Professional Documents
Culture Documents
123
123
የአፈጻጸም መመሪያ
ሰኔ 2013 ዓ.ም
መክሥተ ዘአርእስ
መቅድም................................................................................................................................................I
መግቢያ................................................................................................................................................II
2. የክፍሉ ዓላማ....................................................................................................................................2
3. ስያሜ............................................................................................................................................3
4. መበይነ ቃላት....................................................................................................................................4
5. ተጠሪነት.........................................................................................................................................5
6. አባልነት.........................................................................................................................................6
11.1. ስብሰባ.................................................................................................................................11
11.1.1. የአጠቃላይ የክፍሉ አባላት ስብሰባ.............................................................................................11
11.1.2. የክፍሉ ሥራ አሥፈጻሚ ስብሰባ................................................................................................11
11.1.3. የንዑስ ክፍላት ስብሰባ..........................................................................................................12
11.2. ምርጫ.................................................................................................................................12
11.2.1. በምርጫ ላይ የክፍሉ ጽሕፈት ቤት ተግባርና ኃላፊነት..........................................................................12
11.2.2. የምርጫ ሥነ ሥርዓት..........................................................................................................13
12. የክፍሉ መዋቅር፣ ተግባርና ኃላፊነት........................................................................................................14
እናታችን የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሕገ ልቦና፣ በሕገ ኦሪትና ሕገ ወንጌል ጸንታ
ለኖረችው ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ አለት የጸናች የእምነት ተቋም፣ የጥበብ መገኛ፣ የሕግ መፍለቂያና
የማኅበራዊ ኑሮ መሠረት ሆና በሕዝቡና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ግንኙነት ስትመራ የኖረች ስንዱ
እመቤት መሆኗን የታሪክ ሊቃውንት ዘግበውት የሚገኝ የተገለጠ እውነት ነው፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ትምህርቱ ለቅዱስ ጴጥሮስ በጎቼን፣ ጠቦቶቼንና
ግልገሎቼን ጠብቅ ባለው ቃል መሠረት በጎች ለተባሉ ምዕመናን ሰበካ ጉባኤን፣ ጠቦቶችና ግልገሎች ለተባሉ
ሕፃናትና ወጣቶች ደግሞ ሰንበት ትምህርት ቤትን መሥርተው መንፈሳዊ አገልግሎት ሳይታጎል እንዲቀጥል
አድርገዋል፡፡ የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤትም የዚህ
መንፈሳዊ ዛፍ አንድ ፍሬ ነው፡፡
መግቢያ
i
674834749.docx
“ናሁ ሰናይ ወናሁ አዳም ሶበ ይሄልዎ አኃው ኅቡረ” “እነሆ ወንድሞች በአንድነት ቢቀመጡ መልካም
ነው እጅግም ያማረ ነው” እንዲል የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን
ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል። ቲቶ
፪፥፪-፫
ለፍቅርና ለመልካም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በእርሳችን እንተያይ በአንዳንዶችም ዘንድ እንደሆነው
መሰባሰባችንን አንተው እርስ በእርሳችንም እንመካከር እንጂ ይልቁንም ቀኑ ሲቃረብ እያያችሁ አብልጣችሁ
ይህን አድርጉ፡፡ ዕብ ፲፥፳፬-፳፭
የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት በ፲፱፻፶፱
ዓ.ም ለመንፈሳዊ አገልግሎት ይፋጠኑ በነበሩ አባቶች የተመሠረተ ሲሆን ባለፉት ፶፪ ዓመታት ለመንፈሳዊ
አገልግሎት የሚተጉ በሺዎች የሚቆጠሩ የቤተክርስቲያን ልጆችን ሲያፈራ ቆይቷል።
ይህ የአፈጻጸም መመሪያ በ፪፼፲ ዓ.ም የጸደቀውን የሰንበት ትምህርት ቤቱን መተዳደሪያ ደንብ
መሠረት አድርጎ ሕይወት ተኮር አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችል ተደርጎ ለመረጃና መዛግብት ክፍል
የተዘጋጀ ነው፡፡
ደንቡ ሁለት ዓበይት ክፍሎች ያሉት ሲሆን የመጀመሪያው ዐቢይ ክፍል ስለ ጠቅላላ ደንቡ ያትታል ፣
ሁለተኛው ዐቢይ ክፍል ደግሞ በመረጃና መዛግብት ክፍል ውስጥ ስለሚኖሩት ዐበይት የአገልግሎት ክፍሎች
አወቃቀር፣ ተግባርና ኃላፊነት እንዲሁም በክፍሉ ውስጥ የሚገኙ አባላት መብትና ግዴታ ወዘተ የሚያብራራ
ነው፡፡
ii
674834749.docx
1. የሰንበት ትምህርት ቤቱ ርዕይ
ቅዱሳን አባቶች ጠብቀው ያስረከቡንን የቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖናና ትውፊት አክብሮና አስከብሮ
ተስፋ የምናደርገውን መንግሥተ ሰማያት ለመውረስ የሚያበቃ የጸና ሃይማኖትና ምሳሌ የሆነ ምግባር ይዞ
የሚገኝ ጥበበኛ ትውልድን የሚያፈራ ሰንበት ትምህርት ቤት ተፈጥሮ ማየት።
2. የክፍሉ ዓላማ
1
674834749.docx
የቤተክርስቲያንንና የሰንበት ትምህርት ቤቱን የመረጃ ሀብቶች እያሰባሰበ፤ እያደራጀና እየተንከባከበ የመጠበቅ፤
ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ለማገናዘቢያ አገልግሎት ማቅረብ
3. ስያሜ
ክፍሉ የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት
መረጃና መዛግብት ክፍል ተብሎ ይጠራል፡፡
2
674834749.docx
4. መበይነ ቃላት
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ የአፈጻጸም መመሪያ ውስጥ፡-
ሀ. “ቤተ-ክርስቲያን” ማለት የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ነው።
3
674834749.docx
ለ. “ሰንበት ትምህርት ቤት” ማለት የደብረ ብሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን
ሰንበት ትምህርት ቤት ነው።
ሐ. “መረጃና መዛግብት ክፍል” ማለት የአንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት መረጃና መዛግብት
ክፍል ነው።
ረ. “የሥራ አስፈጻሚ” ማለት ክፍሉን በበላይነት የሚመሩ የመረጃና መዛግብት ክፍል የጽሕፈት ቤት
አባላትና የንዑስ ክፍላት ተጠሪዎችን ነው።
ሰ. “የክፍሉ ጽሕፈት ቤት” ማለት የክፍሉን ሰብሳቢ፣ ምክትል ሰብሳቢ፣ ጸሐፊና ምክትል ጸሐፊን
የያዘ የመረጃና መዛግብት ክፍል ጽሕፈት ቤት ነው።
ሸ. “የሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽሕፈት ቤት” ማለት የአንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት ሰብሳቢ፣
ምክትል ሰብሳቢ፣ ጸሐፊና ምክትል ጽሐፊ ማለት ነው።
በ. “የክፍሉ ጠቅላላ ጉባኤ” ማለት የመረጃና መዛግብት ክፍል ጠቅላላ አባላት ጉባኤ ማለት ነው።
ተ. “የሥራ አመራር” ማለት የአንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት የሥራ አመራር ማለት ነው።
5. ተጠሪነት
4
674834749.docx
6. አባልነት
5
674834749.docx
ሐ. ዕድሜው ከ 16 ዓመት በላይ የሆነ እና ሰንበት ትምህርት ቤቱ የሚሰጠውን ተከታታይ መሠረታዊ
የሃይማኖት ትምህርት ተከታትሎ ከሕፃናት ክፍል የተዘዋወረ፤
መ. ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ሰንበት ትምህርት ቤቶች በበቂ ምክንያት ተዘዋውሮ የመጣ፣ ከነበረበት
ሰንበት ትምህርት ቤት መደበኛ አባል ስለመሆኑና ስለነበረው መልካም ቆይታ የሚገልጽ ከተጻፈ ፫
ወራት ያላለፈው ማስረጃ ያቀረበ፣ የተሰጠውን የአመክሮ ጊዜ በአግባቡ ያጠናቀቀ፤
ሠ. ቀደም ሲል በሰንበት ት/ቤቱ በመደበኛ አባልነት ከ 1 ዓመት በላይ የሆነ የአገልግሎት ቆይታ ኖሯቸው በቂ
በሆነ ምክንያት መደበኛ አባልነታቸው ተቋርጦ የነበረ አባላት ከነበሩበት ተመልሰው በአገልግሎት
ለመሳተፍ ሲፈልጉ ጥያቄቸውን ለሥነ-ምግባር ክፍል አቅርበው ተቀባይነት ካገኘበት ቀን ጀምሮ
እንደ መደበኛ የክፍሉ አባል ይቆጠራሉ።
ሀ. በሰንበት ትምህርት ቤቱ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት መደበኛ አባል የሆነና አባልነቱ ያልተቋረጠ
ለ. ዕድሜው 23 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆነ፤
ሐ. የሥራ አሥፈጻሚ ምርጫ ከመደረጉ በፊት ቢያንስ ለ፪ ዓመት በቅርበትና በትጋት በክፍሉ ያገለገለ፤
መ. በመንፈሳዊ ዕውቀት የበሰለ እና በአመራር እና በውሳኔ ሰጪነት በቂ ክሕሎት ያለው
ሠ. በንስሐ የሚመላለስና በሥነ-ምግባሩ አርዓያ መሆን የሚችል፤
ረ∙ በሰንበት ትምህርት ቤቱ ውስጥ በመደበኛ አባልነት ሦስት ዓመትና ከዚያ በላይ ቆይታ ያለው፡፡
ሰ. የክፍሉን ሥራዎች ለማከናወን በቂ ጊዜ ኖሮት ኃላፊነቱን በትጋትና በብቃት ለመወጣት የሚችል፤
ሸ. በአስኳላ ትምህርት ጥሩ የትምህርት ዝግጅት ያለው።
6
674834749.docx
8. የአባልነት መብት እና ግዴታ
7
674834749.docx
ሠ. በክፍሉ የሚጠየቁ መረጃዎችን የመስጠትና የመተባበር፤
ረ. የክፍሉን ንብረቶች የመጠበቅና የማስጠበቅ፤
ሰ. ከቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖናና ትውፊት ጋር ተቃራኒ በሆኑ ድርጊቶች ተሳታፊ አለመሆን፤
ሸ. የቤተክርስቲያኒቱን ዶግማ፤ቀኖና እና ትውፊት የመጠበቅና በእነርሱም የመመራት፤
ቀ. ያለክፍሉ ፈቃድና እውቅና በክፍሉ ስም ማናቸውንም ተግባራት ያለመፈፀም፡፡
8
674834749.docx
10. በድጋሚ አባል ስለመሆን
9
674834749.docx
11. የስብሰባና የምርጫ ሥነ-ሥርዓት
11.1. ስብሰባ
11.1.1. የአጠቃላይ የክፍሉ አባላት ስብሰባ
ሀ∙ አጠቃላይ የክፍሉ መደበኛ ስብሰባ በወር አንድ ጊዜ ይሆናል፡፡
ለ. አስቸኳይ ወይም አጠቃላይ የክፍሉ ውሳኔና እውቅና የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሲያጋጥሙ
በክፍሉ ሥራ አሥፈጻሚ ወይም ከጠቅላላው መደበኛ የክፍሉ አባላት በ 1/3 ኛው ጥያቄ አቅራቢነት
ከእነዚህ በአንዳቸው የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል።
ሐ. የጉባኤው ውሳኔዎች የሚተላለፉት በስምምነት ሲሆን በዚህ መልኩ ውሳኔውን ማስተላለፍ
ካልተቻለ በአብላጫ ድምጽ ውሳኔው እንዲተላለፍ ይደረጋል። እኩል ድምጽ ሲኖር ሰብሳቢው
የደገፈው ሀሳብ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
መ. በአጠቃላይ የክፍሉ አባላት ከመደበኛ አባላቱ ሃምሳ በመቶ /50%/ በላይ ሲገኙ ምልዐተ ጉባኤ
ይሆናል፣ ይህ ሳይሟላ ከቀረ በአሥራ አምስት ቀናት ውስጥ ሁለተኛ ጥሪ ተደርጎ በአግባቡ
ለአባላት መድረሱ ሲረጋገጥ ለስብሰባው በተያዘው አጀንዳ ላይ ብቻ በዕለቱ በተገኙ አባላት ውሳኔ
እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡
ሠ. ስብሰባው የዕለቱ ስንክሳር፣ የሥራ አፈጻጸም ዘገባ፣ የሕይወት ውይይትና በጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔ
የሚፈልጉ አጀንዳዎች ይነሱበታል።
ረ. ስብሰባው ከ 2:00 ያልበለጠ ጊዜ የሚወስድ ይሆናል።
11.1.2. የክፍሉ ሥራ አሥፈጻሚ ስብሰባ
ሀ. የክፍሉ ሥራ አሥፈጻሚ መደበኛ ስብሰባ የሥራ አስፈጻሚው አባላት በጋራ በሚወስኑት መርሐ-
ግብር መሠረት የሚመራ ይሆናል፡፡
ለ. አስቸኳይ ጉዳይ ሲያጋጥም የክፍሉ ጽሕፈት ቤት የስብሰባ ጥሪ ሊያቀርብ ይችላል፡፡
ሐ. የክፍሉ ሥራ አሥፈጻሚ መደበኛ ስብሰባ ቢያንስ በወር ሁለት ጊዜ ይደረጋል፡፡
መ. የክፍሉ ሥራ አሥፈጻሚ መደበኛ ስብሰባ በክፍሉ ቢሮ ይደረጋል፡፡
ሠ. ከሥራ አሥፈጻሚ አባላቱ ከሃምሳ በመቶ (50%) በላይ የተገኙ እንደሆነ ምልዐተ ጉባኤ ይሆናል፡፡
10
674834749.docx
ረ. የስብሰባው ውሳኔዎች የሚተላለፉት በስምምነት ሲሆን በዚህ መልኩ ውሳኔውን ማስተላለፍ
ካልተቻለ በአብላጫ ድምጽ ውሳኔው እንዲተላለፍ ይደረጋል። እኩል ድምጽ ሲኖር ሰብሳቢው
የደገፈው ሀሳብ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
ሠ. ስብሰባው የዕለቱ ስንክሳር፣ የሥራ አፈጻጸም ዘገባና ጽሕፈት ቤቱ ይዟቸው የሚመጡ አጀንዳዎች
ይኖረዋል ።
ረ. ስብሰባው ከ 1:30 ያልበለጠ ጊዜ የሚወስድ ይሆናል።
11.1.3. የንዑስ ክፍላት ስብሰባ
ሀ. የንዑስ ክፍሉ መደበኛ ስብሰባ የንዑስ ክፍሉ አባላት በጋራ በሚወስኑት መርሐ-ግብር መሠረት
የሚመራ ይሆናል፡፡
ለ. አስቸኳይ ጉዳይ ሲያጋጥም የንዑስ ክፍሉ ተጠሪ የስብሰባ ጥሪ ሊያቀርብ ይችላል፡፡
ሐ. የንዑስ ክፍሉ መደበኛ ስብሰባ ቢያንስ በወር ሁለት ጊዜ ይደረጋል፡፡
መ. የንዑስ ክፍሉ መደበኛ ስብሰባ በክፍሉ ቢሮ ይደረጋል፡፡
ሠ. ከንዑስ ክፍሉ አባላት ከሃምሳ በመቶ (50%) በላይ የተገኙ እንደሆነ ምልዐተ ጉባኤ ይሆናል፡፡
ረ. የስብሰባው ውሳኔዎች የሚተላለፉት በስምምነት ሲሆን በዚህ መልኩ ውሳኔውን ማስተላለፍ
ካልተቻለ በአብላጫ ድምጽ ውሳኔው እንዲተላለፍ ይደረጋል። እኩል ድምጽ ሲኖር ሰብሳቢው
የደገፈው ሀሳብ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
11.2. ምርጫ
የክፍሉ የሥራ አስፈጻሚ (የንዑስ ክፍል ኃላፊዎች) ምርጫ አጠቃላይ በክፍሉ አባላት ጠቅላላ ጉባኤ
የሚደረግ ሲሆን ምርጫውን በበላይነት የሚመራው የክፍሉ ጽሕፈት ቤት ይሆናል።
ሠ. ስለ ምርጫ ሂደቱ አጠቃላይ ዘገባ ለክፍሉ ጠቅላላ ጉባኤና ለሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽሕፈት ቤት ያቀርባል፤
11
674834749.docx
ረ. የክፍሉ ጽሕፈት ቤት ከአባላቱ የሚቀርቡ እጩዎችን መርጦ ለምርጫ ለማቅረብ አመቺና አስፈላጊ
መንገዶችን ሊጠቀም ይችላል፤
ሰ. በምርጫ ሒደቱና ሥርዓቱ ላይ በክፍሉ ጠቅላላ ጉባኤ ሃምሳ (50%) በላይ ድምጽ ተቃውሞ የቀረበ
እንደኾነ የሥራ አሥፈጻሚ ድጋሚ ምርጫ ተካሒዶ ውጤቱ እስኪታወቅ ድረስ ሥራውን ነባሩ ሥራ
አሥፈጻሚ እያከናወነ ይቆያል።
ለ. በሥራ አስፈጻሚነት የመምረጥም ኾነ የመመረጥ መብት ያለው የሰንበት ትምህርት ቤቱ መደበኛ አባልና
የመረጃና መዛግብት ክፍል አባል ብቻ ነው፤
ሐ. መራጮች ድምጽ መስጠት የሚችሉት የምርጫ አስፈጻሚው በዕለቱ ሊያስመርጥ በተዘጋጀው ቁጥር ልክ
ብቻ ነው፤
መ. በምርጫው የቀረቡ እጩዎች ባገኙት ድምጽ ልክ እንደ ቅደም ተከተላቸው ተመዝግበው እንዲይዙ
ያደርጋል።
12
674834749.docx
12. የክፍሉ መዋቅር፣ ተግባርና ኃላፊነት
13
674834749.docx
ቀ. የሰንበት ትምህርት ቤቱን ድኅረ-ገጽ ያዘጋጃል፤ ያስተዳድራል፤ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ
የአገልግሎት ክፍሎች ሰለመረጃና መዛግብት ሥራዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና እንዲያገኙ
ሁኔታዎችን ያመቻቻል።
በ. በመረጃና መዛግብት ዙሪያ ከአገልግሎት ክፍላት ጋር በመተባበር ይሠራል።
ተ. የሥራ አፈጻጸም ዘገባ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ ሥራ አመራር ያቀርባል።
ቸ. በሥሩ ያሉትን ንብረቶች ይጠብቃል፤ ደኅንነታቸውን ይከታተላል።
ኀ. ጥናት በሚያስፈልጋቸው የክፍሉ ሥራዎች ላይ ጥናት ያደርጋል።
ነ. ለአርትኦት ክፍል ተለይተው ከተሰጡት የአርትኦት ሥራዎች በስተቀር ማንኛውንም ወደ ክፍሉ
የሚገቡ ከክፍሉም የሚወጡ ጽሑፎች ወደ አንባብያን ከመድረሳቸው በፊት የመጀመሪያ ደረጃ
የአርትኦት ሥራ ይሠራል።
12.1.2. አጠቃላይ የክፍሉ አባላት ተግባርና ኃላፊነት
ሀ. የክፍሉን አጠቃላይ አባላት በሚመለከቱ አገልግሎቶች ላይ መሳተፍ፤
ለ. ከክፍላት የአገልጋይ ጥያቄ ሲመጣ በአገልግሎቱ ላይ ተሳታፊ መኾን፤
ሐ. ክፍሉን ማጽዳት ማስተካከል፤
መ. ከክፍሉ አገልጋዮች ጋር በስምምነትና በመግባባት ማገልገል፤
ሠ. ዕቅዶችን በጊዜአቸው ተፈጻሚ እንዲሆኑ ማድረግ፤ የማይፈጸሙበት ሁኔታ ሲፈጠር
ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ መፍትሔ መፈለግ፤
12.1.3. የክፍሉ ጽሕፈት ቤት ተግባርና ኃላፊነት
ሀ. የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ማዘጋጀት፤ መምራት፤
ለ. ክፍሉን በበላይነት መምራትና መከታተል፤
ሐ. የክፍሉ አባላት መንፈሳዊና ማኅበራዊ ሕይወታቸውን መከታተል፤ እገዛ ማድረግ፤
መ. አባላቱ በኃዘን፣ በደስታ እንዲተሳሰቡ ማድረግ፤
ሠ. ለክፍሉ አባላት የውይይትና የሥልጠና መርሐ-ግብሮችን ማዘጋጀት፤
ረ. የክፍሉን ንብረት በበላይነት መዝግቦ ይይዛል፤
ሰ. ከሌሎች ክፍላት ጋር የግንኙነት ሥራዎችን ይሠራል፤
12.1.4. የንዑስ ክፍል ኃላፊ ተግባርና ኃላፊነት
ሀ. የንዑስ ክፍሉን መሪ ዕቅድ ያዘጋጃል፣ ለክፍሉ ጽ/ቤት ያጸድቃል ይተገብራል ተፈጻሚነቱን ሪፖርት
ያደርጋል፡፡
ለ. የንዑስ ክፍሉን ስብሰባ በወር ሁለት ጊዜ ያዘጋጃል፤ ይመራል።
ሐ. አባላቱ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲበረቱ ያነቃቃል፤ ይከታተላል፤ ይደግፋል፤ ከአገልግሎት
እንዳይርቁ ይንከባከባል፤
14
674834749.docx
መ. ከክፍሉ ጽሕፈት ቤት የሚሠጠውን ሌሎች ተግባራትን ያከናውናል።
ሠ. የአባላትን የአገልግሎት ሂደት ይከታተላል፤ እገዛ ያደርጋል።
12.1.5. የዘርፍ ተጠሪ ተግባርና ኃላፊነት
ሀ. ከዘርፍ አገልጋዮች ጋር በመኾን ዕቅድ ያዘጋጃል፤ ያጸድቃል፤ ይተገብራል፤
ለ. የዘርፉን ስብሰባ ቀን ከዘርፉ አባላት ጋር በመወሰን አባላቱን ይሰበስባል፤
ሐ. አባላቱ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲበረቱ ያነቃቃል፤
መ. የዘርፍ አባላትን መነፈሳዊ ሕይወት ይከታተላል፤ ይደግፋል፤ ከአገልግሎት እንዳይርቁ ይንከባከባል፤
ሠ. ከንዑስ ክፍል ኃላፊና ከክፍሉ ጽሕፈት ቤት አባላት የሚሠጠውን ሌሎች ተግባራትን ያከናውናል።
12.1.6. የክፍሉ አባል ተግባርና ኃላፊነት
ሀ. ከእርሱ በላይ ካሉት ኃላፊዎች የሚሠጠውን ተግባር በጊዜው ያከናውናል፤
15
674834749.docx
13.1.2. ተጠሪነት
ለደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት ጽሕፈት
ቤት
13.1.3. መዋቅር
ጽሕፈት ቤት
ምክትል ምክትል
ዋና ሰብሳቢ ዋና ጸሐፊ
ሰብሳቢ ጸሐፊ
13.1.4. የመረጃና መዛግብት ክፍል ጽሕፈት ቤት ተግባርና ኃላፊነት
ሀ. የክፍሉን መሪ ዕቅድ ያዘጋጃል፣ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ የሥራ አመራር ያጸድቃል፤ይተገብራል
ተፈጻሚነቱን ሪፖርት ያደርጋል፡፡
ለ. ንዑስ ክፍላት በዕቅዳቸው መሠረት እየሠሩ መኾናቸውን ይከታተላል፤ ያማክራል፤ ድጋፍ ይሰጣል።
ሐ. ገቢና ወጪ ደብዳቤዎችን ይከታተላል፤ ያስፈጽማል።
መ. ለክፍሉ የሚያስፈልጉትን ግብዓቶች ያሟላል።
ሠ. የክፍሉ አባላትን ሕይወት ይከታተላል።
ረ. ከሰንበት ትምህርት ቤቶችም ኾነ ከክፍሉ ጽሕፈት ቤት የሚመጡትን መረጃዎች ለአባላት በተገቢው ሁኔታ
ያደርሳል።
ሰ. ወደ ክፍሉ ለሚገቡ አባላት ሰለ ክፍሉ አሠራር ገለጻ ያደርጋል።
13.1.5. የዋና ሰብሳቢ ተግባርና ኃላፊነት
ሀ. የንዑስ ክፍላትን ኃላፊዎችና ጸሐፊዎች ከክፍሉ አባላት ጋር በመሆን ይመርጣል፣ በክፍሉ ሥራ አመራር
ያጸድቃል፤
ለ. ከንዑስ ክፍል ኃላፊዎችና ጸሐፊዎች ጋር በመሆን ክፍሎችን በበላይነት ይመራል፣
ሐ. ከሥራ አመራር ለክፍሎች የሚወርዱ መመሪያዎችን፣ ውሳኔዎችን፣ መረጃዎችን ለዋና ክፍሉ አባላት
ያሳውቃል፤
መ. የክፍሉን እንቅስቃሴ በተመለከተም ለሥራ አመራሩና ለኦዲትና ኢንስፔክሽን ክፍል ወቅታዊ ሪፖርት
ያቀርባል፤
ሠ. በሥራ አመራሩ የጸደቁ ዕቅዶችን፣ የሚሰጡ መመሪያዎችን ያስተገብራል፤
ረ. በክፍላቱ የሚቀርቡ የወጪና የንብረት ጥያቄ ማቅረቢያ ሰነዶች ላይ ይፈርማል፤
16
674834749.docx
ሰ. የክፍሉን አባላት መንከባከብ፤ በክፍል ውስጥ በሚነሱ ቅሬታዎች ላይ መፍትሔ መስጠት ይህ ሳይሆን ቢቀር
ለሥራ አመራር እንዲሁም ለሥነ-ምግባር ክትትል፣ ምክርና ተግሳጽ ክፍል ጉዳዩን በግልባጭ ያሳዉቃል፤
ሸ. በሥሩ ያሉ ንዑሳን ክፍሎችን ይመራል፡፡
ቀ. የንዑሳን ክፍሎች ኃላፊዎችን ከክፍሉ አባላት ያስመርጣል ለሥራ አመራሩ ተጠሪ አቅርቦ ያስጸድቃል፡፡
በ. የንዑሳን ክፍሎችን የአገልግሎትና የበጀት ዕቅድ በመመርመር ለሥራ አመራሩ ያቀርባል ሲጸድቅም ተግባር
ላይ ያውላል ፡፡
ተ. የንዑሳን ክፍሎችን የአገልግሎት አፈጻጸምና የበጀት እንቅስቃሴ ይገመግማል አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ መመሪያ
ይሰጣል ፡፡
ቸ. የአገልጋዮችን ምደባና ዝውውር በተመለከተ ከሥነ-ምግባር ክፍል ጋር በመሆን በትብብር ይሠራል፡፡
ኀ. የአገልግሎት አፈጻጸም ሪፖርት በየሩብ ዓመቱና እንደ አስፈላጊነቱ የኦዲትና ኤንስፔክሽን ክፍሉ ጥያቄ
ባቀረበ ጊዜ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽሕፈት ቤት በጽሑፍ ያቀርባሉ፡፡
ነ. የክፍሉን መደበኛ የሥራ አመራር ስብሰባ በየ 15 ቀኑ ያደርጋል፤ ለአባላት ጥሪ ያስተላልፋል፤ ስብሰባውን
ይመራል።
ኘ. ከሰንበት ትምህርት ቤቱ ሥራ አመራር የሚሰጠውን ሌሎች ተግባራት ያከናውናል
ሐ. ንዑሳን ክፍሎች ዓመታዊ ዕቅድና በየሦስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እንዲያዘጋጁ ያሳስባል፣
የተዘጋጁትንም አጠናቅሮ ለክፍሉ ዋና ሰብሳቢ ያቀርባል፣
መ. ከሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽሕፈት ቤት የተሰጠውን የክፍሉን ዕቅድ ለንዑስ ክፍላት ኃላፊዎች አባዝቶ
ይሰጣል፣
ሠ. ከክፍሉ ሰብሳቢ የሚሰጠውን ሌሎች ተግባራት ያከናውናል፡፡
13.1.8. የምክትል ጸሐፊ ተግባር እና ኃላፊነት
ሀ. ዋና ጸሐፊው በሌለበት ዋና ጸሐፊውን ተክቶ ይሠራል
17
674834749.docx
ለ. ዋና ጸሐፊውን በሚያስፈልገው ሁሉ ያግዛል፣
ሐ. በክፍሉ ጽሕፈት ቤት የሚሰጠውን ሌሎች ተጨማሪ ተግባራትን ያከናውናል፡፡
13.2.2. ተጠሪነት
ለመረጃና መዛግብት ክፍል ጽሕፈት ቤት ነው።
13.2.3. መዋቅር
18
674834749.docx
ለ. ድኅረ-ገጽ ማልማት፣ መረጃዎችን ማስፈር፣ ወቅታዊነታቸውን መከታተል፣ ደኅንነታቸውን መጠበቅና መከታተል።
ሐ. ሌሎች የመገናኛ ብዙኀንን ማልማት፤ መረጃዎችን ማስፈር፣ ወቅታዊነታቸውን መከታተል፣ ደኅንነታቸውን መጠበቅና
መከታተል።
መ. ለቤተክርስቲያንና ለሰንበት ትምህርት ቤቱ የሚጠቅሙ መተግበሪያዎችን (Software) ማልማትና
ለተጠቃሚዎች ማድረስ
ሠ. ሌሎች ክፍሉን የሚመለከቱ ተግባራትን ያከናውናል፡፡
13.2.5. የድኅረ-ገጽ አስተዳደር ንዑስ ክፍል ተጠሪ
ሀ. የንዑስ ክፍሉን ዓመታዊ ዕቅድ ያዘጋጃል፣ ያጸድቃል፤ በየሩብ ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ዘገባ አዘጋጅቶ ለክፍሉ
ጽ/ቤት ያቀርባል፡፡
ለ. የንዑስ ክፍሉን ስብሰባ ቢያንስ በ 15 ቀን አንዴ ያዘጋጃል፤ ይመራል።
ሐ. በንዑስ ክፍሉ ላይ የሚገኙትን የዘርፋት አባላትን ሕይወት በቅርበት ሆኖ ይከታተላል።
ሠ. ንዑስ ክፍሉን ወክሎ በክፍሉ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ላይ ይገኛል፣ ለዘርፍ አባላትም ውሳኔዎችን ያሳውቃል።
ረ. በክፍሉ ጽሕፈት ቤት የተሰጡትን አዲስ አባላት ስለ ንዑስ ክፍሉ አሠራር ገለጻ ያደርጋል ወደ ዘርፎቹ በመመደብ
እንዲያገለግሉ ያደርጋል።
19
674834749.docx
ሸ. ሌሎች ክፍሉን የሚመለከቱ ተግባራትን ያከናውናል፡፡
20
674834749.docx
13.3. የቤተ-መዛግብት አስተዳደር ንዑስ ክፍል
13.3.1. ስያሜ
ንዑስ ክፍሉ የአንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት የመረጃና መዛግብት ክፍል የቤተ-መዛግብት
አስተዳደር ንዑስ ክፍል ተብሎ ይጠራል፡፡
13.3.2. ተጠሪነት
ለመረጃና መዛግብት ክፍል ጽሕፈት ቤት
13.3.3. መዋቅር
የቤተ-መጻሕፍት አስተዳደር
የመዛግብት አስተዳደር ዘርፍ የንብረት ቁጥጥር ዘርፍ
ዘርፍ
ሠ. ንዑስ ክፍሉን ወክሎ በክፍሉ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ላይ ይገኛል፣ ለዘርፍ አባላትም ውሳኔዎችን ያሳውቃል።
21
674834749.docx
ረ. በክፍሉ ጽሕፈት ቤት የተሰጡትን አዲስ አባላት ስለ ንዑስ ክፍሉ አሠራር ገለጻ ያደርጋል ወደ ዘርፎቹ በመመደም ሥራ
እንዲሠሩ ያደርጋል።
22
674834749.docx
ረ. ሌሎች ክፍሉን የሚመለከቱ ተግባራትን ያከናውናል።
13.3.8. የንብረት ቁጥጥር ዘርፍ
ሀ. የዘርፉን ዓመታዊ ዕቅድ ያዘጋጃል፣ ያጸድቃል፤ በየሩብ ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ዘገባ
አዘጋጅቶ ለንዑስ ክፍሉ ተጠሪ ያቀርባል፡፡
ለ. ንዑስ ክፍሉ ላይ ያሉትን ንብረቶች መዝግቦ ይይዛል፤ አዳዲስ ንብረቶች ወደ ንዑስ ክፍሉ ሲገቡ መዝግቦ ይረከባል፤
በጥንቃቄ ያስቀምጣል።
ሐ. ንብረቶች ያሉበትን ደረጃ ይከታተላል፤ የተጎዱ ንብረቶችን ይጠግናል።
መ. ንዑስ ክፍሉ ላይ ያሉ መወገድ የሚገባቸውን ንብረቶች ሥርዓተ ቤተክርስቲያን በሚፈቅደው መሠረት ያስወግዳል።
ሠ. በወር አንድ ጊዜ ንዑስ ክፍሉ ላይ ያሉትን ንብረቶች ይቆጣጠራል፤ ከመዝገቡ ጋር ያመሳክራል፤ ለሚመለከተው አካል
ዘገባ ያቀርባል።
ረ. ንዑስ ክፍሉ ላይ ያለውን የንብረት አጠቃቀም ይገመግማል፤ ማሻሻያ መደረግ የሚገባቸውን ነገሮች ለሚመለከታቸው
አካላት ያሳውቃል፤ ዘገባ ለንዑስ ክፍሉ ተጠሪ ያቀርባል።
ሰ. ሌሎች ክፍሉን የሚመለከቱ ተግባራትን ያከናውናል።
13.4.2. ተጠሪነት
ለመረጃና መዛግብት ክፍል ጽሕፈት ቤት
13.4.3. መዋቅር
23
674834749.docx
13.4.4. የመረጃ አስተዳደር ንዑስ ክፍል ተግባርና ኃላፊነት
ሀ. የክፍሉን ዓመታዊ ዕቅድ ያዘጋጃል፣ያጸድቃል፣ በየሩብ ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ዘርፍ አዘጋጅቶ ለክፍሉ
ጽሕፈት ቤት ያቀርባል፡፡
ለ. ማንኛውም የቤተክርስቲያንና የሰንበት ትምህርት ቤትን የመረጃ ሀብቶች በተለያዩ መንገዶች
አዘጋጅቶ ለተጠቃሚዎች ያደርሳል።
ሐ. የተቀረጹ የተለያዩ መርሐ-ግብራትን በድምጽ፣ በምስል ወድምጽና በፎቶግራፍ አትሞ ማውጣትና
በአርትኦት ንዑስ ክፍል ፈቃድ ሲያገኝ ለተጠቃሚዎች ያደርሳል።
መ. የዜና መጽሔት ያዘጋጃል።
ሠ. የሰንበት ትምህርት ቤቱን አጠቃላይ የመረጃ ቋት (Database) ያዘጋጃል፤ መረጃዎችን ወደ መረጃ
ቋት ያስገባል፤ ይጠብቃል፤ ያበለጽጋል ለተገቢው አካል ያደርሳል።
ረ. የተለያዩ የመረጃ ማስተላለፊያ መድረኮችን ያዘጋጃል
ሰ. ሌሎች ክፍሉን የሚመለከቱ ተግባራትን ያከናውናል፡፡
13.4.5. የመረጃ አስተዳደር ንዑስ ክፍል ተጠሪ
ሀ. የንዑስ ክፍሉን ዓመታዊ ዕቅድ ያዘጋጃል፣ ያጸድቃል፤ በየሩብ ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ዘገባ አዘጋጅቶ ለክፍሉ
ጽሕፈት ቤት ያቀርባል፡፡
ለ. የንዑስ ክፍሉን ስብሰባ ቢያንስ በ 15 ቀን አንዴ ያዘጋጃል፤ ይመራል።
ሐ. በንዑስ ክፍሉ ላይ የሚገኙትን የዘርፋት አባላትን ሕይወት በቅርበት ሆኖ ይከታተላል።
ሠ. ንዑስ ክፍሉን ወክሎ በክፍሉ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ላይ ይገኛል፣ ለዘርፍ አባላትም ውሳኔዎችን ያሳውቃል።
ረ. በክፍሉ ጽሕፈት ቤት የተሰጡትን አዲስ አባላት ስለ ንዑስ ክፍሉ አሠራር ገለጻ ያደርጋል ወደ ዘርፎቹ ደብዳቤ ከክፍሉ
ጽሕፈት ቤት ሲመራለት ተግባራዊ ያደርጋል።
24
674834749.docx
ሐ. በቤተክርስቲያን፣ በደብሩና በሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ የሚኖሩ መደበኛና ልዩ መርሐ ግብራትን
በድምጽ፣ በምስል ወድምጽ፣ በምስል ቅጂ ያስቀምጣል፤ ለመረጃ ማደራጀት ዘርፍ ይልካል።
መ. ገቢ ሊያስገኙ የሚችሉ መርሐ-ግብራት ላይ በመገኘት መረጃዎችን በምስል፣ በድምጽና በምስል
ወድምጽ ይይዛል፤ ለመረጃ ማደራጀት ዘርፍ ይልካል።
ሠ. የአጽራረ ቤተክርስቲያንን እንቅስቃሴ ይከታተላል፣ መረጃዎችን ይሰበስባል፤ ለሚመለከተው አካል
በማቅረብ አፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኙ ያደርጋል።
ረ. ሌሎች ክፍሉን የሚመለከቱ ተግባራትን ያከናውናል፡፡
25
674834749.docx
ለ. ንዑስ ክፍሉ ላይ ያሉትን ንብረቶች መዝግቦ ይይዛል፤ አዳዲስ ንብረቶች ወደ ንዑስ ክፍሉ ሲገቡ መዝግቦ ይረከባል፤
በጥንቃቄ ያስቀምጣል።
ሐ. ንብረቶች ያሉበትን ደረጃ ይከታተላል፤ የተጎዱ ንብረቶችን ይጠግናል።
መ. ንዑስ ክፍሉ ላይ ያሉ መወገድ የሚገባቸውን ንብረቶች ሥርዓተ ቤተክርስቲያን በሚፈቅደው መሠረት ያስወግዳል።
ሠ. በወር አንድ ጊዜ ንዑስ ክፍሉ ላይ ያሉትን ንብረቶች ይቆጣጠራል፤ ከመዝገቡ ጋር ያመሳክራል፤ ለሚመለከተው አካል
ዘገባ ያቀርባል።
ረ. ከክፍላት የንብረት ውሰት ጥያቄ ሲመጣ በጽሕፈት ቤቱ የይሁንታ ፈቃድ ሲያገኝ በቅጽ መዝግቦ ያስረክባል፤ አገልግሎቱ
ሲጠናቀቅ በአግባቡ ይረከባል።
ሰ. ንዑስ ክፍሉ ላይ ያለውን የንብረት አጠቃቀም ይገመግማል፤ ማሻሻያ መደረግ የሚገባቸውን ነገሮች ለሚመለከታቸው
አካላት ያሳውቃል፤ ዘገባ ለንዑስ ክፍሉ ተጠሪ ያቀርባል።
ሸ. ሌሎች ክፍሉን የሚመለከቱ ተግባራትን ያከናውናል።
26
674834749.docx
14. ሒሳብና ንብረትን በተመለከተ
ለ. በተለያየ ምክንያት ማለትም ከበጎ አድራጊዎች፤ ከአባላት ወዘተ . . . ወደ ክፍሉ የሚመጣ ገቢ ቢኖር
ከገቢው ላይ ምንም ተቀናሽ ሳይደረግ በሒሳብ ክፍል በኩል ለሰንበት ትምህርት ቤቱ ገቢ ማድረግና የገቢ
ደረሰኝ መቀበል ይኖርበታል፤
ሠ. ገቢን በተመለከተ ከሚመለከተው ከልማት ክፍል ጋር በመሆን ከሚያመጣው ገቢ ውጪ በራሱ የገቢ ምንጭ
ፈጥሮ ገቢ መሰብሰብ አይችልም፤
ለ. ክፍሉ የትኛውም ዓይነት ንብረት ለማስወገድ ሲፈልግ በቅድሚያ የሰንበት ትምሕርት ቤቱ ጽሕፈት ቤት
ፈቃድ ሊያገኝ ይገባል፤
ሐ. ከክፍሉም ይሁን ከበጎ አድራጊዎች የሚሰጥ ንብረት ሲኖር በቅድሚያ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽሕፈት
ቤት በደብዳቤ ማሳወቅና ወደ ሒሳብና ንብረት ክፍል ገቢ ሆኖ ተመዝግቦ በድጋሚ ወጪ መሆን
ይኖርበታል፤
መ. ማንኛውም የጎደለ ንብረት ቢኖር የክፍሉ አሥፈጻሚዎች ንብረቱን ፈልገው በቦታው የመመለስ፤
ካልሆነም የመተካት ግዴታ አለባቸው፤
27
674834749.docx
15. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
28
674834749.docx