Professional Documents
Culture Documents
ከአስቸኳይ ህክምና በኋላ
ከአስቸኳይ ህክምና በኋላ
ታህሳስ/2014
መግቢያ
1
በተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁጥር 799/2005 አንቀጽ 27 መሠረት የግልም ሆኑ የመንግስት
የሕክምና ተቋማት ለተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች እስከ 2,000 /ሁለት ሺህ/ ብር ነፃ ህክምና አገልግሎት እንዲሰጡ
በተደረገው ጥረት በአሁኑ ጊዜ መሻሻሎች እየታዩ መሆኑን ከተቋማት ጋር በተደረገው ግምገማ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ነገር ግን ከአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት በኋላ ተኝተውም ሆነ በተመላላሽ ህክምና በተሽከርካሪ አደጋ ጉዳት
የደረሰባቸው ተጎጂዎች ህክምናውን በራሳቸው ወጪ አገልግሎት አግኝተው ተመላሽ ብር(ተገቢ ካሳ) በኢንሹራንስ
ኩባንያዎች ወይም በመድን ፈንድ አገልግሎት እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር መጠየቅና ማግኘት እንደሚችሉ በአዋጅ
የተሰጣቸው መብት ቢሆንም በተጎጂዎች ግንዛቤ እጥረት እና ተቋማት ለዚህ ተገቢውን ትኩረት ባለመስጠት
በተፈለገው መጠን ውጤታማ ነው ማለት አይቻልም፡፡
በሌላ መልኩ ተጎጂዎች የተሻለ ህክምና ከፍለው አገልግሎት ለማግኘት እና በኋላ ተመላሽ ለመጠየቅ አቅም
የሌላቸው ስለሚበዙና አዋጁም ሲወጣ ተሽከርካሪዎች የ 3 ኛ ወገን መድን ሽፋን እንዲገቡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት
በ 3 ኛ ወገን ላይ ለሚያደርሱት አደጋ ተገቢውንና ተመጣጣኝ አገልግሎት እንዲያገኙ ታሳቢ ተደርጎ የወጣ ስለሆነ
በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ በመንግስትም ሆኑ በግል የህክምና ተቋማት አስቸኳይ ህክምና አገልግሎት ካገኙ በኋላ እስከ
40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ ተገቢውን የህክምና አገልግሎት እንዲሰጡ በማድረግ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና
ማህበራዊ ችግር ለመፍታትና ይህንንም አሰራር አንድ ወጥ በሆነ መልኩ ወደ ክልሎች ለማውረድ በማስፈለጉ
በኢንሹራንስ ኩባንያዎች፣ በጤና ሚኒስቴር፣በፌዴራል ፖሊስ፣በህክምና ተቋማት፣በኢትዮጵያ የምግብ፣የመድሀኒትና
የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን እና በመድን ፈንድ አገልግሎት መካከል የጋራ ስምምነት ሰነድ ማዘጋጀት
አስፈልጓል፡፡
1 የስምምነቱ አላማ
ሁሉም የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች ከአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት በኋላ የተሻለ ህክምና ግልጋሎት እንዲያገኙ
ቁልፍ ሚና ያላቸው ባለድርሻ አካላት የየራሳቸውና በጋራ የሚፈጽሟቸው ስራዎች ላይ የተቀናጀ አሰራርና ቅልጥፍና
እንዲኖርማድረግ፡፡
የህክምና ተቋማት ለተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች ለሚሰጡት ሕክምና ተገቢውን ተመላሽ ብር እንዲያገኙ እና
የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎችን ለመርዳት በተነሳሽነት እንዲሰሩ በተቋማቱ መካከል የተሳለጠ የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር
በማድረግ አዋጁን በተገቢው መንገድ ተፈፃሚ እንዲሆን ለማድረግ ነው፡፡
2 የስምምነቱ አስፈላጊነት
1.የህክምና ተቋማት የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎችን እስከ 2,000 /ሁለት ሺህ/ ብር ድረስ በነፃ ካከሙ በኋላ ህክምናው
እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ በመነጋገር ለመቀጠል በተነሳሽነት እንዲሰሩ ወጪያቸውን የሚያስመልሱበትን
አሰራር መዘርጋት በማስፈለጉ፣
2.በስምምነቱ አካላት መካከል ቅንጅታዊ አሰራርን ለመፍጠር፣
3.አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ጉዳዮችን በመነጋገር እልባት እንዲያገኙ ለማስቻል ናቸው፡፡
3 የስምምነቱ አካላቶች
ኢንሹራንስ ኩባንያዎች፣ጤና ሚኒስቴር፣ፌዴራል ፖሊስ፣ህክምና ተቋማት፣የኢትዮጵያ የምግብ፣የመድኃኒትና የጤና
ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን እና የመድን ፈንድ አገልግሎት ናቸው፡፡
2
1.በደንበኞቻቸው ተሽከርካሪዎች ጉዳት የደረሰባቸው ተጎጂዎች በመንግስትም ሆነ በግል የህክምና ተቋማት እስከ ብር
2,000 /ሁለት ሺህ/ ድረስ ነፃ የአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት ካገኙ በኋላ በመነጋገር የቀጠለውን የህክምና አገልግሎት
ወጪ እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ ተመላሽ የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡
2.በደንበኞቻቸው ተሽከርካሪ የተጎዱ ተጎጂዎች የህክምና አገልግሎት ወጭ ከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር በታች ከሆነ
ቀሪውን የሞት እና የአካል ጉዳት ካሳ ውስጥ አካተው ለተጎጂው ወይም ለተጎጂው ቤተሰቦች የመካስ ግዴታ አለባቸው፡፡
3.በደንበኞቻቸው ተሽከርካሪ የተጎዱ ተጎጂዎች ከአንድ የህክምና ተቋም በላይ አገልግሎቱን ሊያገኙ ስለሚችሉ
የሚከፈለው (ተመላሽ) የሚደረገው ክፍያ የሁሉንም ተቋማት ወጪ በድምሩ እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር መሸፈን
አለበት፡፡
4.ተጎጂው ህክምናውን ከጨረሰ ወይም ህይወቱ ካለፈ ደረሰኞች ከህክምና ተቋሙ ሲመጡለት በደረሰኞቹ መሰረት
የወጣውን ወጪ እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ ተመላሽ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
5.የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂ በዱቤ ህክምና እያገኘ መሆኑን ተጎጂዉ ወይም ህክምና ተቋሙ ሲያሳውቀው በስሙ ፋይል
በመክፈት ለህክምና ተቋሙ ተመላሽ ለማድረግ ዝግጁ ሆኖ መጠበቅ አለበት፡፡
6.በተራ ቁጥር 5 ላይ በተገለፀው መሠረት ለህክምና ተቋሙ የተጠየቀውን ክፍያ ሳይከፍል ለተጎጂው ወይም ለተጎጂ
ቤተሰብ ክፍያ መፈፀም የለበትም፡፡
7.ኢንሹራንስ ኩባንያው ለመንግስትም ሆነ ለግል ህክምና ተቋማት እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ ለሰጡት የዱቤ
ህክምና አገልግሎት ክፍያ ለመፈፀም ደረሰኞች እና ማስረጃዎች እንዲቀርቡለት የመጠየቅ መብት አለው፡፡
8.የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች ነፃ አስቸኳይ ህክምና አገልግሎት ካገኙ በኋላ ቀጣዩን እስከ አርባ ሺህ ብር ህክምና
ከኢንሹራንስ ካምፓኒዎች ወይም ከመድን ፈንድ አገልግሎት ጋር በመነጋገር መቀጠል እንደሚችሉ ለህብረተሰቡ
ግንዛቤ ይሰጣል፡፡
9.ለህክምና ተቋማት ተመላሽ ስለተደረጉ ከአስቸኳይ ህክምና በኋላ እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ የህክምና
ወጪዎች ሪፖርት በየወሩ ለመድን ፈንድ አገልግሎት ይልካል፡፡
10.ኢንሹራንስ ኩባንያው የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች ከአስቸኳይ ህክምና በኋላ እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ
የህክምና ወጪ ከህክምና ተቋማት በሚቀርበው ደረሰኝ መሠረት ተመላሽ በኢንሹራንሱ እየተደረገላቸው ስለመሆኑ
የሚከታተል ኃላፊ (focal person) በመመደብ ክትትል ያደርጋል ይህ ኃላፊም ኤጀንሲው በየወሩ በሚያዘጋጀው
ስብሰባ ላይ ሪፖርት ያቀርባል፡፡
3
5.የግልም ሆኑ የመንግስት የህክምና ተቋማት ለተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች ከአስቸኳይ ህክምና በኋላ እስከ 40,000 /አርባ
ሽህ/ ብር ድረስ የህክምና አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንና ሆስፒታሎቹ ለሰጡት አገልግሎት እና ላወጡት ወጪ በወቅቱ
ከኢንሹራንስ ኩባንያዎች እና ከመድን ፈንድ አገልግሎት ተመላሽ እየተደረገላቸው መሆኑን ይከታተላል ችግር ካለም
ከተቋማት ጋር ሆኖ መፍትሄ እንዲያገኝ ይሰራል፡፡
6.መረጃ ያደራጃል እንዲሁም ያሳውቃል፡፡
4
2. በተሽከርካሪ አደጋ የተጎዳን ሰው አስቸኳይ ህክምና አገልግሎት ከጨረሰ በኋላ በተመላላሽነትም ሆነ አስተኝተው
ተጎጂዉን እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ በተገቢው መንገድ የማከም ግዴታ አለባቸው፡፡
3. በተቋማቸው የሰጡት ሕክምና በቂ ካልሆነ ወደ ተሻለ ህክምና ተቋም በእነርሱ የተጠቀመውን የብር መጠን በመግለጽ
ሪፈር ማድረግ አለባቸው፡፡ሪፈር ያደረጉበትም ደብዳቤ ወደ ሚመለከተው ኢንሹራንስ ተቋም ወይም ወደ መድን
ፈንድ መላክ ይኖርበታል፡፡
4. ማንኛውም የሕክምና ተቋም ለሚሰጠው የተመላላሽነትም ሆነ ተኝቶ የመታከም አገልግሎት እንደጀመረ ለመድን
ፈንድ አገልግሎት ወይም ለሚመለከተው ኢንሹራንስ ኩባንያ በወቅቱ ሪፖርት ማድረግ አለበት፡፡
5.የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች ህክምና ጉዳይ የሚከታተልና መረጃ ከተቋማት ጋር የሚለዋወጥ ባለሙያ (focal person)
የመመደብ ግዴታ አለባቸው፡፡
6. በየደረጃው ያሉ የህክምና ተቋማት አመራሮች፣ ሙያተኞችና ሰራተኞች በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ እና ህክምና
እንዲሰጡ ማድረግ አለባቸው፡፡
7.በየደረጃው ያሉ የህክምና ተቋማት ከአስቸኳይ ህክምና በኋላ እስከ 40,000 /አርባ ሺህ/ ብር ድረስ ለተሽከርካሪ አደጋ
ተጎጂዎች መስጠትን በተመለከተ በየወሩ ሪፖርት ለመድን ፈንድ አገልግሎት መላክ እንዲሁም መስሪያ ቤቱ በየወሩ
በሚያካሂደው ስብሰባ ላይ መሳተፍም ይኖርባቸዋል፡፡
5
6.ስለ አገልግሎቱ ለህብረተሰቡ እና ለባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ይሰጣል፡፡
12 ስምምነቱ የሚፀናበት ጊዜ
በዚህ መግባቢያ ሰነድ የተገባ ስምምነት በሚመለከታቸው አካላቶች ከተፈረመበት ቀን ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡