Professional Documents
Culture Documents
18 2013 3 2
18 2013 3 2
1. አጭር ርዕስ
2. ትርጓሜ
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠዉ ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ዉስጥ፡-
1. “አዋጅ” ማለት የሃብት ማሳወቅ እና ምዝገባ አዋጅ ቀጥር 668/2002 ነው፣
2. “ኮሚሽን ወይም ኮሚሽነር” ማለት እንደ ቅደም ተከተላቸው የፌዴራል
የስነምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን እና የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ነው፣
3. ‘‘ሃብት'' ማለት ማንኛውም ተንቀሳቃሽ ወይም የማይንቀሳቀስ ግዙፍነት
ያለው ወይም ግዙፍነት የሌለው ንብረት ሲሆን ይህም የመሬት ይዞታ፣ ህጋዊ የዕዳ
ስምምነትን፣ በባንክ ያለ ሃብት፣ ገቢ እና ጥቅም የሚያስገኝ ባለቤትነትን
ያካትታል፣
ክፍል አንድ ፡- ጠቅላላ
2. ትርጓሜ….
4. ‘‘ሃብት ምዝገባ'' ማለት በሃብት ማሳወቅ እና ምዝገባ አዋጅ አንቀጽ 4 (1) እና (2)
በተገለጸው አግባብ እና በዚህ መመሪያ አንቀጽ 7 መሰረት ሃብት አስመዝጋቢው የራሱንና
የቤተሰቡን ሃብት፣ የገቢ ምንጭ የሚያሳውቅበት እና የሚያስመዘግብበት አሰራር ነው፣
2. ትርጓሜ…..
6. ‘‘ሃብት የሚያሳውቅ ሰው ወይም ሃብት አስመዝጋቢ'' ማለት በሃብት ማሳወቂያና
ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 እና በተሻሻለው የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ
አዋጅ በተደነገገዉ መሰረት ማንኛውም ሃብት የሚያሳውቅና የሚያስመዘገብ
ግዴታ ያለበት ማንኛውም ተሿሚ፣ የህዝብ ተመራጭ፣ በመንግስት መስሪያ ቤት፣
በመንግስት ልማት ድርጅት እና በህዝባዊ ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ ወይም ተመድቦ
በቋሚነት ወይም በጊዜዊነት ከ3 ወር በላይ ለተራዘመ ጊዜ የሚሰራ ሠራተኛ
ነው።
ክፍል አንድ ፡- ጠቅላላ
2. ትርጓሜ …..
2. ትርጓሜ……
8. “አገልግሎት ማቋረጥ” ማለት አንድ ሃብት አስመዝጋቢ በመስሪያ ቤቱ ሃብቱን
ካስመዘገበ 6 ወር እና ከዛ በላይ ሲሰራ ቆይቶ በማንኛውም ሁኔታ መስሪያ ቤቱን
ሲለቅ ሃብት እና የገቢ ምንጩን የሚያስመዘግብበት ሥርዓት ነው፣
9. “ዋና መዝገብ ወይም ባህር መዝገብ” ማለት ሃብት ምዝገባ ተፈፃሚ
የሚሆንባቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ የመንግስት ልማት ድርጅቶች እና
ህዝባዊ ድርጅቶች ውስጥ ሃብት ማስመዝገብ ያለባቸውን አስመዝጋቢዎች በሥራ
መደብ እና ስም ዝርዝር እንዲይዝ በተለይ የተዘጋጀ ወይም የተደራጀ መረጃ ነው፣
ክፍል አንድ ፡- ጠቅላላ
2. ትርጓሜ….
10.“የሃብት ማሳወቅ እና ምዝገባ አሠራር” ማለት የሃብት ማሳወቅ እና
ምዝገባን፣ የሃብት ምዝገባ መረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጥን እና የሃብት ምዝገባ
መረጃ ለህዝብ ተደራሽ የሚያደረግበትን ሂደት የሚያጠቃልል ተግባር ነው፣
2. ትርጓሜ
12. “የሃብት ምዝገባ መረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጥ” ማለት በኮሚሽኑ የሃብት
ማሳወቅ እና ምዝገባ ዳይሬክቶሬት ሃብት የሚያሳውቀው ግለሰብ የሰጠው መረጃ
የተሟላ፣ እውነተኛ፣ የአኗኗር ደረጃው ካስመዘገበው ሀብትና የገቢ ምንጭ ጋር፣
የገቢ ሁኔታው ካስመዘገበው ሃብት እና የገቢ ምንጭ ጋር የሚጣጣም መሆኑን
ለማረጋገጥ የሚያከናወን ሂደትን የሚመለከት ነው፣
13.“የሃብት ምዝገባ ትክክለኛነት ቅድመ-ማረጋገጥ” ማለት በሃብት ምዝገባ
ወቅት የሃብት ምዝገባ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ከመሰጠቱ በፊት መረጃው
በትክክል እና በተሟላ ሁኔታ ስለመሞላቱ እና በሁሉም ገፆች ላይ የሐብት
አስመዝጋቢው ፊርማ ያረፈበት ስለመሆኑ በኮሚሽኑ የሚረጋገጥበት ሂደት ነው፣
ክፍል አንድ ፡- ጠቅላላ
2. ትርጓሜ….
14. “የሃብት ምዝገባ መረጃን ለህዝብ ክፍት ማድረግ” ማለት በጽሁፍ በሚቀርብ
ጥያቄ መሰረት ተመዝግቦ በኮሚሽኑ እጅ የሚገኝ የሃብት ምዝገባ መረጃ
ለሚጠይቅ ሰው ወይም ተቋም ለጠያቂው ተደራሽ የሚደረግበት አሰራር ሲሆን
የሚሰጠው መረጃ በሃብት ማሳወቅና ምዝገባ አዋጅ አንቀጽ 12(4) እና በዚህ
መመሪያ በአንቀፅ 13(1) መሠረት በሚስጥር ተጠብቀው እንዲቆዩ የተለዩትን
የሃብት አስመዝጋቢውን ቤተሰብ ሃብትና የገቢ ምንጭ መረጃን አይጨምርም፣
15. “የፌደራል ተቋማት” ማለት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል በመንግስት በጀት
የሚተዳደሩ የፌደራል መንግስት መስሪያ ቤቶች እና የፌደራል ልማት ድርጅቶችን
ይጨምራል፤
ክፍል አንድ ፡- ጠቅላላ
2. ትርጓሜ…..
16. “የመንግስት መስሪያ ቤት” ማለት በጀቱ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል
በመንግስት በጀት የሚተዳደር እና የፌዴራል መንግስቱ ስራዎች የሚከናወኑበት
ማንኛውም መስሪያ ቤት ነው፣
2. ትርጓሜ…..
18.“ህዝባዊ ድርጅት’’ ማለት በማንኛውም አግባብ ከአባላት ወይም ከህዝብ
የተሰበሰበ ወይም ለህዝባዊ አገልግሎት ታስቦ የተሰበሰበ ገንዘብ፣ ንብረት ወይም
ሌላ ሃብትን የሚያስተዳደር አካልንና አግባብነት ያለው ኩባንያን የሚያካትት የግል
ዘርፍ ሲሆን የሃይማኖት ድርጅትን፣የፖለቲካ ድርጅትን(ፓርቲን)፣ የዓለም አቀፍ
ድርጅት እና ዕድርንና ተመሳሳይ ባህላዊ ወይም ሃይማኖታዊ ይዘት ያለው
ማህበርን አያካትትም።
ክፍል አንድ ፡- ጠቅላላ
2. ትርጓሜ…...
19.“ጥቆማ” ማለት በሃብት ምዝገባ መረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጥ ሂደት
ውስጥ ሃብት አስመዝጋቢው ያላስመዘገበው እና የደበቀው ሃብት መኖሩን ወይም
ሀሰተኛ የሃብት መረጃ መመዝገቡን አስመልክቶ ከማንኛውም ዜጋ በፅሁፍ በስልክ፣
በቃል፣ በኮሚሽኑ ፋክስ፣ በድረ ገፅ ወይም በሌላ በማንኛውም መገናኛ ዘዴ
የሚሰጥ መረጃ ማለት ነው፣
ክፍል አንድ ፡- ጠቅላላ
2. ትርጓሜ….
20. “ቤተሰብ” ማለት የተሿሚ፣ የህዝብ ተመራጭ ወይም የመንግስት ሠራተኛ
የትዳር ጓደኛ ወይም በስሩ የሚተዳደር ዕድሜው 18 ዓመት ያልሞላ ልጅ
ሲሆን፤ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ የሚኖር ሰው እና የጉዲፈቻ
ልጅን ይጨምራል፡፡
21. “ሰው” ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል
ነው፡፡
ክፍል አንድ ፡- ጠቅላላ
3. የፆታ አገላለፅ
በዚህ መመሪያ ውስጥ በወንድ ፆታ የተገለጸው ለሴት ፆታም ያገለግላል፡፡
4. የተፈፃሚነት ወሰን
6.6. ኮሚሽኑ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀፅ 6.5 በተደነገገው መሠረት ሃብትና
የገቢ ምንጭ የማስመዝገብ እና የማሳወቅ ግዴታ የተጣለባቸውን የፌደራል
ተቋማት እና የህዝባዊ ድርጅት ሀብት አስመዝጋቢዎችን ሃብትና የገቢ
ምንጫቸውን ሳያስመዘግቡ እና ሳያሳውቁ ሥራ ያስጀመረ የተቋም ኃላፊ እና
የሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ ክፍል ኃላፊን አግባብ ባለው ህግ ተጠያቂ ያደርጋል፣
ክፍል ሁለት፡- ስለሃብት ምዝገባ
6.10. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 6.9 በተደነገገው መሠረት የተቋሙ ሃላፊዎችና
ሠራተኞች በማንኛውም ምክንያት ተቋሙን ሲለቁ ኪሊራንስ ከመውሰዳቸው
በፊት ሃብትና የገቢ ምንጫቸውን የማሳወቅና የማስመዝገብ ግዴታ አለባቸው፣
ክፍል ሁለት፡- ስለሃብት ምዝገባ
6. የሃብት ምዝገባ ቅድመ ዝግጅት
6.11. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 6.10 በተደነገገው መሠረት የሥራ ሃላፊዎችና
ሠራተኞች በማንኛውም ምክንያት ተቋሙን ሲለቁ ኪሊራንስ ከመውሰዳቸው
በፊት ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ያላደረገ ማንኛውም የፌደራል ተቋማት እና
የህዝባዊ ድርጅት ኃላፊ እና የሰው ሃብት አስተዳደር ሥራ ክፍል ኃላፊ አግባብ
ባለው ህግ መሰረት ተጠያቂ ይሆናሉ፣
6.12. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 6.10 በተደነገገው መሠረት የሥነ ምግባር
መከታተያ ክፍሉ የሥራ ሃላፊዎች እና ሠራተኞች በማንኛውም ምክንያት
ሲያገለግሉበት ከነበረው ተቋም ሲለቁ ኪሊራንስ ከመውሰዳቸው በፊት
በተቋማቸው በአካል በመቅረብ ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ የማድረግ ግዴታ
አለበት፤
ክፍል ሁለት፡- ስለሃብት ምዝገባ
8.2. በዚህ አንቀፅ በንዑስ አንቀፅ 8.1 መሰረት ሃብታቸውን በተገለፀው ቀነ-
ገደብ ቀርበው ያላስመዘገቡ ሃብት አስመዝጋቢዎችን የሥነ ምግባር መከታተያ
ክፍል ስም ዝርዝራቸውን በማስታወቂያ ሰሌዳ ወይም በሌላ አመች ዘዴ
ያሳውቃል፡
ክፍል ሁለት፡- ስለሃብት ምዝገባ
8.3. የሥነ ምግባር መከታተያ ክፍል በዚህ አንቀፅ በንዑስ አንቀፅ 8.2 በወጣው
ማስታወቂያ መሠረት ሀብት አስመዝጋቢዎች ሀብታቸውን ሳያስመዘግቡ
የቆዩበትን አሳማኝ ምክንያት ካላቸው ይህንኑ የሚገልፀ ማስረጃ በጽሑፍ
አያይዘው እንዲያቀርቡ ያደርጋል፤
ክፍል ሁለት፡- ስለሃብት ምዝገባ
8. የሃብት ምዝገባና የቀነ ገደብን ስለማራዘም
8.7. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 8.6 መሰረት ኮሚሽኑ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ
ቅጣቱን ከፍሎ ሳያስመዘግብ የቀረን ሀብት አስመዝጋቢ በህግ የመመርመርና
የመክሰስ ስልጣን ለተሰጠው አካል ያስተላልፋል፡፡
ክፍል ሁለት፡- ስለሃብት ምዝገባ
9.3. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 9.2 በተደነገገው መሰረት ኮሚሽኑ የተረከበውን
የመጀመሪያ ወይም የዕድሳት ቅፅ በትክክል መሞላቱን ሲያረጋግጥ በ5 የሥራ ቀናት
ውስጥ የሀብት ምዝገባ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የመስጠት ግዴታ አለበት፣
ክፍል ሁለት፡- ስለሃብት ምዝገባ
9. የሀብት ምዝገባ ትክክለኛነት ቅድመ ማረጋገጥ
9.4. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 9.1 ላይ የተጠቀሱት አንድ ወይም ከዚያ በላይ
መስፈርቶች ያልተሟሉ ከሆነ ኮሚሽኑ ያልተሟሉ መረጃዎችን በዝርዝር
በመጥቀስ እንዲስተካከሉ ቅፁ ከኮሚሽኑ ጽ/ቤት ከደረሰበት ቀን ጀምሮ ባሉት 3
ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ለተቋሙ የሥነ ምግባር መከታተያ ክፍል
የመመለስ ግዴታ አለበት፣
10.5 በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 10.2 መሠረት ሃብት አስመዝጋቢው በተሰጠው
5 የሥራ ቀናት ውስጥ የሃብት ምዝገባ ቅጹን ሞልቶ ማስረከብ ካልቻለ ተጠያቂ
እንዲሆን ኮሚሽኑ በህግ የመመርመርና የመክሰስ ስልጣን ላለው አግባብነት ላለው
አካል ያስተላልፋል፡፡
ክፍል ሦስት፡- የሃብት ምዝገባ መረጃን ትክክለኛነት ስለማረጋገጥ
14.2. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 14.1 መሠረት የኮሚሽኑ የግዥ፣ ፋይናንስና
ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የባንክ ዋናው ስሊፕ/ደረሰኝ/ እንደደረሰው የገቢ
ደረሰኝ በመቁረጥ ለተቀጭው ይሰጣል፣
14.3 የኮሚሽኑ የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቅጣት
ከከፈሉ ሃብት አስመዝጋቢዎች የተረከበውን ዋናው ስሊፕ/ደረሰኝ/ በማደራጀት
መረጃውን ይይዛል፡፡ በሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ዳይሬክቶሬት በተጠየቀ ጊዜ መረጃውን
የመስጠት ግዴታ አለበት፣
14.4 የኮሚሽኑ የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በዚህ
አንቀፅ በንዑስ አንቀፅ 14.1 እና 14.2 መሠረት ገቢ የተደረገውን የቅጣት ገንዘብ ከዋናው
ስሊፕ/ደረሰኝ/ ጋር በማስታረቅ በየወሩ ለገንዘብ ሚኒስቴር ፈሰስ ያደርጋል፡፡ ስለ አፈፃፀሙም
ለሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ዳይሬክቶሬት ያሳውቃል፡፡
15. የመተባበር ግዴታ
ማንኛውም ሰው የሃብት ማሳወቅና ማስመዝገብ አዋጅ ቁጥር 668/2002 እና
አዋጁን ለማስፈፀም የወጣውን ይህን የአፈፃፀም መመሪያ ኮሚሽኑ
በሚያስፈፅምበት ወቅት መረጃ የመስጠትና የመተባበር ህጋዊ ግዴታ አለበት፡፡
16. ስለ ቅጣት
የሀብት ምዝገባ አዋጅንና አዋጁን ሥራ ላይ ለማዋል የወጣውን ይህንን መመሪያ
በመፈጸም ሂደት ላይ የመተባበር ህጋዊ ግዴታዉን ያልተወጣ ማንኛውም ሰው
አግባብነት ባለው የወንጀል ህግ መሰረት ተጠያቂ ይሆናል፡፡
17. የቅሬታ አቀራረብ
ፀጋ አራጌ
የፌዴራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሸነር
እናመስግናለን!!