Professional Documents
Culture Documents
Zed
Zed
-
የአማርኛ ቋንቋ እና ስነ ጽሑፍ ትምህርት ክፍል
በ
ዘመድ ፀጋየ
ጥር 2013 ዓ.ም.
ዲላ ኢትዮጵያ
'
በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ ያኣ ግቢ በ 2012 ዓ.ም አገልግሎት ላይ የዋሉ ማስታወቂያ ፅሁፎች ቋንቋ
አጠቃቀም
ትንተና
በዲላ ዩኒቨርሲቲ
የማህበራዊ ሳይንስና ሂውማኒቲስ ኮሌጅ
የአማርኛ ቋንቋ እና ስነ-ጽሑፍ ትምህርት ክፍል
በ
ዘመድ ፀጋየ
ጥር 2013 ዓ.ም
ዲላ ኢትዩጵያ
አማካሪ
መ/ር
ኢሳያስ ይልማ
የፈተና ቦርድ አባላት
i
ማዉጫ
ይዘት ገፅ
ምስጋና.................................................................................................................................................i
ማዉጫ...............................................................................................................................................ii
አጠቃሎ...............................................................................................................................................v
ምዕራፍ አንድ.....................................................................................................................................1
1 መግቢያ...........................................................................................................................................1
1.1 የጥናቱ ዳራ...............................................................................................................................1
1.2 የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት..................................................................................................................3
1.3 የጥናቱ አላማ...............................................................................................................................3
1.4 የጥናቱ ጠቀሜታ..........................................................................................................................3
1.5 የጥናቱ ክልል እና ገደብ................................................................................................................4
1.6 የጥናቱ ዘዴ.................................................................................................................................4
1.6.1 የናሙና አመራረጥ ዘዴ............................................................................................................4
1.6.2 የመረጃ መተንተኛ ዘዴ.............................................................................................................4
1.6.3 የመረጃ መተንተኛ ዘዴ.............................................................................................................5
ምዕራፍ ሁለት....................................................................................................................................5
2. ክለሳ ድርሳናት.................................................................................................................................5
2.1 የማስታወቂያ ምንነት................................................................................................................5
2.2 የማስታወቂያ አጀማመር............................................................................................................6
2.3 የማስታወቂያ አይነቶች..............................................................................................................7
2.4 የማስታወቂያ አገልግሎት............................................................................................................7
2.4.1. ማሳሰብ..............................................................................................................................7
2.4.2.ማሳመን.............................................................................................................................8
2.4.3. መገፋፋት..........................................................................................................................8
2.4.4.ማስታወስ..........................................................................................................................8
2.5 የቃላት አጠቃቀም.....................................................................................................................8
2.5.1 መደበኛ የቃላት አጠቃቀም ደረጃ..........................................................................................9
2.5.2 ኢ መደበኛ የቃላት አጠቃቀም ደረጃ......................................................................................9
2.6 የቃላት ምርጫ........................................................................................................................11
2.6.1 እማሬያዊ ፍች..................................................................................................................11
2.6.2 ፍካሬያዊ ፍች..................................................................................................................11
2.7 የሰዋስው ምንነት.....................................................................................................................11
2.7.1 የቁጥር ስምምነት.............................................................................................................12
2.7.2 የጾታ ስምምነት................................................................................................................12
2.7.3 የመደብ ስምምነት............................................................................................................13
2.7.4 የጊዜ ስምምነት................................................................................................................13
2.7.5 የስርዓተ ነጥብ አገልግሎት..................................................................................................15
2.8 የተዛማጅ ፅሁፍ ቅኝት..............................................................................................................15
ምዕራፍ ሦስት..................................................................................................................................17
ii
3. መረጃ ትንተና..............................................................................................................................17
3.1 የቃላት አጠቃቀም ችግር ትንተና......................................................................................................17
3.1.1 የጉራማይሌ ቃላት አጠቃቀም..................................................................................................17
3.1.2 የዘዬ (ቀበልቻ) ቃላት አጠቃቀም..............................................................................................18
3.1.3 የድረታ ችግር......................................................................................................................19
3.1.4 የሙያ ቃላት አጠቃቀም.........................................................................................................20
3.1.5 ድግግሞሽ...........................................................................................................................20
3.2 የሰዋሰውአጠቃቀም ስህተት ትንተና.................................................................................................21
3.2.1 የቁጥር ስምምነት..................................................................................................................21
3.2.2 የመደብ ስምምነት................................................................................................................22
3.2.3 የስርዓተ ነጥብ አጠቃቀም.......................................................................................................23
3.3 ምስል ከሳች እና ታዋሽነት..............................................................................................................25
ምዕራፍ አራት......................................................................................................................................26
4. ማጠቃለያና አስተያየት.......................................................................................................................26
4.1 ማጠቃለያ.................................................................................................................................26
4.2 አስተያየት.................................................................................................................................27
ዋቢ ፅሑፎች.......................................................................................................................................28
ጥቅሶች በመገኛ ቋንቋቸው.......................................................................................................................29
አባሪ 1..............................................................................................................................................30
iii
አጠቃሎ
የዚህ ጥናት ዋና አላማ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ አገልግሎት ላይ የዋሉ የማስታወቂያ ፅሁፎች የቋንቋ
አጠቃቀምን ተንትኖ ማሳየት ነው። ጥናቱ አመቺ የናሙ ናአመራረጥ ዘዴን በመከተል ተካሂዷል። የመረጃ
መሰብሰቢያ ዘዴዎችም ሰነድ ፍተሻ እና ያልታቀደ ምልከታ ናቸው። በተገኘው መረጃ መሠረትም የቋንቋ
አጠቃቀም፣ የቃላት ምስል ከሳችነት እና ታዋሽነት ሁኔታ እንዲሁም ሰዋሰዋዊ የቃላት አጠቃቀም
ተተንትነዋል። በዚህ ጥናት ማወቅ የተቻለው በቃላት አጠቃቀም የዘዬ (ቀበልኛ) ቃላትን ማዘውተር፣ ድረታ
እና ተደጋጋሚ ቃላትን የመጠቀም ችግር፤ ከሰዋሰው አንፃር ደግሞ የቁጥር እና የመደብ አለመስማማት
እንዲሁም ስርአተ ነጥብን በአግባቡ ያለ መጠቀም ችግር ያለበት መሆኑን ነው። እነዚህ ችግሮች ደግሞ
በማስታወቂያ አማካይነት መልዕክት ለአንባቢ በሚቀርብበት ወቅት መልዕክቱን ለማንበብ እና ለመረዳት
አዳጋች እንዳደረጉት ተደርሶባቸዋል።
iv
ምዕራፍ አንድ
1 መግቢያ
1.1 የጥናቱ ዳራ
የሠው ልጅ ሀሳቡን በፅሁፍ መግለፅ የጀመረው የዛሬ አምስት አመት ገደማ እንደነበር ይነገራል። ፅሁፍ ከመጀመሩ
ወይም ከመገኘቱ በፊትም ሠዎች ለብዙ ዘመናት ሀሳባቸውን፣ ስሜታቸውን፣ ወዘተ. ሲገልፁ የኖሩት በንግግር ነበር።
ፅሁፍ የሚታዩ እና የሚዳሰሱ ልማዳዊ ወይም ስምምነታዊ ምልክቶች አማካኝነት የሚቀርብ የንግግር ቋንቋን ቀርፆ
የማቆያ ስልት ነው(አብነት፣277) ።
የመጀመሪያው ፅህፈት ተጀመረ ተብሎ የሚነገረው በሱሜሪያውያን ህዝቦች አማካኝነት ሜሶፓታሜያ ውስጥ ሲሆን
የፅሑፉ መጠሪያ ኩኒፎርም ወይም የሽብልቅ ፅሁፍ በመባል ይታወቃል። ሌሎች ደግሞ ጥንታዊ ፅሁፍ በግብፃውያን
የተፃፈው ሔሮግራፊክስ የተሠኘው ነው ይላሉ። አንዳንዶች ደግሞ የአሜሪካኖች ኮሎምቢያ የዖልሜክ እና የማያን
ህዝቦች እንደጀመሩት እና አየዳበረ እንደመጣ ይታመናል በማለት አብነት (2007፣277) ገልፆታል።
ከዚሁ ጋር አያይዞ የስርዓተ ፅሕፈት አጀማመር እና እድገትን ያጠኑ ጠበብት እንደገለፁት ለዛሬዎቹ ልዩ ልዩ የፅሁፍ
የመሠረቶች ስዕላዊ ፅህፈት፣ ቀለማዊ ፅህፈት፣ ፊደላዊ ፅህፈት የተባሉት ደረጃ በጀረጃ እያደረጉ አሁን ካለበት
እንደደረሰ ያብራራሉ (አብነት 2007፣232) ።
ፅሁፍ ስርዓትን ተከትሎ መልዕክት ለአንባቢ የሚያደርሰው ቋንቋ የሚፈቅደውን የድምፆች፣ የቃላት፣ የሀረጋት፣
የዓአረፍተ ነገሮች፣ የአንቀፅ እና የድርሰት አገባብ ስርዓትን ማወቅ ሲቻል ነው። ይህ ካልሆነ ትርጉም አልባ መሆን እና
የትርጉም መለወጥን በማስከተል ትርጉም እንዲፋለስ ያደርጋል።
በፅሁፍ አማካኝነት ሀሳብን ለማስተላለፍ ደግሞ የፅሁፍ ስርዓቶችን ማወቅ እና መጠቀም ያስፈልጋል። ይሄንን
አስመልክቶ ሳሙኤል (1999) ባዩሬኒ (1988፣1)ን በመጥቀስ የሚከተለውን ሀሳብ አስፍሯል።
ሰንፅፍ እና ስንናገር ከምናወጣቸው ድምፆች ጋር የሚመሳሰሉ ምልክቶች ማለትም ፊደሎች
(የፊደሎችን ቅንጅት) እንጠቀማለን። በአንድ በኩል ፅህፈት የንግግር ድምፆችን የሚወክሉ
ምልክቶችን የመቅዳት እና በወረቀት ላይ የማስፈር ተግባር ነው ሊባል ይችላል፤ ነገር ግን የንግግር
ድምፆችን የሚወክሉ ምልክቶችን፣ ቃላትን፣ ዓረፍተ ነገሮችን ለመመስረት በቋንቋው ስርዓት
መሰረት ተቀናብረው መዋቀር (መሰደር) አለባቸው።
ከዚህም እንደምንረዳው ፅህፈት የራሱ ስርዓት ያለው ድምፆች ቃላትን፣ ቃላት ሀረጋትን፣ ሀረጋት ዓረፍተ ነገሮችን
መገንባት እና አረፍተ ነገሮችም ርስ በዕርሳቸው ተገናኝተው የቋንቋዉን ስርዓት መጠበቅ እንዳለባቸው ነው። ዐረፍተ
ነገሮች የተዛመዱ፣ የተከታተሉ እና የተቆራኙ ከሆነ የሀሳብ አንድነት እና ጥምረት ያለው ፅሁፍ መፃፍ ይቻላል።
በአጠቃላይ ፅሁፍ በአካል መግለፅ ማለትም በንግግር መልዕክትን ማስተላለፍ በማንችልበት ሁኔታ መልዕክትን
ለማስተላለፍ፣ ሀሳብን ቀርፆ ለትውልድ ለማቆየት፣ ዘመን ተሻጋሪነትን ለማጎልበት፣ ወዘተ ያገለግላል። ለምሳሌ
1
ደብዳቤዎች፣ መልዕክቶች፣ የተለያዩ የደስታም ሆነ ሀዘን መግለጫዎች፣ ትምህርታዊ ሰነዶች፣ መፅሄቶች፣ ጋዜጦች፣
ማስታወቂያዎች እና የመሳሰሉት ሁሉ የሚቀርቡበት የሚቀርቡት በፅሁፍ ነው።
በመሆኑም የዚህ ጥናት ዋና ትኩረት የሆነው በፅሁፍ ሀሳብ ከሚገለፅባቸው መንገዶች መካከል አንዱ የሆነው
የማስታወቂያ የቋንቋ አጠቃቀም ነው። የቀደሙ አባቶች ወይም ነገስታት ማስታወቂያ የሚውሉ የክተት ጥሪዎችን፣
የአዋጅ ነጋሪ ቃሎችን፣ የቤተክርስቲያን ደውሎችን፣ የከበሮና ፅናፅል ድምፆችን፣ ወዘተ. ሲሆን በአሁኑ ጌዜ ደግሞ
መስሪያ ቤቶች፣ ድርጅቶች (ግለሰቦች) ለጨረታ፣ ለቅጥር፣ ለደንብ እና ለትዕዛዛት ገለፃ፣ ለመሸጥ፣ ለመግዛት፣
ለመለወጥ፣ የጠፋን ለመፈለግ፣ አዳዲስ ምርቶችን ለማስተዋወቅ፣ ወዘተ. የሚጠቀሙበት ፅሁፍ ነው። በመሆኑም
ነገሮችን ለማስተላለፍ ግልፅ እና ለሰው እይታ በሚመች ቦታ ላይ በመለጠፍ፣ በጋዜጣ፣ በመፅሔት እና በመሳሰሉት ላይ
በመፃፍ እንዲሁም በዜና ማሰራጫዎች በሬድዮ፣ ቴሌቪዥን፣ በኢንተርኔት፣ ወዘተ. የሚያደርጉበት የሀሳብ መግለጫ
ነው (ባህሩ 2004፣122) ።
የማስታወቂያ መሰረተ ሀሳቦች ሲነሱ ብዙዎች የተለያዩ ትርጉም የሚሰጡ ተያያዥ ቃላት እና ሀሳባቸውን
ይሰነዝራሉ። ብዙውን (advertising) ሲነሳ የማሻሻጥ የእወቁልን እና የህዝብ ግንኙነት የሚሉትን ቃላት
በተለዋዋጭነት እንጠቀምባቸዋለን። ዳንኤል (200፣57) “እወቁልን የሚለው ሀሳብ ዕወቁ ብቻ ሳይሆን የማግባባት እና
የዕእመኑኝ ፍላጎትም አለበት። ዕወቁልኝ እነዚህ ባህሪያት ከማስታወቂያ ጋር እጅጉን ያቆራኙት እንጂ የልዩነት
ነጥቦችም አሉት፤ ዕወቁልኝ የመረጃ ምንጭ ሆኖ በማገልገል እጅጉን የቀረበ ነው።” በማለት ይገልፁታል።
ማስታወቂያ የአንድን ምርት፣ አገልግሎት (ሀሳብ) ለማስተዋወቅ ሲሆን ምርቶችን ለማማሻሻጥ ወይም አገልግሎትን
ለሰዎች ለማሳወቅ እና ረጅም የሚቆይ አመኔታን ለማምጣት የሚጠቅም ነው። ስለሆነም ማስታወቂያ በግል፣
በፓለቲካ ፓርቲዎችና እጩዎች፣ በማህበራዊ ተቋማት፣በጎ ፈቃደኛ ቡድኖች እና በመንግስት መስሪያ ቤቶች ጥቅም
ላይ ይውላል (ወርልድ ቡክስ ሳይክሎፒድያ 1994፣72) ።
ማስታወቂያን በሁለት መድበን ስንመለከት የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ወይም የብሮድካስት በማለት ልንለየው
እንችላለን። ከዚህ አመዳደብ በመነሳት የዚህ ጥናት ትኩረት የሆነው የፅህፈት ማስታወቂያ መነሻውም ከህትመት
ወገን ከሆኑት ማስታወቂያዎች ነው። ሳራ (1992፣269) “የህትመት ማስታወቂያ ሰፋ ያለ ቅርፅ ያለው እና ሠፊውን
ሽፋን የሚይዝ ነው። ስለሆነም አስተዋዋቂዎች ለመሳብ በሚፈልጉት ታላሚ አይነት ምስሎች፣ የድምፅ ቃና፣ የቋንቋ
አጠቃቀም እና የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ዘመቻዎችን ያከናውናሉ።” በማለት ገልፃዋለች። የህትመት
ማስታወቂያ በጋዜጣ፣ በመፅሄት፣ እንዲሁም በበራሪ ወረቀቶች የሚወጡ ማስታወቂያዎችን ይመለከታል። ከነዚህም
መካከል በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ ለተለያየ አገልግሎት የሚወጡ ማስታወቂያዎችን የቋንቋ አጠቃቀም
ይመረምራል።
1.2 የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት
የዚህ ጥናት አነሳሽ ምክንያት በዋናነት ሁለት ሲሆን የመጀመሪያው አጥኚዋ በሁለት አመት ቆይታዋ የሚወጡ
ማስታወቂያዎች ላይ የተሰሩ ስህተቶችን በማየቷ ነው። ይህም ማለት በኦዳ'ያኣ ግቢ በየቦታው ተለጥፈው
2
የምንመለከታቸውና የምናነባቸው ፅሁፎች በአብዛኛው የቃላት አጠቃቀም እና ምርጫ፣ የቋንቋ ሰዋሰው አጠቃም
ችግር፣ ወዘተ. እንከኖች ይታዩበታል። በመሆኑም ይህንን ችግር በጥናት ለመመርመር መታሰቡ ነው። ሁለተኛው
ምክንያት ደግሞ በቤተ መዛግብት፣ በቤተ መፅሀፍት እና አጥኚዋ በእስካሁኑ ቆይታዋ የተለያዩ መመረቂያ ፅሁፍ
ስታነብ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ኣያ ግቢ ማስታወቂያዎች የቋንቋ አጠቃቀም ላይ የተሰራ ጥናትና ምርምር
ስላላጋጠማት ነው ። ስለዚህ እነዚህ ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ጥናቱን ለማጥናት በር ከፍተዋል።
1.3 የጥናቱ አላማ
የዚህ ጥናት ዋና አላማ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ የሚዘጋጁ የማስታወቂያ ፅሑፎች የቋንቋ አጠቃቀም ላይ
ትንተና ማካሄድ ነው። በተጨማሪም ጥናቱ የሚከተሉትን ዝርዝር አላማዎች ይዟል።
የማስታወቂያዎቹ የቃላት ምርጫ ምን እንደሚመስል መዳሰስ፤
የማስታወቂያዎቹ ሰዋሰዋዊ የቋንቋ አጠቃቀም ሁኔታ ምን እንደሚመስል መፈተሽ፤
የማስታወቂያ የቋንቋ አጠቃቀም ከታዋሽነት አይረሴነት አኳያ ምን እንደሚመስል መገምገም ናቸው።
1.4 የጥናቱ ጠቀሜታ
ይህ ጥናታዊ ፅሁፍ የሚከተሉት ጠቀሜታዎች አሉት ተብሎ ይታሰባል።
1. ስለ ማስታወቂያ አፃፃፍ እና ምንነት እንዲሁም ምን ምን ነገሮችን ማሟላት እንዳለበት ግንዛቤ
ያስጨብጣል።
2. የሚወጡት ማስታወቂያዎች ምን ምን ችግሮች እንዳሉባቸው ይጠቁማል።
3. ለሚያወጧቸው ማስታወቂያዎች የማስተካከል እና የማረም ብቃት እንዲኖራቸው ያግዛል።
4. ተሰንዶ ቢቀመጥ ለሌሎች ተመራማሪዎች ወይም አጥኚዎች እንደ መነሻ በመሆን ያገለግላል።
1.5 የጥናቱ ክልል እና ገደብ
ይህ ጥናት በዋናነት የሚያተኩረው በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ ውስጥ በህንፃዎች በር እና ግድግዳ ፣ በመመገቢያ
አዳራሽ በር፣ በቤተ መፅሀፍት በር እና በማስታወቂያ መለጠፊያ ሰሌዳ ላይ በሚወጡ የአማርኛ ማስታወቂያዎች
የቋንቋ አጠቃቀም ላይ ብቻ ያተኮረ ነው። ከዚህም ውጭ ግን ተማሪዎች መታወቂያ ጠፋብን፣ መመገቢያ ካርድ
ጠፋብን፣ ሀገር የሚለውጥ፣ ትምህርት ክፍል የሚለውጥ እና የመሳሰሉትን በማለት የሚፅፉትን አያካትትም።
ምክንያቱም ሁሉንም በግቢው ውስጥ የሚለጠፉ ማስታወቂያዎችን ለመቃኘት እና ለመመርመር የአቅም፣ የጊዜ
እንዲሁም የገንዘብ እጥረት ስለሚገድብ ነው። በመሆኑም በኦዳ'ያኣ ግቢ ውስጥ ከተለያዩ ቢሮዎች በሚወጡ
በአማርኛ ቋንቋ በተፃፉ ማስታወቂያዎች ላይ ብቻ በማተኮር ጥናቱ ተካሂዷል።
1.6 የጥናቱ ዘዴ
የጥናቱ ዘዴ ሲባል ጥናቱ በምን መልክ እንደሚጓዝ የሚያሳይ እና የጥናቱን ጠቅላላ ሁኔታ የሚመለከት ነው።
በመሆኑም ጥናቱ በገላጭ የምርምር ስልት ላይ የተመሰረተ ሲሆን በዚህ ክፍል ውስጥም የናሙና አመራረጥ ዘዴ፣
የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ እና የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ተብራርተዋል።
3
1.6.1 የናሙና አመራረጥ ዘዴ
ለዚህ ጥናት የተመረጠው አመቺ የናሙና አመራረጥ ዘዴ ነው። ምክንያቱም አጥኚዋ የምትማረው በኦዳ'ያኣ ግቢ
መሆኑ ለጥናቱ የሚመቸው በዚሁ ግቢ ውስጥ የሚገኙ ማስታወቂያዎች ማግኘት ስለሆነ ከጥቅምት 14 እስከ የካቲት
15/2012 ዓ.ም ድረስ የተለጠፉትን በመሰብሰብ መረጃውን ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ተደርጓል። በኦዳ'ያኣ ግቢ
በአመቺ ናሙና ከተመረጠ በኋላ በዚህ መሰረት ለጥናቱ መሰረት ከተመረጠ ለጥናቱ መረጃ ይገኝባቸዋል ተብለው
ከታሰቡት ቦታዎች፣ መመገቢያ አዳራሽ፣ በማስታወቂያ ሰሌዳዎች እና በተማሪዎች የመኖሪያ ህንፃዎች አካባቢ
የተገኙ 40 ማስታወቂያ ፅሁፎች ተሰብስበዋል። ነገር ግን ሁሉንም ለመስራት የጊዜ እና የአቅም ችግሮች ስላሉ
እንደገና በተራ የእጣ ናሙና ስልት 16 ማስታወቂያዎች ተመርጠው በዚህ ጥናት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ተደርጓል።
1.6.2 የመረጃ መተንተኛ ዘዴ
በዚህ ጥናት አገልግሎት ላይ የዋሉት የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ምልከታ እና ሰነድ ፍተሻ ናቸው።
1.6.2.1 ምልከታ
አንድን መረጃ ትክክለኛ እና እውነተኛ እንዲሆን መረጃ ከሚገኝበት ቦታ ድረስ ዘልቆ በመግባት መረጃን ለመሰብሰብ
ከሚረዱ መሳሪያዎች ትልቁ ምልከታ ነው። ስለሆነም በዚህ ጥናታዊ ፅሁፍ መረጃ ለማግኘት ሲባል ባልታቀደ ምልከታ
ለአምስት ወራት ያህል በተደጋጋሚ በየማስታወቂያ መለጠፊያዎች ድረስ በመሄድ እና የተለጠፉትን ማስታወቂያዎች
በመመልከት እና ፎቶግራፍ በማንሳት መረጃን ለመሰብሰብ ተሞክሯል።
1.6.2.2 ሰነድ ፍተሻ
ሌላው የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ሰነድ ፍተሻ ነው። በመሆኑም አጥኚዋ ከርዕሱ ጋር ተዛማጅነት ያላቸውን የተለያዩ
ሠነድና ሠነድ ነክ ፅሁፎች በማንበብ ለጥናታዊ ፅሁፍ ተሰብስቧል።
1.6.3 የመረጃ መተንተኛ ዘዴ
በዚህ ጥናት የተሰበሰበው መረጃ የሚተነተነው በአይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ነው። ያለው (2004፣410) አይነታዊ
የመረጃ መተንተኛ ዘዴ በሚገባ ከተጠናከረና ተጨባጩን አለም በትክክለኛ መንገድ እንዲያሳይ ተደርጎ ከተሰራበት
ግልፅና ለአንባቢ ትርጉም ያለው ሀሳብ ለመስጠት ያስችላል ይላሉ። በዚህ ጥናት የማስታወቂያ ፅሁፎችን በመጠቀም
የተሠበሰቡት መረጃዎች በየመልካቸው ከተደራጁ በኋላ በአይነታዊ መረጃ መተንተኛ ዘዴ ከስርዓተ ነጥብ እና ከቃላት
ምርጫ እፃር ለመተንተን ተሞክሯል።
4
ምዕራፍ ሁለት
2. ክለሳ ድርሳናት
2.1 የማስታወቂያ ምንነት
በማስታዎቂያ ዙሪያ ጥናት የሚያደርጉ ባለሙያዎች በአንድ ድምጽ “ማስታወቂያ ማለት ይህ ነው” የሚል ድምዳሜ
ላይ አልደረሱም። ምክንያቱ ደግሞ የማስታወቂያ ስራ በስሌት እንደሚደርስበት የቁጥር ቀመር ሳይሆን የምርቶች እና
አገልግሎቶች የመለዋወጥ ሂደት፣ ከሙያው ቴክኖሎጂ እድገት ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው መሆኑ እና የማስታወቂያ
ስራ በራሱ ያላቋረጠ እድገት ማሳየቱ የሚጠቀሱ ናቸው (ዳንኤል፣ 2000፣27)፡፡
ስለማስታወቂያ የተለያዩ ምሁራን ብያኔያቸውን አስቀምጠዋል። ከብያኔዎቹም መካከል የሚከተሉትን
እንመለከታለን።
ተሸገር (1996፣267) ጆንሠን (1887፣4)ን ጠቅሶ ማስታወቂያ አብዛኛውን ጊዜ የምርቱን ጠቀሜታ የሚያሳይ መረጃን
መሰረት በማድረግ ለግዢ የሚገፋፋ ለታዳሚው አመለካከት ተስማሚ ምስል በመፍጠር በእጅ አዙር የማሳመን ሂደት
ነው በማለት ገልፆታል።
በሌላም በኩል የዪናይትድ ኪንግደም ማስታወቂያ ማህበር /https://m.economic times.com /definition/
advertizing/ ማስታወቂያን ማስታወቂያ ከምርት ወይም አገልግሎት ተጠቃሚዎች ጋር የማግባቢያ መንገድ ነው።
ማስታወቂያዎች በሚያስተላልፉት መልዕክት የሚሰሙዋቸው የሚያዪዋቸው ሰዎች ላይ ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ
እንዲያሳምኑ እና እንዲያሳውቁ የታሰቡ ናቸው። በማለት ገልፀዋል።
ስለ ማስታዎቂያ ምንነት ዳንኤል (2000፣28) እንደገለጸው፦
ማስታወቂያ በሚገባ የተነገረ እውነት ነው። በመሆኑም ማስታወቂያ አስደሳችነት ያለው ተሞክሮን
የሚያካፍል፣ሲያዩት የሚማርክ፣ ሲሰሙት የሚለሰልስ መሆን ይገባዋል፡፡ አድማጭና ተመልካችንም
ምነው እዚያው በታደምኩ ኑሮ፣ምነው እኔም አግንቼ የኔ ባደረግሁት ኖሮ ብሎ የሚያስቆጨው
መሆን ይጠበቅበታል። የአንድን ምርት ተጠቃሚዎች እንዲገለገሉበት የሚያግባባ፣ ክፍያ
የሚጣልበትና ግላዊነት የማይታይበት የመረጃ ቅብብሎሸ አይነት ነው።
ከዚህም የምንረዳው ከምርቶቻቸው እና አገልግሎታቸው ወይም ከሚያራምዷቸው ሀሳብ እና ከሚያከናውኗቸው
ተግባራት መካከል የተፈለገውን መልዕክት ታዳሚው ዘንድ እንዲደርስ፣ አላማው ግብ እንዲመታ እና ተቀባይነት
እንዲኖረው የማስታወቂያው መልዕክት በአዕምሮ ውስጥ ምስል በመፍጠር የሚያሳምን እና የሚያስተምር መሆን
አለበት።
2.4.1. ማሳሰብ
ማሳሰብ ማለት ደንበኞች ለመግዛት ( ለመጠቀም ) ያላሰቡትን ነገር ምናልባትም መኖሩንም ያላወቁትን ምርት
እንዲያውቁትና እንዲሞክሩት ማድረግ ነው። የምርቱን ተፈላጊነት በማጉላትም ደንበኛን ይጨምራል። ይህ አይነቱ
ማስታወቂያ ብዙውን ጊዜ ጥቅም ላይ ሲውል የሚታየው በገበያ አካባቢ ነው፡፡ በተለይ አዳዲስ ምርቶች ላይ ነው፡፡
2.4.2. ማሳመን
ይህ የማስታወቂያ አገልግሎት የሰዎችን ስሜት የሚነኩና ሊያሳምኑ የሚችሉ ቃላትንና ጥበባዊ ዘዴዎችን በመጠቀም
ምርቱን ወደ መግዛትና በአገልግሎቱም ወደ መጠቀም እንዲያመሩ የሚያደርግ ነው። ይህ ዘዴ ብዙውን ጊዜ ለፍቅረኛ
6
ስጦታ ማበርከትን፣ ወደሚፈለገው ሀይማኖት ሰብኮ ማስገባትን፣ በራስና በቤተሰብ ላይ ሊደርስ የሚችልን አደጋ
መከላከልን፣ በራስ መተማመንን ማጎልበትን ወዘተ. ይይዛል።
2.4.3. መገፋፋት
ማስታወቂያ ስለ ምርቱና አገልግሎቱ ጠበቅ ያለ መረጃ ሊይዝ ይገባል። ይህም ሲባል ከነበሩ ምርጫዎች መካከል
ሊያስመርጠው የሚችል ከአዲስም ሆነ ከነባሮቹ ልቆ እንዲታይ ማድረግ ሊሆን ይገባል፡፡ በዚህ ሀሳብ እንደተገለጸው
ማስታወቂያው ለእይታ በሚበቃበት ጊዜ ሰዎች ወይም ተደራሲያን አንዳች ሀይል በእዝነ ህሊናቸው አድሮ ወደ
ተገለጸው ነገር የመግባት ፍላጎታቸው ሊጨምር እንደሚችል ማሳየት ነው፡፡
2.4.4.ማስታወስ
ይህ አይነቱ ደግሞ በማስታወቂያ አማካኝነት ለማስታወስ የሚፈልገው ዋነኛው ጉዳይ የምርቱን መለዮ
ምልክት(birand) ሲሆን መለዮውም ዘወትር በደንበኞች ህሊና እንዲመላለስ ማድረግ ነው።
7
2.5.1 መደበኛ የቃላት አጠቃቀም ደረጃ
ይህ ስልት የአፍ መፍቻንም ሆነ ሁለተኛ(የውጭ)ቋንቋን በትምህርት ቤት መማርን ይመለከታል። በትምህርት ቤት
ለመማር ስርዓተ ትምህርት፣ መርሃ ትምህርት፣ የመማሪያና የማስተማሪያ ቁሳቁሶች( መጽሃፍት፣ በራሪ ወረቀቶች፣
የቴፕና የቪዲዮ ክሮች፣ ወዘተ.) መምህርና መማሪያ ቦታ፣ እንዲሁም የመማሪያ ጊዜን መመደብን ሁሉ ይጠይቃል።
በእነዚህ በተጠቀሱት ልዩ ልዩ ተግባራትና ክንዋኔዎች አማካኝነትም ለትምህርት የቀረበውን ቋንቋ ቃላት በአላማው
መሰረት ደረጃ በደረጃ የምንማራቸው ናቸው፡፡ እንዲሁም የምንጠቀምባቸው ናቸው፡፡ በመሆኑም ሰፊ እውቅና
አገልግሎት አላቸው(ደረጀ 1996፣5)።
2.5.2 ኢ መደበኛ የቃላት አጠቃቀም ደረጃ
ይህ የቃላት ማጥኛ ዘዴ ደግሞ በቋንቋው ተናጋሪ ህዝብ ውስጥ መኖር ነው። ተናጋሪው ህብረተሰብ በእየለት ውሎው
እንዳጋጠመው ለቃላት ክብደትና ቅለት ሳይጨነቅ ሃሳቡን ይገልጻል። በማህበረሰቡ ግንኙነት ውስጥም እግረ መንገዱን
የቃላት ችሎታን የምናዳብርበት ስልት ነው። ይህ ከማህበረሰቡ ጋር በመኖር የምናገኘው የእውቀት እና የቃላት
መለማመድ ዘዴ ኢመደበኛ ተብሎ ይጠራል፡፡ ኢመደበኛ የቃላት አጠቃቀም ደረጃ የሚባሉትም፣ ጉራማይሌ፣ የሙያ፣
ያራዳ፣ ዘዬ (ቀበልኛ) ቃላት ወዘተ. ናቸው፡፡ እነዚህም ውስን እውቅና አገልግሎት ያላቸው ናቸው (ደረጀ 1996 ፣5)።
8
በአንድ ቋንቋ ውስጥ የሚገኝ ማንኛውም ቃል መደበኛ ፅሁፍን ዉስጥ አይካተትም። ስለዚህ የቃላት አጠቃቀምን
ለይቶ ማወቅ ግድ ይለናል። ቃላትን ስንጠቀም የተለያዩ ችግሮች ያጋጥማሉ። እነሱም ድረታ፣ ድግግሞሽ፣ የተውሶ፣
ወዘተ. ናቸው (አብነት 2007፣45)።
የቃላት ድረታ የሚለው ጽንሰሃሳብ አንድን ነገር ለመግለጽ ወይም መልእክትን ከምንጩ ወደ ተደራሲያን ለማስተላለፍ ተመሳሳይ
ትርጉም (ፍች) ያላቸውን ቃላት መሰደር ነው። ድረታ በአገባባቸው ሙሉ ስሜት በሚያሳዩ ወይም አንድን ድርጊት በበቂ ሁኔታ
በሚገልጹ ቃላት ላይ ተመሳሳይ ፍች ወይም መልእክት የሚሰጡ ቃላትን መጨመር ነው። ይህ አይነቱ አገላለጽ ደግሞ መልእክትን
በተፈለገው መልኩ ለተፈለገው አካል ለማቅረብ መሰናክል ነው። ተመሳሳይ ድርጊትን የሚገልጹ በርካታ ቃላት መደጋገም ሃሳብን
ግልጽ ከማድረግ ይልቅ ያድበሰብሳል። አንባቢንም ወደ አልተፈለገ መደናገር ውስጥ ያስገባል ( ደረጀ 1996 ፣13) ።
ድግግሞሽ የሚባለው በፅሁፍ ውስጥ ለአፅንኦት ሲባል ቃልን ወይም ሀረግን መደጋገም ነው። ወይም የራሱ የሆነ አላማ
ያለው ሲሆን በድርሰት ውስጥ ቢገባ እንደ ስህተት ላይታይ ይችላል ነገር ከልክ ባለፈ መንገድ የሚፈፀመው ድግግሞሽ
አስፈላጊ አይደለም። አንድ ፀሀፊ ቃላትን ያለምንም ምክንያት መደጋገም እንደማይችል ማወቅ አለበት
(አብነት 2007፣45-46)፡፡
10
2.7.2 የጾታ ስምምነት
ስሞችን በወገን በወገን የምንለይበት ሰዋሰዋዊ ባህሪ ነው። ሰዋሰዋዊ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮአዊም ሊሆን ይችላል።
በተፈጥሮአዊነቱ ስሞችን የወንድና የሴት ወገን ብለን በሁለት እንድንከፍል ይረዳናል። በተፈጥሮአቸው የወንድ
ምልክት ያላቸው የወንድ ጾታ በተፈጥሮአቸው የሴት ምልክት ያላቸው የሴት ወገን ተብለው ይለያሉ። ከሰዋሰው
አኳያም ስሞች ተባእታይ እና አንስታይ ተብለው እንደዚሁ በሁለት ይከፈላሉ። ተባዕታይነት እና አንስታይነት
ከተፈጥሮ ጾታ ማለትም ከወንድነት ወይም ከሴትነት ጋር ሊያያዝ ወይም ላይያያዝ ይችላል። በመጠናቸው ትንሽ
የሆኑ ነገሮችም በአማርኛ እንደ እንስት ስለሚቆጠሩ እነሱን የሚገልጹ ስሞች የአንስታይ ጾታ ምእላድን ያስከትላሉ።
አንስታይነት ትንሽነትን ይመለከታል ማለት ነው። ተባእታይነትም በአንጻሩ ትልቅነትን ሊያመለክት ይችላል።
ስለዚህም በተፈጥሮ ጾታው ወንዴ የሆነ እንስሳ በመጠኑ ትንሽ ከሆነ በአንስታይ ጾታ ሊጠራ ይችላል። እንዲሁም
በተፈጥሮ ጾታው እንስት (ሴቴ ) የሆነ እንስሳ በመጠኑ ትልቅ ወይም በባህሪው ወንዳወንድ ከሆነ በተባእታይ ጾታ
ሊጠራ ይችላል። ስለዚህም ወንዱን አንቺ ብለን በአንስታይ ጾታ ሴቷን ደግሞ አንተ ብለን በተባእታይ ጾታ
የምንጠራበት ጊዜ አለ። ጉዳዩ ጾታ ከወንድነትና ከሴቴነት ጋር ብቻ ሳይሆን ከመጠንና ከባህሪ ጋርም ግንኙነት ሊኖረው
እንደሚችል የሚጠቁም ነው። ቋንቋውም ይህን በምእላድ ወይም በመዋቅር ያሳያል። ከዚህም ሰዋሰዋዊ ባህርያትን
ብቻ ማሳየት ሳይሆን ማህበራዊ ግንኙነቶችንም ማንጸባረቁን ልብ ልንል ይገባል (ባዬ 2009 ፣ 120-121)።
2.7.3 የመደብ ስምምነት
በአማርኛ ቋንቋ ስርዓት የመደብ ስምምነት በነጻና በጥገኛ ተውላጠ ስሞች ይገለጻል። በቋንቋው ውስጥ የሚገኙት ነጻ
ተውላጠ ስሞች ብዙ ጊዜ የተለመዱት ናቸውና እነሱን እናያለን።
13
ምዕራፍ ሦስት
3. መረጃ ትንተና
የዚህ ጥናት ዋና አላማ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ በ 2012 ዓ.ም አገልግሎት ላይ የዋሉ ማስታወቂያዎችን የቋንቋ
አጠቃቀም መተንተን ነው። በመሆኑም መረጃዎችን በየህንፃው እና በየማስታወቂያ መለጠፊያ የተለጠፉትን
ማስታወቂያዎች በመሰብሰብ ከክለሳ ድርሳናት እና ከንዑስ አላማ ጋር በማገናዘብ እንደሚከተለው ማብራሪያ
ተሠጥቷል።
14
3.1.2 የዘዬ (ቀበልቻ) ቃላት አጠቃቀም
ዘዬ የተወሰነ ቡድን (የማህበረሰብ አባላት) የሚጠቀምበት የቋንቋ አጠቃቀም ልዩነት ነው፡፡ የቋንቋ አጠቃቀም
ልዩነቱም የሚመጣው በመልከዓ ምድራዊ ሁኔታና በማህበራዊ ሁኔታ ነው፡፡ የአንድ ቋንቋ ዘዬ ተናጋሪዎች በዘዬ ልዩነት
ሳቢያ ከመግባባት አይታገዱም፡፡ በድምጽ፣ በቃላትና በአባባሎች ልዩነት ሳቢያ ግን ግርታ ወይም የመልዕክት መደናገር
ሊፈጥር ይችላል፡ ይሁንና መልዕክቱን ሊገነዘቡት ስለሚችሉ አለመግባባት አይፈጠርም፡፡ ይሁን እንጂ ግርታን
በመፍጠሩ ለማስታወቂያ ፅሁፍ ተመራጭ አይደለም።
ምሳሌ 1፦ “በተማሪዎች መተዳደሪያ ደምብ የተጠቀሱት የዲሲፕሊን መምሪያ…”
በ 27/04/2012 ዓ.ም በተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ወጥቶ በተማሪዎች ህብረት ህንፃ የተለጠፈ ሲሆን በዚህ
ማስታወቂያ ውስጥ መደበኛ ያልሆነ “ደምብ” የሚል ቃል እናገኛለን። ይህ ቃል በአብዛኛው ጊዜ የቋንቋ ትምህርት
ያላጠኑ ወይም የንግግር ቋንቋን በፅሁፍ የመጠቀም ልምድ ያላቸው ሰዎች እንደዚህ መፃፋቸው ግልፅ ነው። ይህ ቃል
“ደንብ” ተብሎ መፃፍ አለበት።
ምሳሌ 2፦ “…በተጨማሪም ከአቻወቻቹ ጋር መመካከር ትችላላቹ።”
ይህ ማስታወቂያ በሴቶች ህንፃ ቁጥር 512 የሚገኘው ዜሮ ፕላን አባላት የለጠፉት ሲሆን “አቻዎቻችቹ” እና
“ትችላላቹ” የሚሉት ኢ-መደበኛ ቃላት ይገኛሉ። በመሆኑም በማስታወቂያ አፃፃፍ ሂደት እንደነዚህ ያሉ ቃላት
አጠቃቀም ማስወገድ ስለሚገባ “አቻወቻቹ” የሚለው “አቻዎቻችሁ” ተብሎ እንዲሁም “ትችላላቹ” የሚለው
“ትችላላችሁ” ተብሎ መፃፍ ይገባዋል።
15
ምሳሌ 1፦ “ለበርካታ አመታት ስትጠይቁ የነበረው ጥያቄያችሁ ምሳሽ አግኝቷል እና እያገኘም
ስላለ እንኳን ደስ አላችሁ…”
ይህ ማስታወቂያ በ 17/03/2012 በተማሪዎች መማክርት አስተባባሪ የወጣ ሲሆን ይህ ማስታወቂያ ቃላት በግልፅ
ባለመፃፋቸው እና የቃላት መደራረት በመኖሩ መልዕክቱን እንዲዛባ አድርጎታል። የበርካታ አመታት ጥያቄያችሁ ምላሽ
በማግኘቱ እንኳን ደስ አላችሁ ተብሎ መፃፍ ይገባዋል።
ምሳሌ 2፦ “በ 27/04/2012 ዓ.ም እና በ 29/04/2012 ዓ.ም በተካሄደ ድንገተኛ ፍተሻ ቅኝት
በኦዳ'ያኣ ግቢ ሶሻል ሳይንስ ቤተ መፅሀፍት 2 ተኛ ፈረቃ ላይ የተመደባችሁ ሰራተኞች
ስራ ባለመግባታችሁ አገልግሎቱ እንደተስተጓጎለ በሽፍት አስተባባሪው ከላይ
በተጠቀሱት ቀናት ለቤተ መፅሀፍት ዳይሮክቶሬት ሪፖርት አድርገዋል።
ስለሆነም ከላይ በስም ዝርዝራችሁ የተጠቀሳችሁ የሶሻል ሳይንስ ቤተ-መፅሀፍት
ሰራተኞች ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ በእናንተ መሸፈን የሚገባው ስራ
በችልተኝነት እና በግዴለሽነት ባለመሸፈኑ…”
ይህ ማስታወቂያ በ 30/04/2012 በማህበራዊ ሳይንስ ቤተ-መፅሀፍ የተለጠፈ ሲሆን የድረታ እንዲሁም የተውሶ ቃላት
ጥርቅም ነው። በመሆኑም በውስጡ ያሉት የተውሶ ቃላት መልዕክቱን አሰልቺ አድርጎታል። ይሄም
“በ 27 እና 28/04/2012 ዓ.ም በተካሄደ ድንገተኛ ቅኝት በኦዳ'ያኣ ግቢ ማህበራዊ
ሳይንስ ቤተ-መፅሀፍ 2 ተኛ ፈረቃ ላይ የተመደባችሁ ሰራተኞች በእናንተ መሸፈን
የሚገባው ስራ በችልተኝነት ባለመሸፈኑ አገልግሎቱ እንደስተጓጎለ በፈረቃ
አስተባባሪው ለቤተ-መፅሀፍት የስራ አመራር ቦርድ ሪፖርት አደርጓል። ስለሆነም
በእናተ መሽፈን የሚገባዉ ስራ…”
ተብሎ ቢስተካከል አጭር፣ ግልፅ እንዲሁም ለማንበብ የማያሰለች ይሆናል። በተጨማሪም የተውሶ ቃላትን አስወግደን
በቋንቋው ብንፅፈው መልዕክቱ ግልፅ እንዲሆን ይረዳል።
16
ምሳሌ 2፦ “ዛሬ ማለትም በቀን 08/04/2012 የባርሴሎና እና ሪያድ ማድሪድ ጨዋታ መኖሩ
ይታወቃል።…”
ይህ ማስታወቂያ የወጣበት ቀን ባይፃፍም ከፅሁፉ በታህሳስ ወር የተለጠፈ መሆኑን ማወቅ ይቻላል። በዚህ ዓ. ነገር
ውስጥ “ባርሴሎና” እና “ሪያድ ማድሪድ” የሚሉ ሁለት ቃላት እናገኛለን። እነዚህ የእግር ኳስ ቡድን ስሞች የእግር ኳስ
ጨዋታ ዕውቀት እና ትኩረት የሌለው ሰው ላይገነዘባቸው ይችላል።
3.1.5 ድግግሞሽ
አንድን ሀሳብ አንድ ጊዜ ከገለፅን በኋላ እየተመለስን ከተገቢው በላይ ደጋግመን በምንፅፍበት ጊዜ የሚከሰት ነው።
የሚከተሉትን ምሳሌ እንመልከት
17
ምሳሌ 1፦ “የገና በዓልን አስመልክቶ በየትኛውም አካባቢ በተለይ በየትኛውም ክፍል ተቀጣጣይ
እና እሳት ሊፈጥር የሚችል ክብሪት፣ ሰንደል፣ ሻማ፣ ከሠል፣ እስቶቭ እና ሌሎች
ተቀጣጣይ ቁሶች …”
ይህ ዓ. ነገር በ 27/07/2012 ዓ.ም የተማሪዎች ህብረት ዳይሬክተር ማስታወቂያ ላይ የሠፈረ ሲሆን አንድ አይነት ፍቺ
ያላቸው ቃላት ተጠራቅመውበት እናያለን። በዚህ ዓ. ነገር ውስጥ “እሳት ሊፈጥሩ የሚችሉ ነገሮች” የሚለው በቂ
ሆኖ ሳለ ቃላት ያለ አግባብ ገብተው መልዕክቱ እንዲንዛዛ አድርገውታል። በተጨማሪም በየትኛውም አካባቢ በተለይ
በየትኛም ክፍል የሚሉ ሀረጋት እናገኛለን። ስለዚህ “በየትኛውም ቦታ” ተብሎ ቢስተካከል መልዕክቱ ሳይንዛዛ
ለተመልካች ይደርሳል።
18
ማስታወቂያው በ 17/04/2012 በተማሪዎች አገልግሎት ህንፃ ተለጥፎ የተገኘ ሲሆን በውስጡ ሁለት አይነት ስህተት
አለው። የመጀመሪያው ተሳቢ ያለ ቦታው መግባት ሲሆን ሁለተኛው የቁጥር ስምምነት ነው።ዓረፍተ ነገሩ
ከመጀመሪያ በብዙ ቁጥር ይጀምራል፤ በመካከል ነጠላ ቁጥር አለ፤ መጨረሻ ብዙ ቁጥር አለ። ይህ ዓ. ነገር
“ከዚህ በታች በስም የተዘረዘራችሁ ተማሪዎች ዲስፕሊን ቢሮ ስለምትፈለጉ
በ 20/04/2012 ከጥዋት 3:00 ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን።”
ተብሎ ቢስተካከልትክክለኛ ስርዓት ያለው ገላጭ ዓ.ነገር ነው።
19
ምሳሌ 1፦ “ከላይ እንደተገለፀው በግል ችግር ምክንያት 04/05/2012 ዓ.ም
ጀምሮ ስለማልኖር ከራስዎ ስራ ላይ ደርበው የፈረቃ አስተባባሪን ስራ እንዲሰሩ የተወከሊሉ
መሆኑን እያሳወኩ የክፍሉ ሰራተኞች እና ግልባጭ
የተደረገላቸው ክፍሎች አስፈላጊውን ትብብር እንድታደርጉላቸው አሳስባለሁ።”
ይህ ማስታወቂያ በ 29/04/2012 ዓ.ም በማህበራዊ ሳይንስ ቤተ-መፅሀፍ የተለጠፈ ሲሆን ይህ ማስታወቂያ የመደብ
ስምምነት ችግር ይታይበታል። “የተደረገላቸው” የሚለው ሶስተኛ መደብን ሲያመለክት “እንድታደርጉላቸው”
የሚለው ደግሞ ሁለተኛ መደብን ያመለክታል። ስለዚህ የመደብ አለመስማማት ተፈጥሯል። ስለዚህ የተደረገላቸው
የሚለው “የተደረገላችሁ” ተብሎ ቢፃፍ መደቡ ተስማምቶ ትክክለኛው መልዕክት ይተላለፋል።
ምሳሌ 2፦ “የዩኒቨርስቲያችን ተማሪዎች ይሄንን አውቀው የመማር፣ የመግለፅ፣ የመከላከል
ብሎም ለሚመለከተው አካል መረጃ በመስጠት የበኩላችሁን ሀላፊነት
እንድትወጡ አሳስባለሁ።”
ይህ ዓ.ነገር በ 27/04/2012 ዓ.ም ከወጣው ማስታወቂያ የተገኘ ሲሆን “አውቀው” የሚለው ሶስተኛ መደብ
ሲያመለክት “የበኩላችሁን” እና “እንድትወጡ” የሚሉት ቃላት ሁለተኛ መደብን የሚያመለክቱ ናቸው። ስለዚህ
“አውቀው” የሚለውን ሦስተኛ መደብ ቃል “አውቃችሁ” ተብሎ ተስተካክሎ ለአንባቢ ግልፅ መሆን አለበት።
ምሳሌ 3፦ “ማንኛውም ተማሪ በህንፃ ዙሪያ እና ፍሎር ላይ እንዲሁም በመስኮት ላይ ስታጠብ
ወይም ስሸና የተገኘ ተማሪ ከባድ ርምጃ እንደምንወድ እናውቃል።”
ማስታወቂያ 28/02/2017 በወንዶች ህንፃ የተለጠፈ ሲሆን መልዕክት አስተላላፊው ለራሱ እንደፃፈው “ስሸና ወይም
ስታጠብ” እያለ ሲፅፍ እንመለከታለን። ነገር ግን መልዕክት የሚተላለፈው ለሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ ነው።
በዚህም ማስታወቂያ መልዕክት ማስተላለፍ የተፈለገው ለሦስተኛ ወገን መሆኑን ከፅሁፉ ማወቅ ይቻላል። ስለዚህ
“ሲታጠብ ወይም ሲሸና” ተብሎ መስተካከል አለበት።
20
ምሳሌ 1፦ “ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደሞከረው ማንኛውም ተማሪ በህንፃው በላይ
በመስኮት በወንፊት እና በሌሎች በሮች …”
ይህ ማስታወቂያ በ 12/06/2012 በሴቶች ህንፃ የተለጠፈ ሲሆን ስርዓተ ነጥብን በአግባቡ አልተጠቀቀም። ነገሮችን
ወይም ስሞችን ለመዘርዘር፣ ሀረግን ከሀረግ ለመለየት፣ ምዕራፍን ከቁጥር ለመለየት ነጠላ ሰረዝ እንጠቀማለን። ነገር
ግን በዚህ ዓ.ነገር ይህ የስርዓተ ነጥብ ጉድለት አለበት። “ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው ማንኛውም ተማሪ
በህንፃው ላይ፣ በመስኮት፣ በወንፊት እና በሌሎች በሮች …” ተብሎ መስተካከል አለበት።
ምሳሌ 2፦ “የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ካምፓስ ቤተ መፅሀፍት ባልደረባ የሆኑት በወሊድ
ምክንያት በቀን 01/05/2012 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት የተለዩ ሲሆን። እኛ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ቤተ መፅሀፍ ሰራተኞች…”
ይህ ማስታወቂያ ከየኒቨርሲቲው በር ላይ የተለጠፈ የሀዘን መግለጫ ሲሆን ቀን ባይኖረውም ከታች ባለው ቀን በጥር
ወር የተለጠፈ መሆኑን ያመለክታል። በዚህ ማስታወቂያ ላይ አራት ነጥብ ያለቦታው ገብቷል። አራት ነጥብ የሚገባው
አንድን ሀሳብ ለመቋጨቱን ወይም መጨረሱን ለማመልከት ከማሰሪያ አንቀፅ በኋላ ነው። በዚህ ዓ.ነገር ግን “ሲሆን”
ከሚለው ቀጥሎ አራት ነጥብ እናገኛለን። “ሲሆን” የሚለው የሚያመለክተው ያልተቋጨ ወይም የሚቀጥል ሀሳብ
መኖሩን ነው ስለዚህ አራት ነጥብ ከዚህ ቦታ አያስፈልግም።
ምሳሌ 3፦ “ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ለ 2012 ዓ.ም ለጌታችን
መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን …”
ይህ ዓ.ነገር የቀረው ስርዓተ ነጥብ አለው። ይህም ስርዓተ ነጥብ ቃለ አጋኖ ነው። ምክንያቱም ለዲላ ዩኒቨርሲቲ
ተማሪዎች በሙሉ ካለ አፅንኦት ሠጥቶታል ማለት ነው። ስለዚህ ቃለ አጋኖ መጠቀም ነበረበት። “ለዲላ ዩኒቨርሲቲ
ተማሪዎች በሙሉ! እንኳን ለ 2012 ዓ.ም ለጌታችን መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
እያልን …” ተብሎ መፃፍ ነበረበት።
21
ይህ ማስታወቂያ በ 13/04/2012 ዓ.ም የተለጠፈ ሲሆን ማስታወቂያው የታዋቂ ሰዎች ስም እንዲሁም የሚያዝናኑ
እና የሚያስተምሩ መርሀ ግብሮች መኖራቸውን መግለፁ መቼ ቀኑ ደርሶ ባየሁት የሚያስብል እና ድባቡ በአእምሯችን
ውስጥ ምስል እንዲመጣ እና አይረሴ እንዲሆን አድርገውታል።
ምዕራፍ አራት
4. ማጠቃለያና አስተያየት
በዚህ ምዕራፍ ላይ የጥናቱ ማጠቃለያና ከጥናቱ ጋር የተዛመዱ በአጥኚዎቹ የተሰጡ አስተያየቶች በቅደም ተከተል
ይቀርቡበታል፡፡
4.1 ማጠቃለያ
በዚህ ጥናታዊ ጽሁፍ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ ውስጥ በ 2012 ዓ.ም አገልግሎት ላይ የዋሉ ማስታወቂያ ፅሁፎች
ላይ የቋንቋ አጠቃቀም፤ ስዋሰዋዊ ስርዓት እንዲሁም ምስል ከሳችነት እና ታዋሽነት ላይ ፍተሻ ተካሂዷል። በምዕራፍ
አንድ ላይም ለጥናቱ እንደ መነሻ የሆኑ የጥናቱ ዳራ፣ የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት፣ የጥናቱ ዓላማ፣ የጥናቱ ጠቀሜታ፣
የጥናቱ ወሰን፣ የጥናቱ ክልል እና ገደብ፣ የጥናቱ ዘዴ፣ የናሙና አመራርጥ ዘዴ፣ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴና መተንተኛ
ዘዴ ቀርበዋል። ለጥናቱ ትንተናም የየምሁራኑን ንድፈ ሀሳብ በማጣቀስ ተጠቅመናል፡፡ የጥናቱ ዘዴም ገላጭ ነው፡፡
ለጥናቱ መረጃ የሚሰበሰብበት ቦታ ኦዳ'ያኣ ግቢ በአመቺ ናሙና ስልት ተመርጧል፡፡ በማስታወቂያ መለጠፊያ ሰሌዳን፣
በመመገቢያ አዳራሽ በርን፣ በተማሪዎች የመኝታ ህንፃዎች፣ መግቢያ ስፍራን መሰረት በማድረግ 40 የማስታወቂያ
ፅሁፎች ተሰብስበዋል፡፡ ከነዚህ ውስጥም 16 የማስታወቂያ ጽሁፎች በተራ የዕጣ ናሙና ስልት ተመርጠው ለመረጃ
ትንታኔው አገልግለዋል፡፡
በምዕራፍ ሁለት ላይም ክለሳ ድርሳናት ተከልሰዋል። በዚህ ስር የማስታወቂያ ምንነት፣ አጀማመር፣ አይነት፣
አገልግሎት እንዲሁም የቃላት ምርጫ፣ የቃላት አጠቃቀም፣ የስዋስው ምንነትንና የተዛማጅ ጽሁፍ ቅኝቶች የሚሉት
ተዳሰውበታል።
22
ምዕራፍ ሦስት የዚህ ጥናታዊ ጽሁፍ ዋና ክፍል ሲሆን በሰነድ ፍተሻ የተገኙ መረጃዎች በገላጭ የምርምር ስልት
ተተንትነው ቀርበዋል። ለጥናቱ ትንተናም የየምሁራኑን ንደፈ ሀሳብ በማጣቀሻነት አገልግለዋል። በቃላት ምርጫ
ረገድም እማሬያዊ እና ፍካሬያዊ ፍችዎችን በመለየት ለመመርመር ተክሞሯል፡፡ በመሆኑም ከመረጃዎች ለመረዳት
እንደተቻለው በማስታወቂያ ፅሁፎቹ ላይ ከፍካሬያዊ አገላለፆች ይልቅ እማሬያዊ የታየባቸው መሆኑን ለማረጋገጥ
ተችሏል፡፡
በቃላት አጠቃቀም ዙሪያ ደግሞ የባዕድ ቋንቋን በሰፊው የመጠቀም ችግር፣ ዘዬ (ቀበልኛ) ቃላትን የማዘውተር እና
ድረታን እና የተደጋገሙ ቃላት እና ሀረጋትን የመጠቀም ችግሮች እንዳሉ በመረጃዎቹ ተስተውሏል፡፡
በሰዋሰው ስርዓትም በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ የወጡ ማስታወቂያዎች ላይ ዐረፍተ የቁጥር እና የመደብ
አለመስማማት፣ የተሳቢ ያለቦታው መምጣት፣ ተገቢ ስርዓተ ነጥብ አለመጠቀም ችግሮች እንደሚታዩበት ለማረጋገጥ
ተችሏል።
4.2 አስተያየት
የጥናቱን ውጤት መሰረት በማድረግ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ ውስጥ የወጡ ማስታወቂያዎች የቋንቋ አጠቃቀም
ችግሮች ያሉባቸው መሆኑን ለማረጋገጥ ተችለዋል፡፡ ስለዚህም ለተገኙት ችግሮች አጥኚዎቹ የመፍትሄ ሃሳቦች
የሚሏቸውን እንደሚከተሉት አቅርበዋል፡፡
ማስታቂያዎች ሲዘጋጁ አንባቢዎች ሊረዱት በሚችሉት በግልጽ ቋንቋ ወይም መደበኛ በሆነ የቃላት
አጠቃቀም መጠቀምና መጻፍ ቢችሉ፣
የንግግርና የፅሕፈት የቃላት አጠቃቀምን ልዩነት የሚያውቁና የተረዱ ሰዎች ማስታዎቂያ እንዲያዘጋጁ
ማድረግ ቢቻል፣
የስርዓተ ነጥብን ሚና እና አገልግሎት ባንተወው ( ባንዘነጋው ) ጥሩ መስራት እንደምንችል መገንዘብ ቢቻል፣
ማስታወቂያዎችን የሚፅፉ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች ማስታወቂዎችን ከመለጠፋቸው በፊት ደጋግመው
ቢያነቡና የሚታዩ ስህተቶችንና ግድፈቶችን ለማረም ቢችሉ፣
ማስታወቂያዎችን የሚፅፉ ሁሉ የቋንቋው ባለሙያ ናቸው ለማለት ስለማይቻልና የሚታዩትን ስህተቶች
ለማረም ይረዳ ዘንድ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋ እና ስነ ፅሁፍ ትምህርት ክፍል ለአንዳንድ የስራ
ክፍሎች/ለሚመለከታቸው አካላት ስልጠና ቢያመቻች የሚሉ ናቸው፡፡
23
ዋቢ ፅፎች
ሳሙኤል ወልደ ጊዮርጊስ (1999)። “በዲላ መሰናዶ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ 10L ክፍል ተማሪዎች
የፅህፈት ክሂል ፍተሻ።” ያልታተመ። ለመጀመሪያ ድግሪ ማሟያ የቀረበ ጥናታዊ ፅሁፍ። ዲላ
ዩኒቨርሲቲ።
በአካሉ በላይ(2004)። “በ 2003 ዓ.ም በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የወጡ ማስታወቂያዎች የቋንቋ አጠቃቀም
ትንተና።”ያልታተመ። ለመጀመሪያ ድግሪ ማሟያ የቀረበ ጥናታዊ ፅሁፍ።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ።
ባህሩ ዘርጋው (2000) ፡፡ ከፍተኛ መዝገበ ቃላት። አዲስ አበባ ፣ ንግድ ማተሚያ ድርጅት ።
ባዬ ይማም (2009):: የአማርኛ ሰዋሰው። አዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ቢኤ ማተሚያ ቤት፡፡
ተሻገር ሽፈራው (1996)። ማስታወቂያና መገናኛ ብዙሀን የጋዜጠኝነት ሀ.ሁ ። አዲስ አበባ፣ ሜጋ አሳታሚ ድርጅት።
አብነት ስሜ (2007) ። የቋንቋ መሰረታውያን ። አዲስ አበባ፣ ፋር ኢስት ትቴዲንግ ሃላ/የተ/የግ/ማ።
ኢሳያስ ኢልባሶ(2010)። “ከየካቲት 2009 ዓ.ም ወዲህ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የወጡ ማስታወቂያዎች ቋንቋ አጠቃቀም
ትንተና።” ያልታተመ። ለአርት ባችለር ዲግሪ ከፊል ማሟያነት የቀረበ። ዲላ ዪኒቨርሲቲ።
ከፍያለው ዘውዴ (2004) “የኢትዩጵያ ቴሌቪዥን ማስታወቂያ ይዘት ትንተና”። ያልታተመ። ለመጀመሪያ ድግሪ ማሟያ
የቀረበ ጥናታዊ ፅሁፍ። ዲላ ዩኒቨርሲቲ።
የሻው ተሰማ (1996) ። ልሳነ ብዕር ከመልሳነ ሰብዕ ። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ በብራና ማተሚያ ድርጅት ታተመ ።
ያለው እንዳወቀ (2009) ። የምርምር መሰረታዊ መርሆች እና አተገባበር ። ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፣ ተፈራ ስዩም ማተሚያ
ቤት፡፡
ደረጀ ገብሬ (1996) ። ተግባራዊ የጽህፈት መማሪያ ። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ንግድ ማተሚያ ድርጅት።
ዳንኤል ብርሃኑ (2000) ፡፡ የማስታወቂያ መሰረታዊ መርሆች ። አዲስ አበባ።
ዳንኤል እና ሌሎች (1994) ። የትምህርት ጥናት እና ምርምር አተገባበር ። አዲስ አበባ ፣ሜጋ አሳታሚ
ድርጅት።
ጌታሁን አማረ (1990) ። ዘመናዊ የአማርኛ ሰዋሰው በቀላል አቀራረብ። አዲስ አበባ ፣ አልፋ አታሚዎች።
Thone, Sara (1997). Advanced English language. Hong Kong: MACMILLAN PRESS LTD.
word book encyclopedia (1994) Chicago: world book inc.
/Http://m. Economic times. Com definition/ advertising/.
24
ጥቅሶች በመገኛ ቋንቋቸው
Print advertisement is covering a wide range of forms and products, so advertisers design
different kinds of campaign depending upon the kind of intended of audience they wish to
attract. The image, tone and language chosen will all refract the target group but in each case the
variety will be distinctive (Sara 1997,269).
Advertising a massage designed to promote a product, a service or an idea. Is cheapest way to
inform large number of people about products or services for sale and persuade them to long
hence. Advertising is used and sponsored by social organizations, special interest group and
government( world book encyclopedia 1994,72).
Advertising is a means of communication with the users of product or service, advertisement is
massage paid for those who Send them and are intended of inform of influence people who
receive them (/Http://m. Economic times. Com definition/ advertising/)
25