Professional Documents
Culture Documents
03
03
01/2011
ጥር 2011ዓ.ም.
አዲስ አበባ
1
መግቢያ
በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ ያሉትን የግንባታ ስራዎች መምራትና ማስተዳደር ለከተማዋ
ኢኮኖሚያዊ እድገትም ሆነ ጤናና ደህንነት ጠቀሜታ እንዳለው ስለታመነበት፤
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚና ማዘጋጃ ቤት
አገልግሎት አካላት እንደገና ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ፴፭/፪ሺ፬ ዓ.ም (እንደተሻሻለ) አንቀፅ ፹፬
በተሰጠው ስልጣን መሰረት ይህንን መተዳደሪያ ደንብ አውጥቷል፡፡
2
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1.አጭር ርዕስ
2.ትርጓሜ
የቃሉ አገባብ የተለየ ትርጉም የሚያሰጠው ከልሆነ በስተቀር በዚህ መተዳደሪያደንብ መሰረት ፡-
3
13)"የኮንስትራክሽን ስራ ፈቃድ" ማለትበህግ አግባብ ካለው አካል የግንባታ ስራውን
ለመስራት የተሰጠ የፈቃድ ሰነድ ነው፡፡
14)"ስራ ተቋራጭ " ማለት የግንባታ ስራውን የሚያከናውን ተቋም ነው፡፡
15)"የማፍረስ ስራ" ማለት በሰው ኃይል ጉልበት, በማሽነሪ, ወይም በፈንጂዎች በመጠቀም
አንድን መዋቅር ወይም ክፍልን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የማፍረስ ስራ ነው፡፡
16)"ዲዛይን" ማለት ለሚሰራው የግንባታ ስራ ንድፎችን, ስሌቶችን, የንድፍ ዝርዝሮችንእና
ዝርዝር መግለጫዎችን የያዘ ሰነድ ነው፡፡
17)"የመሬት ቁፋሮ ስራ” ማለትከላይኛውን የአፈር ጠረጋ ጀምሮ እስከ ጥልቅ ቁፋሮ ድረስ
ያለውን የቁፋሮ ስራ የሚያጠቃልል ነው፡፡
18)"የጤና እና ደህንነት ፋይል" ማለት በዚህ መተዳደሪያ ደንብ የሚጠየቀውን ፋይል
ወይም ሌላ የጽሁፍ መረጃ የያዘ ሰነድ ነው::
19)"የጤና እና የደህንነት ዕቅድ" ማለት የሰራተኞችን ጤናና ደህንነት በስራ ቦታ ላይ
እንዴት መጠበቅ እንደሚቻል የሚያሳይ በስራ ተቋራጭ የሚዘጋጅ ዝርዝር እቅድ ነው፡፡
20)"የእቃ ማንሻ" ማለት እቃዎችን ወደ ላይ እና ወደ ታች ለማጓጓዝ የሚረዳ መሳሪያ ነው፡
፡
21)"የሰው ማመላለሻ" ማለት ሰዎችን ወደ ላይ እና ወደ ታች ለማጓጓዝ የሚረዳ መሳሪያ
ነው፡፡
22)"ስካፎልዲንግ" ማለት ጊዜያዊየሆነና ከፍባለ ቦታ ላይ ሰራተኞች ለስራ የሚንቀሳቀሱበትና
የስራ እቃዎቻቸውን የሚስቀምጡበትከእንጨት ወይም ከብረት የሚዘጋጅ መዋቅር ነው፡፡
23)‘’ የድጋፍ ሥራ (ሾሪንግ)’’ ማለት በአፈር ቁፋሮ ጊዜ ከጎን ያለው መሬት እንዳይናድ
ለመከላከል የሚሰራ ግንባታ ነው፡፡
24)"ጊዜያዊ ስራዎች" ማለት ዋናውን የግንባታ ስራ ለማከናወን የሚረዱ እና ግንባታው
ካለቀ በኋላ የሚፈርሱ ስራዎችንሁሉ ያጠቃልላል፡፡
25)በዚህ በመተዳደሪያ ደንቡ በወንድ ፆታ የተገለጸው የሴት ጾታንም ይጨምራል
26)“ሰው”ማለትየተፈጥሮ ሰው ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው፡፡
27)የጾታ አገላለጽ
በዚህ መመሪያ ውስጥ በወንድ ፆታ የተገለፀው የሴትንም ፆታ ያካትታል፡፡
3.የተፈጻሚነት ወሰን
4
ክፍል ሁለት
5
መካሄዳቸውን እና የፅሑፍ ማረጋገጫዎች በዋና ተቆጣጣሪ ለዋናው ስራ ተቋራጭ
ኦዲቱ በተደረገ በ7 ቀን ውስጥ መሰጠቱን ማረጋገጥ;
12)ስራ ተቋራጭ ለሰራተኞች ጤናእናደህንነት አስጊ በሆነ ሁኔታ ስራ እንዲሰራ
ሲያደርግ ማስቆምና የማስተካከያእርምጃ መውሰድ፤
13)ተጨማሪ ስራ እንዲሰራለት ካዘዘ የጤንነትና ደህንነት ወጪዎችን ጨምሮ
ተጨማሪውን ስራ ለማጠናቀቅ የሚያስፈልጉ ወጪዎችን መሸፈን፤
14)ከባድ አደጋ በግንባታ ቦታ ላይ ሲያጋጥም ለሚመለከተው የመንግስት አካል ወዲያውኑ
ማሳወቅ፤
15)በተለያየ ምክንያት በዚህ መተዳደሪያ ደንብ የተጣለበትን ኃላፊነት መወጣት ካልቻለ ሌላ
ሰው መወከል ይኖርበታል፤
16)ከዚህ በላይ በተቀመጠው አንቀጽ …..ንኡስ አንቀጽ…….የተወከለ ሰው በዚህ መተዳደሪያ
ደንብ በአሰሪ ላይ የተመለከተው ተግባርና ኃላፊነት ይኖሩታል፡፡
17)በግንባታ ቦታ ለሚከሰቱ የሞት፤ዘላቂ ወይም ጊዜያዊ የአካል ጉደት ለደረሰባቸው
ሰራተኞች ስራ ተቋራጩ አስፈላጊውን ካሳ መፈፀሙን ማረጋገጥ፤
6
7. ለሠራተኞች የጤና እና የደህንነት ስጋት የሚሆኑ የግንባታ ሥራዎችን እና ቦታዎችን
የሚጠቁም ምልክት ወይም በድምፅ የሚሰራ የአደጋ ማስጠንቀቂያ መሣሪያ
ማስቀመጡን ማረጋገጥ፣ ካላስቀመጠም እንዲያስቀምጥ ያደርጋል፣
10. ዋናው ሥራ ተቋራጭ ያስገባውን የጤና እና ደህንነት ዋስትና ሽፋን ጊዜውን ጠብቀው
መታደሳቸውን ያረጋግጣል፣
7
2) በዲዛይን ችግር ምንያት አደጋ ቢከሰት ለተከሰተው አደጋ የመፍትሄ ሀሳብ ያቀርባል
ዲዛይኑንም በአፋጣኝ አሻሽሎ ያቀርባል፤
3) ለሠራተኛ ጤና እና ደህንነት አደገኛ የሆኑ የሥራ ጉዳዮችን እና የግንባታ ግብአቶችን
በዲዛይን ውስጥ ማካተት የለበትም፣
4) ጤና እና ደህንነት መሠረት አድርጐ ከተሰራው ዲዛይን ውጭ ስራ ተቋራጩ
የሚሰራቸውን ማንኛውንም ስራ ያስቆማል፣እና
3. የተሠራው የግንባታ ሥራ በዚህ ደንብ የተደነገጉትን የጤና እና ደህንነት መስፈርቶች
እና በሀገሪቱ ሌሎች ህጎች መሠረት የተሰራመሆኑ በማረጋገጥ ለአሰሪው የደህነነት
ማረጋገጫ ሰነድ እንዲሁም ለስራ ተቋራጩ ቅጅ ይሰጣል፡፡
4. ውሉ ለጨረታ ከመውጣቱ በፊት የጤና እና የደህንነት መስፈርቶች በአስገዳጅነት
ያካትታል፣ እንዲሁም እንደተካተቱ አረጋግጦ ለአሰሪው በጽሁፍ ሪፖርት ያደርጋል፤
5. የአፈር ምርመራ ውጤት እና ግንባታው ምን ያህል ክብደት መሸከም እንደሚችል
ለአሰሪው ሪፖርት ያደርጋል፡፡
6. ጊዜያዊ ሥራዎች ሲሰሩ በግንባታው የመዋቅር ዲዛይን ላይ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ
እንዳይፈጥሩ በቅርብ ሆኖ የስራ ተቋራጩን ያማክራል፣
7. ለጊዜያዊ ሥራ የተሰሩ ዲዛይኖች እና ስሌቶች በግንባታ ቦታ እንዲቀመጡ ያደርጋል
(መቀመጣቸውን) ያጋግጣል፡፡
8
1. የጤና እና የደህንነት መረጃዎችን በግንባታ ቦታ ለሁለም ሠራተኛ፣ የግንባታ ቦታ
ጉብኝት ለሚያደርጉ፣ ለግንባታ ባለቤት ተወካይ እና ለግንባታ ተቆጣጣሪ በቀላሉ
እንዲያገኟቸው ክፍት እና ግልፅ የሆነ ቦታ ማስቀመጥ አለበት፣
2. ሥራውን ለሌላ ሥራ ተቋራጭ ከሰጠ፣
ሀ. የጤና እና የደህንነት ዝርዝር ሁኔታዎችን አማልቶ ሥራውን በብቃት እና
በኃላፊነት ለሚሰራ ንኡስ ስራ ተቋራጭ መስጠት ይኖርበታል፣
ለ. ንኡስ ስራ ተቋራጭ በግንባታ ወቅት ለሚተገብራቸው የጤና እና የደህንነት
እርምጃዎች በቂ የሆነ የገንዘብ መጠን መኖሩን ማረጋገጥ አለበት፣
ሐ. ንኡስ ስራ ተቋራጭ ሥራውን ከመጀመሩ በፊት በሰራተኛው ላይ ለሚደርሱ
የበሽታ፣ የሞት እና የአካል ጉዳቶች ዋስትና ለመስጠት የሚያስችሉት የህይወት
ዋስትና መድህን ሽፋን መኖሩን ማረጋገጥ አለበት፣
መ. ያዘጋጀውን የጤና እና ደህንነት ዕቅድ በግንባታ ቦታ ላይንኡስ ስራ ተቋራጭ
እንዲተገብርማድረግ እና ካልተገበረ እርምጃ መውሰድ፣
9
10. በግንባታ ቦታ የሠራተኞቹ ጤና እና ደህንነት እንዲጠበቅ፣በዚህ መተዳደሪያ ደንብ ላይ
የተደነገጉትን የጤና እና የደህንነት ድንጋጌዎችን እንዲከበሩ፤ የጤና እና የደህንነት
አጠባበቅ ስልጠና የሚሰጥ እና የግንባታ ቦታ ደህንነት እንዲጠበቅ የደህንነት መሀንዲስ
ይመድባል፡፡
11. አደጋ ሊያደርሱ የሚችሉ ነገሮችን ቀድሞ መከላከል እና አደጋ ከደረሰ ወደ ህክምና ቦታ
በመውሰድ አስፈላጊውን ህክምና እንዲወስዱ ያደርጋል፡፡
1) ከሁለት ወለል በላይ ያለን ግንባታ የሚያፈርስ ከሆነ ስራውን እንዴት እንደሚያከናውን
ዝርዝር ዕቅድ አዘጋጅቶ ማቅረብና ማፀደቅ፤
10
2) የኤሌክትሪክ፣ የስልክ እና የሌሎች መሠረተ ልማት መስመሮች ዝርጋታ መቋረጡን
ማረጋገጥ፣
3) ተገቢውን የሰው ኃይልና መሣሪያ ማዘጋጀት፣
4) የማፍረስ ስራውን የሚቆጣጠር በቂ ልምድና ክህሎት ያለው ባለሙያ ይመድባል፤
5) ከአንድ ወለል በላይ የሆኑ ህንፃዎች በሚፈርሱበት ወቅት ከጣሪያው በመጀመር
በየደረጃው መፍረስ ፣
6) የማፍረስ ሥራ ሲከናወን በአጐራባች ይዞታ ወይም ንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርሰ
ተገቢው ጥንቃቄ ማድረግ፣
7) የማፍረስ ሥራ የሚያከናውኑ ባለሙያዎች ተገቢውን የደህንነት መሣሪያ
መጠቀማቸውን ማረጋገጥ፣
8) በማፍረስ ሥራ ወቅት አቧራም ሆነ ሌላ ብናኝ አካባቢው እንዳይበከል ተገቢውን
መከላከያ መጠቀም፣
9) ከፍተኛ ክብደት ያላቸው ነገሮች በሚፈርስበት ወቅት መሬት ላይ ወድቀው ሌላ ጉዳት
እንዳያደርሱ መጠንቀቅ፣እና
10)የድጋፍ ግርግዳዎች በሚፈርሱበት ወቅት የመሬት መናድ እንዳይከሰት ተገቢውን
ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
11.2 የቁፋሮ ሥራ
11
2) የቁፋሮ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ቁፋሮ የሚካሄድበት ቦታ ከማንኛውም የመሠረተ ልማት
ዝርጋታ የፀዳ መሆኑን ፣
3) ዛፎች፣ ቋጥኖች ወይም ሌሎች ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ነገሮች ከቁፋሮው ቦታ
በቅድሚያ መወገዳቸውን፣
4) የግንባታ ቦታው አፈር በአግባቡ መጠናቱንና ተገቢው ጥንቃቄ መደረጉን፣
5) ሠራተኞች በአፈር መናድም ሆነ ጉድጎድ ውስጥ በመውደቅ ምንም ዓይነት ጉዳት
እንዳይደርስባቸውጥንቃቄ መደረጉን፣
6) ቁፋሮ ከመጀመሩ በፊት ቁፋሮ የሚካሄድበትን ቦታ ለይቶ መከለል፤
7) የሚቆፈረው ጉድጓድ 1.5 ሜ በላይ ከሆነ ለሠራተኛ መግቢያና መውጫ መሰላል
መዘጋጀቱንና መሰላሉ ከጉድጓዱ የላይኛው ጠርዝ ከ80 ሴ.ሜ በታች ዝቅ አለማለቱን፣
8) የሚቆፈረው ጉድጎድ ከ3 ሜ በላይ የሚቆፈር ከሆነ በ900 ከመቆፈር ይልቅ አግድም
(ስላይድ) አድርጐ መቆፈሩን ፤
9) የቁፋሮ ስራው በሚሰራበት ወቅት አፈሩ የመናድ ባህሪ ካለውና በአከባቢው ሌሎች
ግንባታዎችና የመሰረተ ልማት አውታሮች ካሉ ደህንነታቸውን ለመጠበቅ ግዜያዊ
የድጋፍ መዋቅር (shoring) መሰራቱን፤
10)ቁፋሮው በሚከናወንበት ወቅት በአከባቢው ስነ ምህዳር (ecology)፤ ታሪካዊ ቅርሶችና
ሌሎች ጥበቃ የሚያስፈልጋቸው ሀብቶች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ አስፈላጊውን ጥንቃቄ
መወሰዱን ፤
11)ተቆፍሮ የሚወጣው አፈር በየጊዜው ከግንባታ ቦታ ላይ መነሳቱን ማረጋገጥ
ይኖርበታል፡፡
1) ፎርም ዎርክ (Form work) ምንም አይነት ክፍተት ሳይኖረው በአግባቡ መገጠም
አለበት፣
2) የውስጠኛው የፎርም ዎርክ (Form work) ክፍል ንፁህ እና ምንም አይነት ወጣ ገባ
የሌለው መሆን አለበት፣
3) ፎርም ዎርክ (Form work) በሚፈታበት ጊዜ በቀላሉ ከመዋቅሩ ላይ እንዲላቀቅና አደጋ
እንዳያደርስ ለዚሁ አላማ የተዘጋጀ ማለስለሻ ዘይት መቀባት አለበት፤
4) ለስላብ የምንጠቀመው ፎርም ዎርክ (Formwork) ከሆነ ሁሉም በእኩል ደረጃ
መደርደር አለባቸው፣
5) የስላብ ፎርም ዎርክ (Formwork) ለመደገፍ የሚቆመው ቋሚ በቂ ጥንካሬ ሊኖረው
ይገባል፣
6) አርማታ (Concrete) በቂ ጥንካሬ እስኪኖረው ድረስ ፎርም ዎርክ (Form work)
መነሣት የለበትም
12
7) ፎርም ዎርክ (Formwork) መነሣት ያለበት የሚመለከተው ባለሙያ ሲፈቅድ ብቻ
ይሆናል፤
1. ፎርም ዎርክ (Form work) በሚነሣበት ወቅት አደጋ እንዳይፈጥር ተገቢውን ጥንቃቄ
መደረግ አለበት፡፡
13
11.6. መሰላል
በግንባታ ሥራ ወቅት የምንጠቀመው መሰላል ከብረት ወይም ከእንጨት የተሠራ ሆኖ
14
11.8 የግንባታ ተሽከርካሪዎች እና ተንቀሳቃሽ የግንባታ ግብዓት
ማቀነባበሪያ
ማንኛውም ሥራ ተቀራጭ ሁሉም የግንባታ ተሽከርካሪዎችና ተንቀሳቃሽ ማቀነባበሪያዎች
ማንኛውም ሥራ ተቋራጭ፡-
ማንኛውም ሥራ ተቀራጭ፡-
1. ተቀጣጣይነት ባህሪ ያላቸው ፈሳሽ ነገሮች በጥቅም ላይ ሲውሉ ወይም ሲቀመጡ አደጋ
በማያስከትሉና የሥራ አካባቢን በማይበክሉ መልኩ መሆኑን፣
15
2. በተከማቸበት ቦታ ከእሳትጋር የተያያዘ ሥራ እንዳይሰራ መከላከልና ይህንኑ የሚያሳይ
ምልክት ማስቀመጥ፣
3. ያሉበት መጋዘን ምቹ በሆነ ቦታ ላይ የእሳት ማጥፊያ መሣሪያ የተቀመጠ መሆኑን፣
4. ለአንድ ቀን ፍጆታ ብቻ የሚውል ከመጋዘን እንዲወጣ መደረጉን፣
5. ተቀጣጣይነት ባህሪ ያላቸው ፈሳሽ ነገሮች በጥቅም ላይ በሚውሉበት ጊዜ የደህንነት
ባለሙያ በቦታው ላይ መገኘቱን፤
6. በደንብ በተከደነ እቃ የተቀመጡ መሆኑንና ካለቀ መያዣው በአግባቡ የተወገደ
መሆኑን፣
7. በቆርቆሮ የታሸጉ ከሆኑ ፈሳሹ ሲያልቅ መያዣው እቃ በተገቢው መንገድ የተወገደ
መሆኑን እና
8. ምንም ዓይነት እሳት ሊያስነሱ የሚችሉና ተቀጣጣይነት ባህሪ ያላቸው ሌሎች ነገሮች
አለመኖራቸውን ማረጋገጥ አለበት፡፡
ማንኛውም ሥራ ተቀራጭ የግንባታ ቦታውን ጥበቃ ቀጥሮ የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለበት መሆኑ
እንደተጠበቀ ሆኖ፡-
16
11.13.ማከማቻ (መጋዘን) በተመለከተ
ማንኛውም ስራ ተቋራጭ፡-
17
1. የመውደቅ መከላከያ እቅድ የሚያዘጋጅ ብቁ የሆነ ባለሙያ ይመድባል፣
2. የተዘጋጀው እቅድ ተግባራዊ እንዲሆን ያደርጋል፣ በአስፈላጊው ጊዜ እና ቦታ እንዲሻሻል
ያደርጋል፣
3. የመከላከያ እቅድ ተግባራዊነት ቀጣይነት እንዲኖረው አስፈላጊ እርምጃዎችን ይወስዳል፡፡
11.18. የጣራ ሥራ
18
2. ከፍተኛ የንፋስ ፋጥነት እና ከባድ ዝናብ ባለበት የአየር ጠባይ ሁኔታ ውስጥ
የሠራተኞች ደህንነት ስለማይጠበቅ የጣራ ሥራ ማስቆም፤
3. በጣሪያ ጠርዝ አካባቢ ለሚሰሩ ሠራተኞች የደህንነት ቀበቶ ወይም እሱን ሊተካ የሚችል
የደህንነት መጠበቂየ መሣሪያ ማቅረብ ፣
ማንኛውም ስራ ተቋራጭ፡-
1) በኮንክሪት ማቀነባበሪያዎች በቂ እውቀትና ልምድ ያለው ባለሙያ መመደብ አለበት፣
2) በኮንክሪት ማቀነባበሪያዎችላይ ለሚመደቡ ሠራተኞች አደጋን ከመቀነስ አንፃር በቂ
ሥልጠና መስጠት አለበት፣
3) ኮንክሪት ማቀነባበሪያውን ከተመደበለት ባለሙያዎች ውጭ ማንም ሰው እንዳይነካ
ጥንቃቄ ማድረግ፣
4) አንድ የኮንክሪት ማቀነባበሪያ ማሟላት ያለበት መስፈርት አሟልቶ መገኘቱን
ማረጋገጥ አለበት፡፡
5) ኮንክሪት ማቀነባበሪያ የተገነባበት ቦታ በቀላሉ ተደራሽ የሆነ እና አደጋዎችን
ለመከላከል ምቹ መሆኑንማረጋገጥ አለበት፣
6) የሚጠቀማቸው የኮንክሪት ማቀነባበሪያዎች ጥራታቸው የተረጋገጠ መሆን አለበት፣
7) የኮንክሪት ማቀነባበሪያውን ወቅቱን የጠበቀ ጥገና በትክክለኛ ባለሙያ ማድረግ
አለበት፡፡
1. የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና መስጫ ቦታና በዘርፉ በቂ እውቀትና ክህሎት ያለው ባለሙያ
መመደቡን፤
19
2. የባኞ (ሻወር) አገልግሎት፣
3. ንጹህና ለሁለቱም ፆታ የተለየ መፀዳጃ ቤት መኖሩን፤
4. ለሁለቱም ፆታ የተለየ የልብስ መቀየሪያ ክፍል፣
5. የተከለለ የመመገቢያና ማረፊያ ቦታ ፤
6. የምግብና የሻይ ቡና አገልግሎት መስጫ ቦታ እና
7. በካምፕ ውስጥ ለሚኖሩ ሠራተኞች ምቹ የመኖሪያ ቦታ መመቻቸቱን ማረጋገጥ
አለበት፡፡
20
ክፍል ሦስት
የጤናና ደህንነትአብይና ንኡስ ኮሚቴዎችን
ስለማቋቋም
የደህንነትና ጤና ንኡስ ኮሚቴ አምስት አባላት የሚኖሩት ሲሆን ሁለቱ ከሠራተኛው አንድ
ከአማካሪ ድርጅት አንድ ከስራ ተቋራጭ እና አንድ ከአሰሪ ሆኖ ከአሰሪው የሚመደበው
በሰብሳቢነት የሚመራ ሲሆን ኮሚቴው ከዚህ ቀጥሎ ያሉት ኃላፊነትና ተግባር ይኖሩታል፡፡
21
13.የግንባታ ሠራተኞች የጤና እና ደህንነት አብይ ኮሚቴ
በክፍለ ከተማው የኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ኃላፊ የሚቋቋምና ከዚህ በታች የተጠቀሱት አባላት
የሚኖሩት የግንባታ ሠራተኞች አብይ ኮሚቴ ይቋቋማል፡፡
1) በክፍለ ከተማው አዳዲስ ግንባታ ቦታዎች ላይ የጤናና ደህንነት ጉዳይ ንኡስ ኮሚቴ ያቋ
ቁማል፤
2) የስራ ዘመናቸውን ከሚያጠናቅቁ ንኡስ ኮሚቴዎች የተረከባቸውን ፋይሎች አደራጅቶ
ይይዛል፤
3) ከፅ/ቤት ኃላፊ የሚመራለትን የስነምግባር ጥሰት ጉዳይ ያጣራል፤ የውሳኔ ሃሳብ ለፅ/ቤት
ኃላፊ ያቀርባል፤
4) ተፈጸመ የተባለውን የጤናና ደህንነት መተዳደሪያ ደንብ ጥሰት ክስ በዚህ ደንብ
ድንጋጌዎች እና ጥፋቱ በተፈጸመበት ጊዜ በስራ ላይ በነበሩ ሌሎች ህጎች መሰረት
ይመረምራል፤ለፅ/ቤት ኃላፊ ያቀርባል፤
5) በየግንባታ ቦታዎች ያጋጠሙ የጤናና ደህንነት አደጋዎች ይመረምራል የመፍትሄ ሀሳብ
ለፅ/ቤት ኃላፊ ያቀርባል፤እና
6) ግንባታ ቦታ በመሄድ ይከታተላል ርፖርት ለፅ/ቤት ኃላፊ ያቀርባል፤
7) በተለያዩ የስራ ቦታዎች የተከሰቱ አደጋዎችን መንስኤና ያስከተሉትን ጉዳት በመቀመር
ለዚህ መተዳደሪያ ደንብ መሻሻልም ሆነ ለሌሎች ህጎች መነሻነት እንዲውል ለቢሮ
ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ይልካል፤ እና
8) ከግንባታ ቦታ የጤናና ደህንነት ንኡስ ኮሚቴ የሚላክለትን ሪፖርት በመቀመር ለፅ/ቤት
ኃላፊ ያቀርባል፤
22
5) ኮሚቴዉ የሚሰጠውን ውሣኔ ለቢሮው በጽሁፍ ወይም በኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ዘዴ
እንዲደርሰው ያደርጋል፣
6) በኮሚቴዉ ውሳኔ የተሰጠባቸውን ጉዳዮች አፈፃፀም ይከታተላል፤
7) በዳኝነት አካል ሲጠየቅ የውሳኔውን ቅጂ ይሰጣል፣
መ) ይግባኞችን ይቀበላል፣
24
ክፍል አራት
የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርዓት
1) ማንኛውም የግንባታ ቦታ ሠራተኛ በንኡስ ኮሚቴ ውሳኔ ቅር የተሰኘ አካል ለፅ/ቤቱ
የጤናና ደህንነት አብይ ኮሚቴ በጽሑፍ በአምስት የስራ ቀናት ውስጥ ማቅረብ
ይኖርበታል፤
2) የፅ/ቤቱ የጤናና ደህንነት አብይ ኮሚቴ ቅሬታው በቀረበለት 5 የስራ ቀናት ውስጥ
ለፅ/ቤቱ ኃላፊ የውሳኔ ሀሳብ ያቀርባል፤
3) የፅ/ቤቱ የጤናና ደህንነት አብይ ኮሚቴ በንኡስ ኮሚቴ የተሰጠውን ውሳኔ
ሊያፀናው፣ ሊያሻሽለው ወይም ሙሉ በሙሉ ሊሽረው እና ሌላ የተለየ የውሳኔ
ሀሳብ ሊሰጥ ይችላል፣
4) የቢሮው ኃላፊ ከይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የሚቀርብለትን የውሳኔ ሃሳብ በሶስት የስራ
ቀናት ውስጥ በመመልከት ውሳኔውን ሙሉ በሙሉ ሊያፀናው፤ በከፊል ሊያሻሽለው
ወይም ሙሉ በሙሉ ሊሽረው ይችላል ይህም የመጨረሻ ይሆናል፡፡
5) ከቢሮው ውሳኔ በኋላ ቅር የተሰኘ አካል ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍ/ቤት የመውሰድ
መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
25
ክፍል አምስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
14.ቅጣት
16.የመተባበር ግዴታ፣
ማንኛውም ሰው ይህን ደንብ በማስፈጸም ረገድ የመተባበር ግዴታ አለበት::
17. ተፈፃሚነትስለማይኖረውሕግ
የዚህን ደንብ ድንጋጌዎች የሚቃረን ማንኛውም ሕግ ወይም የአሰራር ልማድ በዚህ
ደንብ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡
26
19. ደንቡ የሚፀናበት ጊዜ
ታከለ ኡማ (ኢንጂነር)
27