You are on page 1of 152

Social Studies II SoSt- 222

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ

የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል

Social Studies II (SoSt- 222) ሞጁል

መጠነግብር 4/6

አዘጋጆች

1. አሳምነዉ ዱባለ - ታሪክ (ሌክቸረር)

2. ሙላት ጥላሁን - ጅኦግራፊ (ሌክቸረር)

3. ደጀን ደምሴ - ጅኦግራፊ (ሌክቸረር)

ታህሳስ 2007

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ጎንደር

የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል

Social Studies II (SoSt- 222) ሞጁል

መጠነግብር 4/6

አዘጋጆች

1. አሳምነዉ ዱባለ - ታሪክ (ሌክቸረር)

2. ሙላት ጥላሁን - ጅኦግራፊ (ሌክቸረር)

3. ደጀን ደምሴ - ጅኦግራፊ (ሌክቸረር)

ታህሳስ 2007 ዓ.ም

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ማዉጫ ገፅ ምዕራፍ አንድ........................................................1

የከፍታ ልዩነት በካርታ.....................................................................................................................................................................1


1.1 ከፍታ በካርታ ላይ.....................................................................................................................................................................1
1.1.1 ባህላዊ ዘዴዎች (Traditional methods)...................................................................................................2
1.1.2 ስምርቅጦች (Contour lines).......................................................................................................................5
1.1.3 ንብብር ቅልመት/ንቅሰት (Layer Colouring or Layer Tinting)...................................................6
1.1.4 የስምርቅጦች ባህሪያት (Properties of Contour Lines)...................................................................7
1.2 የውስን ከፍታ(Specific Height) ማሳያ ዘዴዎች.............................................................................................10
1.2.1 እውቅ ፍታ (Spot Height)............................................................................................................................10
1.2.2. ትሪግኖሜትሪካል ነጥቦች (Trignometrical Points)...........................................................................10
1.2.3 ማጣቀሻ (Bench Mark).................................................................................................................................11
1.2.4 የከፍታ ስሌት (Calculating Altitudes)....................................................................................................11
1.3 ቆለቆሎችና ድፈቶች...................................................................................................................................................12
1.3.1 የቆለቆል አይነቶች (Types of Slopes)...............................................................................................................14
1.4 ማጠቃለያ................................................................................................................................................................................16
1.5 የምዕራፉ ማጠቃለያ ጥያቄዎች.......................................................................................................................................17
ምእራፍ ሁለት..................................................................................................... 18

የዓለምና የኢትዮጵያ ፊዚካዊ አካባቢ................................................................................. 18

መግቢያ........................................................................................................... 18

2.1 የስነመሬታዊ ጊዜ ሚዛን / Geological Time Scale/.............................................................................................19


2.2 . ስነመሬታዊ ድርጊቶች በኢትዮጵያ (Geological events in Ethiopia)...........................................26
2.3 አየር ቅጥ / Climate /......................................................................................................................................................32
2.3.1 የአለም የአየር ቅጥ ክፍፍል / World’s climate classification/..............................................................33
2.3.2 የኢትዮጵያ አየር ቅጥ................................................................................................................................................37
2.3.3 ወቅቶች በኢትዮጵያ.................................................................................................................................................46
2.3.4 የአየር ቅጥ ለዉጥና ዉጤቱ....................................................................................................................................49
2.4. ስርዓተ ምኅዳር /Ecosystem/................................................................................................................................56
2.4.1 የስርዓተ ምኅዳር አካላት..........................................................................................................................................56
2.4.2. የእንስሳትና የእጽዋት ብዘኃነት / Divresity of Fauna and Flora /......................................................58

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

2.4.3 በስርዓተ- ምኅዳር ስርጭት ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ደንቢዎች........................................................61

ምዕራፍ ሦስት..................................................................................................... 65

የዓለም ሕዝብ፣የኢኮኖሚ ስርዓትና ልማት............................................................................65

መግቢያ........................................................................................................... 65

3.1 የዓለም ሕዝብ ብዛትና የእድገት ሁኔታ.........................................................................................................................65


3.2 የዓለም ሕዝብ ሥርጭት፣ ውቅርና ዝፈት ሁኔታ......................................................................................................68
3.2.1 የአለም ህዝብ ስርጭት ሁኔታ................................................................................................................................68
3.2.2 በህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች..................................................................................................70
1.3.1 3.2.3 የህዝብ ዝፈት (Population Density)..........................................................................................71
1.3.2 3.2.4 የህዝብ ውቅር (Population Structure)......................................................................................73
3.3 የኢትዮጵያ ህዝብና የስነ ህዝብ ፖሊሲ........................................................................................................................73
3.3.1 የስነ ህዝብ መረጃ ምንጮች....................................................................................................................................73
3.3.2 የኢትዮጵያ ህዝብ የእድገት ሁኔታ........................................................................................................................75
3.3.3 የኢትዮጵያ ብሄራዊ የስነ ህዝብ ፖሊሲ..............................................................................................................76
3.4 የአለም ኢኮኖሚ ስርዓት አይነቶች(Types of World Economic Systems)........................................................77
3.4.1 የኢኮኖሚ ስርዓቶች (Economic Systems)....................................................................................................77
3.4.2 የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴ አይነቶች (Categories of Economic Activities)..................................78
1.3.3 3.4.3 የዘላቂ ልማትና እድገት ምንነት...............................................................................................................78
3.4.4 የዘላቂ ልማትና እድገት አመላካቾች....................................................................................................................79
1.4 3.5 የኢኮኖሚ ድርጅቶች..........................................................................................................................................80
3.6 ማጠቃለያ................................................................................................................................................................................81
3.7 የምዕራፉ ማጠቃለያ ጥያቄዎች......................................................................................................................................81
ምዕራፍ አራት..................................................................................................... 83

ኢትዩጵያና የአፍሪካ ቀንድ /እ.ኤ.አ ከ 1855-1991/.............................................................83

4.1 የኢትዩጵያ ማዕከላዊ መንግስት ምስረታ................................................................................................................................83


4.2 የሁለትዮሽ አስተዳደርና የፍፁማዊ ዘውዳዊ ስርዓት መመስረት........................................................................90
4.3 የ 1935 (እ.ኤ.አ) የጣሊያን ወረራና የኢትዩጵያ ነፃነት መውጣት.......................................................................93
4.4 የዘውዳዊ ስርዓቱን በመቃወም የተደረገ እንቅስቃሴና የደርግ መመስረት.........................................................95
4.5 የደርግ መውደቅና የኢህአዴግ ወደ ስልጣን መምጣት..............................................................................................98
ምዕራፍ 5- የአፍሪካ ታሪክ (እ.ኤ.አ በ 1880 ዎቹ)................................................................99

5.1 አፍሪካ በቅኝ ግዛት ዋዜማ................................................................................................................................................99


5.2 የቅኝ ግዛት ምስረታና ቀደምት የአፍሪካውያን ፀረ ቅኝ ግዛት ትግል..................................................................101
የፈረንሳይ የቅኝ ግዛት ምስረታና የአፍሪካውያን ፀረ ቅኝ ግዛት ትግል.......................................................................101
5.3 የአፍሪካውያን ለነፃነት የተደረገ ትግል..........................................................................................................................104
5.4 የቅኝ ግዛት ውርሶች...........................................................................................................................................................105

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

5.5 የአፓርታይድ ስርዓት በደቡብ አፍሪካ...........................................................................................................................106


5.6 የአህጉራዊና ክፍለ አህጉራዊ ድርጅቶች ምስረታ....................................................................................................107
ምእራፍ 6 - የዘመናዊዉና የአሁኑ የአለም ታሪክ...................................................................115

6.1 የዘመናዊዉ የአለም ታሪክ (1815-1945)....................................................................................................................115


6.1.1 የኢንዱስትሪዉ አብዮት..........................................................................................................................................115
6.1.2 የኢጣልያ ውህደት....................................................................................................................................................119
6.1.3 የጀርመን ውህደት.....................................................................................................................................................123
6.1.4 የአሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት (እ.ኤ.አ 1861-65)......................................................................................127
6.1.5 አንደኛው የአለም ጦርነት /እ.ኤ.አ 1914-1918/.............................................................................................131
6.1.6 የፋሽስታዊ ስርዓት በጣሊያንና የናዚ ስርዓት በጀርመን መከሰት...............................................................136
6.1.7 የሁለተኛው የአለም ጦርነት መጀመር (እ.ኤ.አ 1939-1945)...................................................................136
6.2 የአሁኑ አለም ታሪክ እ.ኤ.አ ከ 1945 ጀምሮ..............................................................................................................140
6.2.1 የሁለተኛው የአለም ጦርነት ማግስት.................................................................................................................140
6.2.2 የቅኝ ግዛት መፈራረሰና የተባበሩ መንግስታት ድርጀት መመሰረት...........................................................141
6.2.3 የቀዝቃዛው ጦርነት..................................................................................................................................................143
6.2.4 ኮሙኒስት ቻይና........................................................................................................................................................144
6.2.5 የኮርያ ጦርነት.............................................................................................................................................................146
6.2.6 ቬትናም /ኢንዶቻይና/.............................................................................................................................................147
6.2.7 ኩባ (cuba).............................................................................................................................................................................149

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የሞጁል መግቢያ

የማህበራዊ ጥናት ትምህርት የማህበራዊ ሳይንሶች ዉህድ ነዉ፡፡ ተፈጥሮአዊና ሰዉ ሰራሽ እዉነታዎችንና
ክስተቶችን ለመረዳት፣ ለመንከባከብና በአግባቡ ለመጠቀም ይረዳል፡፡ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ
ግንዛቤዎችን ለማዳበርና ተገቢ የዜግነት ድርሻን ለመወጣት ያስችላል፡፡

ይህ ኮርስ / SoSt - 222 / በ 10+3 የዲፕሎማ ፕሮገራም ለሚከታተሉ የዉህድ ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች
የተዘጋጀ ሲሆን ስድስት የግንኙነት ሰዓት ተመድቦለት የሚሰጥ ኮርስ ነዉ፡፡

በኮርሱ ዉስጥ የተካተቱት ክፍለ ትምህርቶች ምእራፍ አንድ፡- የከፍታ ልዩነት በካርታ፣ ምእራፍ ሁለት፡-
የአለምና የኢትዮጵያ ፊዚካዊ አካባቢ፤ ምእራፍ ሶስት፡- የአለም ህዝብ፣የኢኮኖሚ ስርዓትና ልማት፣ ምእራፍ
አራት፡- ኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ እኤእ ከ 1855-1991፣ምእራፍ አምስት፡- የአፍሪካ ታሪክ እኤእ
በ 1880 ዎቹ፣ ምእራፍ ስድስት፡- የዘመናዊዉና የአሁኑ አለም ታሪክ እኤአ ከ 1815 -1945 የሚሉት ዋና ዋና
ክፍለ ትምህርት ሲሆኑ በየክፍለ ትምህርቱ መጀመሪያ የትምህርት አላማዎች ተገልጸዋል፡፡ እንዲሁም በየክፍለ
ትምህርቱ መጨረሻ ማጠቃለያና የክለሳ ጥያቄዎች ተካተዋል፡፡

ትምህርቱን ተጨባጭ ለማድረግ ልዩ ልዩ ስእላዊ መግለጫዎች፣ ካርታዎች፣ ሰንጠረዦች፣ ፎቶግራፎችና


ግራፎች ተካተዋል፡፡ በተጨማሪም ተማሪዎችን ሊያሳትፉ የሚችሉ የተለያዩ የተግባር ስራዎች የተቀረጹ
ሲሆን አሰልጣኝ መምህራን እነዚህን ጥያቄዎች በማዳበርና ተጨማሪ የፕሮጀክት ስራዎችን በመስጠት
ተማሪዎች እንዲሰሩ ማድረግ ይጠበቃል፡፡

የኮርሱ አጠቃላይ ዓላማዎች


ከዚህ ኮርስ ፍጻሜ በኋላ ሰልጣኞች፡-
 የስምርቅጥ ጽንሰሀሳብንና የካርታለይ አጠቃቀምን ያዉቃሉ
 የአለምንና የኢትዮጵያን ስነመሬታዊ ድርጊቶች ይገነዘባሉ
 የአለምንና የኢትዮጵያን የአየርቅጥ ክልሎችና የስርዓተ ምኅዳር ጽንሰ ሀሳብ ይረዳሉ
 የአለምን ህዝብ ዋና ዋና የስነህዝብ ባህሪያት ይዘረዝራሉ
 የኢኮኖሚ ስርዓቶችንና የኢኮኖሚ እድገት አመልካቾችን ይተነትናሉ
 የኢትዮጵያ የዘመናዊ ማእከላዊ የአጼ መንግስት ምስረታ ሂደትን ያብራራሉ
 የአፍሪካ በቅኝግዛት ቀንበር መዉደቅና ቀደምት ፀረቅኝ ግዛት ትግሎችን ይዘረዝራሉ
 የአፓርታይድ ስርኣት መገለጫዎችን ያብራራሉ
 በአፍሪካ የተመሰረቱ አህጉራዊና ክፍለ አህጉራዊ ድርጅቶችን ይለያሉ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 የዘመናዊዉና የአሁኑ አለም ዋና ዋና የታሪክ ክስተቶችን ይረዳሉ

ምዕራፍ አንድ

የከፍታ ልዩነት በካርታ


መግቢያ
ውድ ሰልጣኞች በመሰረታዊ ማህበራዊ ሳይንስ (BsST101) ስለካርታ ምንነት፣ጠቀሜታ፣የካርታን መስፈርት
በመጠቀም የቦታዎችን ርቀት፣ስፋት እንዲሁም አንድን ቦታ ከሌላ ቦታ አንጻር አቅጣጫን እንዴት ማግኘት
እንደሚቻል ተምራችኋል። በዚህኛዉ መሰረታዊ ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት (BsST222) ደግሞ የገጸ
ምድርን ከፍታና የከፍታ ልዩነት ለመግለጽ የሚያስችሉ ባህላዊ ዘዴዎችና ስምርቅጦች ምንነት፣ ንብብር
ቅልመት፣ የውስን ከፍታ ማሳያ ዘዴች፣ቆለቆሎችና ድፈቶች የሚሉ ርዕሶች ተካተው ይገኛሉ። በመሆኑም
ካርታን በመጠቀም የተለያዩ የመሬት ከፍታዎችን እንዴት መለየት እንደምትችሉ ትማራላችሁ።

ዓላማ
ሰልጣኞች ይህን ምዕራፍ ካጠናቀቃችሁ በሁላ፦
 የገፀ ምድርን ከፍታና የከፍታ ልዩነት ለመግለፅ የሚያስችሉ ባህላዊ ዘዴዎችን ትገልፃላችሁ።
 የስምርቅጦችን ባህሪያት ታብራራላችሁ።
 የውስን ከፍታ ማሳያ ዘዴዎችን ትለያላችሁ።
 የቆለቆል ዓይነቶችን በስዕላዊ መግለጫ ታሳያላችሁ።
 በቆለቆሎችና በድፈቶች መካከል ያለውን ዝምድና ታስረዳላችሁ።

1.1 ከፍታ በካርታ ላይ

 ተግባር 1.1

 ከፍታ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የራሳችሁን ትርጉም አስቀምጡ።

በማንኛዉም የመሬት መዋቅር (ክፍል) ማዕከል ያለ ቦታ ከባህር ወለል በላይ ያለው የጉባጉብ ልዩነት ከፍታ
ይባላል።
የተለያዩ የመሬት ገጽታዎች የከፍታ ልዩነት በካርታ ላይ በተለያዩ መንገዶች ተወክሎ ይገለጻል።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 ተግባር 1.2

 የተለያዩ የመሬት ገጽታዎችን የከፍታ ልዩነት እንዴት በካርታ ላይ መግለጽ ይቻላል?


 እንዴትስ ማንበብና መረዳት ይቻላል?

የተለያዩ የመሬት ገጽታዎችን የከፍታ ልዩነት ካርታ ላይ ለማንበብም ሆነ ለመረዳት በመጀመሪያ የካርታ
ባለሙያዎች የመሬትን ጉባጉብ (ወጣ ገባ) በዝርግ ወረቀት (ካርታ) ላይ የሚወክሉባቸውን መንገዶች ማወቅ
ይገባል። የመሬትን ወጣ ገባ የከፍታ ልዩነት ለመግለጽ የሚያስችሉ ሁለት ዋና ዋና የተለያዩ ዘዴዎች አሉ።
እነሱም ባህላዊ ዘዴዎች (Traditional methods) እና ስምርቅጦች (Contour lines) ናቸው።

1.1.1 ባህላዊ ዘዴዎች (Traditional methods)


የተለያዩ ባህላዊ ዘዴዎችን በመጠቀም የመሬትን (የገጸ ምድርን) የከፍታ ልዩነት በካርታ ላይ መወከል ወይም
መግለጽ ይቻላል። ባህላዊ ዘዴዎች በአራት ይከፈላሉ። እነሱም፦
ሀ. ጥፍተ ምድራዊ ስምር ንድፍ (Physiographic diagram)
ጥንታዊ የካርታ ስራ ባለሙያዎች በተራሮች፣ኮረብታዎች፣ሸለቆዎች እና ሰታቶች መካከል ያለውን የከፍታ
ልዩነት ለማሳየት ጥፍተ ምድራዊ ስምር ንድፍ ዘዴን ይጠቀሙ ነበር። ጥፍተ ምድራዊ ስምር ንድፍ ባለገጠ
ሶስት ገጸ ምድርን ካርታ (ዝርግ ወረቀት ) ላይ ከጎን ወይም ሰያፍ ጎን እንዲታይ አድርጎ የሚወክል ዘዴ ነው።
ጥፍተ ምድራዊ ስምር ንድፍ የካርታ ልዩነት አወካከል ዘዴ ቀላልና ለመረዳት የማስቸግር ቢሆንም የሚከተሉት
ድክመቶች አሉበት።
1 ኛ. አነድን ገጸ ምድር እንደ ስምርቅጦች ከላይ ወደ ታች እንድንመለከት አድርጎ ሳይሆን ከጎን ወይም
ከሰያፍ
ጎድን እንድንመለከት አድርጎ የሚገልጽ መሆኑ።
2 ኛ. የተወሰኑ የገጸ ምድር ክፍሎችን (ቦታዎችን) ከስምር ንድፉ ገጽታ ጀርባ ስለሚሆኑ ድብቅ
አድርጎ የሚያቀርብ መሆኑ።
3 ኛ. የገጸ ምድሩን ትክክለኛ ከፍታና ቆለቆል የማይገልጽ መሆኑ።
4 ኛ. የካርታ መስፈርትን ስለማይጠቀም ትክክለኛነት የሚጎድለው መሆ ናቸው።

 ትኩረት

ጥፍተ ምድራዊ ስምር ንድፍ ዘዴ ጥንታዊ የካርታ ስራ ሙከራ ሲሆን ከላይ በተገለጹት ጉድለቶች
ምክንያት በአሁኑ ጊዜ ጠቀሜታሙ ዝቅተኛ ነዉ።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስዕል 1. ጥፍተ ምድራዊ ስምር ንድፍ

 ተግባር 1.3

 የአካባቢያችሁን ዋና ዋና የገጸ ምድር አይነቶች ዘርዝሩ።


 ጥፍተ ምድራዊ ስምር ንድፍ ዘዴን ተጠቅማችሁ የአካባቢያችሁን የመሬት ቅርጽ ካርታ ላይ
ንደፉ።

ለ. ሽምጥ (Hachures)
ሽምጥ (hachures) ቆለቆሎችን (slopes) በካርታ ላይ ለማሳየት የምንጠቀምባቸው አጫጭር መስመሮች
ናቸው። የሽምጥ መስመሮች የሚሰመሩት የውሃን ፍሰት አቅጣጫ ተከትለው ሲሆን ዋና አገልግሎታቸው
የቆለቆሎችን ድፈት (gradient) ለማሳየት ነው። ነገር ግን ሽምጥ (hachures) መስመሮችን በመጀመሪያ
ጥንታዊ የካርታ ስራ ባለሙያዎች ተራሮችንና ሸለቆዎችን ዝርግ ወረቀት ላይ በቀላሉ ለመንደፍ ይጠቀሙበት
ነበር።

ሽምጥ መስመሮች ጭልጤ ድፈት ቆለቆሎችን (steeper slopes) የሚወክሉ ከሆኑ አጫጭርና ተጠጋግተው
ሲቀመጡ፤ ድኩም ድፈት ቆለቆሎችን (gentle slopes) ሲወክሉ ደግሞ ረጃጅምና ተራርቀው ይቀመጣሉ።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስዕል 2. የሽምጥ መስመሮች ካርታ

ሽምጥ መስመሮች የራሳቸው የሆኑ የሚከተሉት ደካማ ጎኖች አላቸው።


1. ሽምጥ መስመሮች ከባህር ወለል በላይ የቆለቆሎችን ድፈትና ከፍታን በትክክል ማሳየት አይችሉም።
2. በሽምጥ መስመሮች የተወከሉ የተራራ ቁንጮዎችን እና የሸለቆ ወለሎችን መለየት አስቸጋሪ መሆኑ።
ሁለቱን ለይተው ማሳየት አለመቻላቸው።
3. ሽምጥ መስመሮች ሰታቶችን (plains) እና ገበቶችን (plateaus) ለይተው ማሳየት አለመቻላቸው።
4. ጭልጤ ድፈት ቆለቆሎችን የሚወክሉ መስመሮች ተጠጋግተው ስለሚቀመጡ ሌሎች ጠቃሚ የገጸ
ምድር ክፍሎችን በግልጽ እንዲለዩ ማድረግ አለመቻላቸው።
5. ሽምጥ መስመሮችን ካርታ ላይ ማስቀመጥ አድካሚ መሆኑና ለማንበብም ሆነ ለመረዳት አስቸጋሪ
መሆናቸው።

በዚህ ዘመን የሽምጥ መስመሮችን ለብቻቸው ካርታ ላይ መጠቀም እየቀረ ነው። ከዚያ ይልቅ ሽምጥ
መስመሮች የተወሰኑ የገጸ ምድር አይነቶችን ማለትም ዘብጣዘብጥ(escarpment)፣ ገሞራ ቆሬ(crater) እና
ስጥመትን(depression) ለመወከል ከስምርቅጦች ጋር በማቀናጀት ጥቅም ላይ ይውላሉ።

ሐ. ጉባጥለት (Hill-shading)
ጉባጥለት ሌላኛው ካርታ ላይ የከፍታ ልዩነት ወካይ ዘዴ ነው። ጉባጥለት ኮረብታን ወይም ጉባጉብን በካርታ ላይ
የሚያሳየው ከሀሳባዊ የመብራት ምንጭ ነው። የሀሳባዊ መብራት ምንጩ ከካርታው ሰሜን ምዕራብ ማዕዘን
እንደሆነ ይታመናል። ከዚህ አንጻር በካርታው ደቡብ ምስራቅ ላይ የሚገኙ ቆለቆሎች ከሰሜን መዕራብ
ቆለቆሎች ይልቅ የጠቆሩና የተከለሉ ሆነው ይታያሉ።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስዕል 3. ጉባጥለት (Hill-shading)


መ. ቅርጽ መስመሮች (Formlines)
ቅርጽ መስመሮች በካርታ ላይ ተመሳሳይ የከፍታ ነጥብ ያላቸውን ቦታዎች የሚያገናኙ የሀሳብ መስመሮች
ናቸው። ቅርጽ መስመሮች ብዙ ጊዜ ያልተጠናቀቁ ወይም እንደነገሩ የተጠናቀቁ የቅየሳ ስራዎችን ለማሳየት
ካርታዎች ላይ የሚሰመሩ መስመሮች ናቸው። የቅርጽ መስመሮች የባህርን ጥልቀት ማሳየት የሚችሉ ባህላዊ
የካርታ ስራ ዘዴዎች ናቸው።
ቅርጽ መስመሮች ከስምርቅጦች ጋር በጣም የመመሳሰል ባህሪ አላቸው። በመሆኑም ቅርጽ መስመሮች
የግምት ስምርቅጦች ይባላሉ።
ቅርጽ መስመሮች ከስምርቅጦች የሚለዩት በምከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ነው።
1. ቅርጽ መስመሮች ከፍታንና ጥልቀትን በትክክል እንደ ስምርቅጦች ማሳየት አለመቻላቸው።
2. ቅርጽ መስመሮች የመቆራረጥ ባህሪ ሲኖራቸው ስምርቅጦች ግን ተከታታይና ወጥ መሆናቸው።
3. ቅርጽ መስመሮች እንደ ስምርቅጦች ቋሚ ቀጤ ፋታ የላቸውም።
4. ቅርጽ መስመሮች የከፍታ ቁጥሮችን አያሳዩም።

1.1.2 ስምርቅጦች (Contour lines)


አሁን አሁን ብዙ ጊዜ ከፍታንና የከፍታን ልዩነት ለማሳየት የምንጠቀመው ስምርቅጦችን (contour lines)
ነው። የባህር ዳር መስመር (shoreline) ለስምርቅጦች ጥሩ ምሳሌ ነው። ስምርቅጦች ከአማካኝ ባህር ወለል
በላይ (average above sea level) ተመሳሳይ ከፍታ ያላቸውን ቦታዎች የሚያገናኙ የሀሳብ መስመሮች ናቸው።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስዕል 4. (ሀ) የኮረብታ ቦታ ከጎንዮሽ ሲታይ (Side-view of the hilly area)

ስዕል 4. (ለ) የተመሳሳይ ኮረብታ ቦታ ከላይ ሲታይ (Top-view of the same hilly area)

1.1.3 ንብብር ቅልመት/ንቅሰት (Layer Colouring or Layer Tinting)


የከፍታን ልዩነት ቀለማትን በመጠቀም ካርታ ላይ የማሳየት ዘዴ ንብብር ቅልመት/ንቅሰት ይባላል። ከባህር
ወለል በላይ ጀምሮ የተለያየ ከፍታ ያላቸውን ቦታዎች ለማሳየት የቀለም መረጣው በሚከተለው መርህ
ይወሰናል።

 ትኩረት

በጣም ዝቅተኛው የከፍታ ንብር በአረንጓዴ ቀለም ሲቀለም ከዝቅተኛው ቦታ ቀጥሎ ያለው ከፍታ
በቢጫ ቀለም ሆኖ ከፍተኛው ቦታ በቡናማ ቀለም ይቀለማል። በጣም ከፍተኛ ከፍታ ያላቸው
ቦታዎች ደግሞ ጥቁር፣ቀይ፣ሀምራዊ ወይም ነጭ ቀለም በመጠቀም የንብብር ቅልመት ሊሰራ
ይችላል።

ንብብር ቅልመት/ንቅሰት የሚከተሉት ደካማ ጎኖች አሉት፦


1. ንብብር ቅልመት/ንቅሰት የቆለቆልን ቀስ በቀስ ለውጥ (gradual change) አያሳዩም።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

2. ጥልቅ ንብብር ቅልመት/ንቅሰት በከፍተኛ መስፈርት ካርታ ላይ ሌሎችን የገጸ ምድር አይነቶች
የማደብዘዝ ወይም የመሸፈን እድሉ ከፍተኛ ነው። ለአነስተኛ መስፈርት ካርታ ግን ጠቀሜታው የጎላ
ነው።
3. ጥቂት የቀለም አይነቶች ለካርታ አንባቢው የተሳሳተ ግንዛቤን ሊፈጥሩ ይችላሉ። ምሳሌ፦ የአረንጓዴ
ቀለም የቦታውን ለምነት ወይም የደን ሽፋን እንዳለው ግንዛቤ ሊፈጥር ይችላል።
4. ቀለማት የቦታውን የከፍታ ልዩነት እንጅ ሌላ ዝርዝር መግለጫ መስጠት አይችልም።
5. የንብብር ቅልመት/ንቅሰት ካርታዎች ህትመት ውድ መሆናቸው።

1.1.4 የስምርቅጦች ባህሪያት (Properties of Contour Lines)


ካርታን ተጠቅመን የተለያየ ከፍታ ያላቸውን የመሬት ገጽታዎች ለማንበብም ሆነ ለመረዳት በመጀመሪያ
የስምርቅጦችን ባህሪያት ማወቅ ይኖርብናል። በመሆኑም ስምርቅጦች የሚከተሉት ባህሪያት አሏቸው።
1. ስምርቅጦች በካርታ ላይ ከፍታን ለመወከል የምንጠቀምባቸው የሀሳብ መስመሮች ናቸው።
ስምርቅጦች በቋሚ የስምርቅጥ ፋታ የሚሰመሩ፣ እያንዳንዱ ስምርቅጥ ከውስን አማካኝ የባህር
ወለል በላይ ተመሳሳይ ውስን ከፍታ ያላቸውን ቦታዎች የሚያገናኙ መስመሮች ናቸው። የባህር ወለል
በመሬትና በካርታ ላይ የሚገኝ ብቸኛ መስመር ነው።
2. ስምርቅጦች ሁልጊዜም ካርታ ላይ በቋሚ ስምርቅጥ ፋታ ይሰመራሉ። ለምሳሌ ከዚህ በታች በስዕሉ
እንደሚታየው ስምርቅጦች በ 100 ሜትር ስምርቅጥ ፋታ የተሰመሩ መሆናቸውን መመልከት
ይቻላል። በሁለት ተከታታይ ስምርቅጦች መካከል ያለው የከፍታ ልዩነት ቀጤ ፋታ (contour
interval) ወይም ስምርቅጥ ፋታ (vertical interval) ይባላል። ቀጤ ፋታ በአንድ ካርታ ላይ
ሁልጊዜም ተመሳሳይ ሲሆን ይህም በስምርቅጦች የከፍታ ቁጥራቸው ያልተገለጹ ቦታዎችን
ከፍታቸውን ለማስላት ይረዳናል።

ስዕል 5. በስምርቅጦች ላይ ሁለት አይነት የቁጥር አሰጣጥ ዘዴዎች


3. ስምርቅጦች ተከታታይ መስመሮች ሆነው በጥቁር ወይም ቡናማ ቀለም ካርታ ላይ ይታተማሉ።
4. ስምርቅጦች የቦታዎችን ከፍታ ሲገለጹ ሁልጊዜም የከፍታ ቁጥሩ ወደ ሚጨምርበት አቅጣጫ ሆኖ
በሜትር ይገለጻል።
5. ስምርቅጦች በምንም አይነት ቅርንጫፍ የላቸውም፤ አይከፋፈሉም። በካርታ ላይ የተከፈሉ ወይም
ቅርንጫፍ ያላቸው መሰመሮች ስምርቅጦች ሳይሆኑ ወንዞችን፣ መንገዶችን፣ ወሰኖችን ወዘተ
የሚያመላክቱ መስመሮች ናቸው።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

6. ስምርቅጦች ቀጤ ቃጥላ (vetical cliff) ወይም ፏፏቴ (water fall) በሚወክሉበት ጊዜ ካልሆነ
በስተቀር ርስበርሳቸው አይገናኙም፣አይጠላለፉም።

ስዕል 6. ቀጤ ቃጥላ ካርታ ላይ በስምርቅጦች ሲታይ

ስምርቅጦች ሊጠላለፉ የሚችሉበት ልዩ አጋጣሚ ይከሰታል። ይህም እንጥልጥል ቃጥላ (Overhanging


cliff) በሚገኝበት ውስን ገጸ ምድር ላይ ነው። ለምሳሌ ከዚህ በታች በስዕል 7 ስምርቅጦች
ከእንጥልጥል ቃጥላ በታች የሚገኝን ዋሻ (Cave) ሲወክሉ በንድፍና በካርታ ላይ እንዴት
እንደሚቀመጡ ተመልከቱ።

ስዕል 7. እንጥልጥል ቃጥላ ወካይ ስምርቅጦች

7. ስምርቅጦች በአንድ ካርታ ላይ በተለያየ ውፍረት ሊታተሙ ይችላል።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስዕል 8. ስምርቅጦች በተለያየ ውፍረት

8. ስምርቅጦች የቆለቆሎችን ባህሪ ያመላክታሉ። ስምርቅጦች ተራርቀው ሲቀመጡ ድኩም ድፈት


ቆለቆሎችን ሲያመላክቱ በጣም ተቀራርበው ሲቀመጡ ደግሞ ጭልጤ ድፈት ቆለቆሎችን
ያመላክታሉ።

ስዕል 9. ስምርቅጦች ድኩም ድፈት እና ጭልጤ ድፈት ቆለቆሎችን ሲወክሉ

9. ስምርቅጦች ካርታ ላይ የተለያዩ ገጸ ምድሮችን ያሳያሉ። ለምሳሌ ተራሮች(mountains)፣


ገበቶች(plateaus)፣ ኮረብቶች(hills)፣ ሸለቆዎች(valleys)፣ ስጥመቶች(depressions)፣
ድሬዎች(spurs)፣ ተረተሮች(ridges)፣ ጭልጢት ሸለቆዎች(gorges)፣ አንገቶች(cols)፣
አራዳበሮች(passes)፣ ሰታቶች(plains) ወዘተ...። እነዚህ የተለያዩ የመሬት ገጸ ምድሮች ካርታ ላይ
የሚለዩት ከስምርቅጥች ቅርጽ ነው።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

(ሀ) ከንድፋዊ እይታ (ለ) ከስምርቅጦች እይታ


ስዕል 10. የተለያዩ ገጸ ምድሮች በንድፍ እና በስምርቅጥ ሲወከሉ

1.2 የውስን ከፍታ(Specific Height) ማሳያ ዘዴዎች


ስምርቅጦችን በመጠቀም ከፍታንና የከፍታ ልዩነትን በካርታ ላይ ማሳየት (መወከል) እንደሚቻል አይተናል።
በአንድ ስምርቅጥ ላይ ያሉ ነጥቦች ሁሉ ተመሳሳይ ከፍታ አላቸው። ነገር ግን ስምርቅጦች ውስን ከፍታዎችን
(specific heights) ማለትም የተራራ ጫፎችን፣ የኮረብታ ጫፎችን፣ የሸለቆ ወለሎችን፣ የማማዎችን፣
የከተሞችን ወዘተ ከፍታ በተለየ ሁኔታ ሊያሳዩ አይችሉም። ለእነዚህና መሰል የተለያዩ የመሬት ገጽታ
ከፍታዎችን በካርታ ላይ ለማሳየት ወይም ለመወከል የሚከተሉትን ዘዴዎች መጠቀም ይቻላል።

1.2.1 እውቅ ፍታ (Spot Height)


እውቅ ፍታ (spot height) በመንገድ ላይ ወይም በስምርቅጦች መካከል የሚገኝን አንድ የተወሰነ የመሬት
ገጽታ ትክክለኛ ከፍታ በካርታ ላይ ለማሳየት የሚጠቅም ዘዴ ሲሆን ይህም የቦታው ትክክለኛ ከፍታ በደማቅ
ነጥብ ከጎኑ ተገልጾ ይወከላል። ምሳሌ፦ • 3500። እውቅ ፍታዎች በካርታ ላይ እንጅ በትክክለኛው የመሬት
ገጽታ ላይ አይታዩም።

1.2.2.ትሪግኖሜትሪካል ነጥቦች (Trignometrical Points)


በዚህ የውስን ከፍታ ማሳያ ዘዴ ምልክቶች በካርታዎችና በትክክለኛ የመሬት ገጽታዎች ላይ ይቀመጣሉ።
መሀንዲሶች የተመረጡ ቦታዎችን ከፍታ በትክክል በመለካት መሬት ላይ ቋሚ ምልክቶችን ሲተክሉ በካርታ ላይ
ደግሞ በጎነ ሶስት ምልክት ውስጥ ነጥብና የቦታውን ትክክለኛ የከፍታ መጠን ተገልጾ ይቀመጣል።
ምሳሌ፦

1.2.2 ማጣቀሻ (Bench Mark)


የማጣቀሻ ዘዴ በአውራ ጎዳናዎች ወይም በባቡር መንገዶች ላይ የአንድን ውስን ቦታ ትክክለኛ ከፍታ ለመግለጽ
የምንጠቀምበት ዘዴ ነው። ማጣቀሻዎች የአንድን ውስን ቦታ ውስን ከፍታ በአለቶች፣ በጡቦች፣ በተገነቡ ዝርግ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ነሀሶች፣ ወይም በሌላ ምቹ ነገሮች ላይ በማስቀመጥ ለመንገድ ስራ መሀንዲሶችና ለትራንስፖርት አገልግሎት


መረጃን በመስጠት ጠቀሜታቸው ከፍተኛ ነው። ማጣቀሻዎች ካርታ ላይ ደግሞ እንደሚከተለው ይገለጻሉ።
ምሳሌ፦ •BM 1950m

1.2.3 የከፍታ ስሌት (Calculating Altitudes)


በሁለት ተከታታይ ስምርቅጦች መካከል የሚገኝ የአንድ ውስን ነጥብ ወይም ቦታ ውስን ከፍታ ከላይ
በገለጽናቸው መንገዶች ካልተገለጸ በልኬትና ስሌት የምንገልጽበት ዘዴ የከፍታ ስሌት ይባላል። ይህን ዘዴ
የምንጠቀመው በሁለት ተከታታይ ስምርቅጦች ውስጥ የሚገኝ የአንድ ነጥብ ትክክለኛ ከፍታ ለማግኘት
ስንጠየቅ ነው።

ስዕል 10. ስምርቅጦች ከፍታን ሲያሳዩ የካርታ መስፈርት 1: 50,000

 ትኩረት

ካርታውን ተጠቅመን የነጥብ ‘A’ን ከፍታ ለማግኘት የምንከተላቸውን ደንቦች በጥንቃቄ ተመልከቱ።
ሀ. በነጥብ ‘A’ ላይ የሚያልፍ አጭር አቋራጭ ቀጥተኛ መስመር በማስመር ሁለቱን ስምርቅጦች
ማገናኘት
ለ. ያሰመራችሁትን የመስመር ርዝመት መለካት (ምሳሌ 20 ሳ.ሜ)
ሐ. ከታችኛው ስምርቅጥ እስከ ነጥብ ‘A’ ያለውን ርዝመት መለካት (ምሳሌ 15 ሳ.ሜ)
መ. በሁለቱ ስምርቅጦች መካከል ያለውን ስምርቅጥ ፋታ መለየት (የስምርቅጥ ፋታ = 100 ሜ)
ሠ. የነጥብ ‘A’ን ከፍታ እንደሚከተለው መወሰን
600+(15*100)/20 = 675 ሜ ወይም
700+(5*100)/20 =675 ሜ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 ተግባር 1.4

የሚከተሉትን ጥያቄዎች መልሱ


1. ካርታን ተጠቅመን ከፍታን ለማሳየት የምንጠቀምባቸውን ዘዴዎች ዘርዝሩ።
2. ከዚህ በላይ በሚታየው ካርታ ላይ ለተቀመጡ ነጥቦች(ማለትም B፣ C፣ D እና E)የከፍታ ግምት
አሳዩ።
3. ካርታው ላይ ከፍታቸው ከፍተኛና ዝቅተኛ የሆኑ ነጥቦችን አሳዩ።
4. በነጥብ A እና B መካከል ያለውን የመንገድ ርቀት ፈልጉ።
5. የካርታውን አጠቃላይ የቆዳ ስፋት (ground area) አስሉ።
6. በነጥብ A እና ከፍታው ከፍተኛ በሆነው ነጥብ መካከል ያለውን የመስክ ርቀት (ground
distance) ፈልጉ።

1.3 ቆለቆሎችና ድፈቶች


ካርታ ላይ በስምርቅጦች መካከል ያለውን ርቀት በማየት የቆለቆሉ አይነትና የድፈት መጠን ምን ያህል እንደሆነ
መለየት ይቻላል።

 ተግባር 1.5

 የቆለቆሉን አይነት ለመለየት የምንጠቀምበት ዋናው ህግ ምንድን ነው?

ስምርቅጦች ተጠጋግተው የተሰመሩ ከሆነ ቆለቆሉ ጭልጤ ድፈት መሆኑን፤ተራርቀው የተሰመሩ ከሆነ ደግሞ
ቆለቆሉ ድኩም ድፈት መሆኑን በማየት መለየት ይቻላል። የቆለቆሉን የድፈት መጠን ምን ያህል እንደሆነ
ለማወቅ ስንፈልግ በድፈት ስሌት ቀመር ማግኘት ይቻላል።

 ተግባር 1.6

 ድፈት ስሌት ምንድን ነው?

ድፈት አንድ በተወሰነ ገጸ ምድር ወይም በወንዞችና በመንገዶች ላይ በሁለት ነጥቦች መካከል ያለው ርቀት
ቆለቆሉ በምን ያህል ዲግሪ ዥው ያለ(ያጋደለ) መሆኑን የምንገልጽበት የስሌት ዘዴ ነው። ይህም በሁለቱ
ነጥቦች መካከል ያለውን የከፍታ ልዩነት እና ርቀት ግምት ውስጥ በማስገባት ነው።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 ትኩረት

በሁለት ነጥቦች መካከል ያለውን ድፈት ለማስላት የሚከተለውን ቀመር መጠቀም ይኖርብናል።
 ድፈት ንጥጥ = በሁለት ነጥቦች መካከል ያለው የከፍታ ልዩነት ሲካፈል በተመሳሳይ ነጥቦች
መካከል
ያለው የርቀት ልኬት
 ድፈት መቶኛ = ድፈት ንጥጥ * 100
 ድፈት ዲግሪ = ድፈት ንጥጥ * 600

ድፈት በሶስት መንገዶች ይገለጻል። እነሱም፦


1. ንጥጥር፡ በሽቅብታ (አምዳዊ) ጭማሪ (vertical rise) እና በአግድሞሽ ርቀት (horizontal distance)
መካከል ያለውን ዝምድና የምንገልጽበት መንገድ ነው።
ለምሳሌ ፦ 1፡6 ወይም 1/6 ንጥጥር ሲገለጽ በእያንዳንዱ ስድስት ሜትር አግድም ርቀት አንድ ሜትር
ሽቅብታ ወይም አምዳዊ ጭማሪ አለ ማለት ነው።
2. መቶኛ፡ የንጥጥ ውጤትን በ 100 ማባዛት ነው።
ለምሳሌ፦ 1/6 x 100 = 16.7% ሲሆን ይህ ማለት በእያንዳንዱ 100 ሜትር አግድም ርቀት
(horizontal distance) 16.7 ሜትር አምዳዊ ጭማሪ ይኖራል ማለት ነው።
3. ዲግሪ፡ የንጥጥ ውጤትን በ 600 ማባዛት ነው።
ለምሳሌ፦ 1/6 x600 = 100 ሲሆን ይህ ማለት የድፈቱ ቆለቆል በ 10 ዲግሪ ያጋደለ መሆኑ ያሳያል።

 ተግባር 1.7

1. ከዚህ በታች የተሰጡትን የድፈት ንጥጥር ወደ መቶኛና ዲግሪ ለውጡ


ሀ. 1፡200
ለ. 1፡150
ሐ. 1፡50
2. ከዚህ በታች የተሰጡትን የድፈት መቶኛ ወደ ንጥጥርና ዲግሪ ለውጡ
ሀ. 25%
ለ. 40%
ሐ. 15%
3. በተራ ቁጥር 1 እና 2 ከቀረቡት ድፈቶች የትኞች ጭልጤ ድፈቶች የትኞች ደግሞ ድኩም
ድፈቶች ናቸው። ለምን?

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ከዚህ በታች ያለውን ካርታ በማጥናት ድፈትን እንዴት ማስላት እንደሚቻል ሂደቶችን አሳዩ።

ስዕል 11. ስምርቅጦችን ተጠቅመን ድፈትን ማስላት

1.3.1 የቆለቆል አይነቶች (Types of Slopes)


የቆለቆል አይነቶች ብዙ ናቸው፡፡ ዋና ዋናዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል።

ሀ. ትክክል ቆለቆል (even slope)

ከተራራው መነሻ እስከ ተራራው ጫፍ ድረስ እኩል (አንድ አይነት) ድፈት ያለው ቆለቆል ትክክል ቆለቆል
ይባላል። ስምርቅጦች በዚህ ቆለቆል ጊዜ አንዱ ከሌላኛው በእኩል ርቀት ተሰምረው የተቀመጡ ናቸው።

ስዕል 12. ትክክል ቆለቆል(even slope)

ለ. ጉብብ ቆለቆል (Convex Slope)

ከተራራው መነሻ ጭልጤ ድፈት ሆኖ ወደ ተራራው ጫፍ ድኩም ድፈት ያለው ቆለቆል ጉብብ ቆለቆል
ይባላል። ጉብብ ቆለቆል የሚወክሉ ስምርቅጦች ከተራራው መነሻ በጣም ተጠጋግተው፤ ወደ ተራራው ጫፍ
ደግሞ ተራርቀው እናገኛቸዋለን።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስዕል 13. ጉብብ ቆለቆል (Convex Slope)

ሐ. ስርጉድ ቆለቆል (Concave slope)

ከጉብብ ቆለቆል በተቃራኒ ስርጉድ ቆለቆል ተራራው ጫፍ ጭልጤ ድፈት ሆኖ ከተራራው መነሻ ድኩም ድፈት
ያለው ቆለቆል ስርጉድ ቆለቆል ይባላል። ስለዚህ ስርጉድ ቆለቆል ስምርቅጦች ከተራራው መነሻ ተራርቀው
ሲቀመጡ ወደ ተራራው ጫፍ ደግሞ በጣም ተጋግተው እናገኛቸዋለን።

ስዕል 14. ስርጉድ ቆለቆል (Concave slope)

መ. ቆጣቆጥ ቆለቆል (Terraced or Stepped slope)


የቆጣቆጥ ቆለቆል ድፈቱ ብዙ ጊዜ ተለዋዋጭ ሆኖ የደረጃ አይነት ባህሪ አለው። ቆጣቆጥ ቆለቆልን የሚወክሉ
ስምርቅጦች ተቀራርበው እና ተራርቀው በመፈራረቅ ይታያሉ።

ስዕል 15. ቆጣቆጥ ቆለቆል (Terraced or Stepped slope)

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሰ. ዘብጣዘብጥ ቆለቆል (Escarpment)


ዘብጣዘብጥ ቆለቆል ከጭልጤ ድፈት ገጸ ምድር ቀስበቀስ እየቀነሰ ወደሌላኛው ገጸ ምድር የሚሸጋገሩ
ስምርቅጦች የሚወክሉት የቆለቆል አይነት ነው። የገበቶ (plateau) ጭልጤ ድፈት ቆለቆል ሸርተቴ ቆለቆል
(scarp slope) ይባላል። የገበቶ (plateau) ድኩም ድፈት ቆለቆል ደግሞ ድፋት ቆለቆል (dip slope) ይባላል።

ስዕል 16. ዘብጣዘብጥ ቆለቆል (Escarpment)


የገበቶ (plateau) ጭልጤ ድፈት ቆለቆል ሸርተቴ ቆለቆል (scarp slope) ይባላል። የገበቶ (plateau) ድኩም
ድፈት ቆለቆል ደግሞ ድፋት ቆለቆል (dip slope) ይባላል።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ማጠቃለያ
በማንኛውም የመሬት መዋቅር ወይም ክፍል ማዕከል ያለ ቦታ ከባህር ወለል በላይ ያለው የጉባጉብ ልዩነት ከፍታ ይባላል።
የመሬትን ወጣ ገባ የከፍታ ልዩነት ባህላዊ ዘዴዎችን እና ስምርቅጦችን በመጠቀም መግለፅ ይቻላል። ባህላዊ ዘዴዎች
የምንላቸው ጥፍተ ምድራዊ ስምር ንድፍ፣ ሽምጥ፣ ጉባጥለትና ቅርፅ መስመሮች ናቸው። አሁን አሁን ብዙ ጊዜ ከፍታንና
የከፍታን ልዩነት ለማሳየት የምንጠቀምባቸው የሃሳብ መስመሮች ስምርቅጦች ይባላሉ። ነገር ግን ስምርቅጦችን በመጠቀም
ውስን ከፍታዎችን (specific heights) ማለትም የተራራ ጫፎችን፣ የኮረብታ ጫፎችን፣ የሸለቆ ወለሎችን፣ የማማዎችን፣
የከተሞችን ወዘተ ከፍታ በተለየ ሁኔታ ሊያሳዩ አይችሉም። ለእነዚህና መሰል የተለያዩ የመሬት ገጽታ ከፍታዎችን በካርታ ላይ
ለማሳየት ወይም ለመወከል እውቅ ፍታ፣ ትሪግኖሜትሪካል ነጥቦች፣ ማጣቀሻ እና የከፍታ ስሌት ዘዴዎችን በመጠቀም ማሳየት
ይቻላል። ድፈት አንድ በተወሰነ ገጸ ምድር ወይም በወንዞችና በመንገዶች ላይ በሁለት ነጥቦች መካከል ያለው ርቀት ቆለቆሉ
በምን ያህል ዲግሪ ዥው ያለ(ያጋደለ) መሆኑን የምንገልጽበት የስሌት ዘዴ ነው።

የምዕራፉ ማጠቃለያ ጥያቄዎች

1. የገፀ ምድርን ከፍታና የከፍታ ልዩነት ለመግለፅ የሚያስችሉ ባህላዊ ዘዴዎች ጥቀሱ።
2. የስምርቅጦችን ባህሪያት አብራሩ።
3. የውስን ከፍታ ማሳያ ዘዴዎችን በመግለፅ ለእያንዳንዳቸው ተጨባጭ ምሳሌ አቅርቡ።
4. የቆለቆል ዓይነቶችን በስዕላዊ መግለጫ አሳዩ።
5. በቆለቆሎችና በድፈቶች መካከል ያለውን ዝምድና አስረዱ።
ከዚህ በታች በቀረበው ካርታ መሰረት የሚከተሉትን ጥያቄዎች ስሩ።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስዕል 17፡ ጠቃሚ የስምር ቅጦች ባህሪያት

6. የገፀምድሩ የውሃ ተፋሰስ ከየት ወደየት አቅጣጫ እንደሆነ በምክንያት አስረዱ።


7. ካርታውን ተመልክታችሁ የገፀምድሩን ቅርፅ በራሳችሁ ሃሳብ ስላችሁ አሳዩ።
8. ከካርታው ላይ የሚከተሉትን የገፀምድር ክፍሎች አመልክቱ
ሀ/ ከፍተኛውን ቦታ (the highest land)
ለ/ ዝቅተኛውን ቦታ (the lowest land)
ሐ/ ጭልጤ ድፈት (steepest slope)
መ/ ትክክል ቆለቆል (even slope)
ሠ/ ስርጉድ ቆለቆል (concave slope)
ረ/ ጉብብ ቆለቆል (convex slope)
ሸ/ ቆጣቆጥ ቆለቆል (terraced)
9. የ “D” ነጥብ ከፍታ ስንት ነዉ?
10. በነጥብ “A” እና “C” መካከል ያለውን ርቀት አስሉ።
11. ከዚህ በታች በቀረበው ካርታ ላይ ከ (A-G) ያሉትን የስምርቅጦች አቀማመጥ ከ (1-7) ካርታ ላይ
ከተወከሉ የመሬት ገፅታዎች ጋር በማዛመድ የስምር ቅጦችን ስያሜ አስቀምጡ።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስዕል 18፡ የስምር ቅጦች አቀማመጥና የመሬት ገፅታቸው


1. ___________________________________________________________________________
2. ___________________________________________________________________________
3. ___________________________________________________________________________
4. ___________________________________________________________________________
5. ___________________________________________________________________________
6. ___________________________________________________________________________
7. ___________________________________________________________________________

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ምእራፍ ሁለት

የዓለምና የኢትዮጵያ ፊዚካዊ አካባቢ

መግቢያ
በዚህ ምእራፍ ዉስጥ የስነመሬታዊ ጊዜ ሚዛን፣ የኢትዩጵያ ስነመሬታዊ ድርጊቶች፣ የአየር ቅጥ፣ የአለም
የአየር ቅጥ ክፍፍል፣ የኢትዮጵያ አየርቅጥ፣ የአየር ቅጥ ለዉጥና ሊያስከትል የሚችለዉ ጉዳት እና ስርዓተ
ምህዳር የሚሉ ይዘቶች ተካተዋል፡፡ በተጨማሪም እንደ ርእሱ ሁኔታ ተማሪዎችን ሊያሳትፉ የሚችሉ የተለያዩ
የተግባር ስራዎች የተቀረጹ ሲሆን አሰልጣኝ መምህራን እነዚህን ጥያቄዎች በማዳበር ተማሪዎች እንዲሰሩት
ይጠበቃል፡፡

የክፍለ ትምህርቱ አላማዎች


ሰልጣኞች ይህን አብይ ርዕስ ተምራችሁ ካጠናቀቃችሁ በኋላ
 አራቱን ዋና ዋና የመሬት ታሪክ ዘመናት ትዘረዝራላችሁ
 በእያንዳንዱ ዘመን በመሬት ላይ የተካሄዱትን የስነምድራዊና የስነህይወት ድርጊቶችን ትለያላችሁ
 በእያንዳንዱ ዘመን በኢትዮጵያ ምድር ላይ የተካሄዱትን ዋና ዋና ስነምድራዊ ድርጊቶች
ትዘረዝራላችሁ
 በኮፐን የአየር ቅጥ ክፍፍል መሰረት የአለም ዋና ዋና የአየር ቅጥ ክልሎችን ትለያላችሁ
 በኮፐን የአየር ቅጥ ክፍፍል መሰረት በኢትዮጵያ የሚገኙ ዋናዋና የአየር ቅጥ ክልሎችን ትለያላችሁ
 የአየር ቅጥ ለዉጥ መንስኤዎችንና የሚያስከትለዉን ተጽእኖ ታስረዳላችሁ
 ህብረተሰቡ የአየር ቅጥ ለዉጥን ለመከላከል በሚያደርገዉ እንቅስቃሴ ተሳትፎ ታደርጋላችሁ
 በመንግስትም ሆነ በህብረተሰቡ የአየር ቅጥ ለዉጥን ለመከላከል የሚደረገዉን እንቅስቃሴ
ታደንቃላችሁ፡፡
 የስረአተ ምህዳር አባላትን ትዘረዝራላችሁ
 በስረአተ ምህዳር አባለት ስርጭት ላይ ተጸእኖ የሚያሳድሩ ደንቢዎችን ትገልጻላችሁ፡፡

2.1 የስነመሬታዊ ጊዜ ሚዛን / Geological Time Scale/


የስነምድር ተመራማሪዎች መሬት ከተፈጠረችበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያለዉን የ 4.6 ቢሊዮን አመት
ታሪክ በተከታታይ የጊዜ እርከኖች ከፍለዉታል፡፡ ይህ የጊዜ ክፍፍል ስነመሬታዊ የጊዜ ሚዛን ይባላል፡፡ የሁሉም
የጊዜ እርከኖች የጊዜ ርዝመት እኩል አይደለም፡፡ ይህ ሊሆን የቻለዉ የጊዜ ክፍፍሉ የተደረገዉ በተለያዩ ጊዚያት
በመሬት ለይ የተከናወኑ ድርጊቶችን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ነዉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስነመሬታዊ ጊዜ በአራት የጊዜ እርከን ደረጃዎች ይከፈላል፡፡ እነሱም ዘመን /Eon / ክፍለ ዘመን / Era /
ወቅትና/ period/ ክፍለ ወቅት /Epoch/ ናቸዉ፡፡
ዘመን ክፍለ ዘመን ወቅት ክፍለ ወቅት እነዚህ በአንድ ላይ ስነመሬታዊ የጊዜ ሚዛንን
ይመሰርታሉ፡፡
ዘመን / Eon /፡- የመቶ ሚሊዮን አመታት የጊዜ ርዘመት ያለዉ የመጀመሪያዉና በጣም ረዥሙ የስነ መሬታዊ
ጊዜ ክፍፍል ነዉ፡፡ ስነመሬታዊ ጊዜ በአራት ዘመናት ይከፈላል፡፡ እነሱም ትእይንተ ህይወት / phanerozoic /፣
ፕሮትሮይዚክ / protriozoic /፣ አርኪያን / Archean / እና ሀዲያን /Hadean/ ናቸዉ፡፡ እያንዳንዱ ዘመን
እንደገና በክፍለ ዘመናት የተከፋፈለ ነዉ፡፡ ለምሳሌ የስነ መሬታዊ የጊዜ ሚዛንን በሚያሳየዉ ሰንጠረዥ ላይ
እንደምትመለከቱት የትእይንተ ህይወት ዘመን በሶስት ክፍለ ዘመናት የተከፋፈለ ነዉ፡፡ እነሱም የሰብአ፣
የማእከላዊና የዘመነ ጥንተ ህይወት ናቸዉ፡፡
ክፍለ ዘመን / Era / ፡- ይህ ደግሞ ሁለተኛዉ የሰነመሬታዊ ጊዜ ክፍፍል ነዉ፡፡
ወቅት / period /:- ሶስተኛዉ የስነመሬታዊ ጊዜ ክፍፍል ነዉ፡፡
ክፍለ ወቅት / Epoch / ፡- አራተኛዉና ትንሹ የስነመሬታዊ ጊዜ ክፍፍል ነዉ፡፡

በስነምድር ተመራማሪዎች ጥናት መሰረት የመሬት እድሜ ከ 4.5 - 4.6 ቢሊዮን አመት ይሆናል ተብሎ
ይገመታል፡፡ በዚህ ረዥሙ የመሬት እድሜ ዉስጥ ብዙ የተለያዩ ስነመሬታዊና ስነ-ህይወታዊ ድርጊቶች በመሬት
ላይ ተከናዉነዋል፡፡ እነዚህን ድርጊታዊ ክንዋኔዎች በጥልቀትና በዝርዝር ለማጥናት ያመች ዘንድ የስነምድር
ተመራማሪዎች የመሬትን የህይወት ታሪክ በአራት ክፍለ ዘመናት ከፍለዉታል፡፡ እነሱም፡-
ሀ.የቅድመ ካምብራዊ ዘመን/ከ 4.5 ቢሊዮን - 600 ሚሊዮን አመት/
ለ.የዘመነ ጥንተ ህይወት /ከ 600 – 250 ሚሊዮን አመት/
ሐ.የማእከላዊ ዘመን /ከ 250 ሚሊዮን--- 70 ሚሊዮን አመት/ እና
መ.የሰብኣ ዘመን /ከ 70 ሚሊዮን --- አሁን/ ናቸዉ፡፡

እያንዳንዱ ክፍለ ዘመን በወቅቶች የተከፋፈለ ሲሆን ወቅቶች ደግሞ በተለያዩ ክፍለ ወቅቶች የተከፋፈሉ
ናቸዉ፡፡ በእያንዳንዱ ዘመን ክፍፍል የተለያዩ ስነምድራዊና ስነ-ህይወታዊ ድርጊቶች ተካሂደዋል፡፡ እነዘህም
ድርጊቶች የአህጉራትና ዉኃማ አካለት ቅርጽና መገኛ መለዋወጥ፣ የተለያዩ መልክአ ምድሮችና የአለቶች
ስሪት፣ የተለያዩ እንስሳትና እጽዋት ዝግመተ ለዉጥና የተለያዩ የአየር ቅጥ መከሰትን ያካተቱ ናቸዉ፡፡
በመሆኑም እነዚህ ድርጊቶች አንዱን ዘመን ከሌላዉ ለመለየት የሚያስችሉ መነሻ ደንበር ተደርገዉ ይወሰዳሉ፡፡

ሰንጠረዥ-2.1. የስነመሬታዊ ጊዜ ሚዛን


ዘመን / Eon / ክፍለ ዘመን / ወቅት /period / ክፍለ ወቅት /Epoch/ ጊዜ በሚሊዮን
Era / አመት
ሰበብአ ዘመን አራተኛ/Quaternary/ ሆሎሰን 0.01
ትእይን

ህይወ

/Cenozoic ፕሌስቶሴን 1.6



/

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

era/ ሶስተኛ / Teritiary / ፕሌዮሴን 5.3


ማዮሲን 23.7
ኦሊጎሲን 36.6
ኢዮሲን 57.8
ፖሊዮሲን 66.4

የማእከላዊ ክሬታሸስ/cretaceous/
ዘመን 144
/Mesozoic ጁራሲክ 208
era/ ትሪያሲክ 225
ዘመነጥንተህይ ፔሪሚያን 270
ወት ካርቦኒፈረስ 360
/Paleozoic ድቮኒያን 408
phaneorozoic/

era/ ሱሉሪያን 438


ኦርዶቪሺን 505
ካምብሪያን 570
ፕሮተሮዞይክ ቅድመ 2500
/ proterozoic / ካምብራዊ
ዘመን 3900
አርኪያን/
Archen/

/Precambrian
4550
era/
/Hadean/
ሀዲያን

ተግባር 2.1
1.የመሬት ዉጫዊ ገጽታ በየጊዜዉ እንዲለዋወጥ የሚያደርጉ ዉስጣዊና ዉጫዊ ሀይሎች ምን ምን ናቸዉ፡፡
2.የመሬት እድሜ የሚለካባቸዉ መንገዶች ምን ምን እንደሆኑ መጽሀፍ አንብባችሁ ወይም ሰዎችን ጠይቃችሁ ሪፖርት
አቅርቡ፡፡
3.አንዱ ክፍለ ዘመን ከሌላዉ በምን ይለያል?

ሀ. ቅድመ ካምብራዊ ዘመን / ከ 4.5 ቢሊዮን - 600 ሚሊዮን አመት/

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ይህ ዘመን መሬት ከተፈጠረችበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አለፉት 600 ሚሊዮን አመታት ያለዉን ጊዜ ይሸፍናል፡፡
ቅድመ ካምብራዊ ዘመን 88 ከመቶ የሚሆነዉን ስነመሬታዊ ጊዜ ይሸፍናል፡፡ በመሆኑም ቅድመ ካምብራዊ
ዘመን በመሬት የህይወት ታሪክ ዉስጥ እጅግ በጣም ሩቁና የጥንት ዘመን ነዉ፡፡

ስለመሬት ታሪክ ግንዛቤ የምናገኝበት ዋናዉ ዘዴ በተለያዩ ዘመናት በመሬት ላይ በተፈጠሩት አለቶችና ቅሪት
አካላት ላይ ጥናትና ምርምር በማድረግ ነዉ፡፡ በቅድመ ካምብራዊ ዘመን ስለተከናወኑት ድርጊቶች ለማጥናት
መሰረታዊ ችግር የሆነዉ በዚያ ዘመን የተሰሩት አብዛኛዎቹ አለቶች በአሁኑ ጊዜ በአፈር መሸርሸር
መከላታቸዉና ወደ ሌላ አለት በመለወጣቸዉ ምክንያት በቂ መረጃ ማግኘት አለመቻሉ ነዉ፡፡ ይህም በቅድመ
ካምብራዊ ዘመን ስለተከናወኑት ድርጊቶች ያለን እዉቀት ዉስን እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ይሁን እንጅ አንዳንድ
ዛሬ እየተካሄዱ ያሉ ስነምድራዊ ሂደቶች በቅድመ ካምብራዊ ዘመንም ስለመካሄዳቸዉ የሚጠቁሙ መረጃዎች
አሉ፡፡ ለምሳሌ የገሞራዊነት/Volcanism/፣ የአፍር መሽርሸር፣ የአፈር ክምችትና የተራራ ግንባታ ሂደቶች
በቅድመ ካምብራዊ ዘመንም ተካሂደዋል፡፡

መሬት የተሰራችባቸዉ የመጀመሪያዎቹና ጥንታዊ አለቶች ስሪት የተካሄደዉ በቅድመ ካምብራዊ ዘመን ነበር፡፡
በቅድመ ካምብራዊ ዘመን የተሰሩት አለቶች በሌሎች ዘመናት ከተሰሩት አለቶች የሚለዩበት ዋና መለያ ባህሪ
የእንስሳት ቅሪት አካል በዉስጣቸዉ አለመኖሩ ነዉ፡፡ ለዚህም ሁለት መሰረታዊ ምክንያቶች አሉ፡፡ አንደኛዉ
ምክንያት አብዛኛዎቹ የቅድመ ካምብራዊ ዘመን አለቶች ገሞራዊና ልዉጤ አለቶች ነበሩ፡፡ ሁለተኛዉ
ምክንያት ደግሞ በቅድመ ካምብራዊ ዘመን የነበሩት እንስሳት በስስ ቆዳ የተሸፈኑ ስለነበር ለአለቶች ስሪት
የሚሆንና እንደቅሪት አካል ሆኖ በአለቶች ዉስጥ ሊቆይ የሚችል ጠንካራ ቆዳና አጽም አልነበራቸዉም፡፡
በቅድመ ካምብራዊ ዘመን ከተፈጠሩት ጥንታዊ አለቶች መካከከል አብዛኛዎቹ ከነሱ በኋላ በተሰሩ አለቶች
ስለተቀበሩ ልዉጥና ቧልጭታማ አለቶች /metamorphaized and crystalline rocks/ ሆነዋል፡፡

ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት ስነመሬታዊ ድርጊቶች በተጨማሪ እንደ አሜባና ዝልግልግ አሳ /jelly fish/ የመሳሰሉ
ትንንሽ ጥንታዊ ህይወት ያላቸዉ ነገሮች በቅድመ ካምብራዊ ዘመን እንደተፈጠሩ ይታመናል፡፡

ለ.የዘመነ ጥንተ ህይወት /ከ 600 – 250 ሚሊዮን አመት/

ዘመነ ጥንተ ህይወት ከዘመነ ቅድመ ህይወት በመቀጠል በእድሜ ሁለተኛዉ ረዥም ጥንታዊ ዘመን ሲሆን
የጀርባ አጥንት የሌላቸዉ የህይወት ዘመን እየተባለ ይጠራል፡፡ የዘመነ ጥንተ ህይወት ዘመን ለ 375 ሚሊዮን
አመት ያህል የቆየ ነዉ፡፡ ይህ ዘመን ብዙ ስነመሬታዊ ድርጊቶች የተከናወኑበት በመሆኑ በስድስት ወቅቶች
ተከፍሏል፡፡ በእያንዳንዱ ወቅትም የተለያዩ ስነመሬታዊና ስነ-ህይወታዊ ድርጊቶች ተከናዉነዋል፡፡ ለምሳሌ
በዘመነ ጥንተ ህይወት መጨረሻ በፕሌት ቴክቶኒክ ግፊት ምክንያት ሁሉም አህጉራት ተዋህደዉ አንድ አህጉር
መስርተዉ ነበር፡፡ ይህ አህጉር ቅድመ ክፍፍል አህጉር /ዉህድ- አህጉር/ (pangea) ተብሎ ይጠራል፡፡

በመጀመሪያዉ ዘመነ ጥንተ ህይወት ወቅት ህይወት ያላቸዉ ነገሮች የሚገኙት በዉቅያኖሶች ዉስጥና
በዳርቻቸዉ ብቻ ነበር፡፡ በኋላ ግን ህይወት ላላቸዉ ነገሮች አስፈላጊ የሆኑ የከባቢ አየር ይዘቶች ማለትም

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የኦክስጅን፣ የናይትሮጅንና የካርቦንዳይኦክሳይድ መጠን እየጨመረ ሲመጣ ትልልቅ እንስሳትና እጽዋት በየብስ
ላይ እንዲፈጠሩ ምቹ ሁኔታ ተፈጠረላቸዉ፡፡ ዘመነ ጥንተ ህይወት የሚታወቀዉ ብዙ ህይወት ያላቸዉ ነገሮች
የተፈጠሩበት መሆኑ ብቻ ሳይሆን ብዙ ህይወት ያላቸዉ ነገሮች ከምድር የጠፉበት ዘመን በመሆኑ ጭምር ነዉ፡፡
ለምሳሌ በኦረዶቪሲያን፣ በዲቮኒያንና በፐርሚያን ወቅቶች ብዙ ህይወት ያላቸዉ ነገሮች ከምድር ጠፍተዋል፡፡
ይህ ከፍተኛ የህይወት እልቂት ምናልባት በአየር ለዉጥና በእሳተገሞራ ፍንዳታ ምክንያት ሣይሆን አይቀርም
ተብሎ ይገመታል፡፡

ሐ.የማእከላዊ ዘመን / ከ 250 ሚሊዮን - 70 ሚሊዮን አመት /

የማእከላዊ ዘመን ሶስተኛዉ የስነመሬታዊ ዘመን ሲሆን 180 ሚሊዮን አመት ቆይቷል፡፡ ይህ ስነመሬታዊ ዘመን
በሶስት ስነመሬታዊ ወቅቶች ማለትም በትሪያሲክ፣ በጁራሲክና በክሪታሼየስ ወቅቶች በቅደም ተከተል
የተከፈለ ነዉ፡፡ በእያንዳንዱ ወቅትም ብዙ ስነመሬታዊና ስነ ህይወታዊ ድርጊቶች ተከስተዋል፡፡ ለምሳሌ
በትራሲክ ወቅት መጨረሻ ከፍተኛ የፕሌት ቴክቶኒክ እንቅስቀሴ ስለነበር ቅድመ ክፍፍል አህጉር/ዉህድ-
አህጉር/(pangea) ወደ ሁለት አህጉራት ተከፍሎ ነበር፡፡ እነሱም የጎንደዋናላንድ /ደቡባዊ የዉህድ አህጉር ክፍል/
እና ላዉሮዥያ /ሰሜናዊ የዉህድ አህጉር ክፍል/ ተብለዉ ይጠራሉ፡፡ እነዚህ አህጉራት በክሪታሼስ ወቅት
መጨረሻ ተከፋፍለዉ አሁን የምናዉቃቸዉን ሰባት አህጉራት መስርተዋል፡፡ ስእል 2.1 ን ተመልከቱ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስእል- 2.1 የዉህድ አህጉር ክፍፍል

በማእከላዊ ዘመን ዳይኖሰርስና መሰል ተሳቢ እንስሳት በቁጥር ከሌሎች እንስሳት ይበልጡ ስለነበር የማእከላዊ
ዘመን አንዳንድ ጊዜ የተራማጅና የተሣቢ እንስሳት የህይወት ዘመን እየተባለ ይጠራል፡፡ በማእከላዊ ዘመን
የመጨረሻዉ ወቅት ሌላ ሁለት ታላላቅ የስነ-ህይወታዊ ድርጊቶች ተከስተዋል፡፡ እነሱም፡-
 የዳይኖሰርስ ከምድር መጥፋትና
 የአጥቢ እንስሳት፣የአእዋፍና የአበባማ እጽዋት መፈጠር ናቸዉ፡፡

መ.የሠብአ ዘመን (Cenozoic era) ከ 70 ሚሊዮን -አሁን ድረስ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የሰብአ ክፍለ ዘመን አንዳንድ ጊዜ የጡት አጥቢ እንስሳት የህይወት ዘመን እየተባለ ይጠራል፡፡ ይህ የስነመሬታዊ
ዘመን በመሬት ታሪክ ውስጥ እጅግ በጣም የቅርብና የአሁን ዘመን ነው፡፡ የሰብአ ክፍለ ዘመን በሁለት
ስነመሬታዊ ወቅቶች የተከፈለ ሲሁን እነሱም ሶስተኛና አራተኛ ወቅቶች ተብለዉ ይጠራሉ፡፡ ሶስተኛ ወቅት
ከዘሬ 70 ሚሊዮን አስከ 1.6 ሚሊዮን አመታት ያለዉን ጊዜ ሲሽፍን አራተኛ ወቅት ደግሞ ከዛሬ 1.6 ሚሊዮን
እስከ አሁን ድረስ ያለዉን ጊዜ ይሸፍናል፡፡ ልክ እንደሌሎች ወቅቶች በነዚህ ወቅቶችም የተለያዩ ስነመሬታዊ
ድርጊቶች ተካሂደዋል፡፡ ለምሳሌ በሶስተኛ ወቅት በእሳተ ገሞራ የታጀበ የፕሌት ቴክቶኒክ እንቅስቃሴ ተካሒዶ
ዛሬ በመሬት ላይ የምናያቸዉን መልክዓምድሮች እንዲፈጠሩ አድርጓል፡፡ እንዲሁም የትልልቅ ተራራዎች
ግንባታ ሂደት በሰሜን አሜሪካ፣ በእስያና በአዉሮፓ ተካሂዷል፡፡ ለምሳሌ በአዉሮፓ የአልጵስ የተራራ ሰንሰለት፣
በሰሜን አሜሪካ የሮኪ ተራራ፣ በደቡብ አሜሪካ የኤንደስ ተራራ የተፈጠሩት በሰብአ ዘመን በሶስተኛዉ ወቅት
ነበር፡፡

በኳተርናሪ ወቅት ደግሞ በወራጅ ዉሀ፣ በበረዶና በነፋስ አማካኝነት በሶስተኛ ወቅት በተፈጠሩት
መልክአምድሮች ላይ ግጥግጦሽ /denudation/ ተካኂዷል፡፡ እንዲሁም የአየር ቅጥ በከፍተኛ ሁኔታ ቀዝቅዞ
ስለነበር አንድ አራተኛዉ የብሱ የመሬት ክፍል በበረዶ ተሸፍኖ ነበር፡፡ የአሁኑ የሰዉ ልጅ ዝርያ ሆሞሳፒንስ
/Homo Sapiens/ የተፈጠረዉ በአራተኛዉ ወቅት ከዛሬ 500,000 አመታት በፊት ነበር፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ተግባር 2.2
1. በዘመነ ጥንተ ህይወት፣ በማእከላዊና በሰብ ክፍለ ዘመን የተካሄዱ ዋና ዋና ስነመሬታዊ ድርጊቶች ምን
ምን ናቸዉ?
2. የሚከተለዉን ሰንጠረዥ በመመልከት የጎደለዉን ዘመን፣ ክፍለ ዘመን፣ ወቅትና ክፍለ ወቅት
ሙላ/ሙይ
ዘመን /Econ/ ክፍለ ዘመን /Era/ ወቅት/period/ ክፍለ ወቅት ጊዜ በሚሊን
/Epoch/ አመት
የሰብአ ዘመን አራተኛ/Quaternary/ ሆሎሰን 0.01
/Cenozoic era/ ---------- 1.6
ፕሌዮሴን 5.3
---------------- ማዮሲን 23.7
ኦሊጎሲን 36.6
-------------- -------- 57.8
ፖሊዮሲን 66.4

ክሬታሸስ/cretaceous/
--------------- 144
ጁራሲክ 208
ትሪያሲክ 225
ዘመነጥንተህይወት ፔሪሚያን 270
/ Paleozoic era/ ካርቦኒፈረስ 360
---------- 408
ሱሉሪያን 438
----------- 505
ካምብሪያን 570
ፕሮተሮዞይክ ቅድመ ካምብራዊ 2500
/proterozoic/ ዘመን
/Precambrian era/ 3900
------------
4550

-------------

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

2.2 ስነመሬታዊ ድርጊቶች በኢትዮጵያ (Geological events in Ethiopia)

ሀ.በቅድመ ካምብራዊ ዘመን በኢትዮጵያ የተከናወኑ ስነመሬታዊ ድርጊቶች

ይህ ዘመን በኢትዮጵ ላይ በተደጋገሚ የተራራ ግንባታና በጎመራዊ ተግባራት የሚታወቅ ነው፡፡ በቅድመ
ካምብራዊ ዘመን የኢትዮጵያ መሬት ገጽታ በአጐጥጓጭ ላይ ተግባር (intrusive igneous activity) የታጀበ
ከፍተኛ የመሬት መታጠፍ የታየበት ወቅት ነበር፡፡ በግንባታ ተራራ መካከልና ከግንባታ ተራራ በኋላም ቢሆን
ለረዥም ጊዜ የቆየ የግጥ ግጦሽ (denudation) ወቅት ተከስቷል፡፡ ይህ ለረዥም ጊዜያት የቆየ የግጥግጦሽ
ወቅት ከግጥግጦሽ በፊት የተገነቡትን ተራሮች በማጠብ ወደ ሜዳነት ወይም ውስድ ስቶታነት (peneplain)
እንዲቀየሩ አድርጓቸዋል፡
በቅድመ ካምብራዊ ዘመን የተሰሩ አለቶች /ድንጋዮች/ በስነመሬት ተመራማሪዎች የተለያየ ስያሜዎች
ተሰጥቷቸዋል፡፡ እነዚህም የተለያዩ ስሞች ስርጌ ስብጥርጥር /basement complex/፣ ባልጩትና ስርጌ
/crystalline basement / ወይም ስርጌ አለቶች /basement rocks / የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እነዚህ አለቶች
ከእነርሱ በኋላ ለተፈጠሩ አለቶች የመሰረት አለቶች በመሆናቸው እስከ አሁን ከተሰሩት አለቶች ሁሉ ረዥም
እድሜ ያስቆጠሩ ናቸው፡፡ የቅድመ ካምብራዊ ዘመን አለቶች በቅርብ ዘመን በተሰሩ አለቶች ውስጥ ተቀብረው
የሚገኙ ቢሆንም በላያቸው ላይ ባሉ አለቶች ሽርሽር /እጥበት ምክንያት/ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች
ማለትም በሰሜንና በመካከለኛው ትግራይ፣ በመተከል አሶሳ፣ በከፊል የኤሊባቡርና የአባይ ጭልጢት ሸለቆ፣
በመካከለኛው ሲዳሞ፣ በደቡብ ኦሞ እና በተወሰኑ የባሌና የምስራቃዊ ሐረርጌ ቦታዎች ተጋልጠው ይገኛሉ፡፡
በአጠቃላይ በቅድመ ካምብራዊ ዘመን በኢትዮጵያ የሚከተሉት ዋና ዋና ስነመሬታዊ ድርጊቶች የተካሄዱበት
ዘመን ነው፡፡
 በከፍተኛ የመሬት እንቅስቃሴ ምክንያት የትልልቅ ተራራዎች ግንባታ
 ገመራዊ ተግባራት በተለይ ገሞራዊ አጐጥጓጭ ግይ/volcanic intrusion /
 የአለቶች ልውጠት /metamorphism/ እና
 ተከታታይ የሆነ የግጥግጦሽ ሂደቶች ናቸዉ፡፡
ለ. በዘመነ ጥንት ህይወት በኢትዮጵያ የተካሄዱ ስነመሬታዊ ድርጊቶች

በዘመነ ጥንት ህይወት ምንም አይነት ግንባታ ተራራ ያልተካሄደበት ዘመን ሲሆን ዋና የስነመሬታዊ ሂደት
የነበረው ተከታታይነት ያለው ግጥግጦሽ /continuous denudation/ ነበር፡፡ በዚህም የተነሣ በቅድመ ካምብራዊ
ዘመን የተሰሩት ትልልቅ ቅልብሽ ተራሮች /huge fold mountains/ ለከፍተኛና ለረዥም ጊዜያት ለቆየ
ግጥግጣሽና ለውሰድ ስቶታነት ተዳርገዋል፡፡ እንዲሁም የእነዚህ ቅልብሽ ተራራ ሰንሰለቶች ወደ ውስድ ሰቶታ
ወይም ቅድመ ካምብሪያዊ አለት ወለል ተመልሰዋል፡፡ በዘመነ ጥንት ህይወት በተካሄደው ተከታታይነት ያለው
ግጥግጦሽ ምክንያት የተፈጠሩት ደለሎች ኢትዮጵያ ዉስጥ ለአለቶች ምስረታ የሚሆን የደለል ክምችት
ሳይቀር ከምስራቅ አፍሪካ /ከአፍሪካ ቀንድ/ ወደ ደቡብና ምስራቅ አቅጣጫ ተወስደው የደቡባዊ አፍሪካንና
የመካከለኛው ምስራቅን ባህርማና አህጉራዊ ደለል ፈጥረዋል፡፡ በዚህም የተነሳ በዘመነ ጥንት ህይወት
በኢትዮጵያ የአለት ምስረታ ሄደት አልተካሄደም፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሐ.በማዕከላዊ ዘመን በኢትዮጵያ የተካሄዱ ስነመሬታዊ ድርጊቶች

በማእከለዊ ዘመን ጊዜ የአሁኑ የአፍሪካ ቀንድና የአረብ የመሬት ክፍል ተፈራራቂና ዘገምተኛ በሆነ የመሬት
ስርገትና መነሳት /የመሬት ከፍ ዝቅ/ ሂደት የታየበት ዘመን ነበር፡፡ በተመሣሣይ ሁኔታ ያለምንም የመሬት
መታጠፍና መሰንጠቅ በግንባታ ተራራ የታጀበ ከደቡብ ምስራቅ ወደ ሰሜን ምእራብ ያጋደለ የመሬት
አቀማመጥ ሁኔታ የተንፀባረቀበት ወቅት ነበር፡፡ ይህ የመሬት እርፋታ /subsidence / በአፍሪካ ቀንድ የጀመረው
በቀዳማዊ የማእከለ ዘመን ክፍለ ወቅት የዛሬ 225 ሚሊዮን አመት ገደማ አካባቢ ነበር፡፡ የደቡብ ምስራቅ
አካባቢ ቀስ በቀስ ሲሰምጥም የባህር ሞገድ ከሶማልያና ኦጋዴን አካባቢ ጀምሮ ቀስ በቀስ ወደ ሰሜን ምእራብ
በውሀማ አካል ተጥለቀለቀ፡፡ ይህ በምድር ዝቅ /ስጥመት/ የተጀመረዉና ከደቡብ ምስራቅ ወደ ሰሜን ምእራብ
የተደረገ እልፈት ባህር /transgration of sea / እስከ ሁለተኛው የማእከለ ዘመን ወቅት /Jurassic period /
ቀጥሏል፡፡ በዚያን ጊዜ የባህሩ ወሀ ወደ መሬታማው አካል እየተስፋፋ ሲሄድ ከውቅያኖሱ ወደ መሬት አካል
የተወሰደዉ አሸዋማ አፈር ቅድመ ካምፔራዊ አለቶች/ ስርጌ ስብጥርጥር አለቶችን/ በደለል አለበሳቸው፡፡
በተጨማሪም ከጊዜ ቆይታ በኋላ የውሃው ጥልቀት እየጨመረ ሲመጣ በቀድሞ አሸዋ ላይ ተጨማሪ ብሃ
/ድንጋይ/ (shale)፣ ጀሶ( gypsum) እና ኖራ (lime) በላዩ ላይ ሊደረብበት ችሏል፡፡ በጊዜ ብዛት የተደራረቡት
አሻዋና ኖራ እርስ በርሳቸው በመጠባበቅ አሸዋ ድንጋይ (sandstone) እና ኖራ ድንጋይ በቅደም ተከተል ከስር
ወደ ላይ በመሆን ሊፈጠሩ ችለዋል፡፡ እነዚህን የቆዩ የውሃማ ዝቃጭ (ደለል) ንጣፍ መጀመሪያ ላይ በተገኙበት
የቦታ ስም መነሻ በማድረግ በቅደም ተከተል የአድግራት አሸዋማ ድንጋይና የሂንታሉ የኖራ ድንጋይ ተብለው
ይጠራሉ፡፡

በመጨረሻው የማእከላዊ ዘመን ወቅት (cretaceous period) የአፍሪካ ቀንድ መሬት ወደ ላይ በመነሳቱ
ምክንያት የአብዛኛው መሬት ከባህር ወለል በላይ ከፍታ ጨምሯል፡፡ ይህ ሁኔታ ከሰሜን ምእራብ ወደ ደቡብ
ምስራቅ የባህር ሽሽ (sea regrasstion) ክስተትን አስከትሏል፡፡ በዚህ የባህር ሽሽ ሌላ የጀሶ፣ የበሃ (shale) እና
የአሸዋ በሂንታሎ የኖራ ድንጋይ ላይ ተደርበዋል፡፡
ይህ የላይኛው የመጨረሻ የማእከለ ዘመን የደለል (ዝቅጠት) አለት የላይኛዉ አሸዋማ ድንጋይ /upper
sandstone/ እየተባለ ይጠራል፡፡

በስተመጨረሻ የማእከለዊ ዘመን የብሱ የመሬት ክፍል ከውኃማዉ አካል ወደ ላይ ሲወጣ 3 ዋና ዋና ደለል
አለቶች በቅድመ ካምብራዊ አለቶች /ስርጌ ስብጥርጥር/ ላይ ተደርበው ሊፈጠሩ ችለዋል፡፡እነዚህ የጥንት
ባህርማ የደለል አለቶች

1.የአድግራት ታችኛዉ አሸዋማ ድንጋይ - የጥንት 2.የሂንታሎ የላይኛዉ አሸዋማ ድንጋይ


የኖራ ድንጋይ የሂንታሎ የኖራ ድንጋይ
3.የላይኛው አሸዋማ ድንጋይ ተብለው ይጠራሉ - /የቅርብ/ የአድግራት አሸዋማ ድንጋይ
ስርጌ ስብጥርጥር

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የመሬታማው አካል ከአልፋተ ባህርና ባህርሽሽ ቀድሞ በማገደሉ ምክንያትና ከዚያ በኋላ በተካሄደው የእልፈተ
ባህርና ባህረ ሽሽ አቅጣጫ ሂደት የአሸዋማ አለቶች እድሜና ውፍረት ከደቡብ ምስራቅ እስከ ሰሜን ምእራብ
ይለያያል፡፡
 የአድግራት አሸዋማ ድንጋይ በእድሜውና በውፍረቱ በደቡብ ምስራቅ ትልቅ ሲሆን ወደ ሰሜን
ምእራብ አቅጣጫ ስንጓዝ እድሜውና ውፍረቱ እየቀነሰ ይመጣል፡፡
 የላይኛው አሸዋማ ድንጋይ በደቡብ ምስራቅ ወፍራምና በእድሜው ትንሽ ሲሆን በሰሜን ምእራብ
ደግሞ በእድሜው ትልቅና በውፍረቱ ደግሞ ስስ ነው፡፡

የእልፈተ ባህር ክስተትና የማእከለ ዘመን ደለል አለቶች አብዛኛዉን የኢትዮጵያ ክፍል ያካተቱ (የሸፈኑ) ሲሆን
እስከ ማእከላዊ ትግራይና የምእራባዊ ከፍተኛ ቦታዎች ምእራባዊ ግድለት(slope) የከለሉ ነበር፡፡ አብዛኛወቹ
የማእከላዊ ዘመን ደለሌ አለቶች በስብአ ዘመን አለቶች ስር ተቀብረው ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ግን የማእከዊ ዘመን
ቀደምት ባህርማ ደለሌ አለቶች በደቡብ ምስራቅ ዝቅተኛ ቦታዎች (ኦጋዴንና ሶማሊያ) በስፋት በመሬት ገጽ
ላይ ይገኛሉ፡፡ በሌሎች ቦታዎችም ለምሳሌ በማከላዊ ትግራይ፣ በአባይ ጭልጠት (Gorges of Abay) እና በዋቢ
ሸበሌ ተጋልጠው ይገኛሉ፡፡
የማእከላዊ ዘመን የደለሌ አለቶች ስሪት በኢትዮጵያና በአፍሪካ ቀንድ የተካሄደበት ክፍለ ዘመን ነዉ፡፡

መ. በሰብአ ዘመን በኢትዮጵያ የተካሄዱ ስነመሬታዊ ድርጊቶች

በዚህ ዘመን በኢትዮጵያ የተከናወኑት ስነመሬታዊ ክስተቶች በሚከተሉት 3 ዋና ዋና ስነመሬታዊ ድርጊቶች


ይመደባሉ፡፡ እነሱም፡-

ሀ. የኢትዮጵያ አረቢያ መሬት ወደላይ መነሳትና ብዙ መጠን ያለው ጎመራ ትፍ ወደ ውጭ መፍሰስ፡፡


ለ. የትልቁ ስምጥ ሸለቆ መፈጠርና
ሐ.የኳተርናሪ ገሞራዊ ቡልቅሉልቆችና ዝቅጠቶች/Quaternary volcanic eruptions and depositions/
መከናወን ናቸው፡፡

ሀ. የኢትዮጵያ - አረቢያ የመሬት ክፍል ወደ ላይ መነሳትና ብዙ መጠን ያለው ትፍ ወደ ውጭ መፍሰስ


የመጀመሪያዉ የሠብአ ዘመን ወቅት (Teritary period) በአፍሪካ ቀንድ በጣም ከፍ ያለ (ግዙፍ የሆነ) መሬት
ወደላይ የተነሳበት ወቅት ነበር፡፡ ይህ የመሬት መነሳትም እስከ 2000 ሜትር ከፍታ የተነሳ እንደ ነበር በዘርፉ
የተሰማሩ ሙህራን ይገልጻሉ፡፡ ይሁን እንጅ እጅግ በጣም ከፍተኛ የሆነ የመሬት ወደላይ መነሳት የታየው
በማእከላዊ የኢትዮጵያ ክፍል እንደሆነ ይገለጻል፡፡

የኢትዮጵያ መሬት ከቅድመ ካምብራዊ ዘመን ጀምሮ ለተለያዩ የውጫዊና ውስጣዊ ሃይሎች ተጋልጧል፡፡ ይህ
ቀጣይነት የነበረው የመሬት ግልጦሽ የኢትዮጵያን የመሬት አካል እንዲሰነጠቅ አድርጓታል፡፡ በነዚህ ትልልቅ ሰፊ
የመሬት ስንጥቆች በርካታ መጠን ያለው ትፍ (lava) ከመሬት ውስጥ ወደ ውጭ እንዲፈስ አስቻለው፡፡ በመሬት
ውጫዊ ክፍል የፈሰሰው ትፍ ተደራራቢ የሆኑ አለቶችን ፈጥሯል፡፡ እነዚህ ተደራራቢ አለቶች ክምሬ ረድፎች

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ትፍ ወይም ገች አለት (Trappean series of lava or trap rock ) ወይም ኮተቤ (bassal) እየተባሉ ይጠራሉ፡፡
እነዚህ አለቶች በማአከለዊ ዘመን የተፈጠሩትን ውሃማ (ባህርማ) ደለል አለቶች በማልበስ የኢትዮጵያ ገብቶን
(plateau) ፈጠሩ፡፡

ለ. የስምጥ ሸለቆ መፈጠር


ሃይለ ውጥረት (tensional force) የሚባለው በውስጣዊ ሃይል ምክንያት የመሬት ቅርፊት ወደ ተቃራኒ
አቅጣጫ የሚደረግን እንቅስቃሴ ሲሆን ይህ ሃይለ ዉጥረት ለስምጥ ሸለቆ መፈጠር አይነተኛ መንገድ ነው፡፡
ይህ ማለት ስምጥ ሸለቆ የተፈጠረው በውስጣዊ ሃይል ምክንያት አለቶች በተቃራኒ አቅጣጫ ወደጎን
ተገፍተው ሲለያዩና በመካካል ያለው ቦታ ወደታች ሲሰምጥ ነው፡፡
የአለም ትልቁ ስምጥ ሸለቆ የሚባለው ከሰሜን ምስራቅ ፍልስጤም (ጆርዳን) አንስቶ እሰከ ደቡብ ምስራቅ
ማላዊ-ሞዛምቢክ በመዝለቅ 7200 ኪ.ሜ ርቀት ይሸፍናል፡፡ ከዚህ 7200 ኪ.ሜ ርቀት ውስጥ 5600 በአፍሪካ
ሲገኝ 1700 ኪ.ሜ ደግሞ በኢትዮጵያና ኤርትራ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ እጅግ በጣም ሰፊው የስምጥ
ሸለቆ አካል የሚገኘው በአፋር ጎነሶስት ክልል ውስጥ ነው፡፡ ይህ የአፋር ጎን 3 ክልል የስምጥ ሸለቆ ዋና ዋና
ክፍሎች ማለትም የቀይ ባህር፣ የኤደን ወሽመጥ (Gulf of Aden) እና የኢትዮጵያ ዋና ስምጥ ሸለቆ አካል
የሚገናኙበት ቦታ ነው፡፡
የስምጥ ሸለቆ መፈጠር የሚከተሉት የመልከአ ምድር ገጽታዎች እንዲኖሩ አስችሏል፡፡
1.የኢትዮጵያን ገበቶ (Ethiopian plateau) በሁለት ክፍሎች እንዲከፈሉ አድርጓል
2.የአረቢያን የባህር ወሽመጥ ከአፍካ ቀንድ ለያይቷል
3.ሙት ባህር፣ ቀይ ባህርና የኤደን ስምጥ ወሽመጥ እነዲፈጠሩ ሆኗል
4.የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች የተፈጠሩባቸው ዋዲያቶዎችና ስምጥ መፈጠር ናቸዉ፡፡

ሐ. የኳተርነሪ ገሞራ ኩሊቆችና ዝቅጠቶች /Quaternary volcanic Eruptions and Depositions/


የኳተርነሪ ገሞራ ኩሊቆች የቅርብ ጊዚያት የጎመራዊ ክስተቶች (ተግባራት) ሲሆኑ ከስምጥ ሸለቆ መፈጠር
በኋላ የተካሄዱ ናቸው፡፡ እነዚህም የንጥነጣና / tectonic / እና የገሞራ / volcanic/ ሂደቶች ሲሆኑ ስምጥ ሸለቆ
እንዲፈጠር ያደረጉ ሃይሎች ቀጣይ ክፍሎች ናቸው፡፡ በኳታርነሪ ወቅት የተከሰቱት ገሞራዎች የኤደን
ጎመራዎች (Aden volcanics) ወይም የቅርብ ገሞራዎች (recent volcanics) ወይም የኤደን ድርድር ትፍ
(Aden series lava) ተብለው ይጠራሉ፡፡
በኳተርነሪ ገሞራዊ ተግባር የተፈጠሩት የኤደን ድርድር ትፍ ዋና ዋና ገጽታዎች አሏቸው፡፡ እነዚህ አበይት
ገጽታዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡
 ገሞራ ኮረብታና ተራራ
 ገሞራዊ ምድያት (caldera)
 ገሞራ ትፍ ተርተር ወዘተ ናቸው፡፡
ሌላዉ በኳታርነሪ ወቅት የተከናወነ ስነመሬታዊ ሂደት ከኳተርነረ ዝቅጠቶች የዝቅጤ ንብርብሮች
/sedimentary layers/ መፈጠር ነው፡፡ እነዚህ በቅርብ ጊዚያት የተፈጠሩ የኳተርነር ንብርብሮች የተለያዩ
ስሞች ተሰጥቷቸዋል፡፡ አንዳንዶች የኳተርነር ዝቅጠት ሲሏቸው፡፡ ሌሎች ደግሞ የቅርብ ዝቅጦች ይሏቸዋል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

እነዚህ ዝቅጠቶች በሚገኙበት ቦታና በአፈጣጠራቸዉ ሂደት መሰረት በሚከተሉት ምድቦች ይከፈላሉ፡፡
እነዚህም፡-
 ወንዛዊ ዝቅጠቶች / fluvial deposits /፡- በወንዝ ዳርቻ የሚገኙ ደለሎች
 ሀይቃማ ደለሎች / lacustrine deposites/:- በሀይቅ ተሸፍኖ በነበረ ቦታ ላይ የሚፈጠሩ ደለሎች
 ነፋሳዊ ክምቹ / aeolaine deposits /፡- በነፋስ አማካኝነት በዝቅተኛ ቦታዎች ላይ የሚፈጠሩ
ደለሎች
 የበረዶ ዝቅጠቶች / glacial deposit /፡- የበረዶ ክምችት
 ባህርማ ደለሎች /marine deposits/፡- በባህር ተሸፍኖ በነበረ ቦታ ላይ የሚገኙ ደለሎች ይባላሉ፡፡

የኳታርነር ወቅት በመካካለኛውና በከፍተኛ ኬክሮስ ክልል ውስጥ የመጨረሻዉ የበሮደ ዘመን እየተባለ ሲጠራ
በሞቃታማው (ሃሩር) ክልል ደግሞ የዘመነ ዝናብ (Pluvial period) እየተባለ ይጠራል፡፡

ሰንጠረዝ- 2.2 የኢትዮጵያ ስነመሬታዊ ድርጊቶች ማጠቃለያ


ክፍለ ዘመን ወቅት ክፍለ ወቅት እድሜ ዋና ዋና ስነመሬታዊ ድርጊቶች

አራተኛ የቅርብ 100 000 - የቅርብ ዝቅጠቶች በባህር ዳርቻ


መፈጠር
- ሀይቃማ ደለሎች በሀይቆች አካባቢ
መፈጠር
- የነፋሳዊ ደለሎች በበረሀማ ቦታዎች
መፈጠር
- የወንዛዊ ዝቅጠቶች በወንዞች ዳርቻ
መፈጠር
- የኤደን ገሞራዊ ትፍ በስምጥ ሸለቆና
በደቡባዊ ጣና መከሰት ናቸዉ፡፡
ፕሌስቶሴን - የወንዛዊ ዝቅጠት፣ ሀይቃማ ደለሎችና
የበረዶ ዝቅጠት መፈጠር
- በአፋር አካባቢ ሀይቆች ከተፈጠሩ
በኋላ ዉሀቸዉ በትነት ደርቋል፡፡
- በአፋር አካባቢ የገሞራዊ ተግባር
1 ሚሊዮን ተከስቷል፡፡
ሶስተኛ/Teritiary/ ፕሌዮሴን

ማዮሲን 11 ሚሊዮን -በማእከላዊ ኢትዮጵያ የመሬት ስንጥቅ


ተከስቷል፡፡ በዚህም ምክንያት
የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ ተፈጥሯል፡፡
ኦሊጎሲን 25 ሚ -በመሬት ስንጥቆች በርካታ መጠን ያለዉ
ትፍ ከመሬት ዉስጥ ወደ ዉጭ ፈሷል፡፡ ወደ
ዉጭ በፈሰሰዉ ትፍ የክምሬ ረድፍ ትፍ
ወይም የኮተቤ አለቶች ተፈጥረዋል፡፡
ኢዮሲን -የኢትዮጵያ ገበቶ እስከ 2000 ሜትር ከፍታ
ሰብኣ

40 ሚሊዮን ወደላይ ተነስቷል፡፡


ፓሊዮሲን -የኢትዮጵያ ገበቶ ወደላይ መነሳት ቀጥሏል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ክሬታሸስ/ 60 ሚ -ሰምጦ የነበረዉ መሬት ወደላይ


cretaceous/ መነሳት፣የባህር ሸሽና የላይኛዉ አሸዋማ
70 ሚ ደንጋይ መፈጠር ድርጊቶች ተከናዉነዋል፡፡
ጁራሲክ -ከደቡብ ምስራቅ ወደ ሰሜን ምአራብ
የተካሄደዉ እልፈተ ባህር ተባብሶ መቀጠልና
የሂንታሎ የኖራ ደንጋይ መፈጠር ድርጊቶች
135 ሚ ተከናዉኗል፡፡
ትሪያሲክ
ማዕከላዊ

-ከደቡብ ምስራቅ ወደ ሰሜን ምአራብ


የተደረገ እልፈተ ባህርና የአዲግራት አሸዋማ
ደንጋይ መፈጠር ድርጊቶች ተከናዉኗል፡፡
180 ሚ -ለረዥም ጊዚያት የቆየ ግጥግጦሽና ዉስድ
ስታቶነት ድርጊቶችተካሂደዋል፡፡

225 ሚ
ዘመነ ጥንተ
ህይወት

-በዚህ ዘመን ስለተካሄዱት ድርጊቶች በዙ


ካምብራዊ

ባይታወቅም ተከታታይነት ያለዉ ገሞራዊ


ተግባር፣ የአፈር መሽርሸራና ክምችት
ቅድመ

ዘመን

ድርጊቶች ተካሂደዋል ተብሎ ይገመታል፡፡


600 ሚ

ተግባር 2.3
1.በቅድመ ካምብራዊ ዘመን፣ በዘመነ ጥነተ ዘመን፣ በማእከላዊና በሰብአ ክፈለ ዘመን በኢትዮጵያ የተካሄዱ ስነመሬታዊ
ድርጊቶችን ዘርዝሩ፡፡
2.የስምጥ ሸለቆ አፈጣጠር ሂደትን አስረዱ፡፡
3.የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ ያልተረጋጋዉ የኢትዮጵያ ክፍል ለምን ተባለ?
4.የኢትዮጵያን ስምጥ ሸለቆ የሚያሣይ ካርታ ሰርታችሁ ለአሰልጣኝ መምህራችሁ አሳዮ፡፡

2.3 አየር ቅጥ /Climate /


አየር ጠባይ / weather /:- ከቀን ወደ ቀን ከሳምንት ወደ ሳምንት በከባቢ አየር ዉስጥ የሚታዩ የሚትሮሎጅ
ክስተቶችን ለምሳሌ የዝናብ፣ የደመና፣ የጠንካራ ነፋስ፣ የሙቀት፣ የቅዝቃዜ፣ ወዘተ ሁኔታን ለመግለጽ
የምንጠቀምበት ቃል ነዉ፡፡ አየር ጠባይ ስንል ባጭሩ በአንድ አካባቢ በየሠኣቱ፣ በየቀኑና በየወቅቱ የሚከሰት
የአየር ሁኔታ ማለት ነዉ፡፡

አየር ቅጥ፡- አየር ቅጥ ማለት በአንድ አካባቢ ለብዙጊዜ ተደጋግሞ የሚከሰት አየር ጠባይ ነዉ፡ የአየር ጠባይ
ለረዥም ጊዜ ሲጠናቀር አየር ቅጥ በመባል ይታወቃል፡፡ አብዛኛዉን ጊዜ የአንድ አካባቢ የአየር ቅጥ የሚገለጸዉ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ለረዥም ጊዜ የተመዘገበን የአየር ሙቀት፣ የዝናብ መጠን፣ የአየር ርጥበት፣ የነፋስ ፍጥነት፣ ወዘተ መረጃን
ስታስቲካዊ ባህሪ ለምሳሌ ( አማካይ ዉጤት) በማስላት ነዉ፡፡

በዓለም ላይ ብዙ አይነት የአየር ቅጦች ይገኛሉ፡፡ እነዚህ የተለያዩ የአየር ቅጥ ሁኔታዎች የሚፈጠሩት
በየአካባቢዉ በሚለዋወጡ የአየር ቅጥ እና የአየር ጠባይ ይዘቶች ነዉ፡፡ የአየር ቅጥ እና የአየር ጠባይ ይዘቶች
የአንድን የተወሰነ ቦታ የካባቢ የአየር ቅጥ ሁኔታዎችን የሚፈጥሩ ክስተቶች ናቸዉ፡፡ እነሱም ልከ ሙቀት፣
ዝናብ፣ የአየር ግፊት፣ ነፋስና የፀሀይ ብርሀን ናቸዉ፡፡ በሌላ በኩል እነዚህን የአየር ቅጥ ይዘቶች በተለያዩ ቦታዎች
ልዩነት እንዲኖራቸዉ የሚያደርጉ የአየር ቅጥ ተቆጣጣሪዎች አሉ፡፡ እነሱም የመሬት ከፍታ፣ የኬክሮስ ልዩነት፣
ከባህር መራቅ ወይም መቅረብ፣ የአየር ግፊት መለያየት፣ የዉቅያኖስ ሞገድ ወዘተ… ናቸዉ፡፡

ተግባር- 2.4
1.በአየር ቅጥና በአየር ጠባይ መካከል ያለዉን አንድነትና ልዩነት አስረዱ፡፡
2.እያንዳንዱ የአየር ቅጥ ተቆጣጣሪ በአየር ቅጥ የሚያሳድረዉን ተጽእኖ ምሳሌ በመስጠት አብራሩ፡፡
3.የእያንዳንዱን የአየር ቅጥ ይዘት ምንነት ግለጹ፡፡
4.የአየር ቅጥ በሰዉ ልጅ ኑሮ ላይ እንዴት ተጽእኖ እንደሚያሳድር አብራሩ፡፡

2.3.1 የአለም የአየር ቅጥ ክፍፍል / World’s climate classification/

የአለምን አየር ቅጥ በተለያዩ ምድቦች መከፋፈሉ ጥቅሙ ምንድን ነዉ?


የአየር ቅጥ እና የአየር ጠባይ ይዘቶች ስርጭት ከቦታ ቦታና ከጊዜ ጊዜ ይለያያል፡፡ በመሬት ላይ በሁለት ቦታዎች
ፍጹም ተመሳሳይ የሆነ የአየር ሁኔታ የመኖሩ ጉዳይ አጠራጣሪ ነዉ፡፡ በመሬት ላይ ለመቁጠር የሚያዳግት
የተለያየ ገጽታ ያላቸዉ በርካታ ቦታዎች መኖር የአየር ቅጥ አይነትና ብዛትም በዚያዉ ልክ ከፍተኛ እንዲሆን
አድርጎታል፡፡ ይህም የአየር ቅጥ መረጃዎችን ዉስብስብና ለአጠቃቀም አስቸጋሪ እንዲሆኑ አድርጓል፡፡

ይህ በመሬት ላይ የአየር ቅጥ ከቦታ ቦታ ልዩነት የሚያስከትለዉን የአየር ቅጥ መረጃ ዉስብስብነትና


የአጠቃቀም ችግር ለማቃለል ይቻል ዘንድ የአየር ቅጥን ለመከፋፈል የሚያስችሉ ዘዴዎችን መቀየስና
ተመሳሳይ ባህሪያት ያላቸዉን አየር ቅጦች በአንድ ምድብ / ክልል/ መመደብ አስፈላጊ መሆኑን የዘርፉ
ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በአጠቃላይ የአየር ቅጥን በተለያዩ ምድቦች መከፋፈል ብዙ ጥቅሞች አሉት፡፡ ከነዚህ መካከከል ጥቂቶቹን
ቀጥለን እንመለከታለን፡፡
 ዉስብስብ የአየር ቅጥ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት፣ ለመጠቀምና በእያንዳንዱ የአየር ቅጥ አይነት
ላይ የምናካሂደዉን የጥናት ሂደት ለማፋጠንና ለማቅለል ይረዳል
 በአለም ላይ የሚገኙ የአፈር አይነቶችን፣የመልክአምድሮችን፣ የእጽዋትን፣ የእንስሳትንና የምጣኔ
ሀብታዊ እንቅስቃሴዎችን ስርጭት ለመለየትና ለማጥናት ይጠቅማል፡፡ እንዲሁም

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 መሬትን በተለያዩ የአየርቅጥ ክልሎች ለመከፋፈል ይረዳል፡፡

የአየር ቅጥ ክፍፍል አንዴት ይካሄዳል?


አየር ቅጥን በተለያዩ ምድቦች /ክልሎች/ መከፋፈል የሚቻለዉ ለረዥም ጊዜ በየጊዜዉ የተመዘገብ የአየር ቅጥ
ይዘቶች መረጃ ሲኖር ብቻ ነዉ፡፡ የአየር ቅጥ ይዘቶችን መረጃ መነሻ በማድረግ የአለምን አየር ቅጥ በተለያዩ
የአየር ቅጥ ክልሎች ለመከፋፈል የሚያስችሉ የተለያዩ ዘዴዎች በዘርፉ ባለሙያዎች ተነድፈዋል፡፡ ከነዚህ
መካከል ዋናዋና የአየር ቅጥ ክፍፍል ዘዴዎች የሚባሉት የሚከተሉት ናቸዉ፡፡

ሀ.የጥንታዊ ግሪኮች የአየር ቅጥ ክፍፍል ዘዴ


ለ.የኮፐን የአየር ቅጥ ክፍፍል ዘዴ /Koppen’s climate classification method/
ሐ.የቶንዝዋይት / Thornthwaite’s classification method/እና
መ.የሚለር ክፍፍል ዘዴ /Miller’s classification method/ ናቸዉ፡፡
እነዚህ የአየር ቅጥ ክፍፍል ዘዴዎች የራሳቸዉ ጠንካራና ደካማ ጎን አላቸዉ፡፡ ከነዚህ የክፍፍል ዘዴዎች መካከል
የጥንታዊ ግሪኮችና የኮፐን ዘዴዎች በጣም ቀላልና ጠቃሚ ዘዴዎች ተደርገዉ ይወሰዳሉ፡፡
ሀ.የጥንታዊ ግሪኮች የአየር ቅጥ ክፍፍል ዘዴ
ጥንታዊ ግሪኮች የአለምን አየር ቅጥ በተለያዩ የአየርቅጥ አይነቶች /ክልሎች/ ለመከፋፈል ሙከራ ያደረጉ
የመጀመሪያዎቹ ህዝቦች ነበሩ፡፡ እነዚህ ህዝቦች አየር ቅጥን ለመከፋፈል ዋና መሰፈርት ያደረጉት ልከ ሙቀትንና
የፀሀይ ብርሀን ስርጭትን ነበር፡፡ በዚህም መሰረት የአለምን አየር ቅጥ በሶስት የአየር ቅጥ ክልሎች ከፍለዉታል፡፡
አነሱም ገሞጂማ ሰቅ/ Tropical zone/፣ ወይኖጌ ሰቅ /Temperate zone/ እና ዋልታዊ ሰቅ /polar zone/
ናቸዉ፡፡
1.ገሞጂማ ሰቅ / Tropical zone/
ይህ ክልል በ 231/20 ሰ እና 231/20 ደ መካከከል ይገኛል፡፡ የበረድ ወቅት /winter season/ የሌለበት ክልል ነዉ፡፡ በዚህ
የአየር ቅጥ ክልል የቀንና የሌሊቱ ርዝማኔ የጎላ ልዩነት የለዉም፣ ሁልጊዜ ቀጤ የፀሀይ ጨረር ስለሚያገኝ አመቱን በሙሉ
ሞቃት ነዉ፡፡ አማካይ ልከ ሙቀት 200 ሴንቲግሬድ ሲሆን በየቦታዉ ግን ይለያያል፡፡
2.የወይኖጌ ሰቅ /Temperate zone/
ይህ ክልል በ 231/20 - 661/20 ሰሜንና በ 231/20 - 661/20 ደቡብ መካከከል ይገኛል፡፡ የወይኖጌ የአየር ቅጥ ክልል በትክክል
ተለይተዉ የሚታወቁ የሞቄ /summer/ እና በረድ /winter/ ወቅቶች አሉት፡፡ አብዛኞቹ የሰሜን አሜሪካ፣ የአዉሮፓ፣
የሩሲያና የጃፓን ቦታዎች በዚህ ክልል ዉስጥ ይገኛሉ፡፡ በአጠቃላይ ሲታይ ይህ ክልል መካከለኛ የሆነ የአየር ቅጥ አለዉ፡፡
ይህም ሲባል በጣም ያልሞቀና በጣም ያልቀዘቀዘ ማለት ነዉ፡፡

3.ዋልታዊ ሰቅ /polar zone/


የዋልታዊ ሰቅ የአየር ቅጥ ክልል በአርክቲክ / በ 661/20 -900 ሰሜን መካከል/ እና በአንታርክቲክ /በ 661/20 -900 ደቡብ
መካከከል/ ይገኛል፡፡ በዚህ ክልል የሚገኙ ቦታዎች አመቱን በሙሉ ቀዝቀዛ በመሆናቸዉ ሞቄ ወቅት የላቸዉም፡፡ ይህ ሊሆን
የቻለዉ በክልሉ ረጅም በጨለማ የተዋጠ የበረድ ወቅትና አነስተኛ የፀሀይ ብርሀን በመኖሩ ምክንያት ነዉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የጥንታዊ ግሪኮች የአየር ቅጥ ክፍፍል ዘዴ ደካማ ጎኑ የዝናብ መጠንን እንደ መስፈርት ስለማይጠቀም
የክረምትና በጋ ወቅቶችን በትክክል ለመለየት አያስችልም፡፡

ለ. የኮፐን የአየር ቅጥ ክፍፍል ዘዴ


ኮፐን /1846- 1940/ የአለምን አየርቅጥ በተለያዩ የአየር ቅጥ አይነቶች /ክልሎች/ የከፈለ ታዋቂ ጀርመናዊ
ሳይንቲስት ነበር፡፡ ኮፐን አየር ቅጥን ለመከፋፈል መሰረት ያደረገዉ ከጅኦገራፊያዊ መገኛ/Geographical
location/ ይልቅ አመታዊና ወርሀዊ ልከ ሙቀትንና የዝናብ መጠንን ነበር፡፡ በዚህም መሰረት የአለምን አየር ቅጥ
በአምስት የአየር ቅጥ አይነቶች /ክልሎች/ ከፍሎታል፡፡ እነዚህ የአየር ቅጥ ክልሎች በአምስት የእንግሊዝኛ
በፊደላት ማለትም A, B,C,D,E ተሰይመዋል፡፡ እያንዳንዱ የአየር ቅጥ ክልል እንደገና በንኡስ የአየርቅጥ
ክልሎች የተከፋፈለ ሲሆን ንዑስ ክፍሎችም በትንንሽ የእንግሊዝኛ ፊደላት ተሰይመዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ የኮፐን የአየርቅጥ ክፍፍል ዘዴ ክልላዊ የአየር ቅጦችን ለማጥናት ከሁሉም የአየር ቅጥ ክፍፍል
ዘዴዎች የበለጠ በሰፊዉ ተቀባይነትን አግኝቷል፡፡ ይህም ሊሆን የቻለዉ የተጠቀመበት ዘዴ ቀላልና ግልጽ
ከመሆኑ በተጨማሪ በቀላሉ ሊገኙ የሚችሉ መረጃዎችን ማለትም ወርሀዊና አመታዊ አማካይ ልከ ሙቀትንና
የዝናብ መጠንን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ነዉ፡፡
የአምስቱ ዋናዋና የአየርቅጥ ክልሎች ምልክትና መግለጫ ከዚህ በታች ቀርቧል፡፡
1.ገሞጂማ ርጥብ አየር ቅጥ /Tropical Moist Climate /A/
በዚህ የአየር ቅጥ ክልል የሁሉም ወሮች አማካይ ልከ ሙቀት መጠን ከ 18 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ በላይ ነዉ፡፡
የሁሉም ወሮች ልከ ሙቀት ሞቃት ከመሆኑ የተነሳ እዉነተኛ የበረድ ወቅት /real winter season/ የለም፡፡ ይህ
የአየር ቅጥ ክልል በሶስት ንዑስ የአየር ቅጥ ክልሎች ይከፈላል፡፡ እነሱም፡
 የገሞጂማ ስግር አየር ቅጥ /Tropical monsoon climate /Am/፣

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 የገሞጂማ ዶፍ ጫካ አየር ቅጥ / Tropical rain forest climate/ Af / እና


 ገሞጂማ ገሶ አየር ቅጥ/Tropical savanna climate/ Aw/ ናቸዉ፡፡
2. ደረቅ አየር ቅጥ /Dry climate/B/
በዚህ የአየር ቅጥ ክልል በትነት የሚባክነዉ የዉሀ መጠን ከዝናብ ከሚገኘዉ የዉሀ መጠን ስለሚበልጥ ከፍተኛ
የዉሀ እጥረት አለ፡፡ ደረቅ አየር ቅጥ በሶሰት ንዑስ የአየር ቅጥ ክልሎች ይከፈላል፡፡ እነሱም፡-
 ጠራራ ክችሌ /Hot and arid /Bwh/፣
 ከፊል ጠራራ ክችሌ / hot semi arid climate /Bsh/ እና
 ቀዝቃዛ ከፊል ክችሌ አየር ቅጥ /Cool Smi Arid climate /Bsk/ ናቸዉ፡፡

3. ዉሀ አዘል ቀዝቃዛ ማእከላዊ ኬክሮስ አየርቅጥ/Moist mid-Climate with mild winter/C/


ይህ የአየር ቅጥ ክልል ሞቃት ሞቄ ወቅትና መካከለኛ በረድ ወቅቶች አሉት፡፡የ ዚህ አየር ቅጥ ክልል በጣም
ቀዝቃዛ የተባለዉ ወር አማካይ የልከ ሙቀት መጠን ከ 18 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በታችና ከ-3 ዲግሪ ሴንቲግሬድ
በላይ ነዉ፡፡ በዚህ የአየር ቅጥ ክልል ስር ብዙ ንዑስ የአየር ቅጥ ክልሎች ያሉ ሲሆን ዋናዋናዎቹ የሚከተሉት
ናቸዉ፡፡
 ሙቅ ወይኖጌ ዝናብማ አየር ቅጥ /ደረቅ በጋ/ Warm Temperate rainy climate/ with dry winter
Season /cwb/፣
 ሙቅ ወይኖጌ ዝናብማ አየር ቅጥ /warm temperate rainy climate with out distnict dry
Season /cfb/ እና
 ሙቅ ወይኖጌ አየር ቅጥ / criteria of both w and s are meet /cws/ ናቸዉ፡፡
4. ዉሀ አዘል በጣም ቀዝቃዛ ማእከላዊ ኬክሮስ አየር ቅጥ /Moist mid- Climate with sever winter /
D/
ይህ የአየር ቅጥ ክልል በጣም ቀዝቃዛ የበረድ ወቅት አለዉ፡፡ የሞቃታማዉ ወር አማካይ የልከ ሙቀት መጠን
ከ 10 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በላይ ሲሆን ቀዝቃዛማዉ ወር ደግሞ ከ-3 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በታች አማካይ ልከ
ሙቀት አለዉ፡፡ የበረድ ወቀት በጣም ቀዝቃዘ ሲሆን የሞቄ ወቅት ደግሞ መካከለኛ ሙቀት አለዉ፡፡ ይህ የአየር
ቅጥ ክልል በስምንት ንዑስ የአየር ቅጥ ክልሎች ይከፈላል፡፡ እነዚህን ንዑስ የአየር ቅጥ ክልሎች እስከነ
ምልክቶቻቸዉ ዘርዝሩ፡፡

5.ዋልቴ አየር ቅጥ /Polar climate/ E/


በዚህ የአየር ቅጥ ክልል የሞቄና በረድ ወቅቶች ልከ ሙቀት በጣም ቀዝቃዘ ነዉ፡፡ የሞቃታማዉ ወር አማካይ
ልከ ሙቀት ከ 10 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በታች ነዉ፡፡ በዋልቴ የአየር ቅጥ የሁሉም ወሮች ልከ ሙቀት በጣም
ቀዝቃዛ በመሆኑ የተነሳ እዉነተኛ የሞቄ ወቅት /real summer season/ የለም፡፡ በሰሜናዊ ንፍቀ ክበብ ብቻ
የሚገኘዉ የጮቄ አየር ቅጥ / Tundra climate /ET / እና የርግበረድ ቁንጮ/ ice cap /EF / አየር ቅጥ የዋልቴ
አየር ቅጥ ንዑስ የአየር ቅጥ ክልሎች ናቸዉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ከአምስቱ ዋናዋና የአየር ቅጥ አይነቶች መካከል አረቱ ማለትም A, C, D, E ዋና መለያቸዉ አማካይ ልከ


ሙቀት ሲሆን የአምስተኛዉ የአየር ቅጥ (B) ዋና መለያ መስፈርት ደግሞ የጥዱፍ ዉርድ መጠን / amount of
precipitation/ነዉ፡፡

ተግባር-2.5
1.በጥንታዊ ግሪኮች የአየር ቅጥ ክልሎች መካከከል ምን መሰረታዊ ልዩነት ተገነዘባችሁ?
2.እናንተ የምትኖሩት በየትኛዉ የአየርቅጥ ክልል ነዉ?
3.የእያንዳንዱን የኮፐን ንዑስ የአየር ቅጥ አይነቶችን የልከ ሙቀትና የዝናብ ሁኔታ አስረዱ፡፡
4.የጥንታዊ ግሪኮችና የኮፐን የአየርቅጥ ክፍፍል ዘዴ ልዩነት ምንድን ነዉ?

2.3.2 የኢትዮጵያ አየር ቅጥ

ሰልጣኞች ከዚህ ንኡስ ርእስ ፍጻሜ በኋላ


 የኢትዮጵያን የሙቀት ስርጭት ከቦታ ቦታና ከወቅት ወቅት ያለዉን ልዩነት ታስረዳላችሁ
 በኢትዮጵያ ልከ ሙቀትና የዝናብ ስርጭት ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ደንቢዎችን ትዘረዝራላችሁ
 የኢትዮጵያን የአየር ቅጥ ዞኖች ትለያላችሁ
 የኢትዮጵያን የዝናብ ስርጭት በቦታና በጊዜ ታወዳድራላችሁ

የኢትዮጵያ የአየር ቅጥ ተቆጣጣሪዎች

የኢትዮጵያ ዋናዋና የአየር ቅጥ ተቆጣጣሪዎች ምንምን ናቸዉ?


አየር ቅጥ በሰዉ ልጅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ከፍተኛ ተጽእኖ ያሳድራል፡፡ ኢትዮጵያ
ከሜድትራኒያንና ከዋልታዎች አየር ቀጥ በስተቀር ሁሉም አይነት አየር ቅጦች አሏት፡፡ እነዚህን የአየር ቅጥ
ሀብቶች ጥቅም ላይ ለማዋል የአየር ቅጥ ይዘቶችን መጠን፣ ከወቅት ወቅትና ከቦታ ቦታ ስርጭት ማጥናት
አስፈላጊ ነዉ፡፡ በኢትዮጵያ አየር ቅጥ እንዲለዋወጥ የሚያደርጉ ብዙ ተቆጣጣሪዎች አሉ፡፡ ከነዚህ መካከል
ኬክሮስ፣ ከፍታና የአየር ጠባይ ስርዓት በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳሉ፡፡

1.ኬክሮስ /latitude/:- ኢትዮጵያ የምትገኘዉ በ 30 ሰሜንና 150 ሰሜን ሞቃታማዉ ክልል ዉስጥ ነዉ፡፡
በዚህ ክልል ዉስጥ ፀሀይ በአናት ላይ ስለምትገኝ ሁሉም ቦታዎች ከፍተኛዉን የፀሀይ ጨረር ያገኛሉ፡፡ ይህ
ሁኔታ በኢትዮጵያ የሚከተሉት የአየር ቅጥ ሁኔታዎች እንዲከሰቱ አድርጓል፡፡
 ከፍተኛ ልከ ሙቀት
 ከፍተኛ የቀን ልከ ሙቀት ልዩነት
 ዝቅተኛ አማካይ ወርሀዊና አመታዊ ልከ ሙቀት ልዩነት
 ከሞላ ጎደል እኩል የቀንና ሌሊት ርዝመት ናቸዉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

2.ከፍታ/Altitude/:-ኢትዮጵያ የከፍተኛ ቦታ ሀገር በመሆኗ እንደሌሎች የገሞጂማ ክልል ሀገሮች የገሞጂማ


አየር ቅጥ ብቻ የላትም፡፡ አብዛኛዉ የኢትጵያ ክፍል ከመሬት ከፍታ የተነሳ የወይኖጌ አየርቅጥ የሚታይበት
ነዉ፡፡ በኢትዮጵያ የገሞጂማ አየር ቅጥ የሚታየዉ በጠረፍ ዝቅተኛ ቦታዎች ነዉ፡፡

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች የሚገኙት በአገሪቱ ማእከላዊ ክፍል ሲሆን ዝቅተኛ ቦታዎች ደግሞ በጠረፍ
አካባቢ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም አንድ ሰዉ ከጠረፉ የሀገሪቱ ክፍል ወደ ማእከላዊ ክፍል ሲጓዝ ሙቀት ይቀንሳል
የዝናብ መጠን ግን ይጨምራል፡፡ ይህም በኢትዮጵያ የልከ ሙቀትና ዝናብ መጠን ከቦታቦታ በከፍታ ምክንያት
ይለያያል ማለት ነዉ፡፡ በጥቅሉ ሲታይ ዝቅተኛ ቦታዎች ከፍተኛ ልከ ሙቀትና ዝቅተኛ ዝናብ መጠን
ሲኖራቸዉ ከፍተኛ ቦታዎች ደግሞ ዝቅተኛ ልከ ሙቀትና ከፍተኛ የዝናብ መጠን አላቸዉ፡፡

ምንም እንኳ ሁለት ወይም ከሁለት በላይ የሆኑ ቦታዎች በተመሳሳይ ኬክሮስ ቢገኙም በከፍታ ልዩነት ምክንያት
የተለያየ መጠን ያለዉ ልከ ሙቀትና ዝናብ ሊያስመዘግቡ ይችላሉ፡፡ እንዲሁም በተመሳሳይ ከፍታ ነገር ግን
በተለያየ የኬክሮስ መስመር የሚገኙ ሁለት የተለያዩ ቦታዎች ተመሳሳይ የሆነ ልከ ሙቀት ሊኖራቸዉ ይችላል፡፡
ከዚህ የምንረዳዉ ከፍታ ዋናዉ የኢትዮጵያ የአየር ቅጥ ተቆጣጣሪ መሆኑን ነዉ፡፡

ሰንጠረዥ- 2.3 በኬክሮስ፣ በከፍታና በልከ ሙቀት መካከል ያለዉ ግንኙት


ከተማ ኬክሮስ ከፍታ አመታዊ አማካይልከ ሙቀት/0c/
በሜትር
አዲስ አበባ 9 2400 17
አዋሽ 9 916 25
አምቦ 9 2130 18
ነቀምት 9 2005 18.3
ዲሪዳዋ 9.6 1160 25

3.የአየር ጠባይ ስርዓት (Weather system) / ወቅታዊ ነፋሶችና የከባቢ አየር ግፊት/
ፀሀይ በካንሰርና በካፕሪኮርን መስመሮች መካከል የምታደርገዉ አንጻራዊ እንቅስቃሴ ኢንተር ትሮፒካል
ግንኙነት ሰቅ /ITCZ/ ከምድር ሰቅ ወደ ሰሜንና ደቡብ እንዲንቀሳቀስ በማድረግ በኢትዮጵያ የተለያዩ ነፋሶች
በተለያዩ ወቅቶች እንዲነፍሱ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ እነዚህ የአየር ጠባይ ስርአቶች በኢትዮጵያ የአየርግፊት፣
የልከ ሙቀትና የዝናብ መጠንን ልዩነት ያስከትላሉ፡፡
በኢትዮጵያ የአየር ቅጥ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ዋናዋና የአየር ጠባይ ስርአቶች፡-
 የሰሜን ምስራቅ ምስራቄ ነፋሶች(North east trade winds) / በታህሳስ፣ በጥርና በየካቲት ወደ
ኢትዮጵ የሚነፍሱ ነፋሶች/
 መሬት ሰቃዊ ምእራብጌ (Equatorial westerlies) /በሰኔ፣ በሀምሌና በነሀሴ ወደ ኢትዮጵያ የሚነፍሱ
ነፋሶች/

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 መሬት ሰቃዊ ምስራቄ (Equatorial Easterlies) / በመስከረምና በጥቅምት እንዲሁም በመጋቢትና


በሚያዚያ ወደ ኢትዮጵያ የሚነፍሱ ነፋሶች/ ናቸዉ፡፡

የኢትዮጵያ ልከ ሙቀት ስርጭት

የኢትዮጵያ ልከ ሙቀት በዋናነት የሚወሰነዉ በከፍታና በኬክሮስ መገኛ ሲሆን የደመና ሽፋንም የራሱ
አስተዋጽኦ አለዉ፡፡ ከላይ እንደተገለጸዉ ኢትዮጵያ የምትገኘዉ ከፍተኛ ገቢ ጸሀይማ ጨረርና እያንዳንዱ ቦታ
በአመት ሁለት ጊዜ ቀጤ የጸሀይ ጨረር በሚያገኝበት የገሞጂማ ክልል ነዉ፡፡ ይሁን እንጅ አብዛኛዉ የኢትዮጵያ
ክፍል ከፍተኛ ቦታ በመሆኑ ከፍታዉ የገሞጂማ ልከ ሙቀት ሁኔታ እንዳይኖረዉ ተጽእኖ አሳድሮበታል፡፡
በኢትዮጵያ የገሞጂማ ልከ ሙቀት ሁኔታ የሚከሰተዉ በአገሪቱ ዳርቻ /ድንበር/ አካባቢ ነዉ፡፡ በመሆኑም
ከኢትዮጵያ ዳርቻ ወደ ማእከላዊ ክፍል ስንጓዝ ከፍታ ስለሚጨምር ልከ ሙቀት ይቀንሳል፡፡ ከዚህ የምንረዳዉ
ኢትዮጵያ ሞቃትና ቀዝቃዛ ልከ ሙቀት የሚከሰትባት አገር መሆኗን ነዉ፡፡

ከፍታ በልከ ሙቀት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ስላለዉ ኢትዮጵያን በተለያዩ የስነ-ምህዳር /ልከ ሙቀት/ ክልሎች
ለመከፋፈል ዋና መስፈርት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በመሆኑም የከፍታና ልከ ሙቀትን ግንኙነት መሰረት በማድረግ
ኢትዮጵያ በአምስት የልከ ሙቀት /ስነ ምህዳር ክልሎች/ ትከፈላለች፡፡ እነሱም በረሀ፣ ቆላ፣ ወይናደጋ፣ ደጋና
ዉርጭ/ ቁር/ ናቸዉ፡፡

ሰንጠረዥ-2.4 የኢትዮጵያ ሥነ-ምህዳራዊ/ ልከ ሙቀት/ ክልሎች


ከፍታ/ በሜትር/ አመታዊ አማካይ ልከ ተለምዷዊ/የሀገር ዉሰጥ/ አለም አቀፍ መጠሪያ
ሙቀት / በዲግሪ ሴንት/ መጠሪያ ስም
≥3,300 <10 ዉርጭ/ቁር/ አልፓይን/Alpine/
2,300-3,300 10 - 15 ደጋ ወይኖጌ/ Temperate/
1,500- 2,300 15 - 20 ወይናደጋ ገሞጂማጠቀስ/subtropical
500 - 1500 20 -30 ቆላ ገሞጅማ/ Tropical/
≤500 30 - 40 በረሀ ምድረ በዳ/Desert/

ዉርጭ ፡- የአልፓይን የአየር ቅጥ አይነት ነዉ፡፡ አመታዊ አማካይ የልከ ሙቀት መጠን ከ 100 ሴንቲግሬድ በታች
ነዉ፡፡ አመታዊ የዝናብ መጠን ደግሞ ከ 800 - 2000 ሚሊሜትር ይደርሳል፡፡ ይህ የአየር ቅጥ
ከፍታቸዉ ከ 3,300 ሜትር ከባህር ወለል በላይ በሆኑ ቦታዎች ይገኛል፡፡ ለምሳሌ የሰሜን፣ የባሌ፣
የጉና፣ የአማራሳይንትና የጮቄ ተራሮች በዉርጭ ልከ ሙቀት ክልል ይመደባሉ፡፡

ደጋ፡- ደጋ ከወይኖጌ አየር ቅጥ ጋር ተመሳሳይ ነዉ፡፡ ይህ የአየር ቅጥ ከፍታቸዉ ከባህር ወለል በላይ ከ 2,300 -
3,300 ሜትር በሆኑ ቦታዎች ይገኛል፡፡ አመታዊ የዝናብ መጠኑ ከ 1000 -2000 ሚሊሜተር ይደርሳል፡፡
የደጋ ክልል አካባቢዎች ለብዙ አመታት ህዝብ ሰፍሮ የቆየባቸዉ በመሆኑ የተነሳ በአፈር መሸርሸር፣
በንር ግጦሽና በደን መጨፍጨፍ ምክንያት መሬታቸዉ በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዳ ነዉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ወይና ደጋ፡- ከባህር ወለል በላይ ከ 1,500 -2,300 ሜትር ከፍታ ባለቸዉ ቦታዎች ይገኛል፡፡ አመታዊ አማካይ ልከ
ሙቀት በ 15 ና 20 ዲግሪሴንቲግሬድ መካከከል ሲሆን አመታዊ የዝናብ መጠን ደግሞ እስከ 1200
ሚሊሜትር ይደርሳል፡፡ የወይና ደጋ አካባቢዎች አብዛኛዉን የአገሪቱን የእርሻ መሬት የያዙ
በመሆናቸዉ ዋና የእህል /ጥራጠሬ/ ምርት አምራቾች ናቸዉ፡፡

ቆላ፡- ከፊል ክችሌ የአየር ቅጥ /semi arid climate/ አለዉ፡፡ ቆላ ከፍታቸዉ ከ 500 -1500 ሜትር ከባህር ወለል
በላይ በሆኑ ቦታዎች የሚገኝ የአየር ቅጥ ነዉ፡፡ አመታዊ አማካይ ልከ ሙቀት ከ 20-30
ዲግሪሴንቲግሬድ ነዉ፡፡ አመታዊ አማካይ የዝናብ መጠን በ 410 ና 820 ሚሊሜትር መካከከል
ቢሆንም በምእራብ የጋምቤላ ቦታዎች እስከ 1600 ሚሊሜትር ይደርሳል፡፡ የዝናቡ መጠን ከአመት
አመት ከፍተኛ ልዩነት ያሳያል፡፡
በረሀ፡- በረሀ ማለት ጠራራና ክችሌ /hot and arid climate/ የአየር ቅጥ ነዉ፡፡ይህ የአየር ቅጥ ከፍታቸዉ
ከ 500 ሜትር በታች በሆኑ ዝቅተኛ ቦታዎች ይገኛል፡፡ አመታዊ አማካይ የዝናብ መጠን ከ 500
ሚሊሜትር በታች ሲሆን አመታዊ አማካይ ልከ ሙቀት ደግሞ ከ 30 ዲግሪሴንቲግሬድ በላይ ነዉ፡፡
በርሀ ብዙ ጊዜ የሚታወቀዉ በሀይለኛ ነፋስ፣ በከፍተኛ ልከ ሙቅት፣ በአነስተኛ ርጥበትና በትንሽ
የደመና ሽፋን ነዉ፡፡

የኢትዮጵያ ልከ ሙቀት ስርጭት ከቦታ ቦታ እንዲለያይ ተጽእኖ ከሚያሳድሩ ተቆጣጣሪዎች አንዱ የደመና
ሽፋን ነዉ፡፡ የደመና ሽፋን መኖር ለመሬት የሙቀት መጋረጃ /መከላከያ/ ሆኖ ያገለግላል፡፡ ይህም ሲባል ቀን
ከፀሀይ ወደ መሬት የሚመጣዉ ሙቀት ሙሉ በሙሉ መሬት ላይ እንዳይደርስ ይከላከላል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ
ሌሌት በሰማይ ላይ ደመና ካለ መሬት ቀን ከጸሀይ ያገኘችዉ ሙቀት ከመሬት ርቆ ወደ ከባቢ አየር እንዳይሄድ
ይከላከላል፡፡ ስለዚህ የደመና ሽፋን መኖር ወይም አለመኖር የኢትዮጵያ የልከ ሙቀት መጠን ከቦታ ቦታ ልዩነት
እንዲኖረዉ ያደርጋል ማለት ነዉ፡፡

የደመና ሽፋን በክረምት ወቅት / ከሰኔ እስከ ነሀሴ/ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ልከ ሙቀት ሁኔታ ላይ ከፍተኛ
ተጽእኖ ያሳድራል፡፡ ምንም እኳን በክረምት ወቅት ኢትዮጵያ ቀጤ የፀሀይ ጨረር የምታገኝበት ወቅት ቢሆንም
የጸሀይ ጨረር በደመና ተዉጦ ስለሚቀር የከፍተኛ ቦታዎች የልከ ሙቀት መጠን አነስተኛ ነዉ፡፡ ሌላዉ
ኢትዮጵያ ቀጤ የፀሀይ ጨረር የምታገኝበት ወቅት ከመጋቢት እስከ ግንቦት ባለዉ ጊዜ ዉስጥ ነዉ፡፡ በዚህ
ወቅት በኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች የደመና ሽፋን ስለሌለ የልከ ሙቀት መጠን ከፍተኛ ነዉ፡፡ የኢትዮጵያ
ሰሜን ምስራቅና ደቡብ ምስራቅ ዝቅተኛ ቦታዎች ዝቅተኛ ቦታዎች በመሆናቸዉና ንጹህ ሰማይ ስላላቸዉ
ልከ ሙቀታቸዉ ከሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ጋር ሲወዳደር ከፍተኛ ነዉ፡፡

ተግባር- 2.6
1.ከፍታ የኢትዮጵያ የአየር ቅጥ ዋና ተቆጣጣሪ ለምን ተባለ?
2.እናንተ የምትኖሩበት ቀበሌ ከላይ ከተጠቀሱት የልከ ሙቀት ክልሎች ከየትኛዉ ይመደባል?
3.እናንተ የምትገኙበትን የልከ ሙቀት ክልል የአየር ቅጥሁኔታ፣የእጽዋትና የዱር እንስሳትን አይነት የሚገልጽ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሪፖርት አዘጋጅታችሁ ለክፍል ጓደኞቻችሁና ለአሰልጣኝ መምህራችሁ አቅርቡ::


4.በደጋና በቆላ የሚኖሩ ሰዎችን ባህል አስረዱ::

የኢትዮጵያ የቀን አማካይ ልከ ሙቀት፡- የኢትዮጵያ የቀን አማካይ የልከ ሙቀት መጠን ከአመታዊ አማካይ
የልከ ሙቀት መጠን በእጅጉ ይበልጣል፡፡ የሙቀት ስርጭቱም ከቦታ ቦታ ከፍተኛ ልዩነት አለዉ፡፡ ለምሳሌ የቀኑ
ከፍተኛ የልከ ሙቀት መጠን በደቡብ ምስራቅና ሰሜን ምስራቅ ዝቅተኛ ቦታዎች ከ 370 ሴንቲግሬድ በላይ
ሲሆን በከፍተኛ ቦታዎች ደግሞ ከ 10 -150 ሴንቲግሬድ ነዉ፡፡
የቀን ልከ ሙቀት መጠን ከወር ወርም ይለያያል፡፡ ለምሳሌ መጋቢት፣ሚያዚያና ግንቦት በሁሉም የአገሪቱ
ክፍሎች ከፍተኛ ልከ ሙቀት የሚመዘገብባቸዉ ወሮች ናቸዉ፡፡

ወርሀዊ አማካይ ልከ ሙቀት፡- የኢትዮጵያ ወርሀዊ አማካይ የልከ ሙቀት መጠን ከወር ወርና ከቦታ ቦታ ልዩነት አለዉ፡፡
በአብዛኛዎቹ ከፍተኛ ቦታዎች እስከ 00 ሴንቲግሬድ የሚደርስ ዝቅተኛ ወርሀዊ አማካይ ልከ ሙቀት ከህዳር እስከ
ጥር ወር ይመዘገባል፡፡ በጣም ዝቅተኛዉ ወርሀዊ አማካይ ልከ ሙቀት /00 ሴንቲግሬድ ወይም በታች/ በሰሜን ምእራብ
/በጎንደርና ጎጃም/፣በማእከላዊ /በሸዋ/ እና በደቡብ ምስራቅ/ በአሩሲና ባሌ/ ከፍተኛ ቦታዎች በጥር ወር ይመዘገባል፡፡
ከፍተኛዉ ወርሀዊ አማካይ የልከ ሙቀት መጠን ደግሞ ከ 300 ሴንቲግሬድ በላይ ሲሆን በምእራብ፣ በሰሜን
ምስራቅና በደቡብ ምስራቅ ዝቅተኛ ቦታዎች ከመጋቢት እስከ ሰኔ ይመዘገባል፡፡

አመታዊ አማካይ ልከ ሙቀት፡- በኢትዮጵያ አመታዊ አማካይ የልከ ሙቀት መጠን ከቦታ ቦታ ይለያያል፡፡
ዝቅተኛዉ አመታዊ አማካይ የልከ ሙቀት መጠን (ከ 100 ሴንቲግሬድ በታች) በሰሜን ምእራብ፣ በማእከላዊና
በደቡብ ምስራቅ ከፍተኛ ቦታዎች ይመዘገባል፡፡ ከፍተኛዉ አመታዊ አማካይ የልከ ሙቀት መጠን (ከ 350
ሴንቲግሬድ በላይ) ደግሞ በአገሪቱ የሰሜን ምስራቅ ዳርቻ /በዳሎል ዋድያቶ/ ይመዘገባል፡፡ የዳሎል /ዳናክል/
ዋዲያቶ በኢትዮጵያ በጣም ሞቃታማዉ ቦታ ነዉ፡፡

የኢትዮጵያ የቀን ልከ ሙቀት ልዩነት /daily range of temperature/ ፡-ታህሳስ፣ ጥርና የካቲት ጸሀይ
በደቡባዊ ንፍቀ ክበብ አናት ላይ ስለምትሆን በኢትዮጵያ የበጋ ወቅት ነዉ፡፡ በዚህ ጊዜ ሙቀትን አፍኖ የሚይዝ
በቂ የደመና ሽፋን በሰማይ ላይ አይኖርም፡፡ በዚህ ምክንያት ከጸሀይ ወደ መሬት የሚደርሰዉ የሙቀት መጠን
ከፍተኛ ነዉ፡፡ ሌሊት ደግሞ ከመሬት ተንጸባርቆ የሚመለሰዉን ሙቀት አፍኖ የሚያስቀር የደመና ሽፋን
ስለማይኖር የገጸምድር የሙቀት መጠን ይቀንሳል፡፡ በዚህ የተነሳ በበጋ ወቅት የኢትዮጵያ የቀኑ ልከ ሙቀት
ልዩነት በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ከፍተኛ ነዉ፡፡

አመታዊ የሙቀት ልዩነት፡- በኢትዮጵያ ከፍተኛዉ አመታዊ የሙቀት ልዩነት የሚከሰተዉ በዝቅተኛ ቦታዎች
ነዉ፡፡ ነገር ግን ከፍታ ሲጨምር የሙቀት ልዩነት ይቀንሳል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ተግባር- 2.7
1.አንተ / አንች በምትኖርበት/ በምትኖሪበት አካባቢ በጣም ከፍተኛና ዝቅተኛ ልከ ሙቀት የሚከሰትባቸዉን
ወሮች ተናገር/ተናገሪ፡፡

የኢትዮጵያ የዝናብ ስርጭት


በኢትዮጵያ ዝናብ ከቦታ ወደ ቦታና ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲለያይ ከሚያደርጉት ተቆጣጣሪዎች መካከከል ዋና
ዋናዎቹ ከፍታና የአየር ጠባይ ስርአት ናቸዉ፡፡ በአብዛኛዉ ከቦታ ወደ ቦታ እንዲለያይ የሚያደርገዉ ከፍታ ሲሆን
ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲለያይ የሚያደርገዉ ደግሞ በገሞጂማ ክልል ዉስጥ የሚከሰት የአየር ጠባይ ስርአት
/weather system/ነዉ፡፡
1.ከፍታ /ጉባጉብ/ (relief):- የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች በአብዛኛዉ የሀገሪቱ ክፍሎች የተራራ ዝል
ዝናብ /orographic rains/ እንዲፈጠር ያደርጋሉ፡፡ በከፍታ ምክንያት በከፍተኛና ዝቅተኛ ቦታዎች መካከከል
ከፍተኛ የሆነ የዝናብ ልዩነት አለ፡፡
2.የአየር ጠባይ ስርዓት ሁኔታ /weather system/
የኢትዮጵያ ዝናብ ስርጭት ከወቅት ወቅት እንዲለያይ የሚያደርጉ ተቆጣጣሪዎች ወቅታዊ ነፋሶችና የአየር
ግፊት እንቅስቃሴ ናቸዉ፡፡ የፀሀይን አንጻራዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ የአየር ግፊት እንቅስቃሴ ይፈጠራል፡፡ ፀሀይ
በአናት ላይ በምትሆንባቸዉ አካባቢዎች ዝቅተኛ የአየር ግፊት ይፈጠራል፡፡ በምደር ሰቅ አካባቢ ዝቅተኛ የአየር
ግፊት የሚፈጠርበት ቦታ ኢንተርትሮፒካል ግንኙነት ሰቅ /ITCZ/ ይባላል፡፡

ኢንተርትሮፒካል ግንኙነት ሰቅ ከምድር ሰቅ ወደ ሰሜንና ደቡብ በሚያደርገዉ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያን በአመት


ሁለት ጊዜ ያቋርጣል፡፡ ይህ እንቅስቃሴ በተለያዩ ጊዚያት ነፋሶች ከሰሜንና ከደቡብ የአለም ክፍሎች ወደ
ኢትዮጵያ እንዲነፍሱ ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ ኢንተርትሮፒካል ግንኙነት ሰቅ ወደ ሰሜን ሲጓዝ የ መሬት ሰቃዊ
ምእራብጌ ነፋሶች (Equatorial westerlies) ከአትላንቲክ ዉቅያኖስ ወደ ኢትዮጵያ ይነፍሳሉ፡፡
ኢንተርትሮፒካል ግንኙነት ሰቅ ወደ ደቡብ ሲጓዝ ደግሞ የሰሜን ምስራቅ ምስራቄ ነፋሶች(North east trade
winds) ከሰሀራ በረሀና ከአረቢያን ወሽመጥ ወደ ኢትዮጵያ ይነፍሳሉ፡፡ ይህ በየወቅቱ የሚከሰት የነፋስ
መፈራረቅ የኢትዮጵያን ዝናብ ተለዋዋጭና ወቅታዊ እንዲሆን አድርጎታል፡፡

የኢትዮጵያ ወቅታዊ የዝናብ ስርጭት

በኢትዮጵያ አራት ወቅቶች አሉ፡፡ አንዱ ወቅት ከሌላዉ የሚለየዉ በአመታዊ የዝናብ ስርጭትና በአየር ጠባይ
ስርዓት ነዉ፡፡ እነዚህ ወቅቶች፡-
 በጋ /የደረቅ ወቅት/
 በልግ /የአነስተኛ ዝናብ ወቅት/
 ክረምት /የከፍተኛ ዝናብ ወቅት/ እና
 ጸደይ / እንደ በልግ የአነስተኛ ዝናብ ወቅት/ ናቸዉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

1. በጋ፡- ከታህሳስ አስከ የካቲት የሚከሰት ደረቅ ወቅት ነዉ፡፡ በዚህ ወቅት ፀሀይ ከምድር ወገብ በስተሰሜን
አናት ላይ ትሆናለች፡፡ በበጋ ወቅት ከፍተኛ የአየር ግፊት በደቡብ ምእራብ እስያ ሲፈጠር ዝቅተኛ የአየር
ግፊት ደግሞ በማእከላዊ አፍሪካ ይፈጠራል፡፡ እንዲሁም ኢንተርትሮፒካል ግንኙነት ሰቅ ወደ ደቡብ
ይዛወራል፡፡ በዚህ ወቅት የሰሜን ምስራቅ ምስራቄ ነፋሶች (North east trade winds/ ከእስያ ደረቅ
መሬት ተነስተዉ ወደ ኢትዮጵያ ይነፍሳሉ፡፡ አነዚህ ነፋሶች ርጥበት አዘል ባለመሆናቸዉ በኢትዮጵያ
ደረቅ የአየር ሁኔታ ይፈጥራሉ፡፡ በዚህም የተነሳ በጋ በአብዛኛዉ የኢትዮጵያ ክፍል ደረቅ ወቅት ይሆናል፡፡
2.በልግ፡- ይህ ወቅት ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለዉን ጊዜ ይሸፍናል፡፡ በኢትዮጵያ ከፍተኛዉ ልከ ሙቀት
የሚመዘገበዉ በዚህ ወቅት ነዉ፡፡ በዚህ ወቅት የሚፈጠረዉ ዝናብ በከፍተኛ ሁኔታ በጊዜና ቦታ
ይለያያል፡፡ በበልግ ወቅት ኢንተርትሮፒካል ግንኑነት ሰቅ በምድርሰቅ አካባቢ ይሆናል፡፡ በዚህ የተነሳ
ከህንድ ዉቅያኖስ የሚነሱ መሬት ሰቃዊ ምስራቄ ነፋሶች (Equatorial Easterlies) ወደ ኢትዮጵያ
ስለሚነፍሱ የደቡብ ምስራቅ ከፍተኛና ዝቅተኛ ቦታዎች ዝናብ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል፡፡
3. ክረምት ፡- ይህ ከሰኔ - መስከረም የሚከሰት የኢትዮጵያ ዋናዉ የዝናብ ወቅት ነዉ፡፡ በዚህ ወቅት ፀሀይ
ከምድር ወገብ በስተሰሜን አናት ላይ ትሆናለች፡፡ በመሆኑም ዝቅተኛ የአየር ግፊት በደቡብ ምስራቅ
እስያ ይፈጠራል፡፡ ከፍተኛ የአየር ግፊት ደግሞ በካፕሪኮርን መስመር አካባቢ በህንድና በአትላንቲክ
ዉቅያኖስ ላይ ይፈጠራል፡፡ በተጨማሪም ኢንተርትሮፒካል ግንኙነት ሰቅ ከኢትዮጵያ በስተሰሜንና
በሰሜን ምስራቅ በቀይ ባህርና በኤደን የባህር ወሽመጥ ላይ ይሆናል፡፡ በዚህ ምክንያት ዝናብ ጥል
ከሆኑት ከደቡብ ምሰራቅና ሰሜን ምስራቅ ዝቅተኛ ቦታዎች በስተቀር አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ
ክፍሎች ከአትላንቲክ ዉቅያኖስ በሚነሱ መሬት ሰቃዊ ምእራብጌ ነፋሶች (Equatorial westerlies)
አማካኝነት ዝናብ ያገኛሉ፡፡
4.ጸደይ፡-ይህ ወቅት ከመስከረም እስከ ህዳር ያለዉን ጊዜ የሚሸፍን የአነስተኛ ዝናብ ወቅት ነዉ፡፡ በዚህ ወቅት
ከህንድ ዉቅያኖስ የሚነሱ መሬት ሰቃዊ ምስራቄ ነፋሶች (Equatorial Easterlies) ወደ ኢትዮጵያ
ስለሚነፍሱ የደቡብ ምስራቅ ከፍተኛና ዝቅተኛ ቦታዎች ለሁለተኛ ጊዜ ዝናብ ያገኛሉ፡፡

በጥቅሉ የኢትዮጵያ ዝናብ ስርጭት ሁኔታ ሲታይ ከፍተኛ አመታዊ የዝናብ መጠን እስከ 2700 ሚሊሜትር
የሚደርስ የሚመዘገበዉ በሀገሪቱ የደቡብ ምእራብ ከፍተኛ ቦታዎች ነዉ፡፡ ነገርግን ወደ ሰሜን፣ ሰሜን
ምስራቅና ደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ ስንጓዝ እየቀነሰ ይመጣል፡፡ ስእል 2.2 ትን ይመልከቱ፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ስእል- 2.2 የኢትዮጵያ አመታዊ የዝናብ ስርጭት

ተግባር- 2.8
1.ተራራ ዝል ዝናብ የኢትዮጵያ ዋና የዝና አይነት ለምን ሊሆን ቻለ?

2.በኢትዮጵያ አመታዊ የዝናብ መጠን ልዩነት መኖሩ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ ጉዳይና በተፈጥሯዊ አካባቢ
ላይ እያስከተለ ያለዉ ተጽእኖ ምንድን ነዉ?
3.ከፍተኛ የዝናብ መጠን የሚያገኘዉ የትኛዉ የኢትዮጵያ ክፍል ነዉ? ለምን ከፍተኛ የዝናብ መጠን ሊያገኝ
ቻለ?
4.አነስተኛ የዝናብ መጠን የሚያገኘዉ የትኛዉ የኢትዮጵያ ክፍል የትኛዉ ነዉ? ለምን አነስተኛ ዝናብ መጠን
ሊያገኝ ቻለ?
5.የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ከዝቅተኛ ቦታዎች የበለጠ ዝናብ ለምን ሊያገኙ ቻሉ?

የኢትዮጵያ የዝናብ ክልሎች /Rainfall Regions in Ethiopia/


በዝናብ የቦታና የጊዜ ስርጭት መሰረት ኢትዮጵያ በሶስት የዝናብ ክልሎች ትከፈላለች፡፡ እነሱም፡-
1.አመቱን በሙሉ ዝናብ የሚገኙ/ All year round rainfall regions/:- ይህ የዝናብ ክልል የደቡብ ምእራብ
ከፍተኛ ቦታዎችን ማለትም ወለጋ፣ ኢልባቡር፣ ከፋና ጋሞጎፋን ያጠቃልላል፡፡ ክልሉ ከሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች
የበለጠ ዝናብ የሚያገኝባቸዉ ብዙ የዝናብ ቀናት አሉት፡፡ አመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኑም ከ 1400
ሚሊሜተር እስከ 2200 ሚሊሜትር ይደርሳል፡፡
2.በክረምት ዝናብ የሚያገኙ /summer rainfall regions/

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ይህ ክልል የሰሜን ምእራብ ከፍተኛ ቦታዎችንና የምእራብ ዝቅተኛ ቦታዎችን ያቀፈ ሲሆን በሀገሪቱ ትልቁ
የዝናብ ክልል ነዉ፡፡ ክልሉ ዝናብ የሚያገኘዉ ከአትላንቲክ ዉቅያኖስ ተነስተዉ ወደ ኢትዮጵያ በሚነፍሱ መሬት
ሰቃዊ ምእራብጌ ነፋሶች (Equatorial westerlies) አማካኝነት ነዉ፡፡
3.በጸደይና በልግ ዝናብ የሚያገኙ / autumn and Spring Rainfall regions/
እነዚህ አካባቢዎች የደቡብ ምስራቅ ከፍተኛና ዝቅተኛ ቦታዎች ናቸዉ፡፡ የክልሉ ዝናብ አምጭ ነፋሶች መሬት
ሰቃዊ ምስራቄ ነፋሶች (Equatorial Easterlies/ ኛቸዉ፡፡ አማካይ የዝናብ መጠኑ ከ 500 -1000 ሚሊሜተር
ይደርሳል፡፡ የደቡብ ምስራቅ ዝቅተኛ ቦታዎች በአመት ሁለት ጊዜ ዝናብ ስለሚያገኙ በአመት ሁለት ጊዜ
የዝናብ መገኛ ክልል / Duble rainfall region/ ይባላሉ፡፡ ስእል 2.3 ትን ይመልከቱ፡፡

ስእል- 2.3.የኢትዮጵያ የዝናብ ክልሎች

ተግባር- 2.9
1.አንተ/ች የምትኖርበት / የምትኖሪበት ቀበሌ ወይም ወረዳ ከላይ ከተዘረዘሩት የዝናብ ክልሎች ከየትኛዉ
ይመደባል?
2. የምትኖርበት/የምትኖሪበት ቀበሌ/ወረዳ ዝናብ እንዲያገኝ የሚያስችለዉን የነፋስ አይነት ተናገሩ፡፡
3. እናንተ በምትኖሩበት አካባቢ ዝናብ አዘል ነፋስ እንዲነፍስ ያደረገዉ ምክንያት ምንድን ነዉ ትላላችሁ?

2.3.3 ወቅቶች በኢትዮጵያ


ቀደም ብሎ እንደተገለጸዉ ኢትዮጵያ በጎሞጅማ ክልል የምትገኝ ሀገርናት፡፡ በጎሞጅማ ክልል መገኘቷ በሀገሪቱ
የቀንና ሌሊት ልዩነት አነስተኛ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ከፍተኛዉ የቀንና ሌሊት ርዝመት ልዩነት የሚከሰተዉ
በታህሳስና ሰኔ ሲሆን ከ 30 ደቂቃዎች አይበልጥም፡፡ ይህንን ልዩነት ብዙ ሰዎች አይገነዘቡትም፡፡

በጎሞጅማ ክልል የልከ ሙቀት መጠን ከፍተኛ ነዉ፡፡ በዚህ የተነሳ የአመቱ ወቅቶች የሚከፈሉት በዝናብ መጠን
በሚፈጠር ልዩነት መሰረት ነዉ፡፡ ስለዚህ በጎሞጅማ ክልል ሁለት ወቅቶች ብቻ ይኖራሉ ማለት ነዉ፡፡ እነርሱም

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ርጥብ ዝናባማና ደረቅ ወቅቶች ናቸዉ፡፡ በኢትዮጵያም በበጋና በክረምት ወቅቶች መካከል ብዙም የሙቀት
መጠን ልዩነት በማይታይባቸዉ ስፍራዎች ተመሳሳይ አከፋፈል ይታያል፡፡ ጠቅለል ብሎ ሲታይ በኢትዮጵያ
በአመት አራት ወቅቶች አሉ፡፡ እነሱም ክረምት፣ ጸደይ፣ በጋና በልግ ናቸዉ፡፡

ሰንጠረዠ- 2.4 የኢትዮጵያ ወቅቶች


ወሮች የወቅቱ መጠሪያ ስም የፀሀይ መገኛ
በእንግሊዝኛ በአማርኛ
ሰኔ፣ሀምሌና ነሀሴ Summer ክረምት በሰሜናዊ ንፍቀ ክበብ
መስከረም፣ጥቅምትና ህዳር Autumn ጸደይ በምድር ሰቅ አካባቢ
ታህሳስ፣ጥርና የካቲት Winter በጋ በደቡባዊ ንፍቀ ክበብ
መጋቢት፣ሚያዚያናግንቦትና Spring በልግ በምድር ሰቅ አካባቢ

የኢትዮጵያ የአየር ቅጥ ክልሎች


ቀደም ብሎ እንደተገለጸዉ ኮፐን አምስት ፊደላትን በመጠቀም የአለምን አየር ቅጥ በአምስት ዋናዋና የአየር
ቅጥ ክልሎች ከፍሎታል፡፡ ከነዚህ መካከከል ሶስቱ በኢትዮጵያ ይገኛሉ፡፡እነሱም፡-
1.ደረቅ አየር ቅጥ / dry climate / (B) 2.ገሞጂማ /Tropical climate/ (A)
3. ወይኖጌ /Temperate/ (C) ናቸዉ፡፡ እነዚህ ዋናዋና ክልሎች በተለያዩ ንኡስ የአይር ቅጥ ክልሎች ይከፈላሉ፡፡
ይህም፡-
1.ገሞጅማ /Tropical climate/ A/
 ገሞጅማ ርጥብና ደረቅ/ Tropical wet and dry /Aw/
 ገሞጅማ ሞንሱን /Tropical monsoon climate/ Am/
 ክረምትና በጋ ደረቅ አየር ቅጥ /dry winter and summer/Aws/
2.ደረቅ አየር ቅጥ /B/
 ጠራራ ክችሌ /Hot and arid /Bwh/
 ከፊል ጠራራ ክችሌ / hot semi arid climate /Bsh/
 ቀዝቃዛ ከፊል ክችሌ አየር ቅጥ /Cool Smi Arid climate /Bsk/
3.ወይኖጌ/ temperate /C/
 ሙቅ ወይኖጌ ዝናብማ አየርቅጥ /ደረቅ በጋ/ Warm Temperate rainy climate/ with dry winter
Season /cwb/
 ሙቅ ወይኖጌ ዝናብማ አየር ቅጥ /warm temperate rainy climate with out distnict dry
Season /cfb/
 ሙቅ ወይኖጌ አየር ቅጥ / criteria of both w and s are meet /cws/
የቀዝቃዛ ከፍተኛ ቦታ አየር ቅጥ / cool high-land climate / H/

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

በዚህ የአየር ቅጥ ክልል በከፍታ ምክንያት የሞቃታማዉ ወር አማካይ የልከ ሙቀት መጠን ከ 10 ዲግሪ
ሴንቲግሬድ በታች ነዉ፡፡ አመታዊ አማካይ የዝናብ መጠን ደግሞ በ 800 ና 2000 ሚሊሜትር መካከከል ነዉ፡፡
በከፍተኛ ቦታ የአየር ቅጥ ክልል የበጋ ወራቶች ደረቅ ናቸዉ፡፡ ይህ የአየር ቅጥ ክልል ከፍታቸዉ ከ 3500 ሜትር
በላይ በሆኑ ቦታዎች ለምሳሌ በሰሜን፣ በባሌና በአሩሲ ከፍተኛ ቦታዎች ይገኛል፡፡

ተግባር- 2.10
1.ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን የኢትዮጵያ የአየር ቅጥ ክልሎችን የዝናብና የልከ ሙቀት ሁኔታ አስረዱ፡፡
2.የኢትዮጵያን የአየር ቅጥ ክልሎች የሚያሳየዉን ካርታ በመመልከት የሚከተሉትን ቦታዎች ዋና የአየር
ቅጥ አይነት ግለጽ/ጭ፡፡
ሀ.የሰሜን ምስራቅና ደቡብ ዝቅተኛ ቦታዎች አየር ቅጥ ___________________
ለ.የደቡብ ምእራብ ከፍተኛ ቦታዎች አየር ቅጥ__________________
ሐ.የማእከላዊ፣ደቡባዊና ደቡብ ምስራቅ ከፍተኛ ቦታዎች አየር ቅጥ______________
መ.የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ አየር ቅጥ_________________

2.3.4 የአየር ቅጥ ለዉጥና ዉጤቱ


የአየር ቅጥ ለዉጥ
.የአየር ቅጥ ለዉጥ ምን ማለት ነዉ?
የአየር ቅጥ መዛባት ወይም የአየር ቅጥ ተለዋዋጭነት (Climate Variability) ማለት የአየር ቅጥ ይዘቶች
ከመደበኛዉ ወይም አማካይ ስሌታቸዉ ከፍ ወይም ዝቅ የማለት ባህሪ ነዉ፡፡ ለምሳሌ በአንድ ቦታ ከአመት
አመት የሚመዘገበዉ የዝናብ መጠን ከመደበኛዉ (ከአማካዩ) በታች ወይም በላይ ሊሆን ይችላል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የአየር ቅጥ ለዉጥ (climate change) ስንል ግን አማካይ የአየር ቅጥ ይዘቶች ማለትም የአየር ሙቀት፣ የዝናብ
መጠን፣ የአየር ርጥበት፣ የነፋስ ፍጥነት፣ ወዘተ በቀጣይነት መጨመርን ወይም መቀነስን ማለት ነዉ፡፡ ለምሳሌ
የምድራችን አማካይ አመታዊ የአየር ሙቀት በአለፉት መቶ አመታት ጊዜ ዉስጥ እየጨመረ መጥቷል፡፡

የአየር ቅጥ ለዉጥ መንስኤ


የአየር ቅጥ ለዉጥ መንስኤዎች ምንምን ናቸዉ?

የመሬት አየር ቅጥ በተፈጥሯዊ ሂደት ሁልጊዜም ተለዋዋጭ ነዉ፡፡ ዛሬ አለምን በከፍተኛ ሁኔታ እያስሰበ ያለዉ
በሰዉልጅ ድርጊት አማካኝነት የአየር ቅጥ ለዉጥ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ መምጣቱ ነዉ፡፡ በሁሉም
የአለም ክፍል እየታየ ያለዉ የአየር ቅጥ ለዉጥ በሳይንቲስቶች ተጠንቶ መንስኤዉን ለማወቅ ተሞክሯል፡፡
በጥናቱ ዉጤት መሰረት የአየር ቅጥ ለዉጥ መንስኤዎች በሁለት ይመደባሉ፡፡ እነሱም ሰዉ ሰራሽና ተፈጥሯዊ
ምክንያቶች ናቸዉ፡፡

1.ተፈጥሮአዊ ምክንያቶች
የአየር ቅጥ ለዉጥ ሊያስከትሉ የሚችሉ በርካታ ተፈጥሯዊ ደንቢዎች አሉ፡፡ ከነዚህ መካከከል ዋና ዋናዎቹ
አህጉራዊ ሽርተታ (continental drift)፣ ገሞራ (volcano)፣ የዉቅያኖስ ሞገድ (ocean currents)፣ ወዘተ…
ናቸዉ፡፡
ሀ. አህጉራዊ ሽርተታ
ዛሬ የምናዉቃቸዉ አህጉራት የተመሰረቱት አንድ አህጉር ብቻ ከነበረዉ ዉህድ አህጉር /pangea/ መከፋፈል
ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ነዉ፡፡ ዉህድ አህጉር ወደተለያዩ እህጉራት መከፋፈል የጀመረዉ ከሚሊዮኖች አመታት
በፊት ነዉ፡፡ ይህ የአህጉራት መከፋፈል የመሬትን ገጽታ በመለዋወጥና የአህጉራትንና የዉኃማ አካላትን መገኛ
/አቀማመጥ/ በመቀየር በአየር ቅጥ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ አሳድሯል፡፡ በተጨማሪም የአህጉራት ክፋፍል የነፋስና
የወቅያኖስ ሞገዶችን አቅጣጫ በማስቀየር ለአየር ቅጥ መለወጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

ለ. ገሞራ
እሳተገሞራ ሲፈነዳ ከፍተኛ መጠን ያለዉ የሰልፈር ዳይአክሳይድ (so2 )፣ ወሀ ላቮት (water vapour)፣ የአቧራ
ብናኝና አመድ ወደ ከባቢ አየር ይገባል፡፡ ምንም እንኳ የገሞራ ፍንዳታ ለትንሽ ቀናት የሚቆይ ቢሆንም በአንድ
ጊዜ ወደ ከባቢ አየር የሚገባዉ ከፍተኛ መጠን ያለዉ ጋዝና አመድ ለብዙ አመታት በአየር ቅጥ ላይ ተጽእኖ
ያሳድራል፡፡ በተለይምጋዞችና የአቧራ ብናኞች በአናቶስፊር (stratosphere) ዉስጥ በመከማቸትና ከፀሀይ ወደ
መሬት የሚመጣዉን የጨረር ሐይል በማገድ በመሬት ላይ ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ እንዲከሰት ያደርጋሉ፡፡
ሐ. የዉቅያኖስ ሞገድ
የዉቅያኖስ ሞግድ የአየር ቅጥ ስርአት ዋና አካል ነዉ፡፡ የዉቅያኖስ ሞገድ ልከ ሙቀትን ከቦታ ቦታ በማንቀሳቀስ
የአየር ቅጥ ለዉጥ ያስከትላል፡፡ አብዛኛዉ የዉቅያኖስ ሙቀት በዉሀ ላቮት መልክ ወደ ከባቢ አየር በመሄድ
አፍላሽ ጋዝ (Green house gas) ይሆናል:: በተጨማሪም ከወቅያኖስ ወደ ከባቢ አየር የሚገባዉ የዉሀ ላቮት

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ለደመና ስሪት አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ ደመናዉ ደግሞ ከፀሀይ የሚመጣዉን የሙቀት ጨረር መሬት ላይ
እንዳይደረስ በማድረግ በመሬት ላይ ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታን ያስከትላል፡፡

2.ሰዉ ሰራሽ ምክንያቶች


የሰዉ ልጅ የሚያከናዉናቸዉ ተግባራት በአየር ቅጥ ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩት እንዴት ነዉ?
የ 19 ኛዉ ክፍለ ዘመን የኢንዱስትሪ አብዮት ቅሪት ነዳጅን /fossil fuel / ለኢንዱስትሪ ተግባር በስፋት
እንዲያገለግል አድርጎታል፡፡ እንዱስትሪዎቹም ለብዙ ሰዎች የስራ እድል በመፍጠራቸዉ ሰዎች ከገጠር ወደ
ከተማ ፈልሰዋል፡፡ ይህ ሁኔታ ዛሬም ቀጥሏል፡፡ የሰዉ ልጅ የተፈጥሮ ሀብቶችን ለግንባታ፣ ለኢንዱስትሪ፣
ለትራንስፖርትና ለቤት ዉስጥ ፍጆታ በስፋት እየተጠቀመ ነዉ፡፡ የሰዎች ቁሳዊ ፍላጎትም ከልክ በላይ
ጨምሯል፡፡ እንዲሁም የህዝብ ቁጥር በአስገራሚ ሁኔታ ጨምሯል፡፡ እነዚህ ክስተቶች በከባቢ አየር ዉስጥ
የአፍላሽ ጋዝ እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
ለአየር ቅጥ ለዉጥ መንስኤ ከሆኑት ሰዉ ሰራሽ ምክንያቶች አንዱ የአፍላሽ ጋዞች በከባቢ አየር ዉስጥ
መከማቸት ነዉ፡፡
የአፍላሽ ጋዞች ዉጤት /the effect of Green house gases/

ሀ. ተፈጥሮአዊ የአፍላሽ ጋዝ ዉጤት


በስርዓተ ፀሀይ ዉስጥ ዋና የሀይል ምንጭ ፀሀይ ስትሆን በፀሀይና በመሬት መካከል የጨረር ሀይል ልዉዉጥ
ይካሄዳል፡፡ መሬት ከፀሀይ የምታገኘዉን የጨረር ሀይል መልሳ ወደ ህዋ መርጨት አለባት ፡፡ በዚህ የጨረር ሀይል
ልዉዉጥ ከባቢ አየር የራሱን ሚና ይጫወታል፡፡

ከፀሀይ የሚመነጨዉና ወደ መሬት የሚመጣዉ አብዛኛዉ ባለአጭር ሞገድ ጨረር (short wave solar
radation) በከባቢ አየር ዉስጥ ዘልቆ በማለፍ የመሬትን ገጽ እንዲሞቅ ያደርጋል፡፡ መሬትም በበኩሏ የራሷን
ባለረዥም ሞገድ ጨረር (long wave radation) በማመንጨት ወደ ከባቢ አየርና ወደ ህዋ መልሳ ትረጫለች፡፡
በከባቢ አየር የሚገኙ አንዳንድ ጋዞች ከመሬት የሚመነጨዉን የረዥም ሞገድ ጨረር ዉጦ በማስቀረትና መልሶ
በመርጨት የመሬትን ገጽና አቅራቢያዉ የሚገኘዉን አየር ከፍ ያለ ሙቀት እንዲኖር ያደርጋል፡፡ ይህ ተፈጥሯዊ
ክስተት የአፍላሽ ጋዞች ተጽእኖ /ዉጤት/ በመባል ይታወቃል፡፡ ስእል 2.4 ትን ተመልከቱ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ምንም እንኳ ከባቢ አየር በአብዛኛዉ (99 በመቶ) የናይትሮጅን እና ኦክስጅን ድብልቅ ቢሆንም ከመሬት
የሚመነጨዉን ባለረዥም ሞገድ የጨረር ሀይል በይበልጥ ዉጦ የማስቀረት ባህሪ ያላቸዉና ለተፈጥሯዊዉ
የአፍላሽ ጋዞች ዉጤት አስተዋጽኦ የሚያደርጉት በአነስተኛ መጠን የሚገኙት የዉሀ ተን፣ ካርቦንዳይ ኦክሳይድ፣
ሚቴን፣ ናይትረስ አክሳይድ፣ኦዞን፣ ወዘተ ሲሆኑ እነዚህ ጋዞች አፍላሽ ጋዞች /Green house gases/ በመባል
ይታወቃሉ፡፡
ለ. ሰዉ ሰራሽ የአፍላሽ ጋዝ ክምችትና ዉጤት
ከህዝብ ቁጥር ማደግና ከኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ ወደ ከባቢ አየር የሚለቀቀዉ የአፍላሽ ጋዝ
መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ ነዉ፡፡ለምሳሌ ከኢንዱስትሪዉ አብዮት በፊት ከነበረዉ ጋር
ሲነጻጸር በአሁኑ ጊዜ ካርቦንዳይ ኦክሳይድ፣ ሚቴንና ናይትረስ ኦክሳይድ በከፍተኛ መጠን ጨምረዉ ይገኛሉ፡፡
ፍሎሮክሎሮካርቦንስ (CFC)፣ ፐርፍሎሪኔትድካርቦን (PFCS)፣ ሀይድሮፈለሮ ካርቦን እና
ሰልፈርሄክሳይፈሎራይድ (SF6 ) በመባል የሚታወቁ ጋዞች ከሰባ አመታት በፊት ፈጽሞ በከባቢ አየር ዉስጥ
ያልነበሩና ሙሉ በሙሉ ሰዉ ሰራሽ የኢንዱስትሪ ኬሚካሎች ናቸዉ፡፡

የአፍላሽ ጋዞች ክምችት በከባቢ አየር ዉስጥ እየጨመረ መምጣት የአፍላሽ ጋዞች ዉጤት እንዲጠናከር ወይም
እንዲጎለብት በማድረግ የአለማችንን መሞቅና የአየር ቅጥ ለዉጥ ሊያስከትል እንደሚችል ይታመናል፡፡

የአፍላሽ ጋዝ ምንጮች
የአፍላሽ ጋዞች በከባቢ አየር ዉስጥ አንዴ ከገቡ ለብዙ አመታት የመቆየት ባህሪ አላቸዉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ
ከመሬት የሚመነጨዉ ረዥም ሞገድ የጨረር ሀይልን ዉጦ የማስቀረት ችሎታቸዉ የተለያየ ነዉ፡፡ የአፍላሽ
ጋዝ ምንጭ የሆኑ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ብዙና የተለያዩ ናቸዉ፡፡ ከዚህ ቀጥሎ በዋናናት የሚታወቁት

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የሶስቱን አፍላሽ ጋዞች ማለትም ካርቦንዳይኦክሳይድ፣ ሚቴንና ናይትረስ ኦክሳይድ ምንጮችን ለማብራራት
ተሞክሯል፡፡

ሀ.ካርቦንዳይኦክሳይድ
የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች የሀይል ፍላጎትን ለማሟላት ሲባል የቅሬተ አካል ነዳጅ
ማለትም የከሰል ደንጋይን፣ ዘይትን፣ የተፈጥሮ ጋዝን መጠቀም ዋናዉ የካርቦንዳይኦክሳይድ ምንጭ ነዉ፡፡
የኤሌክትሪክ ኀይል ማመንጫ ጣቢያዎች፣ ኢንዱስትሪዎች፣ መኪኖች፣ አዉሮፕላኖች፣ ባቡሮችና መርከቦች፣
ቤት ዉስጥ፣ የንግድና የመንግስት ተቋማት የሀይል ፍላጎታቸዉን የሚያሟሉት የቅሪተ አካል ነዳጅን
በመጠቀም ነዉ፡፡ የደን መጨፍጨፍ ሌላዉ አይነተኛ የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት ምንጭ ነዉ፡፡
ከኢንዱስትሪዉ አብዮት ጀምሮ የቅሪተ አካል ፍጆታ በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር ላይ ነዉ፡፡

ለ.ሚቴን (CH4)
ሰዉ ሰራሽ ሚቴን ወደ ከባቢ አየር የሚገባዉ ከቆሻሻ አያያዝ፣ ከእርሻ እንቅስቃሴና ከቅሪተ አካል ነዳጅ
የአመራረት አጠቃቀምና የስርጭት ሂደት ነዉ፡፡
ካርቦን አዘል ቁስ አካል ኦክስጅን በሌለበት ሁኔታ በባክተሪያ አማካኝነት ሲበሰብስ ወይም ሲፈራርስ ሚቴን
ይፈጥራል፡፡ ለምሳሌ ደረቅ ቆሻሻ የሚጠራቀምባቸዉ ጉድጓዶች በሚቴን አመንጭነታቸዉ ይጣወቃሉ፡፡
ከኢንዱስትሪና ከቤት ዉስጥ የሚወጣ ፍሳሽ ቆሻሻ፣ የሴፕቲክታንክና የጉድጓድ ሽንት ቤቶች የሚቴን ምንጭ
ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የተፈጥሮ ጋዝ አመራረት፣አጠቃቀምና የስርጭት ሂደት ሚቴንን ያመነጫል፡፡

ሐ.ናይትረስ አክሳይድ (N2O)


ናይትረስ ኦክሳይድ የሚፈጠረዉና ወደ ከባቢ አየር ሊገባ የሚችልባቸዉ መንገዶች ናይትሮጅን አዘል
የኬሚካልና የኦርጋኒክ ማዳበሪያዎች ከአፈር ጋር መቀላቀል፣ ቅሬተ አካል ነዳጅ በሚቃጠልበት ጊዜ
የናይትሮጅንና የኦክሲጅን መዋሀድ፣ አሲድ ለማምረት ሲባል አሞኒያ ከኦክሲጅን ጋር ሲገኛኝ፣ወዘተ ናቸዉ፡፡
በመሆኑም የአስተራረስ ዘዴ፣ የአፈር ማዳበሪያ አጠቃቀም፣ ቅሬተ አካል ነዳጅን ማቃጠል ፣የናይትሪክ አሲድ
በፋብሪካዎች መመረት፣ እንዲሁም የሰብል ተረፈ ምርትን ወይም ቃርሚያን የማቃጠል እንቅስቃሴ ለናይትረስ
ኦክሳይድ ዋናዋና ምንጮች ናቸዉ፡፡
የአየር ቅጥ ለዉጥ ዉጤቶች /consequences of climate change/

የአየር ቅጥ ለዉጥ የሚያስከትላቸዉ ዉጤቶች ምንምን ናቸዉ?

የተረጋጋ የአየር ቅጥ ዘላቂነት ላለዉ ልማት አንዱ ቅድመ ሁኔታ ነዉ፡፡ ባለፉት 10 ሽህ አመታት የመሬት
አማካይ አመታዊ የአየር ሙቀት ብዙ ለዉጥ ያልታየበትና የተረጋጋ እንደነበረ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ከላይ እንደተገለጸዉ በአፍላሽ ጋዞች መጨመር ምክንያት ሊከሰት የሚችለዉ የአየር ቅጥ ለዉጥ የተለያዩ
ክስተቶችን ያስከትላል፡፡ ከነዚህ መካከል ዋናዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸዉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሀ. የአለም አማካይ የሙቀት መጠን መጨመር /Global warming/፡- የአለም የሙቀት መጠን መጨመር
ሲባል የገጸምድር አማካይ የሙቀት መጠን መጭመር ማለት ነዉ፡፡ በ 2007 በበየነመንግስታቱ የአየር ቅጥ
ለዉጥ ፓኔል / Intergovernmental panel on climate change / የተዘጋጀዉ አራተኛዉ የአየር ቅጥ ለዉጥ
ግምገማ ሪፖርት እንደሚያሳየዉ በ 20 ኛዉ ክፍለ ዘመን የገጸ-ምድር አማካይ የሙቀት መጠን በ 0.74
ዲግሪ ሴልሸስ ጨምሯል፡፡ ይህ በ 20 ኛዉ ክፍለ ዘመን አጋማሽ የተከሰተዉ የአለም አማካይ የሙቀት
መጠን መጨመር ዋና መንስኤዉ በከባቢ አየር ዉስጥ የአፍላሽ ጋዞች ክምችት መጨመር ነዉ፡፡ ይህም
በጣም ከፍተኛ በመሆኑ የሚያስከትለዉ ጉዳት እንዲሁ በቀላሉ የሚገመት አይደለም፡፡

ለ. የበረሀማነት መስፋፋት፡- በአየር ቅጥ ለዉጥ ምክንያት የሰፈራ ቦታዎች፣ የእርሻ ቦታዎች፣ የሳር ምድሮች፣
ርጥብ መሬት፣በደን የተሸፈኑ ቦታዎች፣ወዘተ ወደ በረሀማ አካባቢ ሊለወጡ ይችላሉ፡፡

ሐ. ድርቅ፡- የአየር ቅጥ ለዉጥ ድርቅ በተደጋጋሚ እንዲከሰት ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ በኢትዮጵያ ለድርቅ ተጋላጭ
በሆኑ አካባቢዎች ድርቅ በ 3 እና 8 አመታት መሀል እንደገና ይከሰታል

መ. የባህር ወለል ከፍ ማለት፡- ዉሀ ሲሞቅ ስለሚለጠጥ የበለጠ ቦታ ይዛል፡፡ ይህ ደግሞ ዉቅያኖስ ሲሞቅ
የባህር ወለል ከፍ እንደሚል ያስረዳል፡፡ በዚህ ክፍለ ዘመን መጨረሻ በአየር ቅጥ ለዉጥ የተነሳ አለምአቀፍ
አማካይ የባህር ወለል ከ 18 -59 ሴንቲሜተር ከፍ እንደሚል ይጠበቃል፡፡ የባህር ወለል ከፍ ማለት ትንንሽ
ደሴቶችንና በባህር ዳርቻ የሚገኙ ከተሞችን በጎርፍ እንዲጥለቀለቁ ሊያደርግ ይችላል፡፡

ሠ. የገሞጅማ ሰቅ መገኛ መስፋፋት፡- በአየር ቅጥ ለዉጥ የተነሳ የገሞጅማ ሰቅ ከትክክለኛ መገኛዉ ከአንድ
ዲግሪ ባላነሰ መጠን ወደ ሰሜናዊና ደቡባዊ ንፍቀ ክበቦች ሊሰፋ እነደሚችል ይጠበቃል፡፡

ረ. የአለም አቀፍ ነፋሶች አቅጣጫ መቀየር፡- የአለም አቀፍ ሙቀት መጠን ከጨመረ ጀት-ስትሪምስ /Jet
streams/ ይዳከማሉ፣ አለም አቀፍ ነፋሶችም መደበኛ አቅጣጫቸዉን እንዲቀይሩ ይገደዳሉ፡፡ ይህ ክስተት
መደበኛዉን ወቅታዊ የዝናብ ስርጭት ያናጋል፡፡

ሰ. የብዘኅ ህይዎት መጥፋት፡- የአለም አቀፍ ሙቀት መጠን መጨመር አንዳንድ ህይዎት ያላቸዉን ነገሮች
ከምድር እንዲጠፉ ያደርጋል፡፡ የአለም አቀፍ አማካይ የሙቀት መጠን አሁን ከአለዉ መጠን በሁለት ዲግሪ
ሴልሸስ ከጨመረ ሁሉም ህይዎት ያላቸዉ ነገሮች ወደ መጥፋት ደረጃ የሚያደርስ አደጋ /ስጋት/ ላይ
ይወድቃሉ ተብሎ ይገመታል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ተግባር- 2.11
1. በአካባቢያችሁ የአየር ቅጥ ለዉጥ መከሰቱን ታዉቃላችሁ? ታዉቁ ከሆን ምን አይነት የአየር ቅጥ ለዉጥ
ተከስቷል?
2. በአካባቢያችሁ የአየር ቅጥ ለዉጥ በተፈጥሮ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ያስከተላቸዉን ጉዳቶች ዘርዝሩ
3. በአካባቢያችሁ የአሁኑ የዝናብና የሙቀት መጠን ከቀደምት አመታት ጋር ሲነጻጸር ልዩነት አለዉ?
ወላጆቻችሁን ወይም ሌሎች ታላላቅ ሰዎችን ጠይቃችሁ ሪፖርት አቅርቡ፡፡
4. በአካባቢያችሁ በአየር ቅጥ ለዉጥ ምክንያት የዉሀ መጠናቸዉ የቀነሰ ወይም የደረቁ ወንዞች፣ሀይቆችና
ረግረጋማ ቦታዎች አሉ? መልሳችሁ አዎ ከሆነ ስለሁኔታዉ ሪፖርት ጽፋችሁ ለክፍል ጓደኞቻችሁ
አቅርቡ፡፡

የአየር ቅጥ ለዉጥን ለመከላከል መወሰድ ያለባቸዉ እርምጃዎች

በአየር ቅጥ ለዉጥ ዙሪያ የሚወሰዱ እርምጃዎች በሁለት አቅጣጫ ያተኮሩ ናቸዉ፡፡


አንደኛዉ የአፍላሽ ጋዝ ልቀት መጠንን የመቀነስ እርምጃ ሲሆን፣ ሁለተኛዉ የአየር ሙቀት መጨመርና የአየር
ቅጥ ለዉጥ ሊያስከትል የሚችለዉን ጉዳት ለመቀነስና ለመቋቋም የሚያስችሉ መንገዶችን ለይቶ በማወቅ
ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ ነዉ፡፡
የአፍላሽ ጋዝ ልቀት መጠንን ለመቀነስ ሊወሰዱ የሚችሉ እርምጃዎች፡-
ሀ.በኢነርጅ ዘርፍ
 የኢነርጅ ቁጠባን የማሻሻል ፕሮግራም መቅረጽና ተግባራዊ ማድረግ
 የከሰል ደንጋይ፣ የተፈጥሮ ነዳጅ ዘይትና የተፈጥሮ ጋዝ ፍጆታችንን መቀነስ
 ንጹህና ታዳሽ ማለትም የጸሀይ፣ የባዮማስ፣ የነፋስና የሀይድሮ ኢነርጅ ምንጮችን መጠቀም
ማበረታታት
ለ.በደን ዘርፍ
 አንድ ዛፍ በቆረጥን ቁጥር ቢያንስ ሁለት ዛፍ መትከላችንን ማረጋገጥ
 በከተሞችና መንደሮች አካባቢ ለማገዶ የሚሆኑ የማህበረሰብ ደኖችን ማልማት
 የደን ጭፍጨፋን ማስቆምና አሁን ላሉት የተፈጥሮ ደኖች ጥበቃ ማድረግ
 የደን ተከላ ፕሮግራም በመዘርጋት አዲስ ደኖችን ማልማት
 ጥምር ግብርናንና ደን ልማት ልምድን ማዳበር
ሐ. በእርሻዉ ዘርፍ
 ዘላቂነት ያለዉ የግብርና ዘዴን መከተል
 አግባብ ያለዉ የመሬት አጠቃቀምን መከተል
 የእርሻ ምርታማነትን ማሳደግ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 የግጦሽ መሬት ምርታማነትን ማሻሻል


 የተለያዩ ሰብሎችን በአንድ ጊዜ የመዝራት ልምድ ማዳበር
 የሰብሎችን ተረፈ ምርት/ቃርሚያ/ ከማቃጠል መቆጠብ
 አግባብነት ያለዉ የከብት እርባታ ዘዴን መከተል
መ. በትራንስፖርት ዘርፍ
 መኪናን ብዙ ከማሽከርከር መቆጠብ
 በተቻለ መጠን የህዝብ ትራንስፖርትንና ባይስክሎችን መጠቀም
 የትራንስፖርት ኢንፍራስትራክቸርን ማሻሻል
 የመኪና ጥገና ጋራዦችን ቴክኒካዊ ብቃት ማጠናከር
ሠ. በደረቅ ቆሻሻ አያያዝ ዘርፍ
 ከከተሞች የሚወጣ የኦርጋኒክ ቆሻሻን የአፈር ለምነትን ለማሻሻል መጠቀም
 በቆሻሻ ማጠራቀሚያ ጉድጓዶች የሚፈጠር ሚቴንን ለኢነርጅ ምንጭነት መጠቀም
 በደረቅ ቆሻሻ መልሶ የመጠቀም ልምድን ወይም ባህልን ማዳበር

ተግባር- 2.12
1. በአካባቢያችሁ የአየር ቅጥን ለዉጥ ለመከላከል በህብረተሰቡና በመንግስት የተሰሩ
ስራዎችን ዘርዝሩ፡
2. የአየር ቅጥ ለዉጥን ለመከላከል የእናንተ ድረሻ ምን መሆን አለበት ብላችሁ ታስባላችሁ?
3. የአየር ቅጥ ለዉጥን ለመከላከል የአደጉ አገሮች ምን ማድረግ አለባቸዉ ብላችሁ ታስባላችሁ?
ታዳጊ አገሮችስ?

2.4. ስርዓተ ምኅዳር /Ecosystem/


 ስርዓተ ምኅዳር ማለት ምን ማለት ነዉ?
 የስርዓተ ምኅዳር አካላት ምንምን ናቸዉ?
 በስርዓተ ምኅዳር አካላት መካከል ያለዉ መስተጋብር ምንድን ነዉ?

ስርዓተ ምኅዳር የሚለዉን ቃል መጀመሪያ ያፈለቀዉ እንግለዛዊ የሰነ ምዳር ተመራማሪ A.G Tansley እ.ኤ.አ
በ 1935 ሲሆን ትርጉሙንም እንዲህ ሲል ገልጾታል “ስርአተ ምህዳር በአንድ ተፈጥሯዊ አካባቢ እጽዋት፣
እንስሳት፣ ሌሎችም ህይወት ያላቸዉና ህይወት የሌላቸዉ ነገሮች የህይወት ዑደት ተሳስሮ የሚገኝበት
ተፈጥሯዊ ስርዓት ነዉ፡፡” በአንድ አካባቢ የሚገኙ ሁሉም ህይወት ያላቸዉና ህይዎት የሌላቸዉ ነገሮች
እርስበርሳቸዉ ግንኙነት / መስተጋብር/ ያደርጋሉ፡፡ ግንኙነታቸዉም ተደጋግፈዉ እንዲቆዩ ይረዳቸዋል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የስርዓተ ምህዳር አካላት ለመኖር ከተፈጥሯዊ አካባቢያቸዉና አርስበርሳቸዉ የሚያደርጉትን ግንኙነት


/መስተጋብር/ በተመለከተ የሚደረግ ሳይንሳዊ ጥናት ስነ ምህዳር/ecology/ ይባላል፡፡

ስርዓተ ምኅዳሮች በስፋታቸዉ ይለያያሉ፡፡ አንዳንዶቹ ትንሽ ቦታ የሸፈኑ ሲሆኑ አንዳንዶቹ ደግሞ በጣም ሰፊ
ናቸዉ፡፡ ለምሳሌ የአፍሪካ የበረሀ ስርዓተ ምህዳርና የበራዚል ዶፍማ ደን (rainforest) ስፊ ቦታ ስለያዙ በጣም
ሰፊ ስርዓተ-ምህዳሮች ናቸዉ፡፡

2.4.1 የስርዓተ ምኅዳር አካላት

የስርዓተ ምኅዳር አካላት ህይወት ያላቸዉና ህይወት የሌላቸዉ ተብለዉ በሁለት ይመደባሉ፡፡ ህይወት የሌላቸዉ
የስርዓተ ምኅዳር አካለት ዉሀ፣ ማእድናት፣ የፀሀይ ብርሀን፣ አየር፣ አየር ቅጥና አፈር ሲሆኑ ህይወት ያላቸዉ
የስርዓተ ምኅዳር አካላት ደግሞ በተፈጥሯዊ መጠለያ የሚኖሩ ሁሉንም ህይወት ያላቸዉን ነገሮች
ያጠቃልላል፡፡ ህይወት ያላቸዉ አካላት ምግባቸዉን ለማግኘት በሚጠቀሙበት መንገድ መሰረት በሶስት ዋና ዋና
ምድቦች ይመደባሉ፡፡ እነሱም አምራቾች (producers)፣ ተመጋቢዎች (consumers) እና አፈራራሾች
(decomposers) ናቸዉ፡፡

አምራቾች፡- እነዚህ በብርሀን ዝግጅ /ብርሀን ቅመም/ (photosynthesis) ሂደት የራሳቸዉን ምግብ የሚያዘጋጁ
አረንጓዴ ተክሎችና ትንንሽ ዉሀ አቅላሚዎች/ Algae/ ናቸዉ፡፡
ተመጋቢዎች፡- እነዚህ ደግሞ የራሳቸዉን ምግብ ማዘጋጀት የማይችሉና የሚፈልጉትን ምግብ ለማግኘት
በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የአምራቾች ጥገኛ ሆነዉ የሚኖሩ ናቸዉ፡፡ በአምራቾች የተዘጋጁ ቁሳዊ ነገሮችን
እየተመገቡና አየተጠቀሙ የሚኖሩ ናቸዉ፡፡ ተመጋቢዎች በአመጋገባቸዉ ልማድ መሰረት በሶስት ይከፈላሉ፡፡
እነሱም እጸ በል (Herbivorous)፣ ስጋ በል (carnivorous ) እና ሁሉን በል /ስጋና እጽዋት/ (omnivorous)
ናቸዉ ፡፡
አፈራራሾች / decomposers /:- እነዚህ ደግሞ የሞቱና የበሰበሱ ቅሪት አካላትን የሚመገቡና ህያዉ ቁስ-አካልን
/organic matter/ ወደ ህይወት የሌለዉ ቁስ-አካል /inorganic matter/ የሚቀይሩ ህይወት ያላቸዉ ነገሮች
ናቸዉ፡፡ ለምሳሌ ባክተሪያዎች የሞቱ ቁስ አካላትን አፈራራሾች ናቸዉ፡፡

ተግባር-2.13
በአካባቢያችሁ ከሚገኙ እንስሳት መካከል እጸ በል፣ ስጋ በልና ሁሉን በል የሆኑትን ለይታችሁ ዘርዝሩ፡፡

የስርዓተ- ምኅዳር አካላት ከፍተኛ መደጋገፍ ወይም ቁርኝት አላቸዉ፡፡ ለምሳሌ እጽዋት በአግባቡ የሚያድጉት
ለም አፈር ሲኖር ነዉ፡፡ የእጽዋት ቅጠል ሲረግፍ መሬት ላይ ወድቆ በመበስበስ የአፈሩን ለምነት ይጨምራል፡፡
እንስሳት ለህይወታቸዉ መቀጠል እጽዋት ያስፈልጋቸዋል፡፡ የእንስሳት ቅሪት አካላት ደግሞ ለአፈር ለምነት
በእጅጉ አስፈላጊ ናቸዉ፡፡ የስጋ በል እስሳት ህልዉና የተመሰረተዉ በቅጠልና ሳር በል በሆኑ እንስሳት ህልዉና ላይ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ነዉ፡፡ ሳር በልና ስጋ በል እንስሳት ህልዉናቸዉ የተመሰረተዉ በአካባቢዉ በሚገኙ እጽዋትና እንስሳት ላይ ነዉ፡፡
ስለዚህ በአንድ ስርዓተ-ምህዳር ዉስጥ የሚገኙ የተለያዩ አካላት መካከል ከፍተኛ የመደጋገፍና የቁርኝት ስርአት
በመኖሩ የአንዱ ህልዉና ወይም ጉዳት በሌላዉ ላይ ቀጥተኛ ወይንም ቀጥተኛ ያልሆነ ተጽእኖ ያስከትላል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በአለማችን በተለያዩ ምክንያት እጽዋት እየወደሙና እየተጨፈጨፉ ይገኛሉ፡፡ ማእድናት በብዛት
ይወጣሉ፡፡ መሬትም በከፍተኛ ደረጃ ይታረሳል፡፡ ዉሀም ለተለያዩ አገልግሎቶች ይዉላል፡፡ የሰዉ ልጅ ፍላጎትና
የአኗኗር ዘይቤ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተለወጠና እያደገ በመምጣቱ በስርዓተ ምህዳር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ
አየፈጠረ ነዉ፡፡

2.4.2. የእንስሳትና የእጽዋት ብዘኃነት / Divresity of Fauna and Flora /


በአንድ በተወሰነ ጅኦግራፊያዊ ክልል የሚገኙ የእጽዋትና እንስሳት ዝርያዎች ብዛትና አይነት የእስሳትና
የእጽዋት ብዘሀነት ይባላል፡፡ በዓለም ላይ የብዘሀ ህይወት ስርጭት ከክልል ክልል ይለያያል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ
የብዘሀ ህይወት ስርጭት በልከ ሙቀት፣ በዝናብ፣ በከፍታና የአፈር ሁኔታ ስለሚወሰን ነዉ፡፡ ለምሳሌ በገሞጂማ
ክልል ከፍተኛ ልከ ሙቀትና ዝናብ ስላለ ብዙ አይነት የእጽዋትና የእስሳት ዝርያዎች ይገኛሉ፡፡ በዋልታዎች
አካባቢ ደግሞ የአየር ቅጡ ለእጽዋትና ለእንስሳት ተስማሚ ባለመሆኑ የእጽዋትና እንስሳት ዝርያና አይነት
አነስተኛ ነዉ፡፡

የስርዓተ ምህዳርን ዓይነት የሚወስኑ ዋና ዋና ደንቢዎች ልከ ሙቀት፣ ዝናብ፣ የአፍር አይነት፣ የኬክሮስ መገኛና
ከፍታ ናቸዉ፡፡ ከነዚህ ደንቢዎች መካከከል የሰርዓተ ምህዳርን አይነት በመወሰን ረገድ አየር ቅጥ የሚጫወተዉ
ሚና በእጅጉ ከፍተኛ ነዉ፡፡ እነዚህ ደንቢዎች በአካባቢያቸዉ ከሚገኙ ህይዎት ያላቸዉ ነገሮች ጋር
የሚያደርጉት መስተጋብር ለተለያዩ የተፈጥሮ ስርዓተ ምህዳሮች መኖር ምክንያት ሆኗል፡፡

የተፈጥሮ ስርተ ምህዳሮች ከሚገኙበት የመሬት ክፍል አኳያ ሲታዩ የዉሀ ዉስጥ ስርዓተ ምህዳሮችና ምድራዊ
ስረዓተ ምህዳሮች ተብለዉ በሁለት ይመደባሉ፡፡ በዉሀ ዉስጥ የሚገኙ ስርዓተ ምህዳሮች የዉሀ ዉስጥ ስርዓተ
ምህዳሮች ተብለዉ ይጠራሉ፡፡ ዉቅያኖሶች፣ ሀይቆች፣ወንዞችና ኩሬዎች የዉሀ ዉስጥ ስርዓተ ምህዳር
ምሳሌዎች ናቸዉ፡፡

በየብስ ላይ የሚገኙ ስርዓተ ምህዳሮች ደግሞ ምድራዊ ስርዓተ ምህዳሮች ይባላሉ፡፡ እነዚህ ስርዓተ ምህዳሮች
ህይወት ያላቸዉና ህይዎት የሌላቸዉ የስርዓተ ምህዳር አካላት በሚያደርጉት መስተጋብር መሰረት በስድስት
ዋናዋና የስርዓተ ምህዳር ክልሎች ይመደባሉ፡፡ እነሱም በርሀ / desert /፣ ጮቄ/ tundra/፣ የሳር ምድር/
grassland /፣ ቅጠል አርጋፊ ደን /deciduous forest /፣ የታይጋ ደን / taiga or coniferious forest / አና
ጎሞጅማ ዶፍ ጫካ / tropical rain forest / ናቸዉ፡፡

እያንዳንዱ ስርዓተ ምህዳር የራሱ የሆነ የአየር ቅጥ፣ የአፈር፣ የእጽዋትና የዱር እንስሳት አይነት አለዉ፡፡
እንዲሁም እያንዳነዱ ስርዓተ ምህዳር በተለያዩ የአለም ክፍሎች ሊገኝ ይችላል፡፡ ለምሳሌ የበረሀ ሥርዓተ
ምህዳር በሰሜን አሜሪካ፣ በአፍሪካ፣ በደቡብ አሜሪካ፣ በእስያና በአዉስትራሊያ ይገኛል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሀ.በረሀ
አንድን ቦታ በረሀ የሚያስብለዉ ዋናዉ ነገር የዝናብ እጥረት ነዉ፡፡ በረሀ ስንል አመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኑ
ከ 25 ሴንቲሜትር በታች የሆነን ማንኛዉንም ቦታ ማለት ነዉ፡፡ ልከ ሙቀቱም በቀን ከ 25-40 ዲግሪ
ሴንቲግሬድና በላይ ሲሆን በሌሊት ደግሞ ከ 0 ዲ.ሴ በታች ይቀዘቅዛል፡፡ በበረሀማ ቦታዎች ብዙ የእጽዋትና
የእንስሳት ዝርያዎች ቢኖሩም የእያንዳንዱ ዝርያ ብዛት ግን አነስተኛ ነዉ፡፡ የእጽዋት ዝርያዎቹም ደረቅ፣
በጣም ሞቃትና ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታን መቋቋም የሚችሉ ናቸዉ፡፡ በሞቃት በረሀማ ቦታዎች የእርጥበትና
የእጽዋት ሽፋን እጥረት ስላለ የአፈር ስሪት ሂደቱ ደካማ ነዉ፡፡ በመሆኑም የበረሀ መሬት በአሸዋ፣ በጠጠርና
በአለቶች የተሸፈነ ነዉ፡፡ እንደ እባብ፣ እንሽላሊት፣ ቀበሮ የመሳሰሉት እንስሳት በአካባቢዉ የተለመዱ ናቸዉ፡፡

ተግባር- 2.14
1.ሶስቱን ዋና ዋና የበረሀ አይነቶች ዘርዝሩ፡፡
2.አንዱ የበረሀ አይነት ከሌላዉ በምን ይለያል?
3.የበረሀ እጽዋትና እንስሳት ሙቀትንና የዉሀ እጥረትን የሚቋቋሙበትን ዘዴ አስረዱ፡፡

ለ. ጮቄ
ይህ ክልል በዋልቴ የበረዶ ቁልልና በቅንምብብማ ጫካዎች መካከል የሚገኝ ነዉ፡፡ የከፍተኛ ኬክሮስ ቀዝቃዛ
የአየር ቅጥ በዋልታዎች አካባቢ እጽዋት እንዳይበቅሉ ስለሚያግድ ጮቄ በጣም ቀዝቃዛና ዛፍ የለሽ ስርዓተ-
ምህዳር እንዲሆን አድርጎታል፡፡ በጮቄ ስስዓተ ምህዳር የፀሀይ ጨረር በጣም ያጋደለ በመሆኑ በ 3 ወይም 4
ወሮች ብቻ ከ 0 ዲግሪሴንቲግሬድ በለይ ልከ ሙቀት ይመዘገባል፡፡ አመታዊ አማካኝ የዝናብ መጠኑ ከ 250
ሚ.ሚ በታች ነዉ፡፡

እጽዋት ለመብቀልና ለማደግ በቂ ሙቀት ስለሚያስፈልጋቸዉ በዚህ ስርዓተ ምድር ብዙ እጽዋት አይበቅሉም፡፡
ይሁን እንጅ መጠነኛ ሙቀት ባላቸዉ አካባቢዎች እንደ በሌሎቶችና በሌሴቶች ያሉ ትንንሽ የእጽዋት
ዝርያዎች ይበቅላሉ፡፡

ይህን ስርዓተ ምኅዳር ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታን ለመቋቋም የሚያስችል ጠንካራ ቆዳና ጸጉር ያላቸዉ እንደ ድብና
የአርክቲክ ቀበሮ መሰል እንስሳት ለግጦሽና ለመጠለያነት ይጠቀሙበታል፡፡

በጮቄ ስርዓተ ምኅዳር መሬት ላይ የተከማቸዉ ግግር በረዶ ዉሀ ወደ ዉስጥ እንዳይሰርግ ስለሚያግድ ታች
አፈር/ sub soil/ ሁልጊዜ በረድ ሲሆን የላይኛዉ አፈር ደግሞ ዉሀ አዘል ነዉ፡፡ በዉሀ አዘል አፈር ዉስጥ
የአክስጅን እጥረት ስላለ የባክተሪያዎችን ቅሪት አካላትን የማፈራረስ ተግባር ይገድበዋል፡፡ ይህም የጮቄ ምድር
በከፊል በፈራረሱ የእጽዋት አካላት እንዲሸፈን አድርጎታል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሐ. የሳር ምድር ክልል


የሳር ምድር ስርዓተ ምህዳር ከአንታረክቲካ በስተቀር በሁሉም አህጉራት ይገኛል፡፡ በክልሉ ከ 60-90 በመቶ
የሚሆነዉ የእጽዋት አይነት ሳር ቢሆንም ቁጥቋጦዎችና ዛፎችም አልፎ አልፎ ይገኛሉ፡፡ይህ ስርዓተ ምህዳር
ከ 600-1500 ሚሊሜትር አመታዊ አማካኝ የዝናብ መጠን የሚያገኝ ሲሆን አመታዊ አማካይ ልከ ሙቀቱ
ደግሞ በ-5 አና 20 ዲ.ሴ መካከል ነዉ፡፡

አነስተኛ የህዝብ ብዛት በሚገኝባቸዉ የሳር ምድር አካባቢዎች ልዩ ልዩ እጸበልና ስጋ በል እንስሳት ይገኛሉ፡፡
ከእጸበል እንስሳት መካከል እንደ ዝሆን፣ የሜዳ አህያ፣ ድኩላ፣ የሚዳ ፍየል የመሳሰሉት ትልልቅ እንስሳት
ይገኛሉ፡፡ ከስጋበል እንስሳት መካከከል ደግሞ አንበሳ፣ነብር፣አቦሸማኔ ፣ተኩላና ጅብ ወዘተ የመሳሰሉት ይገኛሉ፡፡

ተግባር- 2.15
1.ሶስቱን ዋና ዋና የሳር ምድር አይነቶች ዘርዝሩ፡፡
2. አንዱ የሳር ምድር ዓይነት ከሌላዉ በምን ይለያል?
3.በሳር ምድር ተጽእኖ ከሚያሳድሩ የሰዉ ልጅ ድርጊቶች መካከል ቢያንስ አራቱን ጥቀሱ፡፡

መ. ቅጠል አርጋፊ ደን
ቅጠል አርጋፊ ደን የዉሀ ብክነትን ለመከላከል ሲባል ቅጠላቸዉን በየአመቱ የሚያረግፉ ዛፎች የሚገኙበት የደን
ስርዓተ ምህዳር ነዉ፡፡ ከዛፎቹ መካከከል የጠንካራ እንጨት ዝርያዎች እንደ ማፕል፣ልምጭ፣ኦአክ፣ የመሳሰሉት
ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም ብዙ አበባማ እጽዋት በበልግ ወቀት ይበቅላሉ፡፡ዛፎቹ የዉሀ ብክነትን ለመከላከል
በጸደይ ወቅት ቅጠላቸዉን ያረግፋሉ፡፡ ቅጠሉም በባክተሪያዎች አማካኝነት ስለሚፈራርስ አፈሩ ለምነት
እንዲኖረዉ ይረዳል፡፡

ይህ ክልል በአንጻራዊ መልኩ የተስተካከለ ስርጭት ያለዉ ከ 75-100 ሴ.ሜ የሚሆን አመታዊ አማካይ የዝናብ
መጠን ያገኛል፡፡
ስርዓተ- ምድሩ ለብዙ የተለያዩ ተባዮችና ለትንንሽና ትልልቅ አጥቢ እንስሳት መጠለያ ነዉ፡፡ ከአጥቢ እንስሳት
መካከከል አይጥ፣ ድብ፣ ሞል፣ ቀበሮ፣ ባጀረስ /badgers/ አቁስጣ /weasel /፣ ወዘተ የመሳሰሉት ይገኛሉ፡፡

ሠ. የታይጋ / ቅንብብ ቀጥ/ ደን


ታይጋ በወይኖጌ ክልል በሰሜን አሜሪካ፣ በአዉሮፓ፣በእስያ የሚገኝ ትልቅ ስርዓተ ምህዳር ነዉ፡፡ የበረድ ወቅት
በጣም ቀዝቃዛና በረዷማ ሲሆን የሞቄ ወቅት ደግሞ ሙቅና ዝናባማ ነዉ፡፡ የ 6 ወሮች አማካይ ልከ ሙቀት ከ 0
ዲ.ሴ በታች ነዉ፡፡ አመታዊ የዝናብ መጠን ከ 30-85 ሴ.ሚ ይደርሳል፡፡ የታይጋ ደን ስርዓተ ምኅዳር የአየር ቅጥ
ለእጽዋት እድገት ተስማሚ ባለመሆኑ ብዙ የእጽዋት ዝርያዎች የሉም፡፡ ይሁን እንጅ አስከፊዉን የአየር ቅጥ
መቋቋም የሚችሉ ቀጭን ቅጠል ያላቸዉ እንደ ጥድ፣ ስፕረስ /sprce/፣ ፈር /fir/ የመሳሰሉ ቅንብብ ቀጥ ዛፎች
በብዛት ይገኛሉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

በታይጋ ደን ዉስጥ እጸበልና ስጋበል የሆኑ ልዩልዩ እንስሳት ይገኛሉ፡፡ ከስጋበል እንስሳት መካከከል ተኩላ፣ አይጥ
የሚመስሉ ትንንሽ እስሳት/ voles/፣ አጋዘን ወዘተ… የመሳሰሉት ይገኛሉ፡፡ እንዲሁም በሞቄ ወቅት ተባዮችን
የሚመገቡ ወፎች ከሌሎች ክልሎች ወደ ታይጋ ክልል ይመጣሉ፡፡ የበረድ ወቅት ሲጀምር ወደ መጡበት
ተመልሰዉ ይሄዳሉ፡፡

ረ. የገሞጂማ ዶፍ ጫካ ደን
ይህ ክልል የሚገኘዉ በ 60 ሰሜንና በ 60 ደቡብ በምድር ሰቅ አካባቢ ነዉ፡፡ የዶፍ ጫካ ደን ክልል የአማዞንና የዛየር
ወንዝ ተፋሰሶችን፣ የኮሎንቢያን የባህር ዳርቻ፣ በምስራቅ አፍሪካ ታንዛኒያና የደቡብ ምስራቅ እስያ ደሴቶችን
ይሸፍናል፡፡

በዚህ ክልል በየቀኑ የቀትር ፀሀይ በአናት ላይ ትገኛለች፡፡ የአመቱ አማካይ የሙቀት መጠን 27 ደ.ሴ ይሆናል፡፡
ዝናብ በየቀኑ ከሰዓት በኋላ ይጥላል፡፡ አመታዊ የዝናብ መጠን ከ 1500 -2500 ሚ.ሚ ይሆናል፡፡ ዝናብ
የማይጥልበት ወር የለም፡፡ የክልሉ የዝናብ ዓነት ኮንቬንሽናል ነዉ፡፡

ተስማሚ የዝናብና የሙቀት መጠን በክልሉ የሚገኙትን ተክሎች እድገትና አይነት አዳብሮታል፡፡ ይህ አካባቢ
በአለም ከሚገኙ ሌሎች ስፍራዎች በበለጠ ሁኔታ ዉበት በሚሰጡ ተክሎች ተዥጎርጉሮ ይታያል፡፡ በዚህ ክልል
ከሚገኙ ዛፎች መካከል የጠንካራ እንጨት ዝርያዎች እንደ ሮዝ ዉድ፣ ጥቁር እንጨት፣ ማሆጋኒና የመሳሰሉት
ይገኙበታል፡፡

ለምግብና ለመጠለያነት አመች ሁኔታ በሚፈጥረዉ የደፍ ጫካ ደን ዉስጥ ልዩ ልዩ የእንስሳት፣ የነፍሳት፣


የወፎች፣ በልብ የሚሳቡና አጥቢ የሆኑ እንስሳት ዝርያዎች ይገኛሉ፡፡ ከአጥቢ እንስሳት ዝርያዎች መካከል ጦጣ፣
ዝንጀሮ፣ የሌሊት ወፍ፣ ሽኮኮና የመሳሰሉት ይገኛሉ፡፡ በወንዞችና በዳርቻቸዉ የሚገኙ እንደ አዞ፣ አዉራሪስ፣
ነብር፣ አቦሸማኔና የመሳሰሉትን ያጠቃልላል፡፡ በአብዛኛዉ እንስሳቱ በዛፍ ላይ መኖር የሚችሉና ጥቅጥቅ ባለዉ
ደን መሽሎክለክ የሚችሉ ናቸዉ፡፡

2.4.3 በስርዓተ- ምኅዳር ስርጭት ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ደንቢዎች


በማንኛዉ የአለም ክፍል ሊፈጠር የሚችለዉን የስርዓተ -ምህዳር አይነት በመወሰን ረገድ ከፍተኛ ተጽእኖ
ያላቸዉ ሁለቱ ዋናዋና ህይወት አልባ ነገሮች ዝናብና ልከ ሙቀት ናቸዉ፡፡ ከፍታም በበኩሉ በሙቀትና ዝናብ
ስርጭት ላይ ተጽእኖ ያሳድራል፡፡

ዝናብና ልከ ሙቀት በእጽዋት ስርጭት ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩት እንዴት ነዉ?


ዝናብና ልከ ሙቀት በአንድ ስርዓተ- ምህዳር ዉስጥ ሊኖሩ የሚችሉ የእጽዋት አይነቶችን የሚወስኑ ዋና
ደንቢዎች ናቸዉ፡፡ የእጽዋት አይነት በተራዉ በስርዓተ-ምህዳር ዉስጥ በሚገኝ ማናቸዉም ነገር ላይ ተጽእኖ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ያሳድራል፡፡ ዝናብ በስርዓተ-ምህዳር ላይ ሊያደርስ የሚችለዉ የጉዳት መጠን በዝናቡ መጠን፣ አጣጣልና
ወቅታዊ የዝናብ ስርጭት ሁኔታ ይወሰናል፡፡

ልከ ሙቀት በስርዓተ-ምኅዳር ላይ ተጽእኖ የሚያሳድር ሌላዉ ዋና ደንቢ ነዉ፡፡ የልከ ሙቀት መጠን በተለያዩ
የአለም ክፍሎች መካከል የማይናቅ ልዩነት አለዉ፡፡ ለምሳሌ በገሞጂማ ክልል የሚገኙ አብዛኛዎቹ ቦታዎች
አመቱን ሙሉ የማይለዋወጥ ከፍተኛ ልከ ሙቀት ሲኖራቸዉ ዋልታዎች ደግሞ ረዥም ቀዝቃዛ የበረድ ወቅት
/long and cold winter/ እና አጭርና ቀዝቃዛ የሞቄ ወቅት/ short and cool summer / አላቸዉ፡፡ የሌሎች
አካባቢዎች የልከ ሙቀት መጠን ደግሞ በገሞጂማና በዋልታዎች የልከ ሙቀት መጠን መካከል ነዉ፡፡ ይህ የልከ
ሙቀት ልዩነት የስርዓተ-ምህዳር አካላት አይነት ከቦታ ቦታ የተለያዩ እንዲሆኑ አድርጓል፡፡

ከላይ እንደተገለጸዉ ልከ ሙቀትና ርጥበት በአንድ ስርዓተ-ምህዳር ዉስጥ ሊኖሩ የሚችሉ የእጽዋት አይነቶችን
በመወሰን ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ፡፡ ለምሳሌ አነስተኛ ርጥበትና ልከ ሙቀት ያላቸዉ አካባቢዎች የጮቄ
እጽዋት /Tundra vegetation/ አላቸዉ፡፡ ከፍተኛ መጠን ያለዉ ርጥበትና ቀዝቃዛ ልከ ሙቀት ያላቸዉ
አካባቢዎች የቅምብ ቀጥ ደኖች /coniferous forests/ መገኛ ናቸዉ፡፡ ደረቅና ሞቃታማ አካባቢዎች ደግሞ
የበረሀ እጽዋት አላቸዉ፡፡ መካከለኛ የዝናብ መጠን ወይም ወቅታዊ ዝናብ የሚያገኙ ቦታዎች በገሶ /savanna/
አጽዋት የተሸፈኑ ናቸዉ፡፡ ከፍተኛ የዝናብና ልከ ሙቀት መጠን ያላቸዉ አካባቢዎች ደግሞ ለገሞጂማ ዶፍ
ጫካ / Tropical rainforest / እጽዋት ተስማሚ ናቸዉ፡፡

ከፍታ በእጽዋትና በአየር ቅጥ ላይ ተጽእኖ የሚያሳድረዉ እንዴት ነዉ?


ከባህር ወለል በላይ ከፍታ ሲጨምር አማካይ የልከ ሙቀት መጠን ይቀንሳል፡፡ በዚም የተነሳ አንድሰዉ ከባህር
ወለል ተነስቶ ወደ ተራራ ጫፍ ሲጓዝ የተለያዩ የእጽዋት አይነቶች ያላቸዉን ተከታታይ ሰርዓተ-ምህዳሮችን
ያቋርጣል፡፡ ይህም ከምድር ወገብ ተሰተን ወደ ዋልታዎች ስንጓዝ ከሚያጋጥመን ሁኔታ ጋር ተመሳሳይ ነዉ፡፡

ከፍታ በጨመረ ቁጥር አየር ቅጥ ይቀዘቅዛል፡፡ ለምሳሌ ከኢትዮጵያ ዳርቻ ዝቅተኛ ቦታዎች ተነስተን ወደ
ሰሜን ምእራብና ደቡብ ምስራቅ ከፍተኛ ቦታዎች ስንጓዝ ከፍታ አየጨመረ የአየር ቅጥግን እየቀዘቀዘ
ይመጣል፡፡ በገሞጂማ ክልልም ቢሆን አንደ ክሊናማንጃሮ መሰል ትልልቅ ተራራዎች ጫፍ ላይ በረዶ ሊፈጠር
ይችላል፡፡ ስለዚህ የእጽዋት ስርጭት ከአየር ቅጥ ስርጭት ጋር ግንኙነት ስላለዉ ወደ ከፍተኛ ቦታዎች ስንጓዝ
በአየር ቅጥ ላይ የምናየዉ ለዉጥ በተመሳሳይ ሁኔታ በእጽዋት ስርጭትም ሊታይ ይችላል፡፡

ማጠቃለያ
 ስነ-መሬታዊ ጊዜ በአራት የጊዜ እርከን ደረጃዎች ይከፈላል፡፡ እነሱም ዘመን /Eon / ክፍለ ዘመን/
Era / ወቅትና/ period/ ክፍለ ወቅት /Epoch/ ናቸዉ፡፡
 በስነምድር ተመራማሪዎች ጥናት መሰረት የመሬት እድሜ ከ 4.5 - 4.6 ቢሊዮን አመት ይሆናል
ተብሎ ይታመናል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 የስነምድ ተመራማሪዎች የመሬትን የህይወት ታሪክ በአራት ክፍለ ዘመናት ከፍለዉታል፡፡ እነሱም
የዘመነ ቅድመ ህይወት፣ የዘመነ ጥንተ ህይወት የማእከላዊ ዘመን እና የሰብዓ ዘመን ናቸዉ፡፡
 በእያንዳንዱ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያ የተለያዩ ስነ-ምድራዊ ድርጊቶች ተከናዉነዋል፡፡
 አየርቅጥ ማለት በአንድ አካባቢ ለብዙጊዜ ተደጋግሞ የሚከሰት የአየር ጠባይ ነዉ፡፡ የአየር ጠባይ
ለረዥም ጊዜ ሲጠናቀር የአየር ቅጥ በመባል ይታወቃል፡፡
 ዋልድሚር ኩፐን የአለምን የአየርቅጥ በአምስት የአየርቅጥ አይነቶች/ክልሎች/ ከፍሎታል፡፡ እነሱም
ገሞጂማ አየር ቅጥ /A/፣ ደረቅ አየር ቅጥ /B /፣ ዉሀ አዘል ማእከላዊ ኬክሮስ አየር ቅጥ / C/፣ ዉሀ
አዘል በጣም ቀዝቃዛ ማእከላዊ ኬክሮስ አየር ቅጥ/ D/ እና ዋልቴ አየር ቅጥ /E /ናቸዉ፡፡
 በኢትዮጵያ የአየር ቅጥ እንዲለዋወጡ የሚያደርጉ ብዙ ተቆጣጣሪዎች አሉ፡፡ከነዚህ መካከል ኬክሮስ፣
ከፍታና የአየር ፀባይ ስርዓት በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳሉ፡፡
 በኢትዮጵያ ዝናብ ከቦታ ወደ ቦታና ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲለያይ ከሚያደርጉት ተቆጣጣሪዎች መካከል
ዋናዋናዎቹ ከፍታና የአየር ጠባይ ስርአት ናቸዉ፡፡
 በኢትዮጵያ በአመት አራት ወቅቶች አሉ፡፡ እነሱም ክረምት፣ ጸደይ፣ በጋና በልግ ናቸዉ፡፡
 የአየር ቅጥ ለዉጥ ስንል አማካይ የአየር ቅጥ ይዘቶች ማለትም የአየር ሙቀት፣የዝናብ መጠን፣ የአየር
እርጥበት፣ የነፋስ ፍጥነት፣ ወዘተ በቀጣይነት መጨመርን ወይም መቀነስን ማለት ነዉ፡፡
 የአየር ቅጥ ለዉጥ ሊያስከትሉ የሚችሉ ተፈጥሯዊ ደንቢዎች አህጉራዊ ሽርተታ፣ገሞራ፣ የዉቅያኖስ
ሞገድ፣ ወዘተ ሲሆኑ ሰዉ ሰራሽ ምክንያት ደግሞ በከባቢ አየር ዉስጥ የአፍላሽ ጋዞች ክምችት ነዉ፡፡
 የአየር ቅጥ ለዉጥ የሚያስከትላቸዉ ዋናዋና ክስተቶች የአለም አማካይ የሙቀት መጠን መጨመር፣
የበረሀማነት መስፋፋት፣ ድርቅ፣ የባህር ወለል ከፍ ማለት፣የገሞጅማ ሰቅ መገኛ መስፋት፣ የአለም
አቀፍ ነፋሶች አቅጣጫ መቀየር እና የብዙሀ ህይዎት መጥፋት ናቸዉ፡፡
 የመሬት የብሱ ክፍል በስድስት ዋናዋና የስርዓተ- ምዳር ክልሎች ይከፈላል ፡፡እነሱም በርሀ ፣ጮቄ
፣የሳርምድር ፣ቅጠል አርጋፊ ደን፣የታይጋ ደን አና ገሞጂማ ዶፍ ጫካ ናቸዉ፡፡

የክለሳ ጥያቄዎች

1.አራቱን የመሬት ህይወት ታሪክ ክፍለ ዘመናት ከሩቅ ወደ ቅርብ በቅደም ተከተል ዘርዝሩ፡፡2.በኢትዮጵያ
በሰብዓ ዘመን የተሰሩትን የደለሌ አለቶች ዘርዝሩ፡፡
3.ከኮፐን የአየር ቅጥ ክልሎች መካከል በኢትዮጵያ የሚገኙትን ዘርዝሩ፡፡
4. ኢትዮጵያ የከፍተኛ ቦታ አገር ባትሆን ኖሮ ምን አይነት የአየር ቅጥ ይኖራት ነበር?
5.የኢትዮጵያን አየር ቅጥ ዋናዋና ተቆጣጣሪዎች ዘርዝሩ፡፡
6. የአየር ቅጥ ለዉጥና የአየር ቅጥ ተለዋዋጭነትን ልዮነት አበራሩ፡፡
7.የአፍላሽ ጋዞች በአየር ቅጥ ላይ የሚያሳድሩትን ተጽእኖ አብራሩ፡፡
8. ኢትዮጵያን በክረምት ወቅት ዝናብ እንድታገኝ ያደረጋት ምክንያት ምንድን ነዉ?
9. ስርዓተ-ምህዳር ምን ማለት ነዉ?
10. የስርዓተ ምህዳር አካላትን መስተጋብር አብራሩ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ምዕራፍ ሦስት

የዓለም ሕዝብ፣የኢኮኖሚ ስርዓትና ልማት

መግቢያ
ውድ ሰልጣኞች በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የአለም ህዝብ ብዛትና እድገት ሁኔታ፣ በህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ
የሚያሳድሩ ነገሮች፣ የህዝብ ዝፈትና ውቅር፣ የኢትዮጵያ ህዝብና የስነህዝብ ፖሊሲ፣ የአለም ኢኮኖሚ ስርዓት
አይነቶች፣ የዘላቂ ልማትና እድገት መለኪያዎች እና የኢኮኖሚ ድርጅቶች የሚሉ ርዕሶች ተካተዋል።
በመሆኑም በዚህ ክፍለ ትምህርት ስለህዝብ ነክ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ትውውቅ ይደረጋል።

ዓላማ
ከዚህ ምዕራፍ መጠናቀቅ በሁላ ሰልጣኞች፦
 በህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮችን ታስረዳላችሁ።
 የስነህዝብ መረጃ ምንጮችን ትገልፃላችሁ።
 የኢትዮጵያ ሦስት ተከታታይ የቤትና ህዝብ ቆጠራ ውጤቶች ትተነትናላችሁ።
 የኢትዮጵያን ብሄራዊ ስነህዝብ ፖሊሲና ስልቶች ታስረዳላችሁ።
 የስነህዝብ ፖሊሲን ትርጉም ትገልፃላችሁ።
 የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ አይነቶችን ትለያላችሁ።
 የዘላቂ ልማት ፅንሰ ሀሳብ ምንነት ትገልፃላችሁ።

3.1 የዓለም ሕዝብ ብዛትና የእድገት ሁኔታ


ህዝብ ማለት በአንድ አካባቢ፣ አገር ወይም አለም ላይ የሚገኝ ሰብዓዊ ፍጡራን ስብስብ ማለት ነው። ህዝብ
የሰብዓዊ ፍጡራን ስብስብ በመሆኑ በውስጡ የተለያዩ ስነ ህይወታዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲሞግራፊያዊ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ወዘተ... ባህርያት ያላቸውን ቡድኖች ወይም ክፍሎች ያቅፋል። እነዚህ ቡድኖች ወይም ክፍሎች ደግሞ የዚያን
ህዝብ ጥንቅርና አጠቃላይ ባህርያት ይወስናሉ።
በተለያዩ ጊዜያት ስለአለም ህዝብ ብዛትና እድገት እንዲሁ ምስርጭት ጥናቶች ተካሂደዋል። ለምሳሌ የሰው
ልጅ በፍራፍሬ ለቀማና በእንስሳት አደን ይተዳደር በነበረበት ዘመን ከ 10,000 ዓ.ዓ በፊት የአለም ህዝብ ብዛት
4 ሚሊዮን እንደነበር ተገምቷል። ይህ አህዝ ከኢንዱስትሪ አብዮት በኋላ በፍትነት ማደግ ጀመረ።
ከኢንዱስትሪ አብዮት ዋዜማ (1750 ዎች) የአለም ህዝብ ብዛት 1 ቢሊዮን እንደደረሰና በየአመቱ በ 2.6
ሚሊዮን እድገት ያሳይ እንደነበር ከተለያዩ መረጃዎች ለመረዳት ተችሏል። በአሁኑ ዘመን የአለም ህዝብ ከ 7
ቢሊዮን በላይ እንደሆነ የተባበሩት መንግስታት ህዝብ ነክ መረጃ ይገልፃል። ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይ የአለም
ህዝብ ብዛት ከአውሮፓውያን የኢንዱስትሪ አብዮት በኋላ ከፍተኛ እድገት አሳይቷል።

 ተግባር 3.1

የዓለም ህዝብ ቁጥር በተለይ ከአውሮፓውያን የኢንዱስትሪ አብዮት ወዲህ በፍጥነት እየጨመረ
መጥቷል፡፡ ለዚህ ፈጣን የሕዝብ ቁጥር እድገት በምክንያትነት ሊጠቀሱ የሚችሉት ሁኔታዎች
ምንድን ናቸው?

የሚከተለው ሠንጠረዥ የአለም ህዝብ ቁጥር እድገት በምን አይነት ሁኔታ እየጨመረ እንደመጣ ያሳየናል፡፡

ሠንጠረዥ 3.1፡ የዓለም ሕዝብ ቁጥር እድገትና ዓመታዊ ጭማሪ (10000 ዓ.ዓ. -2100 ዓ.ም)
አመት (እ.ኤ.አ) የሕዝብ ብዛት አመታዊ ጭማሬ
በመቶኛ
10000 ዓ.ዓ 100,000-10,000,000 -
5000 5,000,000- 20,000,000 -
1 ዓ.ም 256,000,000 -
1300 400,000,000 -
1650 0.5 ቢሊዮን 0.1
1800 1.2 “ 0.5
1900 1.6 “ 0.6
1950 2.5 “ 1.10
1980 4.4 “ 1.7
2000 6.2 “ 1.4
2025 8.1 “ 0.8
2050 9.5 “ 0.4

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

2100 10.2 “ 0.1

የሰው ልጅ በዱር ፍራፍሬ ለቀማና በእንስሳት አደን በሚተዳደርበት በጥንት ዘመን የአለም የህዝብ ቁጥር እጅግ
በጣም ዝቅተኛ ነበር። ይሁን እንጂ የሰው ልጅ የግብርና ስራን ከጀመረና አንድ ቦታ ላይ በቋሚነት መስፈር
ከጀመረ በኋላ ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጣ። በመቀጠልም ከኢንዱስትሪው አብዮት መከሰት ጋር
ተያይዞ የአለም የህዝብ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ ሊመጣ ችሏል። በዚህ መሰረት በ 1650 ዓ.ም አካባቢ
የአለም ህዝብ ብዛት 0.5 ቢሊዮን እንደነበርና አመታዊ እድገቱም 0.1% ሲሆን በ 2025 ዓ.ም 8.1 ቢሊዮንና
አመታዊ እድገቱም 0.8% እንደሚደርስ ይገመታል።
በአለማችን ፈጣን የህዝብ እድገት የሚታየው በተለይ በታዳጊ አገሮች ሲሆን በበለፀጉት አገሮች ግን የህዝብ
ቁጥር ጭማሬው አነስተኛና አዝጋሚ እንደሆነ ከሚቀጥለው ሠንጠረዥ መረዳት ይቻላል፡፡

ሠንጠረዥ 3.2፡ የአለም ሕዝብ ቁጥር እድገት(በቢሊዮን) እና አመታዊ ጭማሬ (በመቶኛ) በበለፀጉና በታዳጊ
አገሮች (1980 – 2100 እ.ኤ.አ.)
ክልል 1980 2000 2050 2100
ዓለም 4.4 6.2 9.5 10.2
(1.7) (1.4) (0.36) (0.10)
የበለፀጉ አገሮች 1.1 1.3 1.4 1.4
(0.68) (0.04) (0.07 (0.02)
ታዳጊ አገሮች 3.3 4.8 8.1 8.8
(2.04) (1.64) (0.41) (0.11)
አፍሪካ 0.5 0.9 2.2 2.6
(3.0) (2.77) (0.84) (0.31)
ደ. አሜሪካ 0.4 0.6 1.1 1.2
(2.38) (1.92) (0.52) (0.20)
ሰ.አሜሪካ 0.25 0.3 0.4 0.4
(1.04) (0.62) (0.22) (0.06)
ምሥ. እስያ (1.2) 1.5 1.8 1.8
(0.89) (0.03) (-0.04)
ደ. እስያ (1.4) 2.1 3.2 3.3
(2.14) (1.53) (0.30) (0.01)
አውሮፓ 0.5 0.5 0.5 0.5
(0.3) (0.15) (- 0. 08) (0.00)
ኦሺንያ 0.02 0.03 0.04 0.04
(1.44) (0.92 (0.19) (0.07)
ሩሲያ 0.3 0.3 0.4 0.4
( 0.93) (0.60) (0.16) (0.00)
ማስታወሻ፡- በቅንፍ ውስጥ የሚታዩት አሃዞች የሚያመለክቱት አማካይ አመታዊ የህዝብ ቁጥር ጭማሬን
በመቶኛ ነው፡፡

 ተግባር 3.2

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

1. በታዳጊ አገሮች የህዝቡ ቁጥርና አመታዊ ጭማሬው ከፍተኛ ሊሆኑ የቻሉበትን ዋና ዋና ምክንያቶች
ዘርዝሩ፡፡
2. ፈጣን የሕዝብ ቁጥር ዕድገት የሚያሳድረውን ተፅእኖ በዝርዝር አብራሩ፡፡
3. ፈጣን የህዝብ ቁጥር እድገትን ለመግታት ምን መደረግ አለበት ትላላችሁ?
4. ከሚከተሉት ውስጥ በሀሳቡ የምትሰማሙበትን አንዱን በመምረጥ ደግፋችሁ ሌላኛውን በመቃወም
የመከራከሪያ ሀሳብ አቅርቡ፡-
ሀ) የህዝብ ቁጥር መጨመር ችግር ይፈጥራል፡፡
ለ) የህዝብ ቁጥር መጨመር ችግር አይፈጥርም (ጠቃሚ ነው) ፡፡

3.2 የዓለም ሕዝብ ሥርጭት፣ ውቅርና ዝፈት ሁኔታ

3.2.1 የአለም ህዝብ ስርጭት ሁኔታ

 ተግባር 3.3

የህዝብ ስርጭት ምንን ያመለክታል?

የአለም ህዝብ አሠፋፈር በሁሉም የአለም አካባቢዎች ተመሣሣይ አይደለም፡፡ ለምሣሌ፡- ከጠቅላላው የአለም
ህዝብ 2/3 የሚሆነው ሠፍሮ የሚገኘው 1/7 በሚሆነው የመሬት ክፍል ላይ ብቻ ነው፡፡በሌላ በኩል 90%
የሚሆነው የአለም ህዝብ በሰሜን ንፍቀ ክበብ፣ 10% ደግሞ በደቡባዊ ንፍቀ ክበብ ይገኛል፡፡ የአለም ህዝብ
ስርጭት በአህጉር ደረጃ ምን እንደሚመስል ደግሞ ከሚቀጥለው ሠንጠረዥ ማየት ይቻላል፡፡

ሠንጠረዥ 3.3 - የአለም ህዝብ ስርጭት በአህጉር ደረጃ (2000 እ.ኤ.አ.)

አህጉር የህዝብ ብዛት የህዝብ ጥግግት (በካሬ ኪ.ሜ)

አለም 6.2 ቢሊዮን 33


አውሮፓ 0.5 ቢሊዮን 98
እስያ 3.6 ቢሊዮን 95
ሰ.አሜሪካ 0.3 ቢሊዮን 16
ደ.አማሪካ 0.6 ቢሊዮን 14
አፍሪካ 0.9 ቢሊዮን 16
ኦሺንያ 0.03 ቢሊዮን 3

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሩሲያ 0.3 ቢሊዮን 12


አንታርክቲካ 0 0

 ተግባር 3.4

1. በህዝብ ብዛት ከፍተኛውን ቁጥር የያዙ 3 አህጉራትን በቅደም ተከተል አስቀምጡ፡፡


2. ዝቅተኛ የህዝብ ቁጥር የሚገኘው በየትኛው አህጉር ነው? ለምን ?
3. ምንም ህዝብ የማይኖርበት አህጉር የትኛው ነው? ለምን?

የአለም ህዝብ ስርጭት በኬክሮስ ሰረጃ ሲታይ የሚከተለው ገፅታ አለው፡፡


ኬክሮስ የህዝብ ብዛት በመቶኛ
00 – 200 ሰሜን < 10
200 - 400 ሰሜን 50
400 -600 ሰሜን 30
ከ 600 - በስተ ሰሜን 0.5
00 – 900 ደቡብ <10

 ተግባር 3.5

አብዛኛው የአለም ህዝብ በየትኛው ንፍቀ ክበብ ሠፍሮ ይገኛል ? በሁለቱ ንፍቀ ክበቦችና በተለያዩ
ኬክሮሶች መካከል የሚታየው የህዝብ ክምችት ልዩነት ከምን የመነጨ ይመስላችኃል?

ክልላዊ የአለም ህዝብ ስርጭት በሦስት ዋና ዋና ምድቦች ሊከፈል ይችላል ፡፡ እነዚህም ፡-


1. በጣም ከፍተኛ የህዝብ ክምችት የሚታዩባቸው ክልሎች- ደቡብ እስያ፣ ምስራቅ እስያ፣
አውሮፓ እና ሰሜናዊ ምስራቅ ሰሜን አሜሪካ
2. መካከለኛ የህዝብ ክምችት የሚታዩባቸው አካባቢዎች - ካሊፎርኒያ ፣ የብራዚል ጠረፋማ
አካባቢዎች፣ የናይል ሸለቆ፣ ምእራባዊ አፍሪካ ፣ ደቡባዊ ምስራቅ አውስትራሊያ ፣ እና
የምስራቅ አፍሪካ ወይም በአጠቃላይ የትሮፒካል ከፍተኛ ቦታዎች እና
3. እጅግ አነስተኛ የህዝብ ክምችት የሚታይባቸው አካባቢዎች -ዋልታዎች አካባቢ፣ ሙቅ
በረሀዎች፣ ቀዝቃዛ በረሃዎች፣ የትሮፒካል ጥቅጥቅ ደኖች ፣ በጣም ከፍተኛ ቦታዎች
ወዘተ.ናቸው፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

3.2.2 በህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች

 ተግባር 3.6

በህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች ምን ምን ናቸው?

በህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ የሚያትሉ በርካታ ነገሮች አሉ። እነዚህ ነገሮች በሶስት ዋና ዋና ምድቦች
ይከፈላሉ። እነዚህም፦
1. ተፈጥሮዓዊ ነገሮች
2. ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች
3. ታሪካዊ ጉዳዮች ናቸው።
1. ተፈጥሮዓዊ ነገሮች
በህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ዋና ዋና ተፈጥሮዓዊ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው።
 የቦታው ለትራንስፖርትና መገናኛ ያለው ቅርበት
 የመልክዓምድር ሁኔታ
 የአየር ንብረት
 የውሃ አቅርቦት
 የማዕድናት ክምችት
 የአፈር ሁኔታ
 የእፅዋት ሽፋን ናቸው።

 ተግባር 3.7

ከላይ የተዘረዘሩት ዋና ዋና ተፈጥሮዓዊ ነገሮች እንዴት የህዝብን ስርጭት እንደሚቆጣጠሩ


በዝርዝር አስረዱ።

2. ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች


በህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ዋና ዋና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው።
 የሰፈራ ቆይታ ጊዜ
 የኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አይነት
 የቴክኖሎጅ የእድገት ሁኔታ
 ፖለቲካዊ ጉዳዮች ናቸው።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 ተግባር 3.8

ከላይ የተዘረዘሩት ዋና ዋና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እንዴት የህዝብን ስርጭት


እንደሚቆጣጠሩ በዝርዝር አስረዱ።

3.ታሪካዊ ጉዳዮች
የአለም ህዝብ ስርጭት የቅርብ ጊዜ ምክንያቶች ውጤት ብቻ ሳይሆን የጥንታዊ ታሪኮች ምክንያት ውጤት
ጭምር ነው። ለምሳሌ፦ የአፍሪካ ህዝብ ስርጭት በ 19 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የአውሮፓዊያን ቅኝ ገዥዎች
በማዕድን፣ በወደብና በአስተዳደር ከተሞች አካባቢ የነበራቸውን ትኩረት የሚያንፀባርቅ ነው። እንዲሁም
ጦርነት፣ የባሪያ ንግድ፣ ጥንታዊ የንግድ መስመሮች ወዘተ በአለም ህዝብ ስርጭት ላይ ተፅዕኖ የነበራቸ ታሪካዊ
ምክንያቶች ናቸው።

3.2.3 የህዝብ ዝፈት (Population Density)


የህዝብ ስርጭትን ለመለካት የምንጠቀምበት ዋናው መንገድ የህዝብ ዝፈት (population density) ይባላል።
የህዝብ ዝፈት ማለት በአንድ ካሬ ኪሎ ሜትር የሰፈረው የህዝብ ብዛት ማለት ነው። የጂኦግራፊ ባለሙያዎች
የተለያዩ የህዝብ ዝፈት አይነቶች እንዳሉ ይገልፃሉ። ከነዚህ መካከል ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው።
ሀ. ግርድፍ ዝፈት (Crude density)
ለ. የግብርና ዝፈት (Agricultural density)
ሐ. ፊዚዮሎጂካል ዝፈት (Physiological density)

ሀ. ግርድፍ የህዝብ ዝፈት(Crude population density)


ግርድፍ የህዝብ ዝፈት በአንድ በተወሰነ ቦታ ላይ በሚኖረው ጠቅላላ ህዝብና ጠቅላላ የቆዳ ስፋት መካከል
ያለውን ንፅፅር የሚያሳይ የህዝብ ስርጭት መለኪያ ነው። ግርድፍ የህዝብ ዝፈት በሚከተለው ሂሳባዊ ቀመር
ይገለፃል።

ግርድፍ የህዝብ ዝፈት = ጠቅላላ የህዝብ ብዛት


ጠቅላላ የቆዳ ስፋት
ለምሳሌ “ከዊኪፒድያ ፍሪ እንሳይክሎፒድያ” በተገኘው መረጃ መሰረት የኢትዮጵያ ጠቅላላ የቆዳ ስፋት
1,104,300 ካሬ ኪሎ ሜትር ሲሆን ጠቅላላ የህዝብ ብዛቷ ደግሞ 87,952,991 ነው። ስለዚህ የአገሪቷ ግርድፍ
የህዝብ ዝፈት እንደሚከተለው ይሰላል።

ግርድፍ የህዝብ ዝፈት = ጠቅላላ የህዝብ ብዛት = 87,952,991 = 80/ካሬ ኪ.ሜ


ጠቅላላ የቆዳ ስፋት 1,104,300 ካሬ ኪ.ሜ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ይህ ማለት በአገራችን ኢትዮጵያ በአማካኝ 80 ሰዎች በአንድ ካሬ ኪሎ ሜትር ቦታ ላይ ሰፍረው ይኖራሉ


ማለት ነው።

ለ. የግብርና ዝፈት (Agricultural density)


አንድ በተወሰነ የገጠር አካባቢ በሚኖረው የህዝብ ብዛትና ለእርሻ አገልግሎት በሚውለው መሬት መካከል
ያለው ንፅፅር የግብርና ዝፈት ይባላል። ግብርና ዝፈት በሚከተለው ሂሳባዊ ቀመር ይገለፃል።
ግብርና ዝፈት = በገጠር አካባቢ የሚኖረው ህዝብ ብዛት
ለእርሻ አገልግሎት የሚውለው የመሬት መጠን
ምሳሌ በአንድ አገር ውስጥ በገጠር የሚኖረው ህዝብ ብዛት 74,760,042 ቢሆን እና ለእርሻ የሚውለው መሬት
717795 ካሬ ኪሎ ሜትር ቢሆን የግብርና ዝፈት ስንት ይሆናል?

ግብርና ዝፈት = 74760042 =104/ካሬ ኪሎ ሜትር


717795 ካሬ ኪሎ ሜትር

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ይህ የሚያስረዳው 104 የገጠር ነዋሪዎች በአማካኝ 1 ካሬ ኪሎ ሜትር የእርሻ መሬት እንደሚጠቀሙ ነው።

ሐ. ፊዚዮሎጂካል ዝፈት (Physiological density)


ፊዚዮሎጂካል ዝፈት (Physiological density) በጠቅላላው ህዝብ ቁጥርና ለእርሻ ተስማሚ (ምቹ) የሆኑ
ቦታዎች የቆዳ ስፋት ላይ የተመሰረተ መለኪያ ነው። ለስሌት የምንጠቀመው ቀመርም እንደሚከተለው
ይሆናል።
ፊዚዮሎጂካል ዝፈት = የጠቅላላው ህዝብ ቁጥር
ለእርሻ ተስማሚ (ምቹ) የሆኑ ቦታዎች የቆዳ ስፋት
ለምሳሌ በኢትዮጵያ ለእርሻ ተስማሚ (ምቹ) የሆነው ቦታ የቆዳ ስፋት 960,500 ካሬ ኪሎ ሜትር ነው ብንል
እና በተራ ቁጥር የተገለፀውን ጠቅላላ የህዝብ ብዛት ብንወስድ ፊዚዮሎጂካል ዝፈት እንደሚከተለው ይሰላል።
ፊዚዮሎጂካል ዝፈት = 87,952,991 = 9/ካሬ ኪሎ ሜትር
960,500 ካሬ ኪሎ ሜትር

ይህ ማለት ለእያንዳንዱ 9 ሰዎች 1 ካሬ ኪሎ ሜትር ለእርሻ ምቹ የሆነ ቦታ ይደርሳቸዋል ማለት ነው።

3.2.4 የህዝብ ውቅር (Population Structure)

የአንድን ህዝብ የእድሜና የፆታ ስብጥር (ውቅር) የምንተነትንበት ሥእላዊ መግለጫ የህዝብ ፒራሚድ በመባል
ይታወቃል፡፡ የህዝብ ፒራሚድ የአንድ አካባቢን ህዝብ የእድሜና የፆታ ስብጥር ከማሳየቱም በላይ በህዝቡ
ውስጥ ያለውን የውልደትና የሞት ሁኔታ፤ እንዲሁም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ አመልካች ነው፡፡ የተለያየ
ዲሞግራፊያዊ(ህዝበ ነክ) ባህርያት (የውልደት፣ የሞት የእድሜ ወዘተ. ሁኔታዎች) ያላቸው ህዝቦች የተለያየ
የፒራሚድ ቅርፆች ይኖሯቸዋል፡፡ ለምሣሌ፡- የታዳጊ አገሮችንና የበለፀጉ አገሮችን ህዝቦች ዲሞግራፊያዊ ገፅታ
የሚወክሉ ፒራሚዶች በቅርፅ የተለያዩ ናቸው፡፡

 ተግባር 3.9

1. የታዳጊና የበለፀጉ አገሮች ህዝቦችን መዋቅሮች የሚወክሉ ሁለት ናሙና ፒራሚዶችን ከተለያዩ
የፅሁፍ መረጃዎችና መፃህፍት ላይ ካሰባሰባችሁ በኋላ በፒራሚዶች መካከል ያለውን የቅርፅ ልዩነት፣
የቅርፅ ልዩነቱን መንሥኤና እያንዳንዱ ፒራሚድ የሚያስተላልፈውን መልእክት ወይም
የሚወክላቸውን ህዝበ ነክ ባህርያት በገለፃ አቅርቡ፡፡
2. በሁለቱ ፒራሚዶች መካከል ያለውን ልዩነት፡-
ሀ) ከውልደት

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ለ) ከሞት
ሐ) ከእድሜ ስብጥር
መ) ከህዝብ ቁጥር እድገት እና
ሠ) ከማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ሁኔታዎች አንፃር አብራሩ፡፡

3.3 የኢትዮጵያ ህዝብና የስነ ህዝብ ፖሊሲ

3.3.1 የስነ ህዝብ መረጃ ምንጮች


የስነህዝብ መረጃ ፖሊሲዎችን፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቅዶችን ለመንደፍ መሰረታዊ ጠቀሜታ አለው።
የስነ ህዝብ መረጃ አሰባሰብ የአንድ አገር ከሌላው ስለሚለይ በአገሮች መካከል ያለውን የስነ ህዝብ መረጃ
ማወዳደር አስቸጋሪ ነው። ወጥነት ያለው የስነ ህዝብ መረጃ እንዲኖር የተባበሩት መንገስታት ድርጅት
የስነህዝብ ኮሚሽን ሁሉም አገሮች በስነ ህዝብ ቆጠራ ጊዜ ማካተት የሚገባቸውን የህዝብ ነክ ባህሪያት ከዚህ
በታች የተዘረዘሩት መሆን እንዳለባቸው አስተያየት ሰጥቷል።
 በአንድ አገር ውስጥ የሚገኝ አጠቃላይ የህዝብ ብዛትና ስርጭት
 ዕድሜ፣ፆታና የጋብቻ ሁኔታ
 የትውልድ ቦታና ዜግነት
 የአፍ መፍቻ ቋንቋና የትምህርት ደረጃ
 የስራ አይነት
 መኖርያ ቦታ
 የቤተሰብ ብዛትና ውቅር ናቸው።
ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይ የስነህዝብ መረጃ አሰባሰብ ዘዴዎች በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች ይመደባሉ። እነሱም
ሀ. ሙሉ ቆጠራ (Census)
ለ. የናሙና ቆጠራ (Sampling method)
ሐ. የአብይ ምዝገባ (Vital registration)
ሀ. ሙሉ ቆጠራ (Census)
ሙሉ ቆጠራ የህዝብና ቤት ቆጠራ ይባላል። የህዝብና ቤት ቆጠራ ማለት በአንድ አገር ወይም ቦታ ከሚኖረው
ህዝብ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የህዝብ ነክ ባህሪያ መረጃዎች የማሰባሰብ፣ የማደራጀት፣ የመተንተንና
የማተም ሂደት ማለት ነው። የህዝብና ቤት ቆጠራ በስፋት የሚታወቅ የህዝብ ነክ መረጃዎች ማሰባሰቢያ ዘዴ
ነው። ሙሉ ቆጠራ ስለ አንድ አገር ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ የውልደትና የሞት መጠን፣ ከገጠር ወደ ከተማ ወይም
ከከተማ ወደ ገጠር የሚታይን ፍልሰት፣ የቤተሰብን የኑሮ ሁኔታ፣ የቤተሰብ ብዛትና የትምህርት ሁኔታ
በተመለከተ ሰፊና ጥልቀት ያለው መረጃ የሚሰበሰብበት የስነ ህዝብ መረጃ ምንጭ ነው።

የህዝብና ቤት ቆጠራ የሚከተሉት መለያ ባህሪያት አሉት።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 ግለሰባዊ ቆጠራ መሆኑ (Universality))፦ በቆጠራ ጊዜ መረጃ የሚሰበሰበው ከእያንዳንዱ ግለሰብ


ራሱን ችሎ ነው።
 አገር አቀፋዊ መሆኑ (Defined territory)፦ በቆጠራ ጊዜ በአንድ አገር ውስጥ የሚኖረውን ሁሉን
የህብረተሰብ ክፍል ያካትታል።
 ወቅቱን የጠበቀ መሆኑ (Periodicity)፦ ለምሳሌ በአገራችን ኢትዮጵያ ሁልጊዜም በየአስር አመቱ
የህዝብና ቤት ቆጠራ ሲካሄድ በሌሎች አገሮች ግን እንደየ አገሩ ተጨባጭ ሁኔታ ሊለያይ ይችላል።
 በመንግስት በጀት የሚሸፈን መሆኑ (Government sponsorship)፦ የቆጠራ እቅድ፣ በጀትና
አጠቃላይ ሂደት የሚመራው በመንግስት ሀላፊነት ነው።
ለ. የናሙና ቆጠራ (Sampling method)
የናሙና ቆጠራ ከስነ ህዝብ መረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴዎች አንዱ ነው። ሙሉ ቆጠራ በአገር አቀፍ ደረጃ በአምስት
ወይም በአስር ዓመት አንድ ጊዜ ስለሚካሄድ በሁለት ተከታታይ ሙሉ ቆጠራ ጊዜያት መካከል የስነ ህዝብ
መረጃ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የናሙና ቆጠራ (Sampling method) ይካሄዳል። የናሙና ቆጠራ ማለት ከተወሰኑ
የህብረተሰብ ክፍሎች ብቻ መረጃ የሚሰበሰብበት ዘዴ ማለት ነው። የናሙና ቆጠራ ሁለት አይነት አላማዎች
አሉት። እነሱም፦
1. የአንድን አገር ወይም ክልል ጠቅላላ የህዝብ ብዛት ለመገመት
2. የውልደት፣ የሞትና የፍልሰት መጠንን ለመገመት ናቸው።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የናሙና ቆጠራ የሚከተሉት ጠቀሜታዎች አሉት


1. ብዙ ወጭ አይጠይቅም
2. ብዙ የሰለጠነ የሰው ሀይል አይፈልግም
3. በሙሉ ቆጠራ የተገኘውን መረጃ ክፍተት ለማረጋገጥ ይረዳል።
ሐ. የአብይ ምዝገባ (Vital registration)
አብይ ምዝገባ ማለት የስነህዝብ ክስተቶች ማለትም (ውልደት፣ ሞት፣ ጋብቻ፣ ፍችና ፍልሰት) ሲከሰቱ
ወዲያውኑ ተከታትሎ የመመዝገብ ዘዴ ነው። ለምሳሌ ውልደትን በተመለከተ የሚመዘገቡ መረጃዎች ፆታ፣
የትውልድ ቀን፣ ቦታ፣ የእናትየዋ እድሜና ከአሁን በፊት የወለደቻቸው ልጆች ብዛት ይመዘገባሉ። ሞትን
በተመለከተ ፆታ፣ የሞት መንስኤ፣ ጊዜና ቦታን የተመለከቱ መረጃዎች ይሰበሰባሉ።

3.3.2 የኢትዮጵያ ህዝብ የእድገት ሁኔታ


ከሚከተለው ሰንጠረዥ የኢትዮጵያን ህዝብ ብዛት በሶስት ተከታታይ የህዝብና ቤት ቆጠራ የታየውን ጭማሪ
ከፆታ ስርጭት መመልከት ይቻላል።
ሰንጠረዥ 4; የኢትዮጵያ ህዝብ በሶስት ተከታታይ የቤትና ህዝብ ቆጠራ እና በፆታ ስርጭት
የቤና ህዝብ ቆጠራ ፆታ የህዝብ መጠን
ዓ.ም
በቁጥር በፐርሰንት
1984 ወንድ 20,062,490 50.3
ሴት 19,806,082 49.7
ድምር 39,868,572 100
ወንድ 26,910,698 50.3
1994 ሴት 26,566,567 49.7
ድምር 53,477,265 100
ወንድ 37,296,657 50.5
2007 ሴት 36,621,848 49.5
ድምር 73,918,505 100
ምንጭ: የ 2007 እ.ኤ.አ የቤትና ህዝብ ቆጠራ የመረጃ ማጠቃለያ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

በ 1984 እ.ኤ.አ በተካሄደው የመጀመሪያ ቤትና ህዝብ ቆጠራ የኢትዮጵያ ህዝብ ጠቅላላ ብዛት 39.8 ሚሊዮን
ነው። በሁለተኛው (1994 እ.ኤ.አ) ቆጠራ ወደ 53.4 ሚሊዮን የጨመረ ሲሆን በሦስተኛው ቆጠራ (2007
እ.ኤ.አ) ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት ወደ 73.9 ሚሊዮን አሻቅቧል። የኢትዮጵያ ህዝብ እ.ኤ.አ በ 2010 እና
በ 2025 94 ሚሊዮን እና 132 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል።

3.3.3 የኢትዮጵያ ብሄራዊ የስነ ህዝብ ፖሊሲ

ትርጓሜ
የስነህዝብ ፖሊሲ ማለት የአንድ ህዝብ አብይ ዲሞግራፊያዊ ባህርያት (ማለትም የውልደት፣ የሞትና ፣
የፍልሠት ሁኔታዎች) ለአካባቢያዊ ፣ ኤኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ወዘተ. እድገቶች አዎንታዊ
አስተዋፅኦ ሊያበረክቱ የሚችሉበትን መልክ እና አቅጣጫ እንዲይዙ ለማድረግ አንድ መንግስት የሚወስደው
ማንኛውም ህጋዊ እርምጃ ወይም የሚቀይሰው አስተዳደራዊ መርሃ ግብር ነው ማለት ይቻላል፡፡

በኢትዮጵያ ፈጣን የህዝብ ቁጥር እድገትን ለመግታት ይቻል ዘንድ የስነ ህዝብ ፖሊሲ ተቀርፆ የተለያዩ
እስትራተጅዎች ተነድፈዋል። የዚህ ፖሊሲ ዋነኛ አላማም የአገሪቱ ፈጣን የህዝብ ቁጥር ጭማሬ ከምጣኔ
ሀብታዊ እድገቱና ከተፈጥሮ ሃብቱ የመሸከም አቅም ጋር ማመጣጠን ነው። ፖሊሲውን ተግባራዊ ለማድረግ
የተቀየሱ እስትራተጂዎችም የሚከተሉት ናቸው።
 በህዝብ ቁጥርና በምርታማነት መካከል ያለውን ክፍተት ማጥበብ
 ከገጠር ወደ ከተሞች የሚደረገውን ፍልሰት መቀነስ
 የአካባቢ እንክብካቤን በማሳደግ የተፈጥር አካባቢን የመሸከም አቅም ማሳደግ
 የሴቶችን ማህበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ አቅም ማጎልበት
 የውልደት መጠንን መቀነስ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 የእናቶችና የህፃናትን ሞት መቀነስ


 የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎ ማሳደግ
 የተመጣጠነ የህዝብ ስርጭትና አሰፋፈር መፍጠር
 የተለያዩ የስራ እድሎችን መፍጠርና ማስፋፋት
 የስነህዝብ ትምህርትንና መረጃ ልውውጥን ማስፋፋት፤ ወዘተ ናቸው።

3.4 የአለም ኢኮኖሚ ስርዓት አይነቶች(Types of World Economic Systems)

3.4.1 የኢኮኖሚ ስርዓቶች (Economic Systems)


አገሮች ያለባቸውን የምጣኔ ሀብት እድገት ችግር ለመፍታት፣ የተፈጥሮ ሀብቶችን አጠቃቀም ሁኔታ
ለመወሰንና በአጠቃላይ የምጣኔ ሀብቶቻቸውን እድገትና ሂደት ለመምራት የሚከተሏቸው የተለያዩ
የኢኮኖሚ ሥርዓት አይነቶች አሉ፡፡ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ በአለማችን ያሉ የኢኮኖሚ ስርዓቶች በሶስት
ይከፈላሉ። ይህም ክፍፍል የሚከተሉት ሦስት ጥያቄዎች መሰረት ያደረገ ነው። እነርሱም፦
 ምን አይነት ምርት ማምረት?
 እንዴት ማምረት? እና
 ለማን ማምረት? የሚሉትን ጥያቄዎች የሚመልስ ነው።
የኢኮኖሚ ስርዓቶች እነዚህን ሦስት መሰረታዊ ጥያቄዎች የሚመልሱበት መንገድ የተለያየ ነው።

 ተግባር 3.10

1. ሦስቱ የኢኮኖሚ ሥርዓት አይነቶች እንማን ናቸው?


2. እያንዳንዱን የኢኮኖሚ ሥርዓት በተናጠል በመውሰድ ምን አይነትባህሪ እንዳለው አብራሩ፡፡
3. እያንዳንዱ የኢኮኖሚ ሥርዓት ከሌላው እንዴት እንደሚለይ የተለያዩ የማነፃፀሪያ ነጥቦችን (ለምሳሌ
ከመንግስት ሚና ወዘተ. አኳያ ) በመውሰድ አነፃፅሩ፡፡
4. በኢትዮጵያ ውስጥ ካለፉት ሃምሣ ዓመታት ወዲህ የተከሰቱትን የኢኮኖሚ ስርዓቶች በማብራሪያ
በማስደገፍ ዘርዝሩ፡፡

3.4.2 የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴ አይነቶች (Categories of Economic Activities)

የሠው ልጅ ከጥንት ጀምሮ ለመኖር የሚያስፈልጉትን መሠረታዊና ሁለተኛ ደረጃ ፍላጎቶች ለማሟላት
በተለያዩ ምጣኔ ሃብታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተሰማርቶ ይገኛል፡፡ የሠው ልጅ የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴዎች

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

አይነቶችና የእድገት ደረጃቸውም በቦታና ጊዜ እንደሚለያዩ እንገነዘባለን፡፡ በመሆኑም የምርት ሂደቶቹና


ተግባራቱ ካላቸው ባህርያት አንፃር በሦስት ዋና ዋና ፈርጆች እንመድባቸዋለን፡፡

 ተግባር 3.11

1. መሠረታዊ ፍላጎቶችና ሁለተኛ ደረጃ ፍላጎቶች (human needs & Human Wants ) የሚባሉት
ምንድን ናቸው ? ልዩነታቸውን አብራሩ፡፡
2. የሰው ልጅ ፍላጎቶች በምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትና ሥልጣኔ ምክንያት ሊለዋወጡ እንደሚችሉ
ይታመናል ፡፡ ሆኖም ከሁለተኛ ደረጃ ፍላጎት ይልቅ መሠረታዊ ፍላጎቶች በዘመን ልዩነትም ሆነ
በኢኮኖሚ ዕድገት ብዙም ለውጥ አያሣዩም፡፡ ከላይ የተገለፀው አባባል ምን ማለት እንደሆነ
አብራሩ፡፡
3. ሦስቱ ዋና ዋና የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴዎች አይነቶች እነማን ናቸው?
4. የእያንዳንዱ የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴ ባህርይ ምንድን ነው ? በእያንዳንዱ የምጣኔ ሃብት
እንቅስቃሴ ውስጥ ሊመደቡ የሚችሉ ክፍላተ ኢኮኖሚዎችን ዘርዝሩ፡፡
5. በጥንት ሠዎችና በአሁኑ ወቅት ደግሞ በጣም ኋላ ቀር በሆኑ አካባቢዎች መሠረታዊ ፍላጎቶችን
ለማሟላት የሚከናወኑ ምጣኔ ሀብታዊ ተግባራት ምንድን ናቸው? የጠቀሳችኋቸው ተግባራት
በየትኛው የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴ ውስጥ ይመድባሉ?

3.4.3 የዘላቂ ልማትና እድገት ምንነት

ልማት የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሙት የምጣኔ ሀብት ምሁራን እና ፖለቲከኞች በ 20 ኛው ክፍለ
ዘመን ነው። ይሁን እንጅ መቸ፣ እንዴትና በማን የሚለው በውል አይታወቅም። ነገር ግን የልማት ፅንሰ ሀሳብ በአብዛኛው
ከካፒታሊዝም ስርዓት ማቆጥቆጥ ጋር ተያይዞ እናገኘዋለን።

 ተግባር 3.12

ልማት ማለት ምን ማለት ነው?

ልማት በጣም ሰፊ ፅንሰ ሃሳብ ነው። ልማት ሰፊ ፅንሰ ሃሳብ በመሆኑ የሰው ልጆች የእውቀት፣ ቁሳዊ፣ እና መንፈሳዊ ፍላጎቶች
መሟላት (Sustenance) ጋር ይዛመዳል። ልማት የፖለቲካ ልማት (Political Development)፣ የማህበራዊ ልማት
(Social Development)፣ እና የኢኮኖሚ ልማት (Economic Development) ተብሎ በየፈርጁ ይታያል። ነገር ግን
በዚህ ንዑስ ርዕስ ልማትን ከኢኮኖሚ ገፅታ አንፃር ለማየት ይሞከራል። ልማትና የኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ ትስስር/ግንኙነት

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

አላቸው። የኢኮኖሚ እድገት ማለት አንድ አገር በአንድ አመት ያመረተችው አጠቃላይ የሀብት መጠን ሆኖ የግብርና፣ የጥሬ
እቃ፣ የኢዱስትሪ ምርቶችን እና የአገልግሎት አሰጣጥን ያካተተ ነው።

በአንድ አገር ውስጥ የዜጎች ቁሳዊና መንፈሳዊ ፍላጎት ተሟልቶ ሲገኝ ልማት(Development) እንዳለ ይነገራል። ይህ ማለት
በቂ መጠለያ፣ ልብስ፣ የተመጣጠነ ምግብ፣ ትራንስፖርትና መገናኛ፣ የጤናና የትምህርት ተቋማት፣ ንፁህ የመጠጥ ውሃ፣
መብራት፣ ስልክ፣ ፖስታ፣ የነፍስ ወከፍ መጨመር፣ የተሻለ የኑሮ ደረጃ፣ ወዘተ እና አጠቃላይ የዜጎች መንፈሳዊ ፍላጎት
መሟላት የአንድን አገር ልማት ሊመሰክሩ የሚችሉ ጉዳዮች ናቸው።

ዘላቂ ልማት (Sustainable Development) ማለት ቀጣይነት ያለው ተከታታይ የሆነ እድገት ማለት ነው። ዘላቂ ልማት
የአሁኑን ትውልድና የመጭውን ትውልድ ፍላጎት መሟላትን ታሳቢ የሚያደርግ ፅንሰ ሀሳብ ነው። አሁን ያለው ትውልድ
የመጭውን ትውልድ ፍላጎት መሟላት በማይጎዳ ወይም በማያዛባ ሁኔታ ፍላጎቱንና የሚያስፈልጉትን ነገሮች ማሟላት ሲችልና
ቀጣይነት ያለው እድገት ሲያስመዘግብ ዘላቂ ልማት ይባላል።

3.4.4 የዘላቂ ልማትና እድገት አመላካቾች

በአንድ አገር ዘላቂ ልማትና እድገት መኖር ወይም አለመኖር ከላይ በተገለፁት ጉዳዮች ማለትም በቂ መጠለያ፣
ልብስ፣ የተመጣጠነ ምግብ፣ ትራንስፖርትና መገናኛ፣ የጤናና የትምህርት ተቋማት፣ ንፁህ የመጠጥ ውሃ፣ መብራት፣ ስልክ፣
ፖስታ፣ የነፍስ ወከፍ ገቢ መጨመር እና ከአጠቃላይ የዜጎች የኑሮ ደረጃ እና መንፈሳዊ ፍላጎት መሟላት አንፃር መግለፅ
የሚቻል ቢሆንም በሚከተሉት ሦስት ተያያዥ የእድገት ሁኔታች ይገለፃል። እነሱም፦
1. የኢኮኖሚ እድገት ፦ በሸቀጦች ምርትና አገልግሎት አሰጣጥ ተከታታይ የሆነ እድገት በማስመዝገብ የመንግስትን
ስራ በአግባቡ በመምርት የውጭ ብድርን መቆጣጠር ሲችልና በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም በግብርና እና
በኢንዱስትሪ መካከል የተመጣጠነ እድገት ሲኖር ነው።
2. አካባቢያዊ እድገት፦ እድገቱ በአካባቢ ልማት ላይ ጉዳት የማያስከትልና የአካባቢውን የሃብት ምንጮች በአግባቡ
የሚጠቀም፤ አካባቢን ከብክነትና ከጥፋት የሚጠብቅ ማለትም የብዙሃ ህይወትን፤ የአካባቢ አየርን እና የስነ
ምህዳሩን ደህንነት መጠበቅ የሚችል ልማት ሲኖር ነው።
3. ማህበራዊ እድገት፦ እድገቱ ፍትሀዊ ስርጭት ሲኖረው፣ በቂ ማህበራዊ አገልግሎቶችን ምሳሌ ጤና፣ ትምህርት፣
መንገድ፣ እና የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ሲያቀርብ፤ የፆታ እኩልነትን፣ የፖለቲካ ተሳትፎንና ተጠያቂነትን በዘላቂነት
ማዳበር የሚችል ልማት ነው።

3.5 የኢኮኖሚ ድርጅቶች


የአለም ኢኮኖሚ ከቅርብ አመታት ወዲህ በከፍተኛ ሁኔታ ለውጥ እንዳሳየ የመስኩ ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ለለውጡ ዋና ምክንያት ደግሞ በአለም ላይ የተለያዩ የኢኮኖሚ ድርጅቶች መቋቋም ነው። የኢኮኖሚ
ድርጅቶች በምርት አመራረትና አገልግሎት አሰጣጥ፤ በግለሰቦችም ሆነ በአለምአቀፍ ማህበረሰብ የንግድ
ልውውጥ ሂደት ላይ ተፅዕኖ ስለሚያሳድሩ ነገሮች ውይይቶችን፣ ትብብሮችን እና የመፍትሄ ሀሳቦችን
የሚያቀርቡ ተቋማት ናቸው። የኢኮኖሚ ድርጅቶች አለምአቀፋዊ ወይም አህጉራዊ ይዘት ሊኖራቸው
ይችላል።

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

አለምአቀፋዊ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ከሚባሉት መካከል ለምሳሌ ያህል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል።
 የአለም ባንክ (World Bank)
 አለምአቀፍ የገንዘብ ድርጅት (International Monetary Fund)
 አለምአቀፍ የሰራተኞች ድርጅት (International Labour Organization)
 አለምአቀፍ የንግድ ድርጅት (International Trade Organization) እና ሌሎችም
አህጉራዊ ከሚባሉት የኢኮኖሚ ድርጅቶች ደግሞ የሚከተሉት ይጠቀሳሉ
 የአውሮፓ ህብረት (European Union)
 የሰሜን አሜሪካ ነፃ የንግድ ስምምነት (North American Free Trade Agreement) ወዘተ ናቸው።

 ተግባር 3.13

1. በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ የኢኮኖሚ ድርጅቶችን በመጥቀስ ተግባራቸውን አስረዱ።


2. ከላይ የተጠቀሱትን አለምአቀፋዊ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ዋና ዋና ተግባሮች ግለፁ።

ማጠቃለያ
ከኢንዱስትሪ አብዮት ዋዜማ (1750 ዎች) የአለም ህዝብ ብዛት 1 ቢሊዮን እንደደረሰና በየአመቱ በ 2.6
ሚሊዮን እድገት ያሳይ እንደነበር ከተለያዩ መረጃዎች ለመረዳት ተችሏል። በአሁኑ ዘመን የአለም ህዝብ ከ 7
ቢሊዮን በላይ እንደሆነ የተባበሩት መንግስታት ህዝብ ነክ መረጃ ይገልፃል። በአለማችን ፈጣን የህዝብ እድገት
የሚታየው በተለይ በታዳጊ አገሮች ሲሆን በበለፀጉት አገሮች ግን የህዝብ ቁጥር ጭማሬው አነስተኛና አዝጋሚ
ነው። የአለም ህዝብ አሠፋፈር በሁሉም የአለም አካባቢዎች ተመሣሣይ አይደለም፡፡ በህዝብ ስርጭት ላይ
ተፅዕኖ የሚያሳድሩ በርካታ ነገሮች አሉ። እነዚህ ነገሮች በሶስት ዋና ዋና ምድቦች ይከፈላሉ። እነዚህም፦
ተፈጥሮዓዊ ነገሮች፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ታሪካዊ ጉዳዮች ናቸው። የአንድን ህዝብ የእድሜና
የፆታ ስብጥር (ውቅር) የምንተነትንበት ሥእላዊ መግለጫ የህዝብ ፒራሚድ በመባል ይታወቃል፡፡ የህዝብ
ፒራሚድ የአንድ አካባቢን ህዝብ የእድሜና የፆታ ስብጥር ከማሳየቱም በላይ በህዝቡ ውስጥ ያለውን
የውልደትና የሞት ሁኔታ፤ እንዲሁም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ አመልካች ነው፡፡ የስነህዝብ መረጃ
ፖሊሲዎችን፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቅዶችን ለመንደፍ መሰረታዊ ጠቀሜታ አለው። የስነ ህዝብ መረጃ
አሰባሰብ የአንድ አገር ከሌላው ስለሚለይ በአገሮች መካከል ያለውን የስነ ህዝብ መረጃ ማወዳደር አስቸጋሪ
ነው። ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይ የስነህዝብ መረጃ አሰባሰብ ዘዴዎች በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች ይመደባሉ።
እነሱም ሙሉ ቆጠራ (Census)፣ የናሙና ቆጠራ (Sampling method) እና የአብይ ምዝገባ (Vital
registration) ናቸው። በኢትዮጵያ ፈጣን የህዝብ ቁጥር እድገትን ለመግታት ይቻል ዘንድ የስነ ህዝብ ፖሊሲ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ተቀርፆ የተለያዩ እስትራተጅዎች ተነድፈዋል። የዚህ ፖሊሲ ዋነኛ አላማም የአገሪቱ ፈጣን የህዝብ ቁጥር
ጭማሬ ከምጣኔ ሀብታዊ እድገቱና ከተፈጥሮ ሃብቱ የመሸከም አቅም ጋር ማመጣጠን ነው።

የምዕራፉ ማጠቃለያ ጥያቄዎች


1. ሰብዓዊ ፍጡራን ከእንስሳት የሚለዩባቸውን ዋና ዋና ባህርያት በዝርዝር ግለፁ።
2. የአንድን ህዝብ፦
ሀ. ስነህይወታዊ
ለ. ባህላዊ
ሐ. ኢኮኖሚያዊ እና
መ. ዲሞግራፊያዊ ሁኔታዎች ለመግለፅ የሚያስችሉ ዝርዝር ባህርያት አስቀምጡ።
3. የህዝብን ባህርያት የማጥናት ወይም የማወቅ ጠቀሜታው ምንድን ነው?
4. የሚከተሉትን መለኪያዎች ምንነት በቀመርና በምሳሌ አስደግፋችሁ አስረዱ፡፡
 የውልደት ሬት ወይም ፍጥነት (crude birth rate)
 የሞት ሬት ወይም ፍጥነት (Crude death rate)
 የገቢ ፈላሲያን ሬት ( Rate of immigration)
 የወጪ ፈላሲያን ሬት (Rate of emigration)
 የተጣራ ፍልሰት ሬት (Rate of net migration)
 ተፈጥሮአዊ የህዝብ ጭማሬ ሬት (Rate of natural increase)
 የህዝብ እድገት ሬት (ፍጥነት) (Population growth rate)
 ግርድፍ የህዝብ ጥግግት (crude density)
 የህዝብ ጥግግት በመኖሪያ አካባቢ( Residential density)
 ፊዚዮሎጂካዊ የህዝብ ጥግግት (Physiological density)
 የግብርና ጥግግት ( Agricultural density)
 ንፅፅራዊ ጥግግት (Comparative density)

ምዕራፍ አራት

ኢትዩጵያና የአፍሪካ ቀንድ /እ.ኤ.አ ከ 1855-1991/

የምዕራፉ አላማዎች፤- ተማሪዎች ይህን ምዕራፍ ካጠናቀቁ በኃላ፤


 ለዘመናዊ ኢትዮጵያ ማእከላዊ መንግሰት ምስረታ አስተዋጽኦ ያደረጉ ነገስታትና ስራዎቻቸዉን
ያብራራሉ
 የጥምር አገዛዝና የፍጹማዊ ዘዉዳዊ አገዛዝ አመሰራረትን ይገልጻሉ
 የ 1935 (እ.ኤ.አ) የጣልያን ወረራና የኢትዮጵያ ነጻነት መመለስ ሂደትን ይዘረዝራሉ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 የዘዉዳዊ ስርአቱን በመቃዎም የተደረጉ የተለያዩ ተቃዉሞዎችን ይለያሉ


 የደርግን አመሰራረት ይናገራሉ
 የደርግን አወዳደቅና የኢ.ህ.አ.ዴ.ግን አመሰራረትን ይተነትናሉ

4.1 የኢትዩጵያ ማዕከላዊ መንግስት ምስረታ

መግቢያ፡-
የዘመናዊ የተማከለ የአፄ ግዛት ምስረታ በኢትዩጵያ የተጀመረውና የተጠናቀቀው በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛው አጋማሽ
ነው ፡፡ ይህ የተማከለ የአፄ ግዛት ምስረታ በዋናነት የተጀመረው በአፄ ቴወድሮስ 2 ኛ ከ 1855 ዓ.ም ጀምሮ ነበር፡፡ አፄ
ቴዎድሮስ ኢትዩጵያ በተማከለ የአፄ ግዛት እንድትመራና የዘመነ መሳፍንት ዘመን መከፋፈል እንዲቀር ትልቅ ስራ ሰርተዋል፡፡
ይህ ፖሊሲያቸውም ከእርሳቸው ቀጥሎ በተነሱት ነገስታት ተቀባይነት አግኝቶ ሊቀጥል ችሏል፡፡

ከእሳቸው ቀጥሎ የተነሱት ነገስታት ማዕከላዊነትን ለመመስረት የተከተሏቸው ዘዴዎች መካከል ጥቂቶቹ “የፌዴራል” መሰል
አስተዳደር፣ የግዛት ማስፋፋትና ማግባባት ዘዴዎች ይጠቀሳሉ፡፡ በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ይህ የማዕከላዊ መንግስት
ምስረታ መጠናቀቅ ችሏል፡፡ ይህ የተማከለ የአፄ ግዛት ምሰረታ በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን ብዙ መስዋትነት አስከፍሏል፡፡
ለምሳሌ ብንወስድ በጣም ብዙ የሰው ደም ፈሷል፣ ብዙ ንብረት ወድሟል የባህል መጨፍለቅ አስከትሏል፣ የብሄር ጭቆናና
ማህበራዊ ቀውስ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ የማዕከላዊ መንግስት ምስረታውን ፈታኝ ካደረጉት ነገሮች አንዱ ደግሞ የውጭ ወረራ
ሙከራ ስጋት ነበር ፡፡ ስለሆነም ሀገርን ከውጭ ወረራ የመከላከል ጦርነቶች ከግብፆች፣ ከማህዲስቶችና ከጣሊያኖች ጋር
ተደርጓል፡፡ ከዚህ ቀጥሎ ባጭሩ በዚህ የተማከለ የአፄ መንግስት ምስረታ አስተዋፅኦ ያደረጉ ነገስታትን እናያለን፡፡

ተግባር፡- 4.1
- ለተማከለ የዘመናዊ የአፄ መንግስት ምስረታ አስተዋፅኦ ያደረጉ ነገስታትን ዘርዝሩ

የአፄ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግስት /እ.ኤ.አ 1855 – 1868/


ካሳ ሀይሉ የተወለዱት በ 1820 ቋራ ውስጥ እንደሆነ ይታመናል፡፡ አባታቸው የቋራ አስተዳዳሪ እንደነበሩና ኃላም አባታቸው
ከሞቱ በኃላ የሀይማኖት ትምህርት ለመማር ወደ ቸንከር ተክለሀይማኖት ሄዱ፡፡ በዘመኑ የነበረው የርስ በዕርስ ውጊያ
ምክንያት የሚማሩበት ገዳም ሲፈርስ ወደ አጎታቸው ደጅአዝማች ክንፋ በመሄድ ወታደር ሆኑ፡፡ ከአጎታቸው ሞት
በኃላ የቋራ ወረዳ በራስ አሊ እናት ማለትም በእቴጌ ምንትዋብ ስር መስተዳደር ጀመረ፡፡ በዚህ ምክንያት ካሳ
ሀይሉ በቋራ ውስጥ በሽፍትነት ወጡ፡፡ ቀስ በቀስ ብዙ ተከታዬችን በማፍራት ታዋቂነታቸው መግነን ጀመረ፡፡
ራስ አሊና እቴጌ ምንትዋብም የካሳ ሀይሉን ጦር ማሸነፍ ባለመቻላቸው በ 1846 ልጃችሁን ተዋበችን
ዳሩላቸው የቋራ አስተዳዳሪነት ሹመትም አገኙ፡፡ ከአመት በኃላ ግን እንደገና በመሸፈት የራስ አሊን ጦር
አሸነፉ፡፡ በውጤቱም ቀድሞ በአጎታቸው ስር የነበረውን ሰፊ ግዛት በሙሉ ማስተዳደር ቻሉ፡፡ ቀጣዩ የካሳ ሀይሉ
ትግል የነበረው በጊዜው ወደ ኢትዬጵያ ድንበር ይጠጉ ከነበሩት ከግብፆች ጋር ነበር፡፡ በዚህም ዙሪያ በተለይ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

በደባርቂ ጦር ግንባር በ 1848 ሽንፈት አጋጥሟቸዋል፡፡ ከሽንፈታቸውም ጦራቸውን በዘመናዊ መልክ


ማደራጀት እንደሚገባቸው ትምህርት ወስደዋል፡፡

አፄ ቴዎድሮስ 2 ኛ
በ 1852 እንደገና በማመጽ ከራስ አሊ ጋር ወደ ማይቀረው ጦርነት መሄዳቸው አልቀረም፡፡አንድ በአንድ የዘመኑ
ማለትም የዘመነ መሳፍንት አጋፍሪ የሆኑ መሳፍንቶችን ድል በማድረግ ኢትዩጵያን ወደ አንድነት መመለስ
ተግባርን ተወጥተዋል፡፡ በዚህም መሰረት ፡
 በህዳር 1852 የጎጃሙን ደጃች ጎሹን በጉራምባ ጦር ሜዳ
 በሚያዝያ 1853 ብሩ አሊጋዝና ሌሎች የራስ አሊ መሳፍንትን በጎርጎራ ብችን ጦር ሜዳ
 በሰኔ በ 1853 ራስ አሊን በአይሻል ጦር ሜዳ
 በመጨረሻም የትግራዩን ራስ ዉቤን በደረስጌ ጦር ሜዳ ድል በማድረግ አፄ ቴዎድሮስ 2 ኛ በመባል
በደረስጌ ማሪያም የንግስናቸው ስነ-ስርዓት ተፈፅሟል፡፡

የአፄ ቴዎድሮስ የለውጥ /የማሻሻያ/ እርምጃዎች


አፄ ቴዎድሮስ በዘመናቸው ለማሻሻል የሞከሩዋቸው ጉዳዬች እጅግ በርካታ ነበሩ፡፡ ከነዚህ መካከል ጥረቶቹ
የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. ኢትዬጵያን አማክሎ የመግዛት ተግባር

አፄ ቴዎድሮስ አንድ ማዕከላዊ መንግስት ለመመስረት የተለያዩና ከባድ ጦርነቶችን አካሂዷል፡፡ የመጀመሪያ
ዘመቻቸውን ያደረጉት ወደ ወሎ ሲሆን ሂደቱም የተሳካ አልነበረም፡፡ ከወሎ ቀጥሎ ወደ ሽዋ ዘምተዋል ፡፡
በዚህም መሰረት በ 1855 በረከት በተባለው ጦር ግንባር የሸዋውን ሐይለ መለኮት በማሸነፍ ሽዋን በቁጥጥር ስር
ማድረግ ችለዋል፡፡ የአፄ ቴዎድሮስ ህልም በዘመኑ ጥልቅ እንደነበር ብዙ ምሁራን ፅፈዋል፡፡ ኢትዩጵያን አንድ
ማድረግ ብቻ ሳይሆን እየሩሳሌምን ከቱርክ ነፃ አደርጋለሁ የሚል ሀሳብ እንደነበራቸው ይነገራል፡፡
2. ዘመናዊነት፤- አፄ ቴዎድሮስ ዘመናዊ ቴክኖሎጅዎችና የጦር መሳሪያዎች

ለሀገራቸው መግባት ወይም መስራት እንዳልባቸው ያምኑ ነበር፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ያልተሞከሩ
የተሻሻሉ አሰራሮችንም ለማስተዋወቅ ጥረት አድርገዋል፡፡ ከነዚህም መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት
ይገጥባቸዋል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 የማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያዎች- አፄ ቴዎድሮስ ባርነትን ለማቆም አዋጅ አውጥተዋል፣ ከአንድ


በላይ ጋብቻን ከልክለዋል፣ በሀገሪቱ ሰላምና ደህንነት የሚያመጡ ብዙ አዋጆችን አዉጥተዋል፡፡ ይህም
ብቻ ሳይሆን የመንግስታቸውን ገቢ ለማሳደግ ትርፍ የቤት ክ/ያን መሬትን ለገበሬዎች ለማከፋፈል
ሙከራ አድርገዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የቤተ ክህነት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል፡፡
 የጦር ሰራዊቱን አሰራር ማሻሻል- በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ዘመናዊ የጦር ሰራዊት በመገንባት ጥረት
አድርገዋል፡፡ ለዚህም እንዲረዳቸው ውትድርና እንደ አንድ ስራ በደመወዝ የሚከናወንና የራሱ
ዲሲፒሊን እንዲኖረው እንዲሁም የተለያዩ የማዕረግ ስሞችን በዕድገት እንዲገኙ ደንግገዋል፡፡
 ሀይማኖታዊ ማሻሻያዎችና በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበሩ መከፋፈሎችን ለማስቀረት
ብዙ ጥረቶችን አድርገዋል፣ በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚያገለግሉ ቀሳውስት ዲያቆናት ቁጥር
እንዲቀንስ ጫና አድርገዋል፣ በዘመኑ ከፍተኛ ስልጣን የነበራቸውን የግብፅ ፖትርያርኮች ስልጣንን
ለመገደብ ሞክረዋል፡፡

እነዚህና ሌሎቹ የማሻሻያ ሙከራዎች ግን በተገላቢጦሽ ለንጉሱ ብዙ ፈተና ያመጡባቸውና ለርሳቸውና


ለመንግስታቸው መውደቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡
ተግባር 4.2
- የአፄ ቴዎድሮስ ሌሎች ማሻሻያዎችን ዘርዝሩ
- የአፄ ቴዎድሮስ የዉጭ ግንኙነት ፍላጎት ምን ላይ ያተኮረ ነበር?

ንጉሱም የውስጥና የውጭ ጠላቶች ዕረፍት ነስተዋቸዋል፡፡ በተለይም ሀገሪቱን አንድ የማድረግ ተግባራቸው
በተለያዩ የአካባቢያዊ ገዥዎች አልተወደዱም ተድላ ጓሉ በጎጃም ፣ ጢሶ ጎበዜ በወልቃይት፤ ዋግሹም ጎበዜ
በላስታ፤ ንጉሴና ተሰማ በስሜን ፣ካሳ ምርጫ በትግራይ ፣ሐይለ መለኮት በሽዋ ተነስተዉባቸዋል፡፡ ንጉሱም
የስልጣን ዘመናቸውን በሙሉ ማለት በሚቻል በየአካባቢው በጦርነት ቢንከራተቱ በመኖራቸው ከላይ
የተጠቀሱት ማሻሻያ ሀሳባቸውነን ሙሉ በሙሉ መተግበር ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ በተለይ ጨከን ያሉ
እርምጃዎችን እንዲወስዱና ንጉሱ ከለውጥ አርያነታቸው ይልቅ ጭካኔያቸው እንዲታወቅ አስተዋፅኦም
አበርክቷል፡፡

ከላይ እንደተጠቀሰው ሀገሪቱን የማዘመን ራዕያቸውም በመጨረሻው ከእንግሊዞች ጋር እንዲጋጩ አድርጓል፡፡


የእርዳታ ጥያቄ የያዙ የተለያዩ ደብዳቤዎችን ወደ እንግሊዝ ንግስት ቪክቶሪያ ቢልኩም የፈለጉት የቴክኒክ
ድጋፍ ማግኘት አልቻሉም፡፡ በዚህም በመበሳጨት በእጃቸው የነበሩ የእንግሊዝ ሚሲዩናዉያንና የመንግስት
ተወካዩችን አስረዋል፡፡ እነዚህንም ጋፋት በሚባለው ቦታ ከመውሰድ ሴባስቶፖል የሚባል መድፍ አሰርተዋል፡፡
በንጉሱና በእንግሊዝ መንግስት መካከል የሻከረው ግንኙነት በመጨረሻው ወደ ጦርነት ደርሷል፡፡ የታሰሩ
ዜጎቻችን ለማስፈታት በማለት እንግሊዞች በጀኔራል ናፒየር የሚመራ 10‚000 ጦር በመላክ በ 1867 ምፅዋ ላይ
አሰፈሩ፡፡ ይህ የእንግሊዝ ጦር በካሳ ምርጫ መሪነት ወደ መቅደላ በመንቀሳቀስ ከመቅደላ ጦርነት አራት ቀን
በፊት እሮጌ በተባለው ስፍራ ከአፄ ቴዎድሮስ ጦር ጋር ጦርነት ገጠመ፡፡ በዚህም ጦርነት ፈታውራሪ ገብሬና
ሌሎች የንጉሱ ታማኞች ተሰውተዋል፡፡ በሚያዝያ 14/1868 መቅደላ ላይ በተደረገው ውጊያ በዘመኑ ዘመናዊ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ጦር መሳሪያና ዲሲኘሊን የነበረው የእንግሊዝ ሰራዊት የንጉሱን ጦር ድል አደረገ፡፡ በዚሁ ቀንም አፄ ቴወድሮስ
ለጠላት ጦር ላለመማረክ ሲሉ ራሳቸውን በሽጉጥ ገደሉ፡፡ የእንግሊዝ ጦርም ብዙ የኢትዩጵያ ቅርሶችን
በመዝረፍ ምርከኞችን በማስፈታት ተመልሶ ሄደ፡፡

የአፄ ዮሀንስ IV ዘመነ መንግስት /እ.ኤ.አ 1872-1889/


ተግባር. 4.3
- የተማከለ የአፄ መንግስት ምስረታ ዙሪያ በአጼ ዮሃንስና በአጼ ቴዎድሮስ መካካል ያለዉን የፖሊሲ ልዩነትና
አንድነት አብራሩ

ከአፄ ቴዎድሮስ ሞት በኃላ በሀገሪቱ ስልጣን ለመያዝ የተለመደው ውዝግብ ቀጥሏል፡፡ ለአጭር ጊዜም ቢሆን
ስልጣኑን የተረከቡት የላስታው ዋግሹም ጎበዜ ናቸው፡፡ የንግስና ስማቸውንም ተክለ ጉዩርጊስ በማለት
ሰይመዋል፡፡ በወቅቱ ተገዳዳሪ የነበሩት መኳንንት ዋግሹም ጎበዜ /ላስታ/ ፤ካሳ ሞጫ /ትግራይ/ እና የሽዋው
ሚኒሊክ ነበሩ፡፡ ዋግሹም ጎበዜ ንግስናውን ቢረከቡም በተለይ ትግራይንና ሽዋን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡
ትግራይን ለመቆጣጠር ባደረጉት ውጊያ አሳም በተባለ ቦታ በጥር 1872 በካሳ ሀይሉ በመሸነፋቸው አጭሩ
የስልጣን ዘመናቸዉ ተጠናቋል፡፡

አፄ ዮሀንስ 4 ኛ

አፄ ዮሀንስ 4 ኛ በመካከል ካሳ ሞጫ በጥር 1872 ንጉሰ ነገስትነቱን ተረከቡት፡፡ አፄ ዩሀንስ የአፄ ቴዎድሮስን
ማዕከላዊ መንግስት ምስረተ ሀሳብ ቢረከቡም የተከተሉት ስልት ግን የተለየ ነበር፡፡ ከአፄ ቴዎድሮስ በተለየ
መልኩ የአካባቢያዊ መሪዎችን ስልጣን ዕውቅና ሰጥተዋል፡፡ የተከተሉትም ስልት “የፌዴራላዊ” አስተዳደር
መልክን የተከተለ ነበር፡፡ ከረጃጅም ጦርነቶች ይልቅ ስምምነቶችን ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ ለምሳሌ ብንወስድ
ከጎጃሙ አዳል ተሰማ ጋር በመስማማት ተክለ ሀይማኖት በሚል ስያሜ የጎጃም ንጉስ እንዲሆኑ አድርገዋል፡፡
ለረዥም ጊዜ የርሳቸውን ንጉሰ ነገስትነትን ካልተቀበሉት ከአፄ ሚኒሊክ ጋርም ትልቅ ትዕግስት በማሳየት
በመጨረሻ በ 1878 ዓ.ም ላይ በተደረገ ስምምነት የሚከተለውን ቃለ ተግባብተዋል፡፡
 ሚኒሊክ ለአፄ ዩሀንስ ግብር ሊገብሩ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 ሚኒሊክ ንጉስ ነገስት የሚል መጠሪያ በመተው የሽዋ ንጉስ ሊባሉ


 ከአፄ ዩሀንስ እውቅና ውጭ ከኢጣሊያኖች ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ሊያቆሙ
 ሚኒሊክ የአፄ ዩሀንስን ንጉሰ ነገስትነት ሊቀበሉ ናቸው፡፡ አፄ ዩሀንስም ሚኒሊክ ሲወርድ ሲዋረድ
የመጣውን የሽዋ መንግስት ንጉስነትን ሊቀጥሉ እንዲሁም ወሎን እንዲያስተዳድሩ ተፈቅዶላቸዋል፡፡
ሆኖም ግን በተለያዩ ጊዜያት እነዚህ ስምምነቶች ሊጣሱ ችለዋል፡፡

አፄ ዩሀንስ ሀይማኖት ላይ የነበራቸው አቋም ከፖለቲካ አቅማቸው ጋር ፈፅሞ ተቃራኒ ማለት ይቻላል ፡፡
በሌሎች ሀይማኖቶች ላይም ፅኑ ቅጣቶችን ፈፅመዋል፡፡ በ 1878 በቦሩ ሜዳው ጉባኤ መሰረት በተለይ የወሎ
ሙስሊሞች በግዳጅ ወደ ክርስትና መለወጥ እንዳለባቸው ካልተለወጡ ግን ንብረታቸውና መሬታቸው
እንዲወረስ እንዲሁም ፅኑ ቅጣት ማድረሳቸው ፖሊሲያቸው ከባድ እንደነበር ያመላክታል፡፡

የአፄ ዩሀንስ ሀገርን ከውጭ ወረራ የመከላከል ተግባር እጅግ ውጤታማ ነበር፡፡ በዘመናቸዉ በዋናነት የኢትዩጵያ
ሉዓላዊ ድንበርን ጥሶ የገባው ጠላት ግብፅ ነበረች፡፡ የግብፅ መሪ የነበረው ሙሀመድ አሊ ዋና አላማ የነበረው
የአባይ ተፋሰስን እስከ ኢትዩጵያ መቆጣጠር ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ግብፅ በ 1865 አስብን በመቆጣጠር
በሶስት አቅጣጫ ወደ ኢትዩጵያ የመስፋፋት ሙከራ አደረገች፡፡ በዚህም መሰረት እቅዱን ያዘጋጀው
የሲውዘርላንድ ተወላጅ የነበረው ቅጥረኛ ወርነር ሙንዚንገር ነበር፡፡ በምስራቅ በመሀመድ ራቲብ ፓሻ
የሚመራው ጦር ሀረርን ተቆጣጠር፡፡ በጅቡቲ (ታጁራ)በኩል በሙንዚንገር የሚመራው ጦር አፋርን
ለመቆጣጠር ተንቀሳቀሰ፡፡ ሶስተኛው ከምፅዋ የተነሳው ጦር በኮረኔል አረንድሩፕ የሚመራው ሲሆን ወደ ሰሜን
ኢትዩጵያ ተንቀሳቀሰ፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ ሚኒሊክና ተክለሀይማኖት በአፄ ዩሀንስ ላይ ያመጹበት ጊዜ ሲሆን አፄ
ዩሀንስ ግን የውጭ ወራሪን ማጥፋት ላይ ትኩረት በማድረግ በግብፆች ላይ ዘምተዋል የመጀመሪያ
ፖሊሲያቸዉ ጦርነት ሳይሆን ዲኘሎማሲ ነበር፡፡ ስለሆነም ለግብፁ መሪ ደብዳቤ ቢልኩም መልስ ማግኘት
አልቻሉም፡፡ ቀጥለዉ ለአውሮፖ ሀገራት ማለትም ለእንግሊዝ ፈረንሳይና ሩሲያ አቤት ብለዋል፡፡ ነገር ግን
ምላሽ ማግኘት አልቻሉም፡፡ ይህም ወደ አይቀሬው ጦርነት አመራ፡፡ በጥቅምት 23/1875 ጦራቸውን
በማንቀሳቀስ ጉንደትና ጉራ በተባሉ ጦር ግንባሮች ግብፆችን ድል አድርገዋል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በመጋቢት
1889 መተማ ላይ ከማህዲስቶች ጋር በተደረገው ጦርነት ሀገራቸውን ለመጠበቅ መስዋዕት ሆነዋል፡፡

አፄ ምኒሊክ /እ.ኤ.አ ከ 1889 – 1911/


ከአፄ ዩሀንስ ሞት በኃላ የንጉሰ ነገስታትነቱን ስልጣን የተረከቡት የሽዋ ንጉስ የነበሩት ሚኒሊክ ናቸው፡፡ በአፄ
ቴዎድሮስ የተጀመረው የማዕከላዊ መንግስት ምስረታ ሂደት ይበልጥ ያደገውና አሁን ያለችውን ኢትዩጵያ
ቅርፅ የተሰራው በዚህ በአፄ ሚኒሊክ ዘመን ነበር፡፡

በአፄ ሚኒሊክ ዘመን ብዙ ተግባሮች የተከናወኑ ሲሆን ዋና ዋናዎቹ ግን የሚከተሉት ናቸው

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

1. የግዛት ማስፋፋት- አዲስ ወደ ግዛት ከተቀለቀሉ አካባቢዎች የንግድ መስመሮችን ለመቆጣጠርና


ግብር ለመሰብሰብ አፄ ሚኒሊክ ወደ ደቡብ፤ ደቡብ ምዕራብና ደቡብ ምስራቅ ተንቀሳቅሰዋል፡፡
ቦታዎችንም በጦርነትና በዲኘሎማሲ መቆጣጠር ችለዋል፡፡ የግዛት መስፋፋት ሂደቱም በሶስት
ምዕራፎች የተከፈለ ነው፡፡

አፄ ሚኒሊክ 2 ኛ
የመጀመሪያ ምዕራፍ /1878-1889/

በዚህ ምዕራፍ ለሸዋ ቅርበት ያላቸው ቦታዎች ማለትም ጉራጌ፣ አርሲ ፣ሀረርና ስልጤ ወደ ግዛት ተቀላዋል፡፡
በዚህ ምዕራፍ እንደ ሀረር ፣ አርሲና ስልጤ ጉራጌ ያሉ ቦታዎች በጦርነት የተለያዙ ናቸው፡፡ ሌሎች ቦታዎች
ማለትም በሰላም እንገባለን ያሉ እንደ ጉራጌ ፣ ጅማ እና ጌራ በሰላም የተቀላቀሉ ናቸው
 የሁለተኛው ምዕራፍ /1889 – 1896/- ይህ ዘመን ክፉ ቀን /1889-1891/ የተባለው የረሀብ ጊዜ
የነበረበት በመሆኑ አፄ ሚኒሊክ በ 1894 ወደ ወላይታ በመዝመት ንጉሱን ካዎ ጦናን ድል አድርገው
ብዙ ሀብት ይዘው ተመልሰዋል፡፡ በረሀቡ ምክንያት ብዙ ቦታዎች መያዝ አልተቻለም፡፡
 የሶስተኛው ምዕራፍ /1896-1900/ - በዚህ ዘመን የአፄ ሚኒሊክ ትኩረት የነበረው የድንበር
አካባቢዎችን መቆጣጠር ነበር፡፡ ይህም የሆነበት ዋናው ምክንያት በዘመኑ የነበሩ ቅኝኘ ገዥ ሀይሎችን
ለመግታት ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ከፋ፣ አፋር፣ ኦጋዴን፣ ጋንቤላ፣ ቤንሻጉል፣ እና ቦረና ወደ ግዛታቸው
ተቀላቅለዋል፡፡ ከዚህ በኋላ በአካባቢው ካሉ የቅጥ ግዛት ሀይሎች ጋር ንጉሰ ነገስቱ የድንበር ስምምነት
ከ 1897-1908 ድረስ ባለው ጊዜ ተፈራርመዋል፡፡
 በአፄ ሚኒሊክ ዘመን ከተከናወኑት ተግባራት አንዱ ከጣሊያኖች ጋር የጀመሩት ወዳጅነት ነበር፡፡ ይህ
ወዳጅነት የተጀመረው በ 1876 ሲሆን በ 1889 የውጫሌ ስምምነት ድረስ ሰላማዊ ነበር፡፡ ለሁለቱ
ወገኖች ጠብ መንስኤ የሆነው በዋናነት የውጫሌ ስምምነት አንቀፅ 17 ነው፡፡ የአማርኛ ትርጉሙ
ኢትዩጵያ ከፈለገች በጣሊያን በኩል ከሌሎች ሀገራት ጋር መገናኘት እንደምትችል ሲያመላክት
የጣሊያኑ ትርጉም ግን ኢትዬጵያ የግድ የውጭ ግንኙነት ማድረግ ያለበት በጣሊያን በኩል ብቻ
እንደሆነ ነዉ፡፡ ይህም የጣሊያንን የቅኝ ግዛት ፍላጎት በግልፅ ያመላከተ ሲሆን አፄ ሚኒሊክ ጉዳዩን
በድርድር ለመጨረስ ሙከራ አድርገው ባለመሳካቱ በማርች 1/1896 የኢትዩጵያ ድል ሊጠናቀቅ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ችሏል፡፡ ይህ የአድዋ ድል ለኢትዩጵያን ብቻ ሳይሆን ለመላው የአለም ጥቁር ህዝቦች ኩራትና የነፃነት
ቀንዲል ተደርጎ ተወስዷል፡፡

ተግባር፡ 4.4
መፃህፍትን በማገላበጥና ምሁራንን በማማከር ስለአድዋ ጦርነት አጀማመር፣ ሂደትና ውጤት
ጥናት ካደረጋችሁ በኋላ ለክፍል ጓደኞቻችሁ አቅርቡ፡፡

4.2 የሁለትዮሽ አስተዳደርና የፍፁማዊ ዘውዳዊ ስርዓት መመስረት


መግቢያ፡-
ከአድዋ ድል በኃላ የመጀመሪያዎቹ አስር አመታት የአፄ ሚኒሊክ ስልጣን መጠናከር የታየባቸው አመታት ነበሩ፡፡
የአፄ መንግስት ምስረታውም ተጠናቆባቸዋል፡፡ የኢትዩጵያ ደንበሮችም የተከለሉበትና ሰፊ የዲኘሎማሲ ስራ
የተሰራባቸው ነበሩ፡፡ የንጉሰ ነገስቱ ስልጣን የተጠናከረበትና ጠንካራ የውስጥ ችግር ያልነበረበት ጊዜ ነበር ፡፡
ነገር ግን ይህ የመረጋጋትና የመንግስት መጠናከር ጊዜ የቀጠለው እስከ 1906 ነበር ፡፡ ከዚህ አመት ጀምሮ
ኢትዩጵያ በተለያዩ ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮች ወድቃለች፡፡ እነዚህም በውስጥ በዋናነት የስልጣን ሽኩቻ ሲሆን
በውጭ ደግሞ የቅኝ ግዛት ፍላጎት እንደገና መቀስቀስ ናቸው፡፡ የውስጥ ችግሩ ለረጅም ጊዜ የቀጠለና ብዙ ደም
መፍሰስን ያስከተለ ነበር፡፡ በተለይ በ 1930 ከዘውዱ ተቀናቃኞች አራዱ ንጉስ ነገስት መሆን በሀገሪቱ ፍፁማዊ
ዘውዳዊ ስርዓት መመስረት መሰረት ጥሏል፡፡ የውጭ ስጋቱም በዋናነት የመጣው ከእንግሊዝ ፈረንሳይና
ጣሊያን በኢትዩጵያ ላይ ያላቸው ፍላጎት ሲሆን በተለይ የጣሊያን ፍላጎት ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ሊለወጥ
ችሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ጣሊያን ኢትዩጵያን በ 1935 ለመውረር በቅታለች፡፡ ምንም እንኳ እነዚሀ ችግሮች
ቢኖሩም ሀገሪቱ በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አጋማሽ ጥቂት የማህበራዊና የኢኮኖሚያዊ ልማቶችና
እድገቶች ለማሳየት በቅታለች ፡፡
በዚህ ክፍል በዋናነት የምናየው ስለሁለትዩሽ አስተዳደርና ኃላም የፍፁማዊ ዘውዳዊ ስርአት አመሰራረት
ይሆናል፡፡

በሀገሪቱ የስልጣን ሽኩቻዉ መፋፋም የጀመረው ከአፄ ሚኒሊክ ህመም መጀመር ማለትም በ 1906 ነበር፡፡
በዚህ አመት በተለይ ከላይ የተጠቀሱት ሶስቱ ቅኝ ገዥ ሀገሮች ማለትም እንግሊዝ፣ ፈረንሳይና ጣሊያን
የሶስትዬሽ ስምምነት (Tripartite Treaty) ተዋውለዋል፡፡ ሀገሪቱ ከአፄ ሚኒሊክ ሞት በኋላ በስልጣን ሽኩቻ
ስትተራመስ የራሳችንን ፍላጎት እናሟላለን ብለው አስበው ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ፈረንሳይ የባቡር ሀዲድ
ያረፈበትን አካባቢ ለመውሰድ፣ እንግሊዝ የአባይ ሸለቆንና ምንጩን አካባቢ ለመቆጣጠር እንዲሁም ጣሊያን
ሁለቱን ቅኝ ግዛቶችን ማለትም ኤርትራና የጣሊያን ሶማሊላንድን የሚያገናኝ የባቡር መስመር እንድትሰራ
ተስማሙ፡፡ በህመም ላይ ያሉት አፄ ሚኒሊክ እነዚህን ሁለት ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮችን ለመቋቋም
ያሰቡትን ከማድረግ አልቦዘኑም፡፡ በመሆኑም ሁለት ነገሮችን አደረጉ፡፡ የመንግስት እንቅስቃሴው በሰላማዊ
መንገድ እንዲቀጥልና ፖለቲካዊ መረጋጋት እንዲመጣ በጥቅምት 1907 የመጀመሪያውን የሚንስትሮች
ም/ቤት አቋቋሙ፡፡ በመቀጠልም በግንቦት 1909 አልጋ ወራሻቸው እንዲሆን የልጅ ልጃቸውን ልጅ እያሱን
ሾሙ፡፡ በ 1913 ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ከአአፄ ሚኒሊክ ሞት በኃላ ልጅ እያሱ ከእንደራሴያቸው ራስ ተሰማ ናደው ጋር ሀገሪቱን ለማስተዳደር ሙከራ
ቢያደርጉም ከፍተኛ ተቃውሞ ከእትጌ ጣይቱና ከሽዋ መኳንንት በኩል ተጋርጠባቸዋል፡፡ በተለይ ለእስልምና
ሀይማኖት ድጋፍ አድርጓል እንዲሁም ሙስሊም ሴቶችን አግብቷል በሚል ሰበብ የሽዋ መሳፍንት ስልጣኑን ወደ
ሽዋ ለመመለስ ከነበራቸው ፍላጎት አንፃር ከፍተኛ ተቋውሞ ደርሶባቸዋል፡፡ በመሆኑም መስከረም 27/1916
በተደረገ መፈንቅለ መንግስት ከስልጣናቸው ተባረዋል፡፡

የሁለትዩሽ አስተዳደር (Dual rule) እ.ኤ.አ ከ 1917-1930


ከልጅ እያሱ የስልጣን መወገድ እያሱ በኋላ በልጅ እያሱ አባት የወሎዉ ንጉስ ሚካኤልና በሽዋ መሳፍንት
መካከል ሰገሌ ላይ በተደረገ ጦርነት ከ 12‚000 ሰው በላይ አልቋል፡፡ ጦርነቱም በንጉስ ሚካኤል ሽንፈት
ተጠናቋል፡፡ ከላይ እንደተገለፀው መፈንቅለ መንግስት አድራጊ የሽዋ መሳፍንት የአፄ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን
ዘውዲቱን ንግስት ብለው በየካቲት 1917 ስልጣን ላይ ሲያወጡ ራስ ተፈሪ መኮነን ደግሞ የእንደራሴነቱንና
የአልጋ ወራሽነትን ስልጣን ተረክበዋል፡፡
ይህ የፖለቲካ ድራማ /ቀመር/ ከ 1906 ጀምሮ ለተነሳው የስልጣን ሽኩቻ መልስ ለመስጠት የታሰበ ነበር ፡፡
ዘውዲቱ የንጉሰ ነገስቱ ልጅና ወግ አጥባቂ ሲሆኑ ልጅ ስለሌላቸዉ የስልጣን ሽኩቻን ለማስወገድ
የአልጋወራሽነት ለራስ ተፈሪ ተወስኗል፡፡ ተፈሪ የሽዋው መሳፍንትና የንጉሳዊ ቤተሰብ አባል በመሆናቸው
እንዲሁም ቀደም ብሎ በተለይ ሀረርን የማስተዳደር ችሎታቸው ለቦታው ብቁ እጩ አስብሏቸዋል፡፡
በመጀመሪያዎቹ ጊዜያት ይህ የሁለትዩሽ አስተዳደር የሽዋ ሀይላትን በአንድነት በማዕከላዊ መንግስቱ
ያስተሳሰረ ነበር፡፡ ቀስ በቀስ ግን ራስ ተፈሪ ስልጣንን ጠቅልለው ወደ ራሳቸው ማከማቸት ጀመሩ፡፡ ይህም
በንግስት ዘውዲቱና በራስ ተፈሪ መካከል ስልጣን ሽኩቻን አስከትሏል፡፡ወግ አጥባቂ መሳፍንት ንግስት
ዘዉዲቱን ሲደግፉ ተራማጅ የሚባሉት ደግሞ በተለይ የተማሩ ኢትዩጵያውያን ራስ ተፈሪን ደግፈዋል፡፡
እንዲሁም ሊቀ ጳጰሱ ንግስት ዘውዲቱን ሲደግፉ የውጭ አንባሳደሮችና መልዕክተኞች የራስ ተፈሪ ደጋፊዎች
ነበሩ፡፡ በዚህም መካከል የተፈሪ ተራማጅ መስሎ መታየት እንዲሁም የተማሩ አካላት ድጋፍ የስልጣኑን
የመጨረሻ ጫፍ የመያዝ ጉዞን አፍጥኖታል፡፡

የራስ ተፈሪን ወደ ስልጣን የመገስገስ ሂደት በዋናነት ያፋጠኑ ዋና ዋና ክስተቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
 በ 1918 በስልጣን በመባለግና በጉቦ ምክንያት የሚኒስትሮች ም/ቤት አባላት ከንግስት ዘውዲቱ
ከስልጣን መባረር
 በ 1921 የእጅ እያሱ መያዝ
 በ 1923 የኢትዩጵያ ወደ ሊግ ኦፍ ኔሽንስ /የመንግስታቱ ማህበር/ አባልነት መግባትና በ 1924 ራስ
ተፈሪ በተለያዩ አውሮፖ ሀገራት፤ ት/ቤቶችና ሆስፒታሎች ያደረጉት ጉብኝት
 በ 1924 ራስ ተፈራ ዋና ተቃዋሚዎች የሆኑትን ደጅ አዝማች ባልቻ ሳፎን ድል ማድረጋቸው
 በ 1926 የፊት አውራሪ ጊወርጊስና ሊቀ ጰጰስ አቡነ ማቲወስ መሞት
 በ 1928 የክብር ዘበኛ አዛዥ የነበሩት የደጅ አዝማች አባ ውቃው ሽንፈትና እስር
 በ 1928 የራስ ተፈሪ ንግስና /ንጉስ ተፈሪ መባል/

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 በመጨረሻም በ 1930 የንጉስ ተፈሪ ራስ ጉግሳ ወሌን ማሸነፍን የራስ ጉግሳ ሞት ፡፡ ከዚህ ክስተት
ሁለት ቀን በኃላም የንግስት ዘውዲቱ ሞት ናቸው፡፡

ስለሆነም በህዳር 2፤1930 ተፈሪ ንጉሰ ነገስት ሐይለ ስላሴ 1 ኛ በሚል ስያሜ የኢትዩጵያ ብቸኛ ገዥ ሆኑ፡፡
ከዚህ ክስተት በኃላ ሐይለ ስላሴ ፍፀማዊ ዘውዳዊ ስርዓትን ማስፈን ጀመሩ፡፡ አካባቢያዊ ገዥዎች
ስልጣናቸውን ቀስ በቀስ ማጣት ጀመሩ፡፡ ይህ የማማከል ሂደት ያፋጠኑ ዋና ዋና ክስተቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
 በ 1931 የመጀመሪያው የተፃፈ ህገ መንግስት መውጣትና ስልጣኑን ጠቅሎ ለንጉሰ ነገስቱ መስጠት
 ከዚህ በፊት በትውልድ ቅብብሎሽ ሲተዳደሩ የነበሩ ግዛቶች ለምሳሌ ጎጃም ፣ ጅማ በቀጥታ
በማዕከላዊ መንግስት ስር መተዳደር መጀመራቸው
 የፋይናንስና በቀረጥ ስርዓት አስተዳደር በቀጥታ በማዕከላዊ መንግስት ስር መሆን
 ጦር ሰራዊቱን የማዘመን ሂደት መጠናከር ናቸው፡፡

4.3 የ 1935 (እ.ኤ.አ) የጣሊያን ወረራና የኢትዩጵያ ነፃነት መውጣት


ከላይ እንደተገለፀው የአድዋ ድል የአውሮፖውያንን ኢትዩጵያን የመውረር አላማ ሙሉ በሙሉ አላቆመውም፡፡
ከአድዋ ድል አስር አመታት በኃላ የሶስትዩሽ ስምምነት መደረጉን አይተናል፡፡ ይህ ስምምነት በዋናነት
የከሸፈውም አፄ ሚኒሊክ በሳል እርምጃዎች መሆኑን አይተናል፡፡
የጣሊያን ኢትዩጵያ የመውረር አጀንዳ የታደሰው በ 1922 የሞሰሎኒና የርሱ ፖርቲ የሆነው የፋሽስት ፖርቲ
ስልጣን ላይ መውጣትን ተከትሎ ነው፡፡ የዚህ የጣሊያን የጦርነት ፍላጎት ምክንያቶች
 የአድዋ ድል ሽንፈታቸው ለመበቀበልና የቀደመውን የሮማ አፄ መንግስት ሀይል ለመመለስ
 የቤኒቶ ሞሰሎኒ የራሱን ክብርና ጀግንነት የማሳየት ፍላጎት
 በጣሊያን በ 1930 ዎቹ የነበረውን የኢኮኖሚ ውድቀት ተከትሎ የመጣውን የህዝብ ተቃውሞ
ለመቀልበስ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ጣሊያን ኢትዩጵያን በመውረር ድብቅ አላማዋን ለማስፈፀም በ 1934 የወልወል ግጭትን እንደሰበብ
ተጠቅማለች፡፡ በዚህ አመት የጣሊያን ጦር የኢትዩጵያ ድንበር አልፎ ሲገባ ከኢትዩጵያ ጦር ጋር ተጋጭቶ
በሁለቱም ወገኖች ወታደሮች ቆስለዋል፣ ሞተዋልም፡፡ ንጉሰ ነገስት ሐይለ ስላሴ ነገሩን በድርድር ለመፍታት
ለሊግ ኦፋኔሽንስ /የመንግስታቱ ድርጅት/ አቤቱታ ቢያሰሙም በወቅቱ ሀያል የነበሩት እንግሊዝና ፈረንሳይ
የጣሊያን ወዳጅ በመሆናቸው መፍትሄ ሊያገኙ አልቻሉም፡፡

በኢትዩጵያ በኩል በዘመኑ የነበረውን ዘመናዊ የጣሊያን ጦር የሚስተካከል ምንም ዝግጅት ያልነበረ ሲሆን
ጣሊያኖች ግን ከአድዋ ሽንፈት ጀምሮ ሲዘጋጁ እንደነበር ይታመናል፡፡፡
የጣሊያን ወረራ በሁለት አቅጣጫ (በደቡብና በስሜን) የተቃጣ ነበር ፡፡ ጦርነቱም የሚደራጀው ኤርትራ እና
የጣሊያን ሶማሊላንድ ላይ ነበር፡፡ የጦርነቱ ሂደት በአጭሩ የሚከተለውን ይመስላል፡፡ በጥቅምት 3፤1935
የጣሊያን ወታደሮች መረብ ወንዝን በማቋራጥ ወደ ትግራይ ገሰገሱ፡፡ የዚህ ጦር መሪ የነበረው ኢሚሊዩ ዲ ቦኖ
ነበር፡፡ በደቡብ ደግሞ በጀኔራል ግራዚያኒ የሚመራ ጦር ወደ መሀል ተንቀሳቀሰ፡፡ በጥቅምት ሙሉና በህዳር ወር

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

መጀመሪያ የጣሊያን ጦር ያለምንም መከላከል ወደ ኢትዩጵያ ተንቀሳቅሷል፡፡ ለዚህም ሁለት ዋና ዋና


ምክንያቶች የሚባሉት አንደኛ ኢትዩጵያ የጣሊያንን ወራሪነት አለም እንዲረዳው ለማድረግ ሲሆን ሁለተኛው
ደግሞ ለስትራቴጅያዊ ጠቀሜታ ነው ተብሎ ይታመናል የጣሊያን ጦርን ለመመከት የኢትዩጵያን አሰላለፍ
የሚከተለውን ይመስላል፡፡
የሰሜን ግንባር
 የዚህ ግንባር 3 ክፍሎች አሉት ፡፡ በራስ እምሩ የሚመራው በግራ በኩል ማለትም በሽሬ ግንባር
እንዲዋጋ ሲመደብ በመሀል ማለትም በተንቤን ደግሞ በራስ ስዩም መንገሻና በራስ ካሳ ሀይል እንዲዋጋ
ተመድቧል፡፡ ሶስተኛው ክፍልም በቀን ማለትም በአንባ አራዶን በኩል የራስ ሙሉጌታ ይገዙ ጦር
ተመድቧል፡፡ የዚህ ግንባር ጠቅላላ አዛዣ ራስ ካሳ ሀይሉ ናቸው፡፡ የመጀመሪያው መልሶ ማጥቃት
በከተሞች ማለትም በአዲግራት ፣ መቀሌና አድዋ ተደርጓል፡፡
 በዚህ ግንባር ጣሊያኖች ድል ቀንቷቸዋል ፡፡ ጦርነቱን በፍጥነት አልመራም በማለት ሞሰሎኒ ጀኔራል
ዲ ቦኖን በጀኔራል ፒየትሮ ባዶግሊዮ ቀይሮታል፡፡
 ይህ አዲሱ ተሿሚ ባዶግሊዩ በአለም አቀፍ ህግ የተከለከለውን የመርዝ ጋዝ በመጠቀም ግስጋሴውን
ለማፋጠን ችሏል፡፡ በዚህ ግንባር ብዙ ወጊያዎች የተከናወኑ ሲሆን በታሪክ ጎልቶ የሚነገርለት
በመጋቢት 31፤1936 የተደረገው የማይጨው ጦርነት ነው፡፡ በዚህ ጦርነት ንጉሰ ነገስቱ ሐይለ ስላሴ
ተካፋይ የነበሩ ሲሆን በኢትዩጵያውያን ሽንፈት ተጠናቋል ፡፡ ስለሆነም በሚያዝያ 1936 የጣሊያን
ጦር ደሴን መቆጣጠር ችሏል፡፡

የደቡብ ግንባር
ከላይ እንደተገለፀው በዚህ ግንባር ያለው የጣሊያን ጦር የሚመራው በጀኔራል ግራዝያኒ ሲሆን የኢትዩጵያ ጦር
ደግሞ በሁለት ክፍሎች ማለትም በደቡብ በራስ ደስታ ዳምጠው የሚመራ ሲሆን በደቡብ ምስራቅ ደግሞ
በደጀዝማች ነሲቡ ዘአማኑኤል የሚመራ ነው፡፡ ከሰሜን ግንባር በተቃራኒ በዚህ ግንባር ያለው የኢትዩጵያ ጦር
በአንፃሩ ዘመናዊና በወጣት አዛዣች የሚመራ ነበር ፡፡ ሁሉም አዛዦችና በስራቸው ያሉ የአባላት አዛዦች
ጣሊያንን በጀግንነት ቢዋጉም አሸናፊነት ዞሮ ዞሮ ለጠላት ሆነ፡፡ በመጋቢት 26 የራስ ደስታ ዳምጠው ጦር
ተሸንፎ ራሱም በመሸሸታቸው ጠላት ዶሎ ኦደን ተቆጣጠረ ፡፡ ከሳምንት በኃላ ጣሊያን ነገሌ ቦረናን
ተቆጣጠረ፡፡
በመጨረሻም በግንቦት 5፤1936 የጠላት ጦር አዲስ አበባን ተቆጣጠረ
ተግባር 4.4
 የጣሊያን ሰራዊት የኢትዩጵያን ጦር ድል ያደረገበትን ዋና ዋና ምክንያቶች ዘረዝሩ ?
 የኢትዩጵያ ጦር ከተሸነፈ በኃላ ጣሊያኖች የቅኝ ግዛት አስተዳደር መስርተዋል፡፡ እነዚህን
ግዛቶች መፃህፍትን በማንበብ ለክፍል ተማሪዎች ሪፖርት አቅርቡ ?
 የኢትዩጵያ አርበኞች እንቅስቃሴና የጣሊያን ተሸንፎ ከሀገር መውጣትን የሚተነትን
ጥናታዊ ፅሁፍ በማዘጋጀት ለክፍል ተማሪዎች አቅርቡ ? /የሴቶች ሚና ምን ነበር/ ?

4.4 የዘውዳዊ ስርዓቱን በመቃወም የተደረገ እንቅስቃሴና የደርግ መመስረት

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ከነፃነት በኃላ ንጉስ ነገስት ሐይለ ስላሴ ትኩረት በመስጠት የሸሟቸውና ስልጣን የሰጧቸው አብረዋቸው
ተሰደው ለነበርና እንዲሁም ከጣሊያን ጋር ለተባበሩ /ባንዳዎች/ ነበር፡፡ ይህም በእርሳቸው ወደ እንግሊዝ ሀገር
መሰደድ ለተበሳጩት አርበኞችና ለመሳፍንት ዘሮች ከፍተኛ ቅሬታ አስከትሏል፡፡ እንደ በላይ ዘለቀ፤ነጋሽ በዛብህ
እና ታከለ ወልደ ሐዋርያት ያሉ አርበኞች ንጉሱን በፀና ተቃውመዋል፡፡ በውጤቱም በላይ ዘለቀና ሌሎቹ በሞት
ተቀጥተዋል፡፡
የንጉሰ ነገስታዊውን ስርዓት የተቃወሙት ከላይ የተጠቀሱት አርበኞች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም የህ/ሰብ
ክፍሎች ማለትም ገበሬዎች፣ ጦር ሀይሉ፣ ተማሪዎች ወዘተ ነበሩ፡፡

ተግባር ፡- 4.5 የዘውዳዊው ስርዓት መሰረታዊ ችግሮች ምን ምን እንደሆኑ ከክፍል ተማሪዎች ጋር


ተወያይታችሁ ለክፍል ሪፖርት አቅርቡ፡፡

እስኪ ዋና ዋናዎችን ተቃውሞዎች እንመልከት ከጦር ሀይሉ የተነሳዉ ተቃውሞ በታህሳስ 13፤1960 በዋናነት
በሁለት ወንድማማቾች የተቀናበረው መፈንቅለ መንግስት ተሞክሯል፡፡ የክቡር ዘበኛ ሀላፊ የነበሩት ጀኔራል
መንግስቱ ነዋይና ወንድማቸው ግማርሜ ንዋይና ሌሎችንም የፖሊስና የፀጥታ ሀላፊዎችን በማስተባበር
ንጉሳዊ ስርዓቱን በማስወገድ ስልጣኑ በህገ መንግስት የተወሰነ ንጉስ ለማስቀመጥ ቢሞክሩም ከቤተ
ክርስቲያንና ከጦር ሀይል እንዲሁም ከአየር ሀይል ድጋፍ ባለማግኘታቸው መስራው ሳይሳካ ቀርቷል፡፡
በተጨማሪም ህዝቡን ቀድመው ማንቃትና ማስተባበር አልቻሉም ነበር፡፡ ምንም እንኳ የመፈንቅለ መንግስት
ሙከራው ሊከሽፍም ቀጣይ ለተነሳው የተሳካው የወታደሩ መፈንቅለ መንግስት እንዲትልቅ ግብዓት እንደነበር
ይነገራል፡፡

የገበሬዎች ተቃውሞ፡- በዋናነት ተቃውሞው የተነሳው በትግራይ፤ በጎጃምና በባሌ ገበሬዎች ሲሆን የንጉሳዊ
/ዘውዳዊ/ አስተዳደሩን አቅም ፈትኖ አልፏል፡፡

ተግባር ፡- 4.6
- ገበሬዎች ያመፁባቸው ዋና ዋና ምክንያት ምን ምን ነበሩ
- ይህ የገበሬዎች አመፅ በምን መንገድ እንደተከናወነና ውጤቱ ምን እንደሆነ መፅሀፍትን በማንበብ በቡድን
ዘገባ አቅርቡ ፡፡

የወያኔ አመፅ ከ 1942-1943፡- ይህ በትግራይ የተጀመረ ሲሆን በዋናነት በምስራቅ ትግራይ በራያና አዘቦ አካባቢ
ነው፡፡ የአመፁ መሪ ብላታ ሐይለ ማርያም ረዳ ሲሆኑ የአመፁ መነሻ ተብሎ የሚወሰደው የልማት ጥያቄ ፣
ጉቦን መቃወም ፣ የብሄርተኝነት ስሜትና ራስን በራስ የማስተደደር ፍላጎት መሆኑ ይታመናል፡፡ ንጉሳዊ
አስተዳደሩ በወሰደው ጨከን ያለ እርምጃ በጥቅምት 14፤1943 ተቃውሞው በሀይል ሊቆም ችሏል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የጎጃም ገበሬዎች አመፅ /1968/፡- የዚህ አመፅ አንዱ ምክንያት ተብሎ የሚወሰደው የደጅአዝማች ፀሀይ
እንቅስቃሴ አስተዳደር ብልሽነትና ውስን በተጨማሪም በ 1967 የተደረገው የቀረጥ ጭማሪ እንደመነሻ
ይወሰዳል፡፡ አመፁ በዋናነት ያተኮረው በሞጣና በደጋ ዳሞት ወረዳዎች ሲሆን ንጉሳዊ ስርዓቱ በወሰደው
እርምጃ በሀይል ሊቆም ችሏል፡፡

የባሌ ገበሬዎች አመት /1963 – 1970/ ፡- የዚህ አመፅ ምክንያቶች ተብለው የሚጠቀሱት
- የመልካም አስተዳደር ችግር
- የመሬት መነጠቅ
- የብሄራዊ ጭቆና
- የሀይማኖት አድሎ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

በተለይ የመሬት መነጠቅና በብዙ ስፍራዎች በተለይ ከሽዋ በመምጣት በባሌ መስፈራቸው ነዋሪው ሙስሊም
ማህበረሰብ በሂደት ባህሉን የማጣት ስጋት ፈጥሮበት ነበር፡፡ አመፁም በመጀመሪያው አመታት በተለይ
በኢልኬሬ አካባቢ የመራው ካሂን አብዲ ቢሆንም በኃላ ግን ዋቆ ጉቱ በዋናነት መርቶታል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ
ማዕከላዊ መንግስት በወሰደው እርምጃ በ 1970 አመፁ ሊገታ ችሏል፡፡

ተግባር፡- 4.6 እነዚህ የገበሬዎች አመፅ የመጡት ለውጥ ምን ይመስላችኋል


በንጉሳዊ አስተዳደሩ ላይ ምን አይነት ተፅዕኖ አሳድሯል ብላችሁ ታስባላችሁ

የተማሪዎች እንቅስቃሴ፤ በተለይ ከ 1950 ዎቹ ጀምሮ የቀድሞው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች
የሀገራቸው ኋላ መቅረት በአንፃሩ ደግሞ ገና ነፃ ከወጡ ጥቂት ጊዜ የሆናቸው የአፍሪካ ሀገሮች በመመልከት
ንጉሳዊ አስተዳደሩን መቃወም ጀምረዋል ፡፡ የራሳቸውንም ማህበር ማለትም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ
ተማሪዎች ህብረት ወይም በእንግሊዘኛ USUAA /Universty Students Uniun of Addis Abeba/ በሀገር
ውስጥ፤ በውጭም የስሜን አሜሪካ የኢትዩጵያ ተማሪዎች ህብረት /ESUNA/ Ethiopian Students Union
in North American እንዲሁም በአውሮፖ(USUE) The Ethiopian Unviersty Sudents Union In Europe
በማ ss ም ንጉሳዊ አስተዳደሩን ተቃውመዋል፡፡ በተለያዩ መጣጥፎችም ማለትም እንደ “ታገል”፣ “ታጠቅ”
የመሳሰሉ በማሳተም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ዉስጥ በሂደት ገብተዋል
በተለይ በ 1965 ከፖርላማዉ ፊት የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት መሬት ላራሹ /Land to the Tillers/
የሚል መፈክር አስምተዋል፡፡ ቀስ በቀስም ትግሉ ወደ መክረር ሄደ፡፡ ከ 1969 ጀምሮ የራስን እድል በራስ መወሰን
እስከ መገንጠል የሚለውን አጀንዳ በመያዝ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ንጉሳዊ አስተዳደሩም ይህን በመቃወም
የ USUAA መሪ የነበረውን ጥላሁን ግዛው ገሏል፡፡ በ 1970 መጀመሪያዎች ወራት የተማሪዎች አመ å
የተባባሰበትና የ DC-3 የመንገዶች አውሮኘላን እስከመጥለፍ የደረሰበት ጊዜ ነበር፡፡ በተለይ በወሎና በትግራይ
ከ 1972-1974 የነበረው ረሀብና ድርቅን በመቃወም ተማሪዎቹ አመፃቸውን ያፋፋሙበት የንጉሳዊ ስርዓቱም
ውድቀት እየተፋጠነ የመጣበት ጊዜ ነበር፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የ 1974 ቱ የህዝብ አብዮትና የንጉሳዊ ስርዓቱ መውደቅ


ከላይ በጥቂቱ እንደተገለፀው ንጉሳዊ ስርዓቱ በተለያዩ የህ/ሰብ ክፍሎች ውግዘት ሲደርስበት እንዲሁም
የ 1972/3 ድርቅ የስርዓቱን ውድቀት አፋጥኖታል፡፡ በተለይ በየካቲት 1974 የተለያዩ ተቃውሞ ሰልፎች ፣ የስራ
ማቆም አድማዎች የለውጥ ጥያቄዎች ሃገሪቱን ማጥለቅለቅ ጀምረዋል፡፡ ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ ታክሲ
ሹፌሮች በተለይ የጦር ሀይሉ የተለያዩ የለውጥ ጥያቄዎችን ይዘው ተነሱ፡፡ የመጀመሪያው የወታደሩ አመፅ
ተብሎ የሚታሰበው የ 45 ኛዉ ክ/ጦር በነገሌ ቦረና በጥር 12፤1974 የተደረገው የወታደሮች አመፅ ሲሆን
በመቀጠልም በኤርትራ የ 2 ኛዉ ክፍለ ጦር ሲሆኑ መሪዎቻቸዉን በማሰር የተለያዩ ህይወታቸውንና
ደመወዛቸውን የሚያሻሽሉ ጥያቄዎችን አንስተው ከስርዓቱ ጋር የመደራደር ሙከራ አድርገዋል፡፡ አመፁ
እየተባባሰ ሲመጣ የጠ/ሚኒስተር አክሊሉ ሀብተወልድ ካቢኔ በየካቲት 28/1974 በእንዳልካቸው መኮነን ተተክቶ
እስከ ሐምሌ 22፤1974 ብቻ ሊዘልቅ ችሏል፡፡ በተለይ በዚህ ጊዜ ይበልጥ የተደራጀ የነበረው ወታደሩ ቀስ በቀስ
ወደ ስልጣን ኮርቻ እየገሰገሰ የነበረበት ጊዜ ነው፡፡ በተለይ የወታደሩን ጥያቄ አስተባባሪ ቡድን (Armed forees
coordinating committee - AFCC) በዋናነት በኮረኔል አለም ዘውድ ተሰማ መቋቋም ለንጉሳዊ ስርዓቱ
መውደቅ አይቀሬነት አመላካች ነበር ፡፡ በመጀመሪያ ይህ ቡድን የንጉሳዊ ስርዓቱንና የእንዳልካቸውን ካቢኔ
ደጋፊ በመምሰል ተንቀሳቅሷል፡፡ በሰኔ መጀመሪያ ይህ ቡድን እንደገና መቋቋም አለበት በመባሉ ከተለያዩ
የሀገሪቱ የጦር ክፍሎች የተወጣው ወደ 120 እና በላይ የሚጠጉ ከሻለቃ በላይ ማዕረግ የሌላቸው ወታደሮች
ደርግ በሚል ስያሜ ራሳቸውን አደራጁ፡፡ ሻለቃ መንግስቱ ሐይለ ማርያምን ሰብሳቢ ሻለቃ አጥናፋ አባቱን
ደግሞ ም/ሰብሳቢ አድርገው ሾሙ፡፡ ቀስ በቀስ የቀድሞው ባለስለጣናት ህዝቡን በድለዋል በማለት በማሰር
ንጉሳዊ ስርዓቱን ሲያዳክም ከቆየ በኃላ በመጨረሻም በመስከረም 12፤1974 ንጉሱን ከስልጣን በማውረድ
የራሱን አንባገነን መንግስት መመስረት ችሏል፡፡

4.5 የደርግ መውደቅና የኢህአዴግ ወደ ስልጣን መምጣት


ደርግ ንጉሱን ከስልጣን ካወረደ በኃላ የልጅ እንዳልካቸውን ካቢኔ በማፍረስ በሚካኤል እምሩ የሚመራ ካቢኔ
አቋቋሞ በውስጥ ግን ስልጣኑን ራሱ ይዞ ቢመራም በዋናነት በጊዜው የደረጉ ሊቀመንበር በነበሩት በሌተናል
ጀኔራል ሚካኤል አንዶምና በምክትላቸዉ በሻለቃ መንግስቱ ሐ/ማሪያም መካከል በነበረው የስልጣን ሽኩቻ
ምክንያት ሰብሳቢው ተገድለዋል፡፡ ከዚህ በኃላም ቀጣዩ ሰብሳቢ ጀኔራል ተፈሪ ባንቲ እንዲሁም ሌሎች
ተገድለዋል ፡፡ ቀስ በቀስ የደርግ የስልጣን ኮርቻ ላይ ሻለቃ መንግስቱ መውጣት ችለዋል፡፡

ደርግ የመጀመሪያ ተግባሩ ውስጥ የሚካተተው ሀገሪቱ ውስጥ ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፎችና ተቃውሞዎች
እንዳየረደረጉ ማድረግ ነበር፡፡ በተጨማሪም ሌሎች ስር ነቀል የሚባሉ አዋጆች ማለትም መሬት ላራሹ
ቢያውጅም በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት ሊፈጠር አልቻለም፡፡ በተለይ ከኢትዩጵያ ህዝቦች አብዩታዊ ፖርቲ
(EPRP) ጋር በነበረው ግጭት ብዙ ወገኖች ከሁሉቱም ቡድኖች ሊገደሉ ችለዋል፡፡ በሀገሪቱ ተጨባጭ
የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ባለመረጋገጣቸው፤ሌሎች ተቃዋሚዎችም በሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ
ባለመፈቀዱ ከ 17 በላይ የታጠቁ ድርጅቶች ደርግን በመቃወም ተነስተዋል፡፡ በዋናነት በትግራይ የተነሳው
የትግራይ ህዝቦች ነፃ አውጭ ግንባር (TPLF) ነበር፡፡ በሂደትም አራቱ ድርጅቶች ማለትም የኢትዩጵያ ህዝቦች
ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (EPDM) (የአሁኑ ብኤዴን) ፣ የአሮም ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (OPDO) ፤

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የትግራይ ህዝቦች ነፃ አውጭ ግንባር (TPLF) እና የኢትዩጵያ የዲሞክራሲያዊ መኮንኖች አብዩታዊ ንቅናቄ
(EDORM) በጋራ በመሆን የኢትዩጵያ ህዝቦች አብዩታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ መሰረቱ፡፡
በግንቦት 28፤1991 ኢህአዴግ አዲስ አበባን በመቆጣጠሩ የደርግ መጨረሻ ውድቀት ሆነ፡፡

የክለሳ ጥያቄዎች
1. ለዘመናዊ የተማከለ የአጼ ግዛጽ ምስረታ አስተዋጽኦ ያደረጉ ነገስታት እነማን ናቸዉ? ዋና ዋና
ተግባሮቻቸዉን ዘርዝሩ፡፡
2. የሁለትዮሽ አስተዳደር ምን ገጽታች ነበሩት? ለተፈሪ መኮነን ገሮ መዉጣት ዋና ዋና ምክንያቶች ምን
ምን ነበሩ?
3. የፍጹማ ዘዉዳዊ ስርአቱ መለያ ባህርያት የምትሏቸዉን በመዘርዘር በእያንዳነዱ ሀሳቦች ዙሪያ
ተወያዩ፡፡
4. ጣልያን በ 1935 ኢትዮጽያን ለምን ወረረች? የጦርነቱ ዋና ዋና ግንባሮችን ዘርዝሩ፡፡
5. የዘዉዳዊ ስርአቱን በመቃዎም የተደርጉ ዋና ዋና እንቅስቃሴዎችን ዘርዝሩ፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ምዕራፍ አምስት

የአፍሪካ ታሪክ (እ.ኤ.አ በ 1880 ዎቹ)

የምእራፉ አላማዎች - ተማሪዎች ይህን ምእራፍ ካተናቀቁ በኃላ፤


- በቅኝ ዋዜማ የአዉሮፓዉያንን ሁኔታ ይረዳሉ
- በአፍሪካ የቅኝ ግዛት ምስረታና የአፍሪካዉያን የጸረ ቅኝ ግዛት ትግሎችን ያብራራሉ
- የቅኝ ግዛት ዉርሶችን ይዘረዝራሉ
- የአፓርታይድ ስርአት መገለጫዎችን ይናገራሉ
- የአፍሪካ አህጉራዊና ክፍለ አህጉራዊ ድርጅቶች አመሰራረትና አሰራርን ይገልጻሉ

5.1 አፍሪካ በቅኝ ግዛት ዋዜማ


በኢንዱስትሪው አብዩት ምክንያት እንግሊዝ አብዛኛውን የአፍሪካ የውጭ ንግድ እስከ 19 ኛው ክፍለ ዘመን
አጋማሽ ተቆጣጥራ ነበር ፡፡ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን ወደ አፍሪካ በታላላቅ የንግድ መርከቦቿ ማስገባት ችላ
ነበር ፡፡
ከ 1860 ዎቹ ጀምሮ የእንግሊዝ የብቸኛ ቁጥጥር እንቅስቃሴ በዋናነነት በፈረንሳይና በጀርመን የኢንዱስትሪ
ማደግ ምክንያት ተቀናቃኝ መነሳት ጀምሯል፡፡ በሀገራቸው ያለው ገቢያ እየሞላ ሲመጣ የኢንዱስትሪ
ውጤቶቻቸው የሆኑትን በዋናነት ልብሶች፤ አልኮልና የጦር መሳሪያዎችን ወደ አፋሪካ ማስገባት ጀመሩ ፡፡
በዚህም ምክንያት በነፃ ገቢያ (Free trade) ይልቅ በተወሰነ የይዞታ ክልል(protectionism) መንቀሳቀስ
የተመረጠ ነበር ፡፡ ይህም አዲሶቹ የኢንዱስትሪ ሀይላት የራሳቸው የሆኑ ግዛቶችን (Protected areas)
እንዲመሰርቱ ግፊት ፈጥሯል፡፡

ተግባር ፡-5.1 ከአፍሪካ ወደ አውሮፖ የሚላኩ ቁሳቁሶች ምን ምን ነበሩ ?


- ከአውሮፖ ወደ አፍሪካ የሚገቡ ሸቀጦች በአፍሪካ ላይ ምን ተፅዕኖ ያመጡ ይመስላችኃል?

በዚህም ምክንያት በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ ፈረንሳይ የንግድና የባህር ሀይል ጣቢያ
በሴኔጋል፣ ጊኒ፣ አይቮሪኮስት /ኮቲዲቫር/፣ ዳሆሚ፣ ጋቦን እና ማዳጋስካር አቋቋመች፡፡ ጀርመንም ከእንግሊዝ ጋር
በመፎካከር ከውህደቷ በኃላ ወደ አፍሪካ ፊቷን መልሳለች ፡፡
የአውሮፖውያን አፍሪካን ለመቀራመት የተደረገ እንቅስቃሴ በዋናነነት የሚመነጨው የአፍሪካን ተፈጥሮ
ሀብቶች እና ጥሬ ዕቃዎች ለመቀራመትና የኢንዱስትሪ ምርቶቻቸውን ወደ አፍሪካ ለመላክ ነበር፡፡ ዋና

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ዋናዎቹ የአፍሪካ ምርቶች የነበሩት የምዕራብ አፍሪካ የቅጠላ ቅጠል ዘይት፣ የዝሆን ጥርስ፣ ጎማ፣ ወርቅ
ማዕድን ይገኙበታል፡፡

የበርሊኑ ጉባኤ
ከላይ እንደተገለፀው እንግሊዝ በብቸኝነት የአፍሪካን ጥሬ ሀብት የመቀራመት ተግባር ሊቀጥል የቻለው እስከ
1860 ዎቹና በ 1870 ች ብቻ ነበር፡፡ የእንግሊዝ ፍላጎት የሌሎች አውሮፖ ሀገሮች ፍላጎትን መግታት ቢሆንም
በቀላሉ ሊሳካ አልቻለም፡፡ስለሆነም አውሮፓውያን እርስ በርስ ሳይጋጩና ሳይዋጉ አፍሪካን ለመቀራመት ዘዴ
መፈለግ ጀመሩ ፡፡
የአዲሷ ጀርመን ጠቅላይ ሚኒስተር የነበሩት አቶ ቮን ቢስማርክ የእንግሊዝን የብቸኛ የአፍሪካ ተጠቃሚነት
ከሚቃወሙ ዋነኛው ነበሩ ፡፡ በሳቸው አነሳሽነትም የአውሮፖ ሀገራትን በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን ስብሰባ
ጠሩ፡፡ ይህ የበርሊኑ ጉባኤ በመባል የሚታወቀው ከ 1884 – 1885 የተካሄደ ነው፡፡

ተግባር፡-5.2
- የበርሊኑ ጉባኤ ዋና ዋና አጀንዳዎች ምን ነበሩ ?
- የበርሊኑ ጉባኤ ውጤት ምን ነበር ?
- የስብሰባ ተሳታፊ ሀገራት እነማን ነበሩ ?

ስብሰባውን የተሳተፉ ሀገራት እንግሊዝ ፣ ጀርመን ፣ ፈረንሳይ ፣ አውስትራሊያ ፣ ሀንጋሪ ፣ ሩሲያ ፣ ቤልጅየም ፣
ሆላንድ ፣ ስፔየን ፣ ፖሩቹጋል ፣ ጣሊያን ፣ ዴንማርክ ፣ ስዊድንና የአቶማን ቱርክ ነበሩ፡፡ አሜሪካም ወደ
ስብሰባው ተጋብዛለች፡፡ አንድም የአፍሪካ ሀገር በዚህ ስለ አፍሪካ በሚወያየው ጉባኤ ላይ አልተጋበዘም፡፡
በጉባኤው በዋናነት የተነሱ ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፡፡
- ከአፍሪካ ጋር ስለሚደረግ ንግድ
- በአፍሪካ ወንዞች ስለሚደረገው ነፃ የጉዞ ጉዳይ
- ስለ አፍሪካ ህዝቦች ደህንነት ሁኔታ
- አውሮፖውያን አፍሪካን ቅኝ በሚገዙበት ጊዜ እርስ በርስ እንዳይጋጩ ስለመግታት ጉዳይ ሲሆኑ
የስብሰባው ተሳታፊዎች የበርሊን ስምምነት (General Act of Berlin) ተፈራርመዋል፡፡ በዚህም መሰረት
አንድ የአውሮፖ አገር በአፍሪካ ግዛት መያዝ የፈለገውን ቦታ ለሌሎች ማሳወቅ (Notification) እንዲሁም
ብቁ አስተዳደራዊ መዋቅር (Effective admnistration) መመስረት ይጠበቅበታል፡፡ በዚህም ምክንያት
ከበርሊኑ ጉባኤ በኃላ የአፍሪካ መቀራመት በመፍጠኑ በ 1900 ከኢትዩጵያና ላይቤሪያ በስተቀር ሁሉም
የአፍሪካ ሀገሮች በቅኝ ግዛት አስተዳደር ስር ወደቁ ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

5.2 የቅኝ ግዛት ምስረታና ቀደምት የአፍሪካውያን ፀረ ቅኝ ግዛት ትግል

የፈረንሳይ የቅኝ ግዛት ምስረታና የአፍሪካውያን ፀረ ቅኝ ግዛት ትግል


የፈረንሳዩች የመጀመሪያ ወረራ /ማረፊያ/ በዳካርና ሴይንት ሊውስ ሲሆን ቀስ በቀስ ወደ ሴኔጋል ሸለቆ
በ 1850 ዎቹና 1860 ዎቹ ተስፋፍቷል፡፡ በሂደትም መጠነ ሰፊ ቅኝ ግዛት በምዕራብ አፍሪካ በማድረግ
ከ 1870 ዎቹ ጀምሮ መጠነ ሰፊ ዘመቻ ወደ ሴኔጋልና ባማኮ በመስፋፋት የንግድ መስመራቸውን መስርተዋል፡፡
በመቀጠልም በ 1894 ትንቡክቱን በ 1896 ሳይን ተቆጣጥረዋል፡፡ ነገር ግን ወደ ሀውሳላንድ የመገስገሳቸው ጉዞ
በእንግሊዞች ተገቷል፡፡ በፈረንሳይና በእንግሊዝ መካከል ተደጋጋሚ ግጭቶች በናይጀሪያና በጎልድ ኮስት
ተከስቷል፡፡

የአህመዱ ሴኩና የሳሞሪ ቱሪ ፀረ ቅኝ ግዛት ትግል


በምዕራብ ሱዳን የፈንሳዩችን መስፋፋት በዋናነት የተቃወመው አህመዱ ሴኩ ሲሆን በመጀመሪያ
ተቃውሞውን በጦርነት ሳይሆን በዲኘሎማሲ ለመግታት ሞክሯል፡፡ ፈረንሳዩች የቱክሎርን ግዛት
እንዲያስተዳድር እንዲፈቅዱለት ቢያግባባም ስምምነቱን በመጣስ በ 1883 ጀምሮ በቱክሎር መስፋፋታቸውን
ቀጥለዋል፡፡ በቀጣይም የፈረንሳይ ቱክሎር ስምምነት በ 1887 ተፈርሟል፡፡ ነገር ግን በ 1889 ፈረንሳዩች
የተክሎርን ግዛት ጠረፍ ግዛቶች ተቆጣጥረዋል፡፡ ከዚህ በኃላ በአህመዱና በፈረንሳይ ጦር መካከል ተከታታይ
ጦርነቶች ቢከናወኑም በመጨረሻ በ 1893 ድሉ ለፈረንሳዩች ሊሆን ችሏል፡፡

ተግባር ፡5.3 የአህመዱ ኬኩ መሸነፍ ምክንያቶች ምን ይመስላችኃል?

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሁለተኛውና ጠንካራው ተቃውሞ የተደረገው በሳሞሪ ቱሪ ሲሆን የተካሄደውም በማዲንካ ግዛት ነው፡፡ ሳሞሪ
ከ 1870 ዎቹ ጀምሮ ከኒጀር ወንዝ ምንጭ እስከ የላይኛው ቮልታ ሸለቆ ድረስ ያለውን ህዝብ አስተባብሮ
መምራት ችሎ ነበር ፡፡ በስሩም ወደ 30‚000 የሚጠጋ ሰራዊት ነበረው ፡፡ በተለይም የሚዲንካ ብሄርተኝነትን
በመጠቀም የጥንቷን ማሊ ዝና በመጠቀም ህዝቡን ማስተባበር ችሎ ነበር፡፡ በ 1887 ከፈረንሳዩች ጋር
ስምምነት ቢያደርግም እንደተለመደው ፈረንሳዩች ቃላቸውን በማጠፍ በ 1891 ግዛቱን ወረውበታል ፡፡
በመጨረሻም በ 1898 የሳሞሪ ጦር ሙሉ በሙሉ ሊሸነፍ ችሏል፡፡ በአጠቃላይ በምዕራብ አፍሪካ የተደረገው
የፀረ ግኝ ግዛት ትግል ውድቀት መሰረታዊ ምክንያቶች የፀረ ቅኝ አገዛዝ ትባሉ ህብረት አለመኖርና
የአውሮፖውያን የመሳሪያ የበላይነት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

የእንግሊዝ የቅኝ ግዛት ምስረታ


በ 1870 ዎቹ እንግሊዝ በምዕራብ አፍሪካ ጠረፍ የንግድ ቀጠናዎችን ማቋቋም ጀመረች፡፡ ይህም የንግድ ቀጠና
የቅኝ ግዛት እንቅስቃሴውን በገንዘብ በመደገፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት በ 1874
እንግሊዝ አሳንቴንና የፋንቴ ግዛቶችን ለመቆጣጠር ችላለች፡፡ ከ 1895-1896 የአሳንቴን ግዛት እንደገና ሙሉ
በሙሉ መቆጣጠር ችላለች፡፡ በ 1900 እንግሊዞች በጦርነት መሸነፍ ጫፍ ቢደርሱም አጋዥ ጦር ከናይጀሪያና
ከሴራሊዩን በማስመጣት ድል ማድረግ ችለዋል፡፡ ከዚህ በኃላ የጎልደኮስትን ቅኝ ግዛት አውጀዋል፡፡

ተግባር፡-5.4
- ምዕራብ አፍሪካ ከቅኝ ግዛት በፊት በምን ይታወቅ ነበር ?
- እንግሊዝ ምዕራብ አፍሪካን ለመቆጣጠር የተቀጠመችባቸው መንገዶች ምን ምን ናቸው ?

ከላይ እንደተገለፀው እንግሊዝ የናይጀሪያን አብዛኛውን ግዛት ከ 1892-1902 መቆጣጠር ችለዋል፡፡ የዩሩባላንድ
አብዛኛው ክፍልም ከ 1892-1893 ባሉት አመታት በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ፈረንሳዩች እንደጋጠማቸው ሁሉ
እንግሊዞችም ከፍተኛ ተቃውሞና ጦርነት በናይጀሪያ አገጥሟቸዋል፡፡

እንግሊዞች ግብፅን ከተቆጣጠሩ በኃላም የቅኝ የግዛት ማስፋፋታቸውን ወደ ሱዳን አዙረዋል፡፡ ከ 1877 እስከ
1879 ሳሙኤል ቤከር የሱዳን ጠቅላይ ገዥ ተደርጎ ተሹሟል፡፡ 1879 በጀኔራል ጎርደን ተተክቷል፡፡ በሱዳንም
በተመሳሳይ መልኩ በሙሀመድ አህመድ ኢብን አብደላ /አል ማህዲ/ የሚሰራ ፀረ ቅኝ ግዛት ትግል
አጋጥሟቸዋል፡፡ በተለምዶ የማህዲስት እንቅስቃሴ በመባል ይታወቃል፡፡ ነገርግን በ 1898 አምዱር ማን
እንግሊዞች ድል በማድረግ ሱዳንን መቆጣጠር ችለዋል፡፡

የቤልጅየምና የጀርመን በቅኝ ግዛት ምስረታው መከሰት

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የቤልጅየሙ ንጉስ የነበረው ሊዩፖልድ 2 ኛ በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛው አጋማሽ በአፍሪካ የግሉ ቅኝ
ግዛት ለመመስረት ከፍተኛ ፍላጎት ነበረው፡፡ ስለሆነም መእከላዊ አፍሪካናን ለማሰልጠን በሚል ሰበብ የኮንጎ
ሸለቆን የሚሰልል ስታንለይ የተባለ ግለሰብ 1879 ወደ ኮንጎ ላከ፡፡ በመቀጠልም ከፍተኛ ወታደራዊ ዘመቻ
በማድረግ ኮንጎን /የድሮዋን ዛየር/ መቆጣጠር ቻለ፡፡ ጀርመንም በ 1874 ደቡብ ምዕራብ አፍሪካን /ናሚቢያን/
በመቆጣጠር ዜጎቿን ማስፈር ችላለች፡፡ በ 1885 ጀርመን የጀርመን ምዕራብ አፍሪካ ግዛቷን የቶጎላንድንና
ካሜሮንን በመያዝ አውጃለች፡፡ በምስራቅ አፍሪካም ሰፊ መሬት በመያዝ የታንጋኒካ ቅኝ ግዛትን መስርታለች፡፡
ከደቡብ ምዕራብ አፍሪካ በተለይ ጀርመኖች በምዕራብ አፍሪካና በታንጋኒክ ቅኝ ግዛት በዋናነት የመሰረቱት
በተከታታይ ስምምነቶች ከባህላዊ መሪዎች ጋር በማድረግ ነበር፡፡ እንደ ፈረንሳይና እንግሊዝ ጀርመኖች
በተለያየ ቦታ ከፍተኛ የፀረ ቅኝ ግዛት ትግል ተጋፍጠዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ በዋናነት የሚገለፀው የማጅ ማጅ
አመፅ ነበር፡፡

ተግባር፡- 5.5
-ማጅ ማጅ የሚለው ሀሳብ ምን ማለት ነው ?
-የማጅ ማጅ አመፅ የትና በምን ምክንያት ተደረገ ? ውጤቱስ ምን ነበር ?

የማጅ ማጅ አመፅ የተደረገው በታንጋኒክ ሲሆን መሰረታዊ ምክንያቱም የሚከተሉት ናቸው


-ጀርመኖች በህዝቡ ላይ የጣሉት ከባድ ቀረጥ
-ሰፋፊ የእርሻ ማሳዎችን በግዳጅ የነፃ ጉልበት ህዝቡ እንዲያለማ ማድረጋቸው ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ይህ 1905 የተመሰረው አመፅ በጀርመኖች ከፍተኛ ጭካኔ ቢቀለበስም የራሱ ውጤቶች ነበሩት፡፡ አንደኛው
ውጤት ጀርመኖች የቅኝ ግዛት ፖሊሲያቸውን እንዲያሻሽሉ ሲያስገድድ ሁለተኛው ደግሞ ለቀጣይ የታንጋኒክ
ህዝቦች ትግል የራሱን አሻራ አኑሮ አልፏል፡፡
ወደ ስሜን አፍሪካ ስናተኩር ከላይ እንደተጠቀሰው ግብፅ በ 1879 በእንግሊዝ ቁጥጥር ስር ከዋለች በኃላ
በቀጣይ አመታትም ሱዳንን መቆጣጠር ችላለች ፡፡ ቱኒዥያና ሞሮኮም በፈረንሳይ እጅ ሊወድቁ ችለዋል፡፡
ጣሊያንም በ 1911 ሊቢያን መቆጣጠር ችላለች፡፡
ፖርቹጋሎችም የራሳቸውን ቅኝ ግዛት የመሰረቱ ሲሆን ለማጠቃለል ያክል በዋናነት የእንግሊዝ ፣ ፈረንሳይና
የፖርቱጋል ቅኝ ግዛቶችን በሚከተለሙ መልኩ ቀርበዋል
የእንግሊዝ ቅኝ ግዛቶች
- ናይጀሪያ - ደቡብና ሰሜን ሮዲዥያ
- ጎልድኮስት /ጋና/ - ንያሳላንድ
- ሴራሊዩን - የእንግሊዝ ቤቹአናላንድ
- ጋምቢያ - የእንግሊዝ ሶማሊላንድ
- ኡጋንዳ - ዛንዚባርና ፔምባ
- ኬንያ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች
- ሴኔጋል - ጋቦን
- አይቬሪኮስት - ኮንጎ
- ጊኒ - ኢባንጊሻሪ (የአሁን ማኢከላዊ አፍሪካ
- ዳሆሚ ሪፐብሊክ)
- ሱዳን - ቻድ
- ማሊ - ማዳካስከር
- ስሜናዊ ቮልታ - ኮሞሮስ ደሴት
- የፈረንሳይ ሶማሊ ላንድ

የፖርቹጋል ቅኝ ግዛቶች
- አንጎላ - የቤልጅየም ኮንጎ በቤልጅየም
- ሞዛንቢክ - የኢጣሊያ ሶማሊላንድ
- ጊኒ ሲሆኑ - የጣሊያን ኤርትራ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
- ሳኦ ቶሜ /ስፔየን/

5.3 የአፍሪካውያን ለነፃነት የተደረገ ትግል


አፍሪካን ነፃ የማውጣት ግፊት የተጀመረው ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በፊት ቢሆንም ይበልና ውጤታማ
የሆነው ግን ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ፍፃሜ በኃላ ነው፡፡ በተለይ ቀደምት የነበረው የፖን አፍሪካ ንቅናቄ
አፍሪካውያን ራሳቸውን ወደ ነፃነት ለሚያደርጉት ጉዞ እንደ መነሻ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡

ተግባር ፡- 5.6
- ፖን አፍሪካን ንቅናቄ የትና እንዴት በማን ተመሰረተ ?
- መፃህፍትን በማገላበጥ የፖን አፍሪካን የተለያዩ ጉባኤዎችን አጀንዳዎቻቸውን ዘርዝሩ ?
- የፖን አፍሪካን ታዋቂ መሪዎች እነማን ነበሩ ?

በሁለተኛው የአለም ጦርነት ተዋግተው የተመለሱ የአፍሪካ ወታደሮች ከጦርነት መልስ በነጮች ለመገዛት
ዝግጁ አልነበሩም፡፡ ህዝቡንም ስለ ነፃነት ማነሳሳት ችለዋል የአፍሪካ ምሁራንም ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡
ምንም እንኳ በቅኝ ገዥዎቻቸው የሰለጠኑና የነሱን ቢሮክራሲ ለማስተዳደር የተመደቡ ቢሆንም ቀስ በቀስ ግን
የአፍሪካን የነፃነት ትግል በመምራት ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡ በጋና /ጎልድኮስት/ የተባበሩት የጎልድ ኮስት
ኮንቬክሽን (United Goldcoast convention) የተባለውን ድርጅት በመልቀቅ በ 1949 ክዋሜ ንኩርማህ
ኮንቪክሽን ፒውፒልስ ፓርቲ (convention people’s party) በመመስረት በ 1960 ጎልድኮስትን ነጻ ለማውጣት
ችሏል፡፡ ቀስ በቀስም ሴራሊዩን በ 1961፤ ጋምቢያ በ 1970 ነፃ ወጥተዋል፡፡
ግብፅ በ 1956 ነፃነቷን ተቀዳጅታለች፡፡ በኬንያም በጆሞ ኬንያታ የሚመራው የነፃነት ትግል ፍሬ አፍርቶ
በ 1963 ኬንያ ነፃነቷን ማግኘት ችላለች፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ነፃ መውጣት እንቅስቃሴ ከ 1950 ዎቹ ጀምሮ በሰላማዊ መንገድና በጦርነት መከናወን
ችሏል፡፡ ስለሆነም ቱኒዥያ በሀቢብ ቡርጊባ መሪነት በ 1956 ነፃ ስትወጣ አልጀሪያ ደግሞ በአህመድ ቤን ቤላ
መሪነት በ 1962 ነፃ ወጥታለች፡፡ የሁለቱ ሀገሮች ነፃነት በዋናነት የተከናወነው በረጅምና በከባድ ጦርነት በማለፍ
ነበር፡፡ በተለይም በ 1960 ዎቹ የአፍሪካ አመት (Year of africa) በመባል ይታወቃል፡፡ ምክንያቱም አብዛኛው
ሀገሮች ማለትም እንደ ካሜሮን፣ ቻድ፣ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ወዘተ ነፃ መውጣት ችለዋል፡፡ በርግጥ
ከ 1960 ዎቹ በኃላ ዘግየት ብለው ነፃ የወጡ ሀገሮች መካከል አንጎላ በ 1975 ትገኝበታለች፡፡ ደቡብ አፍሪካም
ከአፖርታይድ ስርዓት ማክተም በኃላ በ 1994 አዲሱን ጥቁር ኘሬዜዳንት ኔልሰን ማንዴላ ኘሬዜዳንት በመሆኑ
ከአፖርታይድ ስርዓት ነፃ ወጥታለች፡፡

5.4 የቅኝ ግዛት ውርሶች


ቅኝ ግዛት ከበጎ ይልቅ መጥፎ ጠባሳ ጥሎ እንዳለፈ ብዙ የታሪክ ፀሀፊዎች አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ባህልና ቅርፅ
እንዲሁም የተፈጥሮ ሀብቶች ተሟጥጠዋል፡፡ አፍሪካውያንም ከሰው በታች ሆነው በገዛ ሀገራቸው እንደ
እንስሳ በመቆጣጠር ለነጮች ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ የሀገሪቱም ኢኮኖሚ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ቅኝ
ገዥዎች ምንም አይነት ኢንዱስትሪ በአፍሪካ እንዳይቋቋም በማገዳቸው ለአፍሪካ ኃላቀርነት ዋናው መንስኤ
ቅኝ ግዛት መሆኑ ይታመናል፡፡

በፖለቲካው ረገድም ከፍተኛ ጉዳት እንዳስከተለ ይታመናል፡፡ በተለይ በዘፈቀደ የተሰማሩት የአፍሪካ ደንበሮች
ከነፃነት በኃላ በብዙ ሀገሮች ለርስ በርስ ጦርነት ዋነኛ መንስኤ ለመሆን በቅተዋል፡፡
በባህልም ረገድ የአፍሪካ ባህል የመነመነበትና በአንዳንድ ቦታዎችም ፈፅሞ የጠፋበት ሁኔታ ነበር፡፡

ተግባር፡- 5.7
-የቅኝ ግዛት በጎ ጎኖች ከሚባሉት ውስጥ ጥቂቶችን ዘርዝሩ ?
-ከላይ ከተቀሱት በተጨማሪ የቅኝ ግዛት ማህበራዊ ፣ ባህላዊ ፖለቲካዊ ተፅዕናዎችን ዘርዝሩ?
-በቅኝ ግዛት ሰበብ ከነፃነት በኃላ የተከሰቱ የድንበር ጦርነቶችን ዘርዝሩ ?

5.5 የአፓርታይድ ስርዓት በደቡብ አፍሪካ


የአፓርታይዝ ስርዓት በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ ደረጃ የደረሰው በ 1958 ቱ ምርጫ የናሽናሊስት ፖርቲ ስልጣን
ላይ ከወጣ ጀምሮ ነው፡፡ ፖርቲው በጥቁሮችና በነጮች መካከል ግንኙነታቸውን በሚከተለው መልኩ ወስኗል፡፡
- ጥጥሮች መቸ ፣ በምን ክፍልና ወደ ምን መጓዝ እንዳለባቸው
- ጥቁሮች ምን አይነት ስራ እንደሚሰሩ፤ የት እንደሚኖሩ
- የስዓት እላፊ፣ እገዳዎችን ቅጣቶች
- የሚማሩበት ት/ቤት የሚሄዱበት መኪና ወዘተ ከነጮች ጋር እንዳይደባለቁ ተለይቷል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

በዚህ ከፋፋይ ስርዓት ምክንያት በተለያየ ሰበብ በቀን እስከ 1000 ጥቁሮች በእስር ለመዳረግ በቅተዋል፡፡
ቤተክርስቲያናት ሳይቀሩ የጥቁርና የነጭ በመባል ተከፍለዋል፡፡ በየቦታው ለውሾትና ለጥቁሮች የተከለከለ የሚሉ
ባነሮች የተለመዱ ሆነዋል፡፡ ሌሎች ብዙ ከፋፋይ ህጎችም ተደንግገዋል፡፡ ክፋቱ መከፋፈል ብቻ አይደለም
ይልቁንም ጥቁሮችን በራሳቸው ሀገር ተረግጠው ተንቀውና ተጨቁነው እንዲኖሩ ማድረጋቸው የስርዓቱን
አስከፊነት ያመላክታል፡፡

ተግባር፡- 5.8
-ስለ አፖርታይድ የምታውቁትን ከክፍል ጓደኞቻቸው ጋር በመወያየትለመምህራቸሁ ተናገሩ ?
-አፖርታይድን በዋናነት የተዋጉ መሪ ማን ነበሩ ? ትግላቸውስ ምን ይመስላል?

የመጀመሪያው የጥቁሮች ፖርቲ የሆነው የአፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ (ANC) የተመሰረተው በ 1912 ሲሆን
ከምስረታው ጀምሮ አፓርታይድን በፅናት ተዋግቷል፡፡ የ ANC ትግል ውጤታማ የሆነው በኔልሰን ማንዴላ
ሲሆን ስርዓቱን በመቃወም ለ 27 ዓመታት ለእስር ተዳርገው ነፃ ከወጡ ከ 1994 በኃላ የጥቁር አፍሪካ
የመጀመሪያው ኘሬዜዳንት ሲሆኑ የስርዓቱ ማብቃት ተበስሯል፡፡

5.6 የአህጉራዊና ክፍለ አህጉራዊ ድርጅቶች ምስረታ


የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት /አአድ/ የተመሰረተው እ.ኤ.አ በ 1963 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ
መሪዎች ስብሰባ ነው፡፡ አአድ የተመሰረተው የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ትግል ህብረት ለመፍጠርና ትግሉን ለማፋጠንና
ለማቀናጀት ነበር፡፡ ለአአድ መወለድ አስተዋፅኦ ያደረጉ ዋና ዋና ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
እነሱም፡-
1. ከ 1945 ዓ.ም ጀምሮ የመላው አፍሪካ ንቅናቄ በአፍሪካ ውስጥና በአፍሪካ መሪዎች አዕምሮ መወለድና
ማደግ
2. በወቅቱ ነፃ የነበሩ የአፍሪካ መንግስታት ጉባኤ
3. የመላው አፍሪካ ህዝቦች ጉባኤዎች ናቸው፡፡

በ 1945 በእንግሊዝ አገር ማንቸስተር ከተማ በተካሄደው 5 ኛው የመላው አፍሪካ ጉባኤ ከአፍሪካ ምድር
ተወክለው በሄዱ ወጣት ምሁራን የበዙበትና ከቀደሙት ጉባኤዎች ጋር ሲነፃፀር ንቅናቄውን አንድ ወደ ፊት
በማራመድ አዲስ ምዕራፍ የከፈተነት ነበር ለማለት ይቻላል፡፡
የጉባኤው ዋነኛ አጀንዳ የብሄራዊ ነፃነት ትግል ነበር፡፡ ስብሰባውን ተካፍለው ወደየአገራቸው የተመለሱ
የወደፊቷ ነፃይቱ የአፍሪካ መሪዎች በአዕምሮአቸው ሰንቀውና ወስነው የመጡት በማንኛውም መንገድ
አገራቸውን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት ለመታገል ነበር፡፡ የመላው አፍሪካ ሐሳብንም ወደ አፍሪካ ምድር
አመጡ፡፡ ይህ ማለት ወደ አፍሪካ አንድነት ድርጅት የተደረገው ረጅም ጉዞ የመጀመሪያው እርምጃ
የተጀመረበት ነው፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

አአድ ከመመስረቱ በፊት ማለት ከ 1958-1961 ዓ.ም ድረስ በወቅቱ ነፃ የነበሩ የአፍሪካ መንግስታት አራት
ተከታታይ ጉባኤዎችን አካሂደዋል፡፡
እነሱም፡-
1. የመጀመሪያው ጉባኤ በአክራ /ጋና/ በ 1958 የተካሄደ
2. ሁለተኛው በአዲስ አበባ በተመሳሳይ በ 1958 ዓ.ም
3. ሶስተኛው በሊዩፖልድቪል /ኮንጎ/ በ 1961 ዓ.ም የተካሄዱት ናቸው፡፡

ስምንት የአፍሪካ ነፃ መንግስታት ማለትም ኢትዩጵያ ፣ ላይቤሪያ ፣ ጋና ፣ጊኒ ፣ ግብፅ ፣ ሞሮኮ ፣ ሊቢያና
ቱኒዚያ በሚያዝያ 1958 ዓ.ም በጋና ዋና ከተማ አክራ የመጀመሪያውን የአፍሪካ መንግስታት መሪዎች ስብሰባ
አደረጉ፡፡ በቀጣዩቹ ሶስት ጉባኤዎች አዲስ ነፃ የሚወጡ አገሮች የተሳታፊ መንግስታትን ቁጥር እያሳደገው
ሄዷል፡፡ በእነዚህ ጉባኤዎች የአፍሪካ መንግስታት የፀረ-ቅኝ አገዛዙን ትግል ለማሳለጥና የነፃነት ሂደቱን
ለማፋጠን እጅግ ተቀራርበው መስራት የጀመሩበት ነበር፡፡ ለነፃነት በመታገል ላይ የነበሩ ህዝቦችን ጥረት
በመደገፍ የኘሮፖጋንዳ ፣ ዲኘሎማሲና የፋይናንስ ድጋፍ ሰጥተዋል፡፡ ይህም የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ
ሂደትን አንድ ተጨማሪ እርምጃ ወደፊት ወስዶታል፡፡
ሌላው ለአ.አ.ድ ምስረታ ከረዱ ሁኔታዎች አንዱ የመላው አፍሪካ ህዝቦች ጉባኤ ነው፡፡ ይህ ጉባኤም የፀረ ቅኝ
አገዛዝ ትግሉን ለማጠናከር ረድቷል፡፡ እ.አ.አ ከ 1958-1961 ዓ.ም ድረስ ሶስት የመላው አፍሪካ ህዝቦች
ጉባኤዎች ተደርገዋል፡፡
እነሱም፡-
1. የመጀመሪያው የመላው አፍሪካ ህዝቦች ጉባኤ በታህሳስ ወር 1958 በአክራ /ጋና/ ተካሄደ
2. ሁለኛው ጉባኤ በጥር 1960 በቱኒስ /ቱኒሲያ/ ተሰበሰበ ፡፡
3. ሶስተኛው በመጋቢት 1961 በካይሮ /ግብፅ/ ተደረገ፡፡

የአ.አ.ድ ስኬቶችና ድክመቶች


የአ.አ.ድ ስኬቶች
ሀ/ በአፍሪካ ችግሮች ላይ መሪዎች በጋራ እንዲመክሩ እንደመድረክ አገልግሏል፡፡
ለ/ በአለም መድረክ ፊት የአፍሪካውያን ድምፅ በመሆን አገልግሏል፡፡
ሐ/ አፍሪካውያን እርስ በእርስ እንዲቀራረቡና የመላው አፍሪካ መርህ ህዝባዊ ተቀባይነት እንዲያገኝ ረድቷል፡፡
መ/ የአፍሪካ ነፃነት እንዲሳካ ውጤታማ እገዛ አድርጓል፡፡
የአአድ ግንባር ቀደም ስኬት ተደርጎ የሚወሰደው ለነፃነት የተደረገውን ትግል በመርዳት ለውጤት ማብቃቱ
ነው፡፡ አአድ መጀመያ ከአዲስ አበባ ጽ/ቤቱ የነፃነት ትግሉን ሲያስተባብር ነበር፡፡ በኃላ ደግሞ ይህንኑ ጉዳይ ብቻ
የሚከታተል ኮሚቴ በሉሳካ /ዛምቢያ/ አቋቋመ፡፡ አአድ ቅኝ አገዛዝንና አፖርታይድን ከአፍሪካ እንዲገረሰሱ
ጠንካራና ውጤታማ ድጋፉን እንደ አፍሪካ ብሄራዊ ም/ቤት /ደቡብ አፍሪካ/ ለመሳሰሉ ታጋይ ድርጅቶች
አድርጓል፡፡
የአአድ ድክመቶች
ሀ/ ብዙ የአፍሪካ አገሮችን ክፋኛ የጎዱ የእርስ በእርስ ጦርነቶችን ጣልቃ በመግባት ለማስቆም አለመቻሉ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ለ/ በብዙ የአፍሪካ አገሮች ህጋዊ መንግስታትን በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን ሲያስወግዱ ምንም
ማድረግአለመቻሉ፡፡
ሐ/ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን በአፍሪካ ያሉ የኢኮኖሚ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የገንዘብ
አቅምየሌለው መሆኑ ፡፡
መ/ አአድ በአፍሪካ መንግስታት መካከል የሚነሱ ግጭቶችን የሚፈታበት ፍ/ቤት የሌለው መሆኑ ናቸው፡፡

የአፍሪካ ክፍለ አህጉራዊ ድርጅቶች


የምዕራብ አፍሪካ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ /ኢኮዋስ/ Economic community of west African states-
ECOWAS)

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

በቅኝ ግዛት ዘመንና በቅኝ ግዛት ማግስት አፍሪካን ላጋጠማት የአውሮፖውያን ጫና ለመቀነስና ለመቋቋም
ታስበው ከተደራጁት አያሌ ክፍለ አህጉራዊ ትስስሮች መካከል አንዱ የምዕራብ አፍሪካ መንግስታት የኢኮኖሚ
ማህበረሰብ ወይም በአጭሩ ኢኮዋስ እየተባለ የሚጠራው ክፍለ-አህጉራዊ ድርጅት ነው፡፡
እ.አ.አ በ 1975 ዓ.ም በናይጀሪያ ሌጎስ ከተማ ላይ በተደረገው የመሪዎች ስብሰባ በተደረሰው ስምምነት
ተመስርቶ እ.አ.አ ከ 1977 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ ስራ ጀመረ ፡፡ አስራ ስድስት አባል መንግስታትን በአባልነት ያቀፈ
ትልቅ ማህበረሰብ ነው፡፡ እነሱም ቤኒን ፣ ቡርኪናፋሶ ፣ ኬኘቨርዴ ፣ ኮትዲቫር ፣ ጋምቢያ ፣ ጋና ፣ ጊኒ ቢሳው ፣
ላይበሪያ ፣ ማሊ ፣ ሞርታኒያ ፣ ኒጀር ፣ ናይጀሪያ ፣ ሴኔጋል ፣ ሴራሊዩንና ቶጎ ናቸው ፡፡
ኢኮዋስ የእራሱ ፍርድ ቤትና አምስት የተለያዩ ኮሚሽኖች አሉት ፡፡ እነሱም
1. የንግድ ፣ የቀረጥ ፣ የስደተኞች ፣ የገንዘብና የክፍያ ጉዳይ ኮሚሽን
2. የኢንዱስትሪ ፣ እርሻና የተፈጥሮ ሀብት ጉዳይ ኮሚሽን
3. የትራንስፖርት ፣ መገናኛና ኢነርጅ ጉዳይ ኮሚሽን
4. የማህበራዊና ባህላዊ ጉዳይ ኮሚሽን
5. የአስተዳደርና ፋይናንስ ጉዳይ ኮሚሽን ናቸው፡፡

የደቡባዊ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ ሳድክ /Southern Africa Development Community SADC/
በቅኝ ግዛት ዘመን የደቡባዊ አፍሪካ አገሮች ከሌላው የአፍሪካ ክፍለ-አህጉራት በተለየ ሁኔታ በፖለቲካና
በኢኮኖሚ የተሳሰሩ ነበሩ፡፡ ለደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ ወርቅና አልማዝ ማእድናት ፣ ለስሜን ሮዴዢያ /ዛምቢያ/
የመደብ ማዕድን ፣ በደቡብ ሮዴዢያ /ዚምባቡዌ/ ለተመሰረተው ግዙፍ የትምባሆ እርሻ የሚበቃ ሰራተኛ
ከየአገራቱ በበቂ መጠን ማግኘት ስለማይቻል የተፈጠረውን የሰው ሀይል እጥረት ለመሸፈን ቅኝ ገዥዎች
ከጎረቤት ቅኝ ግዛቶቻቸው ሰው በመውሰድ ይጠቀሙ ነበር፡፡

ተግባር፡-5.9
-ተማሪዎች በደቡባዊ አፍሪካ አካባቢ ዋነኛዋ ቅኝ ገዥ አገር ማን ነበረች ?

በአካባቢው የሚካሄደው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ፣ የጉልበት ሰራተኛ ምልመላና የሰው ከቦታ ቦታ ዝውውሩ
እንዲሁም የሰራተኞች ክፍያ ሁኔታ በአካባቢው የነበሩትን ቅኝ ግዛቶች በኢኮኖሚና በፖለቲካ እንዲተሳሰሩ
አደረገ፡፡ ይህ ቀደም ያለ የትብብር ተሞክሮ ዘላቂ የሆነ የትብብር ባህልን በአካባቢው ፈጠረ፡፡ አንፃራዊ የሆነ
የትራንስፖርት ትስስር /በዋናነት የባቡር ግንኙነት/ መኖር የኢኮኖሚ ትስስር በክፍለ አህጉሩ ቀድሞ
እንዲመሰረት ከረዱ ምከንያቶች አንዱ ነበር፡፡
በቅኝ ግዛት ዘመን የነበረው ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ትስስር ከነፃነት በኃላ በተመሰረተው ኢኮኖሚያዊ ትብብር
/ትስስር/ መሰረት ሆኖ አገልግሏል፡፡ ከአአድ ስኬቶች መካከል የሚጠቀሰው የኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ
ትብብሮች በየክፍለ አህጉሩ እንዲመሰረቱ ማድረጉ ነው፡፡ ውጤታማ ከሆኑ ክፍለ-አህጉራዊ /ከባቢያዋ/
የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች አንዱና ዋነኛው የደቡባዊ አፍሪካ ልማት ማህበሰረሰብ /ሳድክ/ ነው፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሳድክ የድሮ ስሙ የደቡባዊ አፍሪካ ልማት አስተባባሪ ኮሚቴ Southern African Development coordination
committee- SADCC/ ነበር፡፡ ሳድክክ የደቡባዊ አፍሪካ አገሮችን ከአፖርታይድ ደቡብ አፍሪካ ኢኮኖሚ
ጥገኝነት ለማላቀቅና ለአካባቢው ተስማሚ የሆነ /ከደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ በስተቀር/ የአካባቢውን አገሮች
በአባልነት አቅፎ በመካከላቸው የልማት ትብብር ለመፍጠር ታስቦ የተቋቋመ ኢኮኖሚያዊ ክፍለ-አህጉራዊ
ድርጅት ነበር፡፡ የመጀመሪያው ሳድክክ ጉባኤ የተካሄደው በአሩሻ ታንዛኒያ እ.አ.አ በ 1979 ዓ.ም ሲሆን አንጎላ ፣
ቦትስዋና ፣ ሞዛምቢክ ፣ ታንዛኒና ዛምቢያ እንዲሁም ከእርዳታ ሰጭ መንግስታትና ዓለማቀፍ እርዳታ ሰጭ
ተቋማት ወኪሎች በተገኙበት ነበር፡፡ ሌሎች ፣ ስዊዘርላንድ ማላዊና ዚምባቡዌ እ.አ.አ በ 1980 ዓ.ም ሲቀላቀሉ
ናሚቢያ ደግሞ በ 1900 ዓ.ም አባል ሆናለች፡፡

እ.አ.አ በ 1990 ዎቹ መጀመሪያ የሳድክክ አባል መንግስታት ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ውህደት ለመምጣት እንዲሰሩ
ተስማሙ፡፡ ዘመኑ አረመኔውና ዘረኛው የአፖርታይድ ስርአት የተንኮታኮተበትና በምትኩ ነፃዋ ደቡብ አፍሪካ
ሪፐብሊክ በዝነኛው ፀረ- አፖርታይድ ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ መሪነት የተወለደችበት ጊዜ ነበር፡፡ ስለሆነም
ከአፖርታይድ የተላቀቀችውና በአፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው ደቡብ አፍሪካ ለአካባቢው የተሻለ
ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ሁኔታ ልትፈጥር የምትችልበት እድል ተፈጠረ፡፡ ነገር ግን ደቡብ አፍሪካ ወደ
ድርጅቱ ከመግባቷ በፊት የሌሎች አባል መንግስታት ጥቅም እንዳይነካ መጠበቅ የሚያስችል ዝግጅት ማድረግ
ነበረባቸው፡፡

ተግባር፡- 5.10
ተማሪዎች ደቡብ አፍሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚውን ይዛ ያለ ቅድመ ዝግጅት ወደ ሳድክክ ድርጅት አባልነት
ብትቀላቀል በሌሎች አባል መንግስታት ላይ ሊፈጥር የሚችለው ስጋት ምንድን ነው፡፡

እ.አ.አ በ 1992 ዓ.ም ዊንድ ሆክ /ናሚቢያ/ በተደረገው ስብሰባ የወቅቱ የሳድክክ አባል መንግስታት ሳድክክን
በማፍረስ በምትኩ የደቡባዊ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብን - ሳድክ /Southern Africa Development
Community – SADC/ መሰረቱ፡፡ የሳድክክ አላማ የነበረው የአካባቢውን አገሮች ኢኮኖሚ እርስ በርሱ
በማስተሳሰር ከደቡብ አፍሪካ የኢኮኖሚ ጥገኝነት ነፃ ለመውጣት ሲሆን የሳድክ አላማ ግን የክፍለ-አህጉሩን
ኢኮኖሚ ቀስ በቀስ ግን በዘላቂነት በማዋሀድ የጋራ ልማት ለማምጣት ነው፡፡ የሳድክ የእረጅም ጊዜ እቅድ እንደ
አውሮፖ ያለ የኢኮኖሚ ህብረት በአካባቢው መመስረት ነው፡፡

የምስራቅ አፍሪካ ልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን ኢጋድ /Inter Governmental Authority on
Development IGAD/
የበይነ መንግስታቱ ባለስልጣን የተቋቋመው እ.አ.አ በ 1986 ዓ.ም በጣም ጠባብ በሆኑ የድርቅና በርሀማነትን
በክፍለ አህጉሩ መስፋፋትና በጋራ ለመከላከል ታስቦ ነበር፡፡ ከምስረታው ጀምሮ በተለይም እ.አ.አ ከ 1990 ዎቹ
ወዲህ ኢጋድ ስለአካባቢው አገሮች የፀጥታና የፖለቲካ ችግሮች አስፈላጊ የመወያያ መድረክ እየሆነ መጣ፡፡
ኢጋድ ዋና መቀመጫውን ጅቡቲ አድርጎ ኤርትራ ፣ ኢትዩጵያን፣ ጅቡቲን፣ ሶማሊያን፣ ኬንያን ሱዳንና
ኡጋንዳን በአባልነት አቅፏል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የኢጋድ መስራቾች እ.አ.አ በ 1990 ዎቹ አጋማሽ ላይ ኢጋድ ወደ ተሟላ ክፍለ አህጉራዊ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ
ልማት፣ የንግድና ፀጥታ ስራዎችን የሚሰራ ልክ እንደ ሳድክና ኢኮዋስ የሆነ ጠንካራ ድርጅት እንዲሆን ወሰኑ፡፡
ኢጋድ በአዲስ መልክ እንዲደራጅ ካነሳሱት ምክንያቶች አንዱ የድርጅቱ መወቅራዊና ድርጅታዊ አቅም
ዓላማውንና መርሆዎቹን ለመፈፀም የሚያስችል ስላልነበሩ ነበር፡፡ እ.አ.አ በ 1996 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው
ሁለተኛው የኢጋድ አባል አገሮች አስቸኳይ የመሪዎች ጉባኤ አዲስ ቻርተር በማፅደቅ፣ መዋቅርና አዲስ ስም
በመስጠት የልማት በይነ-መንግስታት ባለስልጣን ሆኖ ተቋቋመ፡፡ የኢጋድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሶስት
ቅድሚያ የሚሰጣቸው የትብብር መስኮችን ለየ፡፡
እነሱም፡-
1. ግጭትን መከላከል፣ ግጭትን መቆጣጠርና መፍታት
2. የሰብአዊ መብት ጉዳዩችን ማስከበር
3. የመሰረተ ልማት /በተለይ ትራንስፖርትና መገናኛ/ ማስፋፋት
4. የምግብ ዋስትናና በቀጠናው ማረጋገጥና የአካባቢ ጥበቃ ማድረግ ናቸው፡፡

ኢጋድ ክፍለ አህጉራዊ ደህንነትና ቀጣይ የኢኮኖሚ ልማት በአካባቢው ማበረታታት ፍላጎት ነው፡፡ ስለዚህ
የኢጋድ ዓላማዎች ሰላምና መረጋጋትን ማስፈንና በአገሮች ውስጥ ወይመ በመካከላቸው የሚከሰቱ ግጭቶችን
ለመከላከል፣ መዳኘትና በሰላማዊ መንገድ መፍታት ነው፡፡ ኢጋድ ከመፈጠሩ ጀምሮ በሶማሊያና በሱዳን ሰላም
ለማምጣት ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

ምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ /ኮሜሳ/ (Common Market for eastern ans southern Africa
(COMESA)
የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገቢያ ወይም በእንግሊዘኛው አህፅሮተ ቃል ኮሜሳ የተመሰረተው በመላው
አፍሪካ ራእይ መሰረት የአህጉሩን አንድነት ለመፍጠር ከክፍለ አህጉራዊ ኢኮኖሚያዊ ህብረት ለመጀመር
ተወስኖ እ.አ.አ በ 1994 ዓ.ም ነበር፡፡ ኮሜሳ የመጀመያውን ድርጅት ማለትም የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ
አመቺ የንግድ ቀጠና /ፒቲኤ/ (Pereferential trade area for eastern and southern Africa) (PTA) ይባል
የነበረውን ድርጅት በመተካት ነው፡፡ ኮሜሳ በነፃና ሉአላዊ አገሮች መካከል የተፈጥሮ የሰው ሀይል ሀብታቸውን
ለጋራ ህዝባቸው ጥቅም ተባብረው ለማልማት በስምምነት ያቋቋሙት ድርጅት ነው፡፡ ከኮሜሳ አላማዎች
መካከል አንዱ በአባል አገሮች መካከል የሚታየውን መዋቅራዊና ተቋማዊ ድክመቶች በማስወገድ ቀጣይነት
ያለው የጋራ ልማት ለማረጋገጥ ነው፡፡ ነገር ግን በኮሜሳ የኃላ ታሪክ በመነሳት አሁን ማድረግ የሚችለው ሰፋ
ያለ የኢኮኖሚና የንግድ ቀጠና በማቋቋም የእያንዳንዱን መንግስት ውስጣዊ ድክመቶች እንደችግሩ
ለማስተናገድና ለመፍታት መሞከር ነው፡፡

የኮሜሳ አባል አገራት ለመተባበር የተሰማሙባቸው ዘርፎች የሚከተሉት ናቸው፡፡


እነሱም፡-
- የታሪፍ መሰናክሎችን በአባል መንግስታት መካከል ማስወገድ፤
- በአባል አገሮች የተመሰረቱ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ነፃ ዝውውር እንዲኖር ማድረግ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

- በጉምሩክ ህብረት በመመስረት ከአባል አገሮች ውጭ ተመርተው የሚመጡ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ላይ


የጋራ ታሪፍ ለመጣልና ተግባራዊ ለማድረግ፤
- የጋራ ቪዛ በማዘጋጀት በአባል አገሮች መካከል ነፃ የሰው ዝውውር እንዲኖር፤
- ተመሳሳይ የኢንቨስትመንት ህግና አሰራርን በአባል አገሮች መካከል በማስፈን ነፃ የካፒታልና
ኢንቨስትመንት ዝውውር እንዲኖር ማድረግ፤

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

- በሂደት የጋራ ክፍያ አሰራርና ገንዘብ መመስረት ናቸው፡፡

ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ወደ አፍሪካ ህብረት የተደረገ ሽግግር


ተግባር 5.11
1. አፍሪካ አንድነት ድርጅት የትን መቼ ተመሰረተ
2. መስራች አገሮቹ ስንት ነበሩ አላማዎቹ ምንድን ነበሩ
3. የአአድ ስኬቶች የሚባሉትን ተወያይታችሁ ዘርዝሩ
4. የአአድ ድክመቶችን ለይታችሁ አቅርቡ

የአአድን ድክመቶች ግምት ውስጥ በማስገባት የአፍሪካ ዜጎች መሪዎቻቸውን አአድን ወደ ተሻለ ጠንካራ
ድርጅትነት የሚለወጡትን ሁኔታ በጥብቅ እንዲያጠኑ መጠየቅ ጀመሩ፡፡ ስለሆነም በአፍሪካ የሚገኙ ወደ 54
የሚሆኑ ነፃ ብሄራዊ መንግስታትን ህብረት ፈጥሮ ለጠንካራ ሁለንተናዊ ትብብር የሚያበቃና የአፍሪካን
ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ባህላዊ ችግሮች መፍታት በሚያስችለው አቋምና ችሎታ እንዲደራጅ
ፈለጉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች አአድ ፈርሶ በምትኩ እንደ አውሮፖ ህብረት ያለ ጠንካራ ድርጅት በአፍሪካ መመስረት
አለበት ብለው ጠየቁ፡፡ የአውሮፖ ህብረት እ.አ.አ በ 1990 ዎቹ ትብብርና ህብረትን በአውሮፖ አገሮች መካከል
በማፋጠን ውጤታማነቱን ያስመሰከረ አህጉራዊ ድርጅት ነው፡፡
እ.አ.አ በ 2001 ዓ.ም በሊቢያ የተሰበሰው የአአድ የመሪዎች ጉባኤ በአአድ ምትክ አፍሪካ ህብረትን ለማቋቋም
በሚያስችል ሐሳብ ላይ አትኩረው ተወያዩ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ህብረት ታሪካዊ ምስረታ የሚጀመረው
በ 1960 ዎቹ በክዋሜ ንክሩማህ በህብረቱ አባል መንግስታት መካከል ቅድሚያ ኮንፌዴሬሽን በሂደት የአፍሪካ
ህብረትን ለመፍጠር አአድን እ.አ.አ ግንቦት 25 ቀን 1963 ዓ.ም በአዲስ አበባና የአፍሪካ ኢኮኖሚ ማህበረሰብን
እ.አ.አ በ 1981 ዓ.ም የተደረጉት ጥረት አካል ነው፡፡

የአፍሪካ ህብረትን በመመስረት አሳብ መጀመሪያ የተነሳው በ 1990 ዎቹ አጋማሽ በቀድሞው የሊቢያ መሪ
የነበሩት ኮሎኔል ሙሀመድ አል-ቃዳፊ አነሳሽነት ነበር፡፡ የአአድ የመንግሰታት መሪዎች ሲርጥ /ሊቢያ/
ተሰብስበው የሲርጥ አዋጅ የተባለውን እ.አ.አ መስከረም 9 ቀን 1992 ዓ.ም ለአፍሪካ ህብረት ምስረታ ጥሪ
የሚደረገውን ሰነድ አፀደቁ፡፡ ስለሆነም ቅድመ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቶ የአፍሪካ ህብረት ደርባ /ደቡብ አፍሪካ/
ውስጥ እ.አ.አ በሀምሌ 9 ቀን 2002 ዓ.ም የመጀመሪያውን የምስረታ ስብሰባ የደቡብ አፍሪካ የወቅቱ
ኘሬዜዳንት በነበሩት ታቦ ምቤኪ ሊቀ መንበርነት ስራውን ጀመረ፡፡

የአፍሪካ ህብረት አባል ያለሆነ ብቸኛ አፍሪካዊነት አገር ሞሮኮ ብቻ ናት ፡፡ ምክንያቱም ሞሮኮ ከአፍሪካ ህብረት
በፊት የነበረውን አአድን እ.አ.አ በ 1984 ዓ.ም የምዕራብ ሰሀራ ብሄራዊ ፖሊሳርዩ ግንባርን መደገፋንና
በድርጅቱ የታዛቢነት ወንበር መፍቀዱን በመቃወም ነበር፡፡ ሆኖም ግን ሞሮኮ የድርጅቱ አባል ባትሆንም ቀድሞ
በአአድ አሁን ደግሞ በአፍሪካ ህብረት ጥቅሟን የሚያስጠብቅ ታዛቢ ያላት ሲሆን የአፍሪካ ህብረት አባል

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

አገሮች ከድርጅቱ የሚያገኙትን ጥቅም ሁሉ ማለትም እንደ የአፍሪካ ልማት ባንክ ካሉት ተቋማት እኩል
ታገኛለች፡፡

የአፍሪካ ህብረት መጀመያ በአባል አገር ወታደር በማስማራት ጣልቃ የገባው እ.አ.አ የግንቦት ወር 2003 ዓ.ም
በቡርንዲ የተደረጉ የተለያዩ የሰላም ስምምነቶችን ለመታዘብና ሰላም ለማስከበር ከደቡብ አፍሪካ ፣
ከኢትዩጵያ ፣ ከሞዛንቢክ የተወጣጣ የሰላም አስከባሪ ሰራዊት ነበር፡፡ በተጨማሪ የአፍሪካ ህብረት ሰራዊት
በላይቤሪያ ፣ ሩዋንዳ ፣ ሴራሊዩን ፣ ሱዳን ፣ ሶማሊያና ማሊ በመሳሰሉ አገሮች ሰላም ለማስፈን በተደረገው
ጥረት ከፍተኛ እርዳታ አድርጓል አሁንም ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ ያሰማራቸው ወታደሮች በተጠቀሱት
የአፍሪካ አገሮች ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡

የአፍሪካ ህብረት ብዙ በአህጉራዊ ደረጃ የሚተገበሩ አዳዲስ ጠቃሚ ሰነዶችን በማዘጋጀት ድርጅቱ ሲመሰረት
የተቋቋመበትንና በስራ ላይ ያሉትን አሰራሮችና ህጎች የሚደግፉና ክፍተት የሚሞላ አድርጎ በማዘጋጀት በስራ
ላይ አውሏል፡፡ ከእነዚህ መካከል
ሀ/ እ.አ.አ በ 2003 ዓ.ም የፀደቀው ሙስናን ለመከላከልና ለመዋጋት የሚያስችለው ስምምነት
ለ/ እ.አ.አ በ 2007 ዓ.ም የፀደቀው በዲሞክራሲ ፣ ምርጫና መልካም አስተዳደር ላይ የተዘጋጀው የአፍሪካ
ቻርተር
ሐ/ ለአፍሪካ ልማት አዲስ አጋርነት የሚባለው የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
የአፍሪካ ህብረት የሚከተሉት ውሳኔ ሰጪና አስተዳደራዊ አካላት አሉት፡፡ እነሱም
ሀ/ የህብረቱ ጠቅላላ ጉባኤ ሠ/ የአፍሪካ ፍርድ ቤት
ለ/ የህብረቱ ስራ አስፈፃሚ ረ/ ቋሚ የተወካዩች ኮሚቴ
ሐ/ የመላው አፍሪካ ፖርላማ ሰ/ የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ተቋማትና
መ/ የህብረቱ ኮሚሽን ሸ/ ልዩ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴዎች ናቸው፡፡

የክለሳ ጥያቄዎች
1. የኢንዱስተሪዉ አብዮት ለአፍሪቃ በቅኝ ግዛት መያዝ የነበረዉን አስተዋጽኦ ተወያየበት
2. የበርሊኑ ጉባኤ ለምን ተካሄደ? ዋና ዋና ዉሳኔዎቹን ጥቀሱ፡፡
3. በእንግሊዝ፣በፈረንሳይና በሌሎች ሀገራት ቅኝ ግዛት የተያዙ የአፍሪካ ሀገራትን ዘርዝሩ፡፡
4. የአፍሪካዉያን ቀደምት ፀረ ቅኝ ግዛት ትግል ስኬታማ ያልነበረዉ ለምንድን ነዉ?
5. የአፓርታይድ ስርአት መገረጫዎችን ዘርዝሩ፡፡
6. የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ዋና ዋና ስኬቶችና ድክመቶችን ዘርዝሩ፡፡
7. የአፍሪካ ክፍለ አህጉራዊ ድርጅቶች የሚባሉትን ዘርዝሩ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ምእራፍ ስድስት

የዘመናዊዉና የአሁኑ የአለም ታሪክ


የምእራፉ አላማዎች
- ተማሪዎች ይህን ምእራፍ ካጠናቀቁ በኃላ፤
- የኢንዱስትሪዉ አብዮት ለዉጦችንና ዉጤቶችን ይዘረዝራሉ
- የጣልያንና የጀርመን ዉህደት ሂደትና ዉጤቶችን ያብራራሉ
- የአሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት፣ሂደትና ዉጤቶችን ይገልጻሉ
- የአንደኛዉና የሁለተኛዉ የአለም ጦርነትምክንያት፣ሂደትና ዉጤቶችን ይዘረዝራሉ
- ከሁለተኛዉ አለም ጦርነት በኃላ በአለማችን የተከናዎኑ ዋና ዋና ክስተቶችን ይናገራሉ
- የኮሙኒስት ቻይና፣የኮሪያ ፣የኢንዶ ቻይና እና ኩባ ፖለቲካዊ ክስተቶችን ያብራራሉ

6.1 የዘመናዊዉ የአለም ታሪክ (1815-1945)

6.1.1 የኢንዱስትሪዉ አብዮት

የኢንዱስትሪ አብዩት ከሞላ ጎደል ከ 1750 ዓ.ም ጀምሮ በማምረት ስልት የተካሄዱ ለውጦችን የሚዳሰስ ነው፡፡
እነዚህም አዝጋሚና ውድ ከነበረው በእጅ ማምረት ፈጣንና ርካሽ ወደ ሆነው በማሽን የማምረት ሂደት
መሸጋገርና እንዲሁም በቤት ውስጥ በተለምዶ ከማምረት ተላቆ በሚገባ በተደራጀው ፋብሪካ ደረጃ ማምረት
መጀመሩን ያመለክታል፡፡
የኢንዱስትሪ አብዩት ሰፋ ባለ ሁኔታ ሲተነተን በዘመናዊ ማምረቻ መሳሪያ መጠቀምን፤ በአጠቃላይ በሰው ልጅ
የአኗኗር ሁኔታ ላይ ያስከተለውን ጠቀሜታና ለውጥ የሚቃኝ ነው፡፡ ከታዩ የስራ ውጤቶችና ከጊዜ አንፃር
የኢንዱስትሪ አብዩትን በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች መመደብ ይቻላል፡፡ እነርሱም፡-

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

1. የመጀመያው የኢንዱስትሪ አብዩት /1750 – 1870/


2. የሁለተኛው የኢንዱስትሪ አብዩት ከ 1870 - እስከአሁን ድረስ/ ናቸው፡፡

1. አሮጌው /የመጀመሪያው/ የኢንዱስትሪ አብዮት

የአሮጌው ወይም የመጀመሪያው የኢንዱስትሪ አብዩት መለያ ባህርያትና በዚህ ዘመን የታዩት መሰረታዊ
ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፡፡
ሀ/ የመጀመሪያዎቹ የተወሳሰቡ ማሽኖች የተስፋፈበትና ቀደምት ፋብሪካዎች የተገነቡበት ዘመን ነው፡፡
ለ/ እንፋሎት የሀይል ምንጭ የሆነበትና ይህ ሀይል ለምርትና ለመጓጓዣ አገልግሎት መስጠት የጀመረበት ጊዜ
ነው፡፡
ሐ/ የከሰል ፣ የብረትና የአረርብረት ምርቶች በብዛት መመረት የታየበት ወቅት ነው ፡፡
መ/ አዲስ የመጓጓዣና የመገናኛ ዘዴዎች መጠቀም መሰረት የተጣለበት ዘመን ነው፡፡

2. አዲሱ /ሁለተኛው/ የኢንዱስትሪ አብዮት

አዲሱ የኢንዱስትሪ አብዩት ከ 1870 ጀምሮ እስከአሁን ድረስ በኢንዱስትሪ መስክ የተከሰቱትን ለውጦችን
የሚዳስስ ነው፡፡ በዚህ ዘመን የሰው ልጅ ፈጠራና ግኝት በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል፡፡ ይህ ግኝትና ፈጠራ
በኢንዱስትሪና በሰው ልጅ ኑሮ ላይ ከፍተኛ ለውጥን አስከትሏል፡፡ ይህ አብዩት አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡
በዚህ ዘመን የተከሰቱ መሰረታዊ ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፡፡
ሀ/ የኤሌክትሪክ፤ የነዳጅና የአቶሚክ ጉልበት በሀይል ምንጭነት ማገልገል መጀመራቸውና አዳዲስ
ኢንዱስትሪዎችን ለመጠቀም እገዛ ማድረጋቸው፡፡
ለ/ ሳይንስ ለኢንዱስትሪ ግንባታ ማገልገሉና እንደኘላስቲክ ናይለን ወዘተ የመሳሰሉት ሰው ሰራሽ ምርቶች
በብዛት ስራ ላይ መዋል፡፡
ሐ/ እንደ አውሮኘላን ፣ ሬድዩ ፣ ቴሌ{ዥን የመሳሰሉት አዳዲስና ፈጣን የመጓጓዣና የመገናኛ መሳሪያዎች
መፈልሰፍና ስራ ላይ ማዋል፡፡
መ/ በኮምፒዉተር የሚሰሩና በአጠቃላይ በኤሌክትሮኒክስ ጥበብ የሚደገፋ መሳሪያዎች /ማሽኖች/ መፈልሰፍ፣
ሠ/ በመሬት ዙሪያ የሚሽከረከሩና ወደ ሌሎች ኘላኔቶች በየጊዜው የሚላኩትን መንኮራኩሮች ስራ
የሚያጠቃልል ዘመን ነው፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የኢንዱስትሪ አብዮት በእንግሊዝ መጀመር


የኢንድስትሪ አብዩት የተጀመረው በእንግሊዝ አገር ሲሆን ቀስ በቀስ ወደ ሌሎች የአውሮፖ ሀገሮችና ወደ
አሜሪካ ተዛምቷል፡፡ ይህ አብዩት በዚህ ሀገር ሊጀመር የቻለባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. ምቹ ገበያ
2. የእንግሊዝ ህዝቦች
3. የተፈጥሮ ሀብት
4. የተመቻቸ መስተዳድር
1. ምቹ ገበያ ሁኔታ፡- እንግሊዝ በዚያን ዘመን የበለፀገችና ብዙ ቅኝ ግዛትያላት ሀገር ስለነበረች ምርቷ
በሀገር ውስጥና በውጭ እጅግ ተፈላጊ ነበር
2. የእንግሊዝ ህዝብ ፡- እንግሊዝ በዚያን ወቅት የሚፈለጉትን ማሽኖች የሚሰሩ እውቅ ባለሙያዎች
የነበራት ሲሆን እነዚህን ማሽኖች ገዝቶ የመጠቀም አቅም የነበራቸው ባለፀጎችም ሀገር ነበረች፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በፋብሪካዎች ውስጥ ተቀጥረው ለመስራት የሚፈለጉ አያሌ ስራ ፈላጊዎች
ስለነበሩ በቀላሉ እርካሽ ጉለት ማግኘት ይቻል ነበር፡፡
3. የተፈጥሮ ሀብት ፡- የእንግሊዝ የተፈጥሮ ሀብት ከላይ ከተጠቀሱት ምክንያቶች በተጨማሪ
ለኢንዱስትሪ አብዮት መጀመር ትልቅ ድርሻ አበርክተዋል፡፡ የከሰል እንደልብ መገኘት የእንፋሎር
ሀይልን ለማመንጨት የረዳ ሊሆን የብረት ማዕድን መኖር ማሽኖችን ለመስራት አግዟል፡፡ ከዚህ ሌላ
አገሪቱ ምቹ የባህር ወደቦች ስላሏት እነዚህ ወደቦች ንግድ እንዲዳብርና ጥሩ መሰረት ሆነዋል፡፡
በንግዱ አማካኝነት የተገኘው ትርፍ በበኩሉ የኢንዱስትሪውን ዘርፍ አሳደገው፡፡ ከዚህ ባሻገር
እንግሊዝ የባለ ብዙ ቅኝ ግዛት ሀገር ስለነበረች በቀላሉ ለፋብሪካዎች ተፈላጊ የነበሩ እንደ ጥጥ፣
እንጨት ወዘተ የመሳሰሉት ጥሬ ዕቃዎችን የማግኘት ዕድሉ ነበራት፡፡
4. የተመቻቸ መስተዳድር መኖር፡- በዚህ ዘመን የእንግሊዝ መንግስት ለኢንዱስትሪ መዳበር የበኩሉን
ድርሻ አበርክተዋል፡፡ በኢንዱስትሪ መስክ የተደረገውን ግስጋሴ ለመርዳት በዚህ ዘርፍ ለተሰማሩ
ሰዎች ይጠየቅ የነበረው ግብር አነስተኛ ነበር፡፡ ይህ ብዙ ሀብታሞች ገንዘባቸውን ለኢንዱስትሪ
ግንባታ እንዲውሉ ረድቷል፡፡ በሌላም በኩል መንግስት በቂ አደረጃጀት የነበራቸው ባንኮች ስላቋቋመ
እነዚህ ባንኮች ኢንዱስትሪዎች ለመገንባት በገንዘብ ምንጭነት አገልግለዋል፡፡

የኢንዱስትሪ አብዮት ውጤቶች


የኢንዱስትሪ አብዩት የአለማችን ገፅታ ፍፁም ቀይሯል፡፡ በሰው ልጅ ኑሮ ላይ ቅፅበታዊ ለውጦች ተከስተዋል፡፡
ይህ አብዮት በኢኮኖሚ በፖለቲካ ፣ በማህበራዊና በባህላዊ ዘርፎች መሰረታዊ ለውጦችን አስከትሏል፡፡
በኢንዱስትሪ አብዩት ምክንያት ከተከሰቱ ውጤቶች መካከል አንዳንዶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. የምርት መጨመር፡- በጉልበት ቆጣቢ ማሽኖች መፈልሰፍ የተነሳ በአጭር ጊዜ ብዙ ምርት ማምረት
ተችሏል፡፡ ከድሮው በበለጠ የስራ ክፍፍል ዳብሯል፡፡
2. የዕቃዎች ዋጋ መቀነስ፡- በአጭር ጊዜ የብዙ ዕቃዎች መመረት የሸቀጦች ዋጋ እንዲቀንስ ረድቷል፡፡
ይህም በበኩሉ ከዚህ በፊት የመግዛት አቅም የሌላቸው ድሆች እንኳ በመጠኑም ቢሆን አንዳንድ
ሸቀጦች ገዝተው እንዲገለገሉ ረድቷል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

3. የእንግሊዝ በኢንዱስትሪ መግፋት፡- ከኢንዱስትሪ አብዩት በፊት የእንግሊዝ ኢኮኖሚ በአብዛኛው


በእርሻ ላይ የተመሰረተ ነበር፡፡ በሂደት ግን ኢንዱስትሪው እርሻውን ተካው፡፡ እንግሊዝ ብዙ ቅኝ
ግዛት ስለነበራትና በዘመኑ በኢንዱስትሪ መስክ ግንባር ቀደመ በመሆኗ ዕቃዎቹ በአለም የደራ ገበያ
ነበራቸው፡፡ ስለሆነም ታዋቂና ሀብታም ሀገር ሆነች፡፡
4. የከተሞችና የፋብሪካዎች ማደግ፡- ታላላቅ ፋብሪካዎች በመላ እንግሊዝና በሂደት በሌሎችም ሀገሮች
ተስፋፋ፡፡ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ሰራተኞች በእነዚህ ፋብሪካዎች ተቀጠሩ፡፡ አንድ ወቅት የገጠር
መንደሮች የነበሩ ቦታዎች ወደታላላቅ ከተማነት አደጉ፡፡
5. የትራንስፖርት መሻሻል፡- የድሮዎቹ የመጓጓዝ አይነቶች ለአዲሶቹ የመጓጓዝና የመገናኛ ዘዴዎች
ቦታቸውን ለቀቁ፡፡ ባቡር ፣ በእንፋሎት ኃይል የሚሰሩ ጀልባዎች የተሻሻሉ ጎዳናዎች ወዘተ ተሰሩ፡፡
6. የካፒታሊስቶች ማደግ፡- ፋብሪካዎችን ለማቋቋም እጅግ ብዙ ገንዘብን ይጠይቃል፡፡ የገንዘቡ ምንጭ
የነበራቸው ሀብታሞች በዚህ በአዲሱ ኢኮኖሚ ገንዘባቸውን ማፍሰስ ቀጠሉ፡፡ቀስ በቀስ የእነዚህ
ከበርቴወች ቁጥር ጨመረ ይህም አዲስ የካፒታሊስቶች መደብ መፈጠሩን ያመላክታል፡፡
7. አስደንጋጭ የስራ ሁኔታ፡- አብዛኞቹ የተቋቋሙ ፋብሪካዎች ለሰራተኛው ጤንነትና ደህንነት
በሚያመች ሁኔታ የተደራጁ አልነበረም፡፡ በዚህም ምክንያት ሰራተኞች የጤና ችግርና ያለጊዜ በሞት
መቀጨት ደርሶባቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሀብታሞች ሴቶችና ህፃናትን በአነስተኛ ገንዘብ በመቅጠር
ትርፍ አግበስብሰዋል፡፡ ይህም የሴቶችና የህፃናትን ስብዕና የነካ መጥፎ ተግባር ነው፡፡
8. የሰራተኛው ማህበራት መፍጠር፡- አዳዲስ ፋብሪካዎች በመመስረታቸው የሰራተኛው ቁጥር ጨመረ፡፡
የሰራተኛው ክፍያና የስራ ሁኔታ እንዲሻሻል ትግሉ ቀጠለ፡፡ በጉልበትና ካፒታል መካከል ፍጥጫ
ተፈጠረ፡፡ ሰራተኞች በአሰሪዎች የሚደርስባቸው በደል ለመቋቋም ደረጃ በደረጃ በየማምረቻ
ተቋማት ማህበራቸውን መሰረቱ፡፡
9. የባዶ መንደሮች መፈጠር፡- ከኢንዱስትሪ አብዩት በፊት ገበሬዎች ከግብርና ስራ በተጓዳኝ ልብስ
በማምረትና ሌሎች የዕደ ጥበብ ውጤቶችን በመስራት
ተጨማሪ ገቢ ያገኙ ነበር ፡፡ ከኢንዱስትሪ አብዮት መከሰት በኋላ ግን እቃዎችን በብዛትና በእርካሽ
ማምረት ስለተጀመረ ገበሬዎች ከዚህ በፊት የተለመዱትን ተጨማሪ ገቢ ማግኘት አልቻሉም፡፡
በእርሻ ሞያ ብቻ ኑሯቸውን ማሸነፍ ተሳናቸው፡፡ ስለሆነም የተወለዱበትና ያደጉበትን ቀየ እየለቀቁ
ወደ ከተማ ተሰደዱ ፡፡የብዙ ገበሬዎች መኖሪያ የነበሩ መንደሮች ባዶ ሆኑ ወይም የገጠሬውን ኗሪ
ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ተመናመነ፡፡
10. በከተሞች የሕዝብ ቁጥር መጨመር፡- ከዓመት ዓመት የፋብሪካዎች መጠንና ቁጥር አደገ፡፡ ከዚሁ ጎን
ለጎን የሰራተኞች ቁጥር ከፍ አለ፡፡ ይህ ለከተሞች ማደግ መንገድ ጠረገ፡፡ ከተሞች በህዝብ ተጨናነቁ፡፡
የህዝብ ቁጥር በጣም እየጨመረ በመሄዱ የፅዳት ጉድለት የተፋፈገ ኑሮ፣የወንጀል መከሰት ፣የአየር እና
የዉሃ ብክለት የትራንስፖርት የአስተዳደር ችግር አስከተለ፡፡
11. የቅኝ ግዛት ሕዝብ መበዝበዝ፡- በቀኝ ግዛትነት ይተዳደሩ የነበሩ ሀገር ሕዝቦች የንግድ ግንኙነት
ማድረግ የሚችሉት ከቀኝ ገዥው አገር መንግስት ጋር ብቻ ነበር፡፡ ጥሬ እቃዎችን ለቅኝ ገዥዎች
በርካሽ ይሸጣሉ፡፡ ለእነርሱ የኢንድስትሪ ውጤቶችን በውድ ይገዛሉ፡፡ የራሳቸውን ፋብሪካዎች

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ማቋቋም አይፈቀድላቸውም ነበር፡፡ እነዚህ ቅኝ ግዛት ሀገሮች የኢኮኖሚ ነፃነታቸውን ሲገፈፋ


በአንፃሩ ባለ ኢንዱስትሪ ሀገሮች በቀኝ ተገዥዎች ኪሳራ ከቀን ወደ ቀን በኢኮኖሚ በለፀጉ፡፡

ተግባር 6.1
1. የኢንዱስትሪ አብዮት ለምን እንግሊዝ አገር ተጀመረ?
2. የኢንዱስትሪ አቢዮት አዎንታዊና አሉታዊ ገጽታዎች ከኢኮኖሚ፣ከባህል፣ከፖለቲካ እና
ከማህበራዊ አንፃራዊ በዝርዝር አብራሩ?
3. የኢንዱስትሪ አቢዮት በፋብሪካ ላይ የነበረው ውጤት አብራሩ?
4. የኢንዱስትሪ አቢዮት ቀጣይነት ያለው ሂደት ነው ማለት ምን ማለት ነው ?
5. በመጀመሪያውና በሁለተኛው የኢንድስትሪ አቢዮት ክፍሎች የታየ ጉልህ ልዩነቶችን
በመዘርዘር ግለፁ?
6. የኢንዱስትሪ አቢዮት በአፍሪካ ለምን ዘገየ?

6.1.2 የኢጣልያ ውህደት


ከ 1870 ዓ.ም በፊት በደቡብ አውሮፓ የምትገኘው ኢጣልያ በብዙ ታናናሽ መግስታት የተከፋፈለች ነበረች፡፡
ብዙዎቹም መንግስታት በውጭ ኃያላን መንግስታት ተፅዕኖ ስር ነበሩ፡፡ ከዚህ ቀጥሎ የኢጣልያን ህዝቦች
ውህደት ንቅናቄ ባህሪያት ምን እደሚመስሉ እና ለውህደቱ እንቅፋት የነበሩትን እንዲሁም ውህደቱ እዲፋጠን
የረዱ ምክንያቶችን አንድ በአንድ እናያለን ፡፡

ለኢጣልያ ውህደት እንቅስቃሴ እንቅፋት የነበሩ ምክንያቶች


1. የቬና ጉባኤ(1815)

በኦውስትሪያ የተጣራው የአውሮፓ አገሮች ጉባኤ አላማው ከ 23 ቱ ዓመት የናፖሊዎን ጦርነት ማብቃት ጋር
ተያይዞ የአውሮፓ አገሮች የፖለቲካ ካርታ ለመወሰን እና በአውሮፓ ሰላምና ደህንነትን ለማስፈን የሚል እሳቤ
ቢኖረውም የተወሰኑ የአዉሮፓ ሀገራት ጠትቅም ማሰክበሪያ መሆኑ አልቀርም ፡፡ ለምሳሌ ከጉባኤው በጣም
ተጠቃሚ ከነበሩት መካከል አንዷ ኦውስትሪያ ነበረች ፡፡
በቬና ጉባኤ የኢጣልያ ግዛቶች እንደሚከተው ተከፋፍለዋል
ሀ. ሎምባርዲ እና ቬኒሲያ (በሰሜን ኢጣልያ የሚገኙ ግዛቶች ) በቀጥታ በኦስትሪያ ግዛት ውስጥ እዲካተቱ
ተደርጓል፡፡
ለ. ፓርማ ፣ሞዴና፤ቱስካኒ (ማዕከላዊ ግዛቶች )እንዲሁም ኔፕልስ በራሳቸው የሚተዳደሩ
ቢሆኑም በኦስትሪያ ተፅዕኖ ውስጥ መውደቃቸው አይቀሬ ሆኗል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሐ. የፓፓል ግዛቶች (Papal States) ሮምን በመጨመር በሮም ሊቀ ጳጳስ (pope) ቁጥጥር ስርእንዲሆኑ
ተደርጓል ፡፡
መ. ሳርዲኒያናፔድሞንት የሚባሉ ሁለት ግዛቶች በሰሜን ምዕራብ ኢጣልያ የሚገኙ ሲሆን
ከውጭ ቁጥጥር ወይም ተፅዕኖ ነፃ የነበሩት ራስ ገዝ ግዛቶች ሆነዋል ፡፡ በመሆኑም
የውህደት ንቅናቄው ዋና ፊታውራሪ በመሆን ይታወቃሉ ፡፡
2. የኦስትሪያ መንግስት ተቃውሞ፡
የኦስትሪያ መሪዎች በጣልያን ህዝቦች ላይ የነበራቸው ተፅዕኖና የበላይነት እንዲቀጥል ወይም ጥቅማቸውን
ለማስከበር የውህደቱን ንቅናቄ በጥብቅ ተቃውመዋል ብሎም ጸረ-ውህደት ንቅናቄ ማራመድ ችለዋል፡፡
በመሆኑም የውህደት ንቅናቄ ሂደቱ ሊጓተት ችሏል፡፡
3. የካቶሊክ ቤተክርሲቲያን መሪዎች ተቃውሞ
ሊቀጳጳሱና ሌሎች ቀሳውስት አንድ የተዋህዶች ጠንካር ኢጣሊያ እንድትመሰረት ፈቃደኛ አልነበሩም
ምክንያቱም ደግሞ በፓፓል ግዛቶች የነበራቸውን ስልጣንና ጥቅማጥቅም ለማስቀጠል ወይም ላለማጣት ነበር
፡፡
4. በንቅናቄ መሪዎች መካከል የዓላማ ልዩነት መኖር
ምንም እንኳ የኢጣልያ ውህደት እውን መሆን የመሪዎች የጋራ ዓላማ ቢሆንም በንቅናቄ መሪዎች መካከል
ወደፊት የሚፈጠረው የመንግስት አደረጃጀት እና መዋቅር የተለያየ አመለካከት መኖር ውህደቱን ካጓተቱት
ምክንቶች አንዱ ነበር ፡፡
ለምሳሌ፡- ጁሴፔ ማዚኒና ጁሴፔ ጋሪባልዲ የሚባሉ የውህደት ንቅናቄ መሪዎች የሚመሰረተው መንግስት
ዲሞክራሲያዊ ሪፕብሊክ እንዲሆን ይፈልጉ ነበር ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ካውንት ካሚሎ ዲ. ካቮር የተባለው መሪ
የለዘብተኛ (ሊብራል)መንግስት ስርዓት ምስረታ እንዲኖር ይፈለግ ነበር ፡፡
ጅኦባርቲ የተባለው ንቅናቄ መሪ ቡድን ደግሞ በሊቀጳጳሱ መሪነት የፌዴሬሽን መንግስት እዲመሰረት
ይፈለግ ነበር ፡፡ በነዚህ የተለያዩ አመለካከቶች መኖር ምክንያት ውህደት ከተፈለገው ጊዜ በፊት
እዳይፈፀም ሆኗል፡፡
ተግባር፡-6.2
1. የኦስትሪያ መንግስት የኢጣልያ ውህደት ንቅናቄ ለምን ተቃወመ?
2. ሊቀጳጳሱ አገዛዝ ስር የነበሩ የኢጣልያ ግዛቶችን ስም ዘርዝሩ?
3. የቬና ጉባኤ ለኢጣልያ ውህደት ንቅናቄ የነበረውን አሉታዊ ተፅዕኖ በግልፅ አብራሩ ?
4. ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ማለት ምን ማለት ነው?

ለኢጣልያ ውህደት እንቅስቃሴ አወንታዊ የነበሩ ምክንያቶች


1. የጠንካራ ብሄራዊ ስሜት /መንፈስ/ በህዝቦች ዘንድ መኖር

የኢጣልያ ህዝቦች በተለይ ከናፖሊዎን ጦርነት በኃላ የአንድነትና ጠንካራ የሀገር ፍቅር ስሜታቸው መጨመሩ
ለውህደቱ እንደ አንድ አበረታች ምክንያት ሆኗል፡፡ ብሎም የጥንታዊ ሮምን ዝናና ክብር እዲሁም ኃያልነት

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ለመመለስ ተነሳስተዋል ፡፡ በተጨማሪ ኢጣልያ የተሓድሶ (renaissance) ንቅናቄ መስራችና መናኸሪያ መሆኗ
ማነቃቂያ ሆኗታል፡፡
2. ቁርጠኛና መንፈሰ ጠንካራ አገር ወዳድ ዜጎች ብቅ ማለት

የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያህል ፡-


ሀ/ ጁሴፔ ማዚኒ- በንቅናቄው ከፍተኛ ዝና ያተረፈ ታላቅ አገር ወዳድ መሪ የነበረ ሲሆን
በቅፅል ስሙ የውህደት ንቅናቄው መንፈስ (soul of the unification) ተብሎ ይታወቃል፡፡በተጨማሪ በ 1831
ዓ.ም የወጣት ጣልያን ንቅናቄ በመመስረት ጣልያኖች ለነፃነታቸውና ለአንድነታቸው በንቃት እዲሳተፉ
በማድረግ ይታወቃል፡፡ የንቅናቄው ዓላማም ዜጎችን በማስተማር ለመብቶቻቸው መጣስ አልገዛምነት
ስሜታቸው እዲጨምር በማድረግ ለውህደት ንቅናቄው ስኬት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡
ለ/ ጁሴፔ ጋሪባልዲ - የውህደቱ ንቅናቄ የጦር መሪ ሲሆን በ 1860 ሲሲሊናኔፕልስን ነፃ ያወጣ ሀገር ወዳድ
ጀግና መሪ ነበር፡፡ በነበረውም ያመራር ብቃት /sword of unification/ ተብሎይጠራ ነበር ፡፡
ሐ/ ካቮር- ከ 1852 ዓ.ም ጀምሮ የሳርዲኒያፒድሞንት ጠቅላይ ሚኒስተር እና የንቅናቄ ዋና
ሞተር /Brain of the unification/ እየተባለ ይጠራ ነበር፡፡
መ/ ቪክተር አማኑኤል፡- ከ 1849 ዓ.ም ጀምሮ የሳርዲኒያፒድሞንት ንጉስ፤ በውህደቱ ትግል የካቮር ዋና ደጋፊ
የነበረ ሲሆን ከ 1861 ዓ.ም በኃላ ደግሞ የኢጣሊያ ግዛት ንጉስ ተብሏል፡፡
የኢጣልያ ውህደት ንቅናቄ ዲኘሎማሲና የአብዮት ምዕራፍ
ምንም እንኳ ከ 1848 ዓ.ም በፊት የውህደቱ ንቅናቄ በተወሰነ የማህበረሰብ ክፍሎች ብቻ የተወሰነ ቢሆን
ለኃለኛው ስኬት መሰረት የጣለ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ በ 1820 ዎቹ የተመሰረተውና በህዝቡ ይንቀሳቀስ
የነበረው ምስጢራዊ ድርጀት ካርቦናሪ /carbonari / በቀዳሚነት ሊጠቀስ ይችላል፡፡ በመቀጠልም በ 1831 ዓ.ም
አብዮታዊ ንቅናቄ በቦሎኛ ከተማ ተጀምሮ ወደ ሌሎች ከተሞች በፍጥነት ተሰራጭቷል፡፡ ሆኖም ግን በኦስትሪያ
መንግስት ጣልቃ ገብነት ንቅናቄው በአጭር እንዲቀር ወይም እንዳይሳካ ሆኗል፡፡
በ 1848 ዓ.ም ልክ እንደሌሎች የአውሮፖ ሀገሮች ሁሉ በተለያዩ የጣልያን ከተሞች ታላቅ አብዮት
ተቀስቅሷል፡፡ ፔድሞንቶችም ሎንባርዲንናቬኒሲያን ከኦስትሪያ ቁጥጥር ነፃ ለማውጣት ሙከራ አደረጉ ነገር
ግን በኦስትሪያ ሀያልነት ውጤት አልባ ሆነ፡፡ ለኢጣሊያ ውህደት ስኬት ጦርነት ብቻ መፍትሄ እንዳልሆነ
በመረዳት ጠቅላይ ሚኒስቴር ካቮር የዲኘሎማሲ እንቅስቃሴ ማድረግ ጀመረ፡፡ በመሆኑም ከኦስትሪያ ጋር
በሚያደርገው ጦርነት የፈረንሳይን አጋዥነት ማግኘት ዋነኛ አማራጭ አድርጎ ወሰደ፡፡ በዚህም ረገድ
የናፖሊዩን 3 ኛውን /የፈረንሳይ ንጉስ/ ድጋፍ ካረጋገጠ በኃላ ካቮር ኦስትሪያን ለመጋፈጥ ወሰነ፡፡ ናፖልዩን
በሚያደርገው ድጋፍ ኒስናሳቮይ የተባሉ የጣሊያን ግዛቶች እንደሚሰጡት ቃል ተገባለት፡፡

የማጀንታ እና ሰልፈሪኖ ጦርነቶች


የኢጣሊያና የፈረሳይ ወታደሮች ባደረጉዋቸው ተከታታይ ጦርነት ማለትም ሰኔ 4 እና 24፣1859 ዓ.ም
ማጀንታና ሰልፈሪኖ ላይ የኦስትሪያ ሀይል ተደመሰሰ፡፡ለውህደት እንቅስቃሴው የመጀመሪያ አመርቂ ድል

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ተመዘገበ፡፡ ከጦርነቱ ማግስት በተደረጉ ስምምነቶች መሰረት ኒስይና ሳቮይ ለፈረንሳይ ተሰጡ፡፡ ኦስትሪያ
ሎምባርዲን ለኢጣሊያ አስረከበች፡፡
በሚቀጥሉት አመታት ለውህደቱ ስኬት መገለጫ የሚሆኑ ተግባራት ተካሂደዋል፡፡ በ 1860 ዓ.ም ጋሪባልዲ
ከሽዎች ጋር /Thousands or red shirts/ ከሰሜን ወደ ደቡብ በመዝመት ሲሲሊንናኔኘልስን ነፃ አወጣ፡፡
በመቀጠል ወደ ሰሜን ያደረገው ግስጋሴ በካቮር እምቢተኝነት ተገታ፡፡ በተመሳሳይ አመት የፓፓል ግዛቶች
ከሮም በስተቀር እና ሌሎች የመካከለኛው የኢጣሊያን ክፍል ግዛቶች ወደ ሰሜን የኢጣሊያን ክፍል ተቀላቀሉ፡፡
ስለዚህ ውህደቱ የላይኛውና የታችኛው የኢጣሊያ ክፍሎች የጋራ ትግል ነበር ማለት ይቻላል፡፡ በሌላ በኩል
ደግሞ ውህደቱ የላይኛው ህብረተሰብ ክፍልና የታችኛው የህብረተሰብ ክፍል አንድነት ትግል ውጤት ነበር፡፡

በ 1861 ዓ.ም ከሮምናቬኒሲያ በስተቀር ሌሎች ግዛቶች በውህደቱ ውስጥ በመቀላቀል የኢጣሊያ ግዛት
/The kingdom of ltaly / ታወጀ፡፡ ቪክተር አማኑኤል የኢጣሊያን ንጉስ ሆኖ ተሾመ፡፡ በ 1866 ዓ.ም
በተደረገው የኘሩሽያና የኦስትሪያ ጦርነት /የሳድዋ ጦርነት/ ኦስትሪያ ስትሸነፍ ኢጣሊያ ለኘሩሽያ
በማገዟ ከጦርነቱ ማግስት በተደረገው ስምምነት ቬንስያን አገኘች፡ መጨረሻዋ የኢጣሊያ ግዛት ሮም
ወደ ውህደቱ የገባቸው ደግሞ የፈረንሳይና ኘሮሽያ ጦርነት ተከትሎ ነበር፡፡ ፈረንሳይ ሮም ላይ
አስፍረው የነበረውን ሰራዊት ከኘሮሽያ ጋር በምታደርገው ጦርነት ስታስወጣ ሮም ነፃ ወጣች ፡፡
የኢጣሊያ ዋና ከተማ ሆና ተመረጠች ውህደቱም በ 1870 ዓ.ም ተጠናቀቀ፡፡
ተግባር፡-6.3
1.የኢጣልያ ውህደት ንቅናቄ ለምን ለረጅም ጊዜ ተካሄደ? ምክንያቶችን መዘርዘር በግልፅ አብራሩ ?
2.ከኢጣሊያ ውህደት ንቅናቄ ወቅት ዲሞክራሲ ሪፐብሊክ እንዲመሰረት የሚፈልጉ መሪዎች እነማን
ነበሩ ?
3.በኢጣሊያ ውህደት ንቅናቄ ወቅት የመሪነት ሚና የነበራት ግዛት ማን ነበረች ?
4.ለኢጣሊያ ውህደት መሳካት ምክንያት የነበሩት ጉዳዩችን በመዘርዘር አብራሩ ?

6.1.3 የጀርመን ውህደት


ልክ እንደ ኢጣሊያ ሁሉ ጀርመን ተዋህዳ አንድነቷን ከመመስረቷ በፊት በአያሌና ደካማ እና ታናናሽ
መንግስታት የተከፋፈለች ነበረች፡፡ እነዚህ ብዛት ያላቸው መንግስታትም አብዛኛውን ጊዜ በጥላቻና እርስ በርስ
በመዋጋት ይታወቁ ነበር፡፡ የውጭ ጠላት የመቋቋም አቅም ስላልነበራቸው በአብዛኛው ለወረራ የተጋለጡና
እንዲሁም በሌሎች ሀያላን ተፅዕኖ ውስጥ መውደቃቸው አልቀረም፡፡ ለጀርመን ውህደት መጀመር የኢጣሊያን
ህዝቦች ንቅናቄ መጠናከር ከፍተኛ የሆነ አዎንታዊ ሚና የነበረው መሆኑ ሌላው የሁለቱ አገሮች ትግል
ተመሳሳይ ባህሪ ነው፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የጀርመን መዋሀድ በአውሮፖም ሆነ በአለም ታሪክ እና ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ለውጥ እንዲታይ ሆኗል ወይም
እንደትልቅ ምዕራፍ ይቆጠራል፡፡

ተግባር፡6.4
ተማሪዎች የጀርመን ውህደት አውን መሆን በአውሮፖም ሆነ በአለም ታሪክ እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ
የሚወሰደው ለምን ይመስላችል?
ለጀርመን ውህደት ንቅናቄ አዎንታዊ ምክንያቶች ና እንቅፋቶች ዘርዝሩ

ለጀርመን ውህደት ንቅናቄ እንቅፋቶች


1.የኦስትሪያና ፈረንሳይ ተቃውም

በምንም አጋጣሚ ኦስትሪያና ፈረንሳይ በአውሮፓ ምድር ጠንካራና የተዋሀደች ጀርመንን ማየት አፈልጉም
ነበር ፡፡ ይልቁንም የተበታተነች አቅም የሌላት ጀርመን ሆና እድትቀጥል ይፈልጉ ነበር ፡

ተግባር 6.5
ተማሪዎች ኦውስትሪያም ሆነች ፈረንሳይ የጀርመንን ውህደት ለምን ተቃወሙ? ምክንያቶችን በግልፅ
አብራሩ፡፡

2.ታናናሽ የጀርመን መንግስታት ለውህደቱ ፍቃደኛ አለመሆን

ታናናሽ መንግስታት ውህደቱን በበጎ ጎኑ ያለማየታቸው ምክንያት ከብዙ አቅጣጫ ሊታይ ይችላል፡፡ በአንድ
በኩል ውህደቱን የእነሱን ህልውና እና ውክልና እዲሁም ጥቅም የሚያሳጣ መስሎ ስለታያቸው በሌላ በኩል
ደግሞ የታላላቅ መንግስታት ተፅዕኖ በማፍራት ለውህደቱ ፍቃደኛ አለመሆን አዝማሚያና በነበረው ሂደት
የመቀጠል ፍላጎት ነበራቸው፡፡
3.የጀርመን ህዝቦች በሃይማኖት ፣ በባህል እና በኢኮኖሚ መለያየት
ለምሳሌ፡- በኢኮኖሚ ረገድ የሰሜን ጀርመን መንግስታት ህዝቦች በንግድና አነስተኛ ኢንዱስትሪ የሚተዳደሩ
ሲሆኑ በስልጣኔም ከደቡብ መንግስታት የተሻለ ደረጃ ነበራቸው፡፡ በተቃራኒው የደቡብ ህዝቦች በእርሻ
የሚተዳደሩ መሆኑ ለውህደቱ እንደ ልዩነቱ መፍጠሪያ መንገድ በመሆን ሂደቱን አጓቶታል፡፡ በሃይማኖት ዘርፍ
ደግሞ የሰሜናዊ ጀርመን ህዝቦች በብዛት የፕሮቴስታንት ዕምነት ተከታይ ሲሆኑ የደቡቦች ደግሞ የካቶሊክ
ዕምነት ተከታይ ነበሩ፡፡ ስለሆነም የሃይማኖት ልዩነት ሌላ መሰናክል በመሆን የውህደቱ ሂደት በማዘግየት የራሱ
ሚና ነበረዉ፡፡

ለጀርመን ውህደት ንቅናቄ አዎንታዊ ምክንያቶች (ዉህደቱን ያፈጠኑ ምክንያቶች )

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

1. ጠንካራ ብሄራዊ ስሜት በጀርመናውያን ዘንድ መፈጠሩ

ጠንካራ የብሄራዊ ስሜት በህዝቦች ዘንድ እንዲኖር የተለያዩ ምሁራን ፣ የታሪክ ሰዎች
፣መፅሐፍት ፣ፍላስፋዎች ወዘተ..ታላቅ ሚና ተጫውተዋል ፡፡

ተግባር 6.6
ጠንካራ ብሄራዊ ስሜት ማለት ምን ነው ? እዴትስ ይመጣል ?

2.የናፖሊወን ጦርነት እና የቬና ጉባኤ (1815 ዓ.ም)


ታላቁ ናፖሊወን ወይም ናፖሊወን አንደኛ መላ አውሮፓን ብሎም በአለም ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለመሆን
በነበረው ህልም በበርካታ የአውሮፓ አገሮች ላይ ጦርነት በመክፈት የሚታቅ ገናና የፈረንሳይ መሪ ነበር፡፡
ከአውሮፓም አልፎ ከ 1799 እስከ 1801 ግብፅ በመውረር ይታወቃል፡፡
የናፖሊወን ጦርነት በጀርመናውያን ዘንድ በሁለት በኩል ውህደቱ እንዲጠናከር አድርጓል፡፡ በአንድ በኩል የጋራ
ጠላታቸውን (የናፖሊውንን
ኃይል) ለመመልከት ልዩነታቸውን በማጥበብ የጋራ አንድነት እዲኖራቸውና ለጋራ ዓላማ እዲነሱ አድርጓል ፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ከጦርነቱ ማግስት ወይም ከናፖሊወን ሽንፈት በኋላ በተደረገው ጉባኤ ወይም የቬና
ስምምነት (1815 ዓ.ም ) የጀርመን መንግስታት ቁጥር ወደ 39 (ኦስትሪያን ጨምሮ)ዝቅ እንዲል በማድረግ
ለመግባባት እና ለጋራ አላማ እንዲነሱ አዎንታዊ ሚና ተጫዉቷል፡፡ በስምምነቱ መስረትም የጀርመን
ኮንፌዴሬሽን ተመስርቷል፡፡ የኮንፌዴሬሽኑ የበላይ ጠባቂ ኦስትሪያ ሆናለች ምንም እንኳን በሌሎች የጀርመን
መንግስታት ዘንድ ኦስትሪያ የማትወደድ ብትሆንም ፡፡

3.የጋራ ገበያ ምስረታ (custom union or zollverein)


በ 1819 ዓ.ም በ 38 የጀርመን አገሮች መካከል የተመሰረተ የጋራ ገበያ ስምምነት ሲሆን ኦስትሪያ ከስምምነቱ
ውጭ በማድረግ የእርስ በእርስ ግንኙነት ለማጠናከር የተመሰረተ የገበያ ስርዓት ነበር ፡፡ ዓላማውም በ 38 ቱ
መንግስታት መካከል የቀረጥ ጫናን በመቀነስ የኢኮኖሚ ትስስርን መፍጠር ወይም ከፖለቲካ ውህደት በፊት
የኢኮኖሚ ውህደትን ለማጠናከር የታቀደ ወሳኝ ስምነት ነበር ፡፡

ተግባር 6.7
የኢኮኖሚ ውህደት ለፖለቲካ ውህደት ያለውን አስተዋጽዖ ግለጹ

የጀርመንን ውህደት በፊታውራሪነት ትመራ የነበረች ፕሩሽያ ስትሆን ውህደቱ ግብ እንዲሚታ ከፍተኛ
መስዋት ያደረጉ መሪዎችም የመጡት ከዚሁ ነበር ፡፡ ለምሳሌ ያህል ዊሊያም አንደኛና ኦቶ ቮን ቢስማርክን
በቀዳሚነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ በ 1862 ዓ.ም ቢስማርክ ለፕሩሽያ ጠቅላይ ሚኒስተር ሆኖ መመረጡ ለጀርመን
ውህደት ትልቁ ምዕራፍ ወይም ወሳኝ ወቅት ተደርጎ ይወሰዳል ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የቢስማርክ ሹመትን ተከትሎ በፕሩሽያ ፓርላማ ውስጥ የነበረውን ውዝግብና አለመግባባት በኃይልም ቢሆን
በመፍትሄ አግኝቷል፡፡ የቢስማርክ የመጀመሪያው እርምጃው የወታደር ግንባታ ሆኗል፡፡ ለወታደር ግንባታውም
ገንዘብ ወሳኝ መሆኑን ያለፓርላማው ፍቃድ የወታደሩን በጀት በመጨመር ጠንካራ ሰራዊት መመስረት ችሏል፡፡
ለፓርላማው ባደረገው ንግግርም የጀርመን ውህደት የሚሳካው በጩኸት ወይም በድምፅ ብልጫ ሳይሆን
በሃይል እና በደም (blood and lron policy) እንደሆነ በግልፅ አስረድቷል፡፡

የጦርነትና ዲፕሎማሲ ምዕራፍ


የሆልሰቲንናሽልዝዊግ
ሁለቱ ግዛቶች ከ 15 ኛው መቶ /ክ/ዘመን ጀምሮ በዴማርክ አስተዳደር ውስጥ የነበሩ ሲሆን በ 1863 ዓ.ም
ክርሲቲያን አንደኛ የሚባለው የዴማርክ ንጉስ ሁለቱን ግዛቶች ሙሉ በሙሉ የዴማርክ አካል እንዲሆኑ
ሲያውጁ ከጀርመንያውያን በኩል ቁጣ አመጣ ፡፡
የጀርመንን ውህደት ተግባራዊ ለማድረግ የቢስማርክ የመጀመሪያው ጦርነትም ከዴንማርክ ጋር ሊሆን ችሏል፡፡
ጠንካራ ሰራዊት ከገነባ በኋላ የቢስማርክ እቅድ የነበረው በዲፕሎማሲና ጦርነት አንድነትን እውን ማድረግ ነበር
፡፡ በዚህም ረገድ ቢስማርክ የዲፕሎማሲ ብቃቱን በመጠቀም የኦስትሪያን እርዳታ አገኘ፡፡ በ 1864 ዓ.ም
የመጀመሪያውን ጦርነት ከዴንማርክ ጋር በማድረግ ድል አስመዘገበ፡፡ ከጦርነቱ ማግስት በተደረገ ስምምነት
ሆልስቲን ለኦስትሪያ ስትሸጥ ሽልዝዊግ ደግሞ ለፕሩሽያ ተመለሰች፡፡

የቢስማርክ ጠላትን በተናጠል የማጥቃት ስልት ኦስትሪያ ተጠናክሮ ቀጠለ ፡፡ ኦስትሪያ ቁጥር አንድ የጀርመን
ውህደት ጠላት መሆኑን በመረዳት ሁለተኛ ጦርነት ከኦስትሪያ ጋር በ 1866 ዓ.ም ተደረገ ፡፡ ይህም ጦርነት
የሳድዋ ጦርነት ወይም የሰባት ስምንት ጦርነት ይባላል፡፡ በዚህ ጦርነት ፕሩሽያ ለኢጣልያ ጋር በመተባበር
ኦስትሪያ ድል አደረገች፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ የተመዘገበው ድል ለፕሩሽያ ውህደት ትልቅ ስኬት ነበር ፡፡ ከጦርነት
በኋላ በተደረገ ስምምነት መሰረት ፡
 ቬኒሲያ ለኢጣልያ ተሰጠች
 ሆልስቲን የኦስትሪያ አካል ሆነች
 በጀርመን ኮንፌዴሬሽን የኦስትሪያን የበላይነት አከተመ
 በ 1867 ዓ.ም የሰሜን ጀርመን ኮንፌዴሬሽን በፕሩሽያ የበላይነት የተመሰረተ፡፡

ነገር ግን የደቡብ ጀርመን መንግስታት እስካሁን ድረስ የውህደቱ አካል አልሆኑም ፡፡ ሆኖም የጀርመን
ውህደት በስኬት ጎዳና ለሆኑን ማወቅ ይቻላል ፡፡ለጀርመን ውህደት የመጨረሻው እና ወሳኝ ጦርነት
የሰዳን ጦርነት ነበር፡፡ የተኬሄደውን ከ 1870 እስከ 1871 ዓ.ም ነበር::
ተግባር 6.8
- ኮንፌደሬሽን ማለት ምን ማለት ነው ? የጀርመን ኮንፌደሬሽን ለመጀመሪያ ጊዜ መቼ ተመሰረተ?

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የሰዳን ጦርነት የተከሄደው በጀርመንና በፈረንሳይ መካከል ሲሆን የጦርነቱ ውጤትም በጀርመን የበላይነት
ተጠናቋል፡፡ በዚህ ጦርነት ወቅት የደቡብ ጀርመን መንግስታት ከሰሜን ጀርመን ጋር በመቀላቀል የጋራ
ጠላታቸውን (በፈረንሳይ) ማሸነፍ ችለዋል ፡፡ በናፖሊወን 3 ኛ የሚመራው የፈረንሳይ ሰራዊት ተሸነፈ
ቀጥሎም የፍራንክፈርት ስምምነት ተደረገ፡፡

በፍራንክፈርት ስምምነት የተወሰኑ ጉዳዮች ወይም ውሳኔያቸው


1. አልሳስናሎሬን የተባሉ ሁለት በማዕድን የበለፀጉ የፈረንሳይ ግዛቶች ለጀርመን ተሰጡ
2. ፈረንሳይ ለጦርነቱ ተጠያቂ በመሆናን የጦር ካሳ እንድትከፍለው ተወሰነ፡፡
3. ክፍያው እስኪጠናቀቅ ድረስ የጀርመን ሰራዊት በፈረንሳይ ድንበር እንዲቆይ ተወሰነ

ስለዚህ የጀርመን ውህደት በ 1871 ዓ.ም በድል ተጠናቀቀ፡፡ ለውህደቱ መጠናቀቅ የሰሜኑ የጀርመን ክፍል
ትልቁን ድርሻ ወይንም አስተዋፅኦ ይወስዳል፡፡ ዊሊያም 1 ኛ የጀርመን ንጉስ ነገስት ሲሆን ቢስማርክ ደግሞ
መርዓተ መንግስት (chancellor) ሆኗል፡፡

6.1.4 የአሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት (እ.ኤ.አ 1861-65)


መግቢያ፡- የአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት የተካሄደው ዛሬ ታላቋ አሜሪካ ብለን በምንጠራት (USA) ህዝቦች
መካከል ሰሜንና ደቡብ ተብለው በመከፋፈል የተደረገ ጦርነት ሲሆን መንስኤዎች በተለያዩ ዘርፎች
ይመደባሉ፡፡ የአሜሪካ ህዝቦች ከተለያዩ ሀገሮች በተለያዩ ምክንያቶች የሰፈሩ እና ብዝህነት ጎልቶ
ከሚታይባቸው የአለማችን ህዝቦች ተርታ ይሰለፋሉ፡፡ ጦርነቱ የተካሄደው 23 በሚደርሱ የሰሜን አሜሪካ እና
በ 11 የደቡብ አሜሪካ ግዛቶች መካከል ነበር፡ የሰሜን ግዛቶች ውህደት ፈላጊዎች ሲሆኑ የደቡቦቹ ደግሞ
መገንጠልን የሚፈልጉ ነበሩ፡፡
የጦርነቱ ምክንያትች
1.ኢኮኖሚያዊ ምክንቶች

የደቡብ አሜሪካ መንግስታት የኢኮኖሚ መሰረታቸው እርሻ ሲሆን የባሪያ ጉልበት ደግሞ ዋነኛው የጉልበት
ምንጭ ነበር፡፡ የእርሻ ዘዴው ዘመናዊ ሳይሆን ሰፊ የሰው ጉልበትን መሰረት ያደረገበት ሲሆን በተቃራኒው
የሰሜን አሜሪካ መንግስታት ደግሞ ኢኮኖሚያቸው የተመሰረተው በንግድና ኢንዱስትሪ ሲሆን ባርነትን
ወይም የባሪያ ጉልበትን ይቃወሙ ነበር፡ በሌላ በኩል ደግሞ የደቡብ አሜሪካ ግዛቶች ወደ አገር የሚገቡ
ሸቀጦች ዝቅተኛ ቀረጥ እንዲጣልባቸው ሲፈልጉ ሰሜኖች ደግሞ ከፍተኛ ቀረጥ እንዲጣልባቸው ይፈልጉ
ነበር፡፡ የሰሜኖቹ ዋና አላማ የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ውጤትን ለማበረታት እና ኢንዱብትሪያቸው
እንዲያድግ በማሰብ ነበር፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ተግባር፡- 6.9
- ተማሪዎች ከውጭ ሀገሮች በሚገቡ ሸቀጦች ላይ ወይም ዕቃዎች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ መጣል ምን አገራዊ
ፋይዳ አለው? ክፍል ውስጥ በቡድን በመሆን ተወያዩበት፡፡

2.ፖለቲካዊ ምክንያት

የሰሜን አሜሪካ ግዛቶች ፌደራላዊ መንግስትን ሲደግፍ የደቡብ አሜሪካ ግዛቶች ኮንፌዴሬሽን እንዲመሰረት
ይፈለጉ ነበር፡፡ በዚህም አግባብ ሰሜኖች የጋራ የሆነ ህገ-መንግስታዊ መብት መከበርን ሲደግፉ ደቡቦች ደግሞ
እያንዳንዱ መንግስት የግል መብት መከበር ላይ ትኩረት ያደርጉ ነበር፡፡

3.ማህበራዊ ምክያት

የባርነት ጉዳይ በሁለቱ የአሜሪዊ ህዝቦች ዘንድ የጥላቻ ወይም ቅራኔ መፈጠር ዋነኛ ምክንያት ነበር፡፡ ይህም
ማለት የሰሜን አሜሪካ ህዝቦች የባሪያ ጉልበት መጠቀምን ሲቃወሙ የደቡብ አሜሪካ ህዝቦች ደግሞ የባሪያ
ጉልበት ዋና ተጠቃሚ ነበሩ፡፡ ምንም እንኳ የሰሜን አሜሪካ ህዝቦች ባርነት እንዲጠፋ በይፋ ባያዉጁም ወደ
ሌሎች ግዛቶች እንዲስፋፋ አይፈልጉም ነበር፡፡ የደቡብ አሜሪካ ህዝቦች የሰሜኖችን ጥቃት በመፍራት
መገንጠልን እንዳዋና መፍትሄ ለመውሰዳቸው ለእርስ በርስ ጦርነቱ መጀመር ዋነኛ ምክንያት ሊሆን ችሏል፡፡

ተግባር፡- 6.10
የባርነትና የባሪያ ንግድ ልዩነት ምንድን ነው ?

ከላይ የጠቀስናቸውን ዋና ዋና ምክንያቶች እንዳሉ ሆነው በሰሜንና በደቡብ አሜሪካ ግዛቶች መካከል ቅራኔ
እንዲጨምር ያደረጉ ወይም እንዲፈጠር ያደረጉ ምክንያቶች አልጠፉም፡፡ ለምሳሌ በ 1850 ዎቹ የደቡብ
አገሮች የዲሞክራቲን ፖርቲው የምክር ቤት ውክልና በሰሜን የሪፐኘሊካን ፖርቲው ብልጫ ሲወሰድባቸው
የደቡቦች የመገንጠል ሀሳብ እንዲጠናከር አድርጓል፡፡ ምክንያቱም በደቡቦች ህዝቦች ዘንድ የሰሜኖች የፖለቲካ
ስልጣን የበላይነት መብቱ ለባርነት መጥፋት ስጋት ነው ብለው ያስቡ ስለነበር ነው፡፡ በእርግጥ ከጥንት ጀምሮ
የደቡብና የሰሜን አሜሪካ ግዛቶች የም/ቤት ውክልና ልዩነት ውዝገብ ሲያስነሳ የቆየ ጉዳይ ነበር፡፡ ነገር ግን
ለመገንጠል የሚያደርስ አልነበረም፡፡ በመደራደርና በመግባባት ልዩነታቸውን ሲፈቱ ቆይተዋል፡፡ የሪፐብሊካኑ
ፖርቲ በ 1854 ዓ.ም ከተመሰረተ በኃላ የብዙ አሜሪካንን ቀልብ መማረክ መጀመሩ ብሎም የቀድሞ ታዋቂ
ሰዎችና የዲሞክራቲክ ፖርቲ አባላትን ድጋፍ ማግኘቱ ለደቡብ አሜሪካዉያን የራስ ምታት መሆኑ አልቀረም፡፡
ስለዚህ የደቡብ አሜሪካ ህዝቦች መገንጠል አማራጭ የሌለው መፍትሄ አድርገው ተነሱ፡፡ በ 1859 ዓ.ም
በጆንብራውንስ አማካኝነት የተሞከረ የፀረ-ባርነት አመፅ የደቡቦች ልብ እንዲሸፍት በማድረግ ብሎም አብሮ
የመኖርን ተስፋ በማጨለም የመገንጠልን ጥያቄ የበለጠ አጠናክሯል፡፡ ብራውንስ የሞከረው እንቅስቃሴ
መጨረሻው ተይዞ በአገር መክዳት ወንጀል ተፈርጆ የሞት ቅጣትም ተፈረደበት፡፡ ይህ ያልተሳካ ሙከራ የደቡብ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

አሜሪካ ህዝቦች የሰሜን ህዝቦች በተመሳሳይ አይን እንዲያዩዋቸዉ አድርጓል ማለትም ሁሉም የሰሜን
አሜሪካ ህዝቦች የፀረ-ባርነት አቋም እንዳላቸው በማሰብ በመገንጠልም እንደመፍትሄ ተወስዷል፡፡

በ 1860 ዓ.ም የአብርሀም ሊንከን ሪፐብሊካን ፖርቲውን በመወከል የአሜሪካ ኘሬዘዳንት ሆኖ መመረጥ
ሌላኛዉ የመገንጠልን ጥያቄ ያባባሰ ምክንያት ነበር፡ ምክንያቱም በደቡብ ህዝቦች ዘንድ አብርሀም ሊንከን
የፀረ-ባርነት አቋም እንዳለው በማሰብ ስልጣን በመያዙ የመጀመሪያው እርምጃ ባርነትን ማጥፋት ይሆናል
ማለታቸው አልቀረም፡፡ በእርግጥ አብርሀም ሊንከን ከመመረጡ በፊት 7 የደቡብ አገሮች /በባሪያ ጉልበት
የሚተዳደሩ/ በይፋ መገንጠላቸውን አሳውቀዋል፡፡ በአብርሀም ሊንከን መመረጥ በኃላ የሌሎች አራት አገሮች
ተጨምረው በአጠቃላይ የተገንጠሉ አገሮችን ብዛት 11 አደረጋቸው፡፡ እነዚህ አገሮች አንድ ላይ በመሆን
የራሳቸውን ኮንፌዴሬሽን መሰረቱ፡፡ ኮንፌዴሬሸኑ በጀፈርሰን ዴቪስ ይመራ ነበር፡፡ በእርግጥ ሁሉም በባሪያ
ጉልበት የሚተባዳደሩ መንግስታት ወደ ኮንፌዴሬሸኑ ተቀላቅለው ማለት አይቻልም፡፡ ለምሳሌ በደቡብና ሰሜን
አሜሪካ ድንበር አካባቢ የነበሩ አራት በባርነት የሚተዳደሩ (slave states) መገንጠልን በመተው ከውህደት ጋር
መቆየትን መርጠዋል፡፡ አገሮችም ሚሶሪ ፣ ዴላዌር ፣ ሜሪላንድ እና ኬንቱኪ ነበሩ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቨርጂኒይ
ለሁለት ተከፈለች፡፡ ሰሜን ምዕራብ ቬርጂኒያ ውህደቱን ስትደግፍ ደቡብ ቬርጂኒያ ደግሞ በመገንጠል
ኮንፌዴሬሽኑን ተቀላቅላለች፡፡ ከዚህም አልፎ የኮንፌዴሬሽኑ መቀመጫ ከተማ /ሬችሙንድ/ ከቪርጅንያ
ከተማሪዎች አንዷ ነበረች፡ በሌላ በኩል ደግሞ በሁለቱም ወገን /በሰሜንና በደቡብ/ የተቀላቀለ አመለካከት
የነበራቸው ህዝቦች መኖራቸው አልቀረም፡፡ለምሳሌ የካሊፎርኒይ /በውህደቱ ውስጥ የነበረች/ 20 ፐርሰንት
የሚሆኑ ህዝቦች የደቡብ ዲሞክራቲክ ፖርቲ ተወካይ ለነበረው ዕጩ ድምፃቸውን ሰጥተዋል፡፡

የእርስ በእርስ ጦርነቱ ሂደት

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ሚያዝያ 12፤1861 ዓ.ም የደቡብ ወታደሮች በፌዴራሉ /የሰሜን/ ወታደር ላይ የመጀመሪያውን ተኩስ
ሲከፍቱ የጦርነቱ አይቀሬነት ይፋ ሆነ፡፡ ይህን ድርጊት ተከትሎ አብርሀም ሊከን የመገንጠልን ጥያቄ
ውድቅ በማድረግ ሁሉም የሰሜን ግዛቶች ሰራዊት እንዲልኩ አዘዙ፡፡ የእርስ በእርስ ጦርነቱም በ 11
የደቡብ ግዛቶች (confederate states of America led by Jefferson Davis) እና በ 23 የስሜን ግዛቶች
(Unionists led by Abraham lincoin) መካከል በይፋ ተጀመረ፡፡
ተግባር 6.11
ተማሪዎች የአሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት አላማ ምንድን ነው ? ከተወያያችሁ በኃላ መልሱን ሪፖርት አድርጉ
?

ጦርነቱ እንደተጀመረ በመጀመሪያቹ አመታት ድል ለደቡብ አሜሪካውያን ሆኖ ነበር ምክንያቱም ጦርነቱ


ለእነሱ የመከላከል አይነት ባህሪ ስለነበረው እና እንዲሁም በመጀመሪያው ምዕራፍ የተሻሉ የጦር መሪዎች
ስለነበሩ ህዝቦችም በቆራጥነት ስለታገሉ የተሻለ የማሸነፍ አጋጣሚዎች ነበሩዋቸው፡፡ ከ 1863 በኃላ ደግሞ
በተቃራኒው ድል ወደ ስሜን አሜሪካም ሆነ፡፡ ለዚህም ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡-
የህዝብ ብዛት
የሰለጠነ የሰው ሀይል
የሀብት ብልጫ
 የመሰረተ ልማቶች ብልጫ
የእርሻ ምርት የበላይነት /ብልጫ/ ከጥጥ በስተቀር
በተሻለ /ጥሩ/ የአመራር ብቃት መኖር
የአብርሀም ሊንከን የነፃነት አዋጅ በ 1862 ታወጆ በ 1863 ዓ.ም ተግባራዊ መሆን የባሪያ አመፅን
በማበረታታት የደቡቦችን ሀይል በማዳከም የሰሜኖችን ሀይል አጠናክሯል፡፡

በዚህ ምክንያቶች የማታ ማታ በሰሜን አሜሪካ የበላይነት ጦርነቱ ተጠናቋል፡፡ ምንም እንኳ ደቡብ
አሜሪካውያን በጦርነቱ ወቅት እንግሊዝና ፈረንሳይ ያግዙናል ብለው ቢገምቱም ያሰቡት ሳይሆን ቀርቶ
በፍፁም የበላይነት በበሜኖች ተሸንፈው እጅ ሰጡ፡፡

ተግባር 6.12
ደቡብ አሜሪካዉያን ለምን የእንግሊዝና ፈረንሳይን እርዳታ ተስፋ አደረጉ? ተማሪዎች እስኪ ምክንያቱን
መፅሀፍ በማንበብ ወይም የታሪክ ሰዎችን መጠየቅ መልሱን ለክፍል ሪፖርት አድርጉ

የጦርነቱ ውጤቶች
ከአራት አመታት በላይ የፈጀው የእርስ በእርስ ጦርነት በ 1865 ዓ.ም ሲጠናቀቅ በርካታ ማህበራዊ ፣
ኢኮኖሚይዊ እንዲሁም ፖለቲካዊ ውጤቶች ነበሩት፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

1.የውህደቱ እውን መሆን /የመገንጠል ጥያቄ አከተመ/


2.የህዝብ እልቂት፣ ከሁለቱም ወገን ከ 620,000 በላይ ህይወታቸውን አጥቷል፣
3.የባርነት ስርዓት በ 13 ኛው የህገ መንግስት ማሻሻያ ባርነት እንዲጠፋ ሲታወጅ በ 14 ኛው ማሻሻያ
የዜግነት መብት ለባሮች ተሰጥቷል፡፡ በ 15 ኛው ማሻሻያ ደግሞ የመምረጥ መብት ተሰጥቷቸዋል፡፡
4.የአብርሀም ሊንከን በነጭ አፍቃሪ ደቡብ ጆን ዊክስ ቡዝ በተባለ ግለሰብ መገደል፣
5.ክላራ ባርተን /የፌዴራል ነርሶች መሪ/ የጦር ጀግና እንዲሁም አዳኝ መላክ /Angle of the battle field/
የሚል ስያሜ ተሰጥቷል፣
6.የደቡብና የስሜን አሜሪካ ህዝቦች ቅራኔ ለብዙ አመታት እንዲቀጥሉ ሆነዋል፡፡ ለምሳሌ ከ 1876-1964
ዓ.ም ጆርጅያ፤ አላባማ፤ ሚሲሲፒ እና አርካንሳስ የሚባሉ ግዛቶች በመቶ አመት ውስጥ አንድም ጊዜ
ለሪፐብሪካኑ ፖርቲ ድምፅ አለመስጠት ከጥላቻ መገለጫዎች አንዱ ነው፡፡
7.የገንዘብ ኪሳራና የንብረት ውድመት ይህን መልሶ ለማቋቋም ከ 1866 – 77 ዓ.ም ድረስ የመልሶ
ማቋቋም ኘሮግራም ተዘርግቷል፡፡

6.1.5 አንደኛው የአለም ጦርነት /እ.ኤ.አ 1914-1918/

ተግባር 6.13
ተማሪዎች አንደኛው የአለም ጦርነት በባህሪው ምን አይነት ጦርነት እንደነበር ታውቃላችሁ

የአንደኛው አለም ጦርነት ኢምፔሪያሊስቶች ፍላጎታቸውንና አላማቸውን ለማሳካት ያካሄዱት ጦርነት ነው፡፡
ለነፃነት፣ ለሰላም ፣ ለዲሞክራሲ ወዘተ የተደረገ ጦርነት አልነበረም፡፡ ስለዚህ አንደኛው የአለም ጦርነት
በባህሪው የኢምፔሪያሊዝም ጦርነት ነው ለማለት ያስችላል፡፡ በዘመኑ የነበሩ የአውሮፖ ኃያላን መንግስታት
መካከል ቅኝ ግዛቶች፣ የተፅዕኖ አካባቢዎች ወዘተ በድጋሜ ለመቃረጥ የተካሄደ ጦርነት ነው፡፡

የአንደኛው የአለም ጦርነት መሰረታዊ ምክንያቶች


ተግባር 6.14
ተማሪዎች የጦርነቱን መንስኤዎች ታውቃላችሁ
ለአንደኛው የአለም ጦርነት መካሄድ መሰረታዊ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
እነሱም፡-
1. ኢምፔሪያሊዝም (Imperialism)

ኢምፔሪያሊዝም ማለት ምን ማለት ነው ?


ተግባር፡- 6.15
ኢምፔሪያሊዝምና የካፒታሊዝም አንድነትና ልዩነት ግለፁ
ተማሪዎች ኢምፔሪያሊዝም የአንደኛው የአለም ጦርነት መንስኤ ነው ሲባል ምን ማለት ነው ?

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 ኢምፔሪያሊስት ደረጃ በደረሱት የአውሮፖ ሀያላን መንግስታት መካከል አፍሪካን በቅኝ ግዛት
ለመያዝና የኢኮኖሚ የበላይነት ለማግኘት የታየን ከፍተኛ ፍክክር ነው፡፡ ኢምፔሪያሊዝም ብለን
የምንጠራው ለምሳሌ ከ 1 ኛው የአለም ጦርነት በፊት ከታዩት ከፍተኛ ፋክክሮች የሚከተሉት
ይገኙበታል ፡፡
 ፈረንሳይና ጀርመን ሞሮኮን ለመቀራመት ባደረጉት ፋክክር ሁለት ጊዜ በ 1905 እና በ 1911 ከጦርነት
ጫፍ ደርሰዉ ተመልሰዋል፡፡
 ፈረሳይና ጣሊያን ቱኒዥያን በቅኝ ግዛት ለመይዝ /በ 1881/ ተፎካክረው ነበር፡፡
 ሩሲያና አውስትሪያ-ሃንጋሪ የባልካን ሀገሮችን ለመቆጣጠር በከፍተኛ ደረጃ ይፎካከሩ ነበር፡፡
 እንግሊዝና ጀርመን በአፍሪካና በመካከለኛው ምስራቅ ቅኝ ግዛት ለመያዝና ገቢያ ለማግኘት
ትንቅንቅ ውስጥ ገብተው ነበር፡፡

2. ብሔርተኝነት /Nationalism/

ተግባር፡6.16
ተማሪዎች ብሄርተኝነት እንዴት የአንደኛው የአለም ጦርነት መንስኤ እንደሆነ በቡድን ተወያዩ፡፡
ለአንደኛው የአለም ጦርነት መካሄድ በተለያዩ ሀገሮች የብሄርተኝነት ስሜት መቀስቀስ ምክንያት ነበር፡፡
ለምሳሌ ብንጠቅስ
የጀርመን ብሄርተኝነት (German nationalism)

የጀርመን መንግስት ከውህደት በኃላ ቅኝ ግዛት ለመያዝ ከፍተኛ ፍላጎት አደረበት፡፡


በመሆኑም ቅኝ ግዛት ለመያዝና ለበለጠ ጥቅም ለማግኘት ከቀደምት የቅኝ ግዛት ባለቤቶች ጋር ከፍተኛ
ፋክክር አደረገ፡፡
የፈረንሳይ ብሄርተኝነት (French Nationalism)

ከ 1870-71 በጀርመንናፈረንሳይ መካከል በተደረገው ጦርነት ፈረንሳይ በመሸነፏ፤ ጀርመን የፈረንሳይን ሁለት
ግዛቶች ማለትም አልሳስናሎሬንን ነጥቃለች፡፡ስለዚህ ፈረንሳይ እነዚህን ግዛቶች ለማስመለስና ለመበቀል
አጋጣሚ በመጠቀም ላይ ነበረች ፡፡
የባልካን ብሄርተኝነት (Balkan Nationalism)

በደቡብ ምስራቅ አውሮፓ የሚገኙት የባልካን አገሮች ከቱርክ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት የብሄርተኝነት ስሜት
ተቀጣጥሎባቸው ነበር፡፡ በተለይ በሰርቢያ ሕዝብ ዘንድ ታላቋን ሰርቢያ ለመመስረት ከፍተኛ ፍላጎት ነበር፡፡
ስለሆነም የሰርቢያ መንግስት በአውስትሪያ- ሀንጋሪ ግዛት የሚኖሩት ሰርቦች ገንጥሎ ወደ ሰርቢያ ለመቀላቀል
ትልቅ ምኞት ነበረው፡፡ በዚህ የተነሳ የሰርቢያና የአውስትሪያ- ሀንጋሪ መንግስታት ከፍተኛ ፍጥጫ ወይም ቅራኔ
ውስጥ ገብተው ነበር፡፡

3. ጦርኝነት (militarism)

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ተግባር 6.17

ተማሪዎች ጦርኝነት ማለት ምን ማለት ነው ?

የአውሮፓ ኃያላን መንግስታት በመካከላቸዉ በነበረው ከፍተኛ ፉክክር የተነሳ የወታደራዊ አቅማቸውን
ለማጠናከር ሩጫ ውስጥ ገብተው ነበር፡፡ እንግሊዝና ጀርመንም እንዱ አንዱን ለመቅደም የባህር ሀይል
ግንባታቸውን ተያያዙት፡፡

4. የወታደራዊ ቡድኖች መፈጠር (formation of military alliances)

የአንደኛ የአለም ጦርነት ከመጀመሩ ቀደም ብሎ አውሮፓ በሁለት ወታደራዊ ካምፕ ወይም ቡድን ተካፍላ
ነበር፡፡ እነሱም ፡-ትሪፕል አሊያንስ እና ትሪፕል ኢንተንት በመባል ይታወቃሉ ፡፡በመቀጠል አንድ ባንድ
እንመለከታቸዋለን ፡፡
1.ትሪፕል አሊያንስ (የጀርመን ፣የአውስትሪያ- ሃንጋሪና የኢጣልያ ህብረት )
በ 1879 የአውሮፓ መአከላዊ ሃያላን የነበሩት ጀርመንና ኦውስትሪያ-ሃንጋሪ በህብረት ጠላትን የመከላከል
ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረሙ ፡፡ ከሶስት አመታት በኋላ በ 1882 ዓ.ም ኢጣልያ ህብረቱን ተቀላቀለች
፡፡ በዚህም የጀርመን፤ የኦውስትሪያ- ሃንጋሪና የኢጣልያ ንብረት ተከናወነ ፡፡
ተግባር ፡6.18
ተማሪዎች ለጀርመን፤አውስትሪያ
ሃንጋሪና ኢጣልያ ህብረት መፈጠር ምክንያቶችን መጽሀፍ በማንበብ ወይም የታሪክ መምህራንን በመጠየቅ
ተረዱ ፡፡

2.ትሪፕል ኢንተንት (የፈረንሳይ ፤ሩሲያና እንግሊዝ ህብረት )


ፈረንሳይ ጀርመንን ለመውጋትና የተወሰደባትን ግዛቶች ለማስመለስ ከሩሲያ ጋር ለመወዳጅነት ፈለገች ፡፡
በ 1894 ፈረንሳይናሩሲያ የሁለትዮሽ የህብረት ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ ከ 10 አመት በኋላ 1904 ፈረንሳይ
እና እንግሊዝ በቅኝ ግዛት ላይ የነበራቸውን አለመግባባት በመፍታት የጋራ ስምምነት ላይ ደረሱ
(entente cordiale):: ከሶስት አመት በኋላ በ 1907 እንግሊዝና ሩሲያ በሩቅ ምስራቅ በተለይም በኢራንና
ቻይና ላይ ይከተሉት የነበረውን የፖሊሲ ልዩነት ለማቻቻል ተስማሙ ፡፡ በዚህም መሰረት የፈረንሳይ ፤
ሩስያ እና እንግሊዝ ህብረት ተጠናቀቀ ፡፡
ተግባር፡-6.19
ተማሪዎች በእንግሊዝናፈረንሳይ መካከል ስለነበረው ከፍተኛ የቅኝ ግዛት ፉክክር በምሳሌ በማስደገፍ ግለጹ፡፡

5. ዓለማቀፋዊ ስርዓት አልበኝነት (international anarchy)

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ተግባር ፡-6.20
ተማሪዎች በአለንት ዘመን በሀገሮች መካካል አለመግባባት ሲፈጥር የሚሸመግላቸው አለም አቀፍ
ድርጀት ማን እደሆነ ታውቃላችሁ?

ከአንደኛው የአለም ጦርነት በፊት በሃገሮች መካካል አለመግባባት ቢፈጠር ወደ ጦርነት ከመሸጋገራቸው በፊት
የሚሸመግል ጠንካራ አለማቀፋዊ ድርጀት አልነበረም ፡፡ በ 1899 በሄግ ከተማ የተቋቋመው የአለም ፍርድ
ቤትም (hague tribunal) በአቅም ማነስ የተነሳ ሀገሮችን አስገድዶ የመዳኘት ሀይል እና የሰጠውን ውሳኔ
ተፈፃሚ የማድረግ ጥንካሬ አልነበረውም ፡፡ስለዚህ ሥርዓት አልበኝነት ሰፍኖ ነበር ለማለት ይቻላል፡፡
የጦርነቱ ፍንዳታ (outbreak of WWI)

ተግባር፡ 6.21
ተማሪዎች ለአንደኛው የአለም ጦርነት መፈንዳት የቅርብ መንስኤ (Immediate cause) ምንድን ነው?

ለአንደኛው የአለም ጦርነት መፈንዳት ሰበብ የሆነው የአውስትሪያ-ሀንጋሪ መስፍንና አልጋወራሽ የነበሩት
ፍራንሲስ ፈንዲናንድና ባለቤታቸው ሶፍያ በቦሲኒያ ዋና ከተማ ሳራጅቮ በጉብኝት ላይ እንዳሉ በሰኔ 28 1914
ዓ.ም መገደላቸው ነው፡፡ ግድያውን የፈፀመው የሰርቢያ ተወላጅ የሆነው ጋቭሪሎ ፕሪንሲፕ በመሆኑ
አውስትሪያ-ሀንጋሪ በሰርቢያ ላይ በሐምሌ 28 ቀን 1914 ዓ.ም ጦርነት አወጀች፡፡

ሩሲያ ወዳጇን ሰርቪያን ለመርዳት ጦሯን አንቀሳቀሰች፡፡ ጀርመንም የሩስያን እንቅስቃሴ በመቃወም በነሀሴ 2
ቀን በሩሲያ ላይ በነሀሴ 3 ቀን በፈረንሳይ ላይ የጦር አዋጅ አስተላለፈች፡፡ ጀርመን ፈረንሳይን ለመውጋት
ገለልተኛ ቤልጀየምን እንደመሸጋገሪያ ድልድይ ተጠቅማለች፡፡ እንግሊዝ ጀርመንን ለመውጋት ከጦርነቱ
መግባቷን አስታወቀች፡፡
ይህ ጦርነት ቀስ በቀስ ሌሎች መንግስታትንም እየጨመረ ወደ አለም ጦርነት እየተስፋፋ መጣ፡፡
ቱርክና ቡልጋሪያ ጀርመንና አውስትሪያ - ሀንጋሪን (ማዕከላዊ ሀይሎችን) በመደገፍ በጦርነቱ ገቡ፡፡
የፈረንሳይ ፣ የሩስያንና የእንግሊዝን ቡድን በመደገፍ ደግሞ ወደ ሰላሳ የሚደርሱ ሀገሮች በጦርነቱ
ተሰለፋ፡፡ ከእነዚም መካከል ዋና ዋናዎቹ ጃፖን ፣ ኢጣልያና ፣ አሜሪካ ናቸው፡፡ እነርሱም የተባበሩት
ኃይሎች (Alliied powers) በመባል በታሪክ ይታወቃሉ፡፡
ተግባር፡- 6.22
ተማሪዎች ኢጣሊያ ከትፊኘል ኢልያንስ ወጥታ ወደ ትሊኘል ኢንተንት የገባችበት ምክንያት ምንድን ነው?
አሜሪካ ወደ ጦርነቱ የገባችበት ምክንያትስ ምንድን ነው?
የአሜሪካ በጦርነቱ መሳተፍ ያመጣው ለውጥ ምንድን ነው?

4.1.2 የጦርነቱ ዋና ዋና ግንባሮችና የጦርነቱ ፍፃሜ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የአንደኛው አለም ጦርነት በሶስት ዋና ዋና ግንባሮች ተካሂዷል፡፡ እነሱም፡-


የምዕራብ ጦር ግንባር፡- በዚህ ጦር ግንባር ጀርመን ከፈረንሳይ፤ ከእንግሊዝና ከአሜሪካ ጦሮች ጋር
ተፋልማለች፡፡ ወሳኝ ጦርነቶች የተካሄዱት በዚህ ግንባር ነበር፡፡ ከዚህ በፊት ለጦርነት ያልዋሉ እንደ
አውሮኘላን ፣ ታንክ ፣ መድፍ ፣ የመርዝ ጋዝ የመሳሰሉት የጦር መሳሪያዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ውጊላ
የዋሉት በዚህ ግንባር ነበር፡፡
የምስራቅ ጦር ግንባር፡- በዚህ ጦር ግንባር ሩሲያ በአንድ ወገን ጀርመንና አውስትሪያ ሀንጋሪ በሌላ
ወገን በመሆን ተዋግተዋል፡፡ በዚህ ግንባር ሩስያ ከፍተኛ ሽንፈት ደርሶበታል፡፡ ከዚያም በ 1917 ዓ.ም
የሶሻሊስት አብዩት በሩሲያ በመፈንዳቱ ሩሲያ ከጦርነቱ ልትወጣ ችላለች፡፡
የደቡብ ጦር ግንባር፡- በዚህ ጦር ግንባር ሁለቱም ቡድኖች ከፍተኛ ፍልሚታ አካሂደዋል፡፡ በ 1917 ዓ.ም
ጀርመንና አውስትሪያ- ሀንጋሪ አብዛኛውን የባልካን ግዛት መቆጣጠር ችለው ነበር፡፡ ነገር ግን
የተባበሩት ኃያላት (Alied power) በ 1918 ባደረጉት ጥቃት ከፊሉን የባልካን ግዛት ነፃ አውጥተው
አውስትሪያ- ሀንጋሪ በመሸነፏ ከጦርነቱ ወጣች፡፡ ቀደም ብለው ቱርክና ቡልጋሪያ ከጦርነቱ የወጡ
ሲሆን በመጨረሻም ጀርመን መሸነፏን በመቀበል በህዳር 11 ቀን 1918 ዓ.ም ተኩስ ለማቆም
ተስማማች፡፡ በዚህ መልኩ የአንደኛው የአለም ጦርነት ፍፃሜ ሆነ፡፡ በመቀጠልም የፖሪሱ የሰላም
ጉባኤ ተጠራ፡፡

6.1.6 የፋሽስታዊ ስርዓት በጣሊያንና የናዚ ስርዓት በጀርመን መከሰት


ተግባር 6.23
-የፋሽስታዊ ስርዓት በጣሊያንና የናዚ ስርዓት በጀርመን መከሰት በአለም ምን ችግር አስከተለ?
-የፋሽስታዊ ስርዓት በጣሊያንና የናዚ ስርዓት በጀርመን ሲመሰረቱ በህዝብ ዘንድ ለምን ድጋፍ አገኙ?

የመጀመሪያው የአለም ጦርነት አሸናፊዎች ዋና አላማ አንዱ አለምን ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት
የሰፈነባት ለማድረግ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ጀርመን ዲሞክራሲያዊ ህገ-መንግስት ስትመሰርት ሌሎችን
በተመሳሳይ መልኩ መሄድ ጀምረዋል፡፡
ነገር ግን በ 1920 ዎቹ በጣሊያን የፋሽስት ስርዓት መሰንፋራት ጀመረ፡፡ በ 1922 የፋሽስት ፖርቲ በቤኒቶ
ሞሰለኒ ተመሰረተ፡፡ አላማውም ጣሊያንን ወደ ሮማ የአፄ ዘመን ግዛት ክብር ለመመለስ እንዲሁም የጣሊያንን
ብሄርተኝነት ለማጉላት ነበር፡፡ የአስተዳደር ስርዓቱ ሌላ መገለጫ ወታደራዊ አንባገነንነትና ስልጣንን ጠቅሎ
መያዝ ይገኙበታል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ አዶልፍ ሂትለር በጀርመን የናዚ ፖርቲን በመመስረት ስለጀርመን ብሄር የበላይነት ብቻ
በመስበክ ህዝቡን ወደሱ ማሰባሰብ ጀምሯል፡፡ ሂትለር ለጀርመን ህዝብ የቨርሳይለሱን ስምምነትን
እንደሚሽርና ለጀርመናውያንም ተጨማሪ መኖሪያ መሬት /ከጎረቤት ሀገሮች/ እንደሚያመቻች ገለጠ፡፡
በጃፓንም የነበረው አዝማሚያ ተመሳሳይ ነው፡፡ ስልጣንን ጠቅሎ የያዘ መንግስት በመመስረት በተለይ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ወደቻይና የመስፋፋት ህልም ነበረው፡፡ በዚህም መሰረት ከ 1932 ጀምሮ ማንቹሪያንና ሌሎች የቻይና
መደቦችን መቆጣጠር ቻለ፡፡

6.1.7 የሁለተኛው የአለም ጦርነት መጀመር (እ.ኤ.አ 1939-1945)

ተግባር 6.24
- ለሁለተኛው የአለም ጦርነት መጀመር ተጠያቂ ሀገራት እነማን ናቸዉ?ለምን?
- በሁለተኛው የአለም ጦርነት በሁለት ጎራ የተዋጉ ቡድኖች ማንና ማን ናቸዉ?

በሂደት ከላይ የጠቀስናቸው ሶስቱ ሀገራት በፍላጎታቸው በመሳሳብ የሶስትዩሽ ህብረት የሆነውን የአክሲስ
ጥምረት ወይም የሮም- ቶክዮ-በርሊን ህብረት በመመስረት በአለም ስጋት መሆን ጀመሩ፡፡ በዚህም መሰረት
ጀርመን ወደ አውሮፖ መስፋፋት በመጀመር በመጋቢት 1938 ኦስትሪያንን ወረረች፡፡ በመስከረም 1939
የቸኮዝላቪኪያን የተወሰነ ክፍል፤ ከስድስት ወር በኃላ ማለትም በመጋቢት 1939 የቀረውን ክፍል ተቆጣጠረች፡፡
በዚህ ብቻ ሳይበቃ በመስከረም 1/1939 የጀርመን ጦር ፖላንድን ለመያዝ ተንቀሳቀሰ፡፡ ለረዥም ጊዜ
ከጥቅማቸው አንፃር ምንም እርምጃ ሳይወስዱ የነበሩት የወቅቱ ሀያላን ፈረንሳይእንግሊዝ በመስከረም
3/1939 ላይ ጦርነት አወጁ፡፡
ባጠቃላይ ለሁለተኛዉ የአለም ጦርነት መጀመር ያበቁ ክስተቶች ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸዉ፡፡
በጀርመን በኩል
በ 1935 የግዴታ የወታደርነት አገልግሎት መጀመር፤
ፈረንሳይን ከጥቃት ለመካከል እንዲረዳ ከወታደራዊ ቀጠና ውጭ እንዲሆን የተደረገው የራይን ግዛት
በጀርመን መያዝ፤
ጀርመን ከመንግታቱ ድርጅት በ 1933 መውጣቷ፤
የጀርመንን የህዝብ ቁጥር መጨመር ምክንያት በማድረግ ለህዝቦች ተጨማሪ መኖሪያ በማለት ጀርመን
በ 1938 ኦስትሪያን መውረር
ሱዳንትላን የተባለው የቼኮዝላቪያ ክፍልን ጀርመን 3 ሚሊየን ጀርመናውያን ይኖሩበታል በሚል ሰበብ
ይገባኛል ማቅረቧ፤
የሙኒክ ስምምነት- የእንግሊዙ ኒቫይል ቸምበርሌይን (Neville chamberlain) የጣሊያኑ ሞሶለኒ፤
የጀርመኑ ሂትለር እና የፈረንሳዩ ዳላዲር(Daladier) ሱዳንትላንድን ለጀርመን እንዲሰጥ ወሰኑ፤
በዋናነት ከላይ እንተጠቀሰው የጀርመን ፖላንድን መውረር ለጦርነት መጀመር ምክንያት ሆኗል፤

በጣሊይን በኩል፡- ጣሊያን በ 1935 ኢትዩትጵያን ወረረች፡፡ ኢትዩትጵያም ለመንግስታቱ ማህበር አቤት
ብትልም ሰሚ አላገኝችም፡፡
በጃፖን በኩል፡- በ 1931 ጃፖን የቻይና ግዛት የሆነችውን ማንቹሪያን በመውረሯ ከመንግስታቱ ማህበር ቅሬታ
ሲነሳበት ከማህበሩ አባልነት ራሷን አገለለች፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ከላይ እንደተገለፀው እነዚህ ሶስት ሀገራት ከ 1936 – 1937 የወታደራዊ ግንባር በመጀመሪያ የበርሊን ሮም
አክሲስ በመቀጠልም የበርሊን ሮም ቶክዮ ትሪአንግልን መሰረቱ፤
የጦርነቱ ሂደት
ጦርነቱ የተጀመረው ጀርመን በመስከረም 1/1939 ፖላንድን በመውረሯ ሲሆን ከሁለት ቀን በኃላ እንግሊዝና
ፈረንሳይ በጀርመን ላይ ጦርነት አወጁ፡፡ ይሁን እንጅ እንግሊዝና ፈረንሳይ የፖላንድን ህዝቦች ለመርዳት
ጦራቸውን አላኩም፡፡ ይህ ዝም ብሎ የማየት ፖሊሲ (watch and see policy) ፎኒ ዋር (phoney war) ወይም
‘’sitting war’’ በመባል ይጠራል፡፡
ሶብየት ህብረት የጀርመን መስፋፋትን በመፍራት የፖላንድን ምዕራባዊ ክፍል ተቆጣጠረች፡፡ ከ 1920 ጀምሮ
በፖላንድ ስር የነበሩት ምዕራብ ቤላሩስና ምዕራብ ዩክሬን በሩሲያ ቁጥጥር ስር ሆኑ፡፡ በሰኔ 1940 የባልቲክ
ሪፐብሊክ የሆኑት ሉቲኒያና፤ ላቲቪያና ኢስቶንያ ወደ ሩሲያ ተቀላቀሉ፡፡
በፊንላንድ በኩል የሚደርሰውን የጀርመን ወረራ እሰጋለሁ በሚል ግጭት ተነስቶ ህዳር 1939 የተጀመረው
ጦርነት በየካቲት 1940 በፊላንድ ሽንፈት ተጠናቀቀ፡፡ በ 1940 በሳርቢያ የተባለውን ግዛት ለሩስያ አስረከበች፡፡

ጀርመን ፖላንድ ካሸነፈች በኃላ ወደ ሌሎች የአውሮፖ ሀገራት ፊቷን አዞረች ፡፡ ስለሆነም በሚያዝያ 9/1940
ዴንማርክና ኖርዌይን ወረረች፡፡ ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በኃላ የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቸምበርሌይን
በዊንስተን ቸርችል ተተኩ፡፡ እንግሊዝ እነዚህን ሀገራት ለውርደት ያደረገችው ጥረት አልተሳካም፡፡ በ 1940
ተመሳሳይ እጣ ለቤልጅየምና ሆላንድ ደረሳቸው፡፡ ከአንደኛው የአለም ጦርነት በተሻለ ቤልጅየሞች ሊዋዝም
ድሉ ለጀርመኖች ከመሆን አልዘለለም፡፡ ፈረንሳይ በጀርመን እጅ ልትወድቅ ጫፍ ላይ በነበረችበት ወቅት በሰኔ
10፤1940 ሞሰለኒ በፈረንሳይ ላይ ጦርነት አወጀ፡፡ ከእንግሊዝና ፈረንሳይ ዕቅድ በተቃራኒው ጠራቸውን
ያንቀሳቀሱት የጀርመን ሀይሎች በኒዘርላንድና በቤልጀየም በኩል የፈረንሳይና እንግሊዝ ጥምር ጦርን አሸነፋ፡፡
በሰኔ 22፤1940 በሂትለር ፊት አውራሪነት የፈረንሳይ ዕጅ መስጠትን የሚገልፅ ስምምነት ተፈረመ፡፡

ከፈረንሳይ ሽንፈት በኃላ የጀርመን ኢላማ እንግሊዝ ሆነች ፡፡ የእንግሊዝን ጦርን ከማዳከምም ጀርመኖች
ለንደንና ሌሎች ከተሞችን በአውሮኘላን ቦንብ ደበደቡ፡፡ በጦርነቱ ሂደትም ጀርመን፣ጣሊያንና፣ጃፖን ከጦርነቱ
በኃላ አለምን ለመከፋፈል እንዲሁም አዲስ ስርዓት ለመፍጠር የሶስትዩሽ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ ከ 1940 –
1941 ሀንጋሪ ፣ ሩሲያ ቡልጋሪያና ችኮዝላቫኪያ ስምምነቱን ሲቀላቀሉ ዩጎዝላቪያ ስምምነቱን አልቀበልም
ብላለች፡፡ ስለሆነም በ 1941 በቁጥጥር ስር ውላለች፡፡ አሜሪካ በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ ባትሳተፍም ኮንግረሱ
በየካቲት 1941 ማንኛውም ጀርመንና ጣልያንን ለሚወጋ ሀገር ጦር መሳሪያ ለመርዳት በኮንግረሶ ወስናለች ፡፡
በሰኔ 22፤ 1941 ሰብየት ህብረት (ሩሲያ)በጀርመንና ጣልያን ተወረረች ፡፡ ፈለንድ፣ሃንጋሪ እና ሩማንያ ከጀርመን
ጋር በማበር በሩሲያ ጦርነት አውጀዋል ፡፡ በዚሁ ቀን ዊንስተን ቸርቸል፣ ከሁለት ቀን በኋላ ደግሞ ፕሬዜዳንት
ሩዝቨልት (Roosevelt) ለሩሲያ ድጋፍ እደሚሰጡ አወጁ፡፡ ቀጥሎም የሶብየት፤ እንግሊዝ እና ሶብየት- አሜሪካ
ህብረት ተመሰረተ ፡፡
በነሀሴ 1941 ፕሬዚደንት ሩዝቨልት ኣና ጠ/ሚኒስተር ዊንስተን ቸርቸል በእንግሊዝ የጦር መርከብ ላይ ውይይት
አደረጉ፡፡ ይህም አትላንቲክ ቻርተር (Atlantic charter- 1941) የሚባለው ስሆን የስብዓዊ መብቶች

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ለማስከበር እንደሚዋጉና ከጦርነቱ በኃላ የግዛት ለውጥ በአለም ላይ እንደማይደረግ ተስማሙ ፡፡

በህዳር 7 1941 የጃፓን ጦር በሃዋይ ደሴት የሚገኘውን ፒርል ሀርበር (pear harbor) በሚባለው የአሜሪካ ጦር
ካምፕ እዲሁም ሲንጋርፓር በሚገኘው የእንግሊዝ ጦር ላይ
የአውሮፕላን ጥቃት ስነዘረ፡፡ በመቀጠልም በግንቦት 1942 ማለያ፣በርማ፣ ፊሊፒንስ፣ ኢንዶኒዥያ ኣና
ሌሎችም የአሜሪካና የእንግሊዝ ግዛቶች በጃፓኖች ተያዙ፡፡ በጥር 1 ቀን 1942 በአሜሪካዋ ከተማ ዋሽግተን
26 ሀገራትን ማለትም ሩሲያ ፣ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ፖላንድ፣ ዮጉዝላቪያ፣ወ.ዘ.ተ የአክሲስ ሀገራትን በፅናት
ለመዋጋት ህብረት መሰረቱ የሁለተኛ የአለም ጦርነት በአውሮፓና በእስያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካም ተካሂዷል፡፡
ጣልያኖች የእንግሊዝና የፈረንሳይ ሶማሊላንዳድን በአጭር ጊዜ ተቋጣጥረው ነበር ፡፡ ኢትዮጵያን ወረዋል፡፡
ምንም እንኳ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የጀርመንና የጣልያን ጦር በአፍሪካ ቢከማችም እንግሊዞችን ከአሸናፊነት
አለቆማቸውም፡፡ በተለያዩ ቦታዎች ማለትም በትርፓሊ ፣አልጀሪያ፣ ወዘተ እንግሊዞች ድል መቀናጀት ችለዋል
፡፡ ከኢትዮጵያ ጦር ጋራ በመሆን እንግሊዝ ጣልያንን ከኢትዮጵያ አስወጥተዋል፡፡ (በግንቦት 1941)

ከአፍሪካ ድል በኋላ የተባበሩት ሀይላት (allied forces) የአውሮፓ ሀገራትን ነጻ ለማዉጣት ተንቀሳቅሰዋል ፡፡
በዋናነት ፈረንሳይና ምእራብ አዉሮፓ ሀገራት ነጻ ወጥተዋል፡፡የአክሲስ ደጋፊ (pro-axis) ሀገራት የሆኑት
ፊላንድ ፣ሃንጋሪ ፣ሩማንያ ጀርመንን ለመርዳት ተንቀሳቅሰዋዋል፡፡ በፖለቲካ ቀውስ ምክንያት ሞሶሎኒ በ 1942
በህዝብ ተገደለ፡፡ ጣልያን በመስከረም 8፤1944 እጃን ሰጠች ፡፡ ከአንድ ወር በኋላ የባዶግሊዮ መንግስት ጀርመን
ላይ ጦርነት አወጀ፡፡ ሶብየቶችም ጀርመኖችን ድል ማድረግ ላይ ነበሩ፡፡ በተለይ በ 1943 የስታሊንግራድ ጦርነት
ጀርመኖች ከፍተኛ ሽንፈት ገጥሟቸዋል፡፡ ወደ 900,000 የሚጠጋ የሂትለር ምርጥ ጦር በሩሲያ ተሸንፏል፡፡
ይህም የጀርመን የመጀመሪያው ትልቁ ሽንፈት ነበር፡፡

በመስከረም 6፤1944 የእንግሊዝና አሜሪካ ጦር በስሜን የፈረንሳይ ጠረፍ ሰፈረ፡፡ ኖርማንዲ የተባለችውን
ግዛት ተቆጣጠረ፡፡ በዚህ አመት ሰኔ ወር የሩስያ ቀዩ ጦር ቤላሩስን ነፃ አወጣ፡፡ በመቀጠልም የባልቲክና የዩክሬን
ግዛቶችን ተቆጣጠረ፡፡ በመስከረም 5፤1944 የሩሲያ ጦር በቡልጋሪያ በኩል በማለፍ ሀንጋሪን ተቆጣጠረ፡፡ በቲቶ
የምትመሪው ዩጐዝላቪያ ቀዩን ጦር በመደገፉ የጀርመን ስልጣን በዚች ሀገር ላይ ተጠናቀቀ፡፡ በጥር 17፤1945
የሩስያ ቀዩ ጦር ጀርመኖችን ከፖላንድ ምድር አስለቀቀ፡፡ በተመሳሳይም በሚይዝያ 1945 የሶብየት ጦር በድል
ወደ ቸኮዝላቫኪያና ኦስትሪያ ገባ፡፡

በየካቲት 1945 የያልታ ጉባኤ /yalta conference/ ተደረገ፡፡ በዚህ ጉባኤ ሩስያ ፣ አሜሪካና እንግሊዝ በክሪምያ
ግዛት ያልታ ጦርነቱን በሚጠናቀቁበት ሂደት ላይ ተወያዩ፡፡ ከጦርነቱ በኃላም ነፃ በሚወጡ ሀገራት
ዲሞክራሲያዊ መንግስታት በሚመሰረትበት ሂደትና የኢኮኖሚ ድጋፍ ለማድረግ ተስማሙ፡፡ በዚህ ጉባኤ
የመንግስታቱ ማህበር በአዲስ ጠንካራ አለማቀፍ ድርጅት መተካት እንዳለበትም ተስማሙ፡፡
በቀጣይም በጉባኤው ስምምነት መሰረት በሚያዝያ 16፤1945 ሩሲያ የጠላት ጦርን መውጋት ጀመረች፡፡
ጀርመኖችም የተባበሩት ሀያላትን ጦር መቋቋም ባለመቻላቸው እጅ ለመስጠት ተገደዱ፡፡ ሂትለርና ጎበልስ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ራሳቸውን ሲያጠፋ ሌሎች ከፍተኛ የጦር ሹማምንት የጀርመንን መሸነፍ በግንቦት 6፤1945 ፈረሙ፡፡

ተግባር 6.25
- ከሁለተኛዉ የአለም ጦርነት በኃላ በጀርመን፣በጣልያን እንዲሁም በመላዉ አለም የተከሰቱ ዋና ዋና
ክስተቶችን ዘርዝሩ

6.2 የአሁኑ አለም ታሪክ እ.ኤ.አ ከ 1945 ጀምሮ

6.2.1 የሁለተኛው የአለም ጦርነት ማግስት


በሰኔ 17፤1945 የሩስያ ፣ አሜሪካ ፣ እንግሊዝ እና ፈረንሳይ መሪዎች በፖስትዳም ስብሰባ አደረጉ፡፡
በስብሰባውም የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳለፋ
ጀርመን በአራት ቀጠናዎት ስትከፈል በርሊን ደግሞ ለአራቱ ሀገራት ተከፍላለች፡፡ ሁሉም ሀገራት የጦር
ካሳ ከያዙት ቀጠና ለመሰብሰብ ተስማሙ፡፡
የጀርመን የጦር ወንጀለኞችን ለመዳኘት ኑሬምበርግ ላይ አለምአቀፍ የጦር ፍርድ ቤት እንዲቋቋም
ተወሰነ፡፡
የምስራቅ ኘራሽያ ከፊል ግዛት ለሩሲያ ሲሰጥ ቀሪው ደግሞ በፖላንድር ስር እንዲቆይ ተስማሙ፡፡
በሩቅ ምስራቅ ከ 1943 ጀምሮ እንግሊዞችና አሜሪካኖች በጃፖን ላይ ከፍተኛ ጥቃት ሲሰነዝሩ በኮርያ ፣
በርማ ፣ ፈሊፒንስ እና እንደኒዥያ ደግሞ የነፃነት እንቅስቃሴዎች ተፋፍመዋል፡፡ በተለይ አሜሪካ
ጦርነቱን በአጭር ለማቆም በሚል ሰበብ በሁለቱ የጃፖን ትላልቅ ከተሞች በሂሮሽማ በነሀሴ 6
በናጋሳስኪ በነሀሴ 9፤1945 የአቶሚክ ቦንቦችን ጥላለች፡፡ ሁለቱም ከተሞች ወደ ፍርስራሽነት
ሲለወጡ ከፍተኛ ሰቆቃና የሰው አፅም ክምር እንዲታየ ተፅፏል፡፡ በህይዋት በተረፋትም ለከፍተኛ
የአካል ጉዳትና በሚወለዱት ህፃናት የአቶሚክ ጥቃቱ ውጤት የሆነው የአካል ጉዳት ለረዥም ጊዜ
ቀጥሏል፡፡

ስለሆነም በነሀሴ 14፤1945 ጃፖን እጇን ሰጥታለች፡፡ በሂሮሽማ ወደ 160,000 ሰዎች እንዲሁም በናጋሳኪ ወደ
120,000 ሰዎች እንደሞቱ ይገመታል፡፡
በአውሮፖ ከፍተኛ የሰውና የኢኮኖሚ ቀውስ ተከስቷል፡፡ ወደ 40 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች እንደሞቱ ሲታመን
ከነዚህ ውስጥ ሁለት ሶስተኛዎቹ ሲቢሎች እንደሆኑ ይታመናል፡፡ በጣም ብዙ ከተሞች ወደ ፍርስራሽነት
ተለውጠዋል፡፡ በተለያዩ ሀገራት ጀርመንና ጣሊያንን ጨምሮ የመንግስት ለውጥ ተደርጓል፡፡

ሌላው ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በኃላ የተከሰተው ክስተት የኮሙኒስት ፖርቲዎች ተደማጭነት መጨመር
ነበር፡፡ ለምሳሌ በፈረንሳይና በጣልያን የኮሙኒስት ፖርቲ አባላት ቁጥር በእጅጉ ጨምሯል፡፡ ቀስ በቀስ ግን

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የአባላት ቁጥሩ ለመቀነስ ችሏል፡፡ ሀገራት በኢኮኖሚና በፖለቲካ በማገገም ላይ ባሉበት ጊዜ በጀርመን የጦር
ወንጀለኞችን በመዳኘት ላይ ነበሩ፡፡ በተለይ በ 1945 እና በ 1946 በኑሬምበርግ የተቋቋመው 23 አባላት ያሉት
የአለምአቀፍ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የጦር ወንጀለኞችን ጉዳይ በመመርመር ላይ ነበር፡፡ በመጀመሪያዎቹ ክሶች
22 የናዚ መሪዎች ጦርነትን በማስነሳት ወንጀል /waging a war of aggression/ ተፈርዶባቸዋል፡፡
በተጨማሪም የሰው ዘርን በመጉዳት /crimes againet homanity/ ተከሰዋል፡፡ በዚህም ለ 11 ሚሊየን ሰዎች
ሞት ተጠያቂ ሆነዋል፡፡በዋናነት በተለይ በናዚ ጸረ አይሁዳዊ ፖሊሲ ምክንያት ጀርመንን ጨምሮ በሌሎች
ሀገራት የተገደሉ በሚሊየን የሚቆጠሩ አይሁዳውያን ሞትም ተጠያቂ ሆነዋል፡፡

6.2.2 የቅኝ ግዛት መፈራረሰና የተባበሩ መንግስታት ድርጀት መመሰረት


በሁለተኛው የአለም ጦርነት ምክንያት ቅኝ ገዥ ሀገራት እጀግ በመዳከማቸው አፍሪካውያን ለነፃነት
የሚያደርጉት ትግል ፍሬ ማፍራት ጀመረ፡፡ በተጨማሪም እንደ ሶብየት ህብረት ፣ ኮሙኒስት ቻይና እና አሜሪካ
የአለም ሃያላን መሆን ለአፍሪካውያን ጥሩ አጋጣሚ ሆነ ፡፡ በራሳቸው በቅኝ ገዥ ሀገራትም በህዝብ ጫና
ምክንያት የመንግስታት ፖሊሲ ለውጥ መደረግ ተጀመረ ፡፡ ለምሳሌ ብንወስድ በቻርለስ ዲ ጉሌ (Charles de
goulle) የሚመራው የፈረንሳይ መንግስት ከ 1960 ጀምሮ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ነፃ ለማውጣት ሁኔታ
በማምቻቸት ላይ ነበር፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን የተባበሩ መንግስታት እና የአፍሪካ ህብረት የፀረ-ቅኝ ግዛት
ትግሉን በመደገፋቸው የአፍሪካ ሃገራት ቀስ በቀስ ነፃ መውጣት ችለዋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጀት አመሰራረት


ተግባር 6.26
ተማሪዎች የተባበሩ መንግስታት ድርጀት መቼና እንዴት እንደተመሰረተ በቡድን ተወያዩ፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጀትን ለመመስረት ፀረ-ፋሽስት የሆኑት የቃል ኪዳን አባል ሀገሮች መንግስታት
አብይ ሚና ተጫውተዋል፡፡ በተለይም በወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የነበሩት ፋራንክሊን ሮዝቬልት የድርጀቱ
መሰራች ናቸው ብንል ማጋነን አይደለም፡፡ ይህንን ድርጀት ለመመስረት የተለያዩ ጉባኤዎች ተካሄደዋል ፡፡
ከእነዚህ መካካል ፡-

1.የአትላንክቲክ ቻርተር /1941/


በ 1941 ዓ.ም የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ሩዝሼልትና የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስተር ቸርችል በአትላንቲክ ውቂያኖስ
ቻርተር አውጥተዋል ፡፡ በአትላንቲክ ቻርተር ከተጠቀሱት ስምምነት ነጥቦች መካከል አንድ የአለም ፀጥታ
የሚያስጠብቅ ዓለም አቀፍ ድርጀት ለመመስረት እደሚሹ ይጠቅሳል፡፡ በሚቀጥለው አመት በጥር
በ 1942 ዓ.ም 26 ቱ ፀረ-ፋሽስት ህብረት ሀገሮች ባካሄዱት ጉባኤ የአትላንቲክ ቻርተርን እደሚቀበሉት
መጠሪያ ስማቸውንም የተባባሩ ሀገሮች (United Nations) በማለት ሰይሙ፡፡
2.የሞስኮ ኮንፈረንስ /1943/

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

የአሜሪካ፤ የእንግሊዝ እና የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተሮች በሞስኮ ከተማ ባደረጉት ጉባኤ የዓለምን ሰላምና
ደህንነት ለማረጋገጥ የአለም አቀፍ ድርጅት መመስረትን አስፈላጊነት ተቀብለዋል ፡፡
3.የደምበርተን ኦክስ ጉባኤ /1944/
በዚህ ጉባኤ የአሜሪካ ፣ የእንግሊዝ ፣የሩሲያና የቻይና ተወካዮች ተካፍለዋል ፡፡ አዲስ ለሚመሰረተውም አለም
አቀፍ ድርጅት ረቂቅ ቻርተር አዘጋጅተዋል ፡፡
4.የያልታ ኮርፈረንስ /የካቲት 1945/
በዚህ ኮንፈረንስ ሶስት ታላላቅ መሪዎች ተካፍለዋል ፡፡ እነሱም ፡- አሜሪካዉ ፕሬዚደንት ሩዝቨልት፤እንግሊዙ
ጠ/ሚኒስትር ቸርችል እና የሩሲያዉ መሪ ስታሊን ናቸዉ፡፡በዚህ ጉባኤ፡
በመንግስታቱ ድርጅት በፀጥታው ምክር ቤት ድምፅ አሰጣጥን በተመለከተ ሊኖር የሚገባው አካሄድ
ወስነዋል፡፡
ሀገሮች ተወካዮቻቸውን ለሚቀጥለው የሳንፈራርሲስኮ ጉባኤ እንዲልኩ ጥሪ አቅርበዋል ፡፡

5.የሳንፍራንሲስኮ ጉባኤ /ሚያዚያ- ሰኔ 1945/


ይህ ጉባኤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መስራች ጉባኤ ነው ፡፡ ከሀምሳ ሀገሮች የተላኩ ተሳታፊዎች
በጉባኤው ተገኝተው ድርጅቱን መስርተዋል ፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መተዳደሪያ ቻርተር
አዘጋጅተዋል ፡፡ ይህም ቻርተር ከጥቅምት 24 ቀን በ 1945 ጀምሮ በስራ ላይ ውሎአል ፡፡ የተ.መ.ድ. ዋና
ጽ/ቤትም በአሜሪካ በኒወርክ ከተማ ሆነ፡፡
የድርጅቱ አላማዎች
የተባበሩ መንግስታት ድርጅት የተቋቋመባቸዉ የሚከተሉት አምስት አላማዎች አሉት ፡፡ እነሱም፡-
1.አለም አቀፍ ሰላምና ፀጥታን ለማስጠበቅ፣
2.በህብረት የሰላም እንቅፋቶችን ማስወገድ ፣ የወረራን ተግባር የሚካሄዱ ሀይሎች መደምሰስ፣
3.በእኩልነት ላይ የተመሰረተ መርህ በመመርኮዝ በሀገሮች መካከል የወንድማማችነትና የእህትአማችነት
ግንኙነትን ለማዳበር ፣
4.ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊና ሰብአዊ ችግሮችን በአለም አቀፍ ትብብር ለመወጣት ጥረት ማድረግ፣
5.ሰብአዊ መብቶች ያለምንም ልዩነት እንዲከበሩ ጥረት ማድረግ ናቸው፡፡

ከላይ የተዘረዘሩትን አላማዎች ግባቸውን እንዲመቱ ሀገሮችን በማስተባበር ድርጅቱ በማዕከልነት ያገለግላል፡፡
ሆኖም ግን የሚወስዳቸውን እርምጃዎች ከማስፈፀም በስተቀር በማንኛውም ሀገር የውስጥ ጣልቃ አይገባም፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 6 አካላት አሉት፡፡ እነሱም፡-
የጠቅላላ ጉባኤ (General Assembly)
ፀጥታው ም/ቤት (Security council)
የድርጅቱ ጽ/ቤት (The secretariat)
የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳይ ም/ቤት (Economic and social cuncil)
የሞግዚት አስተዳደር ም/ቤት እና (Trusteeship council)
1.የአለም አቀፍ ፍ/ቤት (International court of justice) ናቸው፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

በኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳም ም/ቤት አስተባባሪነት የሚሰሩ የተለያዩ በርካታ ድርጅቶች እንደ ዩኔስኮ፣
ዩኒሴፍ፣ የአለም ጤና ድርጅት፣ የአለም የምግብና እርሻ ድርጅት ወዘተ ተቋቁመዋል፡፡

ተግባር፡ 6.27
ተማሪዎች የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተመሰረተው ከ 50 አመት በላይ ሆኗታል፡፡ በእነዚህ ጊዜያት
ባከናወናቸው በርካታ ተግባራት መካከል አንዳንዶቹ አዋቂ ሰው በማነጋገር ክፍል ውስጥ ሪፖርት አቅርቡ?

6.2.3 የቀዝቃዛው ጦርነት


በሁለተኛው የአለም ጦርነት በኃላ አለም በሁለት ጎራ ተከፍላለች፡፡ የካፒታሊትት ጎራ በአሜሪካ የሚመራው
ሲሆን የሶሻሊስት ጎራ ደግሞ በሩሲያ ይመራል፡፡ በዚህም ምክንያት በሁለቱ ሀገራት ተከታዩቻቸው መካከል
ከፍተኛ ውዝግብና የዲኘሎማሲ ጦርነት ሲከናወን ቆይቷል፡፡

ተግባር፡- 6.28
ቀዝቃዛው ጦርነት ሊከሰት የቻለበት ምክንያት ምን ይመስላችኋል ?
በዚህ ቀዝቃዛ ጦርነት በአሜሪካና በሩሲያ መካከል ጦርነት ባይከሰትም በነሱ በሚደገፋ ቡድኖች ግን ለተለያዩ
ቦታቸው ጦርነቶች ተከስተዋል፡፡ ከነዚህ ውስጥ ጥቂቶቸን ዘርዝሩ፡፡

የቀዝቃዛው ጦርነት በዋናነት በተለይ ሀያላን ሀገራት መካከል የተከናወነው የኘሮፖጋንዳ /የማጥላላት
ዘመቻ/ ፣ በዲኘሎማሲና በኢኮኖሚያዊ ውድድር ፣ በጦር መሳሪያ እሽቅድድም በስላላ እንዲሁም
በሀገራት ጣልቃ በመግባት በውስጣዊ ጦርነት ነበር፡፡ ይህ ጦርነት ተጠናቀቀ የሚባለው በ 1990
የሚካኤል ጎርባቶቨ በሩሲያ ወደ ስልጣን መምጣትና እርሱን ተከትሎ በተፈረመ ውል ነው፡፡
ተግባር፡- 6.29
ለቀዝቃዛው ጦርነት መጀመር ተጠያቂ ነው የምትሉት ማንን ነው ? እንዴት?
አሜሪካ የቀዝቃዛው ጦርነት የመራችበትን ሁለት ታላላቅ ፖሊሲዎችን ግለፁ፡፡

ከሁለተኛዉ የአለም ጦርነት በኃላ (በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅትና በኃላ) ከተከናወኑ ክስተቶች ጥቂቶችን
እንመልከት፡፡

6.2.4 ኮሙኒስት ቻይና


ከ 1644 እስከ 1911 ቻይና በፊዉዳላዊው የማንቹ (ችንግ) ስርዋ መንግስት ስር ቆይታለች፡፡ በኋላም
በኩሚንታንግ (ናሽናሊስት) እና በኮሙኒስት ፓሪቲ መካከል የእርስበርስ ጦርነት ተደርጐ በ 1926 የቻይና
ኮሙኒስት ፓርቲ ስልጣል ይዟል ፡፡ ኮሚንታንግ የቡርዥዋው ናሽናሊስት ፓሪቲ ሲሆን መሪው ደግሞ ዶክተር
ሰን ያት ሰን (sun yat sen)-1866-1925 ነው፡፡ ሰን ብሄርተኛና ፀረ-ኢምፔሪያሊስት አቋም ሲኖረው የቻይናን

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ኮሙኒስቶችም ድጋፍ ነበረው፡፡ ሰን ያት ሰን ኮመኒስቶችን የተቀበለ ሲሆን የቻይና ኮመኒስት ፓርቲ (ccp)
በ 1921 በሻንጋይ ተመስርቷል፡፡በ 1923 ከላይ የጠቀስ ናቸው ሁለቱም ፓርቲኮች በመዋሀድ የቻይና የጦር
አበጋዞችንና ኢምፔሪያሊቶችን ለማስወገድ ተስማምተዋል፡፡ የሁለቱ ፓሪቲዎች ጥምረት ለሶስት አመታት
የዘለቀ ሲሆን የራሳቸው ወታደሮችም አሰልጥነዋል፡፡ ከሰን ያት ሰን ሞት በኋላ የ KMT መሪነቱን ስልጣን
የተረከበው ችአንግ ካይ ሽክ (chiang kai shek) ነበር፡፡

በ 1926 ወደ ሰሜን በመዝመት ከቻንግ ጅአንግ ደቡብ ያለውን የቻይና ግዛት ለመቆጣጠር ወሰነ፡፡ በዚህ መሀል
ናሽናሊስቶችና ኮሙኒስቶች ግጭት ጀመሩ፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚቆጣጠረው ችአንግ ካይ ሸክ
ኮሚኒስቶችን የሚደግፍ ይምሰል እንጅ በተግባር ግን በ 1927 በሽዎች የሚቆጠሩ ኮሚኒስቶችን የሻንጋይ ግድያ
(shan gai massacre) በሚባለው መጨረሱ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ የናሽናሊስቶችና የኮሚኒስቶች ህብረት
ተቋረጠ፡፡ በ 1928 ሽአንግ ካይ ሽክ በናንጅንጅ አዲስ ሪፐብሊክ መሰረት፡፡ ሀገሪቱን ለማዋሀድ ጥረት አድርጓል፡፡
በዚህ ሂደት ግን ኮሚኒስቶችን ጠላቶቹ እደሆኑ እነሱን ማሳደድ አላቆመም፡፡ በዚህ የተነሳ የኮሚኒስት መሪዎች
በሻንጋይ መደበቅ ጀመሩ፡፡በ 1933 የችአንግ ካይ ሸክ ጦን ኮሚኒስቶችን በጅአንግዚ ከበባ አደረገባቸው፡፡ በዚህ
ጊዜ ማኦ የጦሩ ቁጥር አነስተኛ መሆኑን በመገንዘብ ጦሩን ማለትም የህዝቦችን ነፃ አዉጭ ጦር(peoples
liberation army) የናሽናሊስት ድንበርን በመጣስ ወደ ሰሜን መእራብ ቻይና እንደጓዝ በማዘዝ ጦሩን መራ ፡፡
ከ 600 ማይል ጉዞ በኋላ የመጨረሻ መደበቂ ቤዝ መሰረተ፡፡ በታሪክ ይህ ጉዞ ታላቁ ጉዞ (the long march)
በመባል ይታወቃል፡፡ ጉዞው አንድ አመት ፈጅቷል ፡፡ በጉዞው ወደ 90,000 የሚጠጉ ወታደሮች በጥቂት ምግብ
፣በቀዝቃዛ አየር እና በጉዞ ላይ ጦርነት በማሳለፋቸው ጉዞውን ያጠናቀቁ 9,000 ወታደሮች ብቻ እደሆኑ
ይታመናል፡፡ በዚህ ረጅም ጉዞ ማኦ ወደር የለሽ መሪ መሆኑን አስመሰከረ፡፡ በዚህ ምክንያት የኮሚኒስቶች
ንቅናቄውን ከከተማ ላብአደሩ ጋር በመሆን አጠናከሩ፡፡ ጥቂት የኮሚኒስት መሪዎችም ከችአንግ ጂአንግ
በሰተደቡብ ወደ ጂአንግዚ ግዛት ሂደዋል፡፡ መሪያቸው ማኦ ዜ ዱንግ (mao ze dong) ነበር፡፡ ማኦ የቻይና
አብዮት መጀመር ያለበት በገጠር አርሶ አደሮች እንጅ በከተማ ላብአደሮች አይደለም ብሎም ያምናል፡፡

ችአንግ ካይ ሸክ የኮሚኒስት መሪዎችን ከሻንጋይ ማስወጣት ችሏል፡፡በዚህ ሳቢያ ኮሚኒስቶች ወደ ደቡብ


በመሄድ ማኦን ተቀላቀሉ፡፡ አሁናም ናሽናሊስቶችን ጅአንግዚ የሚገኙ ኮሚኒስቶችን ማጥቃታቸውን ቀጠሉ፡፡
ነገር ግን ማኦ የጎሪላ (የሽምቅ) ዉጊያ ስልት በመጠቀም ብዙ ቁጥር ያለውን ጦር በድል ለማሸነፍ በቅቷል፡፡
በ 1931 ጃፓን የስሜን ምስራቅ የቻይናን ግዛት በማጥቃት ማንቹሪያ የተባለውን ግዛት ተቆጣጠረች፡፡ በ 1937
ጃፓን ጠቅላላ ጦርነት በማወጅ በታሪክ የሳይኖ -ጃፓን (sino japanese war) እንዲጀመር አደረገች፡፡ ይህ
ጦርነት በኢሲያ በ 2 ኛው የአለም ጦርነት አከል ሆነ፡፡ በችአንግ ካይ ቨክ የሚመራው የ KMT ፓርቲ እና የ CCP
ፓርቲ ደግሞ የቻይናን አጠቃላይ ግዛት ለመቆጣጠር የእርስ በእርስ ጦርነት ያካሄዱ ነበር፡፡ ስለሆነም በ 2 ኛው
የአለም ጦርነት ወቅት የተለያዩ የቻይና ክፍሎች በ KMT፣CCP፣እና የጃፓን ቁጥጥር ስር ነበሩ፡፡ በ 1945
የጃፓን በ 2 ኛው የአለም ጦርነት መሸነፍን ተከትሎ በሁለት ባላንጣዎች (KMT እና CCP) መካከል መላውን
ቻይናና የቻይናን ፖለቲካ ለመቆጣጠር ጦርነቱ ቀጠለ፡፡ በዚህ ትግል KMT የተሻለ ሁኔታ ላይ ነበር፡፡ ለዚህ
ምክኒያቶች የሚከተሉት ይገኙበታል ፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

1.የ KMT ተዋጊዎች ቁጥጥር ከ CCP የበለጠ ነበር፡፡ የዚህ ቀመር 3፡1 ነበር፡፡
2.አሜሪካ ችአንግ ካይ ሽክና ፓርቲውን KMT ን ትደግፍ ነበር፡፡
3.ሩሲያን ጨምሮ የተባበሩት ሀይላት KMT ን እንደ ብቸኛ ህጋዊ አካል ይደግፉ ነበር፡፡ ነገ ግን እነዚህ
የናሽናሊስት ሃይሎች የህዝብን ድጋፍ ለማድረግ ያደረጉት እንቅስቃሴ ዝቅተኛ ነበር፡፡

ከ 1946 የእርስ በእርስ ጦርነት በኃላ አብዛኛው የቻይና ስሜናዊ ክፍል በ KMT ቁጥጥር ስር ሆነ፡፡ ነገር ግን
ገጠሩ ክፍል በኮሙኒስቶች ስር ነበር፡፡ በጊዜ ሂደት ግን በ KMT ስር የነበረው ግዛት የኢኮኖሚ ችግር ውስጥ
መውደቅ ፣ በዋጋ ንረት፣ በሙስናና በወታደራዊ ታክቲክ ችግር ምክንያት በጥር 1949 ኮሙኒስቶች በማሸነፍ
ቤጅንግን በመቆጣጠር የቻይና ኮሙኒስት ሪፐብሊክን መሰረቱ፡፡ ችአንግ ካይ ሸክም ወደ ታይዋን በመሸሽ
ብሄራዊ መንግስት በታይፔይ መሰረተ፡፡

ይህ አዲሱ የኮሙኒስት መንግስት በቻይና ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ አገኘ፡፡ በመቀጠልም አለማቀፍ ድጋፍ በተለይ
ከሩስያ ማግኘት ችሏል፡፡ በዚህም ከፍተኛ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ድጋፍ ከሩሲያ አገኘ፡፡ ማኦ የቻይናን ኢኮኖሚ
ለማሳደግ ኢንዱስትሪውን ፣ ንግዱንና እርሻውን ለማሳደግ የሚረዱ ብዙ የለውጥ ፖሊሲዎችን አውጥቷል፡፡
የግል ኩባንያዎችን ወደ መንግስት አዛውሯል፡፡ በ 1953 ማኦ የአምስት አመት እቅድ በማቀድ በዋናነት
ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ ወስኗል፡፡ በ 1957 የቻይና የድንጋይ ከሰልና ሲሚንቶ፣ ብረት እና ኤሌክትሪሲቲ
ምርት በፍጥነት አድጓል፡፡ ከዚህ በኃላም ሌሎች ተከታታይ የአምስት አመት ዕቅዶች በቻይና ተተግብረዋል፡፡

ተግባር 6.30
ተከታታይ የአምስት አመት ዕቅዶች በቻይና መተግበራቸዉ በሀገሪቱ ምን ለዉጥ አስከተለ ?
አዲሱ የኮሙኒስት መንግስት በቻይና ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ ለምን አገኘ?

6.2.5 የኮርያ ጦርነት


የሁለተኛው የአለም ጦርነት መጠናቀቅ ኮርያ በሶብየት ህብረትና በአሜሪካ ተፅዕኖ ስር እንድትወድቅ አድርጓል፡፡
ሰሜኑ ክፍል በሶብየት ህብረት ወታደራዊ እዝ ሲስተዳደር ደቡቡ ክፍል ደግሞ በአሜሪካ እዝ ሆኗል፡፡

ተግባር፡- 6.31
የቀዝቃዛው ጦርነት ሂደት በኮርያ ምን ተፅዕኖ አስከተለ?
የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ኢትዩጵያ በምን መልኩ ከኮሪያ ጦርነት ጋር ያዛምዷቸዋላችሁ?

በየካቲት 1946 ጊዜያዊ ህዝባዊ ኮሚቴ በሰሜን ኮሪያ ተቋቋመ ፡፡ ይህም በዋናነት የተደገፈው በሶብየት ህብረት
ሲሆን ብዙ የማሻሻያ ህጎችን አወጣ፡፡ ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

-በመጋቢት 1946 የእርሻ ለውጥ ተደርጎ መሬት ለገበሬዎች ተከፋፍሏል፡፡


-በተመሳሳይ አመት ኢንዱስትሪዎችን ፣ ባንኮች የመጓጓዝ ዘዴዎች ወዘተ ተወርሰዋል፡፡ /ወደ መንግስት
ንብረትነት ዙረዋል/
-በክፍያ አንፃር የሴቶችና የወንዶች ክፍያ እኩል ተደርጓል፡፡
-የስራ ደህንነትና የህክምና ጥቅማ ጥቅም ተረጋግጧል፡፡
-የኮርያ ቋንቋ የማስተማሪያ ቋንቋ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

በነሀሴ 1946 የኮሪያ ኮሙኒስት ፖርቲና አዲሱ የህዝቦች ፖርቲ (New peoples party)በመዋሀድ የኮርያ
የሰራተኛ ፖርቲ (Korean party of labor) በስሜን ኮሪያ መሰረቱ፡፡ ሊቀ መንበሩም 2 ኛ ኪምሱንግ (Kim II
sung) ሆነው ተመረጡ፡፡ በደቡብ ኮሪያ ሲግማን ሪ(Syngman Rhee) የደቡብ ኮሪያ መሪ ሆነው በግንቦት 1948
ተመረጡ፡፡

በነሀሴ 1948 በመላ ሀገሪቱ ባደረገው የህዝብ ተወካዩች ምክር ቤቶች (Supreme peoples assembly) የኮሪያ
ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (Korean democratic republic) መንግስት ተመሰረተ፡፡ ምክር ቤቱም
የሶብየት ህብረትና የአሜሪካ ወታደሮች ከኮሪያ እንዲወጡ ጠየቀ፡፡ ይህን ተከትሎ ሁለቱም ሀገራት ከኮሪያ
ምድር ወጡ፡፡ ሰሜን ኮሪያም ደቡብ ኮሪያን በመቆጣጠር አንድ ወጥ መንግስት መሰረተች፡፡ ይህን በመቃወም
ደቡብ ኮሪያ አቤቱታዋን ለተባበሩት መንግስት ድርጅት የፀጥታው ም/ቤት አቀረበች፡፡ የፀጥታው መ/ቤትም
ሶብየት ህብረት በሌለችበት በሰሜን ኮሪያ ላይ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት አወጀ፡፡ በሰኔ 1950 የአሜሪካ
ወታደሮች የሲግማን ሪንመንግስት በመደገፍ ሰሜን ኮሪያን ወረረች፡፡ በዚህ የተጀመረው ጦርነት የተባበሩት
መንግስታት ድርጅት ደቡቡን በመደገፍ ጦር ልኳል፡፡ ኢትዬጵያም የተባበሩት መንግስታት ደርጅትን በጦር ከረዱ
ሀገሮች አንዷ ነበረች፡ ይህ አንዱም ጎራ ያላሸነፈበት ጦርነት በመጨረሻ በተኩስ አቁም ስምምነት ሲጠናቀቅ
ኮሪያ ከሁለት ተከፍላ እንድትቀር አድርጓል፡፡

6.2.6 ቬትናም /ኢንዶቻይና/


በ 1990 ዎቹ መጀመሪያ በሃብት የበለፀጉ የደቡብ ምስራቅ እስያ (ኢንዶቻይና) በፈረንሳይ ተይዞ ነበር፡፡
ኢንዶቻይና በመባል የሚታወቀው አካባቢ የአሁኖችን ቬትናም፣ ላኦስ እና ካንቦዲያን የሚያጠቃልል ነው፡፡
የነዚህ ቦታወች ቀስ በቀስ የብሄራዊ ስሜት ማደግ እና የነጻነት እንቅስቃሴ መታየት ጀመረ፡፡በቬትናት በወጣቱ
ብሄርተኛ ሆቺ ሚንህ (ho chi minh) የሚመራ ቡድን ወደ ኮሚኒስት ሀገራት ድጋፍ ማግኘት አዘነበለ፡፡
በ 1930 ዎቹ በእርሱ የሚመራው የኮሚኒስት ፓርቲ የተለያዩ የአመጽና እና የተቃዉሞ እንቅስቅሴዎችን
በፈረንሳይ አገዛዝ ላይ መምራት ችሏል፡፡ ፈረንሳይ ተቃዋሚዎችን በማሰር እንዲሁም በሆ ላይ የሞት ፍርድ
ብትፈርድም ሆ ወደ ውጭ በስደት በመቆየት ከ 1941 ወደሀገሩ ተመለሰ፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ ጃፓን ሀገሩን
በቁጥጥር ስር አድርጋ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ሆ እና ሌሎች ታጋዮች ቬትሚንህ ሊግ (የነፃነት ሊግ) የተባለ ድርጀት
በመመስረት ሲታገሉ ቆይታው በ 2 ኛው የአለም ጦርነት ሽንፈቷ ሳቢያ ጃፓን በ 1945 ከቬትናሞ ወጣች፡፡ ሆ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ከዚህ በኋላ ሀገሩ ነፃነት እደሚጠብቃት ቢያምንም ፈረንሳይ ግን የጥንት ግዛቷን እደገና ለማግኘት ጥረት
ታደርግ ነበር፡፡
በዚህ ሳብያ የቬትናም ብሄርተኞችና ኮሚኒስቶች የፈረንሳይን ጦር ለመዉጋት ህብረት ፈጠሩ ፡፡
ፈረንሳይ አብዛኛውን የከተማ ክፍል ስትቆጣጠር ቪትሚንህ ደግሞ ገጠሩን ክፍል ለመያዝ በቃ፡፡ ዋና
የጦርነት ስልታቸውም የደፈጣ ዉጊያ ነበር፡፡ በግንቦት 14/ 1954 ዴን ቤን ፉ(dien bien phu) ላይ
ፈረንሳይ ከፍተኛ ሽንፈት ገጠማት ፡፡ ስለሆነም ለሆ እጅ ሰጡ፡፡ አሜሪካ በቬትናም የተጀመረዉ
ኮምኒዝምን የመቀበል ነገር በሌሎች የኢሲያ ሃገራት እንዳይስፋፋ ለማድረግ የፈረንሳይ ደጋፊ ነበረች
፡፡ ስለሆነም ከፈረንሳይ ሽንፈት በኋላ በጀኔቫ በተደረገው አለምአቀፍ የሰላም ጉባኤ ላይ ቬትናም በ 17
ዲግሪ ሰሜን ላቲቲዉድ ላይ ከሁለት እንድትከፈል ተወሰነ፡፡ ከዚህ መስመር በስተ ሰሜን የሆች ሚንህ
ኮሚኒስት አስተዳደር ሲመሰረት በደቡብ ደግሞ አሜሪካና ፈረንሳይ በንጎ ዲንህ ዴም(ngo dinh
diem)የሚመራ ፀረ-ኮሚኒስት መንግስት አቋቋሙ፡፡ ዴም ደቡብ ቬትናምናኝ በአንባገነንነት መርቷል፡፡
ተግባር 6.32
ቀዝቃዛው ጦርነት በቬትናም ያስከተለውን ችግር ተወያዩ?
የቬትናም በዚህ መልኩ መከፈል ምን ችግር ያስከተለ ይመስላችኋል ?

በዴም አንባገነን መንግስት ላይ ከፍተኛ ተቋሙሞ ሊነሳ ችሏል፡፡ የኮሙኒስት ደፈጣ ተወጊ የሆነው ቬትኮንግ
ቀስ በቀስ በደቡብ መስፋፋት ጀመረ፡፡ በርግጥ ሌሎች የሰለጠኑ በሰሜን በኩል ቢሆንም አብዛኛዎቹ ግን ከደቡብ
የመነጩ ነበሩ፡፡ ቀስ በቀስም ቬትኮንጎች ሰፊ የገጠር ግዛቶች ተቆጣጠሩ፡፡ በ 1963 ዴም በጀነራሎቹ ተገደለ፡፡
ከሱ በኋላ የመጡ መሪዎች የርሱን ያህል ተቀባይነት አልነበራቸውም፡፡ ስለሆነም የደቡብ ቬትናም በቬትኮንግ
ስር መዉደቅ አይቀሬ ሆነ፡፡ ይህን የኮሚኒስቶች ድል አይቀሬነት በመወቅ አሜሪካ ጣልቃ ገብነቷን ለማሰረፋት
ወሰነች፡፡ በርግጥ ከ 1950 ዎች ጀምሮ ጥቂት የአሜሪካ መኮንኖች ለደቡብ ቬትናም በአማካሪነት ሲሰሩ የቆዩ
ቢሆንም ቀስ በቀስ ቁጥራቸው ማደግ ጀመረ፡፡ በተጨማሪም ለደቡብ የሚደረገው የአይሮፕላንና የጦር መሳሪያ
ድጋፍ ማደግ ጀመረ፡፡

በነሀሴ 1964 የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ልይንዶን ጀንስተን /Lyndon Johnston/ለኮንግረሱ ባስተላለፋት
መልክት የሰሜን ቬትናም ቀኝ መርከብ ሁለት የአሜሪካ መርከቦችን በቶንኪን ስርጥ /gulf of Tonkin/
ማውደሙን ገለፁ፡፡ ይህን ተከትሎ ኮንግሬሱ ፕሬዜዳንቱ ጦራቸውን ወደ ቬትናም እንዲዘምቱ ፈቀዱላቸው፡፡
በ 1965 በመጨረሻ አካባቢ ወደ 185,000 የሚጠጉ የአሜሪካ ወታደሮች በቬትናም በጦርነት ላይ ነበሩ፡፡
የአሜሪካ የጦር አዉሮፕላኖችም ሰሜን ቬትናምን ደብድበዋል፡፡ በ 1968 ከግማሽ ሚሊዩን የሚበልጡ
የአሜሪካ ወታደሮች በቬትናም ጦርነት ላይ ነበሩ፡፡
አሜሪካ በጣም ዘመናዊ የጦር መሳሪያና የሰለጠነ ወታደር ቢኖራትም የሚከተሉት ችግሮች ነበሩባት፡፡
1.የአሜሪካ ወታደሮች በማያዉቁት ቦታና ደን ውስጥ የደፈጣ ዉጊያ ላይ ተዳርገዋል፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

2. አሜሪካ እየደገፈችው የነበረው የደቡብ ቬትናም መንግስት እየተጠላ የመጣበት ጊዜ ነበር፡፡


3. ለቬትኮንግ ከፍተኛ ድጋፍ ከሆቲ ሚንህ ፣ከቻይናና ከሶብየት ህብረት መደረጉ ዋናዋናዎቹ ናቸው፡፡
በጦር ሜዳ ውስጥ ድል ማግኘት ባለመቻላቸው አሜሪካኖች በጦር አውሮፕላኖች ቦንቦች በመጠቀምን እንደ
አማራጭ በመውሰድ በሚሊዮን ካሬ ሜትር የሚገመት ቦታዎችን በቦንድ ደብደብዋል፡፡ በዚህም ስቃይና ስቆቃ
ምክንያት አርሶ አደሮች ይበልጥ የደቡብ ቬትናምን መንግስት ጠሉ፡፡ በ 1960 ዎቹም ጦርነቱም በራሷ
በአሜሪካ ተቀባይነት እያጣ መጣ፡፡ በዚህ የህዝብ ግፊት ሳቢያ ፕሬዜዳንት ኒክሰን (Richard nixon) በ 1969
የአሜሪካ ወታደሮች ከቬትናም ማስወጣት ጀመሩ፡፡ በተጨማሪም ቬትኮንግ የተሸሸገባቸው የላኦስና ካንቦዲያ
ግዛቶች በአዉሮፕላን ቦንብ እንዲደበደቡ ትእዛዝ ሰጡ፡፡ በ 1974 ሰሜን ቬትናሞች ደቡብ ቬትናምን
በመቆጣጠር አንድ ኮሚኒስት ፓርቲ በቬትናም እንዲፈጠር አደረጉ፡፡ ጦርነቱም ቢጠናቀቅም ከፍተኛ ጉዳት
አስከትሏል፡፡ በሰው ሀይል አንጻር 1.5 ሚሊየን ቬትናማውያን ሲሞቱ 58,000 አሜሪካውያንም ህይዎታቸውን
አጥተዋል፡፡

6.2.7 ኩባ (cuba)
በታሀሳስ 1956 የኩባ አርበኞችና አብዮተኞች በፊደል ካስትሮ (fidel Castro) መሪነት በኩባ ደቡብ ምስራቃዊ
ክፍል ከባቲስታ (Batista) መንግስት ጋር ትግል አደረጉ፡፡ ከ 82 ቱ ታጋዮች በህይት የተረፉት 12 ብቻ ሲሆኑ ወደ
ሴራ ሜስትራ (sierra mastera) በማቅናት ትግላቸውን ቀጠሉ፡፡

የኩባ መንግስት ከአሜሪካ እርዳታ ቢያገኝም አማጽያንን በቀላሉ ማሸነፍ አልቻለም፡፡ የአብዮተኞችን ማሸነፍ
የተገነዘበዉ ባቲስታ በጥር 7፣1959 ወደ ዶሚኒካን ሪፕብሊክ ተሰደደ፡፡ ፊደል ካስሮም ህዝባዊ መንግስት
(people’s gorelnment) መሰረተ፡፡ የካስትሮ መንግስት ብዙ ማሻሻያዎችን አውጇል፡፡ ጥቂቶቹ የሚከተሉት
ይገኙበታል፡፡
 በግንቦት 1960 ሰፋፊ የእርሻ ቦታዎች ወደ መንግስት ንብረትነት ተዛዉረዋል፡፡
 ከ 1960-1961 ኢንዱስሪዎች ወደ መንግስት ይዞታነት ተዛዉረዋል፡፡
 የከተማ ትርፍ መኖሪያ ቤቶችን በመንጠቅ ለላብአደሩ ተከፋፍሏል፡፡
 1961 የትምህርት ዓመት /literacy year/ ተብሎ ተሰይሞ ማህይምነትን ለማጥፋት ዘመን ታውጇል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች ሶቫሊስተ ሀገሮች የኩባን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ድግፍ አድርገዋል፡፡ በሌላ በኩል ግን
አሜሪካ ለውጦችን በመቃወም የኩባ ስኳርን መግዛት አቆመች፡፡ ይህም የአሜሪካ ንብረት የሆነ የስኳርና የነዳጅ
ማጥሪያዎች ፣የማዕድን ማዉጫዎች፣ የብረታ ብረት ፋብሪካዎችን በኩባ መንግስት መወረስን በመቃወም
ነው፡፡ በዚህ ጊዜ የኩባ ስኳር ወደ ሩሲያ መላክ የግድ ነበር፡፡

በተለይ በ 1961 ፕሬዜዳንት ኬኔዲ ወደ ስልጣን ሲመጡ የኩባ እና የአሜሪካ ግንኙነት በእጅጉ ሻከረ፡፡ ይህም
አሜሪካ ኩባን ትወራለች በሚለው ስጋት የተባባሰ ነበር፡፡ ይህም እዉን ሆኖ ኩባን ለመያዝ ወደ 1500 ሰው
በካርዶና መሪነት ተንቀሳቅሷል፡፡ በዋናነት ህዝቡ ኩባንያ በሚይዙበት ጊዜ በካስትሮ ላይ ያምፃል በሚል እሳቤ

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

ነበር የታቀደው፡፡ ነገር ግን የተሳበው ሳይሆን ህዝቡ በካስትሮ ላይ አላመፀም፡፡ በተለይ በ 1962 ኩባ የአለም
አቀፍ ውዝግብ ማዕከል ሆነች፡፡ ይህም የሆነው አሜሪካውያን በኩባ የሚሳይል ጣቢያ በሩሲያ ማቋቋሙን
ከደረሱበት በኋላ ነው፡፡ ይህም ጣቢያ ከአሜሪካ ከ 200 ማይል (ከፍሎሪዳ ጠረፍ) ብቻ የሚርቅ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ
ፕሬዜዳንት ኬኔዲ ወደ ኩባ የሚደረጉ ማናቸዉም የሚሳይል መሳሪያዎች በባህር ሃይሉ እንዲታገድ ትዕዛዝ
አወጡ፡፡ ይህ እገዳ እንዲነሳ ኩባ ላይ ያሉ ሚሳይሎች እንዲነሱ አዘዙ፡፡ ለጥቂት ቀናትም አለም በኒኩሊየር
ጦርነት ጫፍ ላይ ቆየች፡፡ በዚህ ጊዜ የሩሲያ ፕሪዜዳንት የነበሩት ክሩስቸቭ (khruschev) ሚሳይሎችን
ለማንሳት በመስማማታቸው አሜሪካ ኩባን ላለመዉረር ቃል ገባች፡፡ ውዝግቡም ሊቆም ችሏል፡፡

ተግባር-6.33
ከላይ በካስትሮ የተደረገው የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በኢትዮፕያ በደርግ ዘመን ከተደረጉ ማሻሻዮዎች ጋር
በማገናዘብ ተወያዩ?
አሜሪካ ከኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች በሻገር ከኩባ ጋር ያጋጫች ሌሎች ምክንያቶች ምን ይመስሎችኋል ?
ተወያዩባቸው ?
የኩባ የዚህ ዘመን ሁኔታ ከቀዝቃዛው ጦርነት ጋር ይዛመዳል ብላችሁ ታስባላችሁ? እንዴት?

የክለሳ ጥያቄዎች
የኢንዱስትሪዉ አብዮት ማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዉጤቶችን ዘርዝሩ፡፡
1. ለጣልያንና ለጀርመን ዉህደት ደጋፊና አደናቃፊ የነበሩ ምክንያቶችን ዘርዝሩ፡፡
3.የአሜሪካ ርስ በርስ ጦርነት መነሳት ዋና ምክንት ምን ነበር? የጦርነቱ ዋና ዋና ዉጤቶችን ዘርዝሩ፡፡
4.ለአንደኛዉ የአለም መነሳ ዋና ዋና ምክንያቶችን ዘርዝሩለ፡፡
5.የሁለተኛዉ የአለም ጦርነትን በማስነሳት የሚጠቀሱ ሀገራት እነማን ናቸዉ?
6.ከሁለተኛዉ የአለም ጦርነት በኃላ በአለማችን የተከናዎኑ ዋና ዋና ክስተቶችን ዘርዝሩ፡፡

የቁልፍ ቃላት ፍች

 ስነ ምድራዊ ጊዜ- መሬት ከተፈጠረችበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያለዉ ጊዜ


 ስነ ምድራዊ ድርጊቶች - በተለያዩ ዘመናት በመሬት ላይ የተከሰቱ ተፈጥሮአዊ ድርጊቶችን ማለት ነዉ
 ግጥግጦሽ - በልዩ ልዩ የተፈጥሮ ሁኔታዎች / ፀሀይ፣ ነፋስ፣ ዝናብና የፈሳሽ ዉሀ አማካኝነት የመሬት
መመናመን
 የባህር ወለል - ከፍታዎችን ሁሉ ለመለካት የሚጀመርበት ድንግግ የባህር ገጽታ አማካይ ቦታ
 አየር ቅጥ - የየወቅቱ የአንድ ቦታ አየር ጠባይ
 ኢንተር ትሮፒካል ግኑኝነት ሰቅ - በምድር ሰቅ አካባቢ ዝቅተኛ የአየር ግፊት የሚፈጠርበት ቦታ፡፡
 መሬት ሰቃዊ ምእራብጌ ነፋሶች - ከመሬት ሰቅ አካባቢ በአጠቃላይ ከምእራብ ወደ ምስራቅ አቅጣጫ
የሚነፍሱ ነፋሶች፡፡

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

 መሬት ሰቃዊ ምስራቄ ነፋሶች - ከመሬት ሰቅ አካባቢ በአጠቃላይ ከምስራቅ ወደ ምእራብ የሚነፍሱ
ነፋሶች፡፡
 ጥዱፍ ዉርድ - ከከባቢ አየር ወደ መሬት የሚወርድ የፈሳሽሳ ወይም የጥጥር ዉሀ ዝቅጠት፡፡
 የአየር ቅጥ ለዉጥ - በአንድ አካባቢ የሚገኝ አየር ቅጥ ተፈጥሮአዊና ሰዉ ሰራሽ በሆኑ ምክንያቶች
ቀደሞ የነበረዉ ጤናማ ሁኔታ ሲለወጥ፡፡
 ብዘኅ ህይወት - በአንድ አካባቢ የሚኖሩ በአይን የማይታዩ ረቂቅ ተዋስያን እንዲሁም ግዙፍ እንስሳትና
እጽዋት አይነትና ብዛታቸዉ፣ በመሐከላቸዉ ያለዉም ትስስርና መደጋገፍ፡፡

ዋቢ መጻህፍት

Namowitz and Spaulding (1985) Earth Science.D.C.Health and Copany.Toronto

Ferede Zewdu (2006). Biogeography / Teaching module / Bahirdar University


Department of Geography and Environmental studies, August 2006
Bahirdar
Ferede Zewdu (2005). Geomorphology/ Teaching module / Bahirdar
University, October 2005, Bahir Dar.

Mulugeta Tesefaye (2006).Introduction to Climate (Teaching module), Bahir Dar


University Department of Geography and Environmental studies, August
2006 Bahirdar
MoE (2006). Geography Student Text Grade 12 revised edition, Kuraz
International Publisher, Addis Ababa
Ministry of Education (2000). Geography Student Text Grade 10,Mega Publishinig Enterprise,
Addis Ababa.
Academy of Ethiopian Languges (1989) Science and Technology Dictionary / English- Amharic/.
Artitic printing press, Addis Ababa.
የኢፊዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር (2003). የህብረተሰብ ሳይንስ የተማሪ መጽሐፍ 8 ኛ ክፍል፣ የአል-ጎሬር
አታሚና ሳታሚ ድርጅት፣ ዱባይ የተባበሩት አረብ ኢሚሬት፡፡
Philip Curtin et al (1995). African History, NY.
Kevin Shiligton (1995). History of Africa
Sven Rubenson (1978). The survival of Ethiopian Independence,UK.
Bahru Zewdie (1998). A Short History of Ethiopia and the Horn, Addis Ababa

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል


Social Studies II SoSt- 222

University
Burns, Edward meniall (1958). Western Civilization, W.W. noron & co.
MoE (2006).History Student Text Grades 11&12

በጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የማሕበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል

You might also like