You are on page 1of 5

የሳይንስ መሳሪያዎች ዘርፍ

ብሔራዊ የሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት ዋና ዋና ዓላማዎች ውስጥ የሳይንስ


መሳሪዎች ጥገና ብሄራዊ አቅም መገንባትና የጥገና አገልግሎት
መስጠት እና ለሳይንስ መሳሪያዎች ተጠቃሚዎች የቴክኒክ፤ የስልጠናና
የምክር የመረጃ አገልገሎቶችን በመስጠት ተግባራቶቻቸወን በብቃት
እንዲያከናውኑ መደገፍ የሚሉት የዘርፉን የትኩረት አቅጣጫዎች
ያሳያሉ፡፡

የሳይንስ መሳሪያ ሲባል ምን ማለት ነው?

እንደየአገራት የዕድገት ደረጃና ተጨባጭ ሁኔታዎች ለሳይንስ መሳሪያ የሚሰጠው ትርጓሜ በይዘት ወሰን የተለያዩ
ቢመስሉም ኢንስቲትዩቱን ለማቋቋም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው ደንብ ቁጥር 194/2003 ወስጥ “ የሳይንስ
መሳሪያ ማለት ለምርምርና ሥርፀት፣ ለትምህርትና ሥልጠና፣ ለጥራትና ቁጥጥርና ፍተሻ፣ ለሥነ-ልክ፣ ለሰው ወይም
ለእንስሳት ህክምና አገልግሎቶች ሥራ ላይ የሚውል መሳሪያ ነው” ተብሎ ተብራርቶ ይገኛል፡፡

ለሳይንስ መሳሪያዎች ለምን ትኩረት መስጠት አስፈለገ?


ባለንበት ዘመን የሳይንስና ቴክኖሎጂን ፈጣን የዕድገት አገራችን ለመከተል በምታደርገው ጥረት ውስጥ በተከታታይ
በሚደረጉ ሳይንሳዊ ምርምሮች፤ ምርመራዎችና ትንተናዎች፤ የምርት ጥራት ክትትሎች፣ ፍተሻዎችና ቁጥጥሮች
እንዲሁም ሊሎች ሳይንሳዊ ተግባራቶች በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ የሳይንስ መሳሪያዎችን በብቃት ከመጠቀም
ውጭ የሚፈለገውን የግብ ስኬት ማስመዝገብ ይከብዳል፡፡
በዚህም ምክንያት በጥቅሉ በአንድ በኩል የሳይንስ መሳሪያዎች በአብዛኛው የውጭ ቴክኖሎጂ ውጤቶች በመሆናቸው
ለማግኘት የሚፈስባቸውን ሀብት ቢያንስ ተመጣጣኝ የሆነ ውጤት በየሴክተሩ ማግኘት አለመቻሉ በሌላ በኩል ደግሞ
እነዚህን ቴክኖሎጂዎች በአገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገው የሳይንሳዊ ምርምር ጥረት ሚዛን ሚደፋ አለመሆን
የሳይንስ መሳሪያዎች ጎዳይ አሳሳቢና ትኩረት የሚሻ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡
በሳይንስ መሳሪያዎች እያጋጠሙ ያሉ ችገሮችና መፍትሄዎች
የሳይንስ መሳሪያዎችን በጥንቃቄ መርጦና ገዝቶ ለሳይንሳዊ ተግባር ሥራ ላይ አውሎ ወጤት ማምጣት ካልተቻለ በሂደቱ
ውስጥ ችገሮች አንዳሉ ለመገንዘብ አያዳግትም፡፡ ችግሮቹ የሳይንስ መሳሪያዎችን ከመምረጥ፣ ከመግዛት፣ ከመጠቀም፣
ከማስወገድና ከማስተዳደር ጋር የተያያዙና በሁሉም ሣይንሳዊ ምርምርና አገልግሎት በሚሰጡ የኢኮኖሚ ሴከተሮች
የሚታዩ ዘርፈ ብዙ ናቸው፡፡ ይሁንና ችግሮቹን ለማስታገስ ብሎም ለመፍታት መንግስት በብሔራዊ የሥነ-ልክ
ኢንስቲትዩት በኩል ስትራቴጂዎች ቀይሷል፡፡ እነዚህም

 ምርምሮችን በማከሄድና በምልስ ምህንድስና አግባብ የሳይንስ መሳሪያዎችን በአገር ምርት መተካት
 የሳይንስ መሳሪያዎችን በብቃት ለመጠቀም የሚያስችሉ አገራዊ የአቅም ግንባታ ተግባር ተኮር የስልጠና
ፕሮግራሞችን ማካሄድ
 ጥገናና ተያያዥ የቴክኒክ አገልግሎቶቸን በመስጠትና በማስፋት በተቋማት የሚሰጡ ሳይንሳዊ አገልገሎቶች
እንዳይደናቀፉና ቀጣይነት እንዲኖራቸው ማድረግ
 የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ተሰማሚነት(ከቴክኖሎጂ፣ ከማህበራዊ፣ ከኢኮኖሚዊ፣ ከሥነ-ምግባራዊና ከአካባቢ
ሁኔታዎች አንጻር) መዳሰስና መረጃዎችን ማሰራጨት
 በሳይንስ መሳሪያዎች ዙሪያ የማማከር አገልግሎቶችን በመስጠት ሳይንሳዊ ተግባራትን የሚከናውኑ ተቋማትን
በመደገፍ ክፍተቶችን መሙላት ናቸው።

በሳይንስ መሳሪያዎች ንዑሳን ዘርፎች


ኢንስቲትዩቱ በአገር ደረጃ የሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሳይንስ መሳሪያዎቸን የህይወት ዘመን ኡደት በተለይ ደግሞ
የመምረጥን፣ የመግዛትን፣ የመጠቀምና የማስወገድ ሂደቶችን በተከተለ መልክ ሆኖ ከተፈጠሩበት ሳይንሳዊ
መነሻዎቻቸው፣ በጥቅም ላይ ከሚውሉባቸው ሳይንሳዊ ዘርፎች አግባብና የምህንድስና ተግባራት በተደራጀ ሁኔታ
ከመከወን አንፃር በአራት ንዑስ ዘርፎች በመክፈል ነው። እነዚህም የህክምና፣ የልኬትና አናሊሲስ፣ የኑክሊየር እና
የኤሌክትሮ-ሜከኒካል መሳሪያዎች ናቸው።
የህክምና መሳሪያዎች
የህክምና መሳሪያዎች በጤና አገልግሎትና ምርምር ተቋማት ለተለያዩ በሽታዎች ምርመራ፣ የታካሚን ሁኔታ
ለመከታታል፣ አክሞ ለማዳን፣ ወስጣዊ አካል ለመተካት፣ የፅኑ ህሙማንን ህይወት ለመታደግ እና ሌሎች
ሆስፒታላዊ አገልግሎቶችን ለመስጠት በጥቅም ላይ የሚውሉ መሳሪያዎች ሲሆኑ ለምሳሌ፡- አልትረሳውንድ፣
ኤሌክትሮካርድዮግራፍ፣ የታካሚ የጤና ሁኔታ መከታተያ ሞኒተሮች፣ ኤሌክትሮሰርጂካል ዩኒት፣ ኢንፉዥን
ፓምፖ፣ ቬንትሌተር፣ወዘተ አመላካቾች ናቸው።
የልኬትና አናሊሲስ መሳሪያዎች
የምርምርና ሳይንሳዊ አገልግሎቶች በሚሰጡ በተለይ የህክምና ባልሆኑ ላቦራቶሪዎች የተለያዩ ፊዚካል
ኳንቲቲዎችን ለመለካት፣ ወህዶችን ለመለየት፣ ናሙናዎች ላይ ትንተና ለማድረግ፣ ለመፈተሸና የጥራት ቁጥጥር
ለማድረግ ወዘተ. የሚያገለግሉ መሳሪያዎች ሲሆኑ ለምሳሌ፡- ክሮማቶግራፍ፣ ስፔክትሮፎቶሜትር፣ ካሊብሬተርስ
(ቮልቴጅ፣ ከረንት፣ፕሬዠር፣ ቴምፕሬቸር ..)፣ አናሊቲካል በላንስ፣ ፒኤች ሜትር፣ ኮንዳከቲቪቲ ሜትር፣ወዘተ
አመላካቾች ናቸው።
የኑክሊየር መሳሪያዎች
አዮን ፈጣሪ ጨረራ በሚለቅቁ ቁሶችና በሚያመነጩ አከላቶች ተመስርተው ለህክምና ምርመራና አክሞ ለማዳን፣
ለምልከታ፣ ለትንተናና ፍተሻ እንዲሁም አዮን ፈጣሪ ጨረራን መኖሩን ለማወቅ ለመለየትና፣ ለመለካት ወዘተ.
በህክምናም ሆነ ሌሎች ሳይንሳዊ አገልግሎቶች በጥቅም ላይ የሚውሉ መሳሪያዎች ሲሆኑ ለምሳሌ፡- ሜዲካል
ዲግኖስቲክና ኢንዱስትረያል ኤከስሬይ፣ ጋማካሜራ፣ ሰርቬይ ሜትር፣ ኑክሊየር ጌጅስ፣ ጋማ ኢራዲየተርስ፣
ዶዚሜትር፣ ጋማሰፔክትሮሜትር ወዘተ አመላካቾች ናቸው።
የኤሌክትሮ-ሜከኒካል መሳሪያዎች
በህክምናም ሆነ ከህክምና ውጭ ባሉ ላቦራቶሪዎች ውስጥ የከባቢ ሀኔታዎችን ለመቆጣጠርና ለማመጣጠን፣
ናሙናዎቸን ጠብቆ ለማቆየት፣ ናሙናዎችን ለመለየት፣ ጎጂ ተወስያንን ለማስወገድ ወዘተ. የሚጠቅሙና
በላቦራቶሪ ውስጥ በብዛት የሚገኙ መሳሪያዎች ሲሆኑ ለምሰሌ፡- አውቶከሌቭ፤ ሴንትሪፊዩጅ፣ ሬፍሪጅሬተርስ፣
ሁድሰ፣ ሼከርስ፣ ኦቨንስ ወዘተ አመላካቾች ናቸው።

አደረጃጀት
በሳይንስ መሳሪያዎች ዘርፍ በጥቅሉና በንዑሳን ዘርፎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለመምራት ሁለት ዋና ዋና የሥራ
ሂደቶች ማለትም የሳይንስ መሳሪያዎች ሥልጠናና ምክር ዳይሬክቶሬት እና የሳይንስ መሳሪያዎች ምህንድስናና ቴክኒክ
ዳይሬክቶሬት በኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ሥር ተዋቅረዋል፡፡ እያንዳንዳቸውም ከላይ በተመለከቱት የሳይንስ መሳሪያ
ንዑሳን ዘርፎች አግባብ የተዋቀሩ ሰምንት ቡድኖች ከነፋሲሊቲዎቻቸው ሲኖራቸው
የሳይንስ መሳሪያዎች ምህንድስናና ቴክኒክ ዳሬክቶሬት በሥሩ በአራቱም ንዑሳን ዘርፎቹ በተዋቀሩት ቡድኖችና
ወርክሾፖች በመታገዝ በዋናነት ከተቋማት ዓቅም በላይ የሆኑና በደንበኛው ጥያቄ መሰረት የሚስተናገድ የተከላ፣
የጥገና፣ የኮሞሺኒንግ፣ የማስወገድና ተያያዥ አገልግሎቶችን ሲያከናውን በእነዚሁ አገልግሎቶች ለመስጠት በግል የንግድ
ተቋምነት የሚቋቋሙ ድርጅቶችን ብቃትንም በመገምገም ያረጋግጣል፡፡
በተጨማሪም ለአራቱም ቡድኖች በጥገናና ተዛማጅ የቴክኒክ
ስራዎች ሂደቶች ውሰጥ በቀላሉ በአገር ውስጥ ገበያ ለማይገኙ
ሜካኒካልና ጠርሙስነክ መለዋወጫዎችንና ተፈላጊ አካለትን
ዲዛይን በማድረግና በመስራት የሚያቀርብ ቡድን ከሜካኒካልና
ግላስብሎዊነግ ወርክሾፖች ጋር ተደራጀቷል፡፡

በሳይንስ መሳሪያዎች ዙሪያ ያሉትን ዘርፈ ብዙ ችግሮች


ለመቅረፍ በአንድ ተቋም ብቻ የሚሰጥ አገልግሎት በቂ
አይሆንም፡፡ በመሆኑም አገልግሎቶችን ለማስፋትና ተደራሽ
ለማድረግ በየተቋማቱና በግል ኩባኒያዎች ጭምር የሳይንስ
መሳሪያ ቴከኒካል አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች አንዲበራከቱ፤
ተግባረቶቹንም በብቃት ሊያከናውኑ የሚችሉ መሀንዲሶችና
ቴክኒሻኖችን ለማበራከት አንዲሁም በሳይንስ መሳሪያዎች
ህይወት ኡደት ወስጥ የሳይንስ መሳሪያዎች ተጠቃሚ ተቋማት
ያለባቸውን ከፍተቶች በመድፈን ለመደገፍ የስልጠናና ምክር
አገልግሎቶች በሳይንስ መሳሪያዎች ሥልጠናና ምክር
ዳይሬክቶሬት ይሰጣል፡፡ ዳይሬክቶሬቱ የሚሰጣቸው ሰልጠናዎች
በተግባር የተደገፉ በመሆናቸው ለዚሁ ተብለው የተዘጋጁ የስልጠና ላቦራቶሪዎች ተደራጅተዋል፡፡
አገልግሎቶች
ኢንስቲትዩቱ ከምርምርና ሥርፀት ውጭ ከላይ በተጠቀሱት የሳይንስ መሳሪያዎች ንዑሳን ዘርፎች በሁለቱም
ዳይሬክቶሬቶች አማካኝነት በቀጥታ ለደንበኞች በአገር ደረጃ የሚሰጣቸው አገልግሎቶች የተከላ፣ የኮሞሺኒንግ፣
የጥገናና የማስወገድ አገልግሎት፤ የሥልጠና አገልግሎት፤ የምከር አገልግሎት አና የብቃት ማረጋገጥ ናቸው።
የተከላ፣ የጥገና፣ የኮሞሺኒንግ፣ የማስወገድና ተያያዥ አገልግሎት
የሳይንስ መሳሪያዎች የተከላ፤ ኮሞሺኒንግ፤ ጥገናና ማስወገድ
አገልግሎቶቹን ለደንበኞቹ በመንግስት በተወሰነለት
የአገልግሎት ክፍያ መሰረት ይሰጣል፡፡ በተለይ የጥገና አገልግሎት
ሊንቀሳቀሱ የሚችሉ መሳሪያዎች በኢንስቲትዩቱ በሚገኙ
ወርክሾፖች ወይም በቋሚነት የተተከሉና ሊንቀሳቀሱ
የማይችሉትን በመስክ በመገኘት ይከናወናል። አገልግሎቶቹን
ለማግኘት፦

 የሚፈለገውን አገልግሎት በዝርዘር በመጥቀስ


የአገልግሎት ጥያቄ በደብዳቤ/ፎርም በመሙላት በፋከስ፣ በአካል፣ በፋክስ ወይም በኢሜል በደንበኞች አገልግሎት
ወይም በመዝገብ ቤት በኩል ማቅረብ፤
 በመስክ ለሚከናወን የሳይንስ መሳሪያ ተከላ፤ኮሚሽኒንግ፤ጥገናና ማስወገድ አገልግሎት ደንበኛው ወደፊት ስራው
ሲጠናቀቅ ታሳቢ የሚሆን 500.00 ብር ቅድሚያ ክፍያ ማስያዝ፤
 በኢንስቲትዩቱ የሚጠገኑ መሳሪያዎችን በአካል ለደንበኞች አገልግሎት ማቅረብና ማስረከብ እና
 ጥገናው ሲጠናቀቅ በኢንስቲትዩቱ በሚቀርበው የአገልግሎት ክፍያ መጠየቂያ መሰረት ክፍያ በመፈፀም ለጥገና
የመጣውን መሳሪያ በመፈተሽ ከደንበኞች አገልግሎት መረከብ ያስፈልጋል።

የሥልጠና አገልግሎት፡
ኢንሰቲትዩቱ በመንግሰትም ሆነ በግል ተቋማት በሳይንስ
መሳሪያዎች ቴክኒካል ተግባራትን በማከናወን ላይ ለሚገኙና
ወደ ስራ ለሚገቡ መሀንዲሶችና ቴክኒሻኖች ዕውቀትና
ክህሎትን የሚያሳደግ በዲዛይን፣ ጥገና አንዲሁም በሳይንስ
መሳሪያዎች ስራ አመራር ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባር ተኮር
ስልጠናዎች ይሰጣል። ስልጠናዎቹ በግሩፕ የሚሰጡ ሲሆኑ
ለዚሁ በተዘጋጁ የስልጠና ላቦራቶሪዎች ወስጥ ነው።
በእያንዳንዱ ስልጠና የሚጠበቀው ትንሹ የሰልጣኝ ቁጥር 10
ሲሆን የሚወስዱት ጊዜም ከአንድ አስከ ሁለት ሳምንት ነው።
በስልጠናው ላይ ከ 80 በመቶ በላይ የሚሆነውን የስልጠና
ይዘት ለሸፈኑ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት ይሰጣል።

የምክር አገልግሎት
በሰይንስ መሳሪያዎች ህይወት ዑደት ማለትም ከመምረጥ፣ ከመግዛት፣ ከመጠቀም እስከ ማስወገድ ድረስ ባሉ ሂደቶች
በርካታ ችግሮች፣ ክፈተቶችና ተግዳሮቶች በየተቋማቱ ይታያሉ። ኢንስቲትዩቱ ተቋማት ተግባራቶቻቸውን በብቃት
አንዲወጡ ለማስቻል በሳይንስ መሳሪያዎች ዙሪያ ከሚሰጣቸው የቴክኒክ አና የስልጠና አገልግሎቶች በተጨማሪም
የሳይንስ መሳሪያዎች ከመምረጥ፣ ከመግዛት፣ ከመጠቀም ወይም ማስወገድ ጋር በተያያዘ የማማከር አገልግሎት
ይሰጣል። አገልግሎቱን ለማግኘት ጥያቄ ማቅረብና የምክር አገልግሎቱ ውጤት እንደቀረበ ክፍያ በመፈፀም
ይጠናቀቃል።
ኢንስቲትዩቱ የሚሰጣቸው አገልግሎቶች ተደራሽነት ለማስፋትና የመጠቀም (የመትከል፣ የመፈሸ፣ የመጠገን
ወይም/እና የማስወገድ) ዓቅምን ለማሳደግ የሳይንስ መሳሪያዎች ተጠቃሚ ተቋማት የራሳቸውን የተክኒካል
አገልግሎቶች የሚሰጥ ክፍል ለማቋቋም በሚያደርጉት ጥረት ውስጥም በሚደረጉ ሰምምነቶች ቀጥተኛ የሆነ ድጋፍ
ይሰጣል።

የብቃት ማረጋገጥ አገልግሎት


ኢንስቲትዩቱን ለማቋቋም በሚኒስትሮች ምከር ቤት ደንብ ቁጥር 194/2003 በተሰጠው ስልጣንና ተግበራት መሰረት
የሳይንስ መሳሪያዎችን ለመጠገንና ተዛማጅ ቴክኒካዊ አገልግሎቶችን ለመስጠት ተቋማት የሚያቋቁሟቸውን
ወርክሾፖች ብቃት በመገምገም የምስክር ወረቀት ይሰጣል። በተጨማሪም የአገልግሎቱ ተደራሸነት በአገር ደረጃ እንዲያሰፋ በሳይንስ
መሳሪያዎች ተከላ፣ ኮሚሽኒንግና ጥገና ስራ ላይ ለሚሰማሩ የግል ድርጅቶች የንግድ ስራ ፍቃድ እንዲያገኙ በኢፌድሪ ተወካዮች ም/ቤት
የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አዋጅ መሰረት የብቃት ማረጋገጫ አገልግሎት ይሰጣል። ይህንንም አገልግሎት ለማግኘት የማመልከቻ ቅፅ
በመሙላት ጥያቄ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ በቀጣይነትም ለአገልግሎቱ የወጡትን መስፈርቶች በመከተልና የሰነድና የስራ ቦታ ግምገማ
ውጤት ላይ ተመርኩዞ የተተመነውን ክፍያ በመፈፀም የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማግኘት ይቻላል፡፡

አድራሻና ሥልክ ቁጥሮች


ብሄራዊ የሥነ-ልክ ኢንሰቲትዩት
የሳይንስ መሳሪያዎች ካምፓሰ-አዲስ አበባ
ከላምበረት-ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ አጠገብ

ለበለጠ መረጃ እና የተከላ፣ የጥገና፣ የኮሞሺኒንግ፣ የማስወገድና ተያያዥ አገልግሎት እና የብቃት ማረጋገጥ አገልግሎት
ለማግኘት፡-

 የሳይንስ መሳሪያዎች ምህንድስናና ቴክኒክ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ጽ/ቤትን በስልክ ቁጥር +251-116
462783 እንዲሁም የደንበኞች አገልግሎትን +251-116 457648 በመደወል ማግኘት ይቻላል።

የሳይንስ መሳሪያዎች ሥልጠና ወይም ምክር አገልግሎቶችን ለማግኘት

 የሳይንስ መሳሪያዎች ሥልጠናና ምክር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ጽ/ቤትን በስልክ ቁጥር +251 116 463031
በመደወል ማግኘት ይቻላል።

You might also like