Professional Documents
Culture Documents
(የመጀመሪያ ረቂቅ)
መግቢያ
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌ
አንቀጽ 1፡ አጭር ርዕስ
ይህ አዋጅ ”የኮንስትራክሽን ኢንዱሰትሪ ልማት አዋጅ ቁጥር……/2014” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
አንቀፅ 2. ትርጓሜ
በዚህ አዋጅ ውስጥ፡-
1) “ሚኒስቴር” ወይም “ሚኒስትር” ማለት እንደቅደም ተከተሉ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ወይም
ሚኒስትር ነው፡
2) “ኮንስትራክሽን” ማለት ከመሬት በታች እና በላይ የሚከናወኑ የህንጻን እና ሌሎች የምህንድስና የመሰረተ
ልማት ሥራዎችን ጨምሮ በቋሚ ንብረቶች ላይ የዕቃዎች እና አገልግሎቶች ጥምር የሆነ የልማት፣
የማስፋፈት፣ የመገጣጠም፣ የጥገና፣ የዕድሳት፣ የማሻሻል፣ የቁፋሮ፣ የማወላለቅ እና የማፍረስ ተግባር
ነው፡፡
3) ”የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ" ማለት የተለያዩ ተፈጥሯዊና የተመረቱ ግብዓትንና ሀብቶችን ለማህበራዊ
እና ኢኮኖሚያዊ ልማት አስፈላጊ ወደ ሆኑ የግንባታ ውጤቶች የሚለውጥ፣ ቋሚ ንብረቶችን በመፍጠር
እና በመንከባከብ ላይ እሴት የሚጨምሩ ኢንዱስትሪዎች እና ዘርፎች ሰፊ ስብስብ ነው፣
4) "ኢንዱስትሪ" ማለት የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ነው፣
5) “ተዛማጅ የኮንስትራክሽን ሥራ” ማለት ለኮንስትራክሽን ሥራ ተዛማጅ የሆኑ የአገልግሎት ወይም
የአቅረቦት ሥራዎች ላይ በተሰማሩ ሰዎች፣ የኮንስትራክሽን ግብአቶች፣ መሳሪያዎችና መገልገያዎች
አቅራቢ፣ አስመጪ፣ ላኪ፣ አከራይ በመሳሰሉት ሰዎችና ድርጅቶች የሚከናወን ተግባር ነው፡፡
6) "አሠሪ" ማለት የኮንስትራክሽን ወይም የምክር አገልግሎት ወይም የአቅርቦት ሥራ እንዲሰራለት
የሚፈልግ ሰው ወይም ድርጅት ነው፣
7) "ሥራ ተቋራጭ" ማለት ሕጋዊ ሥልጣን በተሰጠው አካል ተመዝግቦ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሥራ
ተቋራጭነት የምዝገባ ምስክር ወረቀት የተሰጠው እና በንግድ ሥራ ሂደት ወይም እድገት ውስጥ
የኮንስትራክሽን ሥራዎችን የሚያከናውን፣ የሚመራ ወይም የሚቆጣጠር ነው፣
8) “ ንኡስ ተቋራጭ” ማለት በግንባታ ውል ውስጥ የሚሠራው ሥራ በኮንትራክተሩ ወይም በሌላ ንዑስ
31) “የቅድመ-ግንባታ ደረጃ” ማለት ለአንድ ፕሮጀክት የሚከናወን ፣ በግንባታው ደረጃ ሊቀጥል የሚችል የንድፍ ወይም
የፕሮጀክቱ እቅድ እና ስፔስፊኬሽን specifications የተሟላ መሆኑን የሚረጋገጥበት የንድፍ ወይም የዝግጅት
ስራ የሚከናወንበት ጊዜ ነው።፡
32) "የግንባታ ቦታ"ማለት የግንባታ ሥራ በሚካሄድበት ወይም ሠራተኞቹ የሚደርሱበት ቦታን ያጠቃልላል, ነገር ግን
33) “የግንባታ ምዕራፍ” ማለት በማንኛውም ፕሮጀክት ግንባታ የሚጀመርበትና የዚያ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ
37) “ዋና ሥራ ተቋራጭ” ማለት በአንቀፅ 5(1)(ለ) ከአንቀፅ 12 እስከ 14 የተዘረዘሩትን ተግባራት እንዲያከናውን
38)“የሥራ ቦታ” ማለት ለግንባታ ሥራ ዓላማ ወይም ከግንባታ ሥራ ጋር በተሚገናኘ ለሚነሱ የማናቸውም አይነት
39) "ዋና ዲዛይነር" ማለት በአዋጁ አንቀፅ 5(1)(ሀ) መሰረት በአንቀፅ 11 እና 12 የተመለከተውን ተግባር እንዲፈጽም
40) “ፕሮጀክት” ማለት የኮንስትራክሽን ሥራን የሚያካትት ወይም ለማካተት የታሰበ እና ሁሉንም የዕቅድ፣ የንድፍ፣
እስከ የኮንስትራክሽን መጨረሻ ምዕራፍ የአስተዳደር ወይም ሌሎች ሥራዎችን ድረስ የሚያካትት የፕሮጀክት
አንቀጽ 3፡ ዓላማ
ይህ ዓዋጅ የሚከተሉት ዓላማዎች ይኖሩታል፡-
1) ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነት ያለው ሀገር በቀል የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ እንዲፈጠር በማድረግ
ፍትሃዊነት፣ ተጠያቂነት እና ግልፀኝነት የሰፈነበት እንዲሁም የኢንዱስትሪውን ጤናማ እድገቶች
የሚጎዱ መልካም ያልሆኑ ገፅታዎችን እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል እና ሙያዊ ሥነ ምግባር እንዲከበር
ማድረግ፣
2) ፍታሀዊነት የሰፈነበት በውድድር በሚመራ ገበያ ውስጥ ኢንዱስትሪው ለሚከፈለው ዋጋ ተመጣጣኝ
እሴት ማቅረቡን ማረጋገጥ፣
3) የባለድርሻ አካላት ሚናና ተሳትፎ እና የሰው ሃይል ልማትን ያማከለ የኢንዱስትሪው አቅም በተደማሪነት
እና በዘላቂነት መገንባቱን ማረጋገጥ፣
4) የኮንስትራክሽን ስራ ብቃታቸው በተመዘነ እና በተረጋገጠ ሙያተኞች፣ ባለሙያዎች እና ድርጅቶች ብቻ
እንዲፈፀም የሚያስችል አገር አቀፍ የተሳለጠ የሙያተኛ፣ የባለሙያ፣ የድርጅትና የፕሮጀክት የምዝገባ
እና የፈቃድ አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋት፣
5) ኢንዱስትሪው የማህበረሰቡን ጤንነትና ደህንነት ባስጠበቀና ፣ በጊዜ፣ በጥራት እንዲሁም ወጪ ቆጣቢ
ሆኖ እንዲከናወን እና በውድድር በሚመራ ገበያ ውስጥ ኢንዱስትሪው ለሚከፈለው ዋጋ ተመጣጣኝ
እሴት ማቅረቡን ማረጋገጥ፣
6) የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ግዥና የውል አስተዳደር ውጤታማነት ማሳደግ፣
አንቀጽ 4፡ የተፈፃሚነት ወሰን
ይህ አዋጅ፡-
1) በኮንስትራክሽን እና ተዛማጅ የኮንስትራክሽን ሥራ ዘርፍ ላይ በተሰማሩ ሙያተኞች፣ ባለሙያዎች,
ድርጅቶች እና ፕሮጀክቶች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
2) በሁሉም ክልሎች በማንኛውም የኮንስትራክሽን ሥራ ላይ በተሰማራ ሰው ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
ክፍል ሁለት
1) በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ልማታዊ አቅም እንዲፈጥር በማድረግ ሌብነትና ብልሹ አሠራር የሚጸየፍና
የሚከላከል ኃይል መፍጠር፤
2) ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የሚሆን ፕሮፌሽናል ባለሙያ ማብቃበት
3) በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ ቅልጥፍና እና ወጤታማነትን የሚያረጋግጥ እና ጠንካራ
የገበያ ውድድር የሚያሰፍን አሠራር መዘርጋት፣
4) የፕሮጀክቶች ሥራ አመራር እና የቴክኖሎጂ ዕድገት ሽግግሩን በማቀላጠፍ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን
ማዘመን፤
5) አስተማማኝ የኮንስትራክሽን ግብዓት አቅርቦት ሠንሠለት እንዲዘረጋና ሥርዓትም እንዲገነባለት ማድረግ
6) ዘመናዊና ለኮንስትራክሽን ልማት የተመቻቸ የፋይናንስና የመሣሪያዎች አቅርቦት ድጋፍ የሚሰጥበት ሥርዓት
መፍጠር
7) የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ዋና ዋና ባለሚናዎች ለዘርፉ የተፋጠነ ዕድገት በጋራ የሚሰሩበትን አቅጣጫ መከተል
8) የኮንስትራክሽነ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥርና መጠቀሚያ ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ማጠናከር
9) በሃገራችን ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የሰራተኛውን ጤንነትና ደህንነት የሚጠብቁ ዘላቂ የኮንስትራክሽን ልምዶች
እንዲስፋፉ በኮንስትራክሽን ሥራ ላይ በህይወት እና በንብረት ላይ ጉዳት ሊያስከትሉ ከሚችሉ ሁኔታዎች አስቀድሞ
መከላከል፣
10) የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የልማት አቅጣጫ ለአካባቢ ጥበቃ ሚዛናዊ ትኩረት የሰጠ እንዲሆን ማድረግ
11) የስራ ዕድል ፈጠራን በማሳደግ ድህነትን መዋጋት
12) የኮንስትራክሽን ሕግጋት፣ ኮዶችና ስታንዳርዶች አክብሮ በመስራት የተጠናቀቀው ፐረሮጅክት የመጨረሻ
(ተተቃሚውን)ተገልጋዩን ፍላጎት ያሟላ መሆኑን ማረጋገጥ
13) የህንፃና መሰረተ ልማት ግንባታ ሂደትና ዲዛይን ለአካል ጉዳተኞች ተደራሽ እንዲሆኑ ማድረግ፣
14) የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በሥርዓት እንዲመራ፣ ሥርዓቶችን በአግባቡ መተግበር እንዲበቃ በማድረግ ላይ
የተመሠረተና ኢንዱስትሪው ፈጣን ዕድገት ለማምጣት የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት መፍጠር ነው፡፡
15) በማንኛውም የኮንስትራክሽን ሥራ የሚሳተፍ ድርጅትም ሆነ ባለሙያ የሚጠበቅበትን ሙያዊ ስነ-ምግባር አክብሮ
መስራቱን ማረጋገጥ፤
16) የሚፈለገው የስነ-ምግባር ደረጃ የህይወትና የንብረት ደህንነትን፣ ኢኮኖሚያዊ ስልጠትን፣ ብሄራዊ ደህንነትን፣
ህጋዊና ባህላዊ ተገቢነትን ማገናዘብ፡፡
ይሆናል፤
2) በዚህ አዋጅ የግንባታ ውልን የሚመለከቱት ከግንባታ ሥራዎች ጋር በተገናኘ ሥራ ለመሥራት ወይም
(ሐ) በግንባታ፣ በምህንድስና፣ በውስጥ ወይም በውጪ ማስጌጥ ወይም በመልክዓ ምድር አቀማመጥ ላይ ማማከር
ሥራ፤
አይጨምርም፤
(ሀ) የግንባታ ወይም የምህንድስና አካላት ወይም መሳሪያዎች የማምረት ወይም ወደ ግንባታ አካባቢ የማድረስ፤
(ለ) ለኮንስትራክሽን ስራውን ለማሳለጥ የሚያስፈልጉ የመስሪያ መሳሪያ፣ ተክል ወይም ማሽነሪ፣ ወይም ለማሞቂያ ፣
ለመብራት ፣ የአየር ማቀዝቀዣ ፣ የአየር ማናፈሻ ፣ የኃይል አቅርቦት ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ፣ የንፅህና አጠባበቅ ፣
የውሃ አቅርቦት ወይም የእሳት አደጋ መከላከያ ወይም ለደህንነት ወይም የግንኙነት ስርዓቶች መዘርጋት፤
ሐ) የድፍድፍ ነዳጅ፣ የተፈጥሮ ጋዝና ሌሎች የማዕድን ሀብቶችን የማፈላለግ ወይም የማጣራት ስራ በሚካሄድበት
መ) የድፍድፍ ነዳጅ፣ የተፈጥሮ ጋዝና ሌሎች የማዕድን ሀብቶችን ለማውጣትና ለማጣራት ጥቅም ላይ የሚውሉ
5) ለዚህ አዋጅ ዓላማ የኮንስትክሽን ሥራ ጋር የተያያዙ ሙያዊ አገልግሎቶች የሚባሉት የሒሳብ, የገንዘብ, ወይም
የሚከናወኑ የቅየሳ፣ እቅድ ማውጣት፣ የወጪ ጥናት፣ የቤተ-ሙከራ፣ አርክቴክቸር፣ ዲዛይን፣ ንድፍ ስራ፣
6) ለዚህ አዋጅ አተገባበር በሌላ ህግ የተደነገጉ ከኮንስትራክሽን ሥራ ጋር የተያያዙ ሙያዊ አገልግሎቶች የሚሰጡ
መስፈርት አሟልቶ በተመዘገበና የምዝገባ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ባለው የኮንስትራክሽን አማካሪ
ለመቅጠር የሚመርጠው ሰው በዚህ አዋጅ በተደነገገው መሰረት በዲዛይን ዝግጅት ወይም የአማካሪነት
ስራውን በተገቢሁ ሁኔታ ለማከናወን የሚያስችለውን ብቃት ያለው እና በቂ ሀብት የመደበ ወይም በቂ
ሃብት የሚመድብ መሆኑ አሳማኝ በሆነ ዘዴ ማወቁን ካላረጋገጠ በስተቀር በአማካሪነት ወይም በዲዛይን
የሚያስተባብረው የዲዛይን የባለሙያ በሚመለከተው አካል ተመዝግቦ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያለው
ወይም አርክቴክቱ ነው፡፡ ዝርዝሩ ይህን አዋጅ ለማስፈፀም በሚወጣው ደንብ ይወሰናል፡፡
አንቀፅ /1/ ላይ የተጠቀሰው አማካሪ ድርጅት የፈረመበትና መጠናቀቁን የሚያረጋግጥ ምስክር ወረቀት
ሊደርሱ ለሚችሉ ጉዳቶች ዋስትና ማቅረብ አለበት፡፡ ለፕሮጀክቱ የሚያዘው የዋስትና መጠንና አቀራረብ
ሥራ ተቋራጭ፣ የኮንስትራክሽን አማካሪ ወይም ዲዛይነር ማሰራት አለበት፡፡ ዝርዝሩ ይህን አዋጅ
8. የኮንስትራክሽን ስራው እንደሚጀመር እርግጠኛ በሆነበት ሁኔታ አሰሪው አማካሪ መሾም ወይም መቅጠር
አለበት፣
ለማከናወን ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ለማስተዳደር የሚያስችለው ብቃት ያለው፣ በቂ ሀብት የመደበ ወይም
በቂ ሃብት የሚመድብ መሆኑ አሳማኝ በሆነ ምክንያት ካላረጋገጠ በስተቀር ሥራ ተቋራጩ ጋር ስምምነት
ማድረግ የለበትም፤
10. በዚህ አዋጅ የተቀመጠውን ግዴታ መስፈርት እስካሟላ ድረስ የንዑስ አንቀፅ 7 ድንጋጌ አሰሪው አንድን
እስካሟላ ድረስ አሰሪው አማካሪ ወይም ስራ ተቋራጭ ወየይም ሁለቱንም በተመሳሳይ ስራ ላይ በመሾም
ማሰራት አይከለከልም፤
4) ማንኛውም በፌደራል መንግስት በጀት የሚሰሩ ፕሮጀክቶችን አሰሪው አካል በቅድሚያ ከዲዛይን ጀምሮ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ
እየተገመገመና ይሁንታን እያገኘ እንዲያልፍ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
5) ማንኛውም በፌደራል መንግስት በጀት የሚሰሩ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ከዚህ በታች የተገለጹትን አጠቃላይ የአፈጻጸም መረጃዎች
አሰሪው አካል በየስድስት ወሩ ለባለስልጣኑ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡
1. የኮንስትራክሽን ተዋናኞች መረጃ ለዚሁ ተብሎ በሚዘጋጅ ዳታቤዝ መመዝገብና መደራጀት አለበት፤
2. ማንኛውም ፕሮጀክት አስፈፃሚ አካል የሚከታተለውን የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ከፅንሰሀሳብ
/ከቅድመ-ዲዛይን ጀምሮ እስከ ትግበራ ድረስ ያለውን መረጃ በመደበኛነት ደህንነቱ በተረጋገጠ የመረጃ
ቋት የመያዝ ሀላፊነት አለበት፡፡
3. ዋና ዋና የፕሮጀክቶች መረጃዎች ተደራሽ በሆኑ የመገናኛ አግባቦች ድህረ ገጾችን ጨምሮ
ወቅታዊነታቸውን ጠብቀው ለህዝብ ይፋ እንዲሆን ያደርጋል፤
2) ከአቅም በላይ በሆኑ ምክኒያቶች እስካልሆነ በቀር ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ መጠናቀቅ አለበት
1. ማንኛውም የፕሮጀክት ዲዛይን ክለሳ ጥያቄ በሳይት ማናጀሩ ወይም ፕሮጀክት መሃንዲሱ ሊቀርብ
ይችላል፤
2. ማንኛውም የፕሮጀክት ዲዛይን ክለሳ ወደ ትግበራ ሂደት የሚሸጋገር የክለሳ ጥያቄውን በአሰሪው
ሲታመንበትና ተለዋጭ ስራውን አንድ በአንድ በመዘርዘር ፈቃደኛነቱን በፅሁፍ ሲገልጥ ነው
3. የተለዋጭ ሥራ ትዕዛዝ ማረጋገጫ የተደረገበት ፕሮጀክት የእያንዳነንዱን አይተም ማብራሪያና
የሚከለስበትን ማሃንዲሳዊ ምክንያት በመግለፅ አለበት የማይለወጥ አይተም በጉልህ በሚለይ ሁኔታ
በመገለፅ አፅዳቂው አካል ስም፣ ፊርማ እና ማረጋገጫ የተሰጠበት ቀን ይፃፍበታል፤
4. ማብራሪያው ትርጉም ክፍት ያልሆነ፣ ያልተንዛዛ እና ሌላ ማብራሪያ የምይጠይቅና በቀላሉ መረዳት
እንዲቻል ሆኖ መዘጋጀት አለበት፣
5. የተለዋጭ ስራ ጥያቄ ይሁንታና ማረጋገጫ ካላገኘ ጥያቄው እንደገና ተዘጋጅቶ ሊቀርብ ወይም ውድቅ
ሊደረግ ይችላል
6. ውድቅ የተደረገ የተለዋጭ ስራ ጥያቄ ወዲያውኑ ለሚመለከተው የበላይ ተቆጣጣሪ በፅሁፍ ወይም በስልክ
በቃል ጥያቅው ውድቅ መደረጉን ማሳወቅ አለበት
7. በድጋሜ የቀረበ የተለዋጭ ስራ ጥያቄ በድጋሜ የቀረበ መሆኑን በሚገልፅ መልኩ መቅረብ አለበት
1) በአንቀፅ 15 ንዑስ አንቀፅ (2) እና (3) የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድ ፕሮጀክት የፕሮጀክት ኡደቶችን
ሳይጠብቅ ወደ ትግበራ እንዲገባ ሊደረግ ይችላል፤ዝርዝሩ በደንብ ይወሰናል፡፡
2) የዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 1 ድንጋጌ ቢኖርም የአንድ ኮንስትራክሽን ፕሮጀከት የቅድመ አዋጭነት፣
የአዋጭነት ጥናት እና ዲዛይን ተዘጋጅቶ ተገምግሞ ተቀባይነት ካላገኘ ወደ ቀጣይ ሂደት ሊሸጋገር
አይችልም፡፡
3) በተመረጡ ፕሮጀክቶች ላይ የፕሮጀክቶች ድህረ ትግበራ ግምገማ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ስራ ከገቡ
ቢያንስ ከ 2 ዓመት ቢበዛ በ 10 ዓመት በማይበልጥ ጊዜ ውስጥ መከናወን አለበት፡፡
4) ማንኛውም የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት አስፈጻሚ አንድን የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት በተገባለት ውል መሰረት
የታለመለትን አላማና ውጤት በሚያሳካ መንገድ መጠናቀቁን አረጋግጦ መረከብ እንዲሁም ፕሮጀክቱ ወደ
ምርት ወይም አገልግሎት መስጠት እንደሚችል ማረጋገጥ አለበት፤
5) ተግባራዊ የተደረጉ ከፍተኛ እና መካከለኛ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ እንደ አስፈላጊነቱ የድህረ ትግበራ
ግምገማ ያከናውናል፣ በድህረ ትግበራ ግምገማ የተገኙ ግብዓቶችን በቀጣይ ለሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ዝግጅት
ጥቅም ላይ መዋዋላቸውን ያረጋግጣል፤
2) ለግንባታ የሚቀርበው ግብዓት ደረጃ በውል በግልፅ ባልተቀመጠ ጊዜ ስራ ተቋራጩ የኮንስትራክሽን ስራውን
3) ይሁን እንጂ የጥራት ጉደለት ያለበትን የግንባታ ግብዓት እንዲጠቀም በአሰሪው ትዕዛዝ ግዴታ የተደረገበት
4) በተዋዋዮች መካከል ስለ ፕሮጀክቱ ትግበራ ሂደት ስለሚያሰማራው የባለሙያ ስራንዳርድ በውል በግልፅ
ባልተካተተ ጊዜ ሥራ ተቋራጩ ለስራው ተገቢነት ባለው ባለሙያ ማሳተፍ እና ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ
አላማ ተገቢነት ያለው (fit for the purpose) የግንባታ ግብዓት በመጠቀም የመገንባት ግዴታ አለበት፤
6) ሥራ ተቋራጩ ሆነ ንዑስ ስራ ተቋራጩ አሳማኝ ባልሆነ ሙያዊ አሰራር ላከናወነው ስራ ተጠያቂ ነው፡፡
ለማከናወን በሚያደረገው ጥረት ስራውን እንዳያከናውን ከሚያግድ ማንናውም አይነት ድርጊት በመራቅ
የኮንስትራክሽን ግብዓት አቅራቢ መሰየም፣ አስፈላጊ የሆኑ ትዕዛዛትን፣ መረጃዎችን፣ ዕቅዶችን እና የንድፍ
ስራዎችን ማቅረብ
ላይ ጣልቃ በመግባት ወይም ውሉን እንዲያስተዳድር ስልጣን በተሰጠው ነፃ አካል አሰራር ላይ ጣልቃ
መግባት የለበትም፤
5) በንዑስ አንቀፅ 4 መሰረት እንዲሟላ የሚፈለገው መረጃ በዚህ አዋጅ በተደነገገው መሰረት ከአማካሪው
ግዴታ ጋር ተገቢነተት ያላቸው መረጃዎች እና በአሰሪው ይዞታ ወይም በሌላ ሰው ይዞታ ሲሆን አሳማኝ
መሰረት ግዴታውን አክብሮ በመስራት ፕሮጀክቱ የታለመለትን አገልግሎት መስጠት (the completed
works will be fit for their purpose) በሚያስችል ሁኔታ የማከናወን ኃላፊነት አለበት፣
በፕሮጀክት ጥራትና በጥንቃቄ ጉድለት ምክንያት ሊደርስ ለሚችል ጉዳት ማካካስ የሚረዳ ዋስትና
1) በኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ዲዛይን ለማዘጋጀት ፈቃድ ያለው ባለሙያ ወይም ድርጅት ዲዛይን
የሚዘጋጅለት ፕሮጀክት ለታለመለት አላማ ወይም አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል ሁኔታ ተገቢነት
2) በማንኛውም ሁኔታ በኮንስትራክሽን ዲዛይን የጥራት ጉድለት ለሚከሰት የዲዛይን ስህተት ወይም
በዲዛይን የጥራት ጉድለት ምክንያት ለሚደርሰው ጉዳት ዲዛይኑን ያዘጋጀው አርክቴክት ወይም ድርጅት
ተጠያቂ ነው፤ ሆኖም ግን እንደ ፕሮጀክቱ አይነት ዲዛይን የማዘጋጀትና የኮንስትራክሽን ስራው በአንድ
3) በአሰሪው ይሁንታ ካልሆነ በስተቀር ሌላ ንዑስ ንድፍ አውጭ በውክልና በተሳተፈበት የዲዛይን ዝግጅት
ለሚከሰት ማንኛውም የዲዛይን ስህተት ለሚደርስ ጉዳት ዋና አርክቴክቱ ወይም ዋና ንድፍ አውጭው
ሃላፊ ነው፤
4) ዋና ንድፍ አውጭው አርክቴክት አሰሪው ለሚያሰራው ፕሮጀክት ንኡስ ዲዛይነር እንዲቀጠር አስፈላጊ
መሆኑን ባወቀ ጊዜ ተገቢ ጥንቃቄ እና ሙያዊ ክህሎት ተግባራዊ በማድረግ ለአሰሪው ሃሳብ ማቅረብ
አለበት፣ በቸልተኝነት ያቀረበው ንኡስ ዲዛይነር ለአሪው ጉዳት ዋና ንድፍ አውጭው አርክቴክት ተጠያቂ
ይሆናል፤
5) ዲዛነሩ የኮንስትራክሽን ሥራ ግብዓት ዝርዝር ስፔሲፊኬሽን ዝግጅት ተገቢውን ጥንቃቄና ሙያዊ ክህሎት
ተግባራዊ በማድረግ የሚመረጠው ግብዓት ለታለመለት አላማ እንዲውል የሚያስችል መሆኑን በማረጋገጥ
ማዘጋጀት አለበት፣
6) ማንኛውም የኮንስትራክሽን ዲዛይን አግባብነት ያላቸውን ህግጋት መስፈርት ያሟላ መሆን አለበት፣
1) በውሉ ማሻሻል ወይም መለወጥ በሚለው ስር በግልጽ ካልተካተተ በስተቀር ማንኛውም አማካሪ በዋናው
ውል ስምምነት ይዘት የማሻሻል ወይም የመለወጥ፣ አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ስራን የማስተላለፍ
2) በውል የተሰጠውን ስልጣን በመተላለፍ በሶስተኛ ወገን ላይ ጉዳት እንዲከሰት ምክንያት የሆነ አማካሪ
3) አማካሪው ስራውን በሚሰራበት ሁኔታ አሳማኝ ጥንቃቄ እና ክህሎት የአሰሪውን ጥቅም በሚያስከብር
ሁኔታ ምክር መስጠት እንዲሁም ማንኛውንም የትግበራ ሂደት ክትትል በማድረግ ስራውን ማከናወን
አለበት፤
2) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ በየእርከኑ ክትትል ሊደረግባቸው የሚገቡ የኮንስትራክሽን
ስራዎች ሲከናወኑ ክትትልና ቁጥጥር በሚያደርገው አካል ሳይፈቀድ ሥራው ወደፊት መቀጠል አይችልም፡፡
3) በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኝ ማንኛውም ፕሮጀክት ግንባታው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ ለሥራው በሚመደቡ የግንባታ
ተቆጣጣሪዎች ክትትልና ቁጥጥር ይደረግበታል፣
4) በዚህ አዋጅ የተቀመጠው የቁጥጥር ሥርዓት እንደተጠበቀ ሆኖ በሌሎች ዘርፎች ለሚከናወኑ የኮንስትራክሽን ሥራዎች
የቁጥጥር ዓይነትና አሠራር እንዲሁም የተቆጣጣሪዎች ሥልጣንና ሃላፊነት በህግ ይወሰናል፣
5) ምስክር ወረቀት ሰጪው አካል በመመሪያው መሠረት የሰጣቸውን የብቃት ማረጋገጫ ወይም የምዝገባ ምስክር ወረቀት
ባለሙያው፣ ሙያተኛው ወይም ድርጀቱ ስራውን በህጉ መሠረት መስራቱንና ፈቃዱ ይሰራበታል ተብሎ ለታቀደለት አላማ
6) በዚህ መመሪያ መሠረት ምሰክር ወረቅት ያልያዘ የኮንስትራክሽን ባለሙያ፣ ሙያተኛ፣ ስራ ተቋራጭና አማካሪ ድርጅት
ምሰክር ወረቅት በመያዝ በግንባታ ስራ ላይ እንዲሰማራ በቀባለስልጣን መ/ቤቱ ሚ/ር መ/ቤቱ ቁጥጥርና ድጋፍ ያደረጋል፡፡
7) ማንኛውም ስራ ተቋራጭ እና አማካሪ ድርጅት ለመስፈርት ማሟያነት ባቀረባቸው ባለሙያዎችና ሌሎች በመስፈርቱ ላይ
የተገለጹ ሁኔታዎችን አሟልቶ እየሰራ መሆኑን ለማረጋገጥ ቁጥጥር ያካሂዳል፡፡
8) ማንኛውም የኮንስትራክሽን ባለሙያ ወይም ድርጅት በተሰማራበት የሙያ መስክ ምስክር ወረቀት ደረጃ መስፈርት ያልጠበቀ
ሆኖ ከተገኘ ሚ/ር መ/ቤቱ በሚወስነው የጊዜ ገደብ ውስጥ ጉድለቶቹን እንዲያስተካክል የጽሑፍ ትዕዛዝ ይሰጠዋል፡፡
9) በዚህ አንቀጽ መሠረት የሚደረገው ቁጥጥር በቀባለስልጣን መ/ቤቱ ሚ/ር መ/ቤቱ አመቺ ነው ብሎ ባመነበት ጊዜ ሊያካሂድ
ይችላል፡፡
10) በዚህ አንቀጽ መሰረት ሚ/ር መ/ቤቱ የሚመድባቸው ተቆጣጣሪዎች ለሚያቀርቡለት ጥያቄ ድርጅቱ ወይም ባለሙያው
ተገቢውን መረጃ የመስጠት እና የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡
ሚ/ር መ/ቤቱ የሚመድባቸው ተቆጣጣሪዎች የመታወቂያ ወረቀት እና የሚ/ር መ/ቤቱን ደብዳቤ ቁጥጥሩን
ለሚያካሄድበት ድርጅት ባለቤት ወይም ለህጋዊ ወኪሉ ማሳየት አለባቸው።
አንቀፅ 39. የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ሥራ አመራር
በኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጀመንት ስራ ላይ የተሰማራ ማንኛውም ግለሰብም ሆነ ድርጅት እንዲሁም የመንግስት አካል በዘርፉ
(በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጀመንት ኢንስቲቲዩት የተዘጋጁ 18 ማንዋሎችን ስራ ላይ አውሎ መስራት የሚችል ሲሆን
የሚመለከተው አካል የተዘጋጁ ማንዋሎችን ለማስፈጸም አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ተደራሽ የማድረግ ግዴታ አለበት፣
1) ሌላ የውል ቃል ከሌለ በስተቀር አሰሪው ወይም የፕሮጀክቱ ባለቤት ውሉ ከተፈረመበት ቀን ጀምሮ በሁለት
ወራት ውስጥ ለስራ ተቋራጩ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት የሚከናወንበትን ቦታ ርክክብ ማከናወን አለበት
3) እንዳለ ሆኖ ስራ ተቋራጩ ርክክቡ እንዳይፈጻም የተከለከለው ከአሰሪው አቅም በላይ በሆነ ከሆነ በሶስተኛ
ወገን ጣልቃ ገብነት ወይም ሌላ ህገወጥ ድርጊት ከሆነ አሰሪው ዋስትና እንዲሰጥ አይገደድም ሃላፊም
አይሆንም፤
4) ለሥራው ቅልጥፍኛ ሲባል ማንኛውም የሥራ ተቋራጭ የተለመደና ተገቢ ትጋት በማድረግ የፕሮጀክቱ
6) እንዳለ ሆኖ በግልጽ ሚታይ ጉድለት እስካልሆነ ድረስ የተተወ ስራ ወይም ጥቃቅን መናኛ ጉድለት ቢኖርም
1) በተዋዋይ ወገኖች መካከል የተደረሰው የውሉ ስምምነት እንደተጠበቀ ሆኖ ውሉን የሚቆጣጠረው አካል
ያስከትላል
የተደረገበት ፕሮጀክት ጉድለት የነበረው መሆኑ ዘግይቶ የታወቀ ቢሆንም እንኳን ስራ ተቋራጩ
3) ከተለመደው የተለየ የአየር ንብረት መለዋጥ ሁኔታ ሲያጋጥም እና ክስተቱ ለትግበራው መዘግየት ጉልህ
4) ሰደድ እሳት፣ መብረቅ፣ ፍንዳታ፣ ሞገድ፣ ጎርፍ፣ ገደብ ያለፈ የውሃ ታንከር፣ፍሰት ወዘተ ምክንያት
2) በዚህ ሁኔታ የልዩነቱ/ለውጥ ስፋትና መጠን እና አሰሪው ለሥራ ተቋራጩ የሚከፍለው መጠን ወይም
በሙሉ ግዴታውን አከናውኖ ባያጠናቅቅም ግዴታውን በፈጻመበት መጠን ምክንያታዊ ክፍያ ይከፈለዋል፣
2. በስራው መጠን መጨመር እየታየ የሚከናወን ክፍያን በተመለከተ በአሰሪው ያልተከፈለ ውዝፍ ክፍያን
3. የሥራ ተቋራጩ የሂደት ክፍያ ጥያቄ ተቋራጩ ማንኛውንም ግዴታውን ከፈጸመ በኋላ በማንኛውም ጊዜ
ሊደረግ ይችላል፣
4. የሥራ ተቋራጩ የሂደት ክፍያ ጥያቄ መጠየቅ ሥራ ተቋራጩ በዚህ ውል መሠረት ወይም ከዚህ ጋር
1. ሥራ ተቋራጩ በውል ውስጥ ያሉትን ግዴታዎች አፈጻጸምን በሚመለከት መጠን ገንዘብ እንዲፈለው
2. አሰሪው በውል ውስጥ ያሉትን ግዴታዎች በመፈፀም ወይም አለመፈጸምን በሚመለከት ከስራ ተቋራጩ
1. የክፍያ ጥያቄ የተቀበለው ተዋዋይ ወገን ጥያቄው ውድቅ መደረግ አለበት ብሎ የሚያምን ከሆነ
ጥያቄው በውል መሠረት ስላልቀረበ፤ ወይም የይገባኛል ጥያቄውን በሙሉ ወይም በከፊል
የሚያከራክር ልዩነት ያለበት ሲሆን ጥያቄው የቀረበለት ወገን የይገባኛል ጥያቄውን ከተቀበለ በኋላ በ
2. የክርክር ማስታወቂያ፤
(መ) የማስታወቂያውን ቀን እና
(ረ) የይገባኛል ጥያቄው በንኡስ አንቀጽ (1) (ሀ) ውድቅ ከተደረገ - በውሉ መሠረት የክፍያ ጥያቄው
(ሰ) የይገባኛል ጥያቄው በንኡስ አንቀጽ (1) (ለ) መሠረት አከራከሪ ከሆነ - እያንዳንዱን የይገባኛል
ወይም ሙሉ በሙሉ በንኡስ አንቀጽ (1) መሠረት ካልተከራከረ በስተቀር ፓርቲው ከሚከተሉት
4. (በዚህ ውል መሠረት አሰሪው ለሥራ ተቋራጩ የሚከፍለውን ማንኛውንም የገንዘብ መጠን ከፊሉን
(ለ) አሰሪው በመብቱ ውስጥ የያዘውን ማንኛውንም ገንዘብ ለኮንትራክተሩ በጽሑፍ (በክርክር
1. በውል መሠረት በተወሰነው ቀን ወይም ከዚያ በፊት ለሌላ ተዋዋይ ወገን ተከፋይ መደረግ የተበረበት
ነገር ግን ከዚያ ቀን በኋላ ላልተከፈለ ገንዘብ መጠን ወለድ ታስቦበት ተከፋይ መሆን አለበት፣
3. በማንኛውም ጊዜ የሚከፈለው የወለድ መጠን በብሔራዊ ባንክ የወለድ ልውውጥ መሠረት ለዚያ ጊዜ
ከሚወሰነው ልክ ነው።
የጥንቃቄ መስፈርቶችን ሚና ለመወጣት የሚያስችለውን ክህሎቶች, ዕውቀት እና ልምድ ያለው መሆን አለበት፤
2) በኮንስትራክሽን በፕሮጀክት ላይ የሚሰማራ ማንኛውም አርክቴክት ወይም ሥራ ተቋራጭ በንዑስ አንቀጽ (1)
3) የግንባታ ስራ ለማሰራት የሚፈልግ ማንኛውም አሰሪ ወይም ባለቤት ለስራዉ የሚቀጥራቸው አርክቴክት ወይም
ሥራ ተቋራጭ በንዑስ አንቀጽ (1) ውስጥ ያሉ ሁኔታዎች ያሟላ ባለሙያ ወይም ድርጅት መሆናቸው ማረጋገጥ
ይኖርበታል፤
4) በዚህ አዋጅ መሰረት ግዴታ ያለበት ማንኛውም ሰው ከፕሮጀክት ጋር በተያያዘ ግዴታ ወይም ተግባር ያለበትን ሰው
ደኅንነት ወይም ሌሎችን አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል መረጃ ካወቀ የሚያውቀውን መረጃ ለሚቆጣጠረው ሰው
ማሳወቅ አለበት፤
6) በዚህ አዋጅ መሰረት መረጃ የመስጠት ወይም ሪፖርት የማድረግ ሀላፊነት ያለበት ማንኛውም ሰው በስራ ሂደት
የተያያዙ ጉዳዮችን ማስተባበር፣ በተቻለ መጠን ፕሮጀክቱ በጤና እና ደህንነት ላይ አደጋ ሳያስከትል
2) ንድፍ አውጪው በአንቀጽ (1) ላይ ያለውን ግዴታ በመወጣት ላይ እና በተለይም ደግሞ በአንድ ጊዜ ወይም
በቅደም ተከተል የሚከናወኑትን የንድፍ ስራ፣ ቴክኒካዊ እና ድርጅታዊ ገጽታዎች፣ ሥራውን ወይም የሥራ
የሁሉንም የግንባታ ደረጃዎች እቅድ ይዘት እና ማንኛውም የጤና እና የደህንነት መረጃዎችን ከግምት ውስጥ
አንቀፅ 52. በግንባታ ደረጃ ላይ ከጤና እና ከደህንነት ጋር በተገናኘ የዋና ተቋራጭ ተግባራት
1) ዋናው ሥራ ተቋራጩ የኮንስትራክሽን ምዕራፍ ማቀድ፣ ማስተዳደርና መከታተል እና በግንባታው ምዕራፍ
ውስጥ ከጤናና ከደህንነት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በማስተባበር ለጤናና ለደህንነት አደጋ ሳይጋለጥ የግንባታ
2) ሥራ ተቋራጩ በአንቀጽ (1) ላይ ያለውን ግዴታ በመወጣት ላይ እና በተለይም ደግሞ በአንድ ጊዜ ወይም
በቅደም ተከተል የሚከናወኑትን ቴክኒካዊ እና ድርጅታዊ ገጽታዎች፣ ሥራውን ወይም የሥራ ደረጃዎች
የግንባታ ደረጃዎች እቅድ ይዘት እና ማንኛውም የጤና እና የደህንነት መረጃዎችን ከግምት ውስጥ ባስገባ
4) ዋናው ሥራ ተቋራጭ ለኮንስትራክሽን ስራው ተስማሚ ጣቢያ መዘጋጀቱን፣ የልተፈቀዱ ሰዎች ወደ ግንባታው
2) በግንባታ ንብረት ላይ ያለውን ሀላፊነት የጤና እና የደህንነት ማህደር ሙሉ በሙሉ ያስተላለፈ አሰሪ
ምዕራፍ እቅድ ያወጣል ወይም የኮንስትራክሽን ምዕራፍ ዕቅድ ለማዘጋጀት የሚያስችል ዝግጅት ያደርጋል።
2) የኮንስትራክሽን ምዕራፍ ዕቅድ ዝግጅት የጤና እና የደህንነት ጥንቃቅ ሁኔታዎችን እና የግንባታ ቦታ መርሆችን
3) ንድፍ አውጭው ከፕሮጀክቱ ባለቤት የተገኘ የቅድመ-ግንባታ መረጃ እንዲሁም ከኮንስትራክሽን እቅድ ጋር
ተያያዥነት ያለው ከሌላ አካል የተገኘ ማንኛውምመረጃ ለሥራ ተቋራጭ መስጠት እና የሥራ ተቋራጩን
የኮንስትራክሽን ምዕራፍ ዕቅድ ዝግጅት ስኬታማ እንዲሆን በማድረግ ሂደት የመተባበር ግዴታ አለበት።
4) ሥራ ተቋራጭ በፕሮጀክቱ ትግበራ ሂደት ጊዜ የግንባታው ምዕራፍ ዕቅዱ በትክክል እንዲተገበር፣
ከፕሮጀክቱ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ጨምሮ እንደየ ፕሮጀክቱ ባህሪያት አስፈላጊ የሆነ የጤና እና የደህንነት
6) ዋናው ዲዛይነር ሥራው እና በስራ ሂደት የተደረጉ ለውጦችን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የጤና እና የደህንነት
ማህደሩ በተገቢው ሁኔታ መተግበሩን፣ እንደጊዜው መሻሻሉን እና መከለሱን ማረጋገጥ ማረጋገጥ ይኖርበታል።
መረጃ በጤና እና ደህንነት ፋይል ውስጥ ለማካተት በሚያስችል መልኩ ለዲዛይነር መስጠት አለበት ።
8) የዲዛይነሩ የሥራ ጊዜ ፕሮጀክቱ ከማለቁ በፊት የተጠናቀቀ እንደ ሆነ ዋናው ዲዛይነር የጤና እና የደህንነት
9) የጤና እና ደህንነት ማህደሩ በአንቀጽ (8) ለዋናው ተቋራጭ የተላለፈ እንደሆነ ዋናው ስራ ተቋራጩ የጤና እና
10) በፕሮጀክቱ መጨረሻ ላይ ዋናው ዲዛይነር ወይም ዋና ዲዛይነር በሌለበት ዋናው ሥራ ተቋራጭ, የጤና እና
ክፍል አራት
እንዲያገኙ ወይም ከጉዳት እንዲያመልጡ በሚገባ የለበሱ እና ደህንነቱ በማያሰጋ መልኩ በአግባቡ የተያዘ.መሆን
አለባቸው፡-
2) ኮፈርዳም ወይም ካሲሰን እና ማንኛውም የሥራ መሣሪያዎች እና ቁሶች በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሥራት ጥቅም
ላይ ሊውሉ የሚችሉ ሥራው በሚካሄድበት ፈረቃ መጀመሪያ ላይ ብቃት ባለው ሰው ምርመራ ተደርጎበት
ኮፈርዳም ወይም በካይሰን ጥንካሬ ወይም መረጋጋት ላይ ተጽእኖ ሊያሳድር የሚችል ክስተት መኖር ወይም
ጉዳዮች ላይ (አንቀፅ ቁጥር … በተደነገገው መሰረት ያልረኩበት መሆኑን ካሳወቀ ጉዳዩ በአጥጋቢ ሁኔታ
መከናወኑን የማይችል መሆኑን የተረዳው እንደሆነ በማንኛዉም ሰው ደኅንነት ላይ አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉትን
ጉዳዮች ፍተሻው ከማለቁ በፊት የተሟላ የምርመራ ሪፖርት በማዘጋጀት ሪፖርቱን ወይም ግልባጩን ምርመራው
3) ሰራተኛ ወይም በሌላ አኳኋን) ቀጣሪው ወይም አሰሪው ሰው ፍተሻውን ያከናወነው ሰው በንዑስ አንቀጽ (1)
2) ለኮንስትራክሽን ስራ አደጋ የሚፈጥር ከኤሌክትሪክ ሃይል ኬብሎች የሚመነጭ አደጋ የሚከሰት ከሆነ ከአደጋው
አካባቢ እንዲርቁ ወይም ኃይሉ የተነጠለ እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ መሬት ላይ እንዲቀበር መደረግ አለበት.
4) በተቻለ መጠን አደጋውን ለመከላከል ተስማሚና በቂ የጥንቃቄ ዕርምጃዎች ካልተከናወኑ በቀር (በዚህ አዋጅ
የሚፈለጉትን ማንኛውንም ዕርምጃዎች ጨምሮ) በጤና ወይም በደኅንነት ላይ አደጋ ወይም ጉዳት
ክፍል አምስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
አንቀጽ 64፡ የመተባበር ግዴታ
1. ይህንን አዋጅ ተግባራዊ ለማድረግ ማንኛውም ሰው የመተባበር ግዴታ አለበት፣
2. ማንኛውም ሙያተኛ እና ድርጅት ይህንን አዋጅ እና ተከትሎ የሚወጡ ደንብ እና መመሪያ
ለማስፈጸም አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን የመስጠት ግዴታ አለበት፣
3. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ ግለሰብ እና ድርጅት እንዲሁም የመንግስት አካል በዘርፉ የወጡ ህጎችን
ማለትም አዋጅመ ደንብ፣ መመሪያ፣ እስታንዳርዶች ፣ማንዋሎች ቼክ ሊስቶች አክብሮ የመተግበር
ግዴታ አለበት
አንቀጽ 65፡ ደንብ የማውጣትሥልጣን
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይህንን አዋጅ ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ ደንቦችን ሊያወጣ ይችላል፡፡