Professional Documents
Culture Documents
የቆሎ ተማሪዎች ልማዳዊ የህይወት አኗኗር ይዘት ትንተና
የቆሎ ተማሪዎች ልማዳዊ የህይወት አኗኗር ይዘት ትንተና
ጤና የኔአጋዥ
ደብረ ማርቆስ
በምስራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ከተማ አስተዳደር በ 01 ቀበሌ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ
ክርስቲያን የቆሎ ተማሪዎች ልማዳዊ ህይወት አኗኗር ይዘት ትንተና
ጤና የኔአጋዥ
ደብረ ማርቆስ
,
ማውጫ
ይዘት ገጽ
ማውጫ...........................................................................................................................................................i
ምስጋና...........................................................................................................................................................iv
አጠቃሎ..........................................................................................................................................................v
ምዕራፍ አንድ:- መግቢያ 1...................................................................................................................................1
1.1. ጥናቱ ዳራ.............................................................................................................................................1
1.2. የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት.............................................................................................................................2
1.3. የጥናቱ ዓላማ.........................................................................................................................................2
1.4. ጥናቱ የሚመልሳቸዉ ጥቄዎች.....................................................................................................................2
1.5 የጥናቱ ጠቀሜታ......................................................................................................................................2
1.6. የጥናቱ ወሰን..........................................................................................................................................3
1.7.በትናቱ ወቅት ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ እርምጃዎች......................................................................................3
1.7.1. በጥናቱ ወቅት ያጋጠሙ ችግሮች...........................................................................................................3
3.2.2. ቃለ መጠይቅ................................................................................................................................13
i
,
5.3. ስም ቅየራ............................................................................................................................................19
5.3.1. ከቤተሰብ ለመደበቅ..........................................................................................................................20
5.4.2. ክረምት.......................................................................................................................................22
5.8. መረዳዳት......................................................................................................................................27
ii
,
6.1. ማጠቃለያ...........................................................................................................................................29
6.2. የይሁንታ ሀሳብ.........................................................................................................................................30
አባሪዎች........................................................................................................................................................31
መረጃ አቀባዮች...............................................................................................................................................33
ዋቢ ጽሁፎች..................................................................................................................................................34
ምስጋና
ከሁሉ አስቀድሜ እዚህ እንድደርስ የረዳኝን ልዑል እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ ። ከዚህ በመቀጠልም ሙሉ
ጊዜዋን ሳሰስት ያለ ምንም መሰልቸት የተዋጣለት ስራ እንዳቀርብ የደገፈችኝን አማካርዬ (ዶ/ር) ድርቧ ደበብ
ምስጋየን ማቅረብ እፈልጋለሁ።እንዲሁም ጥናታዊ ጽሑፊን ስሰራ በገንዘብም ሆነ በሀሳብ ድጋፍ እየሰጡ ከጎኔ
ላልተለዩኝ ጓደኞቼ ÷ቤተሰቦች እና መረጃ በመስጠት ለተባበሩኝ ለሞጣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ አቨው
iii
,
አጠቃሎ
የቆሎ ተማሪዎች ልማዳዊ ህይወት አኗኗር በሞጣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ” በሚል ርዕስ
የተካሄደው ጥናት ዋና ዓላማ አድርጎ የተነሳው የቆሎ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ህይወት ምን እንደሚመስል
ማሳየት ነው፡፡ ይህ አላማ ግቡን ይመታ ዘንድ ለጥናቱ ግብአት የሆኑ መረጃዎች በምልከታና በቃለ መጠይቅ
ተሰብስበዋል፡፡ ይህ ጥናት በቆሎ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ጊዜ ተደጋግመው የሚከሰቱና የተማሪ
መገለጫ የሆኑትን እንደ ጉዞ ፣ ስም ቅየራ ፣ ልመና ፣ መረዳዳት የትምህርት ወቅትና የእርስ በርስ መማማር
የመሳሰሉ ጉዳዮች ተዳሰው ቀርበውበታል፡፡ ከጥናቱ መረዳት እንደተቻለው ተማሪዎች የሚፈፅሟቸው እንደ
ጉዞ ፣ ስም ቅየራ፣ ልመና ያሉ ጉዳዮች በተማሪዎች ዘንድ ሀይማኖታዊ ፣ ስነ-ልቦናዊና ፣ ማህበራዊ
ምክንያቶችን የያዙ ናቸው፡፡ እንዲሁም ማህበረሰቡ ለተማሪዎችና ለልመና ያለው አመለካከት ሁለት አይነት
iv
,
እንደሆነ ጥናቱ አሳይቷል፡፡ በህብረተሰቡ ዘንድ ተማሪዎች በአዎንታዊና በአሉታዊ መንገድ እንደሚታዩ ማወቅ
ተችሏል፡፡ ከጥናቱ መረዳት እንደ ተቻለው በቆሎ ተማሪዎች ዘንድ ክረምትና አብይ ፆም ሀሳባቸውን
ሰብስበው ለመማርና አዲስ ነገር ለመፍጠር ስለሚያግዟቸው በጉጉት የሚጠበቁ የትምህርት ወቅቶች ናቸው ፡፡
በተጨማሪም በተማሪዎች ዘንድ በዕውቀት በልጦ መገኘት በሚማሩበት ትምህርት ቤትም ሆነ በቀሪው
ማህበረሰብ ዘንድ ያላቸው ደረጃና ቦታ ከፍ እንደሚያደርግ ጥናቱ አሳይቷል፡፡ በመጨረሻ የቆሎ ተማሪዎች
በዋና ገፀ ባህሪነት የተሳሉባቸው ተረቶች ይዘታቸው ከተማሪ ህይወት ጋር በቀጥታ እንደሚቆራኝ ማወቅ
ተችሏል፡፡ ተረቶቹም ተማሪዎች በማህበረሰቡ ዘንድ የታዘቡትን ነገር የሚቃወሙባቸው፣ የራሳቸውን ማንነት
የሚገልፁባቸው፣ ያጡትን የሚያገኙባቸው ፣ ትዝብትና ተቃውሟቸውን የሚገልፁባቸው እንደሆኑ ጥናቱ
ያሳያል፡፡በተጨማሪም የቆሎ ተማሪዎች ልማዳዊ የህይወት አኗኗር በተመለከተ ከሀይማኖት ይዘታቸዉ
በተጨማሪ ልዩ ልዩ ማህበራዊ ጉዳዮችናእሴቶች የያዙ ስለሆነ የሚመለከታቸዉ አካላት በስፋትና በትኩረት
ሰጥተዉ ቢያጠኑት አለማቀፋዊ እዉቅና እንደሚያገኝ ጥናቱ ይገልጻል፡፡
v
,
1
,
2
,
3
,
ከሚለው የግዕዝ ቋንቋ የመጣ መሆኑን ኪዳነማርያም (198 ዐ፣ 81)ይገልፃል፡፡ስለዚህ ይህ ስያሜ ተማሪዎች
ከትምህርት በኋላ በሚሰጡት አገልግሎት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ የተማሪዎች ጥቅል መጠሪያ ሊሆን
አልቻለም፡፡
“የቆሎ ተማሪዎች” የሚለው መጠሪያ በሁለት ምከንያቶች በዚህ ጥናት ለተማሪዎች መጠሪያ ሆኖ
ተመርጧል፡፡ በመጀመያ ይህ ጥናት ልማዳዊ ጥናት እንደመሆኑ መጠን አካባቢያዊ ስያሜ ትልቅ ድርሻ
ይሰጠዋል፡፡ ለጥናት ከተመረጠው አካባቢ ከሁለቱ ስያሜዎች ይልቅ “የቆሎ ተማሪዎች” የሚለው መጠሪያ
በሰፊው ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ እንዲሁም ተማሪዎች እራሳቸውን የሚጠሩበት መጠሪያ ስለሆነ ሊመረጥ
ችሏል፡፡ በሌላ በኩል ስያሜው የተማሪዎችን ትክክለኛ ህይወት የሚያሳይ በመሆኑ ነው፡፡ በኢትዮጵያ
ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በተዘጋጀው የአማርኛ መዝገበ ቃላት መሰረት “የቆሎ ተማሪ” ማለት
ከየመንደሩ የሚያገኘውን ቁራሽ እንጀራ እንዲሁም ጥራጥሬውን በቆሎ መልክ እያዘጋጀ በመመገብ እንደ
ንባብ፣ ዜማ፣ ቅኔ፣ ወዘተ.ያሉትን የትምህርት አይነቶች የሚቀጽል የቤተክህነት ተማሪ ነው”ይህ ስያሜ
በሁሉም የትምህርት ደረጃዎች የሚገኙ ተማሪዎች ጥቅል መጠሪያ መሆኑ እና ስያሜውም የትምህርት ቤት
ህይወታቸውን የሚገልፅ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ ኪዳነማርያም ጌታሁን “ጥንታዊ የቆሎ ተማሪ” በሚለው
መጽሐፋ የቆሎ ተማሪ ማለት ጥሬ ቆርጥሞ፣ ውሃ ጠጥቶ በችግርና በረሃብ የሚማር መሆኑን ገልጿል
(198 ዐ፣ 6)፡፡ ከላይ የተነሱት ሁለቱም ስያሜዎች እንደገለፁት የቆሎ ተማሪ የሚለው መጠሪያ ህይወታቸውን
መሰረት አድርጎ የተሰጠ መጠሪያ ነው፡፡ በነዚህ ምክንያቶችም ስያሜው ለዚህ ጥናት የተማሪዎች ጥቅል
መጠሪያ ስያሜ በመሆን አገልግሏል፡፡
በገጠሯ ኢትዮጵያ በእያንዳንዱ የገጠር ቀበሌ የእራሱ ቤተክርስቲያንና ትምህርት ቤት አለው፡፡ ትምህርት ቤቶቹም ብዙውን ጊዜ
በቤተክርስቲያን አቅራቢያ የሚሰሩ ናቸው፡፡ ይህን ሃሳብ ለማጠናከር የሪቻርድ ፖንክረስትን ሃሳብ ማቅረቡ ተገቢ ይሆናል፡፡
4
,
ተማሪዎች ሃይማኖታዊ ትምህርትን ዋና ዓላማ አድርገው ቢነሱም በትምህርት ቤት ቆይታቸው እንደ ታሪክ፣
ግጥም፣ ሙዚቃ፣ ፍልስፍናና መድሃኒት ቅመማ፣ ወዘተ. የመሳሰሉትን የትምህርት አይነቶችን ሁሉ
እንደሚማሩ ሪቻርድ ፖንክረስት ያስረዳል Pankhurst (1966፣28)፡፡ ከሪቻርድ ፖንክረስት መረዳት
እንደሚቻለው ዛሬ ላይ የዘመናዊ ትምህርት ትኩረት የሆኑት የትምህርት ዘርፎች ቀደም ብሎም በኢተዮጵያ
የቆሎ ትምህርት ቤቶች ይሰጡ ነበር፡፡ በተጨማሪም እነዚህ ትምህርት ቤቶች በሀገራችን ለሚሰጠው ዘመናዊ
ትምህርት መሰረት መሆናቸውን መገንዘብ ይቻላል፡፡ እነዚህን ተማሪዎች የሚያስተምሯቸው መምህራን
በእውቀት የበለፀጉ እና በአውሮፖ “ኘሮፌሰር” ከሚባሉትምሁራን ጋር እንደሚስተካከሉ ሪቻርድ ፖንክስት
Lady Harber ን በመጥቀስ የመምህራኖቹን አዋቂነት ይገልጻል (1968፣29):: የቆሎ ተማሪዎች በትምህርት
ቤት ህይወታቸው በበዙ የእውቀት መስኮች የበለጸጉ ቢሆኑም የትምህርት ቤት ህይወታቸው ግን በችግርና
በስቃይ የተሞላ ነው፡፡ ችግራቸው የሚጀምረውም ገና ከመነሻው ቤተሰቦቻቸውን ጥለው በመሰደድ
በሚያደርጉት መስዋእትነት ነው፡፡ ይህን የተማሪዎችን ችግር ሀብተማሪያም እንደገለፀው በኢትዮጵያ ህዝቦች
ዘንድ ትምህርት ይወደድ ነበር፡፡ ህዝቡም በህብረት ትምህርት ቤት ይሰራና መምህራን ይቀጥር ነበር፡፡ ነገር ግን
በተማሪዎች ላይ ብዙ ችግር ይደርስባቸው ነበር፡፡ (1963፤29)፡፡
የቆሎ ተማሪዎች ለትምህርት ከቤተሰቦቻቸው ርቀው ሲሰደዱ ምንም ተስፋ የሚያደርጉት ነገር የለም፡፡
ከቤተሰቦቻቸው ፈቃድ ስለማያገኙ ቤተሰቦቻቸውን አማክረው ስንቅ ተሰንቆላቸው ከመሄድ ይልቅ በድብቅ
አስቸጋሪውን ህይወት ይጀምራሉ፡፡ ሪቻርድ ፖንክረስት እንደሚለው እውቀትን ተጠምቶ የሚሰደድ ተማሪ
ብቸኛ ሀብቱ የቁራሽ እንጀራ መለመኛ የምትሆንው “አክፋዳው”ብቻ ናት፡፡ ህይወቱንም በልመና በሚያገኘው
እንጀራ እንደሚመራ ተሰፋ በማድረግ ብቻ ነው ቤተሰቦቹን ጥሎ የሚሰደደው Pankhurst (1966፡29)፡፡ የቆሎ
ተማሪዎች እውቀትን ፍለጋ ከቤተሰቦቻቸው ርቀው ከተሰደዱ በኋላ በየትምህርት ቤቱ ሲገናኙ ኑሯአቸው
በመተሳሰብ ላይ የተመሰረተ የጋርዮሽ ኑሮ ነው፡፡ እምባቆም ቃለወልድ “ Tradasional Ethiopian church
school” በሚለው መጽሐፋ ተማሪዎች በጋራ ጎጆ ይቀልሳሉ ፣በጋራ ይሰራሉ፣ በጋራ ይማራሉ እንዲሁም
በጋራ ይመገባሉ በማለትማህበራዊ ህይወታቻው የጠነከረ መሆኑን ያስረዳል እምባቆም (197 ዐ 16፡19)፡፡
ህይወተቻው በጋርዮሽ ላይ የተመሰረተ መሆኑ እነዚህ ተማሪዎች እንደ አንድ ቡድን ተቆጥረው
ጥቅልህይወታቸውም ይጠናል፡፡
5
,
የቆሎ ተማሪዎችም ለጉዟቸው ምክንያት የሚሆናቸው ፍለጋ ነው፡፡ የቆሎ ተማሪዎች ከቤተሰብ ተነጥለው
ጋራ ሸንተረሩን አቆራርጠው እውቀትና ጥበበ ፍለጋ እጅግ አድካሚ ጉዞ ያደርጋሉ፡፡ቴዎድሮስ(2001፣60)
እንደገለጸው የሚፈልጉትን ነገር ለማግኘት የሚደረገው ጉዞ ዓለማዊም ሃይማኖታዊም መሰረት ሊኖረው
ይችላል የቆሎ ተማሪዎች ጉዞም ሁለቱን ነገሮች አጣምሮ የያዘ ነው፡፡
ልዩ የሚደርጋቸው ለዚህ ጥናታዊ ፅሁፍ የተሰበሰቡት መረጃዎች በፎቶ የተደገፈ ሲሆን ሌላው ልዩነት
የአለማየሁ ርዕስ Traditional Church Education መሆኑና ይህ ደግሞ የቆሎ ተማሪዎች ህይወት ላይ
መስራቱ ነው፡፡
ሌላው ምልከታ የተካሄደበት ጥናታዊ ጽሑፍ በላይነህ ደሴ በ 1999 ዓ.ም.“የቅኔ ቆጠራ ነገራና ዘረፋ በተመረጡ
የጎጃም ጉባኤዎች” በሚል ርዕስ ያደረገው ጥናት ነው፡፡ ይህ ሥራ ለኢትዮጵያ ሥነ ጽሁፍና ፎክሎር ድህረ
ምረቃ መርሃ ግብር ለሁለተኛ ድግሪ ማሟያ የቀረበ ጥናት ነው፡፡
6
,
አጥኚዋ የሪቻርድ ዶርሰንን ሀሳብ በመያዘ ሀይማኖታዊክንውኖችን ከልማዳዊ ጥናት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት
እንደሚኖራቸው ገልጿል፡፡ እነዚህ ባህላዊ ትምህርት ቤቶችም ሪቻርድ ዶርሰን በሚለው የፎከሎር ዘርፍ
ይጠቃለላሉ በማለት ባህላዊ የቅኔ ትምህርት አሰጣጥ በሀገረሰባዊ ልማድ ስር እንደሚጠቃለል ገልጿል፡፡
“የግዕዝ ቋንቋ ትምህርት አሰጣጥ”፡፡ በሚል ርዕስ ምስጢረ ሰዋሰው በ 1974 ዓ.ም.; ያደረገው ጥናት ሌላው
ተዛማጅ ጥናት ነው፡፡ ይህ ጥናት ለመጀመሪያ ዲግሪ ማሟያ የቀረበ ቢሆንም በጥናቱ ከተነሱ ጉዳዮች አንፃር
ግን ጥልቅ ምርምር የተካሄደበት ሥራ ነው፡፡ ጥናቱ ስለ ግዕዝ ቋንቋ አመጣጥ ታሪካዊ ዳሰሳ ካደረገ በኋላ
አባቶች በግዕዝ ቋንቋ ብዙ ፅፈዋል፡፡ እጅግ ብዙ ተመራምረዋል በማለት ይህንን እውቀት ከየት አመጡት
እንዴትስ ተማሩ የሚሉ መጠይቆችን ለመመለስ ጥናቱን ማካሄዱን ገልጿል፡፡ ይህ ቀጥተኛ ፅሁፍ ስለ ግዕዝ
ቋንቋ አመጣጥ መግለጽ በመሆኑም የግዕዝን ቋንቋ በዋነኝነት የሚጠቀሙት ደግሞ የቆሎ ተማሪዎች ናቸው፤
በዚህ የተነሳ እንዲመሳሰሉ አድርጓቸዋል፡፡ መረጃውን የሰበሰበውም ይህንን ትምህርት ከተማሩት አባቶች ጋር
በቀጥታ በመገናኘት ማለትም በምልክት በመሆኑ ተመሳስለዋል፡፡የሚለያዩበት ሚስጢረ ስለትምህርት አሰጣጡ
ያጠና ሲሆን ይህ ጥናት ደግሞ ህይወታቸው ምን እንደሚመስል፣ ምን ምን ነገሮችን በህይወታቸው ውስጥ
ያሳልፋሉ የሚለውን የሚገልፅ በመሆኑ ነው፡፡
ሌላው ልዩነታቸው ሚስጢረ ሁለት የታወቁ የቅኔ ጉባኤዎች በማነፃፀር ያቀረበ በመሆኑ ነው፡፡ በተጨማሪም
የቆሎ ተማሪዎች የለተያዩ አጋጣሚዎች ሲያጋጥማቸው እንደት ራሳቸውን እንደሚያሳውቁና ምን አይነት
የመፍትሔ ሀሳቦችን እንደሚያመነጩ ባለማሳየቱ ይህ ጥናት ደግሞ እነዚህንና መሰል ጉዳዮችን ማሳየቱ
ይለያያቸዋል፡፡
ምስጢረ በማጠቃለያው ባህላዊ ትምህርት ቤቶች ኋላ ቀርና የማይለወጡ ሳይሆኑ ብዙ የህይወት ልምዶች
የሚገኙባቸው የእውቀት ማዕከላት መሆናቸውን በአፅንኦት ገልጿል፡፡ በአጠቃላይ ይህ ሥራ የተማሪዎችን
ህይወትም በጥልቀት ለመመርመር ባደረገው ጥረት ከዚህ ስራ ጋር ሲመሳሰል ማህበረሰቡ ለተማሪዎች ያለውን
አመለካከት ባለመግለፁ እና በስነቃሎቻቸው ህይወታቸው እንዴት እንደሚገለፅ ባለማየቱ ከዚህ ጥናት ጋር
እንዲለያይ አድርጎታል፡፡
7
,
አምሀ ኢየሱስ አስፋ በ 1994 ዓ.ም.“መንፈሳዊ ትምህርት ቤት /ቄስ ትምህር ቤት በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ
ያደረገው ጥናት ምልከታ ተካሂዶበታል፡፡ ጥናቱ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ዲግሪ ማሟያ
የቀረበ ስራ ነው፡፡ አጥኚው ገና ከመነሻው በቄስ ትምህርት ቤቶች ላይ እና በሚያነሷቸው ጉዳዮች ላይ የቀረበ
ጥናት ባለማግኘቱ ይህንን ጥናት ለማካሄድ መነሳቱን ገልጿል፡፡ አጥኚው የሙዚቃ ትምህርት ቤት ተማሪ
እንደመሆኑ መጠን ትኩረት ያደረገው ከቄስ ትምህር ቤት ደረጃዎች መካከል በ “ዜማ ቤት” ላይ ነው፡፡ ጥናቱ
በዜማ ቤት ላይ ቢያተኩርም በመረጃ መሰብሰቢያ መንገዶች ጉድለትምከንያራት ስራውን በትክክል መግለፅ
አልቻለም፡፡ ገና ከርዕሱ ቄስ ትምህርት ቤት በኢትዮጵያ ብሎ ርዕሱን ሰፊ ቢያደርገውም የተጠቀመባቸው
የመረጃ መሰብሰቢያ መንገዶች ግን ከሥራው ጋር አብረው የማይሄዱ ናቸው፡፡ ምክንያቱም ጥናቱ የተካሄደው
በእድሜ ገፋ ያሉ ቄሶችን ብቻ ቃለ መጠይቅ በማድረግ መሆኑ በጥናቱ ተገልጿልና ነው፡፡
የአምሀ ኢየሱስ ጥናት ዋና አላማው የቄስ ትምህርት ቤት በኢትዮጵያ እንዴት እና መቼ እንደተጀመረ ታሪካዊ
አመጣጡን ማሳየት ነው፡፡ በውጤቱም እነዚህ ትምህርት ቤቶች መቼ እንደተጀመሩ በውል ማውቅ ባይቻልም
ለዘመናዊ ትምህርት መነሻ መሆናቸውን ግን አሳይቷል፡፡
ሌላው ቅኝት የተደረገበት ሥራ ገዛኸኝ ጌታቸው የአብነት ትምህርት ቤቶች ለዘመናዊ ትምህርት እድገትና
ለሀገሪቱ አስተዳደር ያደረጉት አስተዋፅኦ /አመተ ምህረት ያልተጠቀሰ/ በሚል ርዕስ ያቀረበው ጥናታዊ ጽሁፍ
ነው፡፡ ጥናቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
8
,
ማህበረ ቅዱሳን ባላቸው ሀገር አቀፍ አውደ ጥናት ላይ የቀረበ ሥራ ነው፡፡ ይህ ጥናት የምርምር ጥያቄዎችን
በማንሳት በጥናቱ መልስ ለማግኘት ሞክሯል፡፡ በጥናቱ እንደተገለፀው በቤተክርስቲያን ትምህርት
የሚሰጥባቸው ማዕከላት በተለምዶ የቆሎ ትምህርት ቤት ይባላል፡፡ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች ዓላማ
የቤተክርስቲያን ሊቃውንትን ማፍራት ቢሆንም አያሌ ሀገራዊ ተግባራትን ለኢትዮጵያ ሲያበረክቱ
መቆየታቸውን መረጃ እያጣቀሰ ማሳየት ችሏል፡፡ ሀገራችን ታሪኳ ተመዝግቦና ተጠብቆ የኖረው ከቆሎ
ትምህርት ቤቶች ተምረው በሚመጡ ተማራዎች እንደነበር ማሳየትችሏል፡፡ በሀገራችን ሕግ አውጭም ሆነ
ሕግ አስከባሪ አካላት የሚመጡት ከእነዚህ የትምህርት ማዕከላት እንደነበር በአፅንኦት ገልጿል፡፡
ገዛኽኝ ከዚህ በፊት በእነዚህ ትምህርት ቤቶች ላይ ጥናት ያካሄዱ ተመራማሪዎች የትምህርት ቤቱን ጠንካራ
ጎን ከመመልከት ይልቅ ለሀገራችን ድህነትና ኋላቀርነት ተጠያቂ ሲያደርጓቸው መቆየታቸውን አንስቷል፡፡
ይህም ሳይንሳዊ ምርምር ሳያደርጉ ከግል ስሜት የመነጫ ሃሳብ ነው በማለትአጥኝዎችን ይነቅፋል፡፡ ይልቁንስ
እነዚህን ትምህርት ቤቶች የታሪክ የባህልና የፖለቲካ ተመራማሪዎች በጥልቀትና በገለልተኛነት ሰሜት
ሊመረምሯቸው ይገባል በማለትየግልአስተያየቱን አስቀምጧል፡፡ አጥኝው በማጠቃለል እንደገለፀው ሀገር
በቀል እውቀት ለአንድ ሀገር እድገት ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው፡፡ የቆሎ ትምህርት ቤቶችም ሲያደርጉ
የኖሩት ይህንን ነው በማለት የነበራቸውን ሀገራዊ ፋይዳ አንፀባርቋል፡፡ አያይዞም የሙዚቃ፣ የሰነ ፅሁፍ፣ የስነ
ልቦናና የፍልስፍና ትምህርት ከፍሎች ከነዚህ ትምህርት ቤቶች ጋር የሚገናኙበት ሁኔታ ስላለ ትኩረት ሰጥተው
ቢመረምሯቸው ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልጿል፡፡ የቆሎ ትምህርት ቤቶች የብዙ ነገር መገኛ መሆናቸውንም
ለማንፀባረቅ ሞክሯል፡፡ ከዚህ አኪያ ጥናቱ ይዞት ከተነሳው ርዕስና የምርምር ጥያቄ አንፃር ግቡን መቷል ማለት
ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ በዚህ ጥናት አድራጊ ቅኝት የተደረገባቸው ስራዎች ለተለያየ ዓላማ የተደረጉ ጥናቶች ቢሆንም
በቀጥታም ሆን በተዘዋዋሪ መልክ ከቆሎ ተማሪዎች ጋር የሚገናኙ ጉዳዮችን ስለሚያነሱ ከዚህ ጥናት ጋር
ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ ጥናቶቹ ከስነ ትምህርት ፣ ከታሪክና ከሙዚቃ ጋር በተያያዘ የተጠኑ ቢሆኑም ሁሉም
የቆሎ ትምህርት ቤቶች የብዙ ነገር መገኛ መሆናቸውን መመስከር ችለዋል፡፡ እያንዳንዱ ሥራ የራሱ ደካማና
ጠንካራ ጎን እንዳለ ሆኖ የተማሪዎችን ህይወት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በማንሳታቸው ከዚህ ጥናት ጋር
ተመሳሳይነት ፈጥረዋል፡፡ በአንፃሩ ሁሉም የተማሪዎችን ህይወት ሲያነሱ ሰነቃሎቻቸወን ሳይመለከቱ
በመቅረታቸው ከዚህ ጥናት ጋር ይለያያሉ፡፡
9
,
3.2.የመረጃ መሰባሰቢያ ዘዴ
ጥናታዊ ስራን ለማቅረብ መሠረታዊ ከሆኑ ነገሮች አንዱ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ነው፡በዚህ ጥናታዊ
ፅሁፍ ውስጥ ካሉት የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ውስጥ ሁለት አይነት የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች
አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ እነሱም ምልከታእና ቃለ መጠይቅ ናቸው፡፡
3.2.1. ምልከታ
አጥኚዋ ለዚህ ጥናት ለ 5 ጊዜ ያህል ዓላማን መሰረት ያደረገ ምልከታ በማድረግ መረጃን መሰብሰብ
ችላለች፡፡ምክንያቱም ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት ዓላማ በማዘጋጀት ና በመንደፍ አመቺ ሁኖ በመገኘቱ
ነዉ፡፡የአጥኚዋ ምልከታም የቆሎ ተማሪዎች ልማዳዊ ህይወት ምን እንደሚመስል ÷የአኗኗር
ዘይቤያቸውን ÷የትምህርት ስዓታቸውንእና የአመጋገብ ስርዓታቸውን በአይነ ህሌናዋ በማየት
ነው።ምልከታው የተካሄደውም ተማሪዎች በሚገኙበት ቦታ በመገኘት ነው። ምክንያቱም አጥኚዋ
በአካል ተገኝታ ለጥናቱ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ለመሰብሰብ ነው። መረጃው የተሰበሰበበት
መንገድም የቆሎ ተማሪዎች የሚያደርጉትን ተግባራት በመቃኘት ነው።በምልከታ ወቅትም የተገኘ
መረጃ የቆሎ ተማሪዎች በትምህርት ወቅት ሲኖሩ አንዱ ከአንዱ ጋር በመተባበር ማለትም ከራሳቸዉ
ይልቅ ለሌላ ቅድሚያ በመስጠት ፣በተለይ ለአዲስ ገብ ተማሪዎች የተለየ ክብር መስጠት፣ለልመና
ሲወጡ ማታ የተማሩትን ሲጠያየቁ፣ምግብ ለመመገብ ሲቀርቡ በጋራ ጸሎት አድርገዉ ሲመገቡ
ተመልክቻለሁ፡፡ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ የትምህርት ስርዓታቸዉ ጀማሪና ነባር ተማሪዎች አብረዉ
በአንድ ላይ ሲማሩ ተመልክቻለሁ፡፡ምልከታ የተካሄደዉ ተማሪዎች በተገኙበት አጥኚዋ በአካል በመገኘት
10
,
ለጥናቱ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በመሰብሰብ ነዉ፡፡ይህ መረጃም የተሰበሰበበት መንገድ የቆሎ
ተማሪዎች የሚያደርጉትን ተግባር በማየት ነዉ፡፡
3.2.2. ቃለ መጠይቅ
አጥኚዋ ያዘጋጀው መጠይቅ ልቅ ቃለ መጠይቅ ነው። ለዚህ ጥናትም ተጠያቂ የሚሆኑ ስዎች
ለቆሎተማሪዎች ቅርበት ያላቸው ስዎች ናቸው።
እነዚህም መርጌታዎች÷ቄሳውስቶች÷መዘምራን እና ተማሪዎች ናቸው፡፡አጥኚዋ ይህንን ጥናት ስታጠና
ለሁለት መርጌታ፣ለሁለት ቄስ፣ለአንድ መዘምር እና ለሁለት ዲያቆን በጠቅላላ ለሰባት ሰዎች ቃለ
መጠይቅ በማዘጋጀት መረጃዎችን ሰብስባለች፡፡የቆሎ ተማሪዎች በብዛት አካባቢያቸዉን ለቀዉ ሂደዉ
ስማቸዉን ቀይረዉ የሚማሩበት ምክንያት የተማሪ ወላጆች የቆሎ ተማሪ እንዲሆኑ ፍቃደኛ
ካለመሆናቸዉ የተነሳና እሽ ብለዉ ስለማያስተምሯቸዉ መሆኑን በቃለ መጠይቅ አረጋግጣለች(ቄስ
ሐይማኖት አጋዥ፣ጥር፣2014 ዓ.ም)፡፡
የቆሎ ተማሪዎች በሚማሩበት ወቅት እንጀራ ሆነ የተገኘዉን ነገር ይለምናሉ ይህ የቆሎ ተማሪዎች
ስርዓት ነዉ፡፡ስረኣቱን ማፍረስና አለምንም ማለት አይቻልም፡፡ሁሉም ተማሪ በጎጥ በጎጥ በመደልደል
ስዓቱን ጠብቆ ያገኘዉን ነገር ይዞ መመለስ አለበት፡፡የመጣዉም ነገር በጋራ ጸሎት ተደርጎ በጋራ ይበላል
(ዲያቆን ዘላለም አዱኛዉ፣መጋቢት፣2014 ዓ.ም)፡፡
በቆሎ ተማሪዎች ዘንድ በትምህርት ቆይታቸዉ የተለየ የትምህርት ወቅት ተብሎ የሚታሰበዉ
በክረምት ና በአብይ ጾም ወቅት ነዉ፡፡ምክንያቱም በእነዚህ ወቅቶች በክረምት ከተፈጥሮ ክስተቶች
ጋር በማያያዝ አዳዲስ ነገሮችን እየፈጠሩ እንዲማሩ ጾም ደግሞ በጾም ና በጸሎት ተግተዉና
በርትተዉ ሲማሩ ትምህርት ይገባቸዋል ተብሎ ስለሚታሰብ ነዉ(መዘምር እዝራ
ማህሪዉ፣የካቲት፣2014 ዓ.ም)፡፡
አዳዲስ የቆሎ ተማሪዎች ሲመጡ የተለያዩ አቀባበሎች ይደርግላቸዋል፡፡ማለትም ለትምህርቱ አዲስ
የሆኑ እንዲሁም የትምህርት እድገት ለማሻሻል ብለዉ የመጡ ተማሪዎችን ልክ እንደ አብሮ አደግ
ጓደኛ በመንከባከብና በማላመድ ከነሹ ህይወት አኗኗር ጋር አብረዉ እንዲሳተፉ ያደርጋሉ (መርጌታ
ዐይነ ኩሉ ደባስ፣የካቲት፣2014 ዓ.ም)፡፡
11
,
ይገባል፡፡ መረጃዎች እንደጥናቱ አይነት መጠናዊ ወይም አይነታዊ ሊሆኑ ይችላሉ ያለውእንዳወቅ ሙሉ
(2004፣ 243)፡፡
ይህ ጥናት ትኩረት ከተሰጠዉ ርዕስ በመነሳት ዓይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴን ማለትም ምልከትና
ቃለ መጠይቅ ተጠቅሞ የተሰበሰበዉን መረጃ በመተንተነና በማብራራት ገለጻና ሀተታ የሚጠይቅ
በመሆኑ ነዉ፡፡ስለሆነም ስለ ቆሎ ተማሪዎች ልማዳዊ የህይወት እይታ አስመልክቶ የመረጃ ምንጮች
የሰጡትን ሃሳብና የተሰበሰበዉን መረጃ ሀተታዊ ስለሆነ አጥኚዋ ለመተንተን ዓይነታዊ የመረጃ
መተንተኛ ዘዴን ተግባራዊ አድርጋለች፡፡
ከዚህ በመነሳት በቃለ መጠይቅና በምልከታ የተሰበሰቡት መረጃዎች በገላጭ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ
ተተንትነዋል።
12
,
ሞጣ ከተማ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሚገኙት ከተማ አስተዳደሮች ዉስጥ
አንዷ ስትሆን፤የተመሰረተችዉም በ 1747 ዓ.ም በወለተ እስራኤል አማካኝነት እንደሆነ አበዉ ይናገራሉ፡፡ሞጣ
ከሌሎች ከተማ አስተዳደሮች ልዩ የሚያደርጋት ዋ ለካ ያ ሰባቱ ዋርካ እየተባለ የሚዜምላት ድንቅ ከተማ
በመሆኗ ነዉ፡፡እነዚህ ሰባቱ ዋርካ ከተማዋ ስትቆረቆር ጀምረዉ አብረዉ የበቀሉ እንደሆሉ ይናገራሉ፡፡ከተማዋ
በስድስት(6) ቀበሌዎች የተዋቀረች ናት፡፡ለመኖር ምቹ (ተስማሚ) የአየር ንብረት ያላት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ
በከተማዋ ዉስጥ የሚኖሩ ህዝቦች በአብዛዉ በንግድ ስራ ፣በመንግስት ስራ እና እንዲሁም በተወሰነ ደረጃ ደግሞ በእደ
ጥበብ ዉጤቶች ፣በከብት እርባታ ይተዳደራሉ፡፡በዚች ከተማ አስር የሚደርሱ ቤተ ክርስቲያን ና አስራ ሁለት መስጊዶች
ይገኛሉ፡፡ከተማዋ በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ የተከበበች ስትሆን በሰሜን መክሊት፣በደቡብ ድመት ገደል፣በምስራቅ ምን
ታዝግባና በምዕራብ ወብ ማርያም ከበሌዎች ያዋስኗታል፡፡የትራንስፖርት አገልግሎት በመኪና ከዞን ከተማ 192 ኪ.ሜ ርቀት
ላይ ስትገኝ ከክልል ከተማ ደግሞ 120 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ሞጣ ከተማ ከደብረ ማርቆስ ከተማ ይልቅ ለባህር ዳር
ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኝ ዉብና ማራኪ ከተማ ናት፡፡በእምነት የተለያዩ ህዝቦች የሚኖሩባት ከተማ ብትሆንም
በደስታና በመከራ ጊዜ የሙስሊምና የክርስቲያን አማኞች የተለየ መዋደድና ፍቅር አላቸዉ፡፡ማለትም በሰርግ ስነ ስርዓት ላይ
የክርስቲያን ከሆነ ከሙስሊሞች ሴቶች ተመርጠዉ ድግሱን ያዘጋጃሉ፤የክርስቲያን ሲሆንም እነዲሁ ያዘጋጁና አብሮነታቸዉን
ሲያዳብሩ የኖሩ ታላቅ ህዝቦች ናቸዉ፡፡በተጨማሪም በሀዘን ስርዓት ላይም በአንድ ላይ የሃዘን ተካፋይ በመሆን አብረዉ
በህበረት በመኖር ባህላዊ እሴታቸዉን እያዳበሩ የሚኖሩ ህዝቦች ናቸዉ፡፡
5.1. ጉዞ
በቆሎ ተማሪዎች ህይወት ውሰጥ ጉዞ የመጀመሪያው ክስተት ነው። ከንባብ ቤት ተማሪዎች በስተቀር
በሁሉም ደረጃዎች ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በአንድም ሆነ በሌላ ምክንያት አድካሚና እልህ አስጨራሽ ጉዞ
13
,
መምህር ሳይቀያየር ምኑን ተማሪ ሆነው፤ በእናት እጅ እየጎረሱና ሆድ ሙሉ እየበሉ ትምህርት የለም።
ፈጣሪም እናንተ ልፉ እኔ እጨምርላችኋለሁ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ተማሪ አብዛኛውን ህይወቱን በራሱ ፍቃድ
የተሰደደ ስደተኛ ሆኖ ይኖራል። አሁን እዚህ እኛ ዘንድ ያሉት ተማሪዎች ከተለያ የ ቦታ የመጡ ናቸዉ የሚሉ
ከላይ በምክንያትነት ከቀረቡት ሃሳቦች መረዳት የሚቻለው በተማሪዎች ስነልቦና ትምህርት መሰዋእትነትን
አላማን ለማሳካት እና ተሽሎ ለመገኘት መፈተንና መቸገር አለብን ብለው ስለሚያምኑ ቤተሰቦቻቸውን
ይቆጥሩታል።
5.2. ልመና
የቆሎ ተማሪዎች ተለይተው የሚታወቁበት አንዱልመና ነው። በትምህርት ቤት የሚያሳልፉትን
ህይወትየሚማሩት (በእንተ ስሟ ለማርያም) ብለው በሚያገኙት ቁራሽ እንጀራ ነው። በቆሎ ተማሪዎች
ለልመና የሚወጡበት ሰዓትበአማካኝ ከዘጠኝ ሰዓትበኋላ ነው። ይህም የሆነበት ሁለት ምክንያቶች አሉት።
አንደኛውምክንያት ከሚለምኑት ማህበረሰብ የስራ ባህል ጋር የተያያዘ ነው። ይህጥናት በተካሄደበት አካባቢ
በየስራው ተሰማርተዉ የሚውሉ ሰዎች ወደ ቤቱ የሚመለሰው ከአስር ሰዓት በኋላ በመሆኑ ነው።
ተማሪዎች ከዚህ በፊት ለልመና ቢነሱ በየቤቱ ሰው ስለማያገኙ ነው። እና በቤት ውስጥ የሚያገኙት ህጻናትን
ብቻ በመሆኑ ነው። ስለዚህ ለልመና ወጥተው ባዶ እጃቸውን እንዳይመለሱ የገበሬዎችን የመመለሻ ሰዓት
ጠብቀው ለልመና ይወጣሉሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ከትምህርት ሰዓታቸው ጋር የሚገናኝ ነው። እስከ
ስምንት እና ዘጠኝ ሰዓት ያለው ሰዓት በአበዛኛው የትምህርት ሰዓታቸው ስለሆነ ከዛ በኋላ ለልመና
ይንቀሳቀሳሉ(ቃለ መጠይቅ)
14
,
ድልድሉም የሚካሄደው በእጣ ነው። እያንዳንዱ ተማሪ በእጣ የደረሰው መንደር ብቻ በመሄድ መለመን
እየተቀያየሩ ሁሉም ተማሪዎች ሁሉንም መንደር የማግኘት እድል እንዲኖራቸው ሲባል ነው።
የተሰራ ሲሆን የሚለምኑትን ቁራሽ እንጀራ ከመያዝ ባለፈ ትልቅ ትምህርት አለው። ይህም ከሃይማኖታቸው
እንጀራ ከመያዝ በተጨማሪ የእመቤታችን ድንግል ማርያም ማደሪያ ነው ብለው ያምናሉ።በዚህም መሰረት
ያገኝናትም ትንሽ ነገር በረከት ይኖራል በተጨማሪም የዕለት ጉርሳችውን የምታዘጋጅላቸውም ሆነ ከክፉ ነገር
እምነታቸውን ለመግለጽ ማንም ተማሪ ለልመና ወጥቶ በመንገድ ላይእያለ አቆፋዳው ውስጥ ያለውን ቁራሽ
የመሽኘት ስርአቱም እራሱን የቻለ ደንብ አለው። አንድ ተማሪ ዛሬ ላይ የመለሰችው ድንግል ማርያም ነገ
ሰአቱ ደርሶ እስክትመትጣ በሰላም መሸኘት አለበት። ከልመና የመጣ ተማሪ የያዘውን አቆፋዳ እንደያዘ ወደ
ጎጆው አይገባም። በአካባቢው ላሉ ተማሪዎች ከአቆፋዳው እያወጣ(የማርያም መሸኛ)በማለት ያቃምሳል።
ይህንን ካደረገ በኋላ በነጻነት መመገብ ይቻላል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመንገድ ላይ ሰው እንኳን ሳያያው የቀመሰ
ተማሪ ካለ ሰይጣን አሳሳተኝ ብሎ ለጓደኞቹ ይናዘዛል እንጂ ዝም ብሎ አይቀመጥም።
ሁለተኛ የመለመኛ ቁሳቁስ በትር ነው። አገልግሎቱ ውሻ በሚመጣበት ጊዜ እራሱን የሚከለክልበት ብቸኛ
መሳሪያ ነው።ረጂም የሚሆንበት ምክንያት ውሻውም ከርቀት ለመመለስ እንዲያመቸው ነው። አንድ ተማሪ
በሚለምንበት ወቅት ውሻው ከርቀት የቱንም ያህል ቢያስቸግረው እራሱን መከላከል እንጂ ውሻውን
መደብደብ አይችልም።የማይደበድብበት ምክንያት ውሻውን ከደበደበ የሚለምነውን ሰውዬ (የውሻው ባለቤት)
15
,
5.2.4.1.አወንታዊ አመለካከት
የቆሎ ተማሪዎች ከቤታቸው የሚወጡት ጥበብን ፍለጋ ነው።የድንግል ማርያምንስም ጠርተው የሚኖሩ
የፈቃደኛ ስደተኛችመሆናቸውአምኖ የሚቀበል ማህበረሰብም ይህን አስቸጋሪ የሆ ነውን ህይወት አልፎ
በአለም የቤተክርቲያን አገልጋይዮች በመሆን እነሱን ከፈጣሪያቸው ጋር የሚያገናኙና የመሸጋገሪያ ድልድይ
መሆናችውን ስለሚያምኑ ልመናቸውን በደስታ ይቀበላሉ፡፡እንዲኖሩም ከፍታኛ ጉጉት አላቸው፡፡የዛሬዎቹ
ተማሪዎች ነገ የእግዚአብሔር አይኖች ናቸው፡፡ስለሆነም ሲለምኑ መስጠት እንደ ጽድቅ ሳይለምኑ መቅረት
ደግሞ በረከት እንደማጣት ይቆጠራል፡፡ነገ የሚደርሱበትን በማሰብለልመና በበራቸውለሚቆም ተማሪ ትልቅ
ክብር ይሰጣሉ፡፡ይህንን በማሰብተማሪ ካለመነ ምነው ረድኤት ተለየንፈጣሪእራቀን ብለው ያምናሉ፡፡ ይህንን
ለማረጋገጥ ተማሪዎችን በልመና ለይተው ከሚተዳደርሸ ሌሎች ሰዎችለይተው የሚመለከቱበት እይታቸው
ነው፡፡ ለምሳሌበአካባቢው ከሚኖሩ ሰዎች በተገኘ መረጃ መሰረት ሌሎች ለማኞች ሲቆሙ”ለማኝ
ቆሟል”ሲሉ ተማሪ ለልመና ሲቆም“ተማሪ ቆሟል” ይላሉ፡፡ስለዚህ ተማሪዎች አጥተው ወይም መስራት
ሳይችሉ ቀርተው ሳይሆን ለትምህርት ሲሉ የወጡ መሆናቸውን አውቀዋል ማለት ነው፡፡ወይም ደግሞ ተማሪ
እግረ እርጥብ ነው በረከት ይዞ ይመጣል በማለት ለሚሰጡት ቁራሽ እንጀራ አንዳች ቅሬታ አያድርባቸውም፡፡
ተማሪ ከበራቸው ላይ ካልቆመ እምነታችንን ተጠራጥሮታል ወይም እግዚአብሔር እርቆኛል ብለው ያምናሉ፡፡
በእንተ ስሟ ለማርያም ብሎ የሚለምን ተማሪበበራቸው ቢቆም ግን ፈጣሪ ታርቆኛል በቤቴ በረከት ሊገባ ነው
የሚል ተስፋ በውስጣቸው ያድራል፡፡
5.2.4.2.አሉታዊ አመለካከት
ይህ አሉታዊ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ተማሪዎችን የሚመለከቱበት አተያይ በተለያየ ምክንያት ፍርሀት
ያለባቸው ናቸው፡፡ ፍርሀታቸውን ተማሪዎች ተንኮለኛ፣ድግምትና ጥንቆላ ያደርሳሉ ብለው ስለሚያምኑ ነው፡፡
ስለዚህ ሳንሰጣቸው ቢመለሱ በልጆቻችንና በንብረታችን ላይ ድግምት ሊያደርሱብን ይችላሉ የሚል
አመለካከት አላቸው፡፡ ከወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ ጋር በተደረገ ውይይት ‹‹ የበሰለ ነገር ባይኖር እንኳ ጥሬ ቢሆን
አፍሰን እንሰጣቸዋለን፡፡ ምጣድም አልጣድን ብለን ብንመልሳቸው ተንኮል ያስቡብናል በማለት ስጋታቸውን
ገልጸዋል፡፡''ይህ አመለካከት የሚሳያን የተማሪዎችን አዋቂነት ከማህበረሰቡ የተሻለ ሁሉንም የማድረግ ችሎታ
እንዳላቸው መገንዘብ ይቻላል፡፡
16
,
5.3. ስም ቅየራ
በቆሎ ተማሪዎች ህይወት ውስጥ ከሚመጡ ክስተቶች መካከል ስም ቅየራ አንዱ ነው።አብዛኞቹ የቆሎ
ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸው ያወጡላቸውን ስም ትተው በሌላ ስም ይጠራሉ።ከተማሪዎች በተገኘ መረጃ
መሰረትም ስማችውን የሚቀይሩበት የራሳቸው ምክንያት አሏቸው፡፡
(ጥር፣17፣2014 ዓ.ም በቅዱስ ጊዮርጊስ ከሚማሩ የዜማ ተማሪዎች ውስጥ ተማሪ በቃሉ ይርጋ እንዳለዉ ወደ
አዲሱ ጉባዔ (ትምህርት ቤት)የሚቀላቀል ተማሪ በምንም መንገድ ትክክለኛ ስሙን አይናገርም።በጣም
የሚቀራረቡና አብሮ አደግ ጓደኛሞች ቢኖሩም እንኳን ትክክለኛ ስማቸውን ላይጠራሩ ይማማላሉ።
17
,
5.4.1. ዓብይ ጾም
በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ የዓብይ ጾም በአማካይ ወደ ሁለት ወር የሚጠጋ ነው፤
ይህ ወቅት ጉባኤዎችከሌላው ጊዜ በተለያየ መልኩ በተማሪዎች የሚደምቁበት ጊዜ ነው።
ተማሪዎችም እንደዋና የትምህርት ወቅት በጉጉት ይጠብቁታል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት አንደኛ
ተማሪዎቹ በጾምና በጸሎት ተግተን ስንማር ትምህርት ይገባናል ብለው ስለሚያምኑ ነው፡፡በጾም ወቅት
ረጅምመንገድ በእግር መጓዝ ስለማይፈቀድ ተማሪዎች በተረጋጋ መንፈስመማር ስለሚችሉ ነው።
ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በዚህ ወቅት የጾም ወቅት ስለሆነ በሃይማኖቱ ተከታዮች ዘንድ ምንም አይነት
ድግስ አይደገስም።ድግስ አለመደገሱ ደግሞ ተማሪዎች ድግስ ፍለጋ ከቦታ ቦታ እንዳይዞሩና በትምህርታቸው
እንዳይዘናጉ ይጠቅማቸዋል።ምክንያቱም የተለያዩ ድግሶች የሚኖሩ ከሆነ መምህሩ በጥሪ ተማሪዎች ደግሞ
ለልመና ስለሚሄዱ በጉባኤ ላይ ላይገኙ ይችላሉ።ስለዚህ በጾም ወቅት መምህራኖች ወዴትም
ስለማይንቀሳቀሱ መምህሩ እና ተማሪዎች እንደልብ የመገናኘት እድላቸው ከፍተኛ ነው። በተጨማሪም በጾም
ወቅት በሚከናወን ቅዳሴ የዜማተማሪ፣ በአብይ ጾም ወቅት በሚከናወን ቅኔ ተማሪ ደግሞ በሚከናወነው ቅኔ
በተግባር የመማር እድልን ያገኛሉ።በቅዳሴ ወቅት በሰሙት መሰረት የራሳቸውን ችሎታ ተጠቅመው አዲስ ቅኔ
ይፈጥራሉ።መምህራኖቹም ቢሆኑ የሃሳብ ነጻነትን ይሰጧቸዋል፡፡ የራሳቸውን ፈጠራ ሲፈጥሩም ለረጅም ጊዜ
በተመስጦ ውስጥ ይሆናሉ።ይህን ለማድረግም ከመማሪያ ቦታቸው ራቅ ብለው ሰው ወደ ማይበዛበት ቦታ
በመሄድ ወደ ውስጣቸው ይመለከታል።አዲስ ነገር ለመፍጠርም የተለያዩ እንቅስቃሴያቸው
ያሳያሉ።ተሸፋፍነው ይተኛሉ፤ዛፍ ላይ ይወጣሉ፤ወደሰማይ ይመለከታሉ፡፡
5.4.2. ክረምት
በቆሎ ተማሪዎች ዘንድ ዋና የትምህርት ወቅት ተደርጎ የሚታወቀው የክረምት ወቅት ነው፡፡ ከዓመቱ አራት
ወቅቶች መካከል ክረምት ተማሪዎች ሃሳባቸውን ሁሉ ሰብስበው ለትምህርት እራሳቸውን የሚዘጋጁበት ጊዜ
18
,
ነው ከተማሪዎች በተገኘ መረጃ መሰረት ክረምት ለትምህር ዋና ወቅት ተደርጎ የተመረጠበት ምክንያት
ከተፈጥሮ ክስተቶች ጋር በተያያዘ ነው፡፡ በቆሎ ተማሪዎች ዘንድ የንባብ ቤትን ያለፈ ተማሪ የአስተሳብ ነጻነት
ተሰጥቶት በራሱ አዲስ ፈጠራ እየታገዘ ትምህርቱን ይቀጥላል፡፡አዲስ ነገር ለመፍጠር ደግሞ የተፈጥሮ
ክስተቶችን እንደ ግብአት ይጠቀማል፡፡ ክረምት ከሌሎች ወቅቶች በተለየ መልኩ ብዙ ነገሮች የሚከሰቱበት እና
የሚለዋወጡበት ጊዜ ነው፡፡ የነገሮች መለዋወጥና በነበሩበት አለመቆየታው ደግሞ ለዜማና ለቅኔ ተማሪዎች
የፈጠራ ልምዳቸውን ያዳብራል፡፡ በክረምት ደመና በሰማይ ላይ የሚያንዣብብበት፣ጉም ወርዶ ወርዶ
የሚረገረግበት ፣መብረቅና ነጎድጓድ ከወዲያ ወዲህ የሚሰማበት፣ወንዞች ሞልተው ከልካቸው በላይ
የሚፈሱበት፣ዝናብ ያለማቋረጥ የሚዘንብበት ጊዜ ነው፡፡ በአጠቃላይ መሬቱ በልምላሜ የሚሞላበትና ለአይን
የሚታክቱ ተፈጥሮአዊ ክስተቶች የሚቀያየሩበት ወቅት ነው፡፡ የቅኔም ሆነ የዜማ ተማሪ በዚህ ተፈጥሮአዊ
ክስተት ታግዘው አዲስ ነገር ይፈጥራሉ፡፡ የዜማ ተማሪውም ከነፋሱ ሽውታ፣ ወንዞች ሲሞሉ ከሚያሰሙት
ድምፅና እንቅስቃሴ ጋር ዜማውን ያዋህዳል፡፡ የቅኔ ተማሪም አይኑን እስከሚታክተው ድረስ ከሚመለከተው
ነገር በመነሳት አዲስ ቅኔ ይፈጥራል፡፡
በአጠቃላይየክረምት ወቅት ይዞት በሚመጣው ክስተት ምክንያት ለፈጠራ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ ስለሆነም
በዚህ ወቅት ተማሪ ከቦታ ቦታ አይንቀሳቀስም፡፡ ከጉባኤ ወጥቶ ወደ ሌላ ጉባኤ አይዞርም፤ ከዚህ ይልቅ ሙሉ
ትኩረቱን ለትምህርቱ ያደርጋል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ክረምት ለትምህርት የሚመረጥበት ሌላው ምክንያት ከላይ እንደተገለፀው በክረምት
ወንዞች ይሞላሉ፣ መንገድ ሁሉ በጭቃ ይዋጣል፣ በሠላም የተሻገሩት ወንዝ ሲመለሱ ሞልቶ ሊጠብቅ
ይችላል፡፡ እነዚህ ሁሉ ክስተቶች ከቦታ ቦታ እንዳይዟዟሩ ወይም መምህር እንዳያማርጡ ያደርጋቸዋል፡፡
ስለሆነም በዚህ ወቅት በጋ ላይ ለክረምት ብለው ያዘጋጁትን ድርቆሽ ባሉበት በመያዝ በአንድ ጉባኤ ረግተው
እንዲማሩ ያደርጋቸዋል፡፡
19
,
ከእለታት አንድ ቀን ተሜ በአቆፋዳው ተልባ ይዞ ከመንደር መንደር እየለመነና ተልባውን የምትቆላለት ምጣድ
የጣደች ሴት ይፈልጋል፡፡በመንደር እየዞረም ባለበት ጊዜም ድንገት ምጣድ የጣደችሴት ያገኛል፡፡እሜቴ እባኮትን
ይህችን ተልባ ባሰሙት ምጣዱ ያምሱልኝ ብሎ ሲጠይቅ አንድሰው ወደ ጓዳ ዘሎ ሲገባ ያያል፡፡ሴትየዋም
ወዲህ በል ብላ ሰትቆላ ተልባው እየተፈናጠረ ያስቸግራል ልትከድነው ስትሞክር ተሜ በሜዳው ላይ ያሞሌ
ጨውና ዳቦ ስላየ የሰውየው እንደሆነ ስለገመተ እሜቴ አይክደኑት የተረፈው ይበቃኛልይላታል፡፡ተልባው
አብዛኛው እየተፈናጠረ ፈስሶ አለቀ እሷም የተረፈውን በአቁፋዳህላድርግልህ ሂድትለዋለች፡፡እርሱም
መዘግየት ስለፈለገ የእመቤቴን ስም የጠራሁበትን ትቼ አልሄድም ይልና የፈሰሰውን መልቀምይጀምራል፡፡
መልቀምእንደጀመረምባል ከሄደበት ከተፍ ይላል፡፡ባልአሞሌ ጨውንና የዳቦውን ክምር ተመልክቶም የማን
እንደሆነ ይጠይቃል፡፡ሚስትም የተማሪው እንደሆነ ትነግረዋለች፡፡ተሜም ይችን አጋጣሚ ተጠቅሞ እሜቴ
የነፍስ ዋጋ ይሁንሎት ብሎ ዳቦውንና አሞሌውን ይዞ ሊሄድ ሲል ያቅተውና አይ እሜቴ ከድካሞት
አይበልጥምና ያሸክሙኝ ይላታል፡፡እርሷም በአይኗ ገላምጣ ወደ ጓዳ ትገባለች ፡፡ ባልም አሸክሚውና
ምርቃትሽን ጨርሺ ይላታል፡፡ሚስትም ካሸከመችውበኃላ ተከትላው ትወጣና እባክህን ዳቦውን ወስደህ
አሞሌ ጨውን ላው ትለዋለች፡፡ እርሱም እግዚአብሔር የሰጠኝን ላንቺ አልሰጥም ብሏት ዳቦውንና አሞሌ
ጨውንም ይዞ እብስ አለ ይባላል፡፡
20
,
አድርጎ መታጠብ ይጀምራል፡፡ሴትየዋም ትኩር ብለው ሲያዩትተሜ ቀልብ ይስባል፡፡በልና ከፍ ብለህ ተቀመጥ
ምግብም ብላ ጠጣ እያሉ ሲንከባከቡት ያመሻሉ፡፡ተሜም ስለተደረገለት ግብዣ ሁሉየነፍስ ዋጋ ያድርግልኝ
በማለት መርቆ እዛው መደብላይ ሊተኛ ሲል በልና ከዚህ ካልጋው ጠጋ ብለህ ተኛ በኔ ልታስፈርድ ነው
ይሉታል፡፡ግድ የለም እዚሁ እተኛለሁ ብሎ እምቢ ይላል፡፡ሴትየዋም ጠጋ ብለው እንደ ማባበል ሲቃጣችው
ተሜ ነገሩ ገባውና እሜቴ አይሆንም አይሆንም እንዲያውም ሞቶብኛል ደግሞም ተማሪ ነኝ
ሲላቸውሴትየዋምየዋዛ አልነበሩምና እኔስ ምን አልኩ አምጣና ቅበረው ነውያልኩት ይሉታል፡፡የሴትየዋ
ድፍረት ያስገረመው ተሜም አይ እሜቴ ቢቀበርም የሚቀበረው በሃገሩ በወገኑበደንቡ መሰረት ብሎ
አሳፈራቸው ይባላል፡፡
ህፃናት÷4 አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ÷4 አንደኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ÷4 ሁለተኛ ደረጃ እና 1 ቴክኒክናሙያ
ስለሚገኝ ነዉ፡፡
መንገድ: የሞጣ ከተማ ከቀበሌዎችም አልፎ ተርፎ የተለያዩ ከተማዎችን የሚያገናኝ መንገድ አለ፡፡ ከቀበሌ
ባለቤት በመሆኗ በከተማዋ ዉስጥ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ቢሰማሩ ትርፋማ ሊያደርጉ የሚችሉ ዘርፎች አሉ፡፡
21
,
ማድለብና ለንብ እርባታ ምቹ፤ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ለመስራት ለም መሬትና ግብዓት መኖሩ
የከተማዋን አሳድጓል፡፡
ዳቦቤት
ሰጋ ቤት
ምግብ ቤት
ቡና ቤት
የተለያዩ ባንክ
በከተማዋ ይገኛሉ፡፡
22
,
በሞጣ ከተማ በቅዱስ ጊዮርጊሰ ቤተ ክርሰቲያን ጉባየ ዘርግቶ ማስተማር አዲስ ባይሆንም ለ ዘርግቶ
አብነት ትምህርት ቤት በአንድ ላይ መስጠት መቻሉ ነው። እንዲሁም የድጓ ቤት መምህር ÷የንባብ ቤት
የምስክርነት ወረቀትን በመስጠትና በርካታ ተማሪዎችንበማስተናገድ የሚታወቅ ጉባኤ ሲሆን አሁን በቅርቡም
የኢትዮጵያ የቅኔ ዮኒቨርስቲ በመባል መስረት ተቀምጦ በመሰራት ላይ የሚገኝ ትልቅ ቦታ ነው።
5.8. መረዳዳት
እያንዳንዱ ተማሪ የራሱ የሆነ ጎጆ ቢኖረውም የሚኖሩት፤የሚመገቡትና የሚለምኑት በጋራ ነው።በቆሎ
ተማሪዎች ዘንድ ለራሱ ሳይሆን ለሌላ ቅድሚያ መስጠት እርስ በርስ መከባበር የመሳሰሉት በጉልህ
የሚንጸባረቁ ባህርያት ናቸው።ከነዚህም መካከል ለዓካል ጉዳተኛና አዲስ ለሚመጡ ተማሪዎች የሚደረጉ
ድጋፎች ይጠቀሳሉ።
ያስተላልፋል።ከተማሪ አስረዲና በተገኘ መረጃ መሰረት መምህሩ አቅማቸው ደከም የለምከሆነ የተመረጠውን
በማድረግ ለጓደኞቹ ያስተላልፋል።በዚህም መሰረት አንድ ተማሪ ሲማር ፤ዳዊት ሲደግም፤ዜማ ሲያወርድ
እውቀታቸውን ለማጠናከር ተራቸው ደርሶ እነሱም አንድ ተማሪ በትምህርት እኩል ደረጃ ላይ ያለውን
ተማሪሲመለከት እርሱም በመንፈሳዊ ቅናት ተነሳስቶ የተሻለ ሆኖ ለመገኘት ይጥራል።ወይም ደግሞ አንድ
23
,
ተማሪ በእውቀት ከሱበታች የሆኑትን አልፎት የመጣንትምህርት ሲመለከት ያለፈውን ክፍተቱን ለመሙላትና
ይሆናል።ከላይ እንደተጠቀሰው በማህበረ ቅኔ የተሻለ እውቀት ያለው ተማሪ በግዕዝ የተነገረውን በአማርኛ
በቅኔ ተቀባዩ በኩል ይጠይቃሉ።ይከራከራሉ፡፡ ቅኔ ተናጋሪውን ተማሪ ሲከራከሩት ከቆዩ በኋላ ጉባኤው በጋራ
የማበረታቻ ሃሳብ በማቅረብ ጉባኤው ይበተናል።ከዚህ በመነሳት እርስ በእርስ የመማማር ልምዳቸውን
መረዳት ይቻላል።
የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የቱንም ያህል ቢሆኑም በጉባኤ ላይ የመገኘት ግዴታ አለባቸው በዚህን ጊዜም
ቢሆን የተለየ እገዛ ይደረግላቸዋል።በጉባኤው ላይም የሚመቻቸውን ቦታ በማዘጋጀት ሲመጡ ቦታ በመልቀቅ
ይንክባከቧቸዋል።
24
,
ሌላው የቆሎ ተማሪዎች በተለያዩ ቦታዎች በሚዘዋወሩበት ጊዜ የተለያየ ገጠመኝ አላቸው፡፡ ይህንን
ገጠመኛቸውን እንዴት እንደሚገልጹ በዚህ ጥናት ታይቷል፡፡
25
,
አባሪዎች
አባሪ አንድ
አንድ ተማሪ ቅኔ ለመቁጠር ሁልጊዜ የሚሄድበት ዘወር ያለ ስፍራ ነበር፡፡ነገር ግን ውሃ ለመጠጣት ወይም ሽንት
ቤት ለመጠቀም ሲነሳ አንዲት ጦጣ ወረቀቱን እየቀደደች እሱ ሲያደርግ የተመለከተቸውን ሁሉ ለማድረግ
እያለች ትረብሸው ነበር፡፡ ይህንን የተመለከተው ተማሪ አንድ ቀን ቢላዋ ይዞ ይመጣል ቁጭ ብሎ ይቆይና ውሃ
ለመጠጣት ዕቃውን አስቀምጦ ሲሄድ ቢላዋውን ያነሳና በደንደሱ በኩል አንገቱን የሚቆርጥ መስሎ ይገዘግዛል፡
26
,
፤ይህንን ስትመለከት የቆየች ጦጣም ቢላዋውን ታነሳና በስለቱ በኩል የገዛ አንገቷን ቆርጣ እዛው ላይ ሞታ
አገኛት” ተማሪ ጦጣንም በለጠ ተብሎ ይወራል፡፡
አባሪ ሁለት
አንድ የንስሃ አባቱን ሚስት እሁድ እሁድ እየጠበቀ የለመደ ተማሪ ነበር፡፡የንስሀ አባቱም እሁድ እሁድ
ከቤተክርስቲያን ቀርተው አያውቁም ተሜም እሁድን እየጠበቀ የልቡን ያደርሳል፡፡አንድ ቀን ሰውው ከመንገድ
የህመም ስሜት ተሰምቷቸው ይመለሳሉ፡፡እነተሜም ሳያስቡት ሲደረስባቸው ደንግጠው ተማሪው ከአልጋ ስር
ይገባል፡፡ባልና ሚስትም ገንፎ አገንፍተው ሲበሉ ሚስት ለአዋዩ እያለች ወደ አልጋ ስር ትወረውራለች በዚህ
ጊዜ የወረወረችው ትኩስ ገንፎ በተማሪው መቀመጫ ላይ ይለጠፋል ትኩስ ገንፎ ያቃጠለው ተማሪም
አልጋውን ከነሰውየው ገልብጦ ወጥቶ ይሮጣል ሚስትም በስመ አብ በሉ መምሩ ሰይጣን እኮ ነው አለች
ይባላል፡፡
አባሪ ሶስት
ከዕለታት አንድ ቀን የቆሎ ተማሪ የእግዜር እንግዳ ብሎ ወደ አንድ መንደር ጎራ ይላል እነሱም ቤት
የእግዚአብሔር ነው ግባ ብለው ይቀበሉታል፡፡ ነገር ግን እራታቸውን ዶሮ ወጥ ሰርተው ነበርና ተሜ እንዳይበላ
ሰስተው ሽሮ ይሰጡትና እነሱም ቀማምሰው ይተኛሉ፡፡ተሜም ሽሮውን ይበላና ይተኛል፡፡ሰዎቹም አንድ ቀበኛ
ጥጃ ስላለች ልብስህን እንዳትበላብህ ብለው ደህና ልምጭ ይሰጡትና በዚህ በላት ይሉታል፡፡ ተሜም የዶሮ
ወጡ ሽታ እንቅልፍ ሲያሳጣው ከተኙ በኋላ ቀስ ብሎ ተነስቶ ጥስቅ አርጎ ይበላና ተመልሶ ይተኛል፡፡
ባለቤቶቹም ተሜ ተኝቷል ብለው ሲነሱ ድስቱ ባዶውን ቀርቷል በዚህ ጊዜ ሴትዮዋ ቆይ ተሜ በልቶት ይሆናል
ብላ አፉን ልታሸት ጎንበስ ስትል ጌታው ኧረ ያሏት ጥጃ መጣች በማለት ሴትዮዋን በያዘው ልምጭ ለምጦ
መለሳት ይባላል፡፡
አባሪ አራት
ከዕለታት አንድ ቀን ተሜ ለልመና ይሄድና አንድ ቤት ሲደርስ በእንተ ስማ ለማርያም ይላል፡፤በዚህን ጊዜ የቤቱ
ባለቤት ትወጣና እቤት ውስጥ ምንም ነገር የለም ቁጭ ብዬ ብቻ ነው ያለው ቁጭ ብዬ ልስጥህ ትለዋለች ቁጭ
ብዬ የእህል አይነት ነው፡፡ ተሜም እመቤቴ ካሉስ ተኝተው ቢሰጡኝ ይሻላል አለ ይባላል፡፡
አባሪ አምስት
አንድ የቆሎ ተማሪ ለልመና ይወጣል ከአንድ ቤት ደረሰም በእንተ ስማ ለማርያም ብሎ ሲለምን የቤቱ ባለቤት
እንጀራ በአኩፊዳው እየከተተች ሀገርህ ወዴት ነው ስትለው እሱም ከእነማይ ይላታል፡፡ እሷም ከሰማይ ብላ
ትጠይቀዋለች ተሜም ምን ለማለት እነደፈለገች ለማወቅ ፈልጎ ነገሩን ገልበጥ አድርጎ አዎ ይላታል፡፡እሷም
እናትና አባቷ ሞተው ስለነበር ተሜ አባቴን አግኝተሀቸዋል ብላ ትጠይቀዋለች እሱም ደህና ናቸው
የሚለብሱት አልቆባቸዋል ይላታል፡፤እሷም በጣም እያዘነች የባሏን ልብሽ ለአባቷ የእሷን ልብስ ለእናቷ
በጨርቅ ቋጥራ ሰጠችው፡፡ ተሜ ይህን ተሸክሞ እብስ ይላል፡፡ ከቆይታ በኋላ ባሏ ከስራ ይመጣና ልብስ ሲቀይር
27
,
ሲሞከረው ልብሶቹ የሉም፡፡ የት ሄደ ልብሱ ብሎ ሲጠማቀት ሁሉንም ትነግረዋለች፡፡ ባልም በሁኔታው ተናዶ
የቆሎውን ጭኑ እየጋለበ ተማሪውን ፍለጋ ይሄዳል፡፡ ትንሽ ሄድ እንዳለም ተማሪውን ያገኘዋል፡፡ ተማሪም ከሩቅ
አይቶት ኖሮ ከረጢቱን ወደ አጥር ስር መወረወርና መንገዱን ይቀጥላል፡፡ ሰውየውም አሁን በዚጅ በኩል አንድ
ተማሪ ሲያልፍ አየህ ብሎ ይጠይቀዋል፡፡ ተማሪውም አዎን ጌታዬ አሁን እየሮጠ አለፈ ነገር ግን ቁልቁለት
ስለሆነ በቅሎዎ እሺ አትለውትም ይላል፡፡ ሰውየውም እባክህ ጠብቅልኝ ብሎት በእግር መሮጥ ጀመረ፡፡
ተማሪው እሽ ብሎ በቅሎዋን ይቀበልና ስምህ ማነው ሲባል የአሁኑ ይባስ ብሎት በበቅሎው እየጋለበ ሄደ
ይባላል፡፡
መረጃ አቀባዮች
28
,
በላቸዉ ቤተ ክርስቲያን
ዋቢ ጽሁፎች
ሀብተ ማርያም ወርቅነህ፡፡ (1963)፡፡ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ትምህርት፡፡ አዲስ አበባ ፣
ኪዳነ ማርያም ጌታሁን፡፡(1980)፡፡ጥንታዊ የቆሎ ተማሪ፡፡አዲስ አበባ ፣ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፡፡
29
,
Almayhu Moges.(1971) .“ the traditional church education”. Addis Ababa. Hile Selassie
University.
Ben Amas Dan. “ To words a definition of fulklurs in context”. Journal of American folklore.
Finnegan, Ruth. (1972). Oral tradition and the verbal arts a guide to research practices.
London, Rutledge.
30
,
1. የቆሎ ተማሪ በብዛት አካባቢው ለቆ በሌላ የሚማርበት ምክንያት ምንድን ነው፡፡ በአካባቢያችሁ
ሆናችሁ ብትማሩ ምን ችግር አለው?
2. ስማችሁን የምትቀይሩበት ምክንያት ምንድነው?
3. በምትማሩበት ወቅት ትለምናላችሁ ባትለምኑስ ሳትለምኑ መማር አትችሉም?
4. እርስ በርሳችሁ በምን በምን ነገሮች ትረዳዳላችሁ?
5. አካል ጉዳተኛ ተማሪ በመካከላችሁ ቢኖር ምን አይነት ድጋፍና እንክብካቤ ታደርጉለታላችሁ?
6. በትምህርት ቤት ቆይታችሁ ለየ የትምህርት ወቅት አለ ካለስ የተመጣበት የራሱ የሆነ ምክንያት
ይኖረው ይሁን?
7. አዲስ ለሚመጣ ተማሪ የሚደረግ አቀባበል በምን ምልኩ ነው?
31