Professional Documents
Culture Documents
271
271
27፡44====
======በነጋም ጊዜ ምድሩን አላወቁትም። =======
የቀጠለ……..
መግቢያ
ወንጌላዊ ቅዱስ ሉቃስ ስለ ወንጌል እስረኛ የሆነዉን የቅዱስ ጳዉሎስን ጉዞ በደንብ ገልጿል። ያሳያል።
በጉዞው ምን እንደገጠማቸው፦
• የጳዉሎስን ምንነት
• የእሰረኞቹን
• የመሪዎቹን ሁኔታ በደንብ ገልጿል።
• እስረኖቹ በመቶ አለቃ በሚመሩ ወታደሮች ይጠበቁ ነበር።
• ቅዱስ ጳዉሎስ እንደ እስረኛ ሳይሆን እንደ የክርስቶስ ወንጌል ሰባኪ ነበር
• ጉዞው በመከራ የተመላ ቢሆንም፣ ወንጌልን ለማስተማር ጥሩ አጋጣሚ ነበር
ጉዞው ፦
ከቂሳርያ ወደ ማይራ 1-5
ከማይራ/ ሙራ/ ወደ መልካም ወደብ 6-8
ከመልካም ወደብ ወደ ማልታ 9-44
ዳግመኛም እንደ ፍርዱ እንዴት እንደ ፈረዱ ተመልከት፤ “አንተ ከራስህ ጋር ነህ” ካሉ በኋላ ለሞት
ብቻ ሳይሆን ለእስራትም ያልተገባ ነው ብለው ነጻ አወጡት፤ በእርግጥም ሊፈቱት ይወዱ ነበር።
ቅዱስ ጳዉሎስም ከእነዚያ ጋር / ከእስረኞቹ ጋር/ አብሮ ታሰረ/ አብሮ ለፍርድ ወደ ሮም ሄደ/ ተባበረ
እንጂ በክፉ ድርጊታቸው አልተባበረም።
በዚህም ድንቅ ነገር ይታያል።
የጳዉሎስ ጉዞ ወደ ሮም
የቀጠለ………….
ጉዞው ተወሰነ፦
"ወደ ኢጣሊያም በመርከብ እንድንሄድ በተቈረጠ ጊዜ፥ ጳውሎስንና ሌሎች እስረኞችን ከአውግስጦስ
ጭፍራ ለነበረው ዩልዮስ ለሚሉት ለአንድ የመቶ አለቃ አሳልፈው ሰጧቸው።
የጳውሎስ ጉደኞች፦
ቅዱስ ሉቃስ፡
ጳዉሎስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ አብሮት ነበር።
በቂሳርያ ጳዉሎስ ሲታሰርም በቂሳርያ ይኖር ነበር
ቅዱስ ጳዉሎስ ወደ ሮም ለፍርድ ሲስሄድ አብሮት ነው የተጓዘው።
አርስጥሮኮስ፦ ተሰሎንቄያውም አብሮቸው ነበር። ከቅዱስ ጳዉሎስ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም አብሮ መጥቷል። የሐዋ.ሥ
19፡29 ወደ ሮም አብሯቸው ተጉዘ።
=====ሁለቱም በጳዉሎስ መታሰር አላፈሩም። የታሰረው ስለ ወንጌል ነውና። ነገር ግን አብረው እርሱ የሚቀበልዉን መከራ፣ በጉዞው
የሚመጣዉን ፈተና ለመቀበል የወሰኑ እዉነተኛ ጉደኛ፣ ደቀመዝሙር ናቸው። ህይወታቸዉን ለእሱ፣ ለስብከት አገልግሎት፣ ክርስቶስን
በአህዛብ ፊት ለመመስከር አሳልፈው የሰጡ ናቸው።=========
አርስጥሮኮስ ከጳውሎስ ጋር ምን ያህል ርቀት እንደሄደ ተመልከት። አርስጥሮኮስ በዚህ ጉዞ መኖሩ/መገኘቱ ለመልካም ነገር
እና ለአላማ ነው። ምክነያቱም የጳዉሎስን የሌሎችንም ስለ ክርስቶስ መከራ መቀበላቸዉን የሁሉንም ዘገባ ወደ መቄዶንያ ሰዎች
ይወስዳልና።
ጉዞው የጀመረው፦ ከቂሳርያ ነው። ከደቡብ ጠርሴስ ወደብ ማለት ነው። ወደ አድራሚጢስ መርከብ ገብተን በእስያ ዳር
ለመጓዝ ተነሳን።
የቀጠለ………….
ነፋሱ ትክክለኛ ነፋስ ቢሆን ኖሮ፣ በቀጥታ ይጓዙ ነበር። ቆጵሮስን በስተቀኝ አድርገው ይሄዱ
ነበር።
ነገር ግን ነፋሱ ትክክለኛ ነፋስ አይደለምና በነፋሱ ተጽዕኖ/ አስገዳጅነት ወደ ተለያየ አቅጣጫ ተጓዙ።
በዚህም ቆጵሮስን በስተግራ አለፏት።
የመርከቡ ሰራተኞች ቀጥታ በባህሩ ለመሄድ አልቻሉም። ነገር ግን በምዕራብ ነፋስ ተጽዕኖ
በኪልቅያና በጵንፍልያ አጠግብ ከተሻገሩ በኋላ በሉቅያ ወደ አለ ወደ ሙራ ደርሱ።
ማጠቃልያ፦
የቅዱሳን ሕይወት በጠቅላላው እንዴት መከራ የበዛበት ህይወት እንደሆን ተመልከት:፡
ከእስር ቤት ወደ ሌላ ፈተና ገቡ።
ግን በመርከብ እና በማዕበል ዉስጥ ወደቁ።
ሙራ፦ በግሪክ የሉቅያ ከተማ ናት። ትልቅ/ ዝነኛ የወደብ ከተማ ናት። ትላልቅ መርከቦችን
የምትስተናግድ ናት። በተለይ ከእስክንድርያ ወደ ሮም ስንዴ የሚያጓጉዙ መርከቦች
ይበዙባታል።
የቀጠለ…………
ጉዞ ከሙራ ወደ መልካም ወደብ
በዚያም የመቶ አለቃው ወደ ኢጣሊያ የሚሄድ የእስክንድርያ መርከብ አገኘ። በውስጧም አኖረን። (ቁ. 5፣6።)
ከከባዱ ነፍስ ለማምለጥ
ለመርከቧም ደህንነት
ቆጵሮስን ተገን አድርገው ተጉዙ። ይህዉም አደገኛዉን ነፋስ ለመሸሽ ነው።
ቀኒዶስ ከሙራ 130 ማይል ይርቃል። በምዕራብ ሙራ የሚገኝ ወደብ ነው። ጉዟቸውም ጥግ
ጥጉን ነው። ሲጓዙም በጭንቅ በዝግታ ነብር።
በዝግታ የሚጉዙበት ምክነያት በሰሜን ምዕራብ ነፋስ ምክነያት ነው። ይህ ነፍስ ጉዞው
በጭንቅ እንዲሆን አድርጓል።
ስለዚህም የቀርጤስን ከተማ ተገን አድርገው በሰልሙና አንጻር ሄዱ።
ለልስያ ከተማ ወደቀረበች ወደ መልካም ወደብ ደርሱ።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ይህ ጾም የአይሁድ ጾም ሲሆን፣ ታላቁ ‘የሥርየት ቀን’ እንደሆነ ያምናል (ዘሌ.
23፡27)።
በሰባተኛው ወር በአሥረኛው ቀን (በመስከረም መጨረሻ አካባቢ) የበልግ ወራትን ተከትሎ፣ ያለው ወር ለመርከብ
ጉዞ አደገኛ በሚሆንበት ጊዜ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ ሐዋርያው መንፈስ ቅዱስ እንዳናገረው ማንም ሊክደው አይችልም። በመርከቡ ጉዞ ላይ ምን
እንደሚገጥማቸው ማለት ነው።
ስንዴዉንም ሮም ትፈልገዋለች።
የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስ ከተናገረው ይልቅ የመርከቡን ባለቤትና የመርከቡን መሪ አመነ። ቁ.11
ምክነያቱም፦
ብዙ ልምድ አላቸው በማለት ነው።
ከጳዉሎስ ይልቅ ለመርከባቸው እና ለደህነታቸው ያስባሉ ያዉቃሉ ብሎ ነው።
በዚህ ምክነያት መቶ አለቃው አመነ። ምንም እንኳ ለጳዉሎስ ርህራሄ እና አድናቆት፣ ክብር ቢኖረውም።
ነገር ግን ምክሩን አልተቀበለም።
"እኛም በዐውሎ ነፋስ ስለ ተናወጥን በማግስቱ መርከቡ ጭነት ወደ ባህር ይጥሉ ነበር።" (የሐዋ. ሥራ 27:18)
በማግስቱ እቃውን በተለይም እህሉን ወደ ባህር መጣል ጀመሩ።
ሀብት እንደማያድናቸው ተረድተዋል።
ነገር ግን ይህ በህይወታችን መርከብ ላይ ያለዉን ከባድ ሸክም ያሳያል።
ይህም ሸክም በዚህ ዓለም ውኃ ውስጥ ልንጥለው የሚገባ ነው።
የቀጠለ…………
ጠቢቡ ሰሎሞን “ሀብት ለባለቤቱ የተቆጠበች መከራው ናት።” ሀብት ጉዳት ነው። (መክ. 5፡13)።
የዚህ ዓለም ሰዎች ጊዜያዊ ሕይወታቸውን ለማዳን ያገኙትን/ያጠራቀሙትን/ በዉድ ዋጋ የገዙትን ሁሉ በቀላሉ እንዴት
እንደሚጥሉ አስገራሚ ነው።
ለዘለአለማዊ ሕይወታቸው ሲሉ ከሱ ትንሽ ክፍል ለድሆች እና ለችግረኛ ወንድሞቻቸው ለመስጠት በጣም ይከብዳቸዋል።
ዘላለማዊነትን ከክብ የሚጠባበቅ ሁሉ በዓለማዊ ጉዳዮች አይጠመድም።
የሚበልጥና ለዘወትር የሚኖር ገንዘብ በሰማይ ለራሳችሁ እንዳላችሁ አውቃችኋል” (ዕብ. 10፡34)።
የዚያች መርከብ መርከበኞች እንዳደረጉት፦ እኛም በዚህ ዓለም ማዕበል መካከል ሆነን ከባድ ሸክማችንን
ለማቅለል፣ በአየር ላይ እንደምትበር ወፍ ቀላል ለመሆን ቆርጠን መነሳት አለብን።
እንደ ፈርዖንና ወታደሮቹ እንዳንሆን። “ በግዙፍ በዉቅያኖስ/ ባህር ውስጥ እንደ እርሳስ ሰመጠን እንዳንቀር ማለት
ነው። " (ዘፀ. 15.10)
በእነዚያ አስጨናቂ ሁኔታዎች ውስጥ የኃይለኛውን ንፋስ ተፅእኖ ለመገደብ ሸራዎቹን ወደ ታች አወረዱ እና የ
1000 ቶን ጭነት መርከቧን ማቅለል ጀመሩ ።
ይኸዉም መርከቧ በኃይለኛ ማዕበል ግርፋት እንዳትፈርስ ነው።
በሦስተኛው ቀን የመርከቧን መያዣ በገዛ እጃቸው ወደ ባህሩ ላይ ጣሉት።
መርከቧ ውሃ መሞላት ስትጀምር፣ በብስጭት በየቦታው እየሮጡ እርስ በእርሳቸው እየተጣደፉ በከፍተኛ ድምፅ ጮሁ።
በዚህ ላይም ደግሞ ፦
ቀዝቃዛው ንፋስ፣
ከባድ ዝናብ
ድቅድቅ ጨለማ መከራቸውን ከፍ አደረገው።
================በዚያም አስፈሪ ድባብ ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ አምላኩ እየጾመ እየጸለየ ከእርሱ
ጋር በመርከብ ለሚሄዱት ሁሉ ሊፈጽምለት የገባውን አምላካዊ ቃል ኪዳን እውን ለማድረግ በቄሳር ፊት ቆሞ
ለጌታውና ለአዳኙ ይመሰክር ዘንድ ተልእኮውን ይፈጽም ዘንድ በመካከላቸው ነው ።
=====================
አንዳንዶች በዚህ ጾም ውስጥ ሁሉም ተሳትፈዋል ብለው ያምናሉ። ግን የጾሙት በአምልኮ ሥርዓት
ሳይሆን ከመከራና ከመራራነት የተነሣ ነው። እራሳቸውን እና መርከቧን ለማዳን አድካሚ ችግር ዉስጥ
ስለሆኑ ነው።
በዚህ ምክነያት በመብልና በመጠጥ አልጠመዱም።
=============አሁን ግን መለኮታዊውን የተስፋ ቃል ተቀብሎ በመካከላቸው ቆሞ ከታሳሪዎቹ እንደ አንዱ ሳይሆን አስደሳች
የምስራች የሚናገር መልካም ጉባኤ ሆኖ ነበር። ከእነርሱም የተስፋ መቁረጥን መንፈስ አርቆ የተስፋን መንፈስ ከሰማይም መጽናኛን
አመጣላቸው።======================
=++++++++++====+++++++++++====++++++++++
ሐዋርያው ጳውሎስ በሞት አደጋ ላይ በነበረበት ጊዜ እና ከእሱ ጋር አብረው ከነበሩት ሰዎች ጋር እንደማይጠፉ መለኮታዊ ቃል ኪዳን
ተገብቶለታል።
በስብከቱ አገልግሎት ላይ የሚያሳስበው ነገር አልነበረም፣ ነገር ግን የህይወቱ ግብ ይህ ነበር።
እዚህ ላይ ጳውሎስ በንጉሠ ነገሥቱ፣ በቤተ መንግሥት ውስጥ እንኳን ለመስበክ ምን ያህል ዝግጁ እንደሆነ
እና የእግዚአብሔርን ሥራ በአገልጋዮቹ በኩል እንደሚገልጽ ተናግሯል።
ጳዉሎስ ልቡን ለክርስቶስ ወንጌል አሳልፎ ሰጥቷል።
በመርከቡ ውስጥ መገኘቱ ታላቅ በረከት ነበር።
ተልእኮውን እውን ለማድረግ ፣እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር በመርከብ ላይ የነበሩትን
ነፍሳት ሁሉ ሰጠው።
ሐዋርያው ጳውሎስ ሞትን አልፈራም፤ ነገር ግን ምናልባትም ከእርሱ ጋር በመርከብ ላይ ከነበሩት ሰዎች ጋር ስለ ፍርሃታቸውና ስለ
ስቃያቸው ተናገረ።
ህይወቱን ሙሉ በእስር ላይ እስር የኖረ።
ከደካሞች ጋር ደካማ
ለሚትሰቃይ ነፍስ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር እየለመነ።
የባሕርም ጌታ ከሆነው ከክርስቶስ በሰው ጥበብ ሳይሆን በመንፈስ ጥበብ ተምሮ ካፒቴን ሆኖ
የሚመራው (ምድራዊ) መርከብን አይደለም፥ የዓለምን ሁሉ ቤተክርስቲያን ነው።
የቀጠለ…………
በዚህ መርከብ/ ዓለም/ ውስጥ ብዙ የመርከብ ስባሪዎች/ መናወጥ፣ ብዙ ማዕበሎች፣
የክፋት መናፍስት አሉ።
ከዉስጥ “ጠብ፣ ክርክር አለ”፣ ከውጭም ፍርሃት አለ። (2ቆሮ7፡5)
ስለዚህ እርሱ/ጳውሎስ/ እውነተኛ አብራሪ/ ካፒቴን ነው።
========አሥራ አራተኛውም ሌሊት በደረሰ ጊዜ በአድርያ ባሕር ወዲያና ወዲህ ስንነዳ፥ መርከበኞች
እኩለ ሌሊት በሆነ ጊዜ መርከበኞች ወደ አንዲት ደሴት የቀረቡ መሰላቸው” (የሐዋርያት ሥራ 27፡26-
27)።=======
========መለኪያ ገመድም ቢጥሉ ኻያ በሰው ቁመት አገኙ ጥቂትም ቈይተው ኹለተኛ ቢጥሉ ዐሥራ
ዐምስት በሰው ቁመት አገኙ።ቁ28==========
=========ድንጋያማም ወደ ሆነ ስፍራ እንዳይወድቁ ፈርተው፥ከመርከቡ በስተኋላ አራት መልሕቅ
አወረዱ፥ቀንም እንዲሆን ተመኙ ።ቁ29======
የድኅነት ነጻነት (በነጻ የተሰጠው መዳን) ማለት ሰው የራሱን ድርሻ አይሰራም ማለት አይደለም።
ቅዱስ ጳዉሎስ ምንም እንኳ እንደማይጠፉ ሁሉም እንደሚድኑ የመዳን ጸጋው ቢሰጠዉም።
ግን ዝም ብሎ ቁጭ አላለም።
ይህ የሚያሳየን ከእኛም የሚጠበቅ ነገር አለ። ለመዳን የምናደረገው ነገር አለ።
ለዚህም ነው ሐዋርያው ጳውሎስ ስለ “እምነት የፍቅር ስራን በመስራት ጭምር ነው።
==============መርከበኞቹ ግን በተነገረው ነገር ስላላመኑ ሊያመልጡ
ፈልገው ነበር፤ የመቶ አለቃው ግን “እነዚህ ሰዎች በመርከቡ ካልቆዩ እናንተ ትድኑ ዘንድ
አትችሉም” ብሎ ጳውሎስን ሲነግረው አምኗል።============
=========“ወታደሮቹም የጀልባውን ገመድ ቈርጠው እንዲወድቅ ተዉት” (ሐዋ.
27፡32)።ስለዚህ መርከበኞች በመርከቧ ውስጥ እንዲቆዩ እና ወደ ባሕሩ ዳርቻ ለማምጣት
እንዲሰሩ አደረጉ።========================
የቀጠለ…………
መርከበኞቹ ግን በተነገረው ነገር ስላላመኑ ሊያመልጡ ፈልገው ነበር፤
የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስን አመነ።
“ቀኑም ሲደርስ ጳውሎስ ምግብ ይበሉ ዘንድ ሁሉን ለመነአቸው እንዲህም አላቸው፡- “እናንተ ከቀራችሁበት ምንም
ሳትቀምሱ በጾማችሁ ዛሬ አሥራ አራተኛው ቀን ነው። (ቁጥር 33)
ጳውሎስ በእስር ቤት ውስጥ የሚያለቅስ እስረኛ አልነበረም።
ነገር ግን በሁሉም ፊት እውነተኛ የመርከቡ አለቃ፣ አስተዋይ አማካሪያቸው፣ ሩኅሩኅ አባታቸው፣ የነፍሳቸው እረኛ፣
በእግዚአብሔር ፊት ስለ እነርሱ የሚማለድ፣ ስለ ምግባቸውም የሚጨነቅ ሆነ።
ምንም ሳይበሉ እንዴት ሄዱ?
ፍርሃታቸው ያዛቸው፣ እና የምግብ ፍላጎት ውስጥ እንዲወድቁ አልፈቀደላቸውም ፣ እነሱ ፣ በጣም ከባድ አደጋ
ላይ ስለሆኑ ነው።
ስለዚህ ለምግብ ምንም ደንታ አልነበራቸውም።
Note.
==============እየዬም ሲዳላ ነው።
እንዲሉ።
(=========በዛ ሰኣት ከመከራው ከሞት
እንዴት እንዳን እንጂ ምግብ ትዝ አላላቸውም።)
የቀጠለ…………
======አሁን በምድር ላይ ለሚታገሉት ሰዎች አንቀላፍተው ያሉት የቅዱሳን ጸሎት አስፈላጊነትን ለመካድ
====“ከሞተ አንበሳ ያልሞተ ውሻ ይሻላል” ======ብሎ ቪጊላንቲየስ ለተነገረው ቅዱስ ጀሮም
እንደሚከተለው መልስ ሰጥቷል።
የቀጠለ…………
መልስ፦
"ሐዋርያትና ሰማዕታት ገና በሥጋ ሳሉ ፥ ለራሳቸው ሊጨነቁ ሲገባቸው ይልቅ፥ ስለሌሎች መጸለይ
ከቻሉ፣ አክሊላቸውን ሲቀዳጁ፥ ድል ሲነሡ፥ ካሸነፉ በኋላማ እንዴት አብልጠው አያደርጉ?
አንድ ብቻውን የሆነ ሰው ሙሴ ለስድስት መቶ ሺህ ለታጠቁ ሰዎች ብዙ ጊዜ ከእግዚአብሔር
ይቅርታን አሰጥቷል።
(ዘፀ. 30.32)፣ እና የጌታ ደቀመዝሙር እና የመጀመሪያው ክርስቲያን ሰማዕት እስጢፋኖስ፣
ለሚያሳድዱት ይቅርታን ለምኗል።
ታዲያ እነዚህ ሰዎች ወደ ክርስቶስ ወደ ሕይወታቸው ከሄዱ በኋላ ከበፊቱ ያነሰ ኃይል ይኖራቸዋልን?
ሐዋርያው ጳውሎስ በመርከብ ውስጥ ሁለት መቶ ሰባ ስድስት ነፍሳት እንደ ተሰጡት ይናገራል
(ሐዋ. 27.37)።
ከሞት በኋላ ወደ ክርስቶስ ከሄደ በኋላ ዝም ሊል ይችላልን?። በዓለም ሁሉ በወንጌሉ ላመኑት
አንዲት ቃል መናገር አይችልምን?
=======ያልሞተው ውሻ ቪጊላንቴዎስ ከሞተው አንበሳ ከጳውሎስ ይሻላልን?====...
እውነታው ግን፦ ቅዱሳን ተኝተዋል ተባለ እንጂ ሙታን አይባሉም" ።-========
የቀጠለ…………
ከዉስጥ “ጠብ፣ ክርክር አለ”፣ ከውጭም ፍርሃት አለ። (2ቆሮ7፡5) ስለዚህ እርሱ/ጳውሎስ/ እውነተኛ
አብራሪ ነበር።
መላ ሕይወታችንን ተመልከት፡-
የእኛም ሕይወት ልክ እንደዚህ ነው። (እንዲህ ዓይነት ጉዞ ነበረ)።
በአንድ ወቅት በደግነት፣ በሌላ ጊዜ በዐውሎ ነፋስ እንናወጣለን።
አንዳንድ ጊዜ ከራሳችን ምክር፣ አንዳንዴ ከሥራ ፈትነት፣ ቁጥር ወደሌለው ክፋት ውስጥ
እንወድቃለን።
ጳውሎስን ባለመስማት፣ እርሱ ወደ አልመራን ወደ ሌላ መሄድ ስንፈልግ ይህ ይከሰታል።
ጳውሎስ ያን ጊዜ እንደ ታሰረ ሳይሆን አሁን ከእኛ ጋር በመርከብ እየተጓዘ ነው።
አሁንም በዚህ ባህር ላይ ለሚጓዙ/ በዚህ ዓለም/ ሁሉ “ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። እያለ ይመክረናል።
ልማድ/experience፦
በልምድ አንማር (በእኛ ወጪ) ነገር ግን ከተሞክሮ በፊት “ጉዳት እና
ኪሳራን እናስወግድ”።
የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስ ከተናገረው ይልቅ የመርከብ መሪውንና
የመርከቡን ባለቤት ያምን ነበር። ሐዋ.ሥ. 27፡11
የመርከቡ መሪ እና የመርከቡ ባለቤት የቅዱስ ጳዉሎስን ምክር
አልሰማ ብለው በራሳቸው ተሞክሮ እና ልምድ ተጉዘው ትልቅ ኪሳራ ዉስጥ
ገቡ።
የራሳቸዉንም ህይወት እስከ ማጣት ደረሰ።
“ሀብታሞች ሊሆኑ የሚወዱ ወደ ፈተና ይወድቃሉ” የሚለውን ስሙ። (1 ጢሞ.6፡9.)
የቀጠለ…………
አትፍራ፥ ቀበሮዎች አንበሶችን እንደሚፈሩ። (ክፉ ሰው) የቅዱሳንን መንገድ ይፈራል። “ጻድቅ እንደ አንበሳ ደፋር
ነው” ይላልና። (ምሳ. 28፡1
1) እነዚያን አንበሶች ወደ ቤታችን እናምጣቸው፥ አራዊትም ሁሉ ይሸሻሉ።
አንበሶች ማገሳት አያስፈልጋቸውም፣ ነገር ግን በቀላሉ ድምፃቸውን ሲያሰሙ ሌላው አራዊት ይሸሻል።
አራዊትን ለማባረር አንበሳ ያን ያህል ጩኸት ማሰማት አይጠበቅበትም፤ ትንሽ ድምጽ ሲያሰማ/ ሲያጉረመርም
ይፈራሉ።
ልክ እንደዚሁ የጻድቅ ጸሎት ክፉ መናፍስት እንዲሸሹ ያደርጋል።
ወደ ቤትህ መጥተው መቀበል ባትችል እንኳ። አንተ ወደ እነሱ ሂድ። ከእነሱ ጋር ኑር። በማደሪያቸውም እደር።
በዚያዉም ትደሰታለህ፣ በረከትም ታገኛለህ።
ታላቁ ነገር ከቅዱሳን በረከት ማግኘት ነውና። በቅዱሳን መባረክ ነዉና።
የቅዱሳን ጸሎታቸው ከእግዚአብሔር ምህረት ያስገኝልናል።