራክሽን ዘርፍም የመንግስት የኮንስትራክሽን ስራ የሚጫረት
ኮንትራክተር ከ30% በላይ የስራው ድርሻ በጥቃቅን አነስተኛ ኢንትርፕራይዞች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 197


ለሚያሰራ 3% ተጨማሪ ነጥብ በጨረታ ውጤቱ ይጨመርለታል፡፡ የተሻለ እንቅስቃሴ
የሚታየው በአማራ፣ ደቡብና አዲስ አበባ ደግሞ የቢሮ ፈርኒቸሮች ከጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፐራይዞች ለመግዛት የሚያስችል አሰራር እየጀመሩ መሆኑ በተደረጉ ውይይቶች
ለመረዳት ተችሏል፡፡ በተለይ በአማራ ክልል ጥቃቅን አነስተኛ በመንግስት የግዥ
ጨረታ የጨረታ ሰነድ ያለ ክፍያ የሚያገኙበት፤ ለአፈፃፀም ዋስትና ሲፒዮ (CPO)
የማይጠየቁበት፤ ግዥ በቁርጥ ዋጋ የሚያገኙበት ደንብ ተዘጋጅቶ መተግበሩ እና
በጨረታ 7% ማበረታቻ ተጨማሪ ነጥብ ይሰጣል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ጅማሮዎች ጥሩ
ቢሆኑም በስፋትና በበቂ ሁኔታ መጠናከር እንዳለባቸው መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

ሠ/ ምልመላና ስምሪት
በአምራች የሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ለኢንዱስትሪው ሰፊ መሰረት መሆን ካለባቸው
ዘርፉን የሚቀላቀሉት መጠን የመጀመሪያ ወሳኝ ሁኔታ ነው፡፡ በዘርፉ በርካታ
ኢንተርፕራይዞች ከተፈጠሩ ወደ መካከለኛ የሚሸጋገሩት ቁጥር ይጨምራል፡፡ ይሁንና
ዘርፉን ለመቀላቀል የግለሰቡ /ኢንተርፕራይዙ/ ሙሉ ውሳኔ ስለሆነ እንደ ሀገር
በአምራች ዘርፍ የተሰማራው ከ16 በመቶ በላይ እንዳልሆነ ይታያል፡፡ በዘርፉ ያሉት
ማበረታቻዎቹና ድጋፎች ያን ያህል ጠንካራ ባለመሆናቸው አምራች ዘርፉን በስፋት
የሚቀላቀል ሀይል የለም፡፡ በኢንዱስትሪ ለመሰማራት አቅም ባለው ሀይል በትጋት
የመመልመል ስራም አልተሰራም፡፡

7.1.2 ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ከመካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ጋር ያላቸው


ትስስር
በተለይ ከጨርቃ ጨርቅና ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ጋር ሙያዊ ስልጠናና የግብዓት
ሰንሰለት ትስስር መፈጠር ተጀምሯል፡፡ ለምሳሌ በትግራይ ክልል ከአልመዳ ጨርቃ
ጨርቅ፣ ከማ-ጋርመንት፣ ሼባ ሌዘር፤ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ በርካታ
ኢንተርፕራይዞች ሙያዊ ስልጠና እንዲያገኙ እና እነዚህ መካካለኛና ከፍተኛ
ኢንዱስትሪዎች መስፈርት አውጥተው ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በንዑስ ኮንትራት
እያሰሩዋቸው ሲሆን ኢንተርፕራይዞች ፈጣን የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲያደርጉ እና
ያልተቋረጠ የገበያ እድል እንዲያገኙ እድል የተፈጠረላቸው ሲሆን የአውትግሮወር እና
ኮንሴሽን (concesion) አሰራሮች ግን ገና ተግባራዊ አልተደረጉም፡፡ በአማራ ክልልም
የደሴና ኮምቦልቻ ጨርቃጨርቅ ሙከራው ያለ ቢሆንም በዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት
አይደለም፡፡ በአጠቃላይ አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለመካከለኛና ከፍተኛ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 198


ኢንዱስትሪዎች ግብአት ለማምረት እንዲችሉና ከከፍተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች
የንዑስ ኮንትራት ስራ የተጀማመሩ ስራዎች ተጠናክው መቀጠል አለባቸው፡፡

7.1.3 በአምራች ዘርፍ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ዕድገትና ሽግግር

የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ የሚያደርገው


የኢንቨስትመንት መጠንና ውጤታማነት ከፍተኛ እምርታ እንዲያስመዘግብ አንዱ
መሠረት የሆነው በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ
አንቀሳቃሾች ጉልህ ሚና ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ የሚሸጋገሩበትና የተማረው ወጣት
በሥራ ፈላጊነት ሳይሆን በስራ ፈጣሪነት አስተሳሰብ እንዲታነፅ ከማድረግ አንፃር
የዘርፉን አፈፃፀም መቃኘት ይጠቅማል፡፡ በዚህም መሠረት በሁለተኛ ደረጃ በተገኘው
መረጃ መሠረት በዘርፉ የተሰማሩ አንቀሳቃሾችና የዕድገት ሽግግር አፈፃፀም
እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ሠንጠረዥ 7.1 በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ብዛት

አመት
2003 2004 2005 2006
ዘርፍ
ከጠቅላላ ከጠቅላላ ከጠቅላላ ከጠቅላላ
ብዛት በፐርሰንት ብዛት በፐርሰንት ብዛት በፐርሰንት ብዛት በፐርሰንት
አገልግሎት 17,517 28.6 21,165 28.2 17,588 27 18,987 25.7
ንግድ 30,589 49.9 34,661 45.9 25,660 39.5 29,071 39.3
ኮንስትራክሽን 2,678 4.4 5,419 7.2 6,418 9.9 5,618 7.6
አምራች ኢንዱስትሪ 7,210 11.7 8,564 11.4 6,747 10.4 7,744 10.5
ከተማ ግብርና 3,037 4.9 4,775 6.4 7,803 11.9 12,062 16.3
ዘርፍ ያልገለፁ 222 0.4 430 0.6 822 1.3 417 0.6
ድምር 61,253 100 75,014 100 65,038 100 73,899 100
ምንጭ፡ (የፌደራል ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጄንሲ, 2007)

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 199


በየአመቱ ዘርፉን የተቀላቀሉ ኢንተርፕራይዞች በዘርፍ

ግራፍ 7.2 በየአመቱ በተለያየ ዘርፍ የተቀላቀሉ ኢንተርፕራይዞች


ምንጭ፡ (የፌደራል ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጄንሲ, 2007)

ከላይ በተገለፀው መረጃ መሰረት ባለፉት አራት አመታት (ከ2003 እስከ 2006 ዓ.ም)
ዘርፉን ከተቀላቀሉት ኢንተርፕራዞች በአምራች ዘርፍ የተሰማሩት ከጠቅላላው (11.7%,
11.4%, 10.4% እና 10.5%) በተከታታይ መሆኑ የሚያሳየው ወደ ዘርፉ የሚቀላቀለው
ኢንተርፕራይዝ ከጠቅላላው 10-11% ያልበለጠ መሆኑ ሲታይ እድገቱም እየጨመረ
ሳይሆን እየቀነሰ መሄዱን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በተጨማሪም የጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ የተሸጋገሩ ያለፋት አራት
አመታት በተመሳሳይ አፈፃፀሙን ስናይ በአገልግሎት፤ በንግድ፤ በኮንስትራክሽን፤
በማኑፋክቸሪንግ፤ በከተማ ግብርናና ሌሎች ዘርፉን ከተቀላቀሉ አንቀሳቃሾች ውስጥ
በ2003 ዓ.ም (0.45%)፤ 2004 ዓ.ም (0.57%)፤ 2005 ዓ.ም (1.06%) እና 2006 ዓ.ም
(2.36%) ያህሉ ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራዝ የተሸጋገሩ ሲሆን የዕድገት
ጉዞው ከአመት አመት እየተሻሻለ የመጣ መሆኑን ቢያመላክትም ዘርፉን ከተቀላቀሉት
ቁጥር አንፃር ሲታይ ግን በጣም አነስተኛ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 200


ሰንጠረዥ 7.2 በየአመቱ ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች ብዛት

አመላካች አመት
2003 2004 2005 2006
ዘርፉን የተቀላቀሉ ኢንተርፕራይዞች ብዛት 61,253 75,014 65,038 73,899
ወደ መካከለኛ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች ብዛት 276 428 695 1,742
ዘርፉን ከተቀላቀሉት ኢንተርፕራይዞች የተሸጋገሩት
በፐርሰንት 0.45% 0.57% 1.07% 2.36%

ግራፍ 7.3 ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች (2003 - 2006 ዓ.ም)


ምንጭ፡ (የፌደራል ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጄንሲ, 2007)

የተለያዩ ጥናቶችና ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት፤ ኢንተርፕራይዞች ከጥቃቅንና አነስተኛ


እርከን ወደ መካከለኛ ደረጃ ያልተሸጋገሩበት ምክንያት ከኢንተርፕራይዞቹ ፍላጎት ጋር
ተያይዞ ሲገለፅ ቆይቷል፡፡ ይህ አገላለፅ በአንድ በኩል ፍላጎት ማነሱ ኢንተርራይዞች
በውድድር ውስጥ ገብተው መጓዝ ስለማይፈልጉ ሁሉም የቤት ስራቸውን መንግስት
እንዲወጣላቸው ስለሚፈልጉ ነው ይላል፡፡ በዚህ ጥናት በናሙናነት ከተዳሰሱ 116
ኢንተርፕራይዞች መካከል 45 ያህሉ (38.8%) በጥቃቅንና አነስተኛ የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ካሉበት ደረጃ በይፋ ታውቆ ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝነት
ለመሸጋገር ያላቸው ፍላጎት ከፍተኛ ነው የሚል እምነት አለ፡፡ ከፍተኛው አሀዝ የያዙት
(48 ኢንተርፕራይዞች) ማለትም 41.4% ያህሉ ደግሞ ኢንተርፕራይዞች ለመሸጋገር
ያላቸው ፍላጎት በመካከለኛ ሲፈርጁት 23 (19.8 %) ያህሉ ደግሞ ፍላጎቱን
በዝቅተኝነት ገልጸውታል፡፡ ከጥቃቅንና አነስተኛ ወደ መካከለኛ ታዳጊ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 201


ኢንተርፕራይዝነት ለመሸጋገር የሚታየው ዳተኝነት የሰጡት ምክንያት ማየት
ያስፈልጋል፡፡

ግራፍ 7.4 ጥ/አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ወደ መካከለኛ ደረጃ ለመሸጋገር ያላቸው ፍላጎት


ምንጭ፡ የመስክ ዳሰሳ፣ 2007 ዓ.ም

በጥናቱ በናሙናነት ከተሳተፉ ኢንተርፕራይዞች አብዛኞቹ (38.8%) በጥቃቅንና


አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ደረጃ ለመሸጋገር ፍላጎት
ያለመኖር ሳይሆን ኢንተርፕራይዞቹ ለሽግግሩ የሚያበቃ የካፒታል ክምችት ስላልፈጠሩ
መሆኑን ይገልፃሉ፡፡ በሌላ በኩል ሰፋ ያለ መልስ የተሰጠባቸው ምክንያቶች በጥቃቅንና
አነስተኛ ደረጃ እያሉ መንግስት የሚሰጣቸው ድጋፎች ከሽግግር በኃላ ስለሚቋረጡ
(21.6%) እና ከሽግግር በኋላ መንግስት ሊሰጠው የሚችል ድጋፍ እንኳ ቢኖር መካከለኛ
ኢንተርፕራይዞች ፍላጎት የማያሟላ ላይሆን ይችላል የሚል ስጋት (20.7%) ናቸው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 202


ሰንጠረዥ 7.3 ጥቃቅን አነስተኛ ተቋማት ወደ መካከለኛ ደረጃ ላለመሸጋገር የሚያቀርቡት
ምክንያት
ዝርዝር ምክንያቶች የተሰጠ መልስ
በቁጥር በመቶኛ
ለሽግግር የሚያበቃ መስፈርት ስለማያሟሉ /በተለይ ከካፒታል አንፃር/ 45 38.8%
ከተሸጋገሩ በኃላ ከፍተኛ ግብር ይጣልብኛል በሚል በመፍራት 10 8.6%
በጥቃቅንና አነስተኛ ደረጃ እያሉ መንግስት የሚሰጣቸው ድጋፎች ከሽግግር 25 21.6%
በኃላ ስለሚቋረጡባቸው
ከሽግግር በኃላ መንግስት ሊሰጠው የሚችል ድጋፍ ፍላጎታቸውን የማያሟላ 24 20.7%
ላይሆን ይችላል በሚል ስጋት
ከእውነት የራቀ የኢንተርፕራይዞች ምክንያታዊ ያልሆነ አመለካከት ችግር 2 1.7%
ኢንተርፕራይዞች ጠንክረው ስለማይሰሩ ዓቅም ባለመፍጠራቸው 3 2.6%
መንግስት በተግባር እየሰጠው ያለ ድጋፍ ለሽግግር የማያበቃ በመሆኑ 1 0.9%
ከላይ የተዘረዘሩ ሁሉንም በምክንያትነት ያስቀመጡ 2 1.7%
መልስ ያልሰጡ 4 3.4%
ድምር 116 100

ምንጭ፡ የመስክ ዳሰሳ (2007 ዓ.ም)

በአጠቃላይ ኢንተርፕራይዞች ወደ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር


የሚያበቃ የካፒታል ክምችት ያለመድረስ የሚል ምክንያት በውይይቱ ላይ በስፋት
ተነስቷል፡፡ በተለይ የብድር አቅርቦቱ ለአምራች ዘርፍ የተወሰነ ማሻሻል ከተደረገበት
በኃላ ኢንተርፕራይዞች የመሸጋገር ፍላጎታቸው እየጨመረ መሆኑ ቢሮ ኃላፊዎችና
ባለሙያዎች ይገልጻሉ፡፡ ይህ የሚያመላክተን ለአምራቹ እየተሰጠ ያለው ድጋፍ ዘርፈ
ብዙ ቢሆንም ከውጤታማነት አንፃር ክፍተት እንዳለው ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ
ለማየት የተቻለው ላለመሸጋገር ዳተኝነት የሚታይባቸው ከአምራቹ ይልቅ በንግድና
በአገልግሎት ዘርፉ የተሰማሩ መሆናቸውን ጥናት በተደረገባቸው ክልሎች ጋር
በተካሄደው ውይይት ለመረዳት ተችሏል፡፡ ኢንተርፕራይዞች በምክንያት ያቀረቡት
ለንግድና አገልግሎት ለመስሪያ ቦታ ያን ያህል የተጠናከረ ድጋፍ ስለማይደረግና
መሸጋገሩ ሊያስገኝላቸው የሚችለው ጥቅም ባለመኖሩ ምክንያት መሆኑን ከውይይቱ
ለመረዳት ተችሏል፡፡ በተለይ የፋይናንስ አቅርቦቱ ዓቅም ውስንነት፣ የቴክኒክና ሙያ
ትምህርትና ስልጠና ተጨባጭ ለውጥ ባለማምጣቱ ምክንያት የዕውቀትና ክህሎት
ክፍተት መኖር፣ እንዲሁም የመረጃ አቅርቦትና የአዋጭነት ድጋፍና ምክር አገልግሎት
አሰጣጥ በደንብ እየተሰራባቸው አይደለም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 203


7.2 በገጠር የአርሶአደሩ ምጣኔ ሀብት

አንድ ሀገር ለልማት የሚያስፈልጉት የተለያዩ የምርት ግብአቶች አሉ፡፡በዚህ ውስጥ


በቅድሚያ የሚጠቀሱት ካፒታል፣ የሰው ጉልበትና መሬት ናቸው፡፡እነዚህን የልማት
ግብአቶች በላቀ ፍጥነትና ውጤታማነት በመጠቀም ቀጣይነት ያለው ልማት ለማረጋገጥ
ወሳኝ እንደሆኑ ሁሉም የኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ይስማሙበታል፡፡

በሀገራችን ከላይ የተጠቀሱትን መሰረታዊ ግብአቶች በተሟላ መንገድ ለመጠቀም ሰፊው


የገጠር ህዝብ በሚተዳደርበት ግብርና ላይ ማተኮር የግድ ይሆናል፡፡በመሆኑም በአንድ
በኩል ለአምራች ኢንዱስትሪው ግብአት የሚሆን ምርት በማምረት በሌላ በኩል ለዚሁ
ኢንዱስትሪ ዕድገት የሚውል ካፒታልን ለመፍጠር የሚችል በመሆኑ ለግብርና ዕድገት
ትኩረት መስጠት ተገቢ ነው፡፡ ስለዚህ በጥቂቱም ቢሆን በአርሶአደሩና አርብቶአደሩ
እየተፈጠረ ያለውን ካፒታል እሴት በሚጨምሩና ዘላቂ የምጣኔ ሀብት ዕድገት
በቀጣይነት በሚያረጋግጡ ዘርፎች ላይ በምንጠቀምበት አቅጣጫ መመራት አለበት፡፡

መንግስት በግብርናው ዘርፍ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ያለው አርሶአደሩ ገበያ ተኮር
ምርቶች ላይ አተኩሮ እንዲሁም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዞ ምርታማነቱ እንዲጨምር
ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በየአካባቢው የሚገኝ አርሶአደር ዕኩል የምርታማነት
አፈፃፀም ደረጃ ላይ ባይደርስም በርካታ ግንባር ቀደም አርሶአደርና አርብቶአደሮች
እየተፈጠሩ ነው፡፡ በአራቱ ክልሎችና ከግብርና ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር
በተደረገው ውይይት ላይ ተመሳሳይ ሃሳብ ቀርቧል፡፡ በእርግጥ ምን ያህል አርሶአደሮች
ትርፍ አምራች እንደሆኑ በየክልሉም ሆነ ከግብርና ሚኒስቴር በተደረጉ ውይይቶች
በአሀዝ የተደገፈ መረጃ አልቀረበም፡፡ በውይይቶቹ ይጠቀሱ የነበሩ ምን ያህል
አርሶአደሮች በግብርና ኤክስቴንሽን እንደሚደገፉ፣ በድምር ምን ያህል ምርት
እየተመረተ እንደሆነ፣ በመስኖ የእርሻ ስራ የተሰማሩትን ሽፋን እና የመሳሰሉትን
አመላካቾች በመጥቀስ ነበር፡፡

ጥናት በተደረገባቸው አራት ክልሎች (ትግራይ፣ አማራ፣ ደቡብ ብ/ብ/ህዝቦች እና


ኦሮሚያ) ውስጥ የሚገኙ አርሶአደሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ የትርፍ አምራች ደረጃቸውን
እያሻሻሉ የመጡበት አዝማሚያ እንዳለ በጥናቱ ውይይት ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎችና
አመራሮች ገልፀዋል፡፡ ለዚህ ማሳያ በ2007 ዓ.ም በእነዚህ አራት ክልሎች ወደ 389

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 204


የሚሆኑ አርሶአደሮች ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩና በአጠቃላይ ወደ 1.4 ቢሊዮን ብር
በጥሬ ገንዘብና በቋሚ ንብረት ሀብት ፈጥረው ያስመዘገቡ ናቸው፡፡በአጠቃላይ ከላይ
በተጠቀሱት አራት ክልሎች ውስጥ ባሉ የግብርናና ገጠር ልማት ቢሮዎች ከተመረጡ
ባለሙያዎችና ሀላፊዎች ጋር በሚከተሉት መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የትኩረትና
የባለሙያ ፓናል ውይይቶች ተደርገዋል፡፡

የመጀመሪያው ጉዳይ በገጠር ምን ያህል አርሶአደር ለገበያ የሚሆን ትርፍ ምርት


ማምረት እንደተቻለ ማወቅ ነው፡፡ ለዚህ ጥያቄ በአራቱም ክልሎች ያሉት ግብርናና
ገጠር ልማት ቢሮዎች ትክክለኛና ግልፅ መልስ በአጭሩ በሀዛዊ መግለጫ
ባያስቀምጡም ነገር ግን በተዘዋዋሪ መንገድ አጠቃላይ የሆነ አመላካች መልስ
ለመስጠት ሞክረዋል፡፡ በዚህም መሰረት በመጀመሪያ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን
ለመቀበል ዝግጁ የሆኑ አርሶደሮችና አርብቶአደሮች የሚሰጣቸውን የኤክስቴንሽን
አገልግሎት ተቀብለው ተግባራዊ ያደረጉና የተለወጡ ሞዴል አርሶአደሮች እተበራከቱ
እንደመጡ ገልፀዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ከላይ እንደተጠቀሰው ትርፍ ምርት
የሚያመርቱ አርሶአደሮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑ ታውቋል፡፡ ለዚህ
ማሳያ የሚሆነው አንደኛ አብዛኛው ህብረተሰብ በምግብ ሰብል ፍጆታ ራሱን እየቻለ
መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የሰጡት ምላሽ በገጠር በርካታ ባለሀብት
አርሶአደሮችና አርብቶ አደሮች እየተፈጠሩ መሆናቸውን ነው፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ
ሁሉም አርሶአደሮች ልጆቻቸውን እያስተማሩ ናቸው፡፡ ጥቂቶቹ ደግሞ በባንክ ገንዘብ
መቆጠብ ጀምረዋል፡፡ የተወሰኑ አርሶአደሮችም ቋሚ ወደ ሆነ ሀብትና ንብረት
የተሸጋገሩ ናቸው፡፡ ለምሣሌ የቤት እንስሳትን መግዛት፣ መኖሪያ ቤታቸውን አሻሽለው
መስራት፣ ወፍጮ መትከል፣ ከተማ ውስጥ ቤት መስራት፣ የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን
መግዛት፣ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪ ላይ ለምሳሌ ብረታብረት ላይ መሰማራት፣
ንግድ ስራ ላይ መሰማራት፣ ሆቴሎችን መክፈትና፣ የመሳሰሉት እንደሚገኙባቸው
ገልፀዋል፡፡

ሁለተኛው ጉዳይ በገጠር ምን ያህሉ አርሶአደሮች ወደ ባለሀብትነት (አነስተኛ፣


መካከለኛና ከፍተኛ ባለሀብት) እንደተሸጋገሩ ለማወቅ ሲሆን በአማራ ክልል በ2ዐዐ7
ዓ.ም ወደ ባለሀብት የተሸጋገሩና ዕውቅናና ሽልማት የተሰጣቸው 38 አርሶአደሮች
መሆናቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተመሳሳይ መንገድ በ2ዐዐ7 ዓ.ም በትግራይ፣ በደቡብ
ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልሎች 69፣ 115፣ እና 167

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 205


አርሶአደሮች ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ መሆኑ ታውቋል፡፡ በአጠቃላይ በ2007 ዓ.ም
በአራቱም ክልሎች 389 አርሶደሮች ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ ሲሆን አጠቃላይ
በባንክ ያስቀመጡት ገንዘብ ብር 156,146,067፣ በቋሚና ተንቀሳቃሽ ኪፒታል ደግሞ
ብር 1,219,949,962 በድምሩ ብር 1,387,146,278 የካፒታል ሀብት የፈጠሩ
መሆናቸውን ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ ይህ አሀዝ ዕውቅናና ሽልማት ተሰጧቸው ወደ
ባለሀብት የተሸጋገሩትን ብቻ የሚመለከት ስለሆነ እንጂ ከላይ እንደተገለፀው በየአመቱ
ብዛት ያላቸው አዳዲስ አርሶአደሮችና ከፊል አርሶአደሮች ተሸላሚዎች ናቸው፡፡

ግራፍ 7.5 በ2007 ዓ.ም ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶአደሮች-(አራት ክልሎች)

የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ የ2006 ዓ.ም (CSA, 2014) የህዝብ ቁጥር
ትንቢያ ሪፖርት መሰረት በአራቱም ክልሎች (ትግራይ፣ አማራ፣ ደቡብና ኦሮሚያ) ወደ
64.594 ሚሊዮን የሚሆነው ህዝብ በገጠር የሚኖር አርሶአደርና አርብቶአደር መሆኑን
ያመለክታል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 206


ሰንጠረዥ 7.4 በአራቱ ክልሎች የሚኖረው ጠቅላላ አርሶአደርና አርብቶአደር ብዛት

ተ.ቁ ክልል በገጠር የሚኖር ህዝብ የአባዋራ ብዛት በ2007 ወደ


ብዛት ባለሀብትነት
የተሸጋገሩ ብዛት
ትግራይ 3,760,000 750,000 69
አማራ 16,892,000 3,610,000 38
ኦሮሚያ 28,812,000 5,760,000 167
ደቡብ ብ/ብ/ሕ 15,130,000 3,030,000 115
ጠቅላላ ድምር 64,594,000 13,150,000 389

ግራፍ 7.6 በአራቱ ክልሎች የሚኖረው ጠቅላላ አርሶአደርና አርብቶአደር ብዛት

ነገር ግን ከላይ እንደተጠቀሰው በእነዚህ አራት ክልሎች በ2007 ዓ.ም ወደ ባለሀብትነት


የተሸጋገረው አርሶአደር ጠቅላላ ድምር 389 ብቻ ነው፡፡ይህ ቁጥር በአጠቃላይ
በክልሎቹ ከሚኖረው አርሶአደርና አርብቶአደር ቁጥር ጋር ሲወዳደር እጅግ ዝቅተኛ
መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ከአባዋራዎች ቁጥር (13.15 ሚሊዮን) ጋር ሲነፃፀር ደግሞ
0.003 ፐርሰንት ብቻ ይሆናል፡፡ይህ አሀዝ የሚያመለክተው በገጠር ሰፊ ቁጥር ያለው
አርሶአደርና አርብቶአደር የመኖሩን ያክል ብዙ ባለሀብት አርሶአደሮች እንዳልተፈጠሩ
እና አብዛኛው አርሶአደር የግብርና ስራውን ለማከናወን የዘመናዊ ቴክኖሎጂ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 207


አጠቃቀሙና ምርታማነቱን ከዚህ በላቀ ለማሳደግ ብዙ ጥረት መደረግ እንዳለበት
ያሳያል፡፡ በሌላ በኩል የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር በመጀመሪያው የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የአፈፃፀም ሪፖርት ላይ እንደገለፀው የግብርና ኤክስቴንሽን
አገልግሎት ተደራሽነት በ2006 ዓ.ም መጨረሻ ላይ ካቀደው 12.849 ሚሊዮን
አባዋራዎች ወደ 13.095 ሚሊዮን እንደደረሰና ከዕቅዱ በላይ ማከናወኑን አስቀምጧል፡፡
የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽነት እየጨመረ ከመጣ አርሶአደሩ በግብርና
ስራው ላይ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚነቱና ምርታማነቱ የዚያኑ ያህል እንዲጨምር
ይጠበቃል፡፡ የዚህም ውጤት ደግሞ ወደ ባለሀብትነት የሚሸጋገሩ አርሶአደሮችንና
አርብቶአደሮችን ቁጥር በተሰጠው የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ልክ የሚጨምር
እንዲሆን ይጠበቃል፡፡ በጥቅሉ በአራቱም ክልሎች ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩት
አርሶአደሮች ቁጥር ከአጠቃላዩ የገጠር አርሶአደር ቁጥር እና የኤክስቴንሽን አገልግሎት
ከሚያገኙት ቁጥር ጋር ሲነፃፀር እጅግ አነስተኛ በመሆኑ የተጀመረውን የግብርና
ቴክኖሎጂ አጠቃቀምና ምርታማነትን የማሻሻል ስራ የበለጠ ትኩረት ያስፈልገዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እና የግብርናው ዘርፍ ተቀናጅተውና
ተናበው በጋራ ሊሰሩ ይገባል፡፡

ግራፍ 7.7 በ2007 ዓ.ም በአራቱ ክልሎች ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶአደሮች


(ተደራሽነት %)

ከላይ ግራፍ 7.6 እንደሚታየው በ2007 ዓ.ም በአራቱም ክልሎች ወደ ባላሀብትነት


የተሸጋገሩትን አርሶአደሮች ቁጥር ከአባዋራዎች ቁጥር ጋር ስናወዳድር በተነፃፃሪነት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 208


የትግራይ ክልል የተሻለ (0.0092 %) ተደራሽነትን ሲያስመዘግብ የአማራ ክልል ደግሞ
ዝቅተኛውን ውጤት (0.0011 %) አስመዝግቧል፡፡

በሌላ በኩል በ2007 ዓ.ም ውጤት መሰረት በእያንዳንዱ ክልል የተፈጠረውን አጠቃላይ
የካፒታል መጠን ወደ ባለሀብትነት ከተሸጋገሩ አርሶአደሮች ጋር ሲወዳደር የደቡብ
ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል የተሻለ ውጤት ሲያስመዘግብ የኦሮሚያ ክልል ደግሞ
ዝቅተኛውን ካፒታል አስመዝግቧል፡፡ ይህ ውጤት በተነፃፃሪነት ለማወዳደር ያህል
እንጂ ሁሉም ክልሎች ከዚህ የተሻለ እጅግ ብዙ መስራት እንዳለባቸው መገንዘብ
ያስፈልጋል፡፡

ግራፍ 7.8 በየክልሎቹ የተፈጠረው ኪፒታል ከባለሀብቶች ቁጥር ጋር ሲወዳደር

ሌላው ጉዳይ አርሶአደሩ ያገኘውን ትርፍ ምርት በምን መልክ እንደሚያከማቸው


ወይም እንደሚጠቀምበት ለማወቅ ከሚመለከታቸው ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር
ውይይት ተደርጓል፡፡ አብዛኛዎቹ ተሳታፊዎች ይህንን ጉዳይ በሚመለከት የሚከተለውን
አስተያየት ሰጠዋል፡፡ በመጀመሪያ በአሁኑ ወቅት አብዛኛው አርሶአደር ምርቱን
ባመረተበት ወቅት ለገበያ የሚያቀርብ ቢሆንም በጣም ጥቂት አርሶ አደሮች ደግሞ
ያመረቱትን ምርት ወዲያው በርካሽ ዋጋ ለገበያ እንደማያቀርቡ ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም
እነዚህ ጥቂት አርሶአደሮች ያመረቱትን ምርት በተሻለ መንገድ አከማችተው ቆይተው
ገበያው የተሻለ ሲሆን የሚሸጡ ሲሆን ቁጥራቸውም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 209


መምጣቱን አስረድተዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደገለፁት፤ አርሶአደሩ ያገኘውን
ትርፍ ምርት በአጠቃላይ በሁለት መልኩ ያከማቸዋል፡፡ አንደኛ በቀጥታ ያመረተውን
ምርት በጐተራና በሌሎች የእህል ማከማቻዎች ለተወሰነ ጊዜ ማስቀመጥ ሲሆን
ሁለተኛው መንገድ ደግሞ፤በጥሬ ገንዘብ ማስቀመጥ (ባንክ)፣ የተሻሉ ዝርያ ያላቸውን
የቤት እንስሳት በመግዛት ማርባት፣ በከተማ ቤት መስራትና ቋሚ የሆኑ የቤት ዕቃዎችን
በመግዛት (በተለይ ከተማ የምንጠቀምባቸው እንደ ሶፋ፣ አልጋ፣ ፍሪጅ የመሳሰሉት
ይገኙበታል)፣ ወደ ንግድ በመሰማራት (ለምሳሌ ሻይ ቤት፣ ወፍጮ፣ ሱቆች፣ ወዘተ)፣
ለመስኖ እርሻ የሚያገለግሉ መሳሪያዎችን በመግዛት፣ ባጃጅና መኪናዎች በመግዛት
የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት፣ ጥቂት አርሶአደሮች ደግሞ ትራክተርና ዘመናዊ
የእርሻ መሳሪያዎች በመግዛት፣ በጣም በጥቂቱም ቢሆን በአግሮ ፕሮሰሲንግ ላይ
የተሰማሩ (ማር ማጣራት፣ ሰሊጥ ማጣራት፣ ቲማቲም ፕሮሰስ ማድረግ፣ ወዘተ)
አርሶአደሮች ይገኙበታል፡፡

በሌላ በኩል በሽልማት ዕውቅና ተሰጧቸው ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩትን


አርሶአደሮች እሴት በሚጨምሩ የኢንቨስትመንት መስኮች ወይም በአምራች
ኢንዱስትሪው እንዲሰማሩ የሚመለከታቸው አመራሮች በዕቅድ ይዘውና ትኩረት ሰጠው
እንዳልሰሩ ገልፀዋል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ውጪ በሌሎች የተለያዩ መስኮች ላይ
እንዲሰማሩ ጥረት እንደሚደረጉ አብራርተዋል፡፡ ለምሣሌ የተወሰኑ አርሶአደሮች
በምርጥ ዘር ብዜት ላይ ተሳትፎ እያደረጉ ነው፡፡ ምርጥ ዘሮችን ከገዙ በኋላ ፕሮሰስ
አድርገው ለአርሶአደሩ የማቅረብ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ ስለዚህ አርሶአደሮቹ በሌሎች
እሴት በሚጨምሩ ዘርፎች ላይ በስፋት እንዲሰማሩ በበቂ ሁኔታ አልተሰራበትም፡፡
አንዱ ምክንያት የአርሶአደሮች ዕሴት ጨምሮ በማቅረብ ላይ ያላቸው የዕውቀትና
ግንዛቤ ደረጃ ዝቅተኛ በመሆኑ ነው፡፡ ነገር ግን ግንዛቤውን ለአርሶአደሮች ለመስጠት
በዕቅድ ተይዞ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ገልፀዋል፡፡ በጥቂቱም ቢሆን አርሶአደሩ
የተሰማራባቸው ዘርፎች፡በወተት ልማት፣ በማር ልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣
እንስሳት በማደለብ ስራ፣ ለቢራ ገብስና ለዱቄት ፋብሪካ ስንዴ ማቅረብ፣ በቡና ልማት፣
ወዘተ ናቸው፡፡

በተለይ ቀደም ሲል እንደሀገር ስንከተለው የነበረ የማበረታቻ ስልት ዕውቅና የተሰጠው


አርሶአደር በከተሞች መሬት እንዲያገኝና የከተማ ቤት እና ህንፃ ባለቤት እንዲሆን
ስለነበር ይህንን ተከትሎ የተወሰነ ሀብት ያፈራ አርሶአደር ግንባር ቀደም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 210


የኢንቨስትመንት ምርጫው በከተማ ቤት መግዛት፣ የተሻለ ዓቅም ካለው ደግሞ ህንፃ
መገንባት እንዲሁም የተለያዩ የንግዱ ስራዎች ማንቀሳቀስ ሆኗል፡፡ ይህ መሰል ሁኔታ
በሁሉም ክልሎች የሚታይ ተመሳሳይ ክስተት መሆኑ ከየክልሉ ግብርና ቢሮዎች
ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር ከተደረጉ ውይይቶች ለመረዳት ተችሏል፡፡ በእርግጥ ይህ
አካሄድ አሁን ትክክል አለመሆኑን መረዳትና እሴት በሚጨምሩ ለምሳሌ በአምራች
ኢንዱስትሪው እንዲሳተፉ የሚያደርግ አቅጣጫ መከተል ያስፈልጋል፡፡

በሽልማት ዕውቅና ተሰጥቷቸው ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮችን


በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ በሚደረገው ሂደት የክልል የግብርና ቢሮዎች ከሌሎች
የሚመለከታቸው አጋር ወይም አቻ መስሪያ ቤቶች (ለምሳሌ የኢንቨስትመንት ጽ/ቤት፣
ኢንዱስትሪ ቢሮ፣ ወዘተ) ጋር ያላቸው የጋራ የስራ ትስስር ጠንካራ እንዳልሆነ
የውይይቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል፡፡ በተለይም ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገረውን ባለሀብት
ከተሸጋገረ በኋላ ያለው ድጋፍና ክትትል በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ በግብርናና ገጠር
ልማት ቢሮና በኢንቨስትመንት ጽ/ቤት መካከል ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ
አርሶአደሮችን የሚመለከት የመረጃ ልውውጥና ህጋዊ ርክክብ አይደረግም፡፡
የኢንቨስትመንት ጽ/ቤት እና የግብርና ገጠር ልማት ቢሮ በጐንዬሽ ግንኙነት ወደ
ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶአደሮችን መቀባበል ካልቻሉ ሜዳ ላይ ተበትነው የሚቀሩ
መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ በመሆኑም በተለይ ወደ አግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ
እንዲሰማሩ የሚደረገው ጥረት ገና በጅምር ላይ በመሆኑ ትኩረት ሰጠው መስራት
ይገባል፡፡ ስለዚህ በግብርናው ዘርፍ እና በኢንቨስትመንት ጽ/ቤቶች ወደ ባለሀብትነት
ለተሸጋገሩ አርሶአደሮች የሚሰጠው ክትትልና ድጋፍ ቀጣይነት ያለው መሆን
እንደሚገባው እና ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶአደሮች በሚመለከት በጋራ የመረጃ
ልውውጥ በማድረግ መስራት ይገባል፡፡

በሌላ በኩል የግብርና ምርቶችን የሚጠቀሙ ኢንዲስትሪዎች በተለይ የአግሮፕሮሰሲንግ


ኢንዱስትሪዎች የግብአት ችግር (በአቅርቦትና በጥራት ለምሣሌ ስንዴ፣ ገብስ፣ ወዘተ)
እንደገጠማቸው ይታወቃል፡፡ አርሶአደሩ የምርት መጠኑንና ጥራቱን እንዲጨምር
የተለያዩ ድጋፎች ለምሣሌ ምርጥ ዘር በማቅረብ፣ የአፈር ማዳበሪያና እንክብካቤ፣
የመስኖ አጠቃቀም ቴክኖሎጂ፣ ወዘተ እየተደረጉለት መሆኑን የውይይቱ ተሳታፊዎች
ገልፀዋል፡፡ በሌላ በኩል ተመሣሣይ ምርት የሚያመርቱ አርሶአደሮች በክላስተር
(Cluster) ለአንድ ገበያ ማምረት ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ የተጀመሩ ተግባራት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 211


መኖራቸውን ገልፀዋል፡፡ በጥቅሉ ሲታይ አርሶ አደሩ ለኢንዱስትሪዎች ግብአት የሚሆን
ምርት በአቅርቦትና በጥራት ከመስራት አኳያ ገና ብዙ እንደሚቀረው አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች ለፋብሪካቸው የሚያስፈልጋቸውን
የግብአት አቅርቦት በሚመለከት ከአርሶአደሩ ጋር አብሮ በቅርበት እንዲሰሩ ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች ወደ ዘመናዊ እርሻ ገብተው
ለፋብሪካቸው ግብአት ማምረት ቢችሉ ደግሞ የተሻለ ይሆናል፡፡

ሰንጠረዥ 7.5 ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶአደሮች ያስመዘገቡት ጥሬ ገንዘብ


የተመዘገበ ካፒታል መጠን ትግራይ አማራ ኦሮሚያ ደ/ብ/ብ/ሕ ድምር
ከብር 100 ሺ በታች 79 11 109 45 244
ብር 100-200 ሺ 30 5 65 25 125
ብር 200-300 ሺ 22 5 59 28 114
ብር 300-400 ሺ 11 - 28 6 45
ብር 400-500 ሺ 7 5 23 11 46
ብር 500 ሺ - 1ሚሊዮን 9 6 77 35 127
ብር 1-2 ሚሊዮን 7 8 25 18 58
ብር 2-3 ሚሊዮን 1 - 13 5 19
ብር 3-4 ሚሊዮን 1 1 2 - 4
ብር 4-5 ሚሊዮን - - - - -
ከብር 5 ሚለዮን በላይ - - 2 2 4
ድምር 167 41 403 175 786
መረጃው የተሰበሰበበት ጊዜ 2005፣ 2007 2005፣ 2007 2002፣ 2003፣ 2005 2003፣ 2005፣ 2007

ምንጭ፡ አራቱ ክልሎች የገጠርና ግብርና ልማት ቢሮዎች

በአጠቃላይ በገጠር አርሶአደሩ እየፈጠረው ያለውን የሀብት ክምችት ቀጣይነት ባለውና


እሴት በሚጨምሩ ዘርፎች በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ እንዲሰማራ ማድረግና
የኢንቨስትመንት ስምሪቱንም በዚህ አግባብ እንዲመራ ማድረግ ተገቢ ይሆናል፡፡
ግብርናው ለኢንዱስትሪ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ግብአት በማቅረብና የካፒታል
ክምችት በመፍጠር ብቻ ሳይሆን በኢንቨስትመንትም በቀጥታ የሚሳተፋበት ዕድል
እየሰፋ መምጣቱን የሚያመላክት ነው፡፡ በግንባር ቀደም አርሶአደርነት ዕውቅና
የተሰጣቸው አርሶአደሮች በአማካኝ ብር 1,318,240 ላይ ጠቅላላ ካፒታል ያስመዘገቡ
ሲሆን አማካይ በባንክ ያስቀመጡት ጥሬ ገንዘብ ሀብት ብር 173,956.85 በላይ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 212


ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶአደሮች ስንመለከት ደግሞ አማካይ ጠቅላላ ሀብታቸው
በአማካይ ብር 2827475.31 ሲሆን በጥሬ ገንዘብ ብቻ ያስመዘገቡት ሀብታቸው ደግሞ
በአማካይ ብር 370,033.21 ነው፡፡

ስለዚህ እየተፈጠረ ያለውን የአርሶአደሩን ካፒታል በታቀደ እና በተቀናጀ መንገድ


በመምራት በርካታ የአነስተኛና መካከለኛ ደረጃ ያላቸው አምራች ኢንዱስትሪዎችን
ማቋቋም የሚችል ዓቅም እንዳለ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ አርሶአደሩ በአምራች ዘርፍ
መሰማራት የሚችል መሆኑም የተግባር ማሳያዎች አሉ፡፡በትግራይ ክልል ሶስት
አርሶአደሮች በብረታ ብረትና ጋራጅ ስራዎች ተሰማርተዋል፡፡ በአማራ ክልል ደግሞ
አንድ አርሶአደር ባህርዳር ከተማ ላይ የከረጢት ማምረቻ ፋብሪካ አቋቁሟል፡፡

7.3 በንግዱ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች

ከአጠቃላይ የሀገራችን የምጣኔ ሀብት የአገልግሎት (የንግድና አገልግሎት) ዘርፍ


የአንበሳውን ድርሻ ይዞ ይገኛል፡፡ የኢንዱስትሪው ዘርፍ በተወሰነ ደረጃ እየተሻሻለ
የመጣና የግብርናው ዘርፍም ሚናውን በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እየቀነሰ ነው፡፡
የአገልግሎት ዘርፉ ለረጅም ዘመናት አስተዋፅኦው ከፍተኛ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ይህ ማለት
ከፍተኛው ድርሻ የሀገራችን ኢኮኖሚ በአገልግሎት ዘርፍ የተከማቸ መሆኑ ነው፡፡

ከአጭርና ከመካከለኛ ጊዜ በሀገራችን በአምራች ዘርፍ በተሻለ ሁኔታ በቀጥታ በስፋት


ይሳተፋል ተብሎ የሚታመነው የተወሰነ ካፒታል እና የገበያ ዕውቀት ያለው በንግድ
ስራ ላይ የተሰማራው ባለሀብት መሆኑ አያከራክርም፡፡ ሆኖም የንግድ ስራው በልምድ
ከትውልድ ትውልድ ሲንከባለል የቆየ እንጂ ሳይንሳዊና ዘመናዊነትን ተላብሶ የሚሰራ
ዘርፍ ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡ በመቐለ፣ ባህርዳር፣ ድሬዳዋ እና ሃዋሳ
ከአስመጪዎች፣ ላኪዎችና ጅምላ ንግድ ከተሰማሩ የንግዱ አመራርና ተወካይ
ነጋዴዎች ጋር የተካሄዱ ውይይቶች ይህንን ሀሳብ የሚያጠናክሩ ናቸው፡፡ በስድስቱ
ከተሞች እና ሀገር አቀፍ የንግድና የዘርፍ ማሕበራት አመራር ጋር የተደረጉ
ውይይቶችም የንግዱ ማሕበረሰብ በኢንዱስትሪ ለማሠማራት ሰፊ የእውቀት ክፍተቶች
እንዳሉበት ለመረዳት ተችሏል፡፡ በንግዱ ዘርፍ የተሰማራው ባለሀብት በሀገራችን
የኢንዱስትሪ ፖሊሲ እና የመንግስት ድጋፍም ሆነ ማበረታቻ የተሟላ ዕውቀት አለው
ለማለት አያስደፍርም፡፡ በንግድ ስራው መቀጠሉ በራሱ ከአለማዊ የምጣኔ-ሀብት ሁኔታ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 213


ያለው መስተጋብር ተፅዕኖ እና ግንኙነት ያለው ዕውቀት ጠንካራ አይደለም፡፡ በእንዲህ
ሁኔታ የተፈለገው ያህል አመቺ ፖሊሲ ቢቀረፅ ለንግዱ ማሕበረሰብ በተገቢው ሁኔታ
እንዲዳረስ ካልተደረገ ፈጣን የኢንቨስትመንት ፍሰት ሊያረጋግጥ አይችልም፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ በኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ድጋፍ ኢንስቲትዩት በየክልሉ የተጠኑ ፕሮጀክት
ፕሮፋይሎች እንኳ በተገቢው ስርዓት ለአዳዲስ ባለሀብቶች እየደረሱ ስላልሆነ
ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት አማራጮችን የሚመለከት በቂ መረጃ እንደሌላቸው
በተካሄዱ የጥናት ውይይት መድረኮች ለመረዳት ተችሏል፡፡

እንደሚታወቀው በሀገራችን እስካሁን ያለው ተጨባጭ ተሞክሮ እንደሚያሳየው


አብዛኛው በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች እየተሰማራ የሚገኘው የንግዱ
ማሕበረሰብ ነው፡፡ ስለዚህ ከፍተኛ ቁጥር ያለው እንዲሁም በተነፃፃሪነት የተሻለ
ካፒታል ያለው በመሆኑ እሴት በሚጨምሩና ለሀገራችን ዘላቂና ቀጣይነት ያለው
ዕድገት በሚያመጡ ዘርፎች ላይ እንዲሰማራ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት
ቅስቀሳ የግንዛቤ መፍጠር ስራዎችን በተከታታይ መስራት ይገባቸዋል፡፡

በመሆኑም በተለይ በአጭርና ከመካከለኛ ጊዜ ከረጅም ጊዜም ቢሆን የንግዱ


ማሕበረሰብ በአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆኑ
የማይቀር ነው፡፡ በተለይ ከአጭርና ከመካከለኛ ጊዜ ዕይታ ካለን ውስን የሀብት ክምችት
ዓቅም ዕውቀት ብቻ ይዞ ካፒታል የሌለው ኃይል በኢንዱስትሪው ለመሰማራት ያለው
ዕድል በጣም ጠባብ ስለሚሆን በንግድ የተሰማራው ማሕበረሰብ በአምራች ኢንዱስትሪ
ዘርፍ እንዲሰማራ ከመንግስት የሚቀርቡ ማበረታቻዎችና ድጋፎች ሳቢ መሆን
አለባቸው፡፡ በንግድ የተሰማራው ማህበረሰብ የአምራች ኢንዱስትሪው ከተሰማራበት
የንግድ ዘርፍ የበለጠ የኪሳራ መጋለጥ አደጋ ስላለው መንግስት በተወሰነ ደረጃም ቢሆን
ጋራንቲ እንዲሰጠው ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ አሁን አምራች ኢንዱስትሪው እየተፈታተኑት የሚገኙ በፖሊሲ ደረጃ እና


በአሰራር ደረጃ መፈታት ያለባቸው ችግሮች ከስራቸው በመፍታት በንግድ የተሰማራ
ማሕበረሰብ በአምራቹ ዘርፍም ሰፊ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በተጠናከረ ንቅናቄ
እየመለመሉ ዘርፉን እንዲቀላቀል ማድረግ፣ ትኩረት ሰጥቶ መደገፍና መምራት ጊዜ
የማይሰጥ መሆኑ አይቀርም፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 214


7.4 በኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች

በኢትዩጵያ ነባራዊ ሁኔታ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ በዋናነት ሶስት ጉዳዮችን


ያካትታል፡፡ የመጀመሪያው የመኖሪያ ቤት ግንባታ (residential) ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ
የመኖሪያ ቤት ያልሆኑ ቤቶች ግንባታ (non-residential) እንደ ፋብሪካ፣ መጋዘን፣ ቢሮ፤
ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤት ያሉትን ግንባታዎች ያካትታል፡፡ በሶስተኛ ደረጃ ሌሎች
ግንባታዎችን (other works) ሲያካትት እነርሱም መንገድ፣ ግድብ፣ የኤሌክትሪክ
ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ያሉትን ያጠቃልላል፡፡ የስራ ዘርፉ ግለሰቦችንና
ተቋማትን አቅፎ የያዘ ሲሆን በውስጡ ልዩ ልዩ ካምፓኒዎችን፣ በማማከር ስራ የተሰማሩ
ባለሙያዎች ወይም ድርጅቶች፣ ተቋራጮችና ንዑስ ተቋራጮች፣ የግብአት፣
መሣሪያዎችና ማሽን አቅራቢዎች፣ ግንበኞችንና ልዩ ልዩ ባለሙያዎችን ያካትታል
(ከልኮሚ፣ 2004 ዓ.ም)፡፡ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ በአገራችን በስፋት ከተጀመረ
የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለው ባይሆንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ግን ከፍተኛ መነቃቃት
እያሳየ ይገኛል፡፡ በተለይም ከደርግ መንግስት መውደቅ በኋላ በሀገሪቱ በተጀመረው
መልሶ ግንባታ ላይ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ
ነው፡፡ይህንን በመገንዘብ መንግስት እ.ኤ.አ በ2012 የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ፖሊሲ
በመቅረጽ ዘርፉ ያለበትን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችልና በዓለማቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ
የሚያደርግ አቅጣጫ እየተከተለ ያለው።

7.4.1 የኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፍ አፈፃፀም እና ለሀገር ኢኮኖሚ ያለው ድርሻ

የኮንስትራክሸን ንዑስ ዘርፍ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ፈርጀ ብዙ ጥቅሞች አሉት፡፡


መጀመሪያ ለጠቅላላ ሀገር ምርት (GDP) ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው፡፡ ዘርፉ
በከፍተኛ ፍጥነት ዕያደገ ያለና እና ለሌሎች ዘርፎች (ለግብርና፣ ኢንዱስትሪና
አገልግሎት) ዕድገት ጉልህ አስተዋፆ እያበረከተ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የኮንስትራክሸን
ንዑስ ዘርፍ ለሰራ ዕድል ፈጠራ ያለው ድርሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው፡፡ በተለይ
ደግሞ ዝቅተኛ ክህሎት ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የስራ እድል በመፍጠር ለድህነት
ቅነሳ የራሱን ድርሻ አየተወጣ ይገኛል፡፡ የ2007 ዓ.ም ያለውን የንዑስ ዘርፎች ዕድገት
ስንመለከት፤ ኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፍ በ36.8% ዓመታዊ ዕድገት ሲያስመዘግብ፣
የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ዕድገት ደግሞ 15.8% ሆኗል፡፡ በስንጠረዥ 7.6
እንደተመለከተው ለምሳሌ በ2007 ዓ.ም ያለውን ዕድገት ስንመለከት የኮንስትራክሽን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 215


ንዑስ ዘርፍ 56.1%፣ የአምራች ኢንዱስትሪ 31.8%፣ የማዕድን ማውጣትና ቁፍሮ 5.6%
እና የኤሌክትሪክና ውሃ ስራ 6.5% ድርሻ ይዘዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ንኡስ-ዘርፎች ለኢንዱስትሪው ያላቸውን ድርሻ ስናይ የግንባታው ዘርፍ


ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ማየት ይቻላል፡፡ የግንባታው ዘርፍ ድርሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ
እየጨመረ የአምራች ኢንዱስትሪ ድርሻ ግን እያነሰ መምጣቱን ከሰንጠረዥ 7.6
መረዳት ይቻላል፡፡ ይህ ከፍተኛ ውጤት ቢመዘገብም ነገር ግን ሁሉም በኮንስትራክሽን
ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ችግር የለባቸውም ለማለት አይደለም፡፡ አብዛኞቹ የካፒታል
አቅም ችግር እንዳለባቸውና ከመንግስት የተበደሩትን ገንዘብ ለመመለስ እንደተቸገሩ
ይገለፃል፡፡ነገር ግን በጣም ጥቂትም ቢሆን በዚህ ዘርፍ ውጤታማ የሆኑ ባለሀብቶች ወደ
አምራች ኢንዱስትሪ እንዲሰማሩ ማድረግ ጠቃሚ ነው፡፡

ሰንጠረዥ 7.6 ከ2005-2007 ኢንዱስትሪ ንዑስ ዘርፎች ከኢንዱስትሪው ያላቸው ድርሻ (%)3
የኢንዱስትሪ ንዑስ ዘርፎች 2005 2006 2007
ግንባታ ኢንዱስትሪ 47.1 49.9 56.1
አምራች ኢንዱስትሪ 33.6 33.4 31.8
መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪ 24.1 24.9 24.6
አነስተኛ አምራችና ሌሎች 9.5 8.5 7.2
ማዕድን ማውጣትና ቁፍሮ 11.0 9.1 5.6
ኤሌክትሪክ ና ውሃ ስራ 8.3 7.6 6.5
ምንጭ፡ ብሔራዊ ባንክ 2007 ዓ.ም አመታዊ ሪፓርት

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የተለያዩ ግብአቶችን


ይፈልጋል፡፡ ይህን ፍላጎት በሰፊው ለማሟላት ደግሞ አቅም ያላቸው አምራች
ኢንዱስትሪዎች በስፋት እንዲኖሩ ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ ከአራት ዓመት በፊት
በሀገራችን በቂ የሆነ የሲሚንቶ አቅርቦት በሌለበት ሁኔታ የኮንስትራክሽን
ኢንዱስትሪው ዕድገት ላይ ቀላል የማይባል አሉታዊ ተፅዕኖ ፈጥሮ ነበር፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት እየተስተዋለ ያለው የኮንስትራክሽን ግብአት ለምሳሌ
የአርማታ ብረት ዕጥረትና ያልተጠበቀ ዋጋ ጭማሪ በዘርፉ ዕድገት ላይ የራሱ ተፅዕኖ
አለው፡፡

3
ብሔራዊ ባንክ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር አሀዙን በመውሰድ 2006/07 አመታዊ ሪፓርቱ ላይ የተወሰደ መረጃ ነው ፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 216


በሌላ በኩል የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ በቀጣይነት የሚያድገው በተለይ
የኮንስትራክሽን ግብአቶች ከአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ሲቀርብለት ነው፡፡ ለምሳሌ
አምራች ኢንዱስትሪ ከኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የግንባታ አገልግሎቶችን ይፈልጋል፡፡
በአምራች ኢንዱስትሪ ውስጥ ሊፈጠር የሚችል የኢኮኖሚ አቅም የኮንስትራክሽን
ሴክተሩን መልሶ የመደገፍ አቅም አለው፡፡ በመሆኑም በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ
እየጨመረ የመጣውን አቅም ያለው ባለሀብት ወደ አምራች ኢንዱስትሪው እንዲሰማራ
ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 217


ክፍል IV
የጥናቱ ማጠቃለያና የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦች

ምዕራፍ 8
የጥናቱ ማጠቃለያ እና ምክረ-ሀሳቦች

8.1 የጥናቱ ማጠቃለያ

አምራች ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ዕሴት በመጨመር (high value addition) እና ሀብት


በመፍጠር ለታዳጊ ሀገሮች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፈጣን ዕድገት የጎላ አስተዋፅኦ
እንዳለው የሚታወቅ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ እና ለግብርና
ልማት የተለየ ትኩረት ሰጣለች፡፡ በአምራች ኢንዱስትሪው ልማት ውስጥ የሀገር ውስጥ
የግል ባለሀብት ፣የውጭ ባለሀብት፣ እና መንግስት ወይም የመንግስት ልማት ድርጅቶች
ተሰማርቶ የሚገኙ ቢሆንም የዚህ ጥናት ትኩረት በአምራች ኢንዱስትሪ ውስጥ የሀገር
ውስጥ የግል ባለሀብት የሞተርነት ሚናው ከመጫዎት አኳያ ያሉት ተግዳሮቶች፣
መልካም ዕድሎች በመፈተሸ እና የመፍትሄ ሀሳቦችን ለማቅረብ የተዘጋጀ ነው፡፡

በሀገራችን ዘላቂ የኢንዱስትሪ ልማትን ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ግንባር
ቀደም ተዋናይ መሆን እንዳለበት የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂያችን ያመለክታል
(ኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ 1994 ዓ.ም)፡፡ብዙ ተመራማሪዎች የሀገር ውስጥ
ኢንቨስትመንት (Domestic investment) እና የኢኮኖሚ ዕድገት ጠንካራ ግንኙነት
(Strong Relationship) እንዳላቸው ይስማማሉ፡፡ ይህ ደግሞ ለሀገራችን የተቀየሰው
የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂክ አቅጣጫ ትክክለኛ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ነገር ግን
ላለፉት አስርና አስራ አምስት አመታት የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በተለይ
በአምራች ኢንዱስትሪው ልማት ላይ የዋና ተዋናይነት ሚናውን በሚገባው ልክ
እየተጫወተ አይደለም፡፡ በመሆኑም በዚህ ጥናት ውስጥ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ
በአምራች ኢንዱስትሪው ውስጥ የዋና ተዋናይነት ሚናውን ከመጫወት አኳያ ያሉትን
ተግዳሮቶች በመለየት የችግሮቹ መንስኤዎችና መፍትሄዎቹን ለማመላከት ተሞክሯል።

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 218


በሀገራችን በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን ለማጠናከርና
ለማስፋፋት የሚያስችሉ ዕድሎች ወይም ምቹ ሁኔታዎች አሉ፡፡ ለምሳሌ፡ መንግስት
ዘርፉን ለማልማት ያለው ቁርጠኝነት፣ የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ መሰረታዊ
የኢንዱስትሪ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች፣ ማበረታቻና ድጋፍ ማዕቀፎች፣ የመሰረተ-ልማት
አቅርቦት ለማሟላት ጥረት እየተደረገ መሆኑ፣ የውጭ ባለሀብት ከጊዜ ወደ ጊዜ
እየጨመረ መምጣቱ፣ ሰፊ የገበያ ዕድል መኖሩ፣ ወዘተ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ መንግስት
የግል ባለሀበቱ በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪው ኢንቨስትመንት በስፋት እንዲሳተፍ
የተለያዩ ማበረታቻዎችን በማቅረብ ጥረት እያደረገ ነው፡፡በመሆኑም ለኢኮኖሚው
ዕድገት ወሳኝና የመሪነት ሚና ያለው የግብርናው ክፍለ-ኢኮኖሚ እንደሆነ የሚታወቅ
ቢሆንም የኢንዱስትሪው ዘርፍም የበኩሉን አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡በተለይ በአንደኛው
የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ውስጥ የተመዘገቡት ውጤቶች ቀደም ሲል
ከነበረው የአምስት አመት የዕቅድ ዘመን አማካይ ጋር ሲነፃፀር የኢንዱስትሪው ዘርፍ
አበረታች መሆኑን ያሳያል፡፡

ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪውን ንዑስ ዘርፍ ለማሳደግ ሰፊ


ጥረት እያደረገ ቢሆንም ነገር ግን የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን በአምራች
ኢንዱስትሪው ልማት የሞተርነት ሚናውን ወይም የዋና ተዋናይነት ድርሻውን
እንዲወጣ ከማድረግ አኳያ የተሰራው ስራ አጥጋቢ ነው ማለት አይቻልም፡፡ በሀገር
ውስጥ የግሉ ሴክተር በኢንዱስትሪው ዕድገት ላይ በሚፈለገው ደረጃ የሚገባውን ሚና
ተጫውቷል ለማለትም አያስደፍርም፡፡ ለምሳሌ የሀገር ውስጥ ባለሀብት
የኢንቨስትመንት ስምሪት ስንመለከት ከ1984-2009 ሩብ አመት ድረስ 78,348
ፕሮጅክቶች የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ ሲሆን
ከዚህ ውስጥ በአምራች ዘርፍ ፈቃድ የወሰዱት 17,519 ፕሮጀክቶች ብቻ ናቸው፡፡
ከ17,519 ፕሮጀክቶች መካከል ደግሞ ወደ ማምረት ተግባር የተሸጋገሩት 1837
(10.44%) ፕሮጀክቶች ብቻ ናቸው፡፡ ከዚህ አንፃር የሀገር ውስጥ ባለሀብት በአማራች
ዘርፍ የመሰማራት ፍላጎቱ አነስተኛ መሆኑ የተሰማራውም ቢሆን በፍጥነት ወደ ትግበራ
አለመግባቱን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለዚህ ችግር በባለሀብቱ እንደምክንያት የሚጠቀሰው
በአብዛኛው መሰረተ-ልማት አለመሟላትና የፋይናንስ ዕጥረት መኖሩን ነው፡፡

በ2007 የበጀት ዓመት የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት የነበረው
ድርሻ 15.1 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህ አፈፃፀም በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 219


የመጨረሻ ዓመት ይደረስበታል ተብሎ ከተያዘው 18.8 በመቶ ግብ አንፃር ጉድለቱ ሰፊ
ከመሆኑ በተጨማሪ አምራች ኢንዱስትሪው ድርሻ አነስተኛ ሲሆን የኮንስተራክሽን
ዘርፍ እድገት ግን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡

በ2007 የበጀት ዓመት የተገኘው 409 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በዕቅድ ዘመኑ መጨረሻ
ሊሳካ ከሚጠበቀው 1.82 ቢሊዮን ዶላር ግብ አንፃር አፈጻጸሙ 22.5 በመቶ ብቻ ነው፡፡
በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪ የተመዘገበው የኤክስፖርት ገቢ 98.1 ሚሊዮን
ዶላር በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ከተያዘው 1 ቢሊዩን የአሜሪካን ዶላር ግብ
አንፃር ሲታይ ከ 10 በመቶ በታች ነው፡፡ በዕቅዱ የትግበራ ዓመታት በንዑስ ዘርፉ
ለ40 ሺህ ዜጐች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ዕቅድ ተይዞ የተሠራ ቢሆንም ማሳካት
የተቻለው የዕቅዱን 50 በመቶ ያህል ብቻ ነው፡፡ በተጨማሪም ባለፉት አምስት
ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች ከቆዳና ቆዳ ውጤቶች እና ሌሎች ኢንዱስትሪ ውጤቶች
ይገኛል የተባለው የውጭ ምንዛሬ እና የዘርፉ እድገት የታቀደውን ያህል አልተሳካም፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪ በጥቅል የሀገር ውስጥ ምርት ላይ ያለው ድርሻ በ1993 ከነበረው
4.3 በመቶ ድርሻ ከ 15 ዓመታት በኋላም 5 በመቶ መድረስ አልቻለም፡፡ የአምራች
ኢንዱስትሪ ዘርፍ በጥቅል የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ አነስተኛ ሲሆን በአንፃሩ
የአግልገሎት ዘርፍ ድርሻ ከፍተኛ እድገት በማስመዝገብ ከ46 በመቶ በላይ ደርሷል፡፡
ይህ የሚያሳየው ሀገራችን ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገው መዋቅራዊ ለውጥ
ይልቅ ከግብርና ወደ አግልግሎት የሚደረግ መዋቅራዊ ለውጥ የቀደመ የሚመስል
ሁኔታ እንዳለ የዘርፎች አፈፃፀም ሪፖርት ያሳያል፡፡

ሌላው በዘርፉ ውስጥ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የሰራተኛ ምርታማነት እ.ኤ.አ በ2005
እሰከ 2013 ያለውን አፈፃፀም ስንመለከት የኢትዮጵያ የስራ ዕድል ፈጠራ በየዓመቱ
3.8 እድገት ያሳየ ቢሆንም የግብርና ዘርፍ አሁንም 72.7 በመቶ የሚሆነው ድርሻ
የሚሽፈን ሲሆን የአገልግሎት ዘርፍ በ34 በመቶ በማደግ በ2005 ከነበረበት 13.1 ድርሻ
በ2013 ወደ 20 በመቶ ድርሻ የሌሎች ኢንዱስትሪዎች ደግሞ 41 በመቶ እድገት
በማሳየት የ3 በመቶ ዕድገት አሳይተዋል፡፡ ነገር ግን የአምራች ኢነዱስትሪ የፈጠረው
የስራ ዕድል ድርሻው 9 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል፡፡ ይህም የአምራች ዘርፉ አፈፃፀም
ማሽቆለቆል እንደማሳያ ሊወሰድ ይችላል፡፡ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ የሰራተኛ
ምርታማነት በ2011/12 ቋሚ የዋጋ ስሌት በ2005 ከነበረው የአንድ ስራተኛ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 220


ምርታማነት 8.9ሺ ብር በየዓመቱ በአማካይ በ5.1 በመቶ ዕድገት በማሳየት በ2013
13.2 ሺ የደረሰ ቢሆንም የአምራች ዘርፍ የሰራተኛ ምርታማነት ግን ከአማካዩ ዕድገት
ያነሰ አፈፃፀም እንደተመዘገበ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

በሌላ በኩል አብዛኛው የአምራች ኢንዱስትሪ በተለያዩ ምክንያቶች ማምረት ከሚችሉት


አቅም በታች (under capacity production) በአማካይ 58% እያመረቱ ነው፡፡ በዋናነት
በባለሀብቶች የተጠቀሱት ምክንያቶች 1) የኤሌክትሪክ ሀይል ማነስና መቆራረጥ፣ 2)
የኢንዱስትሪ ግብአት ችግር (የአቅርቦት ማነስ፣ ከፍተኛ ዋጋ፣ ዝቅተኛ ጥራት)፣ 3)
የውጭ ምንዛሬ ዕጥረት፣ 4) የፋይናንስና ብድር አቅርቦት ችግር (በተለይ ለስራ
ማስኬጃ)፣ 5) የገበያ ችግር፣ 6) የሰራተኛ ብቃት ማነስና በገበያ ላይ አለማግኘት
እንዲሁም 7) የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ናቸው፡፡ በተጨማሪ እነዚህ
ፋብሪካዎች ከአቅም በታች የሚያመርቱበት ዋና ምክንያት የቴክኖሎጂ ማሻሻል
ስለማያደርጉና ብቃት ያለው አመራርና በቂ ክህሎትና ዕውቀት የሌላቸውን
ባለሙያዎች ስለሚጠቀሙ ነው፡፡ ነገር ግን የእነዚህ ችግሮች ሁሉ ዋናው እና ጥቅል
መንስኤው የአመራሩና የባለሙያው የማስፈፀም አቅም ማነስና በሚገባው ልክ በቂ
ትኩረት አለመስጠት ነው፡፡

ስለዚህ የግል ባለሀብቱ ለኢንዱስትሪው ልማትና ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር ወይም ዋና


ተዋናይ እንደሆነ በኢንዱስትሪ ስትራቴጂው በግልፅ ቢቀመጥም ተግባራዊ እንቅስቃሴው
ግን ሰፊ ክፍተት አለበት። ከላይ በምዕራፍ አምስት በስፋት እንደተገለፀው በአምራች
ኢንዱስትሪው የተሰማራው አብዛኛው የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት በብዙ ውስብስብ
ችግሮችና ማነቆዎች ተውጦ መንቀሳቀስ ወደማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡
ከፊሎቹም ከአምራች ኢንዱስትሪ ወጥተው በቀላሉና በአጭር ጊዜ ያለብዙ ድካም
በአቋራጭ ትርፍ ወደሚገኝበት ንግድ፣ ሪል እስቴትና የአገልግሎት ዘርፎች እየኮበለሉ
ነው፡፡ በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማራው አብዛኛው የግል ባለሀብት አጠቃላይ ውስጣዊ
ይዘቱ የሚያሳየው እየተዳከመ መምጣቱንና የተስፋ መቁረጥ ስሜት መኖሩን ነው፡፡
አሁን ሁሉም የሚመለከታቸው የመንግስት አመራሮችና ባድርሻ አካላት ይህ ለምን
እንደሆነ ቆም ብለው ማሰብና መሰረታዊ ለውጥ ማድረግ ያለባቸው ጊዜ ላይ
ተደርሷል፡፡ ከላይ የተገለፁ መሰረታዊ ችግሮችና ማነቆዎች መሰረታዊ መንስኤያቸውን
ስንመለከት በዋናነት፡የአሰራር ክፍተት መኖር፣ የአፈፃፀም ድክመት፣ የአመራሮችና
ባለሙያዎች አቅም ማነስ፣ የአሰራር ስርአት አለመኖር እንዲሁም ተናቦና ተቀናጅቶ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 221


አለመስራት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማራው ባለሀብት ለዘርፉ
ዕድገት የሞተርነት ሚናውን እንዲጫዎት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅዕኖ ያላቸው
ባለድርሻ አካላት ዘርፉን በተፈለገው ደረጃ ለማሳደግ ሁሉም የየራሳቸው ድርሻ
ቢኖራቸውም ድርሻቸውን በመወጣት በኩል በቂ ትኩረትና የተግባር እንቅስቃሴ
እንዳላደረጉ ከላይ በምዕራፍ አምስት ውስጥ በዝርዝር ታይቷል፡፡ የመንግስት አካላት
ለባለሀብቱ በቂ ድጋፍና ክትትል አለማድረግ፣ ለባለሀብቱ የተፈቀዱ ማበረታቻዎች
ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ አለማድረግ፣ የተንዛዛ፣ አድካሚና ውጣውረድ የበዛበት
የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥና ሌሎችም በአምራች ኢንዱስትሪ የባለሀብቱን
እንቅስቃሴ የሚገድቡ አሰራሮች ተከስተዋል።

በሌላ በኩል በ1994 ዓ.ም በወጣው የሀገራችን የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ላይ


እንደተጠቀሰው የሀገር ውስጥ ባለሀብትና የውጭ ባለሀብት ጠንካራና ደካማ ጎኖች
በመመርመር ሁለቱንም ባለሀብቶች አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚያስፈልግ በሰፊው
ያብራራል፡፡ በሰነዱ ላይ እንደተገለፀው የኢንዱስትሪ ስትራቴጂው በዋናነት የሀገር
ውስጥ ባለሀብቱ ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት ይገልፃል፡፡ በተጨማሪም የሀገር
ውስጥ ባለሀብትን እንደዋነኛ ሀይል እንደሚወሰድና ባለሀብቱ የኢንዱስትሪ ዕድገት
ሞተር የመሆን ሚናውን እንዲጫዎት ማስቻል እንዲሁም የባለሀብቱን አቅም
ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ያብራራል፡፡ የግሉ ባለሀብት የኢንዱስትሪ
ልማት ሞተር ይሁን ሲባል የሀገር ውስጥ ባለሀብት ዋነኛው ሀይል የሚሆንበት፣
የውጭው ባለሀብት በሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ላይ በተደራቢነት በሰፊው ተሳታፊ
የሚሆንበት፣ በሁለቱም ድምር አቅም የሀገራችን የኢንዱስትሪ ልማት የሚፋጠንበት
ሁኔታ መፍጠር መሆኑንም ይገልፃል፡፡የውጭ ባለሀብቱ ወደ ሀገራችን ሲገባ የቴክኖሎጂ
ሽግግርን በማፋጠን፣ የማናጅመንት ክህሎትን በማስተላለፍ፣ የገበያ ኔትወርክ
በመፍጠር፣ የኢንዱስትሪ የስራ ባህል በማስፋፋት፣ ከሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ጋር
በጆይንት ቬንቸር (Joint venture) እንዲሰራ በማድረግ፣ ወዘተ የመሳሰሉትን ጥቅሞች
ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱና ለኢኮኖሚው ዕድገት እንዲያበረክት የሚጠበቅ ቢሆንም
በሰፊው አልተሰራበትም፡፡ በሌላ በኩል የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ከላይ እንደተገለፀው
በኢንዱስትሪው ዘላቂ ልማትና ዕድገት ላይ የራሱን ከፍተኛ ሚና እንዲጫወትና ዋናው
አንቀሳቃሽ ሞተር እንዲሆን ይጠበቃል፡፡ ስለዚህ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በዘርፉ
ዘላቂ ዕድገት ላይ ያለው ሚና በዋና ተዋናይነት የሚታይ እንጂ በደጋፊነት የሚታይ
አይሆንም፡፡ በተጨማሪም በውጭ ባለሀብት ላይ የተመሰረተ የልማት ስትራቴጂ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 222


ከተከተልን የካፒታል ክምችታችን ከረጅም ጊዜ አኳያ ማደግ በሚገባው ፍጥነት
እንደማያድግ እንዲሁም የረጅም ጊዜ የኢንዱስትሪ ልማት ዕድገታችን ፍጥነትና
ቀጣይነት ለአደጋ የሚያጋልጥ እንደሆነ በዚሁ ሰነድ ላይ በግልፅ ተቀምጧል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ ከውጭ ባለሀብቱ ተጠቃሚ የምንሆነው የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ተሰፋፍቶና
ተጠናክሮ ሲገኝ ነው፡፡ ምክንያቱም ከውጭ ባለሀብት በዋናነት የቴክኖሎጂ ሽግግር፣
የኢንዱስትሪ አመራር ዕውቀትና ክህሎት ሽግግሩ እንዲፋጠን፣ በውጭ ባለሀብቱ
የሚፈጠረውን የገበያ ኔትዎርከ ለመጠቀም የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በብዛት ተጠናክሮ
መገኘት አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ ከውጭ ባለሀብቱ ማግኘት ያለብንን ጥቅም ማግኘት
አያስችለንም፡፡ በመሆኑም የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ገና ታዳጊ በመሆኑ ወይም
አቅም ስለሌለው ቅድሚያ አይሰጠውም በሚል እሳቤ መዘናጋት እንዳማያስፈልግ
ያመላክታል፡፡

ከላይ እንደተገለፀው በሀገራችን የረጅምና የአጭር ጊዜ ራዕይን ለማሳካት ወሳኝ ከሆኑ


ጉዳዮች አንዱ ጠንካራና ተወዳዳሪ የሆነ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ መገንባት ነው፡፡
የአምራች ኢንዱስትሪ ልማትና ዕድገትን ለማረጋገጥ ፖሊሲዎችን፣ የማስፈፀሚያ
ፕሮግራሞችን እና ልዩ ልዩ ስትራቴጂዎችን ከመንደፍ ባሻገር የኢንዱስትሪ
ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ ራዕይ ያላቸውና ቁርጠኛ የሆኑ አመራሮችና ባለሙያዎች
ያስፈልጋሉ፡፡ የትራንስፎርሜሽን አመራር የሚመሩትን መ/ቤት ራዕይ፣ ግብ እና አላማ
ከሀገራዊ ረዕይና ተልዕኮ ጋር በማስተሳሰር በብቃት ወደ ተግባር መቀየርና ፈጣን ለውጥ
ማምጣትን ይጠይቃል፡፡ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ ከላይ
እንደተገለፀው ጠንካራ የመንግስት አመራር እና ጣልቃገብነት ይፈልጋል፤ እስካሁን
እየተሰራበት ከነበረው የአሰራር ዘይቤ (ከተለመደው አካሄድ) በመውጣት ወይም በተለየ
አካሄድ መስራትን ይጠይቃል፤በአምራች ኢንዱስትሪው ለተሰማራው የሀገር ውስጥ
ባለሀብት የተለየ ትኩረት መስጠትን ይጠይቃል፡፡

በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ድጋፍ የሚሰጡ ተቋማት አመራሮችና


ባለሙያዎች የማስፈፀም አቅም ውስንነት ጎለቶ ይታያል፡፡ ከፌደራል እስከ ክልል
ወረዳዎች ድረስ ያለው የኢንዱስትሪ አመራርና ባለሙያ በሀገሪቱ የኢንዱስትሪ
ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ የጠራ ግንዛቤና ተግባቦት አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡
በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና ፈጻሚ አካላት በኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ
ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ጨብጦ ወደ ስራ ከመግባት አንጻር ሰፊ ክፍተቶች አሉ፡፡ በመሆኑም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 223


የኢንዱስትሪ አመራሩና ባለሙያው አሁን ያለበት የአቅም ክፍተት ለመሙላት
ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና ያስፈልገዋል፡፡

የኢንዱስትሪ አመራሩንና ባለሙያውን አቅም መገንባት ማለት በአምራች ኢንዱስትሪ


የተሰማራውን የግል ባለሀብት የአቅም ክፍተት (የዕውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት)
መሙላት ወይም መገንባት ማለት ነው፡፡ የባለሀብቱ አቅም በሂደት እየተገነባ ከሄደ
ደግሞ ተወዳዳሪ ይሆናል፡፡ ስለዚህ አዳዲስ ባለሀብቶችን ወደ አምራች ኢንዱስትሪው
ለመሳብ እንዲሁም ቀድመው በዘርፉ የተሰማሩትን ባለሀብቶች አቅም ለመገንባት
ብቃት ያለው አመራርና ባለሙያ በስፋት ማፍራት ቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት፡፡

የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በመጠንም ሆነ በዓይነት እድገት አሳይቷል፡፡


ከዚህ ጋር ተያይዞ በሀገራችን የቁጠባ ባህል እያደገ ቢመጣም ከሰሃራ በታች አማካይ
የቁጠባ መጠን ያነሰ መሆኑ፣ የባንኮች ተደራሽነት እና የማበደር አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ
እየጨመረ ቢመጣም የሀገራችን ፋይናንስ ፍላጎት ሊያሟላ በሚችልበት ቁመና ላይ
አለመሆኑን በዚህ ጥናት ለመገንዘብ ተችሏል። የሀገራችን የፋይናንስ ፍላጎት እና
አቅረቦት ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ ከመምጣቱ በተጨማሪ የፋይናንስ ፍሰቱ
በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራው የግል ባለሀብት በሚፈለገው ደረጃ
ተጠቃሚ ያደረገ እንዳልሆነ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የባንኮች የብድር
ወለድ መጣኔ በአንድ በኩል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአጠቃላይ ዘርፍ ያለየ መሆኑ
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የወለድ መጣኔ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
አገልግሎትን ጨምሮ ለሁሉም ዘርፍ ከሚሰጠው የወለድ መጠን የበለጠ መሆኑ እና
በአምራች ዘርፉ ውጤታማ ከሆኑ የምስራቅ ኤስያ ሀገራት አንፃር ከፈተኛ መሆኑ
ታይቷል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የባንኮች የብደር አገልግሎት አሰጣጥ ውስብስብ፣
የተንዛዛና ውጣውረድ የበዛበት እና ለብልሹ አሰራር የተጋለጠ መሆኑ ነው፡፡ሌላው
መታየት የሚገባው ጉዳይ የውጭ ምንዛሬ ችግር ከሁለት መሰረታዊ ችግር የሚመነጭ
መሆኑ በአንድ በኩል በአቅርቦትና ፍላጎት መካከል የተፈጠረ ልዩነት የሚመነጭ ሲሆን
በሌላ በኩል የውጭ ምንዛሬ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ የሚመጣ አፈፃፀምና ዘርፍ ያለየ
አመዳደብና በቁጠባ ያለመጠቀም ችግር ነው፡፡

ለአምራች ኢንዱስትሪ እየቀረበ ያለው ማበረታቻ የግሉ ዘርፍ የቢዝነስ ስምሪት


አምራች ዘርፍ እንዲሆን ማድረግ ያላስቻለ፣ የዘርፉን መዋቅራዊ ለውጥ በሚያረጋግጥ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 224


አቅጣጫ ያልተቃኘ መሆኑ የግሉ ባለሀብት ፊቱን ከአምራች ይልቅ ወደ አገልግሎት፣
ንግድና ሪል እስቴት ዘርፍ ማዞሩን ለመገንዘብ አያዳግትም፡፡ ለምሳሌ ከተለያዩ ሀገራት
ልምድ እና ከሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ስንመለከት የሀገራችን የገቢ ግብር ምጣኔ
ለሁሉም ዘርፍ እኩል 30 በመቶ መሆኑ ዳግም መፈተሸ የሚገባው ነው፡፡ ለአምራች
ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚቀርበው ማበረታቻና ድጋፍ ተወዳዳሪነቱን በሚያጎለብት ሁኔታ
ካለመቅረቡ በተጨማሪ ለጥገኛ ባለሀብቶች መጠቀሚያ የመሆን አዝማሚያ እየታየበት
መሆኑ፣ የተፈቀደ መብትም ጭምር በቀላሉ የማይገኝ፣ ለብልሹ አሰራር የተጋለጠ፣
ከአምራቹ ይልቅ ለአስመጪዎች የተመቸ መሆኑ፣ ከውጤት ጋር በተገቢው መንገድ
ያልተሳሰረ መሆኑና ማበረታቻዎች ለታለመላቸው ዓላማ ስለመዋላቸው ሀላፊነት ወስዶ
የሚከታተልና እርምጃ የሚወስድ አካል በግልፅ አለመለየቱ መሰረታዊ ችግሮች ናቸው፡፡

በሀገራችን የግብርና ውጤቶች በተለይ ለአምራች ኢንዱስትሪው በበቂ አቅርቦት፣


በጥራትና ተወዳዳሪ በሆነ ዋጋ እየቀረበ አለመሆኑን በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ
ባለሀብቶቸ እና የክልል ግብርና ቢሮዎች ይገልፃሉ፡፡ በተለይ ትኩረት የተሰጣቸው
አምራች ኢንዱስትሪዎች (የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ፣ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች
ኢንዱስትሪ፣ አግሮፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪና ሌሎችም) በዋናነት የግብርናውን ምርት
በግብአትነት የሚጠቀሙ መሆናቸው የሚታወቅ ቢሆንም የግብአት ፍላጎታቸውን
ከማሟላት አኳያ ሰፊ ክፍተት አለ፡፡ በአጠቃላይ የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦቱ
እንዳይሳለጥ ካደረጉት ዋና ዋና ምክንያቶች መካከል አርሶአደሩ ባለችው ጠባብ ማሳ
ላይ ገበያ ተኮር ሆኖ፣ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ ባለማምረቱና
ምርታማነቱም በሚፈለገው ደረጃ ባለመጨመሩ፣ ባለሀብቶች በሰፋፊ እርሻዎች በስፋት
አለመሰማራታቸውና የተሰማሩትም በቂ ምርት ባለማምረታቸውና ምርታማነታቸውም
ከአርሶአደሩ ማሳ ምርታማነት የተሻለ አለመሆኑ፣ ረጅምና እሴት የማይጨምር
የግብይት ሰንሰለት መፈጠሩና የገበያ ስርአቱ በውድድር እንዳይመራ ማድረጉ፣
ለኢንዱስትሪ ግብአቶች ባህሪ የሚመጥን የሎጂስቲክስ መሰረተ-ልማት አለመኖር እና
አርሶአደሩ ወይም በግብርና የተሰማራው ባለሀብት ላመረተው ምርት ተገቢ የሆነ ዋጋ
እና ቀጣይነት ያለው እንዲሁም አስተማማኝ ገበያ ያለማግኘቱ በዋናነት ሊጠቀሱ
የሚችሉ ምክንያቶች ናቸው፡፡

ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የገበያና ንግዱ ስርአት ቀልጣፋ፣ ውጤታማ እና ፍትሃዊ


ከማድረግ አኳያ ሲፊ ጉድለቶች እንዳሉት ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ ጥራትና ደረጃውን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 225


ያልጠበቀ ምርት (በተለይ በገቢ- ምርት) በገበያ ላይ መበራከት ህግና ስርአት ተከትለው
በሚያመርቱ አምራቾች እድገት እና ተወዳዳሪነት ላይ ማነቆ እየሆነ ይገኛል፡፡
በተያያዥ የኮንትሮባንድ ንግድ፣ በአስመጭዎች የሚደረግ የተዛባ እና የተጋነነ ምርት
ማስተዋወቅ እንዲሁም ምንጫቸው ያልታወቀና ተመሳስለው የሚመረቱ ምርቶች በገበያ
ላይ ተገቢ ያልሆነ ውድድር (unfair competition) ሲፈጥሩ ይስተዋላል፡፡ ሌላው
ከአለማቀፍ ገበያና ንግድ የሚመነጩ ቀጥተኛ ተፅዕኖዎች መለትም ፍትሃዊ ባልሆነ
ዝቅተኛ ዋጋ በሀገር ውስጥ ገበያ መሸጥ (dumped products) ለመከላከል በባለቤትነት
የሚንቀሳቀስ አካል እና የህግ ማእቀፍ ባለመኖሩ ኢንዱስትሪው አልፎ አልፎ ለሚፈጠሩ
መሰል ችግሮች የመጋለጥ አዝማሚያዎች አሉ፡፡ በተጨማሪ የመንግስት የግዥ
የልማታዊ መንግስት የግዥ ስርአት ባለመላበሱ ከሀገር ውስጥ ምርት ይልቅ
ለአስመጭዎችና ለውጭ ሀገር ተጫራቾች የወገነ ያሰመስለዋል፤ ግልፅነት የጎደለው
አድሏዊ አሰራር የሚስተዋልበትም ሆኗል፡፡ የግዥ ስርአቱ በስፔስፊኬሽን እና ጨረታ
ግምገማ ላይ በሚደረግ የቡድን ሴራ የግዥ ባለሙያዎችና የጨረታ ኮሚቴ እንዲሁም
ቴክኒካል ግምገማ የሚያካሂዱ ባለሙያዎች የፈለጉትን የሚያሳልፉበት እና አቤቱታን
የሚያፍኑበት ሁኔታ መለመዱ የግዥ ስርአቱ ከልማታዊ ባለሀብቱ ይልቅ ለኪራይ
ሰብሳቢው አካል ማበልፀጊያ እየሆነ ይገኛል፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራው የሀገር ውስጥ ባለሀብት በተሰማራበት የስራ ዘርፍ


በአለማቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ከሚያስችሉት ጉዳዮች አንዱ ተስማሚ የሆነ
የቴክኖሎጂ አቅርቦት ማመቻቸት እና ተጠቃሚ ማድረግ ነው፡፡ የሀገራችን ሁለንተናዊ
ልማት የሚጠይቀው የቴክኖሎጂ ግብአት በተለይ ኢንዱስትሪው በማቆጥቆጥ ላይ ያለና
ጀማሪ በመሆኑ ቅድሚያ ትኩረት የተሰጠው የቴክኖሎጂ ኩረጃ ነው፡፡ በተለይም
በአምራች ኢንዱስትሪው የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ቢያንስ ሁለት መሰረታዊ
ችግሮች ይስተዋላሉ፡፡ አንደኛው ቴክኖሎጂውን መቅሰም የሚችል ብቁ የሰው ሀይል
በብዛት አለመኖር ሁለተኛው ደግሞ አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ የተሰማራው
አብዛኛው የሀገር ውስጥ ባለሀብት ለአዳዲስ ቴክኖሎጂዎችና አሰራሮች በሩን ክፍት
አለማድረጉ ነው፡፡ በሌላ በኩል በሀገራችን ሁሉንም አካላት የሚያስተሳስር የተቀናጀ
አጠቃላይ የቴክኖሎጂ ስርአት አልተዘረጋም፡፡ የቴክኖሎጂ ሽግግር ምንጩ የሽርክና
(Joint venture) ኢንቨስትመንት፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት፣ የወሳኝ ፕሮጀክቶች
ኮንትራክት እና የማኔጅመንት ኮንትራት እንደሆኑ ተለይተዋል።ነገር ግን የቴክኖሎጂ
ሽግግር እንቅስቃሴው አጥጋቢ ያልሆነ እንዲሁም አሁን ያለበትን ሁኔታ በሚገባ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 226


ገምግሞ ያላስቀመጠና በትክክል ወደ ተግባር መግባቱም ያልተረጋገጠ እንደሆነ
በየደረጃው የሚገኙ ኢንቨስትመንትንና አምራቹን ዘርፍ የሚመሩ የመንግስት
አስፈፃሚና ፈፃሚ አካላት እንዲሁም በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ይገልፃሉ፡፡

ለአምራች ኢንዱስትሪው ያሉበትን የምርት ጥራትና ምርታማነት፣ የቴክኖሎጂ


አመራረጥና አጠቃቀም፣ የአሰራርና የአመራረት ዘዴ፣ የሰለጠነ የሰው ሀይልና የገበያ
ትስስር ችግሮች ለመፍታትና ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማገዝ ስድስት የሚሆኑ የልማት
ኢንስቲትዩቶች ተቋቁመዋል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ኢንስቲትዩቶች ያሉበት ደረጃ ሲታይ
ቀደም ብለው የተቋቋሙትን ጨምሮ ብቃት ያለው የሰው ሀይል ያልያዙና የጥራትና
የአመራር ችግር ያለባቸው በመሆኑ በዓለማቀፍ ደረጃ በተመሳሳይ ተቋማት ከሚሰጡ
አገልግሎቶች ሊመጣጠን የሚችል ድጋፍ የመስጠት አቅም አልገነቡም፡፡ በዚህም
ምክንያት አምራች ኢንዱስትሪዎች በቂ ድጋፍ እየተደረገላቸው አይደለም፡፡ የልማት
ኢንስቲትዩቶች የሚሰጡት ድጋፍ ከንድፈ-ሐሳብ ያልዘለለና አምራቹ ላጋጠመው ችግር
አጋዥ እንዳልሆነ ይገልፃሉ፡፡በአጠቃላይ የሚሰጡ ድጋፎች በበቂ ክህሎትና ዕውቀት
ላይ ያልተመሰረቱ እንዲሁም መሰረታዊ ለውጥ የማያመጡና ተደራሽነታቸውም ጠባብ
ነው። ከዚህ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዮቶች ከተቋቋሙበት ተቀዳሚ
ዓላማ ወጥተው የፋሲሊቴሽን ስራ ላይ የተጠመዱ መሆኑ፤ እንዲሁም በኢንስቲትዩቶች
ያሉት ተመራማሪዎች አቅምና ተነሳሽነት ማነስ ይስተዋላል፡፡

በሀገራችን ያሉ የሎጂስቲክስ ተቋማት ኢኮኖሚው የሚጠይቀውን አገልግሎት ለመስጠት


በአደረጃጀት እና በአሰራር ስርዓት ውጤታማ አለመሆን ይስተዋላል፡፡ በዚህ ረገድ
የገቢዎች እና ጉምሩክ ሆነ ሌሎች መሰል ተቋማት አሰራር ዓለማቀፍ ደረጃውን
የተጠበቀ በቴክኖሎጂ የዘመነ አሰራር “እየሰራን ነው” ከማለት የዘለለ በተጨባጭ
ለማዘመን የሚደረገው ጥረት ደካመ ነው፡፡ ዘመናዊ የመፈተሻ መሰሪያዎች ለዓመታት
መቆማቸው፣ የጉምሩክ መረጃ ስርዓት ከጁቡቲ አቻቸው ጋር መዋሃድ በዘመናዊ
የተቀናጀ የመረጃ ስርዓት ባለማደራጀቱ አሰራሩ የተንዛዛ እና አላስፈላጊ ወጪ እየዳረገ
መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ምርምር ተቋም በዚህ ዘርፍ የደረገው ጥናት ያሳያል፡፡ የህግ
ማስከበሩ ስራ ባለመዘመኑ እና በተቀናጀ እና በተሟላ መንገድ ሰለማይሰራ (ያዝ ለቀቅ
የበዛበት በመሆኑ) የጉምሩክ አሰራር ለአምራቾች ሳይሆን ለአስመጪዎች እና
ኮንትሮባንዶች የተመቸ ሆኗል፡፡ በሌላ በኩል የመርከብ፣ ደረቅ ወደብና የማሪታይም
ድርጅት በአሰራርም ይሁን በአመራር ለአምራች ዘርፍ ተወዳደሪነት አጋዥ እየሆነ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 227


አይደለም፡፡ ጭነት በየሀገራቱ ወደቦች ለረጂም ጊዜ መቆየቱ ሀገሪቱ ለአላስፈላጊ ወጪ
እና የውጭ ምንዛሬ ብክነት ከማጋለጡም በላይ ለአምራች ግብአት ወጪ በማሻቀብ
ተወዳዳሪ እንዳይሆን አድርጎታል፡፡የመልቲ ሞዳል ሲስተም ቢሆን በአንድ በኩል
ከዩኒሞዳል በላይ የወጋ ብልጫ ያለው በመሆኑ በሌላ በኩል የተሟላ የዘመናዊ
ቴክኖሎጂን የሚፈልግ በመሆኑና ዘመናዊ አሰራር ለመተግበር ባለመቻሉ የታሰበው
ያህል ውጤት ሊያመጣ አልቻለም፡፡

እ.ኤ.አ በ2010 ከኢትዮጵያ ያነሰ አፈፃፀም የነበራት እና አብዛኛው የየብስ


ትራንስፖርት ከሀገርዋ ውጪ የምትፈፅመው ሩዋንዳ በዘርፉ በሰራቻቸው ተጨባጭ
ለውጦች ውጤት ማስመዝገብ የቻለች ሲሆን በአንፃሩ ኢትዮጵያ ከ80 በመቶ በላይ
የትራንዚት ስራዎች በራሷ ሀገር ውስጥ የሚፈፀም መሆኑ ነው፡፡ በተመሳሳይ የአፍሪካ
አማካይ ከ31-37 ቀናት መሆኑ ጥናቱ ያሳያል (የዓለም ባንክ ጥናት, 2014)፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ አንድ ኮንቴነር ከወደብ ወደ መሃል ሀገር ለማስገባት በኢትዮጵያ ከፍተኛ
ውጭ የሚጠይቅ ከመሆኑ በላይ በታንዛንያ እና ኬንያ ከሚያስወጣው ወጪ ከ1000-
2000 የአሜሪካ ደላር የበለጠ የሚያስወጣ መሆኑ፣ የጉምሩክ ክሊራንስ ለመጨረሽ
በኢትዮጵያ 103 በላይ ደረጃዎች የሚያልፍ እና ከ21 በላይ ዶክመንቶች የሚጠይቅ
መሆኑ በአጠቀላይ በሀገራችን የውጭ እና ገቢ ንግድ ስራዎች ከቤትናም፣ ቻይና እና
ኬንያ አንፃር ከሁለት እጥፈ በላይ ጊዜ እና ወጪ የሚጠይቅ መሆኑ ለመገንዘብ
ተችሏል፡፡ ቀላል ኢንዱስትሪዎች በአፍሪካ (LIGHT MANUFACTURING IN
AFRICA) በሚል የአለም ባንክ ጥናት ከላይ የተቀመጠው ሀሳብ ያጠናክራል፡፡ባለ 20
ጫማ ኮንተኔር በጅቡቲ ለማስተናገድ 600 የአሜሪካ ዶላር ድረስ የሚያወጣ ሲሆን
በአንፃሩ በቻይና ከ80 የአሜሪካ ዶላር እንደማይበልጥ፣ በጉምሩክ የሚወስደው ጊዜ
በኢትዮጵያ 25 ከቻይና ተመሳሳይ አገልግሎት አንፃር 25 ተጨማሪ ቀናት እንደሚፈጅ
ይህም በኢትዮጵያ ያለው ተነፃፃሪ አነስተኛ የሰራተኛ ዋጋ ጥያቄ ውስጥ ሊያስገባ
እንደሚችል ጥናቱ ያሳያል፡፡

በዚህ ዓይነት የተንዛዛ እና ከፍተኛ ወጪ የተጋለጠ የሎጁስቲክስ ስርዓት የኢትዮጵያ


አምራች ዘርፍ በዓለም ገበያ ይቅርና በሀገር ውስጥ ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን
እንደሚቸገር መገንዘብ ይቻላል፡፡ኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ አሰራር ለማዘመን ዘርፈ ብዙ
ስራዎች እየተሰሩ ቢሆን አሁንም ድረስ ችግሩን ከምንጭ ለመፍታት የሚያስችል
አለመሆኑ የቅርበ ዓመታት መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ለምሳሌ የዓለም ባንክ 2016 የቢዝነስ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 228


አሰራር ሪፖርት (Doing Business 2016) በዓለም አቀፍ ንግድ ትስስር አሰራር ጋር

የተያያዘ የጉምሩክ፣ ትራንስፖርት እና ዶክመንት አሰራር በተመለከተ ከ190 ሀገራት


ከግማሽ በታች ውጤት በማስመዝገብ 176 ደረጃ ከመያዝዋ በተጨማሪ ከከፊል ሰሃራ
ሀገራት አማካይ ውጤት ያነሰ አፈፃፀም አስመዝግባለች፡፡ በአንፃሩ ጎሮቤቶቻችን ሩዋንዳ
111ኛ፣ ኬንያ 151ኛ፣ ኡጋንዳ 168ኛ በመውጣት ከኢትዮጵያ የተሻለ ደረጃ
አስመዝግበዋል፡፡ ይህ ተመሳሳይ የዓለም ባንክ ሪፖርት ከአንድ ዓመት ቡኋላ በ2017
የቢዝነስ አሰራር ሪፖርት (Doing Business 2017) ኢትዮጵያ ዘጠኝ ደረጃዎች

በማሻሻል 167 ደረጃ ያገኘች ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሩዋንዳ 24 ደረጃዎች


በማሻሻል 87ኛ፣ ኬንያ 46 ደረጃዎች በማሻሻል 105ኛ፣ ኡጋንዳ 32 ደረጃዎች በማሻሻል
136ኛ በመውጣት ከኢትዮጵያ የተሻለ ደረጃ አስመዝግበዋል፡፡ ከዚህ ለመረዳት
እንደሚቻለው የኢትዮጵያ የውጭ እና ገቢ ንግድ በጊዜም ሆነ በውጪ በዓለም
ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል የሎጅስትክና ትራንሰፖርት አሰራር ችግሩን ለመቅረፍ
ካለመቻሉ በተጨማሪ የሚሰሩ ማሻሻያዎች ዘገምተኛ እና ስርነቀል ለውጥ ለማምጣት
የማያስችሉ መሆናቸው እንዲሁም የአምራች ዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆን የማያስችለው
ሁኔታ መፈጠሩን መገንዘብ ተችሏል።

በአጠቃላይ በአምራች ኢንዱስትሪ የግል ባለሀብቱን በሚመለከት በጥንካሬና በድክመት


የተከናወኑ ተግባራት ላይ እንዲሁም ያልተሰሩ ስራዎችን በጥናታችን ለማመላከት
ተሞክሯል፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ የግል ባለሀብቶችን የሚያግዙ ስትራቴጂዎች፣
መመሪያዎች፣ ህጎች፣ ደንቦችና ሌሎች ሪፎርሞች የተዘጋጁ ቢሆንም በተቀመጠላቸው
አቅጣጫ በቁርጠኝነት መተግበር ላይ ሰፊ ክፍተቶች ተስተውለዋል፡፡ በመሆኑም ከላይ
የተጠቀሱ ችግሮችንና ማነቆዎች ለመፍታትና በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ
የግል ባለሀብቱን ለማጠናከር የፖሊሲና የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች ቀርበዋል፡፡ እነዚህ
ምክረ-ሀሳቦች የቀረቡት በመረጃ ትንተና እና ግኝቶች እንዲሁም በተዛማጅ ጥናቶች
ዳሰሳ የታዩ ተጨባጭ ጉዳዮችን ግምት ውስጥ በማስገባት እና አሁን በአምራች
ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ ያለበትን ሁኔታ በመገንዘብ ነው፡፡ የፖሊሲ
ምክረ-ሀሳቦች በዋናነት ከዚህ በፊት በነበሩት ፖሊሲዎች ላይ የማሻሻያ ሀሳቦች የቀረቡ
ሲሆን በፖሊሲ ማዕቀፍ የሚታዩና ትልቅ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል የተባሉት ጉዳዮች
በክፍል 8.2 ቀርበዋል፡፡ የቀረቡት የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦች በሚመለከታቸው የመንግስት
መ/ቤቶችና ተቋማት በጥናት ላይ የተመሰረተ ተጨማሪ ዝርዝር የፖሊሲና ስትራቴጂ
አፈፃፀም መመሪያዎችና ደንቦችን ማዘጋጀት የሚጠይቁ ናቸው፡፡ከዚህ በተጨማሪ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 229


በፖሊሲ ማዕቀፍ ያልተካተቱና በዋናነት የአሰራር ክፍተት፣ የአፈፃፀም ድክመት፣
የአሰራር ስርአት ችግርና በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ለተስተዋሉ ችግሮችና
ማነቆዎች በክፍል 8.3 ላይ የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች ቀርበውላቸዋል፡፡ የቀረቡት
የፖሊሲና መፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራው የሀገር ውስጥ
የግል ባለሀብት በዘርፉ የሞተርነት ሚናውን ከመጫዎት አኳያ ያሉበትን መሰረታዊ
ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉና አቅም ያላቸውን አዳዲስ የሀገር ውስጥ
የግል ባለሀብቶችን ደግሞ ወደ አምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ሊስብ እንደሚችል
ይታመናል፡፡ ስለዚህ ባለድርሻ አካላት በአምራች ኢንዱስትሪ የግል ባለሀብቱ
ለተስተዋሉ ችግሮችና ማነቆዎች የቀረቡ የፖሊሲና መፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች ግምት
ውስጥ በማሰገባት የድርሻቸውን ወስደው ደረጃ በደረጃ ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጡ እና
በቀጣይ አፈፃፀማቸውን መከታተልና ወቅታዊ የአፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ
ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 230


8.2 የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦች

የኢንዱስትሪ ልማት ጉዞ ውስብስብ እና ተፃራሪ ፍላጎት ያላቸውን በርካታ ባለድርሻ


አካላትን የሚያካትት በመሆኑ የመንግስትን የመምራት አቅምና የመሪነት ሚና
የሚጠይቅ፣ የመንግስት ቁርጠኝነትና ተጠያቂነትን በእጅጉ የሚሻ እንዲሁም
ከተለመደው የአመራር ዘይቤ በመውጣት በትጋት ካልሰራ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ
ልማት የሚደረገውን መዋቅራዊ ሽግግር ለማረጋገጥ አስቸጋሪ እንደሚሆን ብዙ ጥናቶች
ይጠቁማሉ፡፡ በዘርፉ ስኬታማ የሆኑ ሀገራት ተሞክሮ የሚያስተምረን እንደዚህ አይነት
ውስብስብ ዘርፍ ላይ መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት ግልፅ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲና
ስትራቴጂ ከማዘጋጀት በተጨማሪ በየደረጃው ያሉ ሁሉም የመንግስት አመራር አካላት
በፖሊሲው ይዘትና አተገባበር ላይ በቂ ግንዛቤ በመያዝ ከፍተኛ ሚና በመጫወታቸው
እንደነበር ከታሪካቸው ለመረዳት ይቻላል።

የኢንዱስትሪ ፖሊሲ በሁለት ተከፍሎ ሊታይ ይችላል፡፡ የመጀመሪያው አይነት


የአምራች ኢንዱስትሪ ስምሪት እና የቢዝነስ ሁኔታዎች ለማሻሻል ያለመ የኢንዱስትሪ
ፖሊሲ (Functional Industrial Policy) ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ለፈጣንና ተከታታይነት
ያለው የኢኮኖሚ ልማትና ዕድገት ትልቅ ፋይዳ ባላቸው ውስን የተመረጡ ዘርፎችን
ለይቶ ለማሳደግ ያለመ የመንግስት ጣልቃ ገብነትና ድጋፍ የሚጋብዝ (Selective
industrial policy) ነው፡፡ ፋንክሽናል (Functional Industrial Policy) የኢንዱስትሪ
ፖሊሲ ገበያው በተወሰነ መልኩ መስራት በሚጀምርበት ጊዜ ገበያው በራሱ እንዲሄድ
የሚያግዝ እና ቁጥብ የሆነ ጣልቃ ገብነት የሚጋብዝ የፖሊሲ ስርዓት ነው፡፡ በዋናነት
የመሰረተ ልማቶች በማመቻቸት፣ የገበያ ጉድለት ባለባቸው ገበያው ውስን ጣልቃ
ገብነት እና ድጋፍ ካገኘ ሊሰራ ይችላል ከሚለው ቅኝት የሚወጣ ፖሊስ በመሆኑ
ለታዳጊ ሀገራት መሰረታዊ መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት ብዙም ውጤታማ ሲሆን
አልታየም፡፡ ይህ የፖሊሲ ቅኝት በላቲን አሜሪካ ተሞክሮ መሰረታዊ መዋቅራዊ ለውጥ
ማምጣት ያልቻለ መሆኑ በተግባር ታይቷል፡፡

በርካታ የበለጸጉ ሀገራት ተሞክሮ የሚያሳየው ያለ አምራች ኢንዱስትሪ ዕድገት የስራ


ዕድል መስፋፋት፣ የገቢ እድገት፣ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እና የሀገር ብልፅግናን
ማረጋገጥ ፈፅሞ እንደማይቻል ያሳያሉ፡፡ በኢንዱስትሪ ልማት ምርጥ ተሞክሮ ያላቸው
የምስራቅ ኤስያ (ጃፓን፣ ኮሪያና ታይዋን) ልማታዊ መንግስታት የተመረጡ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 231


የኢንዱስትሪ ፓሊሲ አቅጣጫዎች መከተላቸው ለስኬታቸው እንደ ዋነኛ ምክንያት
ይጠቀሳል፡፡ እነዚህ ሀገራት የኢንዱስትሪያላይዜሽን ሂደት (industrialization process)
ለማቀጣጠል ተግባራዊ ካደረጓቸው መካከል ዋና ዋናዎቹን ስንመለከት፡ የተመረጡ
ዘርፎችን የሚደግፉ ፓሊሲ (selective industrial strategy/policy)፣ የንግድ ፓሊሲ
ሪፎርም (trade policy reform) እና የኢንቨስትመንት ፓሊሲ (investment policy)
ናቸው፡፡

ሀገራቱ ስትራቴጅካዊ ጥቅም ያላቸውን ወይም ቅድሚያ የተሰጣቸውን ዘርፎች እና


ኢንተርፕራይዞች ላይ የተመረጡ የኢንዱስትሪ ፓሊሲ እርምጃዎችን (selective
industrial policy) ተግባራዊ በማድረግ የመቆጣጠር፣ መምራትና መደገፍ ስራ በስፋት
መስራታቸው ይታወቃል፡፡ የሀገር ውስጥ አምራቾችን ከውጭ ሀገር ኢንዱስትሪዎች
ተፅዕኖ መጠበቅ (በሀገር ውስጥ ገበያ እንዳይሸጡ በመገደብ፣ ምርትን ኤክስፖርት
የማድረግ አስገዳጅ አሰራር በማስቀመጥ፣ ለሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ለተመረጡ ዘርፎች
እንዳይሳተፉ ማድረግ፣ ወዘተ)፣ የፋይናንስ ድጋፍ ለተመረጡ ዘርፎች በመስጠት
(የብድር ዱጎማ፣ የምርት ድጎማ፣ የግብር ድጎማ፣ የኤክስፖርት ድጎማ፣ ወዘተ)፣ ልዩ
የገበያ ፈቃድ (preferential market licensing) በማዘጋጀት፣ የኢንዱስትሪ ሽግግር/
ለውጥ ድጋፍ በመዘርጋት፣ የሰው ሃይል ስልጠና አቅም ግንባታ ድጋፍ በማቅረብ እና
በመሳሰሉት ድጋፎችን ተደራሽ ያደርጉ ነበር፡፡

በተጨማሪ ሀገራቱ የተመረጡ ዘርፎችን ለመደገፍ የተለያዩ የኤክስፖርት እና


ኢምፖርት ንግድ ፓሊሲ (trade policy) እርምጃዎች በአግባቡ በመተግበር ስኬታማ
ውጤት እንዲያስመዘግቡ አግዟቸዋል፡፡ ከንግድ ፓሊሲ ውስጥ አንድ የኢምፖርት
ቀረጥ ሲሆን ይህ ፓሊሲ ከገቢ ምርት የሚመነጭ ውድድር ተፅዕኖን ለመቀነስ ብሎም
የኢንዱስትሪ ግብአቶችን (ካፒታል፣ መለዋወጫና ጥሬ እቃ) በቀላሉ ኢምፖርት
ለማድረግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሮላቸው ነበር፡፡ ሁለተኛው ቀረጥ ነክ ያልሆኑ እርምጃዎችን
የሚመለከት ሲሆን ገቢ ምርቶችን ፈጽሞ ማገድ፣ ቁጥራቸውን መወሰን፣ የገቢ ምርቶች
በገበያ ላይ ድንገተኛ ጉዳት መከላከል (safeguard measures)፣ የኢምፖርት ላይሰንስ
እና ተያያዥ ፓሊሲ ማእቀፎችን መጠቀም ችለዋል፡፡ በተመሳሳይ የሀገር ውስጥ ምርት
ላይ ያተኮረ የመንግስት ግዥ፣ የውጭ ምንዛሬ ቁጥጥርና ክትትል እና የምንዛሬ ተመን
እንደ ቀረጥ-ነክ ያልሆኑ የኢምፖርት ፓሊሲ እርምጃዎች በጥንቃቄ ተግባራዊ ማድረግ
ችለዋል፡፡ ሶስተኛው የኤክስፖርት ማስፋፋት ፓሊሲ ሲሆን ይህም የኤክስፖርት ንግድ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 232


የማስፋፊያ ኤጀንሲዎችን ማደራጀት፣ ኤክስፖርት ፋይናንስ እና ዋስትና፣ የኤክስፖርት
ጥራት ቁጥጥር እና የኤክስፖርት ፕሮሰሲንግ ዞኖችን መገንባት እና ተያያዥ ጉዳዮችን
ይመለከታል፡፡ የምስራቅ ኤሲያ ሀገራት የንግድ ፓሊሲዎች ተመጋጋቢ በሆነ ሁኔታ
ለኢንዱስትሪ አብዮት ማቀጣጣያነት በመጠቀም ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል።

ሌላው የምስራቅ ኤሲያ ሀገራት የፓሊሲ ትኩረት ኢንቨስትመንት ፖሊሲ (investment


policy) ነበር፡፡ ሀገራቱ የሀገር ውሰጥ እና የውጭ ኢንቨስትመንት በተናጠልም ሆነ
በጥምረት የሚያስፈልጋቸውን ንኡስ ዘርፎችን በመወሰንና በመምራት እንዲሁም
የፋይናንስ ድጋፍ በማመቻቸት የኢንዱስትሪው ክፍለ ኢኮኖሚ እድገት በአጭር ጊዜ
ቁልፍ ሚና እንዲኖረው አድርገዋል፡፡ በምስራቅ ኤሲያ የውጭ ኢንቨስትመንት ጥብቅ
ቁጥጥር የሚደረግበት ከመሆኑ አንጻር ቴክኖሎጅ የማሸጋገር፣ የሀገር ውስጥ ግብአት
የመጠቀም (local content)፣ በሽርክና የመደራጀት (joint venture) እና ኤክስፖርት
ላይ የማተኮር ግዳጅ ይጣልበት ነበር፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በውሉ መሰረት ግዳጁን
ያልተወጣ የውጭ ባለሀብት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወስዱ ነበር፡፡

በኮሪያ፣ ጃፓን እና ታይዋን በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ጠንካራ የሀገር ውስጥ


ባለሀብት እንዲፈጠር ካደረጉት ዋና ምክንያቶች ውስጥ፡ የገበያ ከለላ እና የነፃ ገበያ
ውድድርን ጎን ለጎን እንደ አስፈላጊነቱ ተግባራዊ ማድረጉ፣ ንፅፅራዊ ብልጫ ባላቸው
በተመረጡ የኢንዱስትሪ ንኡስ ዘርፎች ላይ ቅድሚያ ሰጥቶ ድጋፍና ማበረታቻ
ማቅረባቸው፣ የማበረታቻ እና ድጋፍ አቅረቦትን በአምራች ኢንዱስትሪ እሴት ሰንሰለት
(ከግብአት-ምርት-ገበያ) ላይ ተመጋጋቢና የማይጣረስ አድርጎ ማዘጋጀት እና
አፈፃፀሙን የሚከታተልና የሚቆጣጠር ጠንካራ አደረጃጀትና ቅንጅት መገንባታቸው፣
በመንግስትና የግሉ ባለሀብት ዘንድ የመተማመን እና የትብብር መንፈስ መኖርና
የፓለቲካ አመራሩ እና በሲቪል ሰርቫንቱ ዘንድ ቁርጠኝነት መኖር ይጠቀሳሉ፡፡

(Rodrik 2008) የተባለ ፀሀፊ የአንዱስትሪ ፖሊሲ አፈፃፀምን በሚመለከት መከናወን


ያለባቸውን ጉዳዮች በ3 ከፍሎ አብራርቷቸዋል፡፡ የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ አብሮ
የመስራት ስርዓት፣ የማበረታቻ እና ግዴታ ስርዓቶች (carrot and stick) ውጤት እና
ስነምግባር መሰረት ያደረገ አስገዳጅ የማበረታቻ ስርዓት መዘርጋት እና በጥሩ
ስነምግባር የመምራት አስፈላጊነት ሲሆን የመጨረሻው የተጠያቂነት ስርዓት በሁሉም
ወገን ሊኖር የሚገባው መሆኑን ያስረዳል፡፡ በኢንዱስትሪ ልማት ምርጥ ተሞክሮ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 233


ያላቸው የምስራቅ ኤስያ ሀገራት (ጃፓን፣ ኮሪያና ታይዋን) በአምራች ኢንዱስትሪ
ለተሰማራው ባለሀብት ከሚያቀርቧቸው ማበረታቻዎች መካከል ለመጥቀስ ያህል፡
የካፒታል ገበያው የግሉ ዘርፍ ስምሪት የአምራች ኢንዱስትሪ እንዲሆን የሚያግዙ
የቀጥታ ብድር፣ የተደጎመ አነስተኛ የብድር ወለድ ስርዓት፣ የብድር ዋስትና ስርዓት
እና ለዘርፉ የተለየ የልማት ባንኮች የብድር አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋት የመሳሰሉት
ይገኙበታል፡፡

በሀገራችን ያለውን የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ስንመለከት ከፋንክሽናል


(Functional Industrial Policy) የኢንዱስትሪ ፖሊሲ ይልቅ የተመረጡ ዘርፎችን ለይቶ
ለማሳደግ ያለመ የመንግስት ጣልቃ ገብነትና ድጋፍ የሚጋብዝ (Selective industrial
policy) እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ ነገር ግን ጥያቄ የሚሆነው የኢንዱስትሪ ልማት
ስትራቴጂው ተግባራዊ አፈፃፀሙ ምን ያህል በተቀመጠው አቅጣጫ መስረት መሆን
አለመሆኑ ነው፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ሚና

የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገትና ልማት ላይ የሚኖረው


ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ በሀገራችን የረጅም ጊዜ የኢንዱስትሪ ልማት ዕድገታችን ፍጥነትና
ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ የማይተካ ሚና አለው፡፡ ከዚህ
አንፃር በተለይ በ2017 ዓ.ም የተቀመጠውን ሀገራዊ ራዕይ ለማሳካት ይቻል ዘንድ
ከሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱና ከአምራች ኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካላት የሚጠበቀው
አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው፡፡

በ2017 ዓ.ም የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በቀላል አምራች ኢንዱስትሪ (Light
manufacturing) በተለይ በአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ዕድገትና ልማት ላይ ዋና
ተዋናይ እንዲሆንና ንዑስ ዘርፉን መምራት የሚያስችለው ሙሉ አቅም (ዕውቀትና
ክህሎት፣ አመለካከት፣ አመራርና የካፒታል አቅም) እንዲኖረው ማድረግ፤

በዚህ ራዕይ መሰረት የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ በተለይ
በአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ልማት ላይ የመሪነት ሚና እንዲጫዎት ማስቻል
አስፈላጊ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 234


8.2.1 የኢንዱስትሪ አመራርና አደረጃጀትን ማሻሻል

በተለያዩ ሀገራት መካከል የዕድገት ልዩነት የመጣው ሀገራት በሚከተሉት የፖሊሲ


አቅጣጫና የመንግስት የማስፈፃፀም አቅም ነው፡፡ ስኬታማ የሆኑ የምስራቅ ኤስያ
ሀገራት ተሞክሮ የሚያሳየው የፖሊሲ አቅጣጫ ማስቀመጥና የማስፈፀም ዓቅምን ማሳደግ
ላይ ትኩረት ማድረጋቸው ነው፡፡ ሁለቱም ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኞች ናቸው፡፡
የአንድን ሀገር የማስፈፀም አቅም ስንለካ የተቋማትን፣ የአሰራር ስርዓትን እና የሰው
ሀይል አቅም ማየት ያስፈልጋል፡፡ በሀገራችን ኢንዱስትሪውን እንዲደግፉ የተቋቋሙ
አደረጃጀቶችን ስንመለከት ተቋማዊ አደረጃጀቱ ወደ ታችኛው የመንግስት መዋቅር
(ክልል፣ ወረዳ እና ከተሞች) በትኩረት ያልተሰራበት ነው፡፡ በእነዚህ መዋቅሮች ውስጥ
በብዛትና በብቃት የሰው ሀይል አልተመደበም፤ የራሱ በጀትም የለውም፤ ስልጣንና
ሀላፊነት አልተሰጠውም፡፡ በአጠቃላይ የኢንዱስትሪ ልማቱን ሊመራ የሚችል አቅም
አልተፈጠረም፡፡ በተጨማሪም አገልግሎት አሰጣጡ በቴክኖሎጂ ያልታገዘ፣ ቀልጣፋ
አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የአሰራር ስርአት አልተዘረጋለትም። በመሆኑም
ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚው መዋቅራዊ ሽግግር የሚጠበቅበትን ማበርከት እንዲችል
የሚከተሉትን ዋና ዋና እርምጃዎች ዝርዝር ጥናት ላይ በመመስረት ማከናወን ተገቢ
ይሆናል፡፡

ሀ. የኢንዱስትሪ ልማት አደረጃጀትና ተግባርን ማሻሻል

የአንደኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ላይ እንደተገለፀው


ሀገራዊ ራዕይን፣ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በትክክልና በተሟላ ሁኔታ ተረድቶ
ያለመጨበጥ፣ የአመለካት ብዥታ እና የዕውቀትና ክህሎት ማነስ ችግሮች ምክንያት
የኢንዱስትሪ ዘርፉን ዕድገት ለማፋጠን የሚያስችል የተቀናጀና የተናበበ አመለካከት
ማስፈን እንዳልተቻለ አመላክቷል፡፡ በመሆኑም በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩትን
የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች በቅርብ በመደገፍ ተወዳዳሪና ሞዴል እንዲሆኑ ከማብቃት
በተጨማሪ አዳዲስ ባለሀብቶችን ከኮንስትራክሽን፣ ከንግድና አገልግሎት ዘርፎች
መልምሎ ወደ ዘርፉ እንዲቀላቀሉ የማድረግ ተግባር በትኩረት ሊሰራበት ይገባል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በስራ ላይ ላሉ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች የማምረት
አቅማቸውን ለማሳደግ “የምርታማነትና ጥራት ማሻሻያ ፓኬጅ” (Productivity and
Quality Improement Package) ማዘጋጀት፤ አዳዲስ ቴክኖሎጂ ተጠቅመው

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 235


ምርታማነትና ጥራት ለሚያሻሽሉ ባለሀብቶች የፋይናንስና የገበያ ትስስር መፍጠር
እንዲሁም በቂ የታክስና የግብር ማበረታቻ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ በተቃራኒ
በዋናነት በራሳቸው ጉድለት ምክንያት ወደ ማምረት ያልተሸጋገሩ ወይም ያላቸውን
ኋላቀር አሰራርና ቴክኖሎጂ ለማሻሻል ዝግጁ ያልሆኑ ባለሀብቶችን ማገድና መዝጋት
ያስፈልጋል፡፡

በሌላ በኩል ለአምራች ኢንዱስትሪ ድጋፍ ለመስጠት የተቋቋሙት የልማት


ኢንስቲትዩቶች ያሉባቸውን የአቅም ክፍተቶች ለመሙላት በውጭ ባለሙያ ቅጥር
እንዲሁም በውጭ ስልጠናና ልምድ (Exposure) በፋሲሊቲ ማጠናከር፤ እንዲሁም
በተለየ መልኩ ዕቅድና በጀት በማዘጋጀት ማጠናከር ያሻል፡፡

በክልሎች እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ከንግድና ከከተማ ልማት ጋር


የተጣመረ በመሆኑና በልምድም ሆነ በተቋማዊ ስልጣን የንግድና ከተማ ልማት ዘርፎች
የጎላ ተፅዕኖ ስላላቸው ለኢንዱስትሪው የተሰጠው ትኩረትም ዝቅተኛ እንዲሆን
አድርጎታል፡፡ በተለይ አብዛኛው የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትና ልማት
የመምራት ኃላፊነት ለክልሎች የተሰጠ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ዘርፉ ከከተማ ልማትና
ንግድ ጋር ተጣምሮ መዋቀሩ አሁንም ኢንዱስትሪ ተገቢውን ትኩረት እንዳያገኝ
ያደርገዋል የሚል ስጋት አለ፡፡ ስለዚህ በክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ ዞኖችና
ወረዳዎች የሚገኘው መዋቅር የኢንዱስትሪ ልማት ተልዕኮውን ለማሳካት በሚያስችል
ደረጃ ላይ መሆኑን መፈተሸና ማረጋገጥ ያሻል፡፡ በእነዚህ ተቋማት በየደረጃው
የኢንዱስትሪ ዘርፉን የሚመሩት ክፍሎች በቂና የተጠናከረ የሰው ኃይል እንዲሁም
ድጋፍ መስጠት በሚችሉበት ደረጃ መሆናቸውን ማረጋገጥም ያስፈልጋል፡፡

በሌላ በኩል በቅርቡ የፌደራል የኢንዱስትሪ አደረጃጀት ለውጥን ተከትሎ በክልሎችና


ከተማ አስተዳደሮች ተመሳሳይ የአደረጃጀት ለውጥ እተደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሠረት አንዳንድ ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የአነስተኛና መካከለኛ
አምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኤጀንሲ አቋቁመዋል፡፡ የኤጀንሲው መቋቋም በራሱ
ክልሎች ያላቸውን የፋይናንስና የሰው ሀይል ሪሶርስ በነፃነት እንዲጠቀሙ፣ የአሰራርና
የተቋም ለውጥ እንደነባራዊ ሁኔታው በመቀያየር እንዲሰሩ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በዚህም
ደንበኛ ተኮር የሆነ አገልግሎት ለባለሀብቱ እና ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ተደራሽ
ለማድረግ ይረዳቸዋል፡፡ በተጨማሪም ኤጀንሲው የስልጠና፣ የአቅም ግንባታ እና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 236


የቅስቀሳ ስራዎችን በስፋት እንዲሰራ ይጠበቃል፡፡ይህ አደረጃጀት ከዚህ በፊት ከነበረው
አደረጃጀት ጋር ሲነፃፀር አምራች ኢንዱስትሪውን በቅርበት ለመደገፍ የሚያስችል
ነው፡፡ በመሆኑም በየክልሉ የተጀመሩ የአነስተኛ እና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪ
ልማት ኤጀንሲን የማደራጀትና የማቋቋም ስራን አጠናክሮ መቀጠል፤ ብሎም
ባልተቋቋመባቸውም ክልሎች እንዲቋቋሙ ማድረግ ያስፈልጋል። በአጠቃላይ አሁን
በክልሉ የተጀመረው አምራች ዘርፉን ተደራሽ የሚያደርግ የመዋቅር ማስተካከያ
የሚበረታታ ቢሆንም የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ ግን የአነስተኛና
መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪ ልማት አደረጃጀትን በዞኖችና ወረዳዎች ላይ ተጠናክሮ
እንዲደራጅ ማድረግ ያሻል፡፡ በዚህ የአስተዳደር እርከን የሚዋቀረው አደረጃጀት አቅም
ባላቸው ባለሙያዎችና በፋሲሊቲዎች ማደራጀት ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም በእያንዳንዱ
ንኡስ ዘርፍ በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ባለሀብቶች ዝርዝር ችግራቸውን በቅርብና
በቀጣይነት እየተከታተሉ የሚፈቱ ወይም ለሚፈታ አካል የሚያቀርቡ የአምራች
ኤክስቴንሽን ድጋፍ ሰጪ ወይም Relations Officer መመደብ ያስፈልጋል፡፡ የሰለጠኑና
ጠንካራ ስነ-ምግባር ያላቸው ባለሙያዎችም በስራ ውጤት እየተመዘኑ በየዓመቱ
ማበረታቻ የሚሰጣቸው የአሰራር ስርአት መዘርጋትም ጠቃሚ ነው፡፡ በተጨማሪም
እንደ አስፈላጊነቱ ከተመረጡ ሀገሮችና ተቋማት ምርጥ የኢንዱስትሪ አመራር ልምድ
ያላቸውን ባለሙያዎች መልምሎ ቀጥሮ ማሰራት ዕውቀትን ለማግኘትና የጥራት ደረጃን
ለማሻሻል ስለሚያግዝ ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡

በክልል ደረጃ የኢንዱስትሪ ቢሮ፣ የአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪ ልማት ኤጀንሲ፣


የኢንቨስትመንት ኤጀንሲ/ኮሚሽን፣ እና የስራ ፈጠራና የምግብ ዋስትና ጽ/ቤቶች
ተናበውና ተቀናጅተው መስራት ስለሚገባቸው ይህን ግምት ውስጥ ያስገባ የአሰራር
ስርአት ሊኖር ይገባል፡፡

ለ. ለኢንዱስትሪ አመራሮችና ባለሙያዎች የታቀደ ሰፊ ስልጠና መስጠት

በኢንዱስትሪ ልማት የሰው ሀይል ሪፎርም ጋር ተያይዞ ለኢንዱስትሪ አመራሩና


ባለሙያው በሀገራችን የኢንዱስትሪ ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስልጠና
መስጠት፤ ብቃት ያለው አደረጃጀት መፍጠር፤ ብዛት ያላቸው አመራሮችና
ባለሙያዎች ማፍራት (በተለይ ክልሎችና ወረዳዎች ላይ) ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 237


ከላይ በምዕራፍ 5 እንደተገለፀው በፌደራልና በክልሎች ያሉ የኢንዱስትሪ አመራሮች
በሀገራችን የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ ግልፅና የጠራ አመለካከትና ተግባቦት አላቸው
ለማለት አያስደፍርም፡፡ ስለዚህ አመራሩ በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማራውን የግል
ባለሀብት በትክክል እየመራው ነው ለማለት አይቻልም፡፡ በመሆኑም ከሁሉም ስራ
በፊት የኢንዱስትሪ አመራሮችን በብዛትና በጥራት ማዘጋጀት ይጠይቃል፡፡ ስለሆነም
በሀገር አቀፍና ክልል ደረጃ ብዛት ያላቸውን አዳዲስ አመራረሮችና ባለሙያዎች
ጨምሮ ለሁሉም የኢንዱስትሪ አመራርና ባለሙያ በተለይ በኢንዱስትሪ ፖሊሲና
ስትራቴጂ እንዲሁም በአመለካከትና በባህሪ ለውጥ ዙሪያ በታቀደ መልኩ የስልጠና
ፓኬጅ ማዘጋጀትና ሰፊ ስልጠና መስጠት መሰረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ በተጨማሪም
በየደረጃው በኢንቨስትመንት፣ አምራች ኢንዱስትሪ ድጋፍ ሰጪዎች፣ የገቢዎችና
ጉምሩክ አካላት የሚሰጡ አገልግሎቶች ፈጣን እና ግልፅ እንዲሆኑ በእነዚህ ፈፃሚ
መስሪያ ቤቶች እያንዳንዱ መስሪያ ቤት በሚመራባቸው የሕግ ማዕቀፎች ላይ ሰፋፊ
እና የተቀናጀ የጋራ ስልጠና መስጠት አስፈላጊ ነው፡፡

በሌላ በኩል ሀገራችን ገና በመጀመሪያው የኢንዱስትሪ ልማት ጉዞ (At early stage of


industrialization) ላይ ስለሆነች እና የኢንዱስትሪ ልማቱ ረጅም ርቀት የሚቀረን
በመሆኑ ከላይ ከተገለጸው የአጭር ጊዜ ስልጠና በተጨማሪ ወደፊት ብቁ አመራሮችንና
ሙያተኞችን በብዛት ማፍራት የሚያስችል የትምህርትና ስልጠና ስርዓት መዘርጋት
ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የኢንዱስትሪ ባለሙያዎችን በመደበኛ ትምህርትና በልዩ
ስልጠና ለማፍራት በዚህ ዘርፍ ስፔሻላይዝ (specialize) የሚያደርጉ እና ስልጠናውን
በባለቤትነትና በብቃት የሚሰጡ ዩኒቨርስቲዎች፣ ኢንስቲትዩቶችና የቴክኒክና ሙያ
ስልጠና ተቋማት (TVET) ተለይተው እንዲሁም ግልፅ ተልዕኮ ተሰጧቸው፣ የተለየ
በጀት ተመድቦላቸው፣ ከውጭ ተቋማት ጋር ትስስር (twining) ፈጥረው የሚፈፅሙት
እንዲሆን ናድረግ ያስፈልጋል፡፡

ሐ) ጠንካራ የአመራርና ባለሙያ ምደባ እና ግምገማ ስርዓት መዘርጋት


ከሰው ሀይል ምደባ በተለይም የአመራሩን ጋር ተያይዞ ትልቁና አሳሳቢው ጉዳይ ብቃት
ያላቸውን አመራሮች ወደዘርፉ እንዲመደቡ ማድረግ ዋናው ጉዳይ ነው፡፡ የኢንዱስትሪ
ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ ወደ ዘርፉ የሚመጡ አመራሮች (በሹመትም ይሁን
በምደባ) በስራ አፈጻጸማቸውም ሆነ በስነ-ምግባር አርአያ የሆኑ መሆን ይገባቸዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 238


ቻይና እና ኮሪያ ተሞክሮን ስንመለከት አመራሩን፣ ቢሮክራሲውን፣ ተማሪና መምህሩን፣
እንዲሁም ባለሀብቱን ልማትን ማዕከል ባደረገ የውጤት ተኮር የአመራርና ምዘና
ስርዓት እንዲተጋና በውጤቱ እንዲሸለም ወይም እንዲጠየቅ የሚያደርግ ስርአት
ዘርግተው ውጤታማ ሆነዋል፡፡ ሁሉም ሰራተኛ ከዚህ ስርዓት ውጭ እንዳይወጣ
ስርዓቱን ከላይ እስከታች በሁሉም የስራ ዘርፍ በጥብቅ እንዲተገበር አድርገዋል፡፡
በተለይም ኮሪያውያን ጠንካራ የውጤት ተኮር አመራር ስርዓትና ውጤት ተኮር ምዘና
ዳጎስ ባለ የማትጊያ ጉርሻና ውጤትን መሰረት ያደረገ ዕድገትና ቅጣት የተገነባ
ቢሮክራሲ ፈጥረዋል፡፡ ሀገር ወዳድ ታታሪና ለውጤት የሚተጋ ሁሌም በተከታታይ
ስልጠናና ፈተና ብቃቱ እየተፈተሸ ሁሌም ብቁ ሆኖ ለውጤት የሚረባረብ ያለማቋረጥ
ሙያውንና አመለካከቱን የሚያዳብር ቢሮክራሲ እንዲሆን አድርገውታል፡፡ ኃላፊዎችም
በዚህ ስርዓት እንዲያልፉና እንዲፈተሹ ያደርጋሉ፡፡ ለተሰጠው ኃላፊነት ብቁ
የሚያደርገውን የምዘናና የፈተና ውጤት ያላገኘ ኃላፊና ሙያተኛ ይሰናበታል፡፡
ሰራተኛው ሁሌም የስራ ውጤት ምዘና እና ፈተና ስለሚኖር ራሱን በስልጠናና በተግባር
በቀጣይነት በማብቃት ተወዳዳሪ ሆኖ መገኘት የግድ እንዲሆንበት አድርገዋል፡፡

በመሆኑም ሀገራችን ያስቀመጠችውን የተለጠጠ የኢንዱስትሪ ልማት ዕቅድ በተሳካ


ሁኔታ ከግብ ማድረስ እንዲቻል ኢንዱስትሪውን በመምራት ላይ የሚገኙ አመራሮች
ከፍተኛ ሚና ሊጫወቱ ይገባል፡፡ አመራሩ የልማቱ መሪ ሆኖ በገበያ ክፍተት ጣልቃ
እየገባና ባለሀብቱን ከጥገኛ መንገድ እያወጣ ወደ ልማታዊ ባለሀብት የሚያስገባና
ተወዳዳሪ የሚያደርግ የመምራት ብቻ ሳይሆን የመግራት ሚና እንዲኖረው
ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ ዘርፉን እንዲመሩ ሀላፊነት የሚሰጣቸው አመራሮች በኢንዱስትሪ
ልማት ስትራቴጂው ላይ በቂ ዕውቀት ያላቸውና ወደተግባር ሊቀይሩ የሚችሉ
አመራሮች ሊሆኑ ይገባል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አመራርና ቢሮክራሲን በተግባር በስራ
ውጤት የሚለካና የሚያበቃ ውጤት ተኮር የአመራር ስርዓትና ምዘና ከተጠያቂነት ጋር
ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

8.2.2 አምራች የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱን ለማጠናከር የቀረቡ የማበረታቻ


ማሻሻያዎች

በሀገራችን መንግስት የግሉ ዘርፍ በዋናነት በአምራች ዘርፍ እንዲሰማራ ማበረታቻዎች


እና የድጋፍ ማዕቀፎች አዘጋጅቶ ወደስራ የገባ ቢሆንም፤ ነገር ግን አሁንም የግሉ ዘርፍ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 239


ስምሪት ትኩረት የአግልግሎት ዘርፍ እንደሆነ ቀጥሏል፡፡ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ
የሚቀርበው ማበረታቻና ድጋፍ ተወዳዳሪነቱን በሚያጎለብት ሁኔታ ካለመቅረቡ
በተጨማሪ ለጥገኛ ባለሀብቶች መጠቀሚያ የመሆን አዝማሚያ እየታየበት ነው፡፡ ከላይ
እንደተጠቀሰው የኢንዱስትሪ ማበረታቻዎች አፈፃፀም ደካማ የሆነበት ዋና ዋና
ምክንያቶች በርካታ ቢሆኑም በዋናነት ማበረታቻው ከተሰጠ በኋላ ለታለመለት አላማ
መዋሉን ክትትልና ቁጥጥር አለመደረጉና አፈፃፀምን መሰረት አድርጎ የማይተገበር
መሆኑ፤ እንዲሁም አገልግሎት ሰጪውና ጥቂት የማይባሉ የግል ባለሀብቶች ኪራይ
በመሰብሰብ ላይ ስለተጠመዱ ማበረታቻዎች በትክክል ተግባራዊ አልተደረጉም፡፡
በመሆኑም የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ
እንዲሰማሩ ለማድረግ አሁን በስራ ላይ ያለውን የማበረታቻና ድጋፍ ማዕቀፍ መከለስና
የበለጠ ማጠናከር ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም በዘርፉ የባለሀብቱን ስምሪት ለማስፋፋትና
ለማጠናከር እንዲቻል የሚከተሉት የማበረታቻና ድጋፍ ፖሊሲ ማሻሻያ ሀሳቦች
ቀርበዋል፡፡

ሀ. ለአምራች ባለሀብቱ የብድር ወለድ መጠን ከሌላ ዘርፍ ባለሀብት ያነሰ ማድረግ

በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ እንደተገለፀው የልማት ባንክ


በአምራች ዘርፍ ለተሰማሩ የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች የመካከለኛና የረጅም ጊዜ
ብድር ያቀርባል፡፡ ነገር ግን በአንድ በኩል የባንኩ የወለድ መጠን የተመረጡ ዘርፎችን
ጨምሮ ለሁሉም ዘርፎች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሚያበደረው የብድር ወለድ መጠን
የበለጠ መሆኑ በሌላ በኩል ደግሞ የብድር አሰጣጥ ስርዓቱ (የብድር ወለድ ተመላሽ
ስርዓቱ) ግልፅነት የሌለው በመሆኑ የባንኩን የብድር ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካት
አልቻለም፡፡ ለምሳሌ ከታይዋን ጋር ስናወዳድር በመጀመሪያዎች የእድገት ዘመናት
(1960 -1990 ዎች) በአምራች እና በሌሎች ዘርፎች የወለድ መጠን ልዩነት ከ7.5
በመቶ በላይ የነበረ ሲሆን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የወለድ መጠን 12 በመቶ
(ለተመረጡ ዘርፎዎች ብቻ 9-9.5 እንዲሆን የሚያደርግ የወለድ ተመላሽ ስርዓት
የሚፈቅድበት አሰራር ባንኩ በብድር ሰነዱ አስፍሯል) እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ
ባንክ ለሁሉም ዘርፎች 9.5 በመቶ ነው፡፡ ስለዚህ የአምራች ኢንዱስትሪውን ባህሪ
ከሌሎች ዘርፎች የተለየ መሆኑን በመረዳት በዘርፉ ለተሰማራው ባለሀብት ልዩ የብድር
አሰጣጥ ስርአት (በአነስተኛ ወለድ፣ የረጅም ጊዜ ብድር፣ የስራ ማስኬጃ፣ ወዘተ)
በመዘርጋት በዘርፉ የተሰማራውን ባለሀብት ማበረታታትና ማጠናከር ያሻል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 240


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሁን ለሁሉም ዘርፎች ያስቀመጠውን የብድር ወለድ
መጠን ቢያሻሻል እና በተለይ ለአምራች ዘርፍ፣ ወደውጭ ለሚልኩ ኤክስፖርተሮች
እና ሌሎች በመንግስት ለተመረጡና ብዜታዊ ጠቀሜታ (Multiplier effect) ላላቸው
ዘርፎች ውጤትን መሰረት ያደረገ አነስተኛ የወለድ መጠን ቢያስቀምጥና ለሌሎች
ዘርፎችም ከአምራች ዘርፍ ከፍ ያለ የወለድ መጠን እንዲኖራቸው የሚያስችል
የብድር ፖሊሲ ያስፈልጋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ


 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአምራች ዘርፍ የተቀመጠው የወለድ መጠን ቢያንስ
ንግድ ባንክ ጨምሮ በሀገራችን ያሉት የግል ባንኮች ከሚያስከፍሉት አነስተኛ
የብድር ወለድ መጠን ያነሰ እንዲሆን ማድረግ የተሻለ ነው፡፡
 ባንኩ ለተመረጡ አንደኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ኤክስፖርተሮች እና ሌሎች
ዘርፎች ያስቀመጠውን አፈፃፀምንና የወለድ መጠን ተመላሽ ስርዓት ውጤትን
መሰረት ያደረገ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በአንድ በኩል አሁን ካለው የወለድ
መጠን የበለጠ መቀነስ የሚቻልበት ሁኔታ አስፈላጊ ሆኖ በሌላ በኩል ደግሞ
የተመላሽ ስርዓቱ የሚፈፀምበት አሰራር ስርዓት ግልፅና በቀላሉ የሚፈፀም እንዲሆን
ቢደረግ የተሻለ ነው፡፡
 ባንኩ የሚሰጠው የመካከለኛና ረጅም ጊዜ የኢንቨስትመንት ብድር ተከትሎ
የሚሰጠው ዋናው ብድር የማይከፈልበት ጊዜ (grace period) ሊከፍል የሚገባው
የወለድ መጠን ተበዳሪው ከመክፈያ ጊዜ ቀደም ብሎ ገና ብድሩ ሳይለቀቅ
የአመታት ወለድ በዝግ ሂሳብ እንዲያስቀምጡ መደረጉ በዘርፉ የሚሳተፉ
ባለሀብቶች ያለባቸውን የፋይናንስ ዕጥረት ያላገናዘበ ነው፡፡ ስለዚህ ባንኩ ባለሀብቱ
ያለበትን የስራ ማስኬጃ ካፒታል ዕጥረት በእጅጉ የሚያባብስ በመሆኑ ይህ አሰራር
ተነስቶ ባለሀብቱ በተቀመጠው የብድር ወለድ መክፈያ ጊዜ መሰረት የሚከፍልበት
ወይም እንደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በባለሀብቱ ምርጫ መሰረት እንዲሆን
የሚያስችል አሰራር መዘርጋት ያሻል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 241


ለ. በታክስ ህግ የሚቀርቡ ማበረታቻዎችን ማሻሻል (የገቢ ግብርና እርጅና ተቀናሽ)

1)የሀገር ወስጥ ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በስፋት መሳተፍ ለዘላቂና


ፍትሀዊ ልማትና ዕድገት ወሳኝነት ያለው በመሆኑ በዘርፉ የተሰማሩትን ነባር
ባለሀብቶች በቅርብ በመደገፍ ተወዳዳሪ እና ሞዴል እንዲሆኑ ከማብቃት ጎን ለጎን
የአዳዲስ ኢንቨስትመንት ምንጭ ሊሆኑ የሚችሉ በኮንስትራክሽን፣ ንግድና
አገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩትን መልምሎ ዘርፉን እንዲቀላቀሉ የማድረግና
የተወዳዳሪነት ብቃት እንዲያጎለብቱ የበለጠ ማበረታታትና መደገፍ ብሎም ዘርፉ
ተመራጭ የማድረግ ስራዎች ትኩረት የሚያሻቸው ናቸው፡፡ የአምራች ዘርፍ ከሌሎች
በተለየ ሁኔታ በቀላሉ ሊመለስ የማይችል ካፒታል ማፍሰስ የሚጠይቅ፣ የረጅም ጊዜ
እይታና ቁርጠኝነት እንዲሁም ዘመናዊ አደረጃጀትና ማኔጅመንትን የሚፈልግ፣
ከፍተኛ ተወዳዳሪነት እና የኪሳራ ተጋላጭነት ያለበት፣ ውስብስብ ችግሮች እና
ውጣውረድ የበዛበት በመሆኑ፣ የትርፍ ህዳጌውም አነስተኛና ከረጅም ዓመታት በኋላ
የሚገኝበት ዘርፍ ነው፡፡ በሌላ በኩል የንግድና አገልግሎት እንዲሁም የኮንስትራክሽን
(የሪል እስቴት) ንዑስ ዘርፍ ያለ ብዙ ውጣ ውረድ በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ትርፍ
የሚገኝበትና ለኪሳራ ተጋላጭ ያልሆነ፣ ቢሮክራሲውም ሆነ የፋይናንስ ተቋማት
አገልግሎት ለመስጠት የሚሽቀዳደሙባቸው ናቸው፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ እና
የኤክስፖርት ንግድ በማሳደግ ውጤት ያስመዘገቡ ሀገራት ልምድም ስንመለከት
ለምሳሌ በቬትናም አጠቃላይ የሀገሪቱ የገቢ ግብር ምጣኔ 25 በመቶ ሲሆን የአምራች
ዘርፍ እንደ ኢንቨስትመንት ዓይነቱ እና ቦታ 10-20 በመቶ ነው። ጋና የአምራች
ዘርፍ ገቢ ግብር ምጣኔ 8 በመቶ ሲሆን፣ የሆቴል 22 በመቶ፣ የፋይናንስ ተቋማት 20
በመቶ፣ የሌሎች ደግሞ 25 በመቶ ሲሆን በቦትስዋና አጠቃላይ የሀገሪቱ የገቢ ግብር
ምጣኔ 25 በመቶ ሲሆን የአምራች ዘርፍ ግን 15 በመቶ መሆኑ የኢንዱስትሪ
ሚኒስቴር ያጠናው ጥናት ያሳያል፡፡ በመሆኑም በሀገራችን እነዚ ዘርፎች በአንድ ላይ
አጭቆ ተመሳሳይ 30% የገቢ ግብር ማሰቀመጡ ተገቢነት የለውም፡፡ ይህ ሁኔታ
በአምራች ዘርፍ አዳዲስ ባለሀብቶች በብዛት መሳብ ይቅርና የገቡትንም በዘላቂነት
ጠብቆ ለማቆየት እንዲሁም ልማታዊ አስተሳሰብና ባህል ለማስረፅ አዳጋች
አድርጎታል፡፡ ስለዚህ አጠቃላይ የስራ ሂደትና ድካም ያገናዘበ እና የባለሀብቱ ስምሪት
በሚስብ መልኩ የተቃኘ አነስተኛ የገቢ ግብር እንዲከፍሉ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
የንግድ፣ ሪል ስቴት፣ የፋይናንስ ተቋማትና ሌሎች የአገልግሎት ዘርፍች በአንፃሩ
አነስተኛ እሴት ጨምረው ከፍተኛ ትርፍ የሚያገኙ በመሆናቸው ባህሪያቸውን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 242


በተናጠል በመለየት የገቢ-ግብር ምጣኔው ከፍ እንዲል በማድረግ ለአምራች
ኢንዱስትሪው የተቀነሰውን ግብር ምጣኔ ለማካካስ እና አምራች ዘርፍ በሀገር ውስጥ
ባለሀብቱ በንፅፅር ቅድሚያ ተመራጭ የኢንቨስትመንት መስክ እንዲሆን የበኩሉን
አስተዋፅፆ ያበረክታል፡፡

2) ገቢ ምርት ለሚተኩ የተመረጡ ኢንዱስትሪዎች የግብአት ቀረጥና ታክስ ፓሊሲ


መሻሻል
የጉምሩክ ቀረጥና ተዛማጅ ግብር ገቢ ምርት ለሚተኩ (Import substitution) የሀገር
ውስጥ አምራች ባለሀብቶችን የሚጎዳ ነገር ግን ለአስመጪዎች ምቹ የሆነና የሚጠቅም
ሆኖ ይታያል፡፡ ለአብነት አንዳንድ ኢንዱስትሪዎች ለምርት በግብአትነት
የሚጠቀሟቸው እቃዎች ለመለዋወጫነት ከሚያስመጡ እሴት የማይጨምሩ
አስመጭዎች ጋር ተመሳሳይ የሆነ የጉምሩክ ቀረጥና ተያያዥ ታክስ እንዲከፍሉ
ይደረጋል፡፡ በተጨማሪ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ ምርቱን በቀጥታ የሚያስመጡ አካላት
እንዲሁ ከቀረጥና ተያያዥ ታክስ ነፃ ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል፡፡ ይህ ሁኔታ ገቢ ምርት
የሚተኩ ኢንዱስትሪዎች በሀገር ወስጥ ገበያ ውድ ስለሚሆኑ ገበያ የማግኘት ዕድላቸው
እንዲቀንስ እና በተለይ ለከባድ ኢንዱስትሪዎች ልማት መሰረት ቀጣይነት ላይ
አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፡፡ ስለሆነም ገቢ ምርትን የሚተኩ የተመረጡ ኢንዱስትሪዎች
በግብአትነት የሚጠቀሙበትን መለዋወጫ እና ሌሎች እቃዎች ከጉምሩክ ቀረጥ እና
ተያያዥ ታክሶች ነፃ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡

3) የግል ባለሀብት ለመደገፍ ያስችል ዘንድ በሀራችን የገቢ ግብር አዋጅ እርጅና
ተቀናሽ ማበረታቻ አቅርቧል፡፡ በዚህ መሰረት ለህንፃዎች እና ለማይዳሰሱ ንብረቶች
የገቢ ግብር እርጅና ተቀናሽ የቀጥተኛ መስመር ዘዴ (straight line method) ሲሆን
የማምረቻ መሳሪያዎችን እና ሌሎች ንብረቶችን በፑሊንግ ዘዴ (pooling system)
እርጅና ተቀናሽ ይደረጋል፡፡ነገር ግን ከላይ የተጠቀሱት እርጅና ተቀናሽ ማበረታቻ
ዘዴዎች የአምራች ዘርፍ ካለበት የስራ ማስኬጃ ፋይናንስ ውስንነትና ተወዳዳሪነቱን
ከማጎልበት አንፃር በቂ አይደለም፡፡ ስለዚህ አምራች ኢንዱስትሪው ምርት ማምረት
በሚጀምርበት ወቅት የስራ ማስኬጃ ካፒታል እጥረት እና ኢንቨስትመንት ማስፋፋት
ዋነኛ ማነቆ እንደሆነ በመገንዘብ የካፒታል እቃዎች ፈጣን የእርጅና ተቀናሽ ስልትን
(Accelerated depreciation method) በመተግበር ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 243


ሐ. የግብር እፎይታ ጊዜ ማሻሻል

በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት በአዲስ አበባና


በዙሪያው በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ዞኖች እና በሌሎች አካባቢዎች የግብር እፎይታ ጊዜ
በጣም ተቀራራቢ (ከአንዳንድ የአምራች ንኡስ ዘርፎች ውጭ በሁለቱ አካባቢዎች
ያለው የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ልዩነት በአማካኝ አንድ አመት ነው) በመሆኑ
የሀገራችን የኢንዱስትሪ ስምሪት በአንድ አካባቢ የመከማቸት ስጋት አለ፡፡ ስለዚህ
የሀገራችን ህዝቦች ከዘርፉ ፈትሃዊ ተጠቀሚ እንዲሆኑና የኢንዱስትሪ ስምሪቱ አቅጣጫ
ለማመላከት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ በክልሎችና በአዲስ አበባ እና ዙርያዋ
ያለውን የግብር እፎይታ ጊዜ ማሻሻል (ልዩነቱን ማስፋት) አስፈላጊ ይሆናል፡፡

8.2.3 ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪ የፋይናንስ አቅርቦት ልዩ ትኩረት መስጠት

በአምራች ኢንዱስትሪ ስኬታማ የሆኑ ሀገራት ልምድ እንደሚያሳየው ለአምራች ዘርፍ


ብቻ ትኩረት አድርጎ ፋይናንስ የሚያቀርብ SME ባንክ አቋቁመው ውጤታማ ሆነዋል፡፡
ለምሳሌ በታይዋን ለአነስተኛና መካከለኛ ተቋማት ብቻ ፋይናንስ የሚያቀርቡ እና
የብድር ማስያዥያ ችግራቸውን ለመፍታት የሚችሉ ተቋማት አሏቸው፡፡ በሀገራችን
ያለው የልማት ባንክ ለሁሉም ዘርፎች ፋይናንሰ የሚያቀርብ በመሆኑ ለአምራች ዘርፉ
ትኩረት በማድረግ የሚጠበቅበትን ሚና መጫዎት አልቻለም፡፡ የአነስተኛና መካከለኛ
ኢንዱስትሪ ባንክ አሁን ባለንበት ወቅት ራሱን ችሎ ማቋቋም የማያስችሉ ሁኔታዎች
(በቂ የፋይናንስ አቅም አለመኖር) ስላሉ በልማት ባንክ ውስጥ ራሱን ችሎና አንድ
የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ የሚደራጅበትን ሁኔታ መፍጠር ይቻላል፡፡ ይህ አማራጭ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የተሟላ የመሰረተ ልማት ስላለው፣ የተጀመረው የሊዝ
ፋይናንስ የተሟላ ፋይናንስ ለመስጠት ጅምር መኖሩ እና ብዛት ያላቸው ቅርንጫፎች
ስላለውና ወደፊትም ስለሚኖሩት በቀላሉ ተደራሽ ለማደረግ ያስችላል፡፡ ስለዚህ
ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ትኩረት አድርጎ የሚሰራና የዘርፉን የፋይናንስ
ፍላጎት ግምት ውስጥ ያስገባ የተለየ የብድር ፖሊሲ፣ ግልፅ ተልዕኮ፣ አደረጃጀት እና
የሰው ሀይል ያለው እንዲሁም ተደራሽ የሆነ መዋቅር ተዘርግቶለት ቢደራጅ የተሻለ
ይሆናል፡፡ ይህ አደረጃጀት አሁን ያለውን የአነስተኛና መካከለኛ ተቋማት ችግር
መፍታት የሚችል እና በቀላሉ ተደራሽ የሚሆን ቢሆንም የአነስተኛና መካከለኛ
ተቋማት ዕድገትን መሸከም የማይችልበት ደረጃ መድረሱ ስለማይቀር በሂደት ራሱን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 244


ችሎ ሊደራጅ ይችላል፡፡ ስለዚህ ልማት ባንክ ለSME በልዩ ሁኔታ በውስጡ ከላይ
እስከታች በማደራጀት ስራ ቢጀምር የተሻለ ይሆናል፡፡ ይህ ክፍል ኢኩፕመንት ሊዝ
ብቻ ሳይሆን የስራ ማስኬጃን ጭምሮ ሌላም ብደር አጠቃሎ የሚሰጥ ቢሆን የተሻለ
ነው፡፡

8.2.4 ተገቢ ያልሆነ የአለማቀፍ ንግድ ውድድር ለመቆጣጠር የሬጉላቶሪ ስርአት


መዘርጋት

ገቢ-ምርቶች የሚፈጥሩት ተገቢ ያልሆነ የንግድ ውድድር የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪን


ተወዳዳሪነትና ምርታማነት ላይ ቀላል የማይባል ተፅዕኖ አለው፡፡ ይህ ኢ-ፍትሃዊ
ውድድር የሀገር ውስጥ ገበያን በድንገት በማጥለቅለቅ (sudden import surge)፣ ገበያን
ለመቆጣጠር ሲባል ተመጣጣኝ ባልሆነ ዝቅተኛ ዋጋ በመሸጥ (dumped products) እና
በመንግስታት ድጎማ አማካኝነት የውድድር የበላይነት በመውሰድ የሀገር ውስጥ
ኢንዱስትሪን ከገበያ በማስወጣት (subsidized products) የሚፈፀም ድርጊት ነው፡፡

ገቢ-ምርቶች በሀገራችን ኢንዱስትሪ ዘርፍ ላይ እየፈጠሩት ያለው ተገቢ ያልሆነ


ውድድር እና የደቀኑትን ስጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍ እያለ በመምጣቱ ችግሩን
ለመቆጣጠር የሚያስችል የፓሊሲ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ በመጀመሪያ
ላለፉት ሃያ አምስት አመታት የነፃ ገበያ ውድድር ስርአት ለመገንባት ዘርፈ-ብዙ
የፓሊሲ ለውጦች መደረጋቸው የሀገር ውስጥ የገበያ ከለላ እየቀነሰ እንዲሄድ
አድርጓል፡፡ ይህን ተከትሎ ገቢ- ምርቶች ተገቢ ያልሆነ ውድድር የመፍጠር አዝማሚያ
ማሳየታቸው በዋቢነት ሊጠቀስ ይችላል። ሁለተኛ ተገቢ ያልሆነ አለማቀፍ ውድድር
በመፍጠር ቅሬታ ከሚቀርብባቸው ጥቂት የኤሲያ ሀገራት ጋር የሀገራችን የንግድ
ግንኙነት የአንበሳውን ድርሻ መያዙ በውጭ ምርቶች አማካይነት የዳንፒንግ፣ የተደጎሙ
ምርቶች እና የድንገተኛ ማጥለቅለቅ አደጋ ተጋላጭነታችን መጨመር ይታያል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ ተገቢ ያልሆነ ውድድር የሚስተዋለው በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጅ
ትኩረት የተሰጣቸው ኢንዱስትሪ ንኡስ ዘርፎች ላይ መሆኑ ችግሩን ለመቆጣጠር
ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግ አመላካች ነው፡፡ ለአብነት የዳንፒንግ ችግር
በብረታ ብረት፣ በኬሚካል፣ በስትራክቸራል ሜታል፣ በጎማ ምርቶች (በተለይ የመኪና
ጎማ)፣ በጫማ ምርቶች እና በጨርቃ ጨርቅ ምርቶች ላይ ይስተዋላል፡፡ በተመሳሳይ
ተደጉመው የሚገቡ ምርቶች ለምሳሌ የተቀነባበሩ ምግብ ነክ ምርቶች፣ የተፈበረኩ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 245


የብረታ ብረት ምርቶች፣ የፈርኒቸር እና ተያያዥ ምርቶችና የህክምና መሳሪያዎች ላይ
እንደሚስተዋል ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ በመሆኑም ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመገንባት
ለሚደረገው ርብርብ መሰናክል እንዳይሆን ከወዲሁ ትኩረት ሰጥቶ መስራት
ያስፈልጋል፡፡

ከዚህ በመነሳት ኢ-ፍትሃዊ ውድድር የሚፈጥሩ ገቢ-ምርቶች በአምራች ኢንዱስትሪው


እና አጠቃላይ ኢኮኖሚው ላይ እያስከተሉ ያሉትን ተፅዕኖ እና ስጋት ለመከላከል እና
ለመቆጣጠር የሚያስችል የፓሊሲ ማዕቀፍ አዘጋጅቶ መተግበር ተገቢ ነው፡፡ ስለሆነም፡
 ዳንፕ የሚደረጉ ምርቶችን መከላከል እና መቆጣጠር የሚያስችል የፓሊሲ
ማዕቀፍ (anti-dumping policy)፣
 በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ገቢ-ምርቶች ቅፅበታዊ ማጥለቅለቅ ለሚያስከትሉት
ጉዳት መቆጣጠሪያ እርምጃዎች (safeguard measures)፣ እና
 የሚደጎሙ ገቢ-ምርቶች አሉታዊ ተፅዕኖ መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችል
አሰራር (countervailing measures) ማዘጋጀት እና ተግባራዊ ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡

እነዚህን የፓሊሲ እርምጃዎች ተግባራዊ ለማድረግ ያስችል ዘንድ የሰው ሃይል ብቃት፣
ፋይናንስ፣ ተቋማዊ አደረጃጀት እና በጉዳዩ ዙሪያ ያለንን ልምድ ታሳቢ ያደረገ
አማራጭ ከዚህ በታች ተመላክቷል፡፡

ሀ. የፀረ-ዳንፒንግ (anti-dumping)፣ ገበያን በድንገት ማጥለቅለቅ (sudden import


surge) እና በድጎማ ገበያን መቆጣጠር (subsidized products) የተመለከተ አንቀፅ
በንግድ አሰራር እና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ እንዲካተት ማድረግ፣ እንዲሁም
የማስፈፀሚያ መመሪያ እና ማኑዋል በማዘጋጀት ችግሩን ለመቆጣጠር መስራት እንደ
አማራጭ ሊወሰድ ይችላል፡፡ በተጓዳኝ በጉምሩክ ቀረጥ እና ታክስ ህግ ውስጥ ጉዳዩን
በማካተት የባለድርሻ አካላትን የስራ ሃላፊነትና ተግባር መለየት ብሎም በቅንጅት
እንዲሰሩ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በሀገራችን ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮች በመከላከል
በኩል ምንም አይነት የፓሊሲ ማዕቀፍ እና ልምድ የሌለ በመሆኑ ፓሊሲ ቀርፆ
እንቅስቃሴ መጀመሩ በጉዳዩ ዙሪያ የሰው ሃይል አቅም ለማሳደግ እና ልምድ ለማካበት
ጥሩ አጋጣሚ ይፈጥራል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 246


ለ. ሁለተኛው አማራጭ ሶስቱን ጉዳዮች ማለትም የፀረ-ዳንፒንግ መከላከል ማዕቀፍ፣
የገቢ-ምርቶ ቅፅበታዊ ማጥለቅለቅ መከላከል እና ተደጉመው የሚገቡ ምርቶች አሉታዊ
ተፅዕኖ መከላከል የሚያስችል ዘርዘር ያለ የህግ ማዕቀፍ ወይም አዋጅ (ፓሊሲ) መቅረፅ
እና ለንግድ ሚኒስቴር ተጠሪ የሆነ ተቋም ማደራጀች፣ እንዲሁም ለፓሊሲው
ተፈፃሚነት የሌሎች ባለድርሻ አካላትን ሃላፊነት እና ድርሻ በመወሰን በቅንጅት
የሚሰራበትን አሰራር ስርአት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡ ይህ አሰራር ከሀገራችን
ተጨባጭ ሁኔታ ጋር የሚጣጣም የፓሊሲ ማዕቀፍ በማዘጋጀት እና ተግባራዊ በማድረግ
ውጤታማ ክትትል እና ቁጥጥር ለማድረግ አቅም ይፈጥራል፤ በዘርፉ የሰለጠነ እና
ልምድ ያለው የሰው ሃይል ለማፍራት ያግዛል፣ ሀገራችን በአለማቀፍ ንግድ ግንኙነት
ለምታቀርበውም ሆነ ለሚቀርብባት ቅሬታም ፈጣን እና ውጤታማ እርምጃ ለመውሰድ
ተሞክሮ ለማዳበር ይረዳል፡፡

8.2.5 የመንግስት ግዥ ፓሊሲን ማሻሻል

የመንግስት ግዥ ለአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነት፣ ተወዳዳሪነት፣ ስራ ፈጠራ እና


ቴክኖሎጅ ሽግግር ለማረጋገጥ የሚያገለግል ቁልፍ የፓሊሲ መሳሪያ መሆኑን የሀገራት
የተግባር ተሞክሮዎች ያረጋግጣሉ፡፡ ልማት ተኮር የግዥ ፓሊሲ አቅጣጫ መከተል
ለጀማሪ ኢንዱስትሪ ከለላ (infant industry protection) ለመስጠት እና ስትራቴጅካዊ
ጠቀሜታ ያላቸውን ኢንዱስትሪዎች ለማነቃቃት አስተዋፅጾው ከፍተኛ ነው፡፡
መንግስት በአንድ ሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ከማንኛውም አካል በላቀ ሁኔታ መጠነ-ሰፊ
ግዥ መፈጸሙ በአምራች ምርት ላይ ገበያ የመፍጠር ተፅዕኖው (demand side
effect) የጎላ እና የግዥ ድጋፍ ከሌሎች የማበረታቻ ስልቶች በበለጠ ውጤታማ መሆኑ
የግዥ ፓሊሲ ለኢንዱስትሪ ልማት ያለውን ቀጥተኛ ፋይዳ ያመለክታል፡፡ ሆኖም
በሀገራችን የፌደራል መንግስት ግዥ ፖሊሲ (ማለትም አዋጅ እና መመሪያ) የአምራች
ኢንዱስትሪ ዘርፍ በመደገፍ በኩል ሰፊ ጉድለቶች ያሉበት ነው፡፡ ከዚህ አንጻር
የመንግስት የግዥ ፓሊሲ የልማታዊ የግዥ መርህ (Developmental Public
Procurment) እንዲላበስ በማድረግ የአምራች ኢንዱስትሪውን ዕድገት ማፋጠን
ተገቢነት አለው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 247


ሀ. ተስማሚ የዋጋ እና የብቃት ልዩ አስተያየት ድጋፍ ማዘጋጀት (preferential
treatment)

የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ አቅምን ያገናዘበ የዋጋ እንዲሁም የብቃት
ልዩ አስተያየት ድጋፍ መዘርጋት ዘርፉ ከአለማቀፍ ምርት አቅራቢዎች ጋር ብቁ
ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀርብ እድል ይፈጥርለታል፤የሀገር ውስጥ ምርት ያለበትን የገበያ
ችግር ያቃልላል፡፡

ከ35% በላይ እሴት ጭማሪ ጣራን መከለስ


ከ35% በላይ በሀገር ውስጥ እሴት የታከለበት ምርት በኢትዮጽያ ውስጥ እንደተመረተ
በመቁጠር በጨረታ ግምገማ ጊዜ የዋጋ ልዩ አስተያየት (ድጎማ) ይደረጋል፡፡ ነገር ግን
የተደነገገው ከ35% በላይ እሴት የመጨመር ጣራ የአምራች ኢንዱስትሪ እድገት ደረጃ
እና ባህሪ ያላገናዘበ፣ በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጅ ትኩረት የተሰጣቸውን ንኡስ
ዘርፎች ለመደገፍ ታስቦ የተቀረፀ አይደለም፡፡ በመጀመሪያ የሀገር ውስጥ የአምራች
ኢንዱስትሪ አጠቃላይ ዕሴት የመጨመር አቅም አነስተኛ ስለሆነ የ35% የእሴት ጣራ
መቀነስ ያስፈልጋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የ35% የእሴት ጣራ የማያሟሉ በርካታ የሀገር
ውስጥ ምርቶች በጨረታ ግምገማ ጊዜ የዋጋ ድጎማ ስለማያገኙ ጨረታ ለማሸነፍ
ይቸገራሉ፤የመንግስት ግዥ ለሀገር ውስጥ ምርት የገበያ እድል ለመፍጠር አይችልም፡፡
ሁለተኛ ለኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጃዊ ጥቅም ያላቸው አምራች ኢንዱስትሪዎች
(ለምሳሌ ገቢ-ምርት የሚተኩ የብረታ ብረት እና ኬሚካል ኢንዱስትሪ) ከሌሎች
አምራች ንኡስ ዘርፎች ጋር ሲነፃፀሩ በጣም ዝቅተኛ ዕሴት የመጨመር አቅም ያላቸው
ናቸው፡፡ ይህን በማገናዘብ ስትራቴጃዊ ፋይዳቸው ላቅ ላለ ንኡስ ዘርፎች በልዩ ሁኔታ
እሴት የመጨመር ጣራ ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ በአጠቃላይ የአምራች ንኡስ ዘርፍ
አቅም እና ስትራቴጃዊ ጠቀሜታ ታሳቢ ያደረገ የዕሴት የመጨመር ጣራ በየደረጃው
በመዘርጋት የዋጋ ልዩ አስተያየት ወይም ድጎማ እንዲያኙ በማደረግ ከገቢ ምርቶች
በተሻለ የጨረታ የበላይነት እንዲኖራቸው ማድረግ እና ለባለሀብቱ ምርት ገበያ
መፍጠር ያስፈልጋል፡፡

የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳግ ማሻሻል (preferential price margin)


በሀገር ውስጥ ተፈላጊውን እሴት የጨመሩ ኢንዱስትሪዎች በጨረታ ግምገማ ጊዜ የዋጋ
ልዩ አስተያየት ህዳግ ወይም ድጎማ ይቀርብላቸዋል፡፡ በዚህ መሰረት ለህክምና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 248


መሳሪያዎች እና መድሃኒት 25% የዋጋ ህዳግ እና ለሌሎች ኢንዱስትሪ ምርቶች 15%
የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳግ ይቀርባል፡፡ ይህ ማለት የውጭ ተጫራቾች ከሚያቀርቡት
ዋጋ ሲነጻጸር የሀገር ውስጥ አምራቾች የሚያቀርቡት የመጫረቻ ዋጋ በ15% ቢበልጥ
እንኳን በጨረታ ግምገማ ወቅት እኩል የመጫረቻ ዋጋ እንዳቀረቡ ይቆጠራል፤
ጨረታውን ማሸነፍ ከቻሉ ደግሞ ከውጭ አቅራቢው ከፍ ባለ ዋጋ ምርት እንዲያቀርቡ
ይረዳቸዋል፡፡ ነገር ግን ለሀገር ውስጥ ምርት የሚቀርበው የ15% የዋጋ ልዩ አስተያየት
በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን ተጠቃሚ ማድረግ አልቻለም፡1)
በስፋት ማምረትና ማቅረብ የሚችለው የውጭ ተጫራች (እንዲሁም አስመጭዎች)
ዝቅተኛ የጨረታ ዋጋ የማቅረብ አቅም ስላለው እና 2) በጨረታ ግምገማ ወቅት
የተጫራቾች ዋጋ የሚነጻጸርበት ስልት (normalized price) የ15% የዋጋ ልዩ
አስተያየት የሚኖረውን ክብደት የሚያሳንስ መሆኑ ናቸው፡፡ ስለሆነም አንደኛው
መንገድ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪ አቅም ባገናዘበ ሁኔታ የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳግ
መጨመር ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ደግሞ ገቢ-ምርቶችን የሚተኩ ኢንዱስትሪዎች
(Import substitution industry) የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳግ በመጨመር ዘርፍን የተሻለ
ተጠቃሚ ማድረግ ያስፈልጋል ምክንያቱም ዘርፉ ታዳጊ እንደመሆኑ መጠን አለማቀፍ
ተወዳዳሪነት አቅም እንዲገነባ በሀገር ውስጥ የገበያ ዕድል ማግኘት ይኖርበታል፤
አምራች ኢንዱስትሪው ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ መዋቅር ሽግግር ለማፋጠን ይረዳል
እንዲሁም ውስን ሆነውን የውጭ ምንዛሬ ሀብት ለመቆጠብ ያግዛል፡፡ ሁለተኛው
አማራጭ በጨረታ ግምገማ ጊዜ የሚቀርበው የ15% የዋጋ ልዩ አስተያየትን ልዩ
ክብደት በመስጠት እና የጨረታ መገምገሚያ መስፈርቱን ምቹ በማድረግ አሰራሩ
ለሀገር ውስጥ ምርቶች የወገነ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በሌላ አገላለጽ የጨረታ
መገምገሚያ መስፈርቶች የሚሰጣቸውን ክብደት እና የተጫራቾች ዋጋ የሚነጻጸርበትን
ስልት ማስተካከል ይቻላል፡፡

ከብቃት መመዘኛ መስፈርት ጋር የተያያዘ የልዩ አስተያየት ድጋፍ መዘርጋት

በግዥ ፓሊሲው ውስጥ እሴት የመጨመር ጣራ እና የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳግ


ማስተካከል ብቻውን የአምራች ኢንዱስትሪውን ተጠቃሚ ያደርገዋል ማለት
አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ፓሊሲው የዘርፉን አቅም ባላገናዘበ ሁኔታ የብቃት መስፈርት
(stringent performance criteria) እንደ ቅድመ ሁኔታ መቀመጡ ነው፡፡ የብቃት
መስፈርት በጨረታ ለመወዳደር እንደ ቅድመ ሁኔታ መቀመጡ እና ተፈላጊውን እሴት

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 249


ያከለ የሀገር ውስጥ ምርትና የውጭ ምርት በተመሳሳይ የብቃት መስፈርት
መመዘናቸው የሀገር ውስጥ ምርት አቅራቢዎች መስፈርቱን ለማሟላት ሲቸገሩ
ይስተዋላል፡፡

ስለሆነም ለሀገር ውስጥ አምራች ልዩ የብቃት መስፈርት (ማለትም አጠቃላይ ልምድ፣


ተዛማጅ የስራ ልምድ፣ የፋይናንስ አቅም፣ የካፒታል መጠን፣ በማምረት ስራ ላይ
የሚሰማሩ ባለሙያዎች የትምህርት ዝግጅትና ብቃት፣ የማምረቻ መሳሪያ ሁኔታ፣
የማምረት አቅም ወዘተ) በማዘጋጀት በጨረታ የመሳተፍ ዕድል ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡
ለምሳሌ በፓሊሲው ውስጥ ለግንባታ ዘርፍ የተደረገለትን የብቃት ልዩ አስተያየት
ለአምራች ዘርፍ ተግባራዊ ቢደረግ ዘርፉ ከግዥ ስርአቱ ተጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡

የስራ ፈጠራ እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልዩ አስተያየት ድጋፍ ማሻሻል

ለስራ ፈጠራ (ጥቃቅን) እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተፈላጊውን ዕሴት ካሟሉ


በብሄራዊ ጨረታ ወድድር ጊዜ ተጨማሪ የ3% የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳግ
ይደረግላቸዋል፡፡ ሆኖም ግን ከኢንተርፕራይዞቹ አጠቃላይ አቅም አንፃር የ3% የዋጋ
ልዩ አስተያየት ህዳግ በጨረታ ተወዳድሮ ለማሸነፍ በቂ መስሎ አይታይም፡፡ የስራ
ፈጠራ እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የዋጋ ልዩ አስተያየት ህዳግ ከ3% ከፍ ማድረግ
ከግዥ ፓሊሲው ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደገፍ ያስፈልጋል፡፡ ሁለተኛ መንግስት
አብዛኛውን ጊዜ በአንድ ጊዜ ጨረታ ከፍተኛ የእቃ ግዥ ስለሚፈፅም ኢንተርፕራይዞቹ
ተፈላጊውን የዕቃ መጠን የማቅረብ አቅም አይኖራቸውም፡፡ ከዚህ አኳያ ተፈላጊውን
የእሴት ማከልና የጥራት መስፈርት ላሟሉ ኢንተርፕራይዞች ለጨረታ ከቀረበው የግዥ
መጠን የተወሰነ እጅ እኩል ተከፋፍለው እንዲያቀርቡ ማድረግ፣ በጋራ በማደራጀት
(consortia formation) እንዲጫረቱ አሰራር መዘርጋት እንዲሁም በጨረታ ያሸነፉ
መካከለኛና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች በንኡስ-ተቋራጭ እንዲያሰሯቸው ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡

ጨረታ ሰነድ ማስረከቢያ ጊዜ እና ምርት ማቅረቢያ ጊዜ መከለስ


የጨረታ ሰነድ ማስረከቢያ ጊዜ እና ምርት ማቅረቢያ ጊዜ ለሀገር ውስጥ ምርት
አቅራቢና ለውጭ ተጫራጭ/ምርት/ አቅራቢ አንድ አይነት ሆኖ እናገኛዋለን፡፡ ይህ
አሰራር ባለሀብቱ ከሰነድ ዝግጅት እስከ ውል መፈጸም ብሎም ምርትን በታቀደው ጊዜና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 250


ቦታ ለማቅረብ ከውጭ አቅራቢው ጋር ሲነፃፀር የአቅም እና ልምድ ችግር ያገናዘበ
አይመስልም፡፡ በመሆኑም ባለሀብቱ የሚሰጠው ጊዜ በንፅፅር አነስተኛ መሆኑ በጨረታ
ለመሳተፍም ሆነ በውሉ መሰረት ምርት ለማቅረብ ችግር እንደፈጠረበት ለመረዳት
ይቻላል፡፡ ስለዚህ ከውጭ ምርት አቅራቢዎች (ተጫራቾች) በተለየ ሁኔታ ለሀገር ምርት
የጨረታ ሰነድ ማቅረቢያ ጊዜ (bids' floating period) እና ምርት የሚቀርብበት ጊዜ
(lead time) መጨመር ተገቢ ነው፡፡

ለ. ለሀገር ውስጥ ምርት ቅድሚያ የሚሰጥ ስርአት መዘርጋት (Domestic preference)

ከፌደራል የመንግስት ግዥ ፓሊሲ መረዳት እንደሚቻለው ጥራት ያለው ምርት


በተመጣጣኝ ዋጋ በሀገር ውስጥ መኖሩ ከተረጋገጠ በብሄራዊ ጨረታ ብቻ ግዥ
ሊካሄድ ይችላል፡፡ ሆኖም ግን በመንግስት ግዥ ስርአት የሚስተዋለው የባለሙያ
አቅም፣ የአመለካከት እና የመልካም አስተዳደር ችግር የተነሳ በርካታ ግዥዎች
የሚፈፀሙት ከአስመጪዎችና በአለማቀፍ ጨረታ አማካይነት ነው፡፡

የግዥ ባለሙያውን አቅም መገንባት እና የአመለካከትና መልካም አስተዳደር ችግር


ለማስተካከል ከሚሰሩ ስራዎች ጎን ለጎን የመንግስት መ/ቤቶች የሀገር ውስጥ ምርት
ቅድሚያ ሰጥተው እንዲገዙ የሚያደርግ አስገዳጅ የግዥ ስርአት ማዘጋጀት
ያስፈልጋል፡፡ ነገር ግን አምራች ኢንዱስትሪዎች የመንግስት ዕቃ ፍላጎት ማሟላት
በሚችሉበት ቁመና ላይ ስለማይገኙ ለመንግስት መ/ቤቶች የሚዘረጋው አስገዳጅ የግዥ
ስርአት በሂደት ተግባረዊ እንዲሆን ተደርጎ መቀረጽ አለበት፡፡
 በበቂ ሁኔታ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ምርቶችን መጠን (በተለይ በሥራ ዕድል
ፈጠራና አነስተኛ ኢንተርፐራይዞች) ጥራት እና ዋጋ በጥናት መለየት የመንግስት
መ/ቤቶች በአመታዊ የግዥ እቅዳቸው አካተው ቅድሚያ ሰጥተው እንዲገዙ
ማድረግ፤ የእቅድ አፈፃፀማቸውን በአመታዊ ሪፓርት ማካተት ያስፈልጋል ፡፡
በሀገር ውስጥ ምርት መሸፈን የማይችለው የመንግስት ግዥ በኮታ ስርአት ከውጭ
እንዲገባ የአሰራር ስርአት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡
 ለሀገር ኢኮኖሚ ስትራቴጃዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ምርቶች (አምሳሌ የካፒታል
እቃዎች) በዝርዝር በመለየት (catalogue of key products) ከፍተኛ ግዥ
በሚፈጽሙ የፌደራል መ/ቤቶች አማካኝነት የገበያ ዕድል እንዲፈጠርላቸው
ማድረግ፣

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 251


 በሂደት አብዛኛው የመንግስት ሀብት በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ እንዲውል
የሚያስችል ጠንከር ያለ አስገዳጅ ፖሊሲ መንደፍ፣ የኢትዩጵያን ምርት ይግዙ
(Buy Ethiopians) መርህ መተግበር ያስፈልጋል፡፡

ሐ. የውጭ ተጫራቾች የሀገር ውስጥ ግብአት በሰፊው እንዲጠቀሙ አቅጣጫ


መቀየስ (Domestic content requirement policy)

በአለማቀፍ ጨረታ ለሚፈጸሙ ግዥዎች የሀገር ውስጥ ግብአት እና ምርት በሰፊው


ለመጠቀም የሚያስችል ስርዐት ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ቁልፍ ጉዳይ
የሀገር ውስጥ ግብአት እና ምርት እንዲጠቀሙ የሚያደርግ ማበረታቻ ወይም የጨረታ
መመዘኛ መስፈርት ማካተት ጠቃሚ ነው፡፡ በተለይ በግዙፍ ግንባታ ስራ ፕሮጀክት
(ግድብ፣ መንገድ፣ ባቡር፣ ኤሌክትሪክ ሃይል ወዘተ) ጨረታ ለሚሳተፍ የውጭ ተቋም
በፕሮጀክት ስፔስፊኬሽን እና በጨረታ መገምገሚያ መስፈርት አማካይነት የሀገር
ውስጥ ጥሬ እቃ፣ የሰው ሃይልና የኢንዱስትሪ ምርቶች ወይም በሀገር ውስጥ ግብአትና
ካፒታል ዕቃ አምርተው እንዲጠቀሙ ማድረግ ያሻል፡፡

መ. የግዥ ቅድመ ክፍያ ምጣኔ ማስተካከል (advance payment)

በጨረታ ላሸነፈ አካል የቅድመ ክፍያ ዋጋ ከአጠቃላይ የውል ዋጋ ከ30% መብለጥ


እንደሌለበት በግዥ ፓሊሲው ተደንግጓል፡፡ ይህ የቅድመ ክፍያ ምጣኔ የሀገራችን
አምራች ዘርፍ የፋይናንስ (በተለይ የስራ ማስኬጃ ፋይናንስ) አቅም ታሳቢ ያደረገ
አይደለም፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በጨረታ ያሸነፈው ባለሀብት የተለያዩ የዋስትና
ማረጋገጫዎች እንዲያቀርብ ይጠየቃል፡፡ አንደኛ ባለሀብቱ ቅድመ ክፍያ የሚሰጠው
በቅድመ ክፍያ መልክ ከሚወስደው ገንዘብ መጠን ጋር እኩል የሆነ ዋስትና ከታወቀ
ባንክ ቸክ ወይም ሌላ ማረጋገጫ ሊያቀርብ ይገባል፡፡ ሁለተኛ ጨረታ አሸናፊው አካል
ከውሉ ጠቅላላ ዋጋ ከ10% ያላነሰ የጨረታ ውል ስምምነት በተደረገ በጥቂት ቀናት
ውስጥ የውል ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ፣ ቸክ ወይም የባንክ ዋስታና በማረጋገጫነት
ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ ስለዚህ የቅድመ ክፍያ መጠን፣ የቅድመ ክፍያ ዋስትና፣ የውል
ማስከበሪያ ዋስትና እና ሌሎች ጉዳዩች ባለሀብቱ ያለበትን የፋይናስ ዕጥረት ያገናዘበ
መሆን አለበት፡፡ በመሆኑም የቅድመ ክፍያ ዋጋ መጠን ከፍ ማድረግ፣ እንዲሁም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 252


የቅድመ ክፍያ እና የውል ማስከበሪያ ዋስትና ማረጋገጫ ስልቶችን ምቹ በማድረግ
የሀገራዊ ባለሀብቱን የውል አፈፃፀም ብቃት ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡

ሠ. የመንግስት ግዥ ስርአት ከሙስና የፀዳና ብቃት ባለው ባለሙያና አመራር


ማደራጀት

በመንግስት ግዥ አስተዳደር የሰለጠነ የሰው ሃይል እጥረት እና ግልፅነት የጎደለው


አድሏዊ አሰራር በሰፊው ይስተዋላል፡፡የመንግስት ጨረታ እየተካሄደ ባለበት ሁኔታ
በስፔስፊኬሽን እና ጨረታ ግምገማ ላይ በሚደረግ የቡድን ሴራ እና ሙስና የግዥ
ባለሙያዎችና የጨረታ ኮሚቴ እንዲሁም ቴክኒካል ግምገማ የሚያካሂዱ ባለሙያዎች
የፈለጉትን የሚያሳልፉበት፣ ያልፈለጉትን የሚጥሉበት እና አቤቱታን የሚያፍኑበት
ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ተንሰራፍቶ ይገኛል፡፡ አንዳንዴ በውስን ጨረታ ወይም
ከአስተማማኝ አቅራቢ የሚገዛ እቃ በግልጽ ጨረታ ከሚገዛው እቃ በዋጋም ሆነ በጥራት
የተሻለ ሆኖ እያለ ደንብና ህግ መከተል አለብን በሚል ሰበብ ጥራት ከጎደለው እቃ
በውድ ዋጋ ሲገዛ ይስተዋላል፡፡ ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች እና ፓሊሲው ለሀገር
ውስጥ ባለሀብት አቅም ያላገናዘበ በመሆኑ አብዛኛው የመንግስት ግዥ ከአስመጭዎች
እንዲሆን እየተደረገ ነው፡፡

ይህን ችግር ለመፍታት አሁን ያለውን የመንግስት ግዥ ኤጀንሲ ለማጠናከር በውስጡ


የሀገር ውስጥ ግዥ እና የውጭ ግዥ ቢሮዎች/ክፍሎች/ በማለት ሁለት ክፍሎች
እንዲኖሩት ማድረግ እንዲሁም ተቋሙን በአመራር፣ በባለሙያና በፋሲሊቲ ማጠናከር
ያስፈልጋል፡፡ማንኛውም ግዥ ምርቱ በጥራትና በተገቢ በዋጋ በከፊልም ሆነ ሙሉ
በሙሉ በሀገር ውስጥ የማይቀርብ መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ብቻ በከፊል ወይም ሙሉ
በሙሉ ወደውጭ ግዥ እንዲያመራ የሚወሰንበት አስራር መኖር አለበት፡፡ በተጨማሪ
የተለመዱ የማዕቀፍ ግዥዎች (framework/ critical bulk purchase) በሀገር ውስጥ እና
በውጭ የሚገኙ የታወቁ አምራቾች ወይም ዋነኛ ወኪሎቻቸው በቀጥታ ድርድር
በረጅም ጊዜ ኮንትራት (multi-year contract) እንዲገዙ ስምምነት የማድረግ አሰራር
ቢኖር የተሻለ ይሆናል፡፡ በተያያዥ የሀገር ውስጥ አምራቾች በአጭር ጊዜ በጣም
በከፍተኛ መጠን ማቅረብ አይችሉም በሚል ምክንያት ከውጭ ቀጥታ የሚገዛበትን
አሰራር በመቀየር የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች የአቅማቸውን እንዲያቀርቡ የሚፈቅድ
አሰራር መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 253


8.2.6 ያልተማከለ የገጠር ኢንዲስትሪ ልማት አቅጣጫ መከተል

በግብርና ላይ በተሰማራው አርሶአደርና አርብቶአደር እየተፈጠረ ያለውን የሀብት


ክምችት ቀጣይ የኢንቨስትመንት ስምሪቱን መምራት (የአሰራር ስርአትና አቅጣጫ
ማስቀመጥ) አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ ከፍተኛ ሀብት ወደ ሚፈለገው ዘርፍ በአግባቡ
ባለመመራቱ አብዛኛው የገጠር አረሶአደር ያገኘውን ሀብት በከተማ ቤት መግዛት፣
መኪና መግዛት፣ ወዘተ እየተጠቀመበት ይገኛል፡፡ ስለዚህ የገጠሩን ሀብታም
አርሶአደርና በገጠር የሚኖሩ የተማሩ ወጣቶች በተናጥልም ሆነ በማደራጀት በአነስተኛ
አምራች ኢንዱስትሪ (በተለይ በአግሮ-ፕሮሰሲንግና የኮንስትራክሽን ግብአት ንዑስ-
ዘርፎች) በብዛት ማሰማራት ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡

ስኬታማ የሆነውን የቻይናን የገጠር የኢንዱስትሪ ልማት ተሞክሮ በመውሰድ፣ ለወረዳ


አመራሮች ወይም ለአርሶአደሩ ቅርበት ላላቸው አካላት ኃላፈነትን በመስጠት፣ በገጠር
የተፈጠሩትን ልማታዊ ባለሀብቶች ከፍተኛ ካፒታል የማይፈልጉ፣ ጉልበትን በሰፊው
የሚጠቀሙ እና እሴት የሚጨምሩ ቀላል ኢንዱስትዎች እንዲገቡ ማበረታታት
አለባቸው፡፡ የሀገራችን የገጠር ኢንዱስትሪ ልማት እውን ይሆን ዘንድ ያልተማከለ
አመራር ይሻል፡፡ በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ ከዞን እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉ አመራሮችን
በገጠር ኢንዱስትሪ ልማት ላይ በተለያዩ መንገዶች እንዲሳተፉ ብቻ ሳይሆን በወሳኝነት
የኢንዱስትሪ ልማቱ ኃላፊነት እንዲወስዱ ማድረግ ያሻል፡፡

ከሁሉ በፊት መንግሥት ያልተማከለ የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እንደ መሠረታዊ


የልማት አቅጣጫ እውቅና ሊሰጠው ይገባል፡፡ ከዚህም ጎን ለጎን ይህ የልማት ሂደትን
የመምራት ኃላፊነት በወሳኝነት የአካባቢ አስተዳደር እንደሆነ ማረጋገጥ ይገባል፡፡
የአካባቢ መስተዳደር አካላት የአካባቢያቸውን ጸጋ በትክክል ለይተው በዚህ ላይ እሴት
ለመጨመር የሚያስችላቸውን አነስተኛ የገጠር ኢንዱስትሪዎች የመምረጥ ኃላፊነት
እንዲወስዱ መድረግ ይገባል፡፡ በተለይ ከዞን እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉ አመራሮች
ከአርሶአደሩ ጋር ቅርበት ያላቸው በመሆኑ አማራጭ የኢንቨስትመንት ሀሳቦችን
ማቅረብ፣ አዋጪ የኢንቨስትመንት መስኮችን በማሳየት፤ በማደራጀት፣ ዕቅድ
በማውጣት፣ ግንዘቤ በማስጨበጥ በማሰልጠን እና ከተሰማሩ በኋላ በቂ ክትትልና ድጋፍ
በማድረግ ጉልበትን በሰፊው የሚጠቀሙ እና እሴት የሚጨምሩ ቀላል ኢንዱስትዎች
ላይ እንዲሰማሩ ማበረታታት ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 254


በተጨማሪ የአካባቢ አስተዳደር በገጠር ቁጠባን በማስፋትና የኢንዱስትሪ ልማት ሼር
ገበያን አሳታፊ በሆነ መንገድ በመፍጠር የገጠር ካፒታል ወደገጠር ኢንዱስትሪ
እንዲሠማራ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ የገጠር ካፒታል የማሰባሰብ ተግባር ከፍተኛ
ኃላፊነት እና ዲሲፒሊን የሚጠይቅ ተግባር ብቻ ሳይሆን በጠራ የአሠራር መመሪያና
ግልፅነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት አኳኋን የሚተገበር እንዲሆን ማድረግ ይገባል፡፡
በአጠቃላይ የገጠር ኢንዱስትሪ የልማት ጉዳይ የሕብረተሰባችን ከመካከለኛ ገቢ ወደ
ከፍተኛ ደረጃ ለማሸጋገር የሚረዳ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ በአካካቢ
መስተዳድር ደረጃ ተፈላጊው የፖለቲካዊ እና መዋቅራዊ አቅም ተገንብቶ ተግባሩን
በብቃት እንዲመራው የማድረግ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡

የግብርና ልማታችን ስኬታማነት ሊመጣ የቻለው ከምንም ነገር በላይ ባልተማከለ


የልማት ሥራ አመራራችን እንደሆነ ሁሉ ያልተማከለ የገጠር ኢንዱስትሩ ልማት
ሥራችንም ሊሳካ የሚችለው በዚሁ ቅኝት በመጓዝ ብቻ ነው፡፡ ከራሳችን የግብርና
ልማት ሆነ ከቻይና የገጠር ኢንዱስትሪ ልማት ተሞክሮ የተማተርነው ይህንን ነው፡፡
ስለሆንም የፌደራል እና የክልል መንግስታት የአካባቢ መስተዳደርን የገጠር ኢንዱስት
ልማት የመምራት አቅም ለመገንባት በልዩ ሁኔታ ሊረባረቡ ይገባል።

ሀ. ከከፍተኛ ኢንዱስት ጋር የተቀናጀ ተመጋጋቢ የገጠር ኢንዱስትሪ ማልማት

የገጠር ኢንዱስትሪ ለከፍተኛ ኢንዱስትሪ በከፊል ያላለቁ ምርቶችን በማቅረብ ቁርኝት


የሚፈጥሩበትን መንገድ መፈለግ አለብን፡፡ የገጠር መካካለኛና አነስተኛ
ኢንዱስትሪዎች የሚያዘጋጇቸውን በከፊል ያላለቁ ምግብ፣ የቆዳ፣ የኮንስትራክሽን፣
ወዘተ ምርቶችን በትላልቅ ከተሞች ወይም የኢንዱስትሪ ማዕከላት ወደ ተሰባሰቡ
ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች እንዲሸጋገሩ ማድረግ ይገባል።ይህ ሲሆን በሀገራችን
ኢንዱስትሪዎች መካከል ቀጥተኛ እና የጎንዮሽ መስተጋር ተፈጥሮ የኢንዱስትሪው
ብዜታዊ ተፅዕኖ ይበልጥ እንዲያድግ ማድረግ ይቻላል፡፡ በሀገራችን በገጠር የሚስፋፉ
ቀላልና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችና በከተሞች የሚፈጠሩ ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች
መካከል ቅንጅትና ተመጋጋቢነት እንዲኖር ከማድረግ አንፃር የመንግሥት የልማት
ድርጅቶችን ኢንዶመንቶችንና ትላልቅ ኢንዱስትሪያሊስቶች ከገጠር ኢንዱስትሪ ጋር
የሚኖራቸውን ትስስር ማጠናከር የተወዳዳሪነትን አቅም ለመገንባት ትልቅ አስተዋፅኦ
አለው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 255


ለ. በገጠር መሰረተ-ልማትን ማስፋፋት

የገጠር ኢንዱስት ልማት መስፋፋት መንገዶች የኤሌክትሪክ ኃይል እና የኮምዩኒኬሽን


አውታሮች ማስፋፋትንና የውሃ ልማትን በሰፊው ማስፋፋት እንደሚጠይቅ እሙን
ነው፡፡ እነዚህ ለኢንዱስትሪ ልማት ወሳኝ የሆኑ ቅድመ ሁኔታዎች ባልተሟሉበት ሁኔታ
የገጠር ኢንዱስትሪን ማልማት አስቸጋሪ ስለሚሆን የገጠር መሰረተ-ልማት ላይ
በትኩረት መስራት አስፈላጊ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 256


8.3 ለተስተዋሉ ችግሮችና ማነቆዎች የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች

8.3.1 ኢንዱስትሪ ፋይናንስና ብድር አቅርቦት ላይ የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች

 የልማት ባንክና የግል ባንኮች የብድር አሰጣጥ ስርዓት በዋናነት በዋስትና ላይ


የተመሰረተ የብድር አሰጣጥ (Collateral based lending) ነው፡፡ ይህ የአሰራር
ስርዓት ለባንኩም ሆነ በሀገራችን ዋስትና ለማቅረብ ከፍተኛ ችግር ያለባቸው
አምራቾች የማይመች በመሆኑ የባንኩ የብድር አሰጣጥ ስርዓት የገንዘብ ፍሰት
መሰረት ያደረገ (cash-flow based lending approch) እንዲሆን በማድረግ
ባለሀብቱን ማገዝ ያስፈልጋል፡፡
 ለአምራች ኢንዱስትሪው ውስብስብ፣ የተንዛዛና ውጣውረድ የበዛበት የብድር
አገልግሎት አሰጣጥ ግልፅነት ያለውና ከኪራይ ሰብሳቢዎች የፀዳ እንዲሁም
በዘመናዊ አሰራር ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
 የአምራች ኢንዱስትሪውን ባህሪ ከሌሎች ዘርፎች የተለየ መሆኑን በመረዳት በዘርፉ
ለተሰማራው ባለሀብት ልዩ የብድር አሰጣጥ ስርአት በመዘርጋት የተራዘመ የብድር
መክፈያ ጊዜ በማመቻቸት በዘርፉ የተሰማራውን ባለሀብት ማበረታታት
ያስፈልጋል፡፡
 አንዳንድ ባለሀብቶች የሚያቀርቡት የብድር ጥያቄ ከአንድ ባንክ አቅም በላይ
የሚሆንበት ወይም ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ ለአንድ ድርጅት ለማበደር ከኪሳራ ሪስክም
ሆነ አስተዳደራዊ አቅም ጋር ተያይዞ ሲቸገሩ ይታያል፡ ይህን ችግር ለማቃለል
ጥምር ፋይናንስ (joint financing) ሁለት ወይም ከዛ በላይ ባንኮች በጋራ አንድ
ፕሮጅክት ፋይናንስ ማድረግ የሚቻልበት አሰራር ቢዘረጋ የተሻለ ይሆናል፡፡
 ሀገራዊ የኢንዱስትሪ ቦንድ የሚዘጋጅበትና የሚሸጥበት አሰራር በመዘርጋት
አስፈላጊ ፋይናንስ በማሰባሰብ ለኢንዱስትሪ አማራጭ የፋይናንሰ ምንጭ ማፈላለግ
(Exploting the possibilities of establishing national industrial bounds)
ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ቦንድ በመሸጥ ካፒታል ማሰባሰብ
የሚችልበት አሰራር ቢከተል፡፡
 የጡረታ፣ ኢንሹራንስና ማህበራዊ ዋሰትና የህብረተሰቡ ማህበራዊ ዋስትና ድህነት
ከማረጋገጥ የዘለለ ለኢንቨስትመንት አገልግሎት የሚውል የረጅም ጊዜ ቁጠባ
ከማረጋገጥ አኳያ ያላቸው ጠቀሜታ ከፍተኛ በመሆኑ በዚህ መልክ እንዲቃኙና

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 257


የተሰበሰበው ገንዘብ ለአምራች ኢንዱስትሪ አማራጭ የፋይናንስ ምንጭ የሚሆንበት
አሰራር መዘርጋት ያሻል፡፡
 ከውጪ በሚገባው ሸቀጥ ላይ የተጣለው ቀረጥ የሀገር ውስጥ አምራቾች
ለማበረታታት ያገዘ ቢሆንም የውጪ ንግዱን ግን ጎድቶታል፡፡ በዚህ ምክንያት
አምራቾች ከውጪ ገበያ ይልቅ የሀገር ውስጥ ገበያ እንዲመርጡ
አድርጓቸዋል፡፡አሰራሩ በታሰበለት አላማ ተጠቃሚ ያደረገው አምራቾች ሳይሆን
ሌሎች ጥገኛ ባለሀብቶችን ስለሆነ እንደገና በጥናት ቢፈተሽ፡፡
 ወደ ሀገራችን ከሚገባው ሸቀጥ 90 በመቶ የአምራች ዘርፍ ውጤቶች ሲሆኑ
ከሀገራችን የሚላከው ከአምራቹ ዘርፍ የሚገኘው ግን የገቢውን 20 በመቶ ያህል
ብቻ ይሸፍናል፡፡ ከዚህ አንፃር የገቢ ንግድ መተካት በተለይ በተነፃፃሪና የተሻለ
ተጠቃሚ የሚሆንበት ላይ በትኩረት ቢሰራበት የተሻለ ይሆናል፡፡
 በሀገራችን በአሁኑ ወቅት የውጭ ምንዛሬ አቅርቦቱና ፍላጎቱ ከፍተኛ ልዩነት
ያለውና የማይጣጣምበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ወደፊትም የአምራች ኢንዱስትሪው
ኢንቨስትመንት በብዛት እየጨመረ ስለሚሄድና የውጭ ምንዛሬ ፍላጎቱም
ስለሚጨምር በአቅርቦቱ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጦት መስራት እንዳለበት
ያመለክታል፡፡
 የተገኘውን የውጭ ምንዛሬም ቢሆን በአግባቡ የመጠቀም ልምዳችን ደካማ በመሆኑ
በተቻለ መጠን ወደ ሀገር ውስጥ ግዥ በማተኮር እንዲሁም የኢንዱስትሪ
ግብአቶችን ከሀገር ውስጥ ገበያ በመግዛት ማተኮር ያስፈልጋል፡፡
 የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ቅድሚያ ለአምራች በተላይ ለኤክስፖርት ኢንዱስትሪ
እንዲሰጥ የወጣውን መመሪያ የተግባር አፈፃፀም ላይ ችግር ያለበት በመሆኑ፤
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ግልፅነት ያለው አሰራር በመዘርጋት የመመሪያውን
አፈፃፀም የሚከታተልበትና የሚገመግምበት ስልት በመቀየስ መቆጣጠር ይገባዋል፡፡
 ለግብርና ኢንዱስትሪ የሚውለው የረጅም እና መካከለኛ ጊዜ ኢንቨስትመንት
በሁለተኛው የእድገት እና ትራንስፎርመሽን እቅድ 154.84 ቢሊዮን ለአምራች
18.62 ቢሊዮን ለግብርና በአጠቃላይ 173.46 ቢሊዮን እንደሚያስፈልግ በየዓመቱ
በአማካይ 34.7 ቢሊዮን መሆኑ እንዲሁም በዋናነት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
እንደሚያቀርብ ተቀምጧል፡፡ የልማት ባንኩ ላለፉት አምስት ዓመታት ለሁሉም
ዘርፍ ያቀረበው ብድር በአጠቃላይ ከ26 ቢሊዮን ብር አይበልጥም፡፡ የ2008
አፈፃፀሙ ብር 6.33 ቢሊዮን ለሁሉም ክፍለ ኢኮኖሚ አበድሯል፡፡ ከዚህ አንፃር
ስናይ በሚቀጥት አምስት ዓመታት የተሰጠው የመካከለኛና ረጅም ጊዜ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 258


የኢንቨስትመንት ብድር ለማቅረብ በእጅጉ ከባድ እንደሚሆንበት ይገመታል፡፡
በመሆኑም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የኢንቨስትመንት
ብድር በማቅረብ የልማት ባንኩን ካላገዘ በስተቀር የአምራች ኢንዱስትሪ የብድር
ፍላጎት በልማት ባንክ አቅም ብቻ መሸፈን አስቸጋሪ እንደሚሆን ከወዲሁ መገመት
ይቻላል፡፡

8.3.2 ኢንዱስትሪ ማበረታቻና ድጋፍ አቅርቦት ላይ የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች

መንግስት በተለይ ለሀገሪቱ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸውን


የአምራች ኢንዱስትሪና ሌሎች ተዛማጅ ዘርፎችን ለማስፋፋትና ለማጠናከር የተለያዩ
ማበረታቻና ድጋፍ ፓኬጆች አቅርቧል፡፡ ነገር ግን እነዚህን ማበረታቻዎችና ድጋፎች
የተግባር አፈፃፀማቸው በተለያዩ ምክንያቶች ደካማ ነው፡፡በዚህ ጥናት ውስጥ በተለይ
ጎላ ብለው የወጡትና የአምራች ኢንዱስትሪውን ባለሀብት በስፋት የተቸገረባቸው
የግብር፣ ታክስና ቀረጥ ይዘት እና አፈፃፀም ችግሮች ከላይ የቀረቡ ሲሆን ለችግሮች
የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

 ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ አሰራር ጋር ተያይዞ ብዙ ፕሮጆክቶች የጉምሩክ ስነስርዓት


ሳይፈፀምና የቀረጥ እዳቸው ሳይከፍሉ / ሳያወራርዱ የሚዘዋወሩና የሚሸጡ እንዳሉ
በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ባደረገው ጥናት አረጋግጧል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ
ንግድ ፍቃዳቸው ወይም የኢንቨስትመንት ፍቃዳቸው በመጠቀም የመብቱ
ተጠቃሚዎች ከሆኑ ከተወሰነ ዓመታት በኋላ ደርጅታቸውን ዘግተው ወይም ሽጠው
በሚሆዱት ላይ የሚወሰድ ርምጃም ሆነ ክትትል፣ በገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን
፣ንግድ ሚኒሰቴር እና ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ የቅንጅት ጉደለት የሚመነጭ
በመሆኑ እነዚህ ተቋማት ተቀናጅተው እንዲሰሩ ከፍተኛ ትኩረት መሰጠት
ይገባዋል፡፡
 በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች የስልጠና፣ የምርምርና ሥርፀት
የገበያ ማፈላለግ፤ ደንበኛች የመሰተንግዶ እና ልምድ ልውውጥ ወጪዎችን
ያደርጋሉ፡፡ እነዚህ ወጪዎች ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘላቂ ተወዳዳሪነት ለመገንባት
እንዲረዳ ሊሚያወጧቸው ወጪዎች ገደብ ወይም ጣራ ተበጅቶላቸው ከገቢ ግብር
ተቀናሽ የሚሆኑበት የአሰራር ስርአት ቢቀየስ መልካም ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 259


 በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ትኩረት የተሰጣቸው ዘርፎች ሆነው ለሀገር ውስጥ
ወይም ለውጭ ገበያ ምርታቸውን የሚያቀርቡ ከኤክሳይስ ታክስ ነፃ መሆን
ይኖርባቸዋል፡፡
 የመንግስት የግብር እና ቀረጥ ማበረታቻዎችን ወስደው ግዴታቸውን ለማይወጡ
ባለሀብቶች ለመቆጣጠር እና ለመከታተል ብሎም አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ
በተቀላጠፈ ሁኔታ ለመውሰድ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ እና የማስፈጸሚያ
ስትራቴጅ ማዘጋጀት ያሻል፡፡

8.3.3 ኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦት ላይ የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች

በሀገራችን ጥጥ፣ ቆዳና ሌሎች ለአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ግብአት የሚውሉ


የግብርና ምርቶችን ለማምረት የሚያስችል ዕምቅ ሀብት ያለን ቢሆንም በሚፈለገው
ጥራት፣ መጠንና ዋጋ ለአምራች ኢንዱስትሪው ማቅረብ አልተቻለም፡፡ በአጠቃላይ
ከላይ የተስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የሚከተሉት የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦችን ግምት
ውስጥ ማስገባት ተገቢ ነው፡፡

 የኢንዱስትሪ ግብአት በሀገር ውስጥ በስፋት የማምረት አቅጣጫን አጠናክሮ


መከተል

በሀገራችን ማምረት የምንችላቸውን የኢንዱስትሪ ግብአቶች በተለይ የግብርና


ውጤቶች ከውጭ ሀገር ማስገባት እንደአቅጣጫ ባይወሰድ ይመረጣል፡፡ይልቁንም
የሀገራችንን ሀብት ተጠቅመን ግብአቶችን በጥራትና በብዛት ለማምረት ትልቅ
ትኩረት ተሰጦት ቢሰራ ቢያንስ ሶስት መሰረታዊ ጥቅሞችን ያስገኛል፡፡ አንደኛው
የውጭ ምንዛሬ ለማዳን፣ ሁለተኛ የሀገር ውስጥ ባለሀብቱን ተጠቃሚ ለማድረግና
ተጨማሪ የስራ ዕድል ለመፍጠር፣ ሶስተኛ ከውጭ ጥገኝነት ለመላቀቅና የግብአት
አቅርቦቱን አስተማማኝና ዘላቂ ለማድረግ ይረዳል፡፡ ስለዚህ መንግስት፡
1)የኢንዱስትሪ ግብአት አምራቹን ማበረታታት አለበት፡፡ መንግስት አምራች
ኢንዱስትሪውን ለማበረታታትና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች ያለቀላቸው እና
የተሻለ ዋጋ እንዲኖራቸው በማሰብ በተለያዩ ጊዜያት በልዩ ልዩ የግብርና ውጤቶች
(ጥጥ፣ ጥሬ ቆዳ እና ሌጦ፣ ወዘተ) ላይ እሴት ሳይጨመር ወደ ውጭ እንዳይላኩ
ገደብ ጥሏል፡፡ከዚህ በተጨማሪም በተወሰኑ የግብርና ምርቶች (ለምሳሌ፡ የጥሬ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 260


ቆዳና ሌጦ) ላይ መንግስት የመሸጫ ዋጋ ለመወሰን ሙከራ ያደረገበትም ወቅት
ነበር፡፡ ይህ አሰራር አምራች ኢንዱስትሪውን የሚያበረታታ ቢመስልም በሌላ በኩል
ግን በግብርና የተሰማራው አርሶአደርና አርብቶአደር እንዲሁም የግል ባለሀብቱ
ላመረቱት የግብርና ምርት አማራጭ ገበያ እንዳይኖራቸው አድርጓል፡፡ በመሆኑም
ላመረቱት ምርት ተገቢውን ዋጋ እንዳያገኙና በሀገር ውስጥ ያለው ገበያ ላይ
እምነት በማጣት ምርታቸውን በስፋትና በጥራት እንዳያመርቱ አድርጓቸዋል፡፡
ስለዚህ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የግብርና ምርት አምራቹን በማይጎዳና
ይልቁንም በብዛትና በጥራት እንዲያመርት በሚያበረታታ ሁኔታ አሰራሩን መከለስ
ያስፈልጋል፡፡ በተጨማሪም ከገበያው ፍላጎት በላይ ትርፍ ከተመረተ አምራቹን
(አርሶአደሩ /አርብቶአደሩ /ባለሀብቱን) በማይጎዳና ቀጣይ አቅርቦትን በሚያረጋግጥ
ሁኔታ ግብይቱ ሊካሄድ እንደሚገባ ግልጽ አሰራር እና የህግ ማህቀፍ ማዘጋጀት
ያስፈልጋል፡፡ 2) በሰፋፊ እርሻዎች የግል ባለሀብቱ በስፋት እንዲሰማራ ሊያበረታታ
የሚችል አሰራር መዘርጋት (ለምሳሌ መንግስት የመሬት ዝግጅት ወጪን
እንዲያግዝ፣ የአዋጭነት ጥናት እንዲያጠና ማድረግ) ያስፈልጋል፡፡
 የኢንዱስትሪ ግብአት ጥሬ ዕቃ ክላስተር፡ አርሶአደሮች በየአካባቢያቸው
ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚሆን ተመሳሳይ ምርት በብዛትና በጥራት ማምረት
የሚያስችላቸውን አደረጃጀት (Clustering) በመዘርጋት ከአምራች ኢንዱስትሪው
ባለሀብት ጋር ተሳስረውና ተቀናጅተው እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠር ያስፈልጋል፡፡
ይህ አሰራር ለሁለቱም ወገኖች ጥቅም ያስገኛል፡፡ በአንድ በኩል የአምራች
ኢንዱስትሪ ባለሀብቱ አርሶአደሮች ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂን ተጠቅመው
ምርታቸውን በሚፈለገው የአቅርቦት መጠንና ጥራት አምርተው እንዲያቀርቡለት
አስፈላጊውን ዕገዛ ለማድረግ የሚረዳ ሲሆን በሌላ በኩል ሁለቱም ወገኖች
ፍላጎታቸውን ተናበው ለጋራ ጥቅም እንዲሰሩ ያደርጋቸዋል፡፡ በተጨማሪም
በአቅራቢያቸው በካፒታል የሚረዱ፣ የእርሻ ግብአቶችና መሳሪያዎች የሚያቀርቡ
ተቋማት እንዲሁም የማሰልጠኛና ምርምር ጣቢያዎች የመክፈት ዕድላቸው ከፍተኛ
ይሆናል፡፡
 ጥሬ ቆዳ ለፋብሪካዎች በጥራት ማቅረብ ይቻል ዘንድ አርብቶአደሩና ከፊል
አርብቶአደሩ በዘመናዊ መንገድ የእንስሳት እርባታ እንዲያካሄድ እንዲሁም
ከእንስሳት እርድ ጀምሮ ጥሬ ቆዳው ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እስኪደርስ ተገቢው
አያያዝ እንዲደረግለት ማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተግባር በመሆኑ
ድርሻቸውን በትክክል እንዲወጡ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 261


በተጨማሪም በቆዳ ጥራት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እየፈጠሩ ያሉትን ችግሮች
ለማስወገድ ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘዴን ማስፋፋትና ማጠናከር ተገቢ ነው፡፡
 ከውጭ ሀገር ለሚገቡ የኢንዱስትሪ ግብአቶች በፍጥነት ማስገባት፣ የትራንስፖርትና
ሎጂስቲክስ ዋጋ ተወዳዳሪ ማድረግ፣ በአስመጪነት የሚሰማሩ ባለሀብቶች
የኢንዱስትሪ ግብአት በማስመጣት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ከንግድ ፈቃድ
አሰጣጥ ጀምሮ መከታተልና የማስተካከያ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል፡፡
በተጨማሪም ጉምሩክ እና ተያያዥ መ/ቤቶች አሰራራቸውን በኢንፎርሜሽን
ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

 የኢንዱስትሪና የግብርና ሴክተሮች በቅንጅት ተናበው እንዲሰሩ የአሰራር ስርአት


መፍጠር
በኢንዱስትሪና ግብርና ሴክተሮች መካከል አስተማማኝ የመረጃ ልውውጥ
የሚካሄድበትን ስርዓት መዘርጋት (Developing reliable information exchange
system between agriculture and industry sectors- MoA, MoI and
manufacturers) ያስፈልጋል፡፡ ከአጭር ጊዜ አኳያ የተሟላና ትክክለኛ መረጃ
ለአምራች ኢንዱስትሪው ማድረስ እንዲቻል ግብርና ሴክተሮች ስለ ግብርና ምርቶች
ዓይነት፣ ጥራትና የምርት መሰብሰቢያ ጊዜ፣ ወዘተ የመሳሰሉ መረጃዎችን ማዘጋጀት
ያሻዋል፡፡ አምራች ኢንዱስትሪ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በበኩላቸው ምን ዓይነት
የግብርና ምርት፣ ምን ያህል፣ በምን የጥራት ደረጃ፣ መቼ እና የት አካባቢ
እንደሚያስፈልግ (firms’ effective demand) የሚገልፅ የተሟላ መረጃ የግብርና
ምርቶች ማምረት ከመጀመሩ በፊት /in advance of the production season/
ለሚመለከታቸው የግብርና ሴክተሮች ሊያሳውቅ ይገባል፡፡ የመረጃ ልውውጡ
አምራች ኢንዱስትሪውን ለማጠናከር ከማገዙም በላይ አላስፈላጊ ሀገራዊ የሀብት
ብክነትን ለማስወገድ ይጠቅማል፡፡ በተጨማሪም መረጃው በቅድሚያ ለግብርና
ሴክተሮች እንዲደርስ መደረጉ በሰብል ማምረት እና በእንስሳት ሀብት ልማት
የተሰማሩ አርሶአደሮች እና አርብቶአደሮች በሚፈለገው ምርት ላይ ትኩረት ሰጠው
እንዲሰሩ ያግዛቸዋል፡፡ በመሆኑም የግብርና ሴክቶሮች ዕቅዳቸውን ሲያወጡ
ከኢንዱስትሪ ሴክተሮችና ከአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች በተገኘው መረጃ
መሰረት ቢሆን ለሁሉም ወገን ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 262


8.3.4 ኢንዱስትሪ ምርቶች ገበያና የንግዱ ስርአት ዙሪያ የቀረቡ መፍትሄ ምክረ-
ሐሳቦች

 የጥራት እና ደረጃ ቁጥጥር አቅምን ማጎልበት፡ የጥራት እና ደረጃ የጠበቀ ምርት


በገበያ ላይ እንዲውል የንግድ ሚኒስቴር፣ የንግድ አሰራር እና ሸማቾች ባለስልጣን፣
የደረጃ እና ስነልክ ተቋማት፣ ገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን፣ ወዘተ አዋጅ/በህግ
በተሰጣቸው ስልጣን መሰረት የበኩላቸውን እየሰሩ ቢገኙም የአምራች ዘርፍ ጥራት
እና ደረጃ የጎደላቸው ምርቶች በሚፈጥሩት ኢፍትሃዊ ውድድር ምክንያት ለኪሳራ
መጋለጥ፣ በቅናሽ ምርትን ለመሸጥ መገደድ፣ ለእቃዎቻቸው ገዥ ማጣት ብሎም
ከገበያ የመውጣት እጣፈንታ ተደቅኖበት ይገኛል፡፡ የድርጊት መርሃ ግብር በቅንጅት
አለመፈጸም፣ የተቋማዊ አቅም ውስንነት፣ የአመራር ቁርጠኝነት እና አመለካከት
ችሮች የታሰበውን ያህል መሰራት አልተቻለም፡፡ በመሆኑም ችግሩን ከምንጩ
ለማድረቅ የሚያግዙ ስልቶችን ንድፎ ርብርብ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
 የህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ትግበራ ላይ ጠንካራ ርብርብ ማድረግ፡ ጥራትና
ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶችን ለመከላከል ታልመው የተዘጋጅ እንደ ንግድ አሰራር
እና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ፣ ደረጃ አዋጅ፣ ተስማሚነትና ምዘና አዋጅ፣ የወንጀል ህግ፣
የንግድ ህግ፣ የገቢዎችና ጉምሩክ አዋጅ እና የመሳሰሉትን በአግባቡ በስራ ላይ
ያለማዋል ችግር በሰፊው ይስተዋላል፡፡ ስለሆነም የመንግስት አስፈፃሚ አካላት የወጡ
ህጎችን፣ አዋጆችንና መመሪያዎችን ተገቢው መንገድ በስራ ላይ እንዲያውሉ
የተጠናከረ እና ቅንጅታዊ ስራ ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡ እንዲሁም በየደረጃው ያሉ
ፈጻሚ አካላትን ተጠያቂነት በሚፈጥር መልኩ የክትትል እና ቁጥጥር ተግባር
ማጠናከር ይገባል፡፡
 ህገወጥ ንግድን ለመቆጣጠር ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተጀመሩ የሁለትዩሽ
ስምምነቶችን ማጠናከርና እና በቅንጅት መስራት፡ ጥራት እና ደረጃ የጎደላቸው
ምርቶች በገበያ ላይ መስፋፋት ዋነኛ ምክንያት የኮንትሮባንድ ንግድ በመሆኑ
በድንበር አካባቢ የሚደረገውን ህገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ለማጠናከር እንዲያስችል
ከጎረቤት ሀገራት የጋራ ስምምነት ማድረግ፣ የጋራ ተቋማትን መፍጠር እና መተግበር
የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሁኔታ የመከላከል ስራ መስራት
ያስፈልጋል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 263


 ደረጃ ላልወጣላቸው ምርቶች ደረጃ ማውጣት እና ጥራትና ደረጃን ለመቆጣጠር
ተቋማዊ አቅም መገንባት፡ አንደኛ የጥራት እና ደረጃ ተቋማት ጥራት እና ደረጃ
ችግር ተጋላጭ ለሆኑ ምርቶች ቅድሚያ በመስጠት አስገዳጅ ደረጃ ማዘጋጀት፡፡
ሁለተኛ ደረጃ ተቋማትን የሰው ሀይልና ፋሲሊቲ አቅምን በማጎልበት በሀገራዊ ምርት
ላይ የጎላ ችግር የሚፈጥሩትን ምርቶች ላይ ትኩረት በመስጠት የቁጥጥር ስራውን
ማከናወን ያስፈልጋል፡፡ በተጨማሪ ጥራትና ደረጃ መስፈርቶችን በማሻሻል አለማቀፍ
ጥራትና ደረጃውን የጠበቁ ምርቶችን ስብጥር ማሳደግ ተገቢ ነው፡፡
 አላስፈላጊና ዕሴት የማይጨምር የኢንዱስትሪ ግብአት የግብይት ሰንሰለት ለማሳጠር
ይቻል ዘንድ የኢንዱስትሪ ግብአት አምራቾችንና የአምራች ኢንዱስትሪ
ባለሀብቶችን የሚያገናኙ (የአርሶአደሮች፣ ዩኒዮኖችና የሸማቾች ማህበር) በመፍጠርና
በማጠናከር የተቀናጀ ፍትሀዊ የገበያ ስርአት በመዘርጋት የተጋነነ የዋጋ ንረትን
ማስወገድ ያስፈልጋል፡፡
 የንግድ ፈቃድ እና ምዝገባ ስርአቱ ለአምራች ኢንዱስትሪው ጥሬ እቃ እና በከፊል
ያለቀላቸው ግብአት የሚያገለግሉ ምርቶችን ለሚያስመጡ ተቋማት ትኩረት
ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም አስመጭዎች በብዛት የሚገኙባቸውን (crowded)
ዘርፎች የንግድ ፈቃድ እና ምዝገባ መቀነስ ያስፈልጋል፡፡
 የገበያ ከለላ የተደረገላቸው የገቢ ምርቶን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የገበያ
ከለላውን በሞኖፖል አለመያዙን፣ የከለላ ተጠቃሚዎች በበቂ መጠን ለገበያ
መቅረባቸውን እና የገበያ ከለላው የተፈለገውን አላማ መምታቱን በማረጋገጥ ብሎም
የተዛባ የገበያ ውድድር ስርአትን የማያስከትል መሆኑን በየጊዜው በመከታተል
ማስተካክያ እርምት መውሰድ ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም የገበያ ከለላ የተሰጣቸው ጥሬ
እቃዎችና በከፊል ያለቁ የኢንዱስትሪ ምርቶች አቅራቢ ተቋማት በተፈለገው ዋጋ፣
ጥራትና ብዛት ሳያጓድሉ እንዲያቀርቡና ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር ትስስርና
ቅንጅት እንዲኖራቸው ሁኔታዎችን ማመቻቸት አስፈላጊ ነው፡፡ በተጨማሪም
በሀገሪቱ የታሪፍ ስርአት የፈጠረውን የገበያ ከለላ እንዲሁም መንግስት የሚሰጣቸው
ማበረታቻዎች ታክሎበት ኤክስፖርት-ተኮር እቃዎችን አምራች ኢንዱስትሪዎች
በሀገር ውስጥ ገበያ የመወሰን አዝማሚያን ለማስቀረት ኢንዱስትሪው ግዴታውን
እንዲወጣ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
 በሰፊው የሚስተዋለውን ፀረ-ውድድር እና ህገ-ወጥ ንግድን ለማምከን ወይም
ለመከላከል በተለያዩ የመንግስት እርከን ያሉ ተቋማትን የአፈፃፀም አቅማቸውን
በማሳደግ ተያያዥ ፓሊሲዎችን ወቅታዊነታቸውን እንዲጠብቁ ማስቻል

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 264


ያስፈልጋል፡፡ በተለይ ደግሞ የአምራች ኢንዱስትሪ ማህበራት እና የህዝብ ክንፎችን
ቀጥተኛ ተሳታፊ በማድረግ ከመንግስት ተቋማት ጋር በጋራ መስራት የሚያስችል
ስትራቴጅ መቀየስ ያስፈልጋል፡፡
 ህገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድን በተለይ በሀገሪቱ የጠረፍ ከተሞች ላይ እንዳይስፋፋ
የተጀመረው ስራ አጠናክሮ በመቀጠል እና ከውጭ የሚገቡ ምርቶች የሚፈለገውን
የጥራት ደረጃ ያሟሉ እና ተገቢ ዋጋ እንዲኖራቸው ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
 የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ፣ የዕድሳት፣ የማሻሽያ እንዲሁም የስረዛ አሰራር
ስርአቶችን ንግድ ሚኒስቴር እና የክልል/ የከተማ ንግድ ቢሮዎች መካከል ወጥ-ነት
ያለው እንዲሆን ማስቻል፤ የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ አሰጣጥ ውጣ ውረድ
በመቀነስ ቀልጣፋ እና ፍትሃዊ ለማድረግ በተለያዩ እርከን የሚገኙ ተቋማት ቅንጅዊ
እና ተጠያቂነት የሚፈጥር አሰራሮችን ለመፍጠር ጥረት መደረግ አለበት፡፡
 የነፃ ቀረጥ ተጠቃሚ የሆኑ ዘርፎች (ማለትም ከአምራች ኢንዱስትሪው ወጪ ያሉት)
ከውጪ ለሚያስገቧቸው ግብአቶችና በከፊል ያለቀለት ዕቃዎች ላይ የመጠን
መስፈርት (Standard) እና ክትትል ስልት በማጠናከር ከፍላጎታቸው በላይ ወደ ሀገር
አስገብተው ለሌላ አላማ (ሽያጭ) የሚያውሉ አካላትን ለመከላከል ያስችላል፡፡
 የንግድ ስርአቱን የሚያዛቡና ማህባራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸው አናሳ የሆኑ የውጭ
ዕቃዎችን በጥናት ላይ ተመስርቶ በመለየት የኢምፖርት መጠናቸው እንዲቀንስ
ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
 የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ የፈጠራና የቴክኖሎጅ አቅም ለማጠናከር በጨረታ
መመዘኛ መስፈርቶች ውስጥ የፈጠራና የቴክኖሎጅ መመዘኛዎችን ማካተት አስፈላጊ
ነው፡፡ ለምሳሌ የምርምርና ስርፀት ክፍል (R&D Department) ያላቸው አምራቾች
ለጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ቴክኖሎጅና ዕውቀት የሚያሸጋግሩ መካከለኛና ከፍተኛ
አምራች ኢንዱስትሪዎች እና የመሳሰሉትን መስፈርቶች በማወዳደሪያ የጨረታ ሰነድ
ውስጥ ማካተት አስፈላጊ ነው፡፡
 ከሀገሪቱ የልማት ፍላጎት ጋር የሚጣጣሙ የካፒታል እቃዎች ወይም የገቢ እቃዎችን
የሚተኩ ምርቶችን (import substitution) በመለየት በግዥ ማዕቀፉ የልዩ አስተያተት
ተጠቃሚ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
 በአብዛኛው የሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪው የባለቤትነት አደረጃጀት ሀላፊነቱ
በተውሰነ የግል ማህበር እና በግለሰብ የተያዘ ሲሆን በአክስዮን ማህበር የተደራጁ
ተቋማት ቁጥራቸው ውስን ነው፡፡ የአክስዮን ማህበራት አደረጃደት እውቀት፤
ካፒታል፤ ቴክኖሎጅ እና ዘመናዊ አመራርን ለማቀናጀት ምቹ ቢሆንም አሁን

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 265


ባለው ሁኔታ በማህበራቱ ውስጥ የመልካም አስተዳደር እጦት፤ የንግድ ህጉ ላይ
የሚስተዋሉ ጉድለቶች እና አስፈጻሚ አካላት ቁጥጥርና ድጋፍ ማነስ ምክንያት
ለአምራች ኢንዱስትሪው እድገት ያበረከተው ፋይዳ አነስተኛ ሆኖ ይገኛል፡፡
ስለሆነም የማህበራቱን መልካም አስተዳደር ደንቦች እና የንግድ ህጉን ማሻሻል
እንዲሁም ድጋፍ ተቋማትን አቅም መገንባት ያስፈልጋል፡፡

8.3.5 በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ ለተስተዋሉ ችግሮች የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-


ሐሳቦች

በቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት ሂደት ውስጥ የመንግስት፣ የምርምር ተቋማት እና የግሉ


ባለሀብት ሁሉም በየፊናቸው የሚጫወቱት ሚና አለ፡፡ የቴክኖሎጂ ሽግግሩ በተፈለገው
ፍጥነት እንዲሄድ እና የታለመለትን ዓላማ እንዲያሳካ ካስፈለገ ባለድርሻ አካላቱ
ተናበውና ተቀናጅተው መስራት አለባቸው፡፡ በመሆኑም በሀገራችን ከቴክኖሎጂ ሽግግር
ጋር ተያይዞ ከላይ የተነሱ ችግሮችን ለመፍታት የሚከተሉትን ምክረ-ሀሳቦች ግምት
ውስጥ ማሰገባት ያስፈልጋል፡፡

 በቴክኖሎጂ ሽግግርና በኢንዱስትሪ ልማት ስኬታማ ከሆነ የሩቅ ምስራቅ ሀገራት


መረዳት እንደሚቻለው የቴክኖሎጂ ፖሊሲ ለዕድገታቸው መፋጠን ወይም መዘግየት
ትልቅ አስተዋፅኦ አለው፡፡ በሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ በሀገር አቀፍም ይሁን በተቋም
ደረጃ ቴክኖሎጂ እንዴት እና በምን ሁኔታ ማሸጋገር እንዳለብን ሊመራ የሚችል
ግልጽ ፖሊሲ የለንም፡፡ በመሆኑም ምን ዓይነት ቴክኖሎጂ ከማን፣ እንዴት እና
በምን ስልት ማሸጋገር እንደምንችል፣ በምን ዓይነት ተቋማዊ አደረጃጀት፣ ከየት
በሚገኝ ፋይናንስ፣ በምን ዓይነት የህግ ማዕቀፍ፣ ወዘተ በግልፅ ያስቀመጠ እንዲሁም
ከዕድገታችን ጋር አብሮ የሚሄድ የቴክኖሎጂ ሽግግር ፖሊሲ ሊኖረን ይገባል፡፡ በሌላ
በኩል ከአጭር ጊዜ አንፃር በቴክኖሎጂ ሽግግር መንግስት የመሪነትን ሚና
እንዲጫወት ማድረግ፤ ለዚህም ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትና ከሌሎች ምንጮች
የሚገኙ ቴክኖሎጂን የማሸጋገርና የማልማት ስራውን በባለቤትነት የሚያስፈፅም
ተቋም ያስፈልጋል፡፡ ተቋሙ በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ከፍተኛ ሚና ካላቸው
የመንግስት ተቋማት ጋር ግልፅ የአሰራር ግንኙነትና አቅጣጫ ሊኖረው ይገባል፡፡
በመሆኑም በፌደራልና በክልል ደረጃ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት ስራን ለማሳጠን
በባለቤትነት ትኩረት ሰጦ የሚመራ፣ ቴክኖሎጂ ሸግግር ባለድርሻ አካላትን
የሚያስተባብርና የሚከታተል፣ ውጤቱን በመገመገም ክፍተቱን የሚለይ እንዲሁም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 266


ከአደረጃጀት፣ ከህግ እና ከፋይናንስ አንጻር ያለባቸውን ችግር በመፈተሸ የማስተካከል
ስራ የሚሰራ ተቋም ያስፈልጋል፡፡
 እንደኛ ባሉና የጎላ የገበያ ክፍተት በሚታይባቸው ታዳጊ ሀገራት ብቃት ያላቸው
ደጋፊ ተቋማት (የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩቶች) ማደራጀት የግሉን ዘርፍ
ተወዳዳሪነት ለማጠናከርና የኢንዱስትሪ ልማትን በማፋጠን መዋቅራዊ ለውጥ
ለማምጣት ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ነባር ተቋማት ያለማቋረጥ
አቅማቸው እንዲገነባ ማድረግና የታለመላቸውን ዓላማ እንዲያሳኩ የሚያስችላቸውን
ብቃት ወቅቱ ከሚጠይቀው ፍላጎት ጋር በማስተሳሰር የመስጠት፣ አዳዲስ
የተቋቋሙትም መሰረተ-ልማት ከማሟላት ጀምሮ የተሟላ ቁመና እንዲኖራቸው
የማድረግ፣ ከፋሲሊቴሽን ይልቅ የተቋቋሙበትን ዓላማ በማስፈጸም ላይ እንዲያተኩሩ
የማድረግ፣ የተቋማት ትስስርን በመፍጠር (ኢንዱስትሪውን ከዩኒቨርስቲዎች፣
ከቴክኒክና ሙያ፣ ከምርምር ተቋማት) የሚፈለገውን የሰው ሀይል ልማት
የሚሰለጥንበት፣ የምርምርና ስርጸት ስራዎች የሚዳብሩበት ሁኔታ እንደሚመቻች
ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በተጨማሪም የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩቶች ከቴክኒክና
ሙያ ተቋማት ጋር ተቀናጅተው እንዲሰሩ በማድረግ ተደራሽነታቸውን ማስፋት
በዚህም የክልል መንግስታት ከእነዚህ ኢንስቲቱቶች ቀጥተኛ ድጋፍ እንዲያገኙ
ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
 ከውጭ የሚመጣ ባለሀብት ከሀገር ውስጥ ባለሀብት ጋር በአሽሙር ሽርክና እንዲሠራ
ሊያበረታታ የሚያስችል የማበረታቻ ስርዓት መዘርጋት፣ ይህንንም የግብር እፎይታ
ጊዜን በማራዘምና ከቀረጥ ነፃ የሆኑ ግብአቶች ለተራዘመ ጊዜ እንዲያስገባ በማድረግ
እንዲሁም ሀገር ውስጥ ያለውን ሰፊ ገበያ እንደ ማበረታቻ እንዲጠቀም በማድረግ
ሊሆን ይችላል፡፡ ካስፈለገም ከሀገር ውስጥ ባለሀብት ጋር እንዲሰራ የሚያስገድድ
ስልት መጠቀም፤ በአሁኑ ወቅት የውጭ ባለሀብቱ የሚመራበትን ህግና ደንብ
በማሻሻል ማለት ነው፡፡
 በቴክኖሎጂ አቅማቸው እና በአመራር ጥበባቸው መልካም ስም ያላቸውን የውጭ
ኩባንያዎች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ መደገፍና ማበረታታት
(ልዩ ድጋፍ መስጠት)፤ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብን ስናስብ እና
ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ስንለካ በሚፈጥሩት የስራ ዕድል እና በሚያስገኙት የውጭ
ምንዛሬ ብቻ ሳይሆን በሚፈጥሩት የቴክኖሎጂ አቅምም ቢሆን መልካም ነው፡፡
በተጨማሪም ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ልንቀስመው የሚገባን አዳዲስ
ቴክኖሎጂዎችን ለይተን በየዓመቱ አቅደን መስራት ይጠበቅብናል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 267


 የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቱን በትላልቅና ግዙፍ የመንግስት
አምራች ኢንዱስትሪዎች እና ፕሮጀክቶች ውስጥ በንኡስ-ተቋራጭነት በማሳተፍ
የቴክኖሎጂ ሽግግሩንና የአመራር ብቃቱን ማጎልበትና ማሳደግ ያስፈልጋል፡፡
በተጨማሪም የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲያሳልጥ በመንግስት የተቋቋመው ድርጅትም4
አቅሙን እንዲያጎለብት በማድረግ አነስተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች እያጋጠማቸው
ያለውን የቴክኖሎጂ አቅም ክፍተት በመፍታት ወደ መካከለኛ ኢንዱስትሪ
የሚያደርጉትን ሽግግር ማፋጠን ይገባል፡፡
 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የምርምር ማዕከላት ምርታማነትንና ተወዳዳሪነትን
ሊያጎለብቱ የሚችሉ ወቅታዊ ቴክኖሎጂዎችን ከዓለም ገበያ በማፈላለግ
የማስተዋወቅ፣ የማላመድ፣ የማበልጸግና አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲጠቀሙበት
ማድረግ፤ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም የሚያጋጥማቸውን ችግሮች በቅርበት
በመከታተልና መፍታት፣ የክህሎት ክፍተቶችን እየለዩ ለፋብሪካ አመራሮችና
ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት፤ የመሳሰሉ ስራዎችን የማገዝ ሀላፊነታቸውን
በአግባቡ ሊወጡ ይገባል፡፡ ለምሳሌ አምራች ኢንዱስትሪ እያጋጠመው ያለውን
የቴክሎጂ ልማትና ሽግግር ዓቅም ውስንነት ዩኒቨርስቲዎች በጥናትና ምርምር
ሊፈቱት ይገባል፡፡ ነገር ግን ይህን በተግባር ለማስፈፀም የሚያስችል ግልፅና ዝርዝር
አሰራር የሌለ በመሆኑ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ አዲስ አሰራር አውጥቶ
በስራ ላይ ማዋል ያስፈልጋል፡፡ በተጨማሪም በፈጠራ የተገኙ አዋጭ የሆኑ
የምርምር ውጤቶች የበለጠ የማበልጸግ፣ የማባዛት፣ የማስተዋወቅና ለገበያ የማቅረብ
ስራዎችን መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡
 በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማራ የግሉ ባለሀብት ለአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በሩን
ክፍት ማድረግ፤ በምርምር ተቋማት የሚካሄዱ ቴክኖሎጂን የማላመድና የማበልጸግ
ስራዎች ማገዝ፤ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ከምርምር ተቋማት ጋር በጋራ
ተቀናጅቶ መስራት፤ ቀጣይነት ባለው መልኩ የሰው ሀይል አቅም ግንባታ ስራዎችን
እና የምርምርና ስርፀት ስራዎችን ትኩረት በመስጠት በመስራት ቴክኖሎጂን
የመቀበልና የማበልፀግ አቅሙን ማሳደግ ይጠበቅበታል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢ
ያሉ ተመሳሳይ ኢንዱስትሪዎች (በሀገር ውስጥ /በውጭ ባለሀብት የተቋቋመ)
እየተጠቀሙ ያሉትን ወቅታዊ ቴክኖሎጂዎችን በማጥናት ለመኮረጅ ጥረት ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡

4
የ ብረታ ብረትና ኢንጂነ ሪንግ ኮርፖሬሽን (METEC) በሀገ ሪቱ ቴክኖሎጂን ለአነ ስተኛ እና መካከለኛ ኢንደስትሪዎች
እንዲያሸጋግር ሀላፊነ ት ተሰጥቶታል፡ ፡
የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 268
 ውጤታማ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲኖር መንግስት የቴክኖሎጂ ሽግግርን ሊያሳልጥ
የሚችል የማበረታቻ ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የምርምርና
ስርጸት ማእከል ከፍተው ጥረት ለሚያደርጉ የግል ባለሀብቶች የተለየ ማበረታቻ
ስርዓት መዘርጋት፤ በቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤታማ የሆኑ ተቋማትን እውቅና
መስጠትን እንደ አንድ ማበረታቻ መተግበር ያስፈልጋል፡፡
 በሁሉም ኢንዱስትሪ ሴክተር ተቀጥረው ለሚሰሩ የክህሎት ክፍተት ላለባቸው
ሰራተኞች አጫጭር ስልጠና የሚሰጥበት ሁኔታ ማመቻቸት ያስፈልጋል፡፡ይህንንም
በየአካባቢው ባሉ ዩኒቨርስቲዎችና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በኩል ተፈጻሚ ማድረግ
ይቻላል፡፡ ስልጠናው ለትላልቅና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በስራ ቦታቸው
እንዲሁም ለአነስተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በኢንዱስትሪ ክላስተር መንደሮች
ሊሆን ይችላል፡፡

8.3.6 በአምራች ባለሀብቱ ዙሪያ ለተስተዋሉ ችግሮች የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች

የግል ባለብቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሞተርነት ሚናውን እንዲጫወት


የመንግስትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጥረት እንዳለ ሆኖ ባለሀበቱ ራሱ መሪና ዋና
ተዋናይ መሆን ይጠበቅበታል፡፡ የግል ባለብቱ የራሱን ችግሮች በመለየትና በመገምገም
ችግሮቹን ወደ ሌላ አካል ከመግፋት ይልቅ ራሱን ግንባር ቀደም የመፍትሄው አካል
አድርጎ መንቀሳቀስና የኢንዱስትሪ ልማቱ በታለመለት አቅጣጫ እንዲጓዝና ውጤታማ
እንዲሆን ከመቸውም ጊዜ የበለጠ ሀላፊነቱን ለመወጣት ብዙ መስራት ይጠበቅበታል፡፡
ባለሀብቱ ልማታዊ አስተሳሰብ የተላበሰ የኢንዱስትሪ ባለቤት በመሆን ኢንዱስትሪ
ልማትና ትራንስፎርሜሽን እውን ለማድረግ ሀላፊነቱን ይወጣ ዘንድ የሚከተሉት ምክረ-
ሀሳቦች ቀርበዋል፡፡
 መንግሰት የግል ባለሀብቱን የአቅምና አመለካከት ክፍተት መሙላት አለበት
የሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት ለኢንዱስትሪው ዕድገት እንደዋነኛ ተዋናይ ሲወሰድ
ባለሀብቱ የተሰጠውን ሚና እንዲጫዎት የማስቻልና አቅሙን የማጎልበት ስራ ደግሞ
በመንግስት ትኩረት ተሰጦ መሰራት አለበት፡፡ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ
ያለውን እጅግ ከፍተኛ አለማቀፍ ውድድር በራሱ አቅም ብቻ ሊወጣው አይችልም፡፡
ስለዚህ በአንድ በኩል ባለሀብቱ በተሰማራበት ዘርፍ ዕውቀትና ክህሎቱን ማስፋት፣
ኢንተርፕርነር መሆን፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂን መጠቀም፣ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ
አመራር መዘርጋት፣ በጥራትና ምርታማነት በማምረት ተወዳዳሪ መሆን እንዲሁም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 269


ከኪራይ ሰብሳቢነትና ኋላቀር አመለካከት መላቀቅ ይኖርበታል፡፡ በሌላ በኩል
መንግስት የባለሀብቱን ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ ሀገራዊ ባለሀብቱን አቅም
በዘላቂነት ለመገንባት የሚያስችሉ አሰራር (በመንግስት ስልጠና ፤ማማከር እና መረጃ
አገልግሎት ተቋማትን ማጠናከር፣ የግል ተቋማት በተመሳሳይ አቅም ማጎልበት ሥራ
ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ) መዘርጋት ይጠበቅበታል፡፡ በተጓዳኝ አፈፃፀምን መሰረት
ያደረገ ግልፅ የሆነ የመመልመያ መስፈርት በማዘጋጀት ጥራት እና ብቃት ያለውን
ሀገራዊ ባለሀብት በመለየት አምራች ኢንዱስትሪው እንዲቀላቀሉ ማድረግ እንዲሁም
በግል ባለሀብቱ ላይ የተጀመረው የንቅናቄ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡
 ባለሀብቱ ውጣውረድ የመፍራትንና በአቋራጭ ሀብት ማካበት አመለካቱን ቀይሮ
የረጅም ጊዜ ተጠቃሚነቱን የሚያጎለብት ራዕይ በመሰነቅ፣ በዕውቀት የሚመራ፣
የሀገራችን ፖሊሲና ስትራቴጅን የተረዳና አለማቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን ጥረት
ማድረግ ይገባዋል፡፡ በተጨማሪም በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራው ባለሀብት
ሀገር ወዳድ፣ በንግድ ዲሲፕሊንና ስነምግባር የታነፀ የልማታዊ ባለሀብት ባህሪ
መላበስ ይኖርበታል፡፡
 የአምራች ኢንዱስትሪው ባለሀብቶች በንግድ ማህበራት በመደራጀት በኢንዱስትሪ
ፎረሞች በመሳተፍ በዘርፉ ያሉትን ችግርችና መፍትሄ ሀሳቦችን በውይይት
መድረኮች ለመንግስት አካላት በማስረዳት ተገቢ እርምጃ እንዲወስድ ያላሰለሰ
ጥረት ማድረግ ይገባቸዋል፡፡
 በዘልማዳዊ ቤተሰብ መርና ኢ-መደበኛ ኢንተርፕራይዞች አደረጃጀት በማስወገድ፣
ዕውቀትና ክህሎት ባለው ባለሙያ የሚቀጥር፣ በፕሮጀክት አዋጭነት ጥናት መሰረት
የኢንዱስትሪ ስምሪቱን የሚወስን፣ አለማቀፋዊ እና ነባራዊ ሁኔታ ጋር ራሱን
የሚያላምድ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብት መሆን እንደሚገባው መረዳት
ያስፈልጋል፡፡
 ጥሬ እቃና በከፊል ያለቀለት ምርቶችን በጥራት፣ በብዛትና በተመጣጣኝ ዋጋ
ለማግኘትና ተያያዥ ችግሮችን ለመቅረፍ፣ አቅም በፈቀደ መጠን ባለሀበቱ
በግብርናው ዘርፍ ኢንቨስት (backward linkage) በማድረግ የኢንዱስትሪ ጥሬ እቃ
ማቅረብ ይገባዋል፡፡ እንዲሁም ጥሬ እቃ ለሚያቀርቡ አርሶአደሮችና አርብቶአደሮች
ተገቢውን የቴክኒክና የስልጠና ድጋፍ ማድረግና ከገጠር የስራ ማህበራት ጋር
በመቀናጀት መስራት ይጠበቅበታል፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ ባለሀብቶች፣

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 270


አርሶአደሮች፣ አርብቶአደርችና የግብርና ዘርፍ ኢንቨስተሮች ጋር በመቀናጀት ተናቦ
መስራት ይገባል፡፡
 በውጭና ሀገር ውስጥ ገበያ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ ጥራትና ምርታማነት ላይ
በትኩረት መስራት ይጠበቅበታል፡፡ በሀገር ውሰጥ ገበያ በተመለከተ የምርቱን
ጥራትና ተወዳዳሪነት ከግምት ውስጥ ያላስገባ የትርፍ ህዳጌ መሻት የረጅም ጊዜ
ተወዳዳሪነትን ስለሚያከስም ፍትሀዊ የዋጋ ትመናና ትርፍ መሻት ተገቢ መሆኑን
መረዳት አለበት፡፡ በውጭ ገበያ ተወዳዳሪነትን ለማጠናከር የግል ባለሀብቱ ጥራትና
ምርታማነት ያለማቋረጥ ማሳደግና በአለም ገበያ ትስስር በመፍጠር የገበያ
ድርሻውን ማስፋት ይጠበቅበታል፡፡
 ፀረ-ውድድርና ህገ-ወጥ የንግድ አሰራር (የኮንትሮባንድ ንግድ፣ ዕጥረት ለመፍጠር
ምርት መሰወር፣ ጥቂት ነጋዴዎች በስምምነት ዋጋ መተመን፣ ያለደረሰኝ ግብርና
ቀረጥ ሳይከፍሉ ምርትን ለገበያ ማቅረብ፣ ለገቢ ዕቃዎች ዋጋ አሳንሶ መተመን
ወዘተ) ፍትሀዊ ውድድር እንዳይኖር በማድረግ አምራቹን ለኪሳራና ከፍተኛ ወጭ
ይዳርጋል፡፡ ስለዚህ አምራቹ ቀጥተኛ ተጎጅ በመሆኑ ከመንግስት ጎን በመቆም ህገ-
ወጥነትን መከላከል አለበት፡፡
 ባለሀብቱ በመንግስት አገልግሎት ዘርፎች፤ ማለትም ገቢዎችና ጉምሩክ አገልግሎት፣
መሰረተ ልማት አቅርቦት፣ ኢንቨስትመንት ፈቃድ አሰጣጥ፣ የባንኮች ፋይናንስ
አገልግሎት ያሉበትን የመልካም አስተዳደርና ኪራይ ሰብሳቢነት ችግሮች፣ የፍትህ
መጓደል፣ በቢሮክራሲ የታጠረ ኋላቀር አሰራር፣ ደንበኛ ተኮር ያልሆኑ አገልግሎቶች
እንዲስተካከሉና ለችግሮቹ መፍትሄ ሀሳብ በማቅረብ መሪ ተዋናይ መሆን
አለባችው፡፡እንዲሁም በማህበራት በንቃት በመሳተፍ ያሉበትን ችግሮች
ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ መፍታት ይገባዋል፡፡
 ብቃት ያለውና የሰለጠነ የሰው ሀይል በአምራች ኢንዱስትሪው መቅጠር፣
ለሰራተኛው ተመጣጣኝ ማበረታቻ ማቅረብ፣ ተደራጅቶ እንዲንቀሳቀስ ማስቻል፣
በባለቤትነት ስሜት ችግር ፈቺ ሆኖ በጥንካሬ እንዲሰራ የሚያስችል አሳታፊ አሰራር
መፍጠር ተገቢ ነው፡፡
 የግል ባለሀብቱ አዋጭ የሆኑ ቴክኖሎጅዎችን በማፈላለግ፣ በመምረጥ፣ በማሸጋገርና
በማላመድ የግል ባለሀበቱ በራሱ ተነሳሽነት ምርታማነቱንና አለማቀፍ ተወዳዳሪነቱን
ማጎልበት አለበት፡፡ በመሆኑም በላይሰንሲንግ፣ በጆይንት ቨንቸር፣ ቴክኖሎጅዎች
በመግዛት፣ በፋብሪኬሽን፣ የውጭ ባለሙያዎችን በመጋበዝ፣ በቴክኒክ ትብብር፣
ለልምድ ልውውጥና ሥልጠና ሰራተኛን በመላክ፣ መሰል ተቋማትን መልካም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 271


ተሞክሮ በመውሰድ፣ ቴክኖሎጅን ማልማት ያስፈልጋል፡፡በተጓዳኝ ከዩኒቨርስቲዎች
ጋር ጥምረት በመፍጠር፣ ምርምርና ስርፀት በማካሄድና የሰራተኛውን የቴክኒክ
ብቃት ለማሳድግ መስራት አለበት፡፡
 የመንግስት ማበረተቻና ድጋፍ ለሌላ ጥቅም ማዋልና በአቋራጭ ለመበልፀግ
መሯሯጥ በሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በብዛት ይስተዋላል፡፡ በተለይ መሬት ወስዶ አጥሮ
ማስቀመጥ፣ መጋዘን ሰርቶ ማከራየት፣ ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት ወዘተ
ችግሮች በስፋት የተስተዋሉ በመሆኑ ባለሀብቱ ከእነዚህ ድርጊቶች መቆጠብ
ይኖርበታል፤ ከዚህ በተቃራኒ በመሰለፍ እነዚህን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት
ከመንግስት ጋር አብሮ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ የመንግስት ማበረታቻዎችና
ድጋፎች ፍትሀዊ፣ ግልጽና ተጠያቂነትን በሚያሰፍን መልኩ ለታለመለት አላማ
እየዋሉ መሆኑን ለማረጋገጥ ከመንግስት ጎን መቆም አለበት፡፡
 በአጠቃላይ ከላይ የተዘረዘሩትን ተግባሮች እውን ለማድረግ እና የግል ባለሀብቱ
በቁርጠኝነት እንዲሰራቸው የመንግስት ድጋፍ ዓብይ በመሆኑ ውጤት ተኮር
መስፈርት አዘጋጅቶ ባለሀብቱን በመመልመል እንዲሁም ግንዛቤውን ለማሳደግ
የሚያስችል ንቅናቄ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተጋጋለ ሁኔታ መጀመር ያስፈልጋል፡፡

8.3.7 መሬትና መሰረተ ልማት አቅርቦት ላይ የቀረቡ የመፍትሄ ምክረ-ሐሳቦች

የልማታዊ ዲሞክራሲ ፍልስፍና የሚከተሉ ሀገራት ገበያው በራሱ ሊሸፍናቸው ያልቻሉ


ክፍተቶችን በመንግስት ቀጥታ ተሳታፊነት በመሸፈን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር
ለማድረግ በትጋት እየተሰራ ነው፡፡ በሀገራችን መንግስት ለፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት
የመሰረተ ልማት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑን በመረዳት ሰፊ ስራዎችን አከናውኗል፡፡ ይህ
እንዳለ ሆኖ በመሰረተ ልማት አቅርቦት በተለይ በአፈፃፀም ሂደት ላይ ችግሮች
ተከስተዋል፡፡ ለችግሮቹም የሚከተሉት የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች ቀርበዋል፡፡
 መሬት አልምቶ ለባለሀብት ማቅረብ እና ክትትል ማድረግ
በሀገራችን በሁሉም አካባቢዎች ለኢንቨስትመንት የሚሰጡ ቦታዎች የለሙ እና
መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ይህም ኢንቨስተሩ ያለምንም
መዘግየት ወደ ስራ እንዲገባ ያግዘዋል፡፡ ያልለማ መሬት ለኢንቨስተሮች ማስተላለፍ
ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል፡፡ በተጨማሪም መሬት ወስደው ያላለሙ እና
ላልታለመለት ዓላማ ያዋሉ ባለሀብቶች፣ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች ላይ መንግስት
በየወቅቱ እየተከታተለ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ይጠበቅበታል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 272


ለኢንቨስትመንት የተሰጠውን ነገር ግን በአግባቡ ያልለማና ታጥሮ የተቀመጠ፣
ያለአግባብ ላልተፈቀደ አገልግሎትና ተግባር የዋለ መሬት በየከተሞቹ ቆጠራ ተካሄዶ
በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲመለስ በማድረግ ለአዳዲስ አምራች ኢንቨስትመንቶች
መስጠት ተገቢ ይሆናል፡፡ ካፒታል የፈሰሰበትም ቢሆን ካሳ ተከፍሎ እንዲመለስና
ጥራት ላላቸው አምራች ባለሀብቶች እንዲሰጥ ማድረግ ይገባል፡፡
 መረጃዎች እንደሚያሳዩት በቅርብ ጊዜ አምራች ዘርፉን እየተቀላቀለ ያለው
ባለሀብት በተነፃፃሪ መካከለኛ እና አነስተኛ የካፒታል ዓቅም ያለው ነው፡፡ ስለዚህም
የመሬት አሰጣጥ መስፈርቱ የሀገራችንን ባለሀብት ዓቅም ያላገናዘበ በመሆኑ፤
በኢንዱስትሪ መንደር እና በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያልተካተተውን እንዲሁም
በአምራች ኢንዱስትሪ መሰማራት የሚፈልገውን የሀገር ውስጥ ባለሀብት መሬት
ለማግኘት እንደማንኛውም ባለሀብት በሊዝ ጨረታ ውስጥ እንዲሳተፍ ከማድረግ
ይልቅ መሬቱን በዝቅተኛ የሊዝ ዋጋ እንዲያገኝ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡
 እንደሚታወቀው አሁንም ቢሆን ለሀገር ውስጥ የግል ባለሀብቱ የኢንቨስትመንት
መሬት አቅርቦትና አሰጣጥ ስርአቱ ውጣውረድ የበዛበት፣ ረጅም ጊዜ የሚወስድና
በሚመለከታቸው የመሬት አስተዳደር ባለስልጣናት እና ሰራተኞች ላይ ከፍተኛ
የሆነ የተቀናጀ የኪራይ ሰብሳቢነት ባህሪ ስላለ በተጠናከረ መንገድ ከምንጩ
እንዲደርቅ ማድረግ ይጠይቃል፡፡
 ከሩቅ ምስራቅ ሀገሮች (ለምሳሌ፡ ደቡብ ኮሪያ እና ቻይና) ተሞክሮ የምንረዳው
የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ከማስተዳደር ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን ለመቅረፍ
ፓርኮቹ በኢንተርፕራይዝ ደረጃ እንዲቋቋሙ ማድረግ በዚህም በራሳቸው ገቢ
እንዲተዳደሩ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ይህ በማድረግ ፓርኮቹ አዋጭ መሆናቸው
እስከተረጋገጠ ድረስ ለተጨማሪ ማስፋፊያ በራሳቸው ዋስትና ከውጭ የፋይናንስ
አቅራቢ ተቋማት ብድር የማግኘት እድላቸውን የሰፋ ይሆናል ተብሎ ይታሰባል፡፡
በፓርኮቹ ግንባታ እና ለባለሀብቶች ማስተላለፍ እንዲሁም ማስፋፋት ሂደት
የአካባቢው አስተዳደር እንዲሳተፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
 የኤሌክትሪክ ሀይል ዕጥረት አሁን ካለው ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር ተያይዞ የመጣው
የኃይል ፍጆታ ፍላጎት በየዓመቱ እስከ 40 በመቶ ያህል እየጨመረ መምጣቱ ነው፡፡
ስለዚህ ከሀገራዊ የኃይል ምርት የሚመነጭ የአቅርቦት ዕጥረት እንዳለ ግልፅ ነው፡፡
ነገር ግን የኤሌክትሪክ ሀይል ሲያንስ እና ሲቆራረጥ ፕሮግራሙ ቢታወቅ ለአምራች
ኢንዱስትሪው ከተጨማሪ ወጪ ስለሚያድነው ጊዜያዊ መፍትሔ ይሆናል፡፡
በተጨማሪም የኢንዱስትሪ ዞንና ማዕከላት ተብለው የተለዩትና በብዛት አምራች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 273


ኢንዱስትሪው የሚስፋፋባቸው አካባቢዎች ብቻ የሚመግብ ከሌሎች መስመሮች
የተለየ የኤሌክትሪክ መስመር እና ማሰራጫ ጣቢያዎች በመገንባት ለዘላቂ መፍትሔ
ማሰብ ያስፈልጋል፡፡
 ለአምራች ኢንዱስትሪ መንደሮች የመንገድ፣ የውሀ እና የኢንተርኔት መሰረተ
ልማቶች በጥራትና በበቂ ሁኔታ ስላልተዳረሱ በሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶችና
ተቋማት አሁንም ተገቢውን ትኩረት ሰጠው መሰራት አለባቸው፡፡

8.3.8 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን በብዛትና በስፋት ማጠናከር

በተደጋጋሚ እንደተገለፀው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሀገር ውስጥ


ባለሀብት በስፋት የሚፈጠርባቸውና የሚለማመድባቸው መስኮች ሆነው ሊያገለግሉ
ስለሚችሉ በብዛትና በስፋት (Massive) እንዲፈጠሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት
እንደሚያስፈልግ መገንዘብ ያሻል፡፡ ከዚህ በፊት የጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዝ በሚል የሚታወቀው አደረጃጀት በአሁኑ ወቅት በሁለት ተከፍሎ
አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ወደ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሁም ጥቃቅን
ኢንተርፕራይዝ በስራ ፈጠራ (Entreprenur) ላይ ትኩረት አድርጎ በከተማ ልማትና
ቤቶች ሚኒስቴር ስር በአዲስ መልክ እንደተደራጁ ተደርጓል፡፡ይህ አደረጃጀት
በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እስከ ወረዳ ድረስ በተመሳሳይ ሁኔታ ተዋቅሯል፡፡
አዲሱ አደረጃጀት ከዚህ በፊት የነበራቸውን ተልዕኮ የበለጠ እንደሚያጠናክር ታሳቢ
ያደረገ ነው፡፡ ስለዚህ በክልልና በወረዳ ደረጃ አምራች ኢንዱስትሪን የሚመለከቱ
ሶስት ተቋማት (የስራ ፈጠራና ምግብ ዋስትና፣ አነስተኛና መካከለኛ አምራች
ኢንዱስትሪ እና ኢንዱስትሪ ዘርፍ) ተናበውና ተቀናጅተው መስራት
ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከዚህ በፊት ጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች የገጠሟቸውን የፋይናንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የዕውቀትና ክህሎት፣
የመስሪያ ቦታና ገበያ ችግሮችን መፍታት እና በተለይ በወረዳ ደረጃ በአነስተኛ
አምራች ኢንዱስትሪ በብዛትና በስፋት እንዲሰማሩ ትልቅ ትኩረት ተሰጦት ሊሰራ
ይገባል፡፡ ከዚህ ባሻገር እነዚህ ኢንተርፕራይዞች ከትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ጋር
በቅንጅት እንዲሰሩ የተጀማመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የአሰራር ስርአት
መዘርጋት ያስፈልጋል።

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 274


8.3.9 በንግዱ ዘርፍ የተሰማራውን የሀገር ውስጥ ባለሀብት ወደ አምራች መሳብ

 በንግዱ ዘርፍ የተሰማራውን የሀገር ውስጥ ባለሀብት ወደ አምራች ኢንዱስትሪ


ለመሳብ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በኩል የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉ እንገነዘባለን፡፡
ነገር ግን ይህን ስራ ለመስራት ከፌደራል እስከ ክልል ያለው የኢንዱስትሪ አመራር
በብቃትና በብዛት አለ ለማለት አያስደፍርም፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ ይህን ተግባር
በብቃት ለማከናወን የሚያስችል ቅድመ ሁኔታ መኖር አለመኖሩን ማረጋገጥ
ያስፈልጋል፡፡ ዞሮ ዞሮ በሀገራችን በየክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በስፋት በንግድ
ስራ ላይ ተሰማርቶ የሚገኘውን እንዲሁም በተነፃፃሪነት የተሻለ ካፒታል ያለውን
ባለሀብት በተጠናከረ ቅስቀሳና ንቅናቄ ወደ አምራች ኢንዱስትሪ እንዲሰማራ
ለማድረግ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጦት ሊሰራ የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም
ከመንግስት የሚቀርቡ ማበረታቻዎችና ድጋፎችም ባለሀብቱን ከንግድ ወደ አምራች
ኢንዱስትሪ መሳብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡ በሌላ በኩል በተለይ በአስመጪነት
የተሰማሩ ነጋዴዎች የሚያገኙትን ዕሴት የማይጨምርና የተጋነነ ትርፍ መቀነስ
የሚያስችሉ ስልቶችን መጠቀም (ግብር፣ ታክስና ቀረጥ ማስተካከል)፣ ግብርና ታክስ
የማጭበረብር ክፍተቶች መዝጋት ያሻል፡፡

8.3.10 በኮንስትራክሽን የተሰማሩ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ወደ አምራች መሳብ

 ከላይ እንደተገለፀው በኮንስትራክሽን ንዑስ ዘርፍ የተሰማሩ አብዛኛዎቹ የሀገር ውስጥ


የግል ባለሀብቶች ብዙ ችግሮች ያሉባቸው ቢሆንም ጥሩ ልምድ ያላቸው ጠንካራ
ባለሀብቶችም ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም በዘርፉ የተሰማሩ አቅም ያላቸውን ባለሀብቶች
መመልመልና በዋናነት በኮንስትራክሽን ግብአት ማምረቻ ኢንዱስትሪዎች ላይ
ኢንዲሰማሩ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ ለኮንስትራክሽን ግንባታ የሚውሉ
የኢንዱስትሪ ግብአቶችን (ብረታብረት፣ ሲሚንቶ፣ ሴራሚክስ ምርቶች፣ ወዘተ)
የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች እንዲያቋቁሙ ማድረግ ይቻላል፡፡

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 275


ዋቢ ምንጮች (References)

1. Uryu, K.(2006). Government procurement as industrial policy: in support of Japan's defense


aircraft, start-up and venture companies, and information technology sectors, USJP Occasional
Paper 06-14.
2. Yulek, M. A. & Taylor, T. K. (2012). Designing Public Procurement Policy in Developing
Countries፡ How to Foster Technology Transfer and Industrialization in the Global Economy.
Springer.
3. Joe stud well, (2013), How Asia works: Success and failure in the world’s most dynamic region,
Grover press, Newyork.
4. Ministry of Urban Development, Housing and Construction (MUDHCo) & Ethiopian Civil
Service University (2015). State of Ethiopian Cities report 2015, Addis Ababa.
5. National Bank of Ethiopia (2015). Annual Performance Report 2014/2015 , Addis Ababa.
6. Chacko, Elizabeth & Gebre, Peter (2009). Diaspora investments, motivations and challenges: The
Case of Ethiopia. World Bank International Conference on Diaspora and Development, July 13-
14.
7. Addis Ababa Chamber of Commerce and Sectoral Association (2015). An overview of Ethiopian
manufacturing sector -2014, Addis Ababa.
8. Merso Fikremarkos Imeru Tamirat, Seyoum Yohannes, Yoseph Endeshaw & Tilahun Teshome
(2009). Review of the Legal and Institutional Framework for Market Competition in Ethiopia፣ the
Addis Ababa Chamber of Commerce and Sectoral Associations
9. UNIDO (2015). Overcoming Constraints in the Manufacturing Sector,4th Ethiopia Economic
Update:
10. Ministry of Finance & Economic Development (2010). Federal public procurement directive,
Addis Ababa
11. The World Bank (20016). Doing Business Ethiopia.
12. Central Statistical Agency & Ministry of Urban Development and Construction (2012). Contract
construction survey-2010/2011, statistical bulletin, Addis Ababa.
13. The government of India-ministry of commerce and industry (2011). National manufacturing
policy, press note No.2, 2011 series.
14. Global Legal Research Center (2010). Government Procurement Law and Policy: Brazil, Canada,
China, European Union, India, Japan, Russian Federation.
15. Ariel, B., 'Challenges to the World Bank and IMF: Developing country perespective', London,
Anthem Press.

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 276


16. Ashford C., 2012, 'The East Asian Development Experience: Policy Lessons, Implications, and
Recommendations for Sub-Saharan Africa (SSA) Global Competitiveness', International Journal
of Academic Research in Business and Social Sciences, Vol. 2, No. 7, PP. 82-112, viewed on 21
Feb 2015.
17. Central Statistical Agency, 2015, Report on large and medium scale manufacturing and electricity
industries survey, The Federal Democratic Republic of Ethiopia, Addis Ababa.
18. Development Bank of Ethiopia, Annual report for the year ended Jun 2007 - 2012.
19. Eugene, B. & Jonathan, M., 2014, Technology gap, imported capital goods and productivity of
manufacturing plants in Sub-Saharan Africa, African Development Bank, viewed on 21 Nov2014.
20. Guillermo, R., 2006, Why have all development strategies failed in Latin America? Research
paper No. 2006/12, United Nations University, viewed on 15 Jan 2015.
21. John, W., 2005, Export growth and industrial policy: Lessons from East Asian miracle
experiences, Asian Development Bank, viewed on 10 Dec, 2014.
22. Kanayo Ogujiuba, Uche Nwogwugwu and Enwere Dike, 2011, 'Import substitution
industrialization as learning process: Sub-Saharan African experience as distortion of the [“good”]
business model', Business and Management Review Vol. 1(6) pp. 08 – 21.
23. Kim, K. & Leipziger, D., 1997, 'Korea: a case of government-led development' in D. Leipizer,
Lessons from East Asia.
24. Kwan, S.K., 1991, The Korean miracle (1962-1980) revisited: Myths and realities in strategy and
development, working paper #166, Kellogg Institute, viewed on 8 Feb 2015.
25. Léonce, N., 2014, 'Savings, capital flight, and African development', A Political Economy
Working Paper No. 353, Political Economy Research Institute.
26. Miria, P. & Wenxia, T., 2015, ‘China anad Africa: Expanding Economic ties in an evolving
global context’, Investing in Africa forum, Mar 2015, Addis Ababa, Ethiopia.
27. National Bank of Ethiopia, Annual report for the year 2010/11- 2015/16, Addis Ababa.
28. Nelson, R. & Pack, H., 1999, 'The Asian growth miracle and modern growth theory', Economic
Journa.
29. Pahariya, N.C., 2008, Import substitution and export promotion as development strategies:
Briefing paper, CUTS, viewed on 10 Feb 2015.
30. Peter, N., 2002, Foreign direct invesmsnt in developing countries: What economists (don't) know
and what policy makers should (not) do!, viewed on 20 Jan, 2015.
31. Premachandra, A. & Jayant, M., 1996, Foreign Investment and Industrialization in Malaysia:
Exports, Employment and Spillovers, Asian Economic Journui 1996, Voi. 10 No I, pp 29-43,
2015.

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 277


32. Rhys, J., (1991), 'The Political Economy of Industrialization: A Comparison of Latin American
and East Asian Newly Industrializing Countries', Development and Change (SAGE, London,
Newbury Park and New Delhi), Vol. 22, pp197-23.
33. Robert, H. (2005), Bringing the State Back In: Lessons from East Asia’s Development
Experience, 2015.
34. Rodrik, D., (1999), The new global economy and developing countries: Making openness work,
Overseas Development Council, Washington DC.
35. Roy, C. & Aniket, B., (2008), Domestic resource mobilization: A neglected factor in
development strategy, a background paper prepared for workshop on Domestic mobilization in
Sub-Saharan Africa, 28 May 2008, Entebbe Uganda.
36. Sanjaya Lall, Manual Albaladejo and Mauricio M. Moreira, (2004), Latin America industrial
competitiveness and the Special issue on trade and investment, Inter American Development
Bank.
37. Sanjeev, K., (2007), Rural development through rural industrialization: exploring the Chinese
experience, viewed on 21 Oct 2014.
38. Steven, D. & Jennifer, T., (2002), Understanding the Link Between Research and Policy, Rural
Communities Impacting Policy Project.
39. Tianbiao, Z., (2006), Rethinking Import-substituting Industrialization: Development Strategies
and Institutions in Taiwan and China, Research Paper No. 2006/76, United Nations University.
40. Tilman, A., (2010), Industrial policy in Ethiopia, a discussion paper, German Development
Institute.
41. UN-ECA (2013), 'Industrialization for an Emerging Africa: Issues', paper, Sixth Joint Annual
Meetings of the ECA Conference of African Ministers of Finance, Planning and Economic
Development and AU Conference of Ministers of Economy and Finance, Abidjan.
42. UN-ECA, (2013b), African Economic Outlook: Structural Transformation and Natural Resources.
43. UN-HABITAT, (2014), Structural transformation in Ethiopia: The urban dimension, UN-habitat.
44. Wilson, P. & Annalisa, P., (2009), Theory and practice of industrial policy; Evidence from the
Latin American experience.
45. World Bank, (1993), The East Asian miracle: Economic growth and public policy, Oxford
University Press.
46. X.Wu, (2011), Rethinking China's path of industrialization: Working paper, United Nations
University.
47. የኢፌዴሪ የሚኒስትሮች ምክር ቤት (2005)፡ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች እና ለአገር
ውስጥ ባለሀብቶች የተከለከሉ የስራ መስኮች፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር
270/2005፣ አዲስ አበባ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 278


48. የንግድ አሰራርና የሸማቾች ጥበቃ (2006)፡ የንግድ አሰራርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ፣
አዲስ አበባ
49. ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር (2007)፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ
ትራንስፎርሜሽን የንቅናቄ ሰነድ፣ አዲስ አበባ
50. ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር (2007)፡ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሁለተኛው የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ፣ አዲስ አበባ
51. ንግድ ሚኒስቴር (2007)፡ የአክስዮን ማህበራትን ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት
ለማደራጀት የተደረገ አጭር የዳሰሳ ጥናት
52. የኢፌዴሪ (2002)፡ የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 686/2002
53. ንግድ ሚኒስቴር (2008)፡ የ2008 በጀት ዓመት የ9 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
54. ንግድ አሰራር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን (2007)፡ ጥራትና ደረጃቸውን ሳይጠብቁ ወደ
ኢትዮጵያ የሚገቡ ምርቶች በሸማቹ ህብረተሰብ እና በንግድ ውድድሩ ላይ የሚያሳድሩት
ተፅዕኖ (በምግብ ኤሌክትሮኒክስ፣ አልባሳት እና መድሀኒት ምርቶች ላይ በማተኮር የተጠና)፣
አዲስ አበባ
55. የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን(2007)፡ የንግድ ዉድድር ፖሊሲና ህግ
አጠቃላይ ገፅታ ማሳያ ሰነድ (competition policy & law overview)፣ አዲስ አበባ
56. የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር (2008)፡ የመንግስት ግዥ አፈፃፀም መመሪያ
እንደገና ለማሻሻል የወጣ መመሪያ
57. ymNGST G™Â NBrT xStÄdR x@jNs! (2008)Ý bØd‰L mNGST G™ xfÚ[M
z#¶Ã y_”QN xnSt¾ x!NtRP‰YøC mBT GÁ¬ãC፣ www.ppa.gov.et
58. የገንዘብ እና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር(2001)፡ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት የግዥ
እና የንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001፣ አዲስ አበባ
59. UNCTAD, 2014, www.unctad.org/fdistatistics

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 279


አባሪዎች (Appendix)

አባሪ I: በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ለተሰማሩ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች/ኩባንያዎች/ የተዘጋጀ የፅሁፍ መጠይቅ

መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ በሀራችን የሚገኝ አምራች አንዱስትሪ በምን ደረጃ እንዳለ ለማጥናት የሚፈለገውን መረጃ በአምራች ኢንዱስትሪው
ዘርፍ ከተሰማሩ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ የጥናቱ ዓላማም አምራች ኢንዱስትሪው ያሉት ችግሮች ከመሰረታቸው
መረዳትና ዘርፉን ለማሳደግ በሀገር ደረጃ ሊኖሩን የሚችሉ መልካም ዕድሎች በመለየት አምራች ኢንዱስትሪው በገበያ ተወዳዳሪ ሁኖ
እንዲቀጥልና ይበልጥ እንዲሰፋ የሚያስችል ሁኔታ መፍጠር ነው፡፡ በመሆኑም ባለሀብቶች ወይም የኩባንያው አመራሮች አልያም ከፍተኛ
ባለሙያዎች ተፈላጊውን ትክክለኛ መረጃ በቅንነት በመሙላት አምራች ኢንዱስትሪው የሚያድግበት መፍትሔ ለማፈላለግ ያልተቆጠበ
አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ይጠየቃሉ፡፡ ጥናቱ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራስያዊ ሪፓብሊክ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማእከል የሚካሄድ
ነው፡፡ የሚሰጡት መረጃም ሆነ አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ በምንም መልኩ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ
ከወዲሁ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

ማሳሰቢያ፡- አማራጭ መልስ ላላቸው ጥያቄዎች ከፊታቸው ባለው ሳጥን የ "" ምልክት ያስቀምጡ፡፡

ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!


ሀ. ስለ ኩባንያው አጠቃላይ ገጽታ የሚመለከት መረጃ
1. ኩባንያው/ፋብሪካው/ የተቋቋመበት ጊዜ _______________/________/___________ዓ/ም
2. የኩባንያው ህጋዊ ሰውነት፡- ግለሰብ/ቤተሰብ ሕ/ሽርክና ማሕበር  ኃ/የተ/የግል ማሕበር አክሲዮን ማሕበር
3. የኩባንያው ባለቤትነት ሁኔታ ፡-  የሀገር ውስጥ ብቻ  የሀገር ውስጥና የውጭ በሕብረት
መልስዎ "የሀገር ውስጥና የውጭ " የሚል ከሆነ ከውጭ ባለሀብት ጋር መስራት የፈለጉበት ምክንያት ምንድነው? ______________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
4. የኩባንያው ባለቤትነት ድርሻ ፡- የሀገር ውስጥ ባለሀብት ________________ % የውጭ ባለሀብት _______________%
5. የምርት ዓይነት፡- ቋሚ የፍጆታ ምርቶች ቋሚ ያልሆኑ የፍጆታ ምርቶች የካፒታል ዕቃዎች
6. የኩባንያው ንዑስ የስራ ስምሪት፡- ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ማምረት ለውጭ ገበያ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያዎች
ለ. ዋና የጥናቱ ጥያቄዎች
7. ፋብሪካው/ኩባንያው/ ለማቋቋም መነሻ ካፒታል /የፋይነንስ/ ምንጭ ከምን አገኙ? ከባለሀብቱ ከራስ ገቢ ወይም ተቀማጭ ___________%
ከባንክ ብድር ___________% ከሌላ አማራጭ (ከግለሰብ፣ ከዕድር፣ ከእቁብ ወዘተ) __________%
8. ስራ ማስኬጃ ፋይናንስ ምንጭዎ ከምንድነው? ከንግድ ባንክ ብድር ከልማት ባንክ ብድር ከከቡባንያው ገቢ ሌላ
9. በንዑስ ዘርፉ እንዲሰማሩ የመረጡበት ምክንያት፡- የቴክኖለጂ ተነጻጻሪ ብልጫ /ብቃት የጥሬ ዕቃ/ግብኣት/ አቅርቦት የተሻለ
በመሆኑ የገበያ ዕድሉ የተሻለ ስፋት ስላለው የመነሻ ኢንቨስትመንት ካፒታል ዓቅም የመንግስት የኢንቨስትመንት
ማበረታቻዎች ስላሉት በዘርፉ ያለዎት ዕውቀት የተሻለ በመሆኑ
10. የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ በስፋት ተሰማርተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ከሀገራችን ኢኮኖሚ እና
የባለሀብቱ አጠቃላይ ሁኔታ የተቃኘ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲዎችና ስተራተጂዎች ነድፎ ከመተግበር በተጨማሪ በዘርፉ
ኢንቨስትመንት ለተሰማሩ የማበረታቻ ፓኬጅ ቀርጾ እየተገበረ ሲሆን ዘርፉን የሚደግፉ የኢንዱስትሪ ልማት ተቋማት ሳይቀር አደራጅቶ
የግሉን ባለሀብት ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት ስያደርግ ባለሀብቱ ግን በስፋት በአምራች ኢንዱስትሪው እየተሰማራ አይደለም፡፡ የዚህ ሁኔታ
ዋነኛ ምክንያቶች ምን ሊሆኑ ይችላሉ? ____________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

11. የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ወደ አምራች ኢንዱስትሪው እንዲሰማራ በመንግስት የተሰጠው ማበረታቻ (Financial and non-Financial
incentive) በቂ ነው ይላሉ? አዎ አይደለም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 280


መልስዎ አይደለም ከሆነ ተጨማሪ የሚያስፈልጉ ማበረታቻዎችን ይጥቀሱ፡፡
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________________
12. በአምራች ኢንዱስትሪው ፖሊሲና ስትራቴጂ ውስጥ ለባለሀብቱ ትልቅ ችግር (Obstacles) ነው ብለው የሚገምቷቸውን ይጥቀሱ፡፡
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
13. የሚከተሉት የመንግስት ተቋማት በሀገራችን የኢንዱስትሪን ፖሊሲና ስትራቴጂ ለማስፈፀም አስተዋጽኦ ያላቸው ናቸው፡፡ የኢንዱስትሪ
ፖሊሲው ለማስፈጸም ያላቸውን ቁርጠኝነትና ውጤት እንዴት ይገመግሙታል?
ባለድርሻ መስሪያ ቤት ከፍተኛ መካከለኛ ዝቅተኛ
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር/የኢንዱስተሪ ቢሮ/የኢንዱስተሪ ጽሕፈት ቤት
ኢንቨስትመንት ኮሚሽን/ቢሮ/ኤጀንሲ/ጽሕፈት ቤት
የንግድ ሚኒስቴር/ቢሮ/ጸሕፈት ቤት
የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር
ብሔራዊ ባንክ
ንግድ ባንክ
የልማት ባንክ
ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን
ግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር
የማዕድን ሚኒስቴር
የከተማ መሬት አስተዳደር

14. የሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪ በዘላቂነት መስፋፋትና መጠናከር ካለበት ከፍተኛ ሚና መጫወት ያለበት አካላት እነማን ናቸው?
መንግስት ሀገር ውስጥ የግል ባለሀብት የውጭ ባለሀብት መንግስትና የውጭ ባለሀብት
15. እርስዎ በቀጣይነት በአምራች ኢንዱስትሪው ለመሰማራት ፍላጐት አለዎት? አዎ አይደለም
መልስዎ አዎ ከሆነ በምን አይነት አምራች ኢንዱስትሪ ላይ መሰማራት ይፈልጋሉ ?/ቢያንስ ሶስት ይጥቀሱ/
i. _______________________________________________________________________________________________________________________________________
ii. _______________________________________________________________________________________________________________________________________
iii. _______________________________________________________________________________________________________________________________________
16. የእርስዎ ፋብሪካ የአዋጭነት (Economical Feasibility) እንዲሁም ከአካባቢ ብክለት ነፃ መሆኑ አልያም አለመሆኑ ተጠንቷልን?
አዎ አይደለም
መልስዎ አዎ ከሆነ በማን ተጠና?________________________________________________________________________________________________________________
17. እርስዎ ለአቋቋሙት ፋብሪካ /ዎች/ የሚሆን ጥሬ ዕቃ የሚያገኙት/የሚገዙት/ ከየት ነው?
ከሀገር ውስጥ ከውጭ ሀገር ከሀገር ዉስጥና ከውጭ ሀገር
መልስዎ " ከሀገር ውስጥ " የሚል ከሆነ የጥሬ እቃው በአቅርቦት፣ በዋጋና በጥራት ያለውን ሁኔታ ይግለፁ
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
18. የእርስዎ ፋብሪካ የማምረት አቅም (Production Capacity) በፐርሰንት ምን ያህል ነው ?________________________________________________

19. የእርስዎ ፋብሪካ ማምረት ከሚገባው በታች (Under Production capacity) ከሆነ ምክንያቶች ምን ሊሆኑ ይችላሉ?
ጥሬ ዕቃ ዕጥረትና ጥራት መጓደል የተመረተው ምርት ገበያ ማጣት
የሀይል አቅርቦት ችግር የሰራተኛው ብቃት ማነስ
ሌላ ምክንያት ካለም ይጥቀሱ ___________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
20. እርስዎ ፋብሪካ ምርት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ገበያ ላይ በዋጋ፣ በአቅርቦት፣ በጥራት ተወዳደሪ ነው ይላሉ?
አዎ አይደለም

መልስዎ "አይደለም " የሚል ከሆነ ተወዳዳሪ ያልሆነበት ምክንያቶች ይዘርዝሩ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 281


21. በተሰማሩበትአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በቂ ዕውቀት፣ ክህሎትና ተወዳዳሪ ብቃት ያለው ሰራተኛ ቀጥረዋል?
አዎ አይደለም
መልስዎ " አይደለም" የሚል ከሆነ ድርጅትዎ ተወዳዳሪ ያልሆነበት ምክንያት ይግለፁ፡፡
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________
22. የእርስዎ ኩባንያ በፈለጉት ደረጃ ላለማደግ ግንባር ቀደም ማነቆ ምክንያቶች ተብለው ከሚታሰቡ በሰንጠረዡ በደረጃቸው የ "" ምልክት
በማድረግ ያመልክቱ
ምክንያት የተፅዕኖ ደረጃ
እጅግ ከፍተኛ ከፍተኛ መካከለኛ ዝቅተኛ ተጽኖ የለውም
የመንግስት ድጋፍ ተደራሽ አለመሆን
የብድር ፍላጎት አለማሟላት
የገበያ እጦት ችግር
የሰራተኛ ሙያዊ ብቃት ማነስ
የቢዝነስ ማኔጅመንት ዕውቀትና ክህሎት ክፍተት
የንግድ ሕጎችና አሰራሮች አስቸጋሪነት
የጥሬ ዕቃ ግብአት አቅርቦት ዕጥረት

ሌሎች ካሉ ከዚህ በታች ይዘርዝሩዋቸው


i:_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
ii:_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
iii_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
23. የእርስዎ ዓይነት ኩባንያ የተሰማራበት ተመሳሳይ የኢንዱስትሪ ዘርፍ በፍጥነት ላለማደግ ግንባር ቀደም ማነቆ ምክንያቶች ተብለው
ከሚታሰቡ በሰንጠረዡ በደረጃቸው የ "" ምልክት በማድረግ ያመልክቱ

ምክንያት የተፅዕኖ ደረጃ


እጅግ ከፍተኛ ከፍተኛ መካከለኛ ዝቅተኛ ተጽኖ የለውም
የመንግስት ድጋፍ ተደራሽ አለመሆን
የብድር ፍላጎት አለማሟላት
የገበያ እጦት ችግር
የሰራተኛ ሙያዊ ብቃት ማነስ
የቢዝነስ ማኔጅመንት ዕውቀትና ክህሎት ክፍተት
የንግድ ሕጎችና አሰራሮች አስቸጋሪነት
የጥሬ ዕቃ ግብአት አቅርቦት ዕጥረት
የባለሀብቱ የነቃ ተሳትፎ ማነስ

ሌሎች ካሉ ከዚህ በታች ይዘርዝሩዋቸው


i:_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
ii:________________________________________________________________________________________________________________________________________________
iii:_______________________________________________________________________________________________________________________________________________

24. በእርስዎ እምነት አምራች ኢንዱስትሪው ባጠቃላይ በፍጥነት ላለማደግ ግንባር ቀደም ማነቆ ምክንያቶች ተብለው ከሚታሰቡ በሰንጠረዡ
በደረጃቸው የ "" ምልክት በማድረግ ያመልክቱ

ምክንያት የተፅዕኖ ደረጃ


እጅግ ከፍተኛ ከፍተኛ መካከለኛ ዝቅተኛ ተፅኖ የለውም
የመንግስት ድጋፍ ተደራሽ አለመሆን
የብድር ፍላጎት አለማሟላት
የገበያ እጦት ችግር
የሰራተኛ ሙያዊ ብቃት ማነስ
የቢዝነስ ማኔጅመንት ዕውቀትና ክህሎት ክፍተት
የንግድ ሕጎችና አሰራሮች አስቸጋሪነት
የጥሬ ዕቃ ግብአት አቅርቦት ዕጥረት
የባለሀብቱ የነቃ ተሳትፎ ማነስ

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 282


ሌሎች ካሉ ከዚህ በታች ይዘርዝሩዋቸው
i:_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
ii:_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
iii:_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

25. ብዙውን ጊዜ በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራ የሀገር ውስጥ ባለሀብት በተሰማራበት ዘርፍ ዉጤታማ እየሆነ እንዳልሆነ እንዲሁም
የገበያ ችግር እንዳለበት ይነገራል፡፡ ነገር ግን የውጭ በለህብቶች በሀገራችን በተመሳሳይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ተሰማርተው ዉጤታማ
ሲሆኑና በሀገራችን ያለውን የገበያ ዕድልም አሟጠው ሲጠቀሙበት ይታያል፡፡ ስለዚህ በሀገራች ባለሀብት እና በውጭ ባለሀብት ያለው
የስኬት ልዩነት ምንድነው ብለው ያስባሉ ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
26. በእርስዎ ድርጅት ከሚመለከተው የኢንዱስትሪ ድጋፍ ሰጪ ተቋም (ጨርቃ ጨርቅ፣ ቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ ብረታ ብረት፣ ምግብ
መጠጥና መድሀኒት፣ ኬሚካል ልማት ኢንስቲትዩቶች) የሚያገኘት ድጋፍ የትኞች ናቸው?
 የጥራት ፍተሻ ሥራዎች  የቴክኖሎጂ ትውውቅና ሽግግር የገበያ ጥናት
 የፋብሪካው ሰራተኛ ሙያዊ ስልጠና የሰው ሀይል ሙያዊ ብቃትና ፍላጎት ጥናት  የኢንዱስትሪ ሥራ አመራር ድጋፍ
 የብድርና ፋይናንስ ስራዎች የማመቻቸት ድጋፍ ሀሉንም ድጋፎች እናገኛለን ምንም ዓይነት ድጋፍ አናገኝም
27. ከላይ ከተጠቀሱት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩቶች ድጋፍ የሚያገኙ ከሆነ ድጋፉ ምን ያህል አጋዥ ነው ብለው ያስባሉ/ያምናሉ?
 ከፍተኛ መካከለኛ  ዝቅተኛ
28. በጥያቄ ተራ ቁጥር 26 ከተዘረዘሩት ድጋፎች የተወሰኑትን ወይንም ሁሉንም ዓይነት ድጋፍ የሚያገኙ ከሆኑ ከድጋፎቹ በተሻለ ጠንካራ
የሚሉት የትኛው ነው? ___________________________________ እጅግ ዝቅተኛውስ ? __________________________________

29. መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪው የፈቀዳቸው ዘርፈ-ብዙ ማበረታቻዎች ተግባራዊ እየሆኑ ነው ይላሉ?
 አዎ  አይደለም  በከፊል ተግባራዊ እየሆኑ ነው
30. ለጥያቄ ተራ ቁጥር 29 ከላይ መልስዎ “አይደለም” ወይም “በከፊል” የሚል ከሆነ በመንግስት አሰራር በኩል የሚታዩ ክፍተቶች ምን ምን
ናቸው ይላሉ?
i. _______________________________________________________________________________________________________________________________________
ii. ________________________________________________________________________________________________________________________________________
iii. _______________________________________________________________________________________________________________________________________
iv. _______________________________________________________________________________________________________________________________________
v. ________________________________________________________________________________________________________________________________________

31. እርስዎስ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የፈቀዳቸው ማበረታቻዎች በሚገባ ይጠቀሙበታልን?


 አዎ  በከፊል እጠቀማሉ  ተጠቃሚ አይደለሁም
32. በጥያቄ ተራ ቁጥር 31 መልስዎ "በከፊል " አልያም "ተጠቃሚ አይደለሁም " የሚል ከሆነ ምክንያቱ ከእርስዎ ድክመት ነው ወይስ
ከመንግስ በኩል? በምክንያቱ ይግለፁ __________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________

33. በመንግስት የአምራች ኢንዱስትሪው ለማሳደግና ችግሮቻቸውን ለመፍታት ከባለሃበቱ በየጊዜው ውይይት ይካሄዳል፡፡ የመወያያ አጀንዳው
በማዘጋጀት ባለሀብቱ ይሳተፋልን?  አዎ  አይሳተፍም
34. በመንግስት የአምራች ኢንዱስትሪው ለማሳደግና ችግሮቻቸውን ለመፍታት ከባለሃበቱ በየጊዜው የሚካሄዱ ውይይቶችስ ምን ያህል
መፍትሔ ሰጪ ናቸው ብለው ያምናሉ?
 ጠንካራ መፍትሔ እያስገኙ ነው  በከፊል መፍትሔ እያስገኙ ነው
 ዝቅተኛ መፍትሔ እያስገኙ ነው  ምንም መፍትሔ አያስገኙም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 283


35. ለጥያቄ ቁጥር 34 መልስዎ ዝቅተኛ ኣልያም ምንም መፍትሔ አያስገኙም የሚል ከሆነ ምክንያቱ ምን ሊሆን ይችላል ብለው ያምናሉ?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________________________________
36. አብዛኛው የሀገር ውስጥ ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪ ከመሰማራት ይልቅ በአገልግሎት ዘርፍ መዋእለ ንዋዩን ማፍሰስ የሚመርጥበት
ምክንያቶች ምንድን ናቸው ይላሉ? __________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________
37. በእርስዎ ድርጅት/ ኩባንያ የሰው ሀይል ብቃት ምን ይመስላል?
23.1. በምርታማነት  ከፍተኛ መካከለኛ  ዝቅተኛ
23.2. የኢንዱስትሪ ባህል ከመላበስ  ከፍተኛ መካከለኛ  ዝቅተኛ
23.3. በፈጠራ ክህሎት  ከፍተኛ መካከለኛ  ዝቅተኛ
23.4. በምርት ንድፍ/ዲዛይን ክህሎት  ከፍተኛ መካከለኛ  ዝቅተኛ
23.5. ከምርት ጥራት ክትትልና ቁጥጥር  ከፍተኛ መካከለኛ  ዝቅተኛ
23.6. የስራ አመራር ክህሎት  ከፍተኛ መካከለኛ  ዝቅተኛ
38. እንደ እርስዎ መሰል ኩባንያዎች ከመንግስት የሚፈለጉዋቸው አስቸኳይ ድጋፎች /መፍትሔዎች/ ምንድናቸው?
ሀ/__________________________________________________________________________________________________________________________________________________
ለ/_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
ሐ/_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
መ/____________________________________________________________________________________________________________________________________________
ሠ/____________________________________________________________________________________________________________________________________________
ረ/ _________________________________________________________________________________________________________________________________________________
ሰ/_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
39. በሀገራችን የአምራች ኢንዱስትሪው እንዴት ሊስፋፋና ሊጠናከር ይችላል ብለው ያምናሉ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 284


አባሪ 2: በየደረጃው ከሚገኙት ንግድና ዘርፍ ማሕበራት አመራር አካላት እና ኮሚቴ ኣባላት (ፌዴራል፣ ክልሎች እና ከተሞች) ባለ
ሙያዎች ጋር ለውይይት የተዘጋጁ ጥያቄዎች
መግቢያ- ይህ መጠይቅ በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ምን ያህል ዓቅም እንዳለ እና ልማታዊ ባለ ሀብቱ በዘርፉ ተሰማርቶ ይበልጥ
ተጠቃሚ የሚሆንበት ጥናት ለማካሄድ ዓላማ ያደረገ ነው፡፡ ይህንን ዕውን ለማደረግ ከሚመለከታቸው የመንግስት አስፈጻሚ እና ድጋፍ ሰጪ
መስሪቤቶች፣ የፋይናንስ ተቋማት እንዲሁም ከባለሀብቱ እና የተለያዩ የባለሀብቱ አደረጃጀቶች አስፈላጊዉን መረጃ መሰብሰብ አስፈላጊ ነው፡፡
የመረጃው አንድ አካል በየደረጃው ከሚገኙት የንግድ ምክር ቤቶችና የዘርፍ ማሕበራት እንዲሁም ኮሚቴዎችና ባለሙያዎች እንዲሆኑ
ተደርጓል፡፡ እነዚህ አካለት ትክክለኛ እና ቀጥተኛ ባለሃብቱን የሚወክል መረጃ ይሰጣሉ ተብሎ ይታመናል፡፡ በመሆኑም በዚህ ጥናት
እንዲሳተፉ ዕድሉ ያገኙ በየደረጃው የሚገኙ የባለሀብት አደረጃጀቶች አስፈላጊውን ትክክለኛ መረጃ በቅንነት በመስጠት ለባለሀብቱ ችግሮች
መፍታት የሚያስችል አማረጮችና መፍትሔዎች ለማፈላለግ በሚደረግ ጥናት ያልተቆጠበ አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ይጠቃል፡፡ የሚሰጡት
መረጃም ሆነ አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡
ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!
I- የተሳታፊዎች ዝርዝር መግለጫ
1. የተቋሙ ስም _______________________________________________________________________________________________
2. ተሳታፊዎች ዝርዝር
ስም ዝርዝር የት/ት የተመረቀበት የስራ የስራ ኃላፊነት
ደረጃ ሙያ ዓይነት ልምድ

II- ዋና የጥናቱ ጥያቄዎች


1. የንግድና ዘርፍ ማሕበራት በጥቅል ዋነኛ ተልእኮ ምን እንደሆነና የተልዕኮው ትክክለኛነት፡-
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________
 የፕሮጀክት አመራርና ማስተባበሪያ አገልግሎት የሚሰራቸው ዋና ዋና ተልእኮዎች ምንድንው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
 የጥናትና ማማከር አገልግሎት ተልእኮዎች ምንድናቸው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________
 የውጭ ንግድ ልማት ኮሚቴ ዋና ዋና ተልእኮዎች ምንድንው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________
 የቆዳ ቆዳ ዉጤቶች ኢንዱስትሪዎች ኮሚቴ ዋና ዋና ተልእኮዎች ምንድናቸው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________________________
 የግብር፣ ታክስና ፋይናንስ ኮሚቴ ዋና ዋና ተልእኮዎች ምንድናቸው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 285


2. በሀገር ዉስጥ በንግድ ስራ የተሰማራ የዘርፍ ስብጥሩ (የንግድ ዘርፍ/መስክ ስምሪት)ምን መልክ አለው? ጥያቄው የኢንዱስትሪ
ዓቅም ሁኔታ (large, medium, small scale businesses) ፣ የምርት ዓይነት (primary, industrial-outputs, services)፣
የንግድ መዋቅሩ (export versus imports) ወዘተ በሚል መልኩ ይታይ፡፡ ይህ ዓይነት ስብጥር እዲይዝ ያደረገውን ምክንያቱስ
ምንድነው?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
3. በገቢ እና ወጪ ንግድ (Import-Export) ስራ ስምሪት ሲታይ አብዛኛው ባለሃብት በአስመጪነት ተሰማርቶ እናየዋለን፤
ምክንያቱ ምንድነው?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
4. በውጭ ሰደድ ንግድ ስራ (Export) የተሰማራ ባለሀብት አብዛኛዉን የኢንዱስትሪ ውጤቶች ምርት ከመነገድ ይልቅ ጥሬ ምርት
ሰደድ ላይ የሚበዛበት ምክንያትስ ለምንድነው?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
5. በወጪ እና ገቢ ንግድ የሌሎች ሀገራት ዜጎችም ፈቃድ ተሰጥተዋቸው ይሰራሉ፤ እነሱ የሚሰማሩበት የንግድ ዘርፎች በሀገራችን
ባለሀብት ዓቅም (ከካፒታል ዓቅም፣ ከቢዝነስ ማነጅመንት፣ ከገበያ ሽፋን ወዘተ) የማይሸፈኑት አለያም የገበያ ክፍተት (የገበያ
ፍላጎት መሸፈን) ያለባቸው ነውን?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
6. በንግድ ስራ ላይ የተሰማራ ማሕበረ ሰብ በአምራች ኢንዱስትሪ ስምሪቱ ምን ይመስላል? በፍላጎት እና በአሃዝ እንዴት
ይግላጻል?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
7. ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ /ልማት/ ከመሰማራት ይልቅ በንግድ ስራ መሰማራት የሚመርጥበት ምክንያት ምንድነው?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________
8. በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ያለው አጠቃላይ ሁኔታ የኢንዱስትሪ ልማት ስትራተጂውና ፖሊሲዎች፣ የሕግ
ማዕቀፎች፣ ማበረታቻዎች ወዘተ የንግድ ምክርቤቱ እና በንግድ ስራ የተሰማራው ባለሀብቱ እንዴት ይመለከተዋል?

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 286


__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
9. የንግድ ማሕበረሰብ አደረጃጀት/የንግድ ምክር ቤት እና የዘርፍ ማሕበራት/ የንግዱ ማሕበረሰብ በኢንዱስትሪ ልማት እንዲሰማራ
ያደረገው አስተዋጽኦ ካለ? ከሌለ ምክንያቱ?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________

10. መንግስት የንግዱ ማሕበረሰብ በኢንዱስትሪ ልማት እንዲሰማራ ያደረገው ጥረትና የማስተዋወቅ ስራ ካለ?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
11. በንግድ የተሰማራው ባለሀብት በአምራች ኢንዱስተሪ እንዲሰማራ ከተፈለገ ከንግድ ማሕበረሰብ ከራሱ ሊደረጉ የሚገባቸው
ጉዳዮች ምን ናቸው ተብለው ይታሰባሉ?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________
12. በንግድ የተሰማራው ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪ እንዲሰማራ ከተፈለገ በመንግስት ሊደረጉ የሚገባቸው ጉዳዮች ምን
ናቸው ተብለው ይታሰባሉ?
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 287


አባሪ 3: በየደረጃው ከሚገኙ የንግድ አስፈጻሚ አካላት (የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ንግድ ሚኒስቴር፣ ክልል ንግድ ቢሮዎች እና የከተሞች ንግድ
ጽ/ቤቶች) ጋር ለውይይት እና ቃለ መጠይቅ የተዘጋጁ ጥያቄዎች

መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ምን ያህል ዓቅም እንዳለ እና ልማታዊ ባለሀብቱ በዘርፉ ተሰማርቶ ይበልጥ
ተጠቃሚ የሚሆንበት ጥናት ለማካሄድ መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ በመሆኑም ከሚመለከታቸው የመንግስት አስፈጻሚ እና ድጋፍ
ሰጪ መስሪቤቶች አስፈላጊዉን መረጃ መሰብሰብ የታሰበ በመሆኑ በዚህ ጥናት እንዲሳተፉ ዕድሉ ያገኙ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና
ባለሙያዎች ትክክለኛ መረጃ በቅንነት በመስጠት ለጥናቱ ዉጤታማነት ያልተቆጠበ አስተዋፅኦ እንድያበረክቱ ይጠበቃል፡፡ የሚሰጡት መረጃም
ሆነ አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!


I- የተሳታፊዎች ዝርዝር መግለጫ

1. የተቋሙ ስም _______________________________________________________________________________________________
2. ተሳታፊዎች ዝርዝር
ስም ዝርዝር የት/ት የተመረቀበት ሙያ የስራ የስራ ኃላፊነት
ደረጃ ዓይነት ልምድ

II- ዋና የጥናቱ ጥያቄዎች


1) በሀገር ዉስጥ በንግድ ስራ የተሰማራ ባለሀብት የዘርፍ ስብጥሩ ምን መልክ አለው (የንግድ ዘርፍ/መስክ ስምሪት)? ምክንያቱስ ምንድነው?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
2) በገቢ እና ወጪ ንግድ (Import-Export) ስራ ስምሪት ሲታይ አብዛኛው ባለ ሃብት በአስመጪነት (Import) ተሰማርቶ እናየዋለን፤
ምክንያቱ ምንድነው?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
3) በዉጭ ሰደድ ንግድ (Export) የተሰማራ ባለሀብት አብዛኛዉን የኢንዱስትሪ ዉጤቶች ምርት ከመነገድ ይልቅ ጥሬ ምርት ሰደድ ላይ
የሚበዛበት ምክንያትስ ምንድነው?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
4) በወጪ እና ገቢ ንግድ የሌሎች ሀገራት ዜጎችም ፈቃድ ተሰጥተዋቸው ይሰራሉ፤ እነሱ የሚሰማሩበት የንግድ ዘርፎች በሀገራችን ባለሀብት
ዓቅም የማይሸፈኑት (ከካፒታል፣ ከንግድ ስራ አመራር፣ የሎጂስቲክስና ትራንስፖርት፣ ከአቅራቢዎች ያለው ግንኙነት/Supplies chain
management/፣ ወዘተ) አለያም የገበያ ክፍተት ያለባቸው ነውን? ከሀገራችን የምጣኔ ሃብታዊ መዋቅር እና ከሀገር ዉስጥ ባለሀብት ዓቅም
ሊኖረው የሚችል እንደምታ ምንድን ነው?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 288


_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
5) በንግድ ስራ ላይ የተሰማራ ማሕበረሰብ በአምራች ኢንዱስትሪ ስምሪቱ ምን ይመስላል? በፍላጎት እና በአሃዛዊ መረጃ እንዴት ይገለጻል?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
6) አብዛኛዉን ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪ ከመሰማራት ይልቅ በንግድ ስራ የሚሰማራበት መሰረታዊ ምክንያት ምን ሊሆን ይችላል?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
7) የሀገራችን የአምራች ኢንዱስትሪ ውጤቶች የውጭ ገበያ ዕድል እንድያገኙ ከሚመለከታቸው አካላት ማለትም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣
ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የግድ ማሕበረ ሰብ አደረጃጀቶች ወዘተ በመሆን በተግባር እየተሰራ ያለ ስራ ካለ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
8) የንግድ ፖሊሲዎቻችንና ሕጎቻችን ለሀጋር ውስጥ አምራች ኢንዱስተሪዎች ልማት ምን ያህል የተመቸ ነው ብለን እናምናልን? እንዴት?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
9) ዜጎች የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲጠቀሙ ወይም እንዳይጠቀሙ ምርቱ በዋጋ እና ጥራት ተወዳዳሪ ሁኖ መገኘት፣ የልማታዊ
ብሄርተኝነት አስተሳሰብ ስፋትና ጥልቀት፣ ወዘተ ከሚወስኑዋቸው ነገርች ይጠቀሳሉ፡፡ ከአምራቹ አኳያ ሲታይ ደግሞ አመቺ ፖሊሲዎችና
ስትራተጂዎች መኖሩ በዘርፉ ለተሰማሩ ለሁለም ወሳኝ ከመሆኑም ባሻገር አርአያ የሆኑ ጀግኖች (development patriotism) የመፍጠር
ስራንም ይጠይቃል፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ስልቶች ምን ያህል የተግባር ስራ ይሰራበታል?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
10) በወጪ ሰደድ ንግድ የተሰማሩ ባገኙት የውጭ ምንዛሬ ምክንያት ጥሩ አፈጻጸም ያስመዘገቡ የንግድ ድርጅቶች ይሸለማሉ፡፡ ይህንን ሽልማት
በየዘርፉ ተለይቶ የሚሰጥ ነውን? በተለይ ጥሬ ዕቃ እና የኢንዱስትሪ ውጤቶች ሰደድ በተሰማሩ ላይ ልዩነት ካለ? በየዘረፉ ተለይቶ የሚሰጥ
ከሆነ በመረጃ ተደግፎ ይብራራ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 289


11) አሁን በገቢ እና ወጪ ንግድ እንዲሁም በሀገር ውስጥ ከፍተኛ አከፋፋይነት ተሰማርቶ የሚገኘውን ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪ
እንዲሰማራ ከተደረገ በሀገራዊ ምጣኔ ሀብታችን ሊኖረው የሚችል አወንታ እና አሉታዊ ተፅዕኖ ምንድናቸው? የተጽኖ ስፋቱስ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
________________________________________________________________________________________________________________________________________________
12) በንግድ የተሰማራው ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪ እንዲሰማራ ከተፈለገ ከንግድ ማሕበረሰብ ከራሱ ሊደረጉ የሚገባቸው ጉዳዮች ምን
ናቸው ተብለው ይታሰባሉ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
13) በንግድ የተሰማራው ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪ እንዲሰማራ ከተፈለገ በመንግስት ሊደረጉ የሚገባቸው ጉዳዮች ምን ናቸው ተብለው
ይታሰባሉ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 290


አባሪ 4: ከኢ.ፌ.ዴ..ሪ. ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩቶች ከፍተኛ ባለሙያዎች እና አመራሮች ጋር ለውይይትና
ቃለ መጠይቅ የተዘጋጁ ጥያቄዎች

መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ምን ያህል ዓቅም እንዳለ እና ልማታዊ ባለሀብቱ በዘርፉ ተሰማርቶ ይበልጥ
ተጠቃሚ የሚሆንበት ጥናት ለማካሄድ መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ በመሆኑም ከሚመለከታቸው የመንግስት አስፈጻሚ እና ድጋፍ
ሰጪ መስሪቤቶች አስፈላጊዉን መረጃ መሰብሰብ አስፈላጊ ነው፡፡ በዚህ ጥናት እንዲሳተፉ ዕድሉ ያገኙ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና
ባለሙያዎች ትክክለኛ መረጃ በቅንነት በመስጠት ለጥናቱ ውጤታማነት ያልተቆጠበ አስተዋፅኦ እንድያበረክቱ ይጠበቃል፡፡ የሚሰጡት መረጃም
ሆነ አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡
ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!
I- የተሳታፊዎች ዝርዝር መግለጫ

1. ተሳታፊዎች ዝርዝር
ስም ዝርዝር የት/ት የተመረቀበት ሙያ የስራ የስራ ኃላፊነት
ደረጃ ዓይነት ልምድ

II- ለውይይት የተዘጋጁ መነሻ ጥያቄዎች


1. በውጭ ሰደድ ንግድ (Export trade) የተሰማራ ባለሀብት አብዛኛዉን የኢንዱስትሪ ውጤቶች ምርት ከመላክ ይልቅ ጥሬ ምርት ሰደድ ላይ
የሚበዛበት ምክንያት ምንድነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
2. አብዛኛዉን የሀገር ውስጥ ባለሀብት በኢንዱስትሪ ልማት ከመሰማራት ይልቅ በንግድ ስራ መሰማራት የሚመርጥበት ኢኮኖሚያዊ፣ ባህርያዊ
እና ሌሎች መሰረታዊ ምክንያቶች ምንድነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
3. የሀገር ውስጥ የኢንዱስትሪ ውጤቶች በሀገር ውስጥ የገበያ ችግር ያጋጥማቸዋልን? የገበያ ችግር የሚያጋጥማቸው ምርቶች በዋናነት የትኞቹ
ናቸው? የሀገር ውስጥ የኢንዱስትሪ ምርቶች የመጠቀም ባህል እንዲዳብር ምን ስራ ተሰርቶበታል/እየተሰራበት ነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
4. የሀገራችን የኢንዱስትሪ ውጤቶች የውጭ ገበያ ዕድል እንድያገኙ ከሚመለከታቸው አካላት ማለትም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከንግድ
ሚኒስቴር፣ የግድ ማሕበረሰብ አደረጃጀቶች ወዘተ በመሆን በተግባር እየተሰራ ስራ ካለ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 291


5. በገቢ ምርቶች የሚተኩ (Import-substituing) ኢንዱስትሪዎች እና ለውጭ ገበያ የሚያመርቱ (export-oriented) ኢንዱስትሪዎች
የአፈጻጸም ልዩነት እና የሚያሳዩት የዕድገት ፍጥነትም ሆነ ጥንካሬ ምን ይመስላል? ምክንያቱስ ምንድ ነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

6. በሀገር በቀል ኢንዱስትሪዎችና በውጭ ኩባንያዎች ከአጠቃላይ አፈጻጸም (ምርታማነት፣ የገበያ ሽፋን፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት ወዘተ) ልዩነት
አላቸውን? ካላቸው የልዩነቱ ስፋት በምን ደረጃ ይገለጻል? ልዩነታቸውስ ከምን የመነጨ ነው ተብሎ ይታሰባል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
7. የመንግስት ሪፖርቶችና በተለያዩ አካላት በተለያዩ ጊዜያት የተካሄዱ ጥናቶች አምራች ኢንዱስትሪያችን በተፈለገው ፍጥነት እንዳላደገ
ያትታሉ፡፡ ያለደገበት ምክንያቶች ምን ምን ናቸው? ዋነኛ ተጠያቂውስ ማን ይሆን? እንዴት?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
8. የሀገር ውስጥ በለሃብት በአምራች ኢንዱስተሪ ስራ ዘርፍ እንዲሰማራ (በዘርፉ የሚሰማሩ አካላት በመመልመል፣ የሞቢላይዜሽን ስራዎች
በመስራት ወዘተ) ምን ተጨባጥ ስራ ተሰርቷል? ዉጤቱስ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
9. የአምራች ኢንዱስትሪዎች ከውስጣቸው የሚመነጩ ዋና ዋና ማነቆቹ ምንድን ናቸው? የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ፈጻሚ መስሪያቤቶቹ በምን
መልኩ ይፈቱታል? እስካሁን በተግባር የተኬደ ርቀትና የተገኘ ውጤት በሚገልጽ መልኩ ቢቀርብ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
10. የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት ድጋፍ ሰጪ መስሪያቤቶች የሚሰጡት የመንግስት አጋልግሎት ኢንዱስትሪው በተግባር
እየደገፉት እንዳልሆነ ይገለጻል (KOICA, 2013; World Bank, 2014)፤ እዉነታው ልክ ከሆነ ምክንያቱ ምንድን ነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
11. መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የፈቀዳቸው የማበረታቻ ፓኬጆች ጉድለት እንዳለበት (being functional instead of performance
based) ብቻ ሳይሆን የተፈቀደው ማበረታቻ በአግባቡ መተግበር እንዳልተቻለ በልዩ ልዩ ጥናቶች ይገለጻል (KOICA, 2013)፤ የዚህ
መሰራታዊ ችግር መነሻ ምክንያት ምንድነው? ተጠያቂውስ ማንነው? መፍትሔውስ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 292


12. በአምራች ኢንዱስትሪው ተሰማረቶ የሚገኝ የሰው ሀይል ሞያዊ፣ ፈጠራዊ፣ ሞያዊ ስነ-ምግባር/ኢንዱስትሪያል ባህል ከማዳበር አኳያ/፣ ስራ
አመራር ክህሎት ወዘተ ብቃቱና ተወዳደሪነቱ ምን ይመስላል? ኢንዱስተሪውን የሚፈልገው የበቃ እና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል ለማፍራት
የኢንዱስተሪ ሚኒስቴርና ፈጻሚ መስርያቤቶቹ ምን ተጨባጭ ስራ እየሰሩ ነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
13. ለኢንዱስትሪው የሚያስፈልገው የሰው ኃይል ልማት እየተከተልነው ያለን የትምህርትና የስልጠና ስርዓት (የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ትምህርት ተግባር ተኮር ከመሆነና ካለመሆን፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ውጤታማነት፣ በፋሪካዎች ደረጃ የሚሰጥ ስልጠናዎች ውጤታማነት
ወዘተ) ምን ያህል ውጤታማ ነው ተብሎ ይታመናል? (በተለይ የተካሄደ ጥናት ካለ መሰረት ተደርጎ ቢታይ)
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
14. ለኢንዱስትሪ ልማታችን ማነቆ ከሆኑት ጉዳዮች አንዱ በቴክኖሎጂ ልማት ሰፊ መሰረት አለመጣላችን መሆኑ በመታመኑ የቴክኖሎጂ ዓቅም
ለመፍጠር ከአጭር እና መካከለኛ ጊዜ አኳያ ቴክኖሎጂን ለማሸጋገር ኩረጃ ላይ ትኩረት አድርገን መስራት እንዳለብን እንደ አማራጭ
ስትራተጂ ተወስዶ እየተተገበ ቢሆንም ሀገር በቀል ፈጠራዎች ማስፋፋትም የግድ መሆኑ ታምኖበታል፡፡ በመሆኑም፡-

14.1. የቴክኖሎጂ የመቅዳት፣ የማላመድና የመጠቀም ዓቅማችን በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?


_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________________________________
14.2. በተካሄዱት የንግድና ስራ ፈጠራ ውድድር እንዲሁም በግላቸው በመገናኛ ብዙሓን በኩል ብቅ የሚሉ የፈጠራ ውጤቶች
ለኢዱስተሪው ልማት ግብአት ይሆኑ ዘንድ ፈጠራዎቹ ይበልጥ እንዲዳብሩ እና እንዲስፋፉ /እንዲለሙ/ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
ከመመለከታቸው አካለት (ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት፣
የፈጠራ ባለቤቶች ወዘተ) በመሆን የሰራው ተግባራዊ ስራ ምን አለ? ውጤቱስ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
15. የመንግስት ድጋፍ ጉድለት እና አሰራር መዛነፍ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዉጤታማነት አደጋ ላይ እንደሚጥልበት ስለሆነም ባለሀብቱ
በአምራች ኢንዱስትሪ ላለመሰማራት ምክንያት ሁኖታል የሚል ከሆነ ይህ ችግር እንዴት መፍታት ይቻላል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
16. የኢንዱስትሪዎች የግብኣት ችግር የሀገራችን አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ ምን ያህል ተጽኖ አሳድሮበታል? የግብአት ችግር የሚያጋጥማቸው
እና የማያጋጥማቸው ኢንዱስትሪዎ በየጊዜው እየተለዩ ችግሩ ከመድረሱ በፊት በታቀደ ሁኔታ መፍትሔ በማስቀመጥ አንዱስትሪው
የመምራት ልምዳችንና ክህሎታችን/ዓቅማችን/ ምን ይመስላል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 293


17. የግብአት ችግር የሌለባቸው ኢንዱስትሪዎች ጨምሮ ከዓቅም በታች እያመረቱ እንደሚገኙ እ.እ.አ በ2013 (KOICA) የተጠና ጥናት
ያሳያል፡፡ ምክንያታቸው ምንድነው? መፍትሔውስ ከመንግስት፣ በተለይም ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በላይ ነውን? እንዴት?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
18. የግብርና ምርቶች ዉጤት በግብኣትነት የሚጠቀሙት ኢንዱስትሪዎች ከሌሎች ኢንዱስትሪዎች በማነጻጻር ሲታይ ዕድገታቸው አመርቂ
እንዳልሆነ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በሁለተኛ የድገትና ሽግግር ዕቅዱ አመላክቷል፤ የገንዘብና የፋይናንስ ሚኒስቴር በ2011 ባካሄደው ጥናት
እንዲሁም ኮይካ በ2013 ጥናተ አመላክቷል፡፡ የዚህ መዋቅራዊ ችግር ምንድነው? ሴክተሩ መንግስት ቅድምያ ትኩረት የሰጠው ከመሆኑ ጋር
ተያይዞ ያለው እንደምታ ምንድ ነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
19. የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት በምን ደረጃ እንገኛለን? ሂደቱስ ምን ይመስላል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
20. በአምራች ኢንዱስትሪ ተሰማርተው ያሉትን ባለሀብቶች ከብክለት በተያያዘ ጉዳይ እየተቸገሩ እንደሚገኙ ይገለጻል፡፡ ይህ ጉዳይ
በኢንዱስተሪዎቹ ምን ያህል ተጽኖ እየፈጠረ ነው እንላለን? መፍትሔውስ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
21. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪያችን መሰረት መሆናቸው የሚታወቅ ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ ዘርፉን በእርግጥ የኢንዱስትሪ
ሰፊ መሰረት እንደሆን ከማብቃት አኳያ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚና ምንድነው? አሀን ያለው የዘርፉ አደረጃጀትስ ያመቻል ወይ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

22. የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲዩቶች የሀገራችን ኢንዱስትሪ ልማት በመንግስት ፋሲሊቴሽን ስራዎች፣ የአምራች ኢንዱስትሪ ቴክኒካዊ እና ስራ
አመራር ዓቅም ከማሳደግ፣ ዘርፉን የሚመለከቱ ፖሊሲዎችና ስትራተጂዎች ከማዘጋጀትና ከማስፈጸም፣ የዘርፉ ፕሮጀክት ፕሮፋይሎችን
ማዘጋጀት፣ ጥናትና ምርምሮችን ከማካሄድ አንጻር ምን ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

23. ከኢንዱስትሪ ልማት ስትራተጂያችን እና ሀገራዊ ፍላጎታችን የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲዩቶች አደረጃጀት እና ተልእኮ በቂ ነውን?
እንዴት?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 294


24. ለአምራች ኢንዱስትሪው ማነቆ የሆኑት የሎጂስቲክስ እና የኢንዱስትሪ ፋይናንስ ችግሮች እንዴት መፍታት ይቻላል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
25. ግብርና መር የኢንዱስትሪ ልማት ስትራተጂያችን በተግባር ለመተርጎም የኢንዱስትሪ ልማት ስትራተጂ ከጸደቀ ወዲህ በአምራች
ኢንዱስተሪው ላይ ምን ፕሮግራሞች እና ፕሮጀክቶች ተሰርተው ተተግብረዋል?
 በየዓመቱ/በተወሰነ ጊዜ/ የሀገር ውስጥ የግል እና መንግስት ኢንቨስትመንት ድርሻ በመለየት ከመስራት አኳያ
 በየዓመቱ/በተወሰነ ጊዜ/ በየሴክተሩ የሚውል የኢንቨስትመንት መጠን እየወሰኑ በመስራት ረገድ
 በየዓመቱ/በተወሰነ ጊዜ/ የሚታዩ ክፍተቶች በማስተካከል የኢንዱስትሪው የልማት ፍጥነት በማረጋገጥ ረገድ
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
26. በተለይ ከ1998 ወዲህ ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ እንዲሰማራ የተሰሩ ስራዎች?
 ፕሮጀክቶች ከመለየት ስራዎች ዕይታ
 የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በቀጥታ በማወያየት ሂደት በመስኩ እስከማሰማራት የተሰራው ስራ እና የተገኘ ውጤት
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
27. በአምራች ኢንዱስትሪ የተሰማሩት የመንግስት የልማት ተቋማት በምርታማነታቸው፣ ቢዝነስ ማነጅመንት ዓቅማቸው፣ የቴክኖሎጂ ልማትና
ሽግግር፣ የግብአት-ውጤት/ምርት-ግብይት ሰንሰለት አመራር ብቃታቸው፣ ወዘተ ምን ያህል ርቀት እየተጓዙ ይገኛሉ? ከተመሳሳይ የግል
ኢንዱስትሪዎች በአንጻራዊነት ግምገማ ይሻላሉን? የሚሻሉ ከሆኑ ለተመሳሳይ የግሉ ዘርፍ ማስተማርያ ሊሆኑ ይችላሉን? በተጨባጭ መረጃ
አስደግፈው ያብራሩት፡፡
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 295


አባሪ 5: ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከፍተኛ ባለሙያዎች እና አመራሮች ለውይይት የተዘጋጁ ጥያቄዎች
መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ምን ያህል ዓቅም እንዳለ እና የሀገር ውስጥ ልማታዊ ባለሀብቱ በዘርፉ
ተሰማርቶ ይበልጥ ተጠቃሚ የሚሆንበት ጥናት ለማካሄድ መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህም ሲባል ከሚመለከታቸው የመንግስት
አስፈጻሚ እና ድጋፍ ሰጪ መስሪቤቶች አስፈላጊውን መረጃ መሰብሰብ አስፈላጊ ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ ጥናት እንዲሳተፉ ዕድሉ ያገኙ
የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ትክክለኛ መረጃ በቅንነት በመስጠት ለጥናቱ ውጤታማነት ያልተቆጠበ አስተዋፅኦ
እንድያበረክቱ እና የችግሩ መፍትሔ የሚያፈላለግ አካል እንዲሆኑ ይጠየቃሉ፡፡ የሚሰጡት መረጃም ሆነ አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ በምንም
መልኩ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡
ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!
I- የተሳታፊዎች ዝርዝር መግለጫ

1. ተሳታፊዎች ዝርዝር
ስም ዝርዝር የት/ት የተመረቀበት ሙያ የስራ የስራ ኃላፊነት
ደረጃ ዓይነት ልምድ

II ለዉይይት የተዘጋዱ መነሻ ጥያቄዎች

1) መረጃዎች እንደሚያሳዩት አብዛኛዉ (በተለይ የሀገር ውስጥ) ባለሀብት በአምራች ኢንዱስተሪ ከመሰማራት ይልቅ በአገልግሎት መዋእለ
ንዋዩ የማፍሰስ አዝማምያ ይታይበታል፡፡ ባለሀብቱ ይህንን ዘርፍ የሚመርጥበት ምክንያቶች ይታወቃሉ ወይ? ከታወቁ ምንድናቸው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________

2) የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሀብቱ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ስምሪት (manufacturing, agriculture, services) የምጣኔው ልዩነት
ምክንያት ምንድ ነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 296


3) የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ እንዲሰማራ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን በተግባር የሚገለጽ የሰራው ስራ ምንድነው? በሌሎች
የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያቤቶችስ የተደረገ ጥረት አለ ወይ? ውጤታቸው ምን ይመስላል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________

4) መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የፈቀዳቸው የማበረታቻ ፓኬጅ ጉድለት እንዳለበት (being functional instead of performance
based) ብቻ ሳይሆን የተፈቀደው ማበረታቻዎች በአግባቡ መተግበር እንዳልተቻለ በልዩ ልዩ ጥናቶች ይገለጻል (KOICA, 2013)፤ ይህንን
መሰራታዊ ችግሩ ምንድነው? ተጠያቂውስ ማን ይሆን? መፍትሔውስ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________

5) በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የተፈቀዱ የማበረታቻ ስልቶች (የካፒታል፣ የማነጅመንት ወዘተ) ዓላማዎች ዙርያ ባስፈጻሚው
የመንግስት አካላት እና በባለሀብቱ ዘንድ ያለው ግንዛቤ ምንድነው? የማበረታቻ ስልቶቹስ አምራች ኢንዱስትሪው በልዩ ሁኔታ
የሚያበረታቱ ናቸውን? ካልሆነ ለምን?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________

6) ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ ላለመሰማራት ከመንግስት ድጋፍ ጉድለት እና አሰራር መዛነፍ ምክንያት ኢንዱስትሪው ኪሳራ ሊከሰትበት
እንደሚችል ስጋት የሚፈጠር ከሆነ ይህ ችግር እንዴት መፍታት ይቻላል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________

7) በአምራች ኢንዱስትሪ የሚሰማራው ባለሀብት የሚያነሳው የኢንቨስትመንት ዋስትና ጉዳይ እና የገበያ ከለላዎች ካሉ ምን ምን መሆናቸውን?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 297


አባሪ 6: በየደረጃው ከሚገኙ የጥቃቅና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጀንሲዎች፣ ቢሮዎችኽ ጽ/ቤቶች (ፌደራል፣ ክልሎችና
ከተሞች) ከፍተኛ ባለሙያዎችና አመራሮች ጋር ለውይይትና ቃለ መጠይቅ የተዘጋጁ ጥያቄዎች

መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ምን ያህል ዓቅም እንዳለ እና ልማታዊ ባለሀብቱ በዘርፉ ተሰማርቶ ይበልጥ
ተጠቃሚ የሚሆንበት ጥናት ለማካሄድ መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ደግሞ ዋነኛ የአምራች
ኢንዱስትሪ መሰረት መሆናችው በማወቅ ያላሰለሰ ስራ ሲሰራበት የቆየ ሲሆን በዘርፉ ያለቸው ተሳትፎ እንዲሁም የዕድገት ዕድል ከአጠቃላይ
የአምራች ኢንዱስትሪዎች ልማት በአንድነት ማጥናት ተገቢ ሁኖ ተገኝቷል፡፡ በመሆኑም ከሚመለከታቸው የመንግስት አስፈጻሚ እና ድጋፍ
ሰጪ መስሪቤቶች አስፈላጊዉን መረጃ መሰብሰብ አስፈላጊ ነው፡፡ በዚህ ጥናት እንዲሳተፉ ዕድሉ ያገኙ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና
ባለሙያዎች ትክክለኛ መረጃ በቅንነት በመስጠት ለጥናቱ ዉጤታማነት ያልተቆጠበ አስተዋፅኦ እንድያበረክቱ ይጠበቃል፡፡ የሚሰጡት መረጃም
ሆነ አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡
ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!
I- የተሳታፊዎች ዝርዝር መግለጫ

1. የተቋሙ ስም _______________________________________________________________________________________________
2. ተሳታፊዎች ዝርዝር
ስም የት/ት ደረጃ የተመረቀበት የስራ ልምድ የስራ ኃላፊነት
ሙያ ዓይነት

II- የውይይቱ መነሻ ጥያቄዎች

1. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፐራይዞች በአምራች ኢንዱስትሪዎች ያላቸውን ስምሪት እጅጉን ዝቅተኛ የሆነበት ዋና ዋና ችግሮችና ማነቆዎች
ምንድናቸው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________

2. ጥቃቅና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ዋና መሰረት እና መፍጠርያ መሆናቸውን አውቀን በአምራች ኢንዱስትሪ የተሳካ ጉዞ
እንዲያደርጉ (በየደረጃው) ምን ተጨባጭ ስራ ተሰራ?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________

3. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች እርስ በራሳቸው እና ከመካከለኛ አና ከከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች በግብኣትና ዉጤት ሰንሰለት (Input-
output value addition chain) እንዲተሳሰሩ እና አብረው እንዲያድጉ ምን ዓይነት ስራ ተሰርቷል? በአሃዝ የሚገለጽ ነገር ካለ?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 298


4. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ መሠረት መሆናቸው ከታወቀ እነዚህ ኢንተርፕራይዞች በአምራች ኢንዱስትሪ
እንደሰማሩ እና እንዲያድጉ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በጋራ የተሰራ ተጨባጭ ስራ ካለ?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________

5. ለኢንቨስትመንት የሚያበቃ ዓቅምን ያካበቱ አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በአምራች ኢንቨስትመንት ለመሰመራት ይችሉ ዘንድ
ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን/ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮዎች/ከተሞችና ወረዳ ኢንቨስትመንት ጽሕፈት ቤቶች በተጨባጭ እየተሰራ ያለ ስራ
ምንድን ነው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________
6. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዕድገት ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪ ለመሰማራት ሲመለመሉ አልያም
ራሳቸው ሲያመለክቱ ስለሚመርጡት ዘርፍ የቢዝነስ ዕድል የሚያውቁበት ስልት አለ ወይ? ከሌለ ይህንን የዕይታ ግብኣአት ከዬት ያገኛሉ?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________

7. በአንደ አንድ ጥናቶች እንደሚንገነዘበው የአብዘኞቹ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፐራይዞች ትኩረት ከረጅም ጊዜ የልማትና የመስፋፋት
ራዕይ ይልቅ ላጭር ጊዜ ዕድገት የሚንቀሳቀሱና ባመዛኙ የጥገኝነት መንፈስ የሚታይባቸው ናቸው (ለምሳሌ በፍጥነትና በስፋት የደረጃ
ሽግግር አለማድረግ)፡፡ እንደ ኢንቨስትመንት መስተንግዶ ተቋምነታችሁ የዚህ ድምደሜ ዕውነታ ምን ድረስ ነው? መልሱ እውነት ከሆነ
መፍትሔው ምን ይሁን?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________

8. በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ልማት በኢንዱስትሪ ዘርፍ በካፒታል፣ በጥሬ እቃ አቅርቦት፣ በተስማሚና በተወዳዳሪ
ቴክኖሎጂ አቅርቦት፣ በገበያ፣ በሰለጠነ የሰው ኃይል፣ በመሠረተ ልማትና አገልግሎት አቅርቦት፣ በገበያ ትስስር ወዘተ ረገድ
በሀገራችን ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ምን ይመስላል?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________
9. የተቋማቱ አንጻራዊ ስልጠት (Relative Efficiency) ከግብአት ምርታማነት፣(Factor Productivities) ከጥልቀት
(Intensity)እና ከቴክኒካዊ ስልጠት (Technical Efficiency) አኳያ ሲቃኝ አፈጻጸሙ ምን ይመስላል?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________
10. አሁን ባለንበት ሁኔታ ማለትም አብዛኞቹ ኢንተርፕራይዞቻችን በአገልግሎት እና ንግድ በተሰማሩበት እንዲሁም የዕድገት ደረጃቸው
ዘገምተኛ በሆነበት (ለምሳሌ የከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር 1998-2004 ስታቲስቲካዊ መጽሔት መረጃ
እንደሚያሳየው) ኢንተርፕራይዞቻችን የኢንዱስትሪ መሰረት መሆን ይችላሉ ተብሎ ይታመናል? እንዴት? ካልሆነ አፋጣኝ መፍትሔው
ምን ሊሆን ይችላል?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________

11. የመንግሥት ፖሊሲዎች ሴክተሩን ከማገዝ አኳያ /በተለይም በረዥም ጊዜ ብድር፣ በዘርፉ የመቆየትን እድል በማስፋትና ሌሎች
ማበረታቻዎች በማቅረብ የማምረቻ ሥፍራዎችን (industrial estates) በማዘጋጀት ረገድ የቱን ያህል አጋዥ ናቸው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 299


12. የኤ.ፌ.ዴ.ሪ መንግስት የልማት ስትራጂ የግሉን ሴክተር እንደ ስትራቴጂክ አጋርና እንደ ኢኮኖሚው ዋነኛ አንቀሳቃሽ ሞተር
ተቀብሏታል፡፡ /2ዐዐ1፡5/፡፡ ለሴክተሩ ካላችሁ ቀረቤታ አንጻር በእናንተ ሥር የተደራጁት የኢንዱስትሪ ማህበራት አንቀሳቃሾች
ለዚህ ልማታዊ ግብ ያላቸወ ቁርጠኝነት ምን ድረስ ነው?/ መልሱ በግምት በመቶኛ ቢገለጽ
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________
13. በጥቃቅንና በአነስተኛ በመካከለኛ እና በታላቅ እና ኢንዱስትሪዎች መካከል ያለው የውድድር መንፈስ እንዴት ይገለጻል?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________
14. የጥቃቅንና የአነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ልማታዊ ፋይዳ ከመካከለኛና ከታላላቅ ኢንዱስትሪዎች ጋር ሲነፃፀር ለሀገራዊ
ኢኮኖሚያዊ እድገትና ልማት አስተዋጽኦአቸው ምን ያህል ነው? እንዴት ሊሆን ቻለ? ባጭሩ ቢያመለክቱ?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________
15. በሁለተኛው የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ የግብርናው ሴክተር አሁን ከሚገኝበት የ(Primary Production) ወደ
ኘሮሰሲንግና ግብይት (Marketing) እንደሚሸጋገር ግብ ተነድፏል ከዚህ አኳያ ግብርና የሚፈጥረውን ተረፈ ካፒታል፣
ጉልበት፣ የውጭ ምንዛሬ፣ ወዘተ በሚገባ ለመጠቀም ሴክተሩ ምን ያህል ተዘጋጅቷል? የዝግጅቱ ምዕራፍስ በምን ይገለጻል?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________
16. የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት አደረጃጀት ከኢንዱስትሪ ልማት ሁኔታ ሲታይ ተቋሙ ባለበት ወይስ ከኢንዱስትሪ
ሚኒስቴር/ቢሮዎች/ ጽሕፈት ቤቶች ጋር ቢሆን ይመረጣል ይላሉ? እንዴት?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________
17. በአምራች ኢንዱስትሪዎች የሚሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚፈቀድላቸው የመነሻ ካፒታል እና የስራ ማስኬጃ የፋይናንስ
መጠን በቂ ነውን? ካልሆነ መፍትሔውስ?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________
18. በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ስትራተጂያችን አሉ የምሉዋቸው መሰረታዊ ውስንነቶች ምንድናቸው?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________

19. ከጥቃቅንና አነስተኛ ወደ መካከለኛና ከፍተኛ ባለሀብትነት እየተሸጋገሩ ያሉት አንቀሳቃሶች ምን ዓይነት ድጋፍ ይደረግላቸዋል? ቀጣይ
የስራ ዘርፍ ስምሪትስ ገደብ ይደረግባቸዋልን?
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 300


አባሪ 7: ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሶች መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ የፅሁፍ መጠይቅ

መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ምን ያህል ዓቅም እንዳለ እና ልማታዊ ባለሀብቱ በዘርፉ ተሰማርቶ ይበልጥ
ተጠቃሚ የሚሆንበት ጥናት ለማካሄድ መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ደግሞ ዋነኛ የአምራች
ኢንዱስትሪ መሰረት መሆናችው በማወቅ ያላሰለሰ ስራ ሲሰራበት የቆየ ሲሆን በዘርፉ ያላቸው ተሳትፎ እንዲሁም የዕድገት ዕድል ከአጠቃላይ
የኣምራች ኢንዱስትሪዎች ልማት በአንድነት ማጥናት ተገቢ ሁኖ ተገኝቷል፡፡ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚመለከት መረጃ
በየደረጃው ከሚገኙ ዘርፉን የሚመሩ የመንግስት አካላትና እና ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ከራሳቸው መሰብሰብ ተገቢ
ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ጥናት እንዲሳተፉ ዕድሉ ያገኙ የጥቃቅና አነስተስታኛ ኢንተርፕራይዞች አንቀሳቃሾች ይህንን መጠይቅ ትክክለኛ መረጃ
በመሙላት እንዲተባበሩና ለዘርፉ ቀጣይ ስኬት የራስዎን አሰተዋጽኦ እንድያበረክቱ ይጠበቃል፡፡ የሚሰጡት መረጃም ሆነ አስተያየት ከዚህ
ጥናት ውጭ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!

I- ይህንን መጠይቅ የሞላው አንቀሳቃሽ ግለሰብ/ኢንተርፕራይዝ/ አጠቃላይ መግለጫ


1. ኢንተርፕራይዙ የተሰማራበት የስራ ዘርፍ .
በአገልግሎት በችርቻሮ ንግድ በኮንስትራክሽን በአምራች ኢንዱስትሪ
2. የተቋቋመበት ዘመን _______/___________/___________ዓ/ም_
3. ሕጋዊ ሰብነት ዓይነት ... በግል  ሕብረት ሽርክና ሕብረት ስራ ማሕበር  ኃላ/የተ/የግል ማሕበር

II- የጥናቱ ጥያቄዎች


1. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፐራይዞች በአምራች ኢንዱስትሪዎች በብዛት ላለመሰማራት ምክንያት ናቸው ከሚባሉት ከዚህ በታች
ተዘርዝረዋል፡፡ እነዚህ ምክንያቶች በክበደት ደረጃቸው ያመልክቱ?
ዝርዝር ምንክያት የክብደት ደረጃ
እጅግ ከፍተኛ ከፍተኛ መካከለኛ ዝቅተኛ ችግር አይደለም
ከሌሎች ዘርፎች ትርፋማነቱ ዝቅተኛ መሆኑ
ከሌሎች ዘርፎች ትልቅ የመነሻ ከፒታል (ገንዘብ) ስለሚጠይቅ
ሙያዊ ክህሎት እና ዕዉቀት ያለመኖር
ትርፍ ከማግኘት ከሌሎች ዘርፎች የበለጠ ረጅም ጊዜ ስለሚጠይቅ
የማሽነሪ ብድር አለያም ማሽነሪ አለማግኘት
የገበያ እና የአዋጭነት ዕውቀት ማነስ
የግአት ጥሬ ዕቃ ማነስ

ከላይ በሰንጠረዡ ያልተጠቀሱ ሌሎች መሰረታዊ ችግሮች ካሉ ከዚህ በታች ይዘርዝሩ


ሀ/_________________________________________________________________________________________________________________________
ለ/_________________________________________________________________________________________________________________________
ሐ/_________________________________________________________________________________________________________________________

2. እርስዎስ በአምራች ኢንዱስትሪ ላለመሰማራት ምክንያት ከሆኑዋቸው ምክንያቶች በክበደት ደረጃቸው ያመልክቱ?
ዝርዝር ምንክያት የክብደት ደረጃ
እጅግ ከፍተኛ ከፍተኛ መካከለኛ ዝቅተኛ ችግር አይደለም
ከሌሎች ዘርፎች ትርፋማነቱ ዝቅተኛ መሆኑ
ከሌሎች ዘርፎች ትልቅ የመነሻ ከፒታል (ገንዘብ) ስለሚጠይቅ
ሙያዊ ክህሎት እና ዕዉቀት ያለመኖር
ትርፍ ከማግኘት ከሌሎች ዘርፎች የበለጠ ረጅም ጊዜ ስለሚጠይቅ
የማሽነሪ ብድር አለያም ማሽነሪ አለማግኘት
የገበያ እና የአዋጭነት ዕውቀት ማነስ
የግአት ጥሬ ዕቃ ማነስ
ከላይ በሰንጠረዙ ያልተጠቀሱ ሌሎች መሰረታዊ ችግሮቼ ናቸው የሚሉዋቸው ከዚህ በታች ይዘርዝሩ
ሀ/_________________________________________________________________________________________________________________________
ለ/_________________________________________________________________________________________________________________________
ሐ/_________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 301


3. በአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰማሩት የጥቃቅንና አነስተኛ አንቀሳቃሾች/ኢንተርፕራይዞች/ በግብአትና ግብይት የተሻለ ትስስር የሚፈጠረው
ከየትኛው ነው? እርስ በራሳቸው፣ ከመካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ጋር ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ጋር

4. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች እርስ በራሳቸው እና ከመካከለኛ አና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች በግብኣትና ዉጤት ሰንሰለት (Input-
output value addition chain) ትስስር እንድፈጥሩ የማድረግ ሓላፊነት የማን ነው ይላሉ?
የአንቀሳቃሹ የራሱ  የጥቃቅንና አነስተኛ አንድ ማእከሉ አገልግሎት

5. የቴክኒክና ሙያ የስልጠና ተቋማት በአምራች ኢንዱስትሪው ለሚሰማሩ/ለተሰማሩት/ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በተግባር
የሚሰጡት ድጋፍ የትኛው ነው? የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር ሙያዊ የክህሎት ስልጠና የስራ ፈጠራ
6. ከላይ በጥያቄ ቁጥር 5 ከተጠቀሱት የቴክኒክና ሙያ ድጋፎች የተሻለ ውጤታማ የትኛው ነው? _________________________________________________
7. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የዕድገት ሽግግር ፍላጎታቸው በምን ደረጃ ይገመገማል?
ከፍተኛ  መካከለኛ  ዝቅተኛ 
8. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የዕድገት ሽግግር ፍላጎታቸው ዝቅተኛ የሚሆንበት ዋነኛ ምክንያት ምንድነው?
 ከተሸገገሩ የሚጣልባቸው የግብር መጠን ከፍተኛ ስለሚሆን ነው 
ለሽግግር የሚያበቃ ዓቅም ስለማያፈሩ የተለያዩ
የመንግስት ድጋፎች ስለሚቋረጡ  ከሽግግር በኃላ ለዕድገቱ የሚመጥን ድጋፍ ስለማይሰጥባቸው 
ሌላ ምክንያት ከሆነ ይጥቀሱ___________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________
9. አንድን ጥቃቅንና አነስተኛ አንቀሳቃሽ በአምራች ኢንዱስትሪ ለመሰማራት የሚያስፈልገው አማካኝ የመነሻ ካፒታል ምን ያህል ሊሆን
ይችላል? _________________________ ብር
10. ሰዎች በጥቃቅናና አነስተኛ ኢንተርፐራይዝ ልማት ለመሰማራት ሲፈልጉ የሚመርጠት ዓይነት አደረጃጀት ምን ዓይነት ነው?
በግል፣ በሕብረት ሽርክና ማሕበር፣ በሕብረት ስራ ማሕበር ፣ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማሕበር
ምክንያቱስ ምንድነው? _______________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
11. በሕብረት ሽርክና ወይም በሕ/ስ/ማሕበር መልክ በመደራጀት የፋይናንስ ዕጥረት ችግር መፍታት ይቻላል ብለው ያምናሉ?
ያስችላል አያስችልም
አያስችልም የሚሉት ከሆነ ምክንያቱን ያብራሩ _____________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
ያስችላል የሚሉ ከሆነ ለምን ሰዎች በግል መስራት ይመርጣሉ _______________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________
12. በአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፐራይዞች በፍጥነት የደረጃ ሽግግር እንድያደርጉ ራሳቸው አንቀሳቃሾች
ሊሰሩት የሚገባ ምንድነው ብለው ያስባሉ? ___________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
________________________________________________________________________________________________________________________________________________

13. ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በብዛት በአምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲሰማሩ ከመንግስት የሚፈልጉት፣ ነገር ግን በራሳቸው ጥረት
መፍታት ያልቻሉት/መፍታት የማይችሉት/ ድጋፍ ምንድናቸው ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________________________________

14. በአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰማሩት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች/አንቀሳቃሾች/ ለውድቀት የሚዳርጓቸው ዋና ዋና ምክንያቶች
ይዘርዝሩ
ሀ/______________________________________________________________________________________________________________________________________________
ለ/______________________________________________________________________________________________________________________________________________
ሐ/_____________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 302


አባሪ 8: ከግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር እና ክልል ቢሮዎች ከፍተኛ ባለሙያዎችና ኃላፊዎች ጋር ለውይይት የተዘጋጁ ጥያቄዎች

መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ምን ያህል ዓቅም እናዳለ እና ልማታዊ ባለሀብቱ በዘርፉ ተሰማርቶ ይበልጥ
ተጠቃሚ የሚሆንበት ጥናት ለማካሄድ መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ በሀገራችን ግብርና መር የኢንዱትተሪ ልማት ስትራተጂ ግንባር
ቀደም ትኩረት የተሰጠው የኢንዱስትሪ ዘርፍ የግብርና ምርቶች በግብአት የሚጠቀም ዘርፍ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ባለፈም በገጠር ልማት
በተሰራው ስራ ቁጥሩ ቀላል የማይባል አርሶ አድር እንዲሁም አርብቶ አደር ወደ መካከለኛ እና ከፍተኛ ባለሃበትነት እየተሸጋገረ ይገኛል፡፡
በመሆኑም የግብርናው ትርፍ ጉልበትና ምርት/ሃብት/ በአምራች ኢንዱስትሪ ልማት መሰማራት የሚችልበት ዕድል ከአጠቃላይ የአምራች
ኢንዱስትሪዎች ልማት በአንድነት ማጥናት ተገቢ ሁኖ ተገኝቷል፡፡ በመሆኑም ከሚመለከታቸው የመንግስት አስፈጻሚ እና ድጋፍ ሰጪ
መስሪቤቶች አስፈላጊዉን መረጃ መሰብሰብ ተገቢ ይሆናል፡፡ በዚህ ጥናት እንዲሳተፉ ዕድሉ ያገኙ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች
ትክክለኛ መረጃ በቅንነት በመስጠት ለጥናቱ ውጤታማነት ያልተቆጠበ አስተዋፅኦ እንድያበረክቱ ይጠበቃል፡፡ የሚሰጡት መረጃም ሆነ
አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!


I- የተሳታፊዎች ዝርዝር መግለጫ

1. የተቋሙ ስም _______________________________________________________________________________________________
2. ተሳታፊዎች ዝርዝር
ስም የት/ት ደረጃ የተመረቀበት የስራ ልምድ የስራ ኃላፊነት
ሙያ ዓይነት

II- ለውይይት የተዘጋጁ መሪ ጥያቄዎች


1) በገጠር ልማት በተሰራው ተከታታይና እልህ አስጨራሽ ጥረት ከ25-30 በመቶ የሚሆነውን አርሶ አደር እና አርብቶ አደር ለገበያ የሚሆን
ትርፍ ምርት (commercial scale produce) ማምረት እንደቻለ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከዚህ ጋር ታየይዞም ቁጥሩ ቀላል የማይባል
አርሶ አደር እና አርብቶ አደር ወደ መካከለኛ እና ከፍተኛ ባለሀብትነት እየተሸጋገረ ይገኛል፡፡ ይህ ዓይነት የግብርናው ትርፍ ምርት በምን
መልክ ያከማቸዋል/በምን ኢንቨስትመንት ያሰማረዋል/?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
2) ወደ ባለሀብትነት እየተሸጋገረ የሚገኘው አርሶ አደር እና አርብቶ አደር የሚያስመዘገብው ሀብት በምን መልክ ነው (ጥሬ ገንዘብ፣ ማሽነሪ፣
ቋሚ ህንጻ፣ ሰብል ምርት ግምት፣ የቋ ተክል ግምት፣ የእንስሳት ግምር፣ ተሽከርካሪ፣ ማንኛውም ዓይነት ፋብሪካ ወዘተ)?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 303


3) ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች በየክልሉ እና በፌደራል ደረጃ በየዓመቱ ሸልመን ዕዉቅና መስጠት ተገቢ
እና ለበለጠ ምርታማነት የሚያነሳሳ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ነገር ግን ወደ ባለሀብትነት እየተሸጋገረ ያለው አርሶ አደርና አርብቶ አደር
ሀብታቸውን በቀጣይነት እሴት በሚጨምር የኢንቨስትመንት መስክ እንድያሰማሩ ከማድረግ አኳያ የግብርና እና ገጠር ልማት ሚኒስቴር
እና የክልሎች ግብርና ገጠር ልማት ቢሮዎች በሚመለከታቸው ደረጃ ምን ዓይነት ተጨባጭ ሚና እየተጫወቱ ነው? ጥረቱ ካለ ትርፍ
አምራች አርሶ አደርና አርብቶ አደር በምን ዓይነት የኢንቨስትመንት መስክ እንድያሰማሩ ይፈለጋል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________

4) ትርፍ አምራች አርሶ አደርና እርብቶ አደር ወደ አምራች ኢንዱስትሪ እንዲሰማራ የተደረገ ተጨባጭ ስራ ምን ኣለ? ይህንን ስራ ከመስራት
አኳያ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የኢንቨስትመንት ኮሚሽን አልያም በየክልሉ ያሉ ቢሮዎች ምን ዓይነት ግንኙነት አለን?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________

5) የግብርና ምርቶች በግብኣትነት የሚጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች ሁሉንም ከዓቅም በታች የሚሰሩበት ምክንያት አንዱ የግብአት ችግር መሆኑ
በርካታ ጥናቶችና ሪፖርቶች ይጠቁማሉ፤ ስለዚህ የግብርና ዘርፋችን ምን ያህል ትርፍ አምራች ነው ማለት ይቻላል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________

6) የሀገራችን የግብርና ምርቶች በተለይ ጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች እንዲሁም የቁም እንስሳት እሴት ሳይጨመርበት ወደ ዉጭ ሰደድ
የሚደረግበት ሁኔታ ለማስቀረት መፍትሔው ምንድነው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 304


አባሪ 9: ከደደቢት ቁጠና ብድር፣ አማራ ብድርና ቁጠባ፣ ኦሮምያ ብድርና ቁጠባ፣ ኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ፣ ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ እና
አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ለቃለ መጠይቅ የተዘጋጁ ጥያቄዎች
1. አጠቃላይ መረጃዎች
1.1. ተቋሙ በማን ተቋቋመ? ___________________________________________________________________________________
1.2. መነሻ ካፒታል መጠኑ በብር? _____________________________________________________________________________________
1.3. የመነሻ ካፒታል መዋጮ በአመንጪና በመቶኛ?
አመንጢ መዋጨ በመቶኛ
ሀ. ____________________ ______________________ %
ለ. ____________________ ______________________ %
ሐ. ____________________ ______________________ %
1.4. የተቋሙ ተልዕኮዎች
_______________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________________________________
1.5. የ2006 በጀት ዓመት መረጃ መሰረት በማድረግ የተቋሙ አገልግሎት ቀጥተኛ ተገልጋዮች ተጠቃሚዎች (በዘርፍበመቶኛ)
በዘርፍ በመቶኛ
ሀ. በግብርና ዘርፍ ______________________ %
ለ. በኢንዱስትሪ ዘርፍ ______________________ %
ሐ. በአገልግሎት ዘርፍ ______________________ %
መ. ሌሎች ካሉ ______________________ %

2. ዝርዝር መረጃዎች/ከአፈጻፀም አካላት/


2.1. ተቋሙ እስከ 2ዐዐ6 ያበደረው የካፒታል መጠን በብር ___________________________________________________________________________
2.2. የተበዳሪዎች ድርሻ በብርና በመቶኛ
በዘርፍ በብር በመቶኛ
ሀ. ግብርና ______________________ ______________________ %
ለ. ኢንዱስትሪ ______________________ ______________________ %
ሐ. አገልግሎት ______________________ ______________________ %
2.3. የተበዳሪዎች የመመሪያ አካባቢና የመቶኛ ድርሻ
በገጠር ______________________ %
በከተማ ______________________ %
2.4. የብድር ዓይነት በዝርዝር /over draft, mortgage, bridging fund, investment etc/
በብር በመቶኛ
1. ____________________ ______________________ %
2. ____________________ ______________________ %
3. ____________________ ______________________ %
4. ____________________ ______________________ %
5. ____________________ ______________________ %

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 305


3. ተቋማዊ መረጃዎች
3.1. ተቋሙ የሚያካሄደው የአገልግሎት እንቅስቃሴ ተቋሙን ከፍተኛው የፋይናንስ አገልግሎት ተቋም ጋር ያመሳስለዋል?
ከንግድ ባንክ
ከልማት ባንክ
3.2. በእንቅስቃሴው ከንግድ/ወይንም ከልማት ባንክ አገልግሎት ጋር እንዲመሳሰል ያስፈለገበት ምክንያት ምንድን ነው?
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.3. አንዳንድ የዘርፉ ተመራማሪዎች የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን የሚመለከቷቸው መንግሥታዊ የልማት ባንኮችን ድክመት (የአነስተኛ
የኢንቨስትመንት ብድር ፍላጎት ከማሟለት ተደራሽነት አኳያ) ተከትለው ብቅ እንዳሉ የፋይናንስ አገልግሎት ተቋማት ነው? ይህ
እይታ ከሀገራችን ተሞክሮ አንጻር ሲገመገም ምን ያህል እውነታነት አለው?
________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.4. ተቋማቱ የመንግሥታዊ የልማት ባንኮችን ውድቀት ተከትለው የመጡ ከሆነ ለመሆኑ በእንቅስቃሴአቸሁ ምን ያህል የባለንብረቶቹን
(ባለቤቶቹ) ና የተገልጋዬች ፍላጐት አርክተዋል?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.5. የተቋሙ ተሞክሮስ ምን ያመለክታል?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.6. ባንኩ ከሚሰጠው አገልግሎት አኳያ የኢንዱስትሪውን ዘርፍ በአጠቃላይ የማኑፋክቸሪንግ ንኡስ ሴክተሩን በተለይ ፍላጐት ለማርካት
ምን ያህል የተዘጋጀ ነው?
________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.7. እንደ ፋይናንሻል አገልግሎት/ተቋምነታችሁ ከ risk አንፃር ሲታይ ተቋሙ ምርጫ ቢሰጠው ለየትኛው ዘርፍ ቢያበድር ያዋጣዋል?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.8. አንዳንድ በቅርብ የወጡ መረጃዎች ባንኮችን ባጠቃላይ የፋይናንስ አገልግሎት ዘርፉን በተለይ የወለድ መጠኑ ገደቦች (Interest
Rate Restrictions) ባንኮች ደሀ አካባቢዎችን በማገልገል በኩል እጅጐን ገደብ ጥሎባቸዋል ይላሉ፡፡ ከሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ
አንፃር ይህ አስተያየት ምን ያህል ተቀባይነት አለው?
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 306


3.9. የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ብድር በማቅረብ በተጨማሪ ቁጠባንም ያስተናግዳሉ ከዚህ አኳያ ተቋሙ በዚህ አገልግሎት ዘርፍ ምን
ደረጀ ላይ ነው?
________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.10. ቁጠባ በማበረታታት ረገድ የትኛው ዘርፍ (ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ አገልግሎት) ነው የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገበው?
________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.11. የተገልጋዮች ብድር የመመለስ ባህልስ ምን ይመስላል? /በአዎንታዊ ወይንም በአሉታዊ መልክ ቢገለጽ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________

3.12. በተለይ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለኢንቨስትመንት የተፈቀደ ብድር ተጠቃሚው ለተፈቀደለት ዓላማ እያዋለው መሆኑ
እየተከታተሉ ኢንቨስትመንቱ የማስተግበር ስራ ይሰራልን?
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.13. ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚፈልጉትን የፋይናንስ አቅርቦት በሽፋንና በወለድ ምጣኔ ተደራሽ
እንዲሆኑ የሚሰጡት አጠቃለይ አስተያየት ካለ?
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3.14. አሁን በስራ ላይ የሚገኝ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚፈቀድ የብድር ጣሪያ በቂ እንዳልሆነ በተጠቃሚዎችና ሌሎች
አካለት በስፋት ይወሳል፡፡ የተቋምዎ ዕይታስ ምንድነው? ዕይታው ትክክል ከሆነ እና የብድር ተሪያው መሻሻል የሚያስፈልገው ከሆነ
መፍቀድ ያለበት መን ነው?
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________________________________________________________________
________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 307


አባሪ 10: በአስመጪነት፣ ላኪነትና ከፍተኛ ደረጃ አከፋፋይነት ለተሰማሩ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች የተዘጋጀ የፅሁፍ መጠይቅ

መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ የሀራችን አምራች አንዱስትሪ በምን ደረጃ እንዳለ እንዲሁም በተለያዩ የዘርፎች ተሰማርቶ የሚገኝ በለሀብታችን
የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለመቀላቀል ያሉትን ተግዳረቶች ለማወቅ ይቻል ዘንድ የሚፈለገውን መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ የጥናቱ
ዓላማም አምራች ኢንዱስትሪው ያሉት ችግሮች ከመሰረታቸው መረዳትና ዘርፉን ለማሳደግ በሀገር ደረጃ ሊኖሩን የሚችሉ መልካም ዕድሎች
በመለየት አምራች ኢንዱስትሪው በገበያ ተወዳዳሪ ሁኖ እንዲቀጥልና ይበልጥ እንዲሰፋ የሚያስችል ሁኔታ መፍጠር ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ
ጥናት የሚሳተፉት ባለሀብቶች ትክክለኛ መረጃ በመስጠት አምራች ኢንዱስትሪው የሚያድግበት መፍትሔ ለማፈላለግ ያልተቆጠበ አስተዋፅኦ
እንዲያበረክቱ ይጠበቃል፡፡ ጥናቱ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራስያዊ ሪፓብሊክ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማእከል የሚካሄድ ነው፡፡
የሚሰጡት መረጃም ሆነ አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ በምንም መልኩ ለሌላ ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ
ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡
ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!

1. በአስመጪነት እና ላኪነት የንግድ ስራ የተሰማሩ ኩባንያዎች ሕጋዊ ሰውነታቸው በአብዛኛው በግለሰው ደረጃ (Sole ፕroprietorship)
በሁለተኝነትም ኃ/የተ/የግል ማሕበር (Private Limited Companies) መልክ የተደራጁ ናቸው፡፡ በአንጻሩ ሽርክና ማሕበር እና
አክሲዮን ማሕበር እነዲሁም ሕብረት ስራ ማሕበር ቁጥራቸው ጥቂት ነው፡፡ ምክንያቱ ምንድነው?
________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________
2. በወጪ ሰደድ እና ገቢ ንግድ የተሰማራ የንግዱ ማሕበረ-ሰብ ሲወዳደር በአብዛኛው በአስመጪነት ስራ ዘርፍ ተሰማርቶ ይገኛል፡፡ ይህንን
ዓይነት ስምሪት ከምን የመነጨ ነው ማለይ ይቻላል?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________
3. በውጭ ሰደድ ንግድ ስራ (Export) የተሰማራ ባለሀብት አብዛኛዉን የኢንዱስትሪ ውጤቶች ምርት ከመነገድ ይልቅ ጥሬ
ምርት ሰደድ ላይ የሚበዛበት ምክንያትስ ለምንድነው?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________
4. አብዘኛውን በአስመጪነትና ላኪነት እንዲሁም አካፋፈይነት የንግድ ስራ የተሰማራው ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪው ለመሰማራት
ያለው ፍላጎት በምን ይገለጻል?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________
5. የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ በስፋት ተሰማርተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ከሀገራችን ኢኮኖሚ እና
የባለሀብቱ አጠቃላይ ሁኔታ የተቃኘ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲዎችና ስተራተጂዎች ነድፎ ከመተግበር በተጨማሪ በዘርፉ
ኢንቨስትመንት ለተሰማሩ የማበረታቻ ፓኬጅ (የግብር እፎታ፣ ብድር ቅድምያ እንድያገኝ፣ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክት ዝግጅት ምክር
አገልግሎ እንዲያገኝ፣ መሬት በምደባ ቅድሚያ እንዲሰጠው ወዘተ) ቀርጾ እየተገበረ ሲሆን ዘርፉን የሚደግፉ የኢንዱስትሪ ልማት
ተቋማት ሳይቀር አደራጅቶ የግሉን ባለሀብት ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት ስያደርግ ባለሀብቱ ግን በስፋት በአምራች ኢንዱስትሪው
እየተሰማራ አይደለም፡፡ የዚህ ሁኔታ ዋነኛ ምክንያቶች ምን ሊሆኑ ይችላሉ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 308


______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________
6. ብዙውን ጊዜ ባለሀብቱ በአምራች ኢንዱስትሪ እንዳይሰማራ በርከት ያሉ መነቆዎች ይጠቀሳሉ፡፡ ነገር ግን የውጭ በለህብቶች በሀገራችን
በተመሳሳይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ተሰማርተው ዉጤታማ ሲሆኑና በሀገራችን ያለውን የገበያ ዕድልም አሟጠው ሲጠቀሙበት
ይታያል፡፡ በሀገር ውስጥ ባለሀብት እና በውጭ ሀገር ባለሀብት የሀገር ውስጥ ባለብት የሚያቅባቸው ምክንያቶች ምን ያህል አሳማኝ
ናቸው?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
__________________________________________________________________________________________________________________________

7. የአምራች ኢንዱስተሪ እና የንግድ ስራ በትርፋመነት የቱ የተሻለ ነው ይላሉ? ምክንያቱስ?


_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________
8. የሀገራችን ባለሀብት በአምራች ኢንዱስትሪው እንዲሰማራ እና ውጤታማ እንዲሆን ከመንግስት ምን ተጨማሪ እርምጃዎች ያስፈልጋሉ
ብለው ያምናሉ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________________________

9. በንግድ የተሰማራው ባለሀብት በአምራች ኢንዱስተሪ እንዲሰማራ ከተፈለገ ከንግድ ማሕበረሰብ ከራሱ ሊደረጉ የሚገባቸው
ጉዳዮች ምን ናቸው ተብለው ይታሰባሉ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 309


አባሪ 11፡ ከክልል ኢንቨስትመንት የስራ ሂደት መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ቃለመጠይቅ

መግቢያ፡- ይህ መጠይቅ በሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ምን ያህል ዓቅም እንዳለ እና የሀገር ውስጥ ልማታዊ ባለሀብቱ በዘርፉ
ተሰማርቶ ይበልጥ ተጠቃሚ የሚሆንበት ጥናት ለማካሄድ መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህም ሲባል ከሚመለከታቸው የመንግስት
አስፈጻሚ እና ድጋፍ ሰጪ መስሪቤቶች አስፈላጊውን መረጃ መሰብሰብ አስፈላጊ ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ ጥናት እንዲሳተፉ ዕድሉ ያገኙ
የኢንቨስትመንት የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ትክክለኛ መረጃ በቅንነት በመስጠት ለጥናቱ ውጤታማነት ያልተቆጠበ አስተዋፅኦ
እንድያበረክቱ እና የችግሩ መፍትሔ የሚያፈላለግ አካል እንዲሆኑ ይጠበቃል፡፡ የሚሰጡት መረጃም ሆነ አስተያየት ከዚህ ጥናት ውጭ ለሌላ
ተግባር የማይውል እና ምስጢሩ የተጠበቀ መሆኑ ከወዲሁ እንገልፃለን፡፡

ስለትብብርዎ በቅድሚያ እናመሰግናለን!!


ጥያቄዎች

1) የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ በስፋት ተሰማርተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ከሀገራችን ኢኮኖሚ እና የባለሀብቱ
አጠቃላይ ሁኔታ የተቃኘ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲዎችና ስተራተጂዎች ነድፎ ከመተግበር በተጨማሪ በዘርፉ ኢንቨስትመንት
ለተሰማሩ የማበረታቻ ፓኬጅ ቀርጾ እየተገበረ ሲሆን የግሉን ባለሀብት ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት ስያደርግ ባለሀብቱ ግን በስፋት በአምራች
ኢንዱስትሪው እየተሰማራ አይደለም፡፡ የዚህ ሁኔታ ዋነኛ ምክንያቶች ምን ሊሆኑ ይችላሉ?
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________________________________________________________________________________
2) የመንግስት ሪፖርቶችና በተለያዩ አካላት በተለያዩ ጊዜያት የተካሄዱ ጥናቶች አምራች ኢንዱስትሪያችን በተፈለገው ፍጥነት እንዳላደገ
ያትታሉ፡፡ በዚህ ክልል ለአምራች ኢንዱስትሪው መጎልበት ዋነኛ ማነቆዎች ምንድናቸው ይላሉ? ዋነኛ ተጠያቂውስ ማን ይሆን? እንዴት?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
3) መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪው የፈቀዳቸው ዘርፈ-ብዙ ማበረታቻዎች ተግባራዊ እየሆኑ ነው ይላሉ? የሀገር ውስጥ ባለሀብቱ ወደ
አምራች ኢንዱስትሪው እንዲሰማራ በመንግስት የተሰጠው ማበረታቻ (Financial and non-Financial incentive) በቂ ነውን? ካልሆነ
ተጨማሪ የሚያስፈልጉ ማበረታቻዎችን ይጥቀሱ፡፡
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________
4) የመንግስት ድጋፍ ሰጪ መስሪያቤቶች የሚሰጡት የመንግስት አጋልግሎት ኢንዱስትሪው በተግባር እየደገፉት እንዳልሆነ ይገለጻል
(KOICA, 2013; World Bank, 2014)፤ እዉነታው ልክ ከሆነ ምክንያቱ ምንድን ነው?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
5) በዚህ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስት እንዲያደርግ የሚጠበቅ የትኛው የሕብረተሰብ ክፍል ነው? ምክንያቱስ?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 310


6) የንግዱ ማሕበረሰብ በአምራች ኢንዱስትሪ ልማት እንዲሰማራ የትግራይ ክልል ከተማ ልማት፣ ንግድና ኢንዱስተሪ ቢሮ እና
ወረዳዎች/ከተሞች ያደረጉት ተጨባጭ ስራ ካለ? ከሌለ ምክንያቱ?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
7) ብዙውን ጊዜ በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማራ የሀገር ውስጥ ባለሀብት በተሰማራበት ዘርፍ ዉጤታማ እየሆነ እንዳልሆነ እንዲሁም
የገበያ ችግር እንዳለበት ይነገራል፡፡ ነገር ግን የውጭ በለህብቶች በሀገራችን በተመሳሳይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ተሰማርተው ዉጤታማ
ሲሆኑና በሀገራችን ያለውን የገበያ ዕድልም አሟጠው ሲጠቀሙበት ይታያል፡፡ ስለዚህ በሀገራች ባለሀብት እና በውጭ ባለሀብት ያለው
የስኬት ልዩነት ምንድነው ብለው ያስባሉ ?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
8) በሀገራችን የአምራች ኢንዱስትሪው እንዴት ሊስፋፋና ሊጠናከር ይችላል ብለው ያምናሉ?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
9) ለኢንዱስትሪው የሚያስፈልገው የሰው ኃይል ልማት እየተከተልነው ያለን የትምህርትና የስልጠና ስርዓት (የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ትምህርት ተግባር ተኮር ከመሆነና ካለመሆን፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ውጤታማነት፣ በፋሪካዎች ደረጃ የሚሰጥ ስልጠናዎች ውጤታማነት
ወዘተ) ምን ያህል ውጤታማ ነው ተብሎ ይታመናል? (በተለይ የተካሄደ ጥናት ካለ መሰረት ተደርጎ ቢታይ)
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
የግብርና ምርቶች ዉጤት በግብኣትነት የሚጠቀሙት ኢንዱስትሪዎች ከሌሎች ኢንዱስትሪዎች በማነጻጻር ሲታይ ዕድገታቸው አመርቂ
እንዳልሆነ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በሁለተኛ የድገትና ሽግግር ዕቅዱ አመላክቷል፤ የገንዘብና የፋይናንስ ሚኒስቴር በ2011 ባካሄደው ጥናት
እንዲሁም ኮይካ በ2013 ጥናተ አመላክቷል፡፡ የዚህ መዋቅራዊ ችግር ምንድነው? ሴክተሩ መንግስት ቅድምያ ትኩረት የሰጠው ከመሆኑ
ጋር ተያይዞ ያለው እንደምታ ምንድ ነው?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
10) የግብአት ችግር የሌለባቸው ኢንዱስትሪዎች ጨምሮ ከዓቅም በታች እያመረቱ እንደሚገኙ እ.እ.አ በ2013 (KOICA) የተጠና ጥናት
ያሳያል፡፡ ምክንያታቸው ምንድነው? የኢንዱስትሪዎች የግብኣት ችግር ተጽዕኖውስ ምን ያህል ነው? መፍትሔውስ ከመንግስት በላይ
ነውን? እንዴት? የግብአት ችግር የሚያጋጥማቸው እና የማያጋጥማቸው ኢንዱስትሪዎ በየጊዜው እየተለዩ ችግሩ ከመድረሱ በፊት በታቀደ
ሁኔታ መፍትሔ በማስቀመጥ አንዱስትሪው የመምራት ልምዳችንና ክህሎታችን/ዓቅማችን/ ምን ይመስላል?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 311


11) ግብርና መር የኢንዱስትሪ ልማት ስትራተጂያችን በተግባር ለመተርጎም የኢንዱስትሪ ልማት ስትራተጂ ከጸደቀ ወዲህ በአምራች
ኢንዱስትሪው ላይ ምን ፕሮግራሞች እና ፕሮጀክቶች ተሰርተው ተተግብረዋል?
 በየዓመቱ/በተወሰነ ጊዜ/ የሀገር ውስጥ የግል ኢንቨስትመንት ድርሻ በመለየት ከመስራት አኳያ
 በየዓመቱ/በተወሰነ ጊዜ/ በየሴክተሩ የሚውል የኢንቨስትመንት መጠን እየወሰኑ በመስራት ረገድ
 በየዓመቱ/በተወሰነ ጊዜ/ የሚታዩ ክፍተቶች በማስተካከል የኢንዱስትሪው የልማት ፍጥነት በማረጋገጥ ረገድ
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
12) በሁለተኛው የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ የግብርናው ሴክተር አሁን ከሚገኝበት የ(PrimaryProduction) ወደ ኘሮሰሲንግና
ግብይት (Marketing) እንደሚሸጋገር ግብ ተነድፏል ከዚህ አኳያ ግብርና የሚፈጥረውን ተረፈ ካፒታል፣ ጉልበት፣ የውጭ ምንዛሬ፣ ወዘተ
በሚገባ ለመጠቀም የኢንቨስትመንት ሴክተሩ ምን ያህል ተዘጋጅቷል? የዝግጅቱ ምዕራፍስ በምን ይገለጻል?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
13) ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች በየክልሉ እና በፌደራል ደረጃ በየዓመቱ ሸልመን ዕዉቅና መስጠት ተገቢ እና
ለበለጠ ምርታማነት የሚያነሳሳ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ነገር ግን ወደ ባለሀብትነት እየተሸጋገረ ያለው አርሶ አደርና አርብቶ አደር
ሀብታቸውን በቀጣይነት እሴት በሚጨምር የኢንቨስትመንት መስክ እንድያሰማሩ ከማድረግ አኳያ የክልሉ ግብርና እና ገጠር ልማት ቢሮ
ምን ዓይነት ተጨባጭ ሚና እየተጫወተ ነው? ጥረቱ ካለ ትርፍ አምራች አርሶ አደርና አርብቶ አደር በምን ዓይነት የኢንቨስትመንት መስክ
እንድያሰማሩ ይፈለጋል?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
14) የኢንቨስትመንት የስራ ሂደት ተልዕኮ ምንድነው? በዚህ ተልዕኮ እና ስልጣንና ተግባር ኢንቨስትመንት በትግራይ ክልል በከፍተኛ ደረጃ
እንዲስፋፋ ለማድረግ የሚያስችል ዓቅም ይኖረዋል ተብሎ ይታሰባል? እንዴት?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
15) ዜጎች የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲጠቀሙ ወይም እንዳይጠቀሙ ምርቱ በዋጋ እና ጥራት ተወዳዳሪ ሁኖ መገኘት፣ የልማታዊ
ብሄርተኝነት አስተሳሰብ ስፋትና ጥልቀት፣ ወዘተ ከሚወስኑዋቸው ነገርች ይጠቀሳሉ፡፡ ከአምራቹ አኳያ ሲታይ ደግሞ አመቺ ፖሊሲዎችና
ስትራተጂዎች መኖሩ በዘርፉ ለተሰማሩ ለሁለም ወሳኝ ከመሆኑም ባሻገር አርአያ የሆኑ ጀግኖች (development patriotism) የመፍጠር
ስራንም ይጠይቃል፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ስልቶች ምን ያህል የተግባር ስራ ይሰራበታል?
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
___________________________________________________________________________________________________________________________________________________
16) ተጨማሪ አስተያየት ካለዎት?
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_____________________________________________________________________________________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________________________________________________________________________________

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 312


አባሪ 12፡ በሀገራችን ከ1985 ዓ.ም እስከ 2006 ዓ.ም የነበረው አጠቃላይ የኢንቨስትመንት ፍሰት
1.1. ዝርዝር መረጃ
የሀገር ውስጥ ባለሀብት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የመንግስት የልማት ድርጅቶች
በጀት ፕሮጀክት ካፒታል አማካይ ፕሮጀክት ካፒታል አማካይ ፕሮጀክት ካፒታል አማካይ
ዓመት ቁጥር (ሚልዮን ብር) ካፒታል ቁጥር (ሚልዮን ብር) ካፒታል ቁጥር (ሚልዮን ብር) ካፒታል

1985 542 3,750 7 3 233 77.67 0 0 0


1986 521 2,926 6 4 438 109.5 1 57 57
1987 684 4,794 7 7 505 72.14 2 39 19.5
1988 897 6,050 7 10 434 43.4 1 6 6
1989 752 4,447 6 42 2,268 54 1 7 7
1990 816 5,819 7 81 4,106 50.69 1 14 14
1991 674 3,765 6 30 1,380 46 9 4915 546.11
1992 561 6,740 12 54 1,627 30.13 9 5760 640
1993 635 5,675.70 9 45 2,923 64.96 7 257 36.71
1994 756 6,117.3 8 35 1,474 42.11 10 1598 159.8
1995 1127 9,362.9 8 84 3,369 40.11 6 706.11 117.69
1996 1862 12,177.7 7 347 7,205 20.76 16 1837.04 114.82
1997 2240 19,571.7 9 622 15,405 24.77 10 1486.48 148.65
1998 5100 41,841.1 8 753 19,980 26.53 6 18215.08 3035.85
1999 5322 46,630.1 9 1150 46,949 40.83 0 0 0
2000 7307 77,868.2 11 1651 92,249 55.8 3 261.56 87.19
2001 7184 83,630.2 12 1613 73,111 45.33 10 82783.52 8278.35
2002 5080 40,852.2 8 1413 55,169 39.04 3 393.89 131.3
2003 5360 42,093 8 952 53,357 56.05 10 154019 15401.9
2004 5042 59288.9 12 604 84,018 139.1 3 2877 959
2005 6,273 34,823 6 722 49,485 68.54 16 27763 1735.19
2006 128 628 5 34 2,500 73.53 0 0 0
Total 58863 424111.1 7 10256 466200 45.46 124 302995.68 2443.51

የመረጃ ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ 2006 ዓ/ም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 313


አባሪ 13፡ አምራች ዘርፍ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች አፈፃፀም 1997 ዓ.ም እስከ 2007 ዓ.ም ግማሽ በጀት ዓመት

የሀገር ውስጥ የውጭ ሀገር ባለሀብቶች የልማት ድርጅቶች ጠቅላላ ድምር


በጀት ጠቅላላ ፈቀድ ወደ ትግበራ የተሸጋገሩ ጠቅላላ ፈቀድ ወደ ትግበራ የተሸጋገሩ ጠቅላላ ፈቀድ ወደ ትግበራ የተሸጋገሩ ጠቅላላ ፈቀድ ወደ ትግበራ የተሸጋገሩ
ዓመት የወሰዱ ፕሮጀክቶች የወሰዱ ፕሮጀክቶች የወሰዱ ፕሮጀክቶች የወሰዱ ፕሮጀክቶች
ፕሮጀክቶች ፕሮጀክቶች ያስመዘገቡት ፕሮጀክቶች ፕሮጀክቶች ያስመዘገቡት ፕሮጀክቶች ፕሮጀክቶች ያስመዘገቡት ፕሮጀክቶች ፕሮጀክቶች ያስመዘገቡት
ቁጥር ቁጥር ካፒታል (በ ቁጥር ቁጥር ካፒታል (በ ቁጥር ቁጥር ካፒታል (በ ቁጥር ቁጥር ካፒታል (በ
000 ብር) 000 ብር) 000 ብር) 000 ብር)
1997 89 29 147,670 0 0 0 0 0 0 89 29 147,670
1998 1,122 82 328,671 91 65 6,514,446 0 0 0 1213 147 6,843,117
1999 891 63 743,654 145 101 2,715,092 0 0 0 1036 164 3,458,746
2000 1,476 55 556,066 154 106 2,351,436 3 1 103,000 1633 162 3,010,502
2001 1,137 35 111,305 155 107 9,433,801 0 0 0 1292 142 9,545,106
2002 886 37 309,805 149 80 3,943,106 4 3 10,526,446 1039 120 14,779,357
2003 993 33 347,085 144 75 9,277,358 2 0 0 1139 108 9,624,443
2004 1,006 14 75,949 198 58 7,403,504 1 0 0 1205 72 7,479,453
2005 759 6 57,767 336 59 21,683,218 1 0 0 1096 65 21,740,985
2006 1,004 24 246,323 310 51 4,852,035 8 0 0 1322 75 5,098,358
2007 625 2 63,000 106 5 22,423 18 0 0 749 7 85,423
ድምር 9,988 380 2,987,294 1,788 707 68,196,418 37 4 10,629,446 11813 1091 81,813,158

የመረጃ ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ የመረጃ ቋት 2007 ዓ.ም

የኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 314


አባሪ 14፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብት አጠቃላይ የኢንቨስትመንት ፍሰት የክልሎች መረጃ (ፕሮጀክት ቁጥርና በካፒታል መጠን)

4.1. ዝርዝር መረጃ በዘርፍ


ክልል መግለጫ 1998 1999 2000 2001 2002 2003 2004 2005 2006 2007 ድምር
ፕሮጀክት ቁጥር 9 19 29 20 34 29 16 10 16 28 210
አገልግሎት

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 29857.2 87980 160901.9 57886.4 316503.1 154473.3 204971.7 101010 29850 449461 1592894.5
ፕሮጀክት ቁጥር 88 130 111 144 116 103 45 59 135 156 1087
ኢንዱስትሪ

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 512983.9 1456792 2975377 669387.9 2602922 1116852 479546.6 1250670 2921257 2706308 16692096.4
ፕሮጀክት ቁጥር 35 143 33 65 199 106 54 73 151 83 942
ትግራይ

የታቀደ ጠ/ካፒታል
ግብርና

(000 ብር) 45180.5 265600.5 124341.8 334156.3 733971.9 9181436 904954.3 193824.5 569259.5 338990.5 12691715.8
ፕሮጀክት ቁጥር 45 49 42 90 89 248 159 439 270 143 1574
ኮነስትራክሽን

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 134248 139789.4 237572.1 1032963 295973.3 722851.9 619397.4 5086624 1722557 569520.6 10561496.7
ፕሮጀክት ቁጥር - - - - - - - - - - -
ቱሪዝምና

የታቀደ ጠ/ካፒታል
ሆቴል

(000 ብር) - - - - - - - - - - -
ፕሮጀክት ቁጥር 48 51 86 67 57 41 15 35 24 - 424
አገልግሎት

የታቀደ ጠ/ካፒታል
ንግድና

(000 ብር) 69545.1 353339 343047.8 373847.9 401128.6 256572.6 69422.1 415215.4 197516.1 - 2479634.6
አማራ

ፕሮጀክት ቁጥር 48 75 116 78 52 47 49 194 262 - 921


ኢንዱስትሪ

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 390715.3 2206261 962617.6 3412365 2269976 16069376 1567859 3724962 4528632 - 35132763.9

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 315


ፕሮጀክት ቁጥር 78 169 264 406 195 211 168 213 469 - 2173
የታቀደ ጠ/ካፒታል
ግብርና

(000 ብር) 257935.2 422711.8 638017.6 968729.8 431126.7 521433.6 502194.1 643973.2 2110685 - 6496807
ፕሮጀክት ቁጥር 97 125 129 53 100 137 195 446 297 - 1579
ኮነስትራክሽን

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 294920.2 1521705 857087.4 116337.1 2405482 463226.6 9238823 1899641 1183211 - 17980433.3
ቱሪዝምና ሆቴል

ፕሮጀክት ቁጥር 33 58 231 174 121 158 51 85 66 - 977


የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 148813.7 309294 798885 710908.3 999489.9 952032.2 552496.3 1313948 902095.5 - 6687962.9
ፕሮጀክት ቁጥር 271 379 616 431 335 113 106 110 55 - 2416
አገልግሎት

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 1644959.1 1477590 3465440 1547969 1601350 381972.5 404227.3 1869074 516966.5 - 12909548.4
ፕሮጀክት ቁጥር 89 139 346 123 101 36 62 59 26 - 981
ኢንዱስትሪ

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 866465.5 1502574 5189598 1422488 1062356 3729493 1194605 1499782 1327756 - 17795117.5
ፕሮጀክት ቁጥር 12 13 36 35 14 13 32 35 20 - 210
ኦሮሚያ

የታቀደ ጠ/ካፒታል
ግብርና

(000 ብር) 6801.4 20074.6 118484.9 170649 287220.8 52856 200382 607333.3 388182.3 - 1851984.33
ፕሮጀክት ቁጥር - - - - - - - - - - -
ኮንስትራክሽን

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) - - - - - - - - - - -
ፕሮጀክት ቁጥር - - - - - - - - - - -
ቱሪዝምና

የታቀደ ጠ/ካፒታል
ሆቴል

(000 ብር) - - - - - - - - - - -

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 316


ፕሮጀክት ቁጥር 4 7 3 9 8 12 10 0 19 - 72
አገልግሎት
የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 2666.6 15843.1 10486 26083.8 12640.3 47766.6 30997.8 0 95937.8 - 242422.07
ፕሮጀክት ቁጥር - - - - - - - - - - -
ኢንዱስትሪ

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) - - - - - - - - - - -
ፕሮጀክት ቁጥር 13 8 21 23 12 27 15 16 17 - 152
ድሬ ዳዋ

የታቀደ ጠ/ካፒታል
ግብርና

(000 ብር) 10748.6 8955.6 35040.2 32902.3 23032.1 103774.6 24544.2 52523.47 77226.1 - 368747.16
ፕሮጀክት ቁጥር 11 61 100 84 84 145 58 116 68 - 727
ኮነስትራክሽን

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 45305.7 603142.3 383032.8 219800.7 302101.3 487872.8 219850.3 668327.2 420890.1 - 3350323.2
ቱሪዝምና ሆቴል

ፕሮጀክት ቁጥር 7 4 21 12 18 4 6 5 3 - 80
የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 18142.2 48930 140628.9 29437.7 67977.4 26052.4 44559.5 110800 19725.9 - 506254.01
ፕሮጀክት ቁጥር 209 332 369 179 65 36 20 14 17 - 1241
አገልግሎት

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 500492.83 1263323.7 1231618.7 893833.7 349493.4 137481.2 82576.9 59094.7 195086.9 - 4713002
ደ/ብ/ብ/ሕዝቦች

ፕሮጀክት ቁጥር 225 75 145 128 66 50 71 25 26 - 811


ኢንዱስትሪ

የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 693380.25 325715.7 722031.9 348525.3 273126.5 981734.5 381655.4 1244514 351852 - 5322535.6
ፕሮጀክት ቁጥር 166 244 440 255 63 70 57 49 70 1414
የታቀደ ጠ/ካፒታል
ግብርና

(000 ብር) 1045383.5 1237401.1 3294299.1 1993800 518227.9 773373.3 1254189 1252803 531873.7 11901350.63

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 317


ፕሮጀክት ቁጥር 172 37 56 37 30 28 40 50 21 471
ኮነስትራክሽን
የታቀደ ጠ/ካፒታል
(000 ብር) 354716.2 179095.3 344315.991 112491.1 88942.5 222075.6 166970.9 216302.7 95001.2 1779911.438
ፕሮጀክት ቁጥር 224 179 246 127 43 28 19 16 15 897
ቱሪዝምና

የታቀደ ጠ/ካፒታል
ሆቴል

(000 ብር) 830604.94 640118.5 1651771.7 653675.8 462642.9 444563.2 238802.7 165618.4 520043.7 5607841.897

የመረጃ ምንጭ፡ ከትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደ/ብ/ብ/ሕዝቦች ክልሎና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት የስራ ሂደቶች

4.2. የሀገር ውስጥ ባለሀብት የኢንቨስትመንት ፍሰት (በክልል ደረጃ ተጠቃሎ የቀረበ)
2007
ክልል መግለጫ 1998 1999 2000 2001 2002 2003 2004 2005 2006 ታ ሕ ስ 30 ድ ምር
ፕሮጀክት ቁጥር 177 341 215 319 438 486 274 581 572 410 3813
ትግራይ ካፒታል (000,000 ብር) 722.27 1950.16 3498.19 2094.39 3949.37 11175.61 2208.87 6632.13 5242.92 4064.23 41538.142
ፕሮጀክት ቁጥር 304 477 826 778 526 594 478 971 1118 6072
አማራ ካፒታል (000,000 ብር) 1161.93 4813.31 3599.66 5582.19 6507.2 18262.64 11930.8 7997.74 8922.14 68777.61
ፕሮጀክት ቁጥር 83 114 207 178 166 211 125 161 146 56 1447
ድሬዳዋ ካፒታል (000,000 ብር) 186 768 717 1,265 623 739 585 1,070 1,211 628 7791.95
ፕሮጀክት ቁጥር 866 867 1256 650 267 212 207 154 149 4628
ደ/ብ/ብ/ሕ ካፒታል (000,000 ብር) 3424.58 3645.65 7244.04 4002.33 1692.43 2559.23 2124.2 2938.33 1693.9 0 29324.69
ፕሮጀክት ቁጥር 1430 1799 2504 1925 1397 1503 1084 1867 1985 466 15960
ድምር ካፒታል (000,000 ብር) 5,495 11,178 15,059 12,944 12,772 32,737 16,848 18,638 17,070 4,693 147,432
የመረጃ ምንጭ፡ ከትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደ/ብ/ብ/ሕዝቦች ክልሎና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት የስራ ሂደቶች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 318


አባሪ 15፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብት የአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ፍሰት የክልሎች መረጃ (የፕሮጀክት ቁጥርና የካፒታል መጠን)
2007
ክልል መግለጫ 1998 1999 2000 2001 2002 2003 2004 2005 2006 ታሕሳስ 30 ድምር

ፕሮጀክት ቁጥር 88 130 111 144 116 103 45 59 135 156 1087
ትግራይ

ካፒታል(ሚ. ብር) 512.98 1456.79 2975.38 669.39 2602.92 1116.85 479.55 1250.67 2921.26 2706.308 16692.1
አማራ ፕሮጀክት ቁጥር 48 75 116 78 52 47 49 194 262 921 1842
ካፒታል(ሚ. ብር) 390.72 2206.26 962.62 3412.37 2269.98 16069.38 1567.86 3724.96 4528.63 35132.76 70265.53
ፕሮጀክት ቁጥር 89 139 346 123 101 36 62 59 26 26 1007
ኦሮሚያ ካፒታል(ሚ. ብር) 866.47 1502.57 5189.6 1422.5 1062.36 3729.5 1194.6 1499.78 1327.76 1567.42 19362.54
ፕሮጀክት ቁጥር 48 34 62 50 44 23 36 24 39 12 372

ድሬዳዋ ካፒታል(ሚ. ብር) 109.4 91.61 147.8 956.63 217.24 73.63 264.55 237.91 597.13 371.67 3067.55
ፕሮጀክት ቁጥር 94 75 144 51 66 50 71 25 25 20 621
ደ/ብ/
ብ/ሕ ካፒታል(ሚ. ብር) 688.38 325.72 719.33 347.42 273.13 981.75 381.68 1244.51 346.85 96.13 5404.87
ፕሮጀክት ቁጥር 367 453 779 446 379 259 263 361 487 1135 4929
ድምር
ካፒታል(ሚ. ብር) 2567.94 5582.95 9994.72 6808.3 6425.62 21971.1 3888.21 7957.84 9721.63 39874.29 114792.6

የመረጃ ምንጭ፡ ከትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደ/ብ/ብ/ሕዝቦች ክልሎና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት የስራ ሂደቶች

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 319


አባሪ 16፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ስርጭት

የመረጃ ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ 2007 ዓ.ም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 320


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ስርጭት በመቶኛ በደንበኞች ዓይነት 1998-2007 በጀት ዓመታት

የመረጃ ምንጭ፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ 2007 ዓ/ም

የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ Page 321

You might also like