You are on page 1of 10

የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ


I. አጠቃላይ መግለጫ
የመስሪያ ቤቱ ስም የሥራ መደቡ መጠሪያ የሥራ ዘርፍ/የሥራ ሂደት
ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማት የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ
ስታንዳዳይዜሽን ዴስክ ኃላፊ ልማት ስታንዳዳይዜሽን ዴስክ

የቅርብ ኃላፊ የሥራ መደብ የሥራው ደረጃ የሥራው ኮድ


/ተጠሪነት
የከተማ ልማት ስታንዳርዳይዜሽን
ዋና ሥራ አስፈፃሚ

መስሪያ ቤቱ የሚገኝበት ቦታ

II. የሥራ መደቡ ዋና ዓላማ፣ከሥራ መደቡ የሚጠበቁ ውጤቶችና ተግባራት


2.1. የሥራ መደቡ ዓላማ፡-
የዴስክን ሥራ በማቀድ፣ በመምራት፣ አፈጻጸሙን በመከታተልና በመደገፍ፣ በመገምገምና በማረጋገጥ፣ የዴስኩን
የአሠራር ሥርዓት እንዲሻሻል በማድረግ፣ በከተሞች ለሚገነቡ የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ
ልማቶች ስታንዳርድ ዲዛይን በማዘጋጀት፣ በከተሞች ለሚገነቡ የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ
ልማቶች ስታንዳርድ በማዘጋጀት፣ የመሰረተ ልማት ስታንዳርድ የኮንትራት አስተዳደር ስርዓት
በመፍጠር፣ የኢኮኖሚ መሰረተ ልማቶች የአካባቢና ማህበራዊ ደህንነት ባረጋገጠ መልኩ ድጋፍና
ክትትል በማድረግ፣ በከተሞች የሚገነቡ አረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች ደረጃውን በጠበቀ
ስታንዳርድ እንዲገነቡ በማድረግ የመሠረተ ልማት አቅርቦቱ በሥርዓት እንዲመራ ማድረግ ነው፡፡

2.2.ከሥራ መደቡ የሚጠበቁ ውጤቶችና ተግባራት


ውጤት 1፡ የዴስኩን ሥራ ማቀድ፣ መምራት፣ ማስተባበርና መገምገም
 የዴስኩን የረጅምና የአጭር ጊዜ የበጀትና የስራ ዕቅድ ያዘጋጃል፣ ለባለሙያዎች ያከፋፍላል፣ አስፈላጊውን እገዛ
ያደርጋል፣
 ለዴስኩ ግብ መሳካት ልዩ ልዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ክፍሉ አስፈላጊ በሆኑ ግብአቶች እንዲሟላ ያደርጋል፣
 በዴስኩ የሚከናወኑ ስራዎች በተቀመጠላቸው የግዜ ገደብ ወጪና ጥራት መሰረት መከናወናቸውን ይገመግማል፣
ያረጋግጣል፣
 የዴስኩን ስራ በበላይነት ያሰተባበራል፣ ያደራጃል፣ ይመራል፣ ይቆጣጠራል፣ ውሳኔ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ወቅታዊ
ምላሽ ይሰጣል፣

1
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

 የባለሙያዎችን አፈፃፀም በየወቅቱ ይለካል፣ ይገመግማል፣ አስፈላጊ ማስተካከያዎችን ያደርጋል፣


 የዴስኩን ባለሙያዎች የስልጠና ፍላጎት ይለያል፣ ስልጠናዎችን ያመቻቻል፣ በተግባር ላይ እንዲውል ያደርጋል፣
 የዴስኩን የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ውጤት ለበላይ ሃላፊዎች ሪፖርት ያቀርባል፣

ውጤት 2፡ በዴስኩ የሚዘጋጁ የተለያዩ ጥናቶች መገምገምና ማረጋገጥ፣

 የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች አስመልክቶ በሚዘጋጁ የፖሊሲና የስትራቴጂ ሰነዶች ሲቀረጹ ይሳተፋል፣
ይገመግማል፣ ለውሳኔ ያቀርባል፣
 የከተማ መሰረተ ልማት በተመለከተ የፖሊሲ ግብአትና የፖሊሲ አፈጻጸም ግምገማ ጥናትና ምርምሮች እንዲካሄድ ያደርጋል፣ ይገመግማል፣
ያስጸድቃል፣

 የከተማ መሰረተ ልማት ፖሊሲና ስትራቴጅና መተግበሪያ አማራጮች ይቀይሳል ለተግባራዊነታቸውም ለክልሎች፤ ከተሞችና ለግሉ ዘርፍ ድጋፍ
ያደርጋል፡፡

 ለለአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች የዲዛይን ዝግጅት የሚስፈልጉ ጥናቶች ያስደርጋል፣ ለዲዛይን ዝግጅት
በግብዓትነት ይጠቀማል፣
 በግንባታ ሂደት በዲዛይን ምክንያት የሚያጋጥሙ ችግሮችን፣ መንስኤውንና መፍትሔውን በጥናት ይለያል፣
 የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማት ስታንዳድር ዝግጅት ለማካሄድ የሚያስችል የዲዛይን አዘገጃጃት አሰራር
እንዲዘጋጅ ያደርጋል፣
 የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሠረተ ልማቶች የጥገና አፈጻጸም ነባራዊ ሁኔታ ያጠናል፣ ለስታንዳድ ዝግጅት በግብዓትነት
ይጠቀማል፣
 የከተሞች የመሰረተ ልማት ስራዎች ግንባታ ዲዛይኖች፤ ግብአቶች፤ የግንባታ ውህዶች፤ የግንባታ ሂደትና ውጤት ደረጃ
ለማውጣት የሚያስችል ጥናት ያስደርጋል፣ የጥናት ውጤት ይገመግማል፣ ያስጸድል፡፡
 በከተሞች የሚገነቡ መሰረተ ልማቶች የአካባቢና ማህበራዊ ደህንነት እያረጋገጡ የሚተገበሩ መሆኑን በጥናት እንዲረጋገጥ ያደርጋል፣
ይገመግማል፣ ውጤቱን ያስፈጽማል፣
 የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች የግንባታ አተገባበር ሂደትን በማጥናት የአሰራር ማሻሻያ እንዲደረግ ሀሳብ ያቀርባል፣ ያጸድቃል፣
እንዲተገበሩም ይሰራል፡፡
ውጤት 3፡- የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማት አቅርቦት ሊከተላቸው የሚገባ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት
 የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች በከተሞች ደረጃ መተግባር የሚችሉበትን ሁኔታ ከከተሞች ያልተማከለ
አስተዳደር ስርዓት ጋር በማስተሳሰር መሰረተ ልማቶቹና የከተሞች ደረጃ የተጣጣመ እንዲሆን በጥናት ይለያል፣ በዚሁ
መሰረትም ስራዎችን እንዲሰሩ ያደርጋል፣
 በስራ ላይ ያሉ የከተማ መሰረተ ልማት የግንባታ ዲዛይኖችን በመፈተሽ ሞዴል ዲዛይኖችን እንዲዘጋጁ ያደርጋል፣
ዲዛይኖቹ በከተሞች ጥቅም ላይ እንዲውሉ ያስተባበራል፣ ይመራል፣
 ከተቋሙ አቅም በላይ የሆኑ የዲዛይን ሥራዎች ሲኖሩ በክልሎች ወይም በከተሞች ውክልና በውጭ አማካሪ መሃንዲሶች እንዲሰሩ

2
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

ያደርጋል፣ ግባታም ይደግፋል፣


 የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች ስታንዳርድ እንዲዘጋጅ ያደርጋል፣ ያስገመግማል፣ ያስጸድቃል፣
 ለአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሠረተ ልማቶች የግንባታ ግብዓት፣ የግብዓት አጠቃቀም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ወዘተ
ሥራዎችንና አገልግሎቶችን በመለየት ደረጃ እንዲዘጋጅ ያደርጋል፣ ያጸድቃል፣ ያስተገብራል፣
 በውስጥ አቅም በሚዘጋጁ የስታንዳርድ ቴክኒካል ሰነዶች ላይ የዝግጅት ቡድኖች በማደራጀት አጠቃላይ ስራውን
በበላይነት ይመራል ይከታተላል፤
 የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች የግንባታ ክትትል ስታንዳርድ እንዲኖር በማድረግ፣ አፈጻጸም እንዲገመገም
ያደርጋል፣
 የግንባታ አፈጻጸም ስርዓቱን ለማዘመን የሚያስችሉ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ዓይነቶች ታሳቢ ያደረገ የአሰራር
ማንዋሎች፣ሞዳሊቲዎች፣ ፎማቶች፣ ወዘተ እንዲዘጋጁ ያደርጋል፣ ይገመግማል፣ ያጸድቃል፣ ተግባራዊ እንዲሆኑ
ይሰራል፡፡
 በውጭ አቅም የተዘጋጁና የተሻሻሉ የስታንዳርድ ደረጃዎች እንደአስፈላጊነቱ ሰነዶቹን የሚያዳብሩ ግብዓቶች አካተው
በየደረጃው የሚጠበቅባቸው ሂደት በማለፍ ፀድቀው ወደ ስራ እንዲገቡ ያደርጋል፡፡
 ከባለድርሻ አካላት እና ከፈጻሚና አስፈጻሚ አካላት አስተያየቶች የሚሰባሰቡበትን ስልት ይቀይሳል፣ አስተያየቶች
እንዲሰበሰቡ ያደርጋል፣ይገመግማል፡፡
 በዲዛይን ዝግጅት፣ በግንባታ አተገባበር ሂደቶች፣ በስታንዳድ ዝግጅትና የግንባታ ሥራና አገልግሎት ደረጃ አወጣጥ ዙሪያ ምርጥ
ተሞክሮዎችን ያፈላልጋል፣ ስራዉ ከሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር የተገናዘበና የተጣጣመ መሆኑን ይገመግማል፤ ያረጋግጣል፣
 ከተገኙ ተሞክሮች እና ከተለዩ ክፍተቶች መነሻ በማድረግ የስታንዳርድ ዝግጅት፣ የክትትልና ድጋፍ ስርአቱን ያሻሽላል ተግባራዊ
ያደርጋል፡፡
 ለዘርፉ ተዋንያንና ባለድርሻ አካላት ስታንዳርዶች ጥናቶችና አውደ ጥናቶችን በማዘጋጀት የምክክር መድረኩን ይመራል፤
 የስታንዳርድ ዝግጅት ዝክረ ተግባር እንዲዘጋጅ በማድረግና በማፅደቅ ተግባራዊ እንዲሆን ያደርጋል፣
 የሚገነቡ የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች የአካባቢያዊና ማህበራዊ ደህንነት ያረጋገጡ እንዲሆኑ የአሰራር ስልት እንዲነደፍ
ያደርጋል፣ ስርዓት ይዘረጋል፣
 የግልና የመንግስት አጋርነትና የመሰረተ ልማት ፋይናንስንግ ፕሮጀክቶች መረጣ፣ ዝግጅትና ምክክር ላይ ይሳተፋል፣
ውጤት 4፡ የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሠረተ ልማት ስታንዳዶች፣ ዲዛይን ትግበራ፣ የአሠራርና አገልግሎት ደረጃዎች መከታተልና መደገፍ፣

 በክልሎችና ከተሞች የሚተገበሩ አረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶችን በመስክና በመድረክ በመገኘት አተገባበራቸውን ይከታተላል
ይገመግማል፣

 የተዘጋጁ ዲዛይኖችና ስታንዳርዶች በከተሞች ተግባር ላይ ሲውሉ ያስገኙትን ፋይዳ ይገመግማል፣ ይደግፋል፣ ማሻሻያ ሲያስፈልግ ያስፈጽማል፣

 በክልሎችና ከተሞች የሚቀርቡ የዲዛይን ዝግጅት ድጋፍ ጥያቄዎች አጥንቶ ድጋፍ ያደርጋል፣

 አዲስ ለሚሰሩና በመሰራት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች በውሉ መሠረት ጥራታቸውንና ደረጃቸውን ጠብቀው በተያዘላቸው ጊዜ መሠራታቸውን

3
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

ያረጋግጣል፣

 ለዲዛይን ዝግጅት የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ተከታትሎ እንዲሟሉ ያደርጋል፣


 በከተሞች የሚገነቡ መሰረተ ልማቶች ከጥራት አኳያ ያላቸውን አዋጭነት/value for Money/ ናሙና በመውሰድ ያጠናል፣ ውጤቱን መነሻ
በማድረግ ይደግፋል፣

ውጤት 5 ፡- የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች ስታንዳርዶች ማስተዋወቅ፣ ማስፋፋትና የማስረጽ ስልጠናዎች እንዲከናወኑ ማድረግ፣

 አዲስ የወጡና የተሻሻሉ የጸደቁ ስታንዳርዶች ለዘርፉ ተዋንያንና ባለድርሻ አካላት መዳረሳቸውንና መተዋወቃቸውን
ያረጋግጣል፤
 በስልጠና ፍላጎት ዳሰሳ መሰረት በስታንዳርዶች ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የሚያስችሉ ስልጠናዎች እንዲሰጡ ውሳኔ
በመስጠት አፈፃፀሙን ይከታተላል፡፡
 አዲስ የወጡና የተሻሻሉ ስታንዳርዶች በባለድርሻ አካላትና የዘርፉ ተዋንያን ለማስረጽ የሚያስችል ሥልጠና እንዲዘጋጅ
ያደርጋል የስልጠናውን ዝክረ ተግባር ያፀድቃል፤
 ስልጠና እንዲሰጥባቸው በተመረጡ ስታንዳርዶች ላይ አስፈላጊ የሆኑ የስልጠና ሰነዶችና ግብዓቶች መዘጋጀታቸውን
ያረጋግጣል፣
 በአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች በተዘጋጁ ደረጃዎችና ስታንደርዶች ዙርያ የግንዛቤ ማስጨበጫ የስልጠና
ፅሑፎች እንዲዘጋጁና አንዲሰጡ በማድረግ የስልጠና ሂደቱን ያስፈፅማል ይመራል፣

ውጤት 6፡ የዴስኩን የአሠራር ሥርዓት እንዲሻሻል ማድረግ


 የዴስኩን ጠንካራና ደካማ ጎን በማጥናት ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ጥራቱን የጠበቀ አሰራር እንዲኖር ያደርጋል፣
 በዴስኩ የሚገጥሙ ተግዳራቶችን በመለየት ችግር ፈቺ ጥናቶችን ያካሂዳል፣
 የዴስኩ አፈጻጸም ስርዓት አዳዲስ የአሰራር ዘዴዎችን የተከተለ እንዲሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተሞክሮዎችን
በመቀመር የአሰራር ስልት ይቀይሳል፣ ተግባራዊ እንዲሆን ያደርጋል፣
 የተገልጋዮች እርካታና ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት እንዲካሄድ በማድረግ አሰራሩ የሚሻሻልበትን ሁኔታ ይቀይሳል፣
 የዴስኩን ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያዘጋጃል፣ ያቀርባል፡፡

III. የሥራው ባህሪ መግለጫዎች


3.1. የሥራ ውስብስብነት

 ሥራው የዴስኩን ሥራ ማቀድ፣ መምራት፣ ማስተባበርን፣ በዴስኩ የሚዘጋጁ የተለያዩ የአረንጓዴና አካባቢ

4
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

ጥበቃ መሠረተ ልማት ኮዶችና ስታንዳርዶች ጥናቶችና የሚዘጋጁ ስትራቴጂዎች በመገምገም ማስወሰን፣ ለሚዘጋጁ
ዲዛይኖች ቅድመ ዲዛይን የሚሰሩ የአዋጭነት ጥናቶችን መገምገምና ማስጽደቅ፣ የሚዘጋጁ የመሠረተ ልማት
የግንባታ ዲዛይኖችን ከመሰረተ ልማት ዓይነትና ከከተሞች ደረጃ አንጻር አግባብነቱን መርምሮ ማስወሰን፣ በከተሞች
ለሚገነቡ መሰረተ ልማቶች የስራና የአገልግሎት የጥራት ደረጃ ለመወሰን የሚዘጋጁ ሰነዶችን መርምሮ ማስጽደቅን፣
የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማቶች ስታንዳርዶች እንዲዘጋጁ ማድረግ፣ መገምገምና ማስጸደቅ፤ ከሌሎች
አካላት የሚቀርቡ የዲዛይን ዝግጅትና የግንባታ አፈጻጸም ድጋፍ ጥያቄዎች መርምሮ መደገፍን፣ የስታንዳርድ ዓለም
አቀፍ ተሞክሮ መቀመርና ከሀራዊ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ እንዲተገበሩ ማድረግ፣ የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ
መሠረተ ልማቶች የግብዓት ዓይነቶችን መለየትና የጥራት ደረጃ እንዲዘጋጅ ማድረግ፣ መገምገምና ማጸደቅ፣
የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሠረተ ልማቶች የግንባታ አተገባበር ስርዓት መፍጠር መደገፍና መከታተል፣ በዴስኩ
የሚሰሩ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸውን ስራዎችን መወሰን፣ የዴስኩ የአፈጻጸም ስርዓት አዳዲስ የአሰራር ዘዴዎችን
የተከተለና የተገልጋዮች እርካታና ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት እንዲካሄድ በማድረግ የአሰራር ስልት በመቀየስ ተግባራዊ
እንዲሆን ማድረግ የሚጠይቅ ነው፡፡
 የሚዘጋጁ የአረንጓዴና አካባቢ ጥበቃ መሰረተ ልማት ጥናቶች ውስብስብነት የአካበቢና ማህበራዊ

ተጽዕኖ የሚያከትሉ መሆናቸው፣ የሚዘጋጁ ሞዴል ዲዛይኖች ብዙ መስፈርቶችን የሚጠቀሙና


የግንባታ ጥራት ላይ ጉድለት ሊያስከትሉ የሚችሉ መሆናቸው፣ የሚዘጋጁ ስታንዳርዶች ደረጃውን
የጠበቀ አለመሆንና አገሪቷ ከምትፈልገው የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ አለመሆን፣ ለመሰረተ
ልማቶች የሚወጡ የጥራት ደረጃዎች የሚፈለገውን ጥራት ያለማስጠበቅና ቅሬታ ማስነሳት፣
የመሰረተ ልማት ዓይነቶች በርካታ በመሆናቸው ከግንባታ ክትትልና ድጋፍ እንዲሁም ከአዋጭነት
ጥናት ግምገማ አኳያ ዘርፈ ብዙ ክህሎት የሚፈልጉ መሆን፣ በዘርፉ የሚገኘውን የተለያየ የውጭ
ሀገራት የፖሊሲ፣ ስትራቴጂና ሕግጋት ተሞክሮዎች ወደ አገራዊ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር
አለመጣጣም፣ የአፈጻጸም ሪፖርቶች ከአስፈጻሚ አካላት ወቅቱን ጠብቆ አለመቅረብ፣ የአፈጻጸም
መረጃዎች ተሟልተውና ተደራጅተው አለመገኘት፣ በፈጸሚዎች መካከል በደረጃዎችና
ስታንዳርዶች ላይ የግንዛቤና የእውቀት ክፍተት መኖር በደረጃዎች ላይ ያልተካተቱ ቴክኒካል ጉዳዮች
ማጋጠም የሚያጋጥሙ ችግሮች ሲሆኑ፤
 የሚከናወኑ ጥናቶች በአሳታፊነትና የተጠናከረ ግብረመልስ በማሰባሰብና በማስተካከል፣የሚዘጋጁ

ዲዛይኖች ላይ መስፈርቶችን ጥራት በማሳደግና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍና በማስተካከል፣


የሚዘጋጁ ስታንዳርዶች የሀገራዊ ዕድገትን በሚመጥን መልኩ እንዲሆኑ በጥልቀት በመፈተሸና
አዘጋጅቶ፣ በማላመድ፣ የግንባታ ጥራት ለማስጠበቅ የሚያስፈልጉ የግብዓት፣ የአጠቃቀምና

5
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

ዲስፕሊን እንዲጎለብትና ደረጃ እንዲወጣ በማድረግ፣ የሚገነቡ መሰረተ ልማቶች የአካባቢና


ማህበራዊ ደህንነትን ያረጋገጡ እንዲሆኑ በመስራት፤የአፈጻጸም ሪፖርቶች ከክልሎችና ሌሎች
ባለድርሻ አካላት በወቅቱ እንዲደርሱ ከሚመለከታቸው አመራሮች ተነጋግሮ በመፍታት፤ ለታዩ
የአፈጻጸም ክፍተቶች ግብረመልስ በመስጠት፤ በፈፃሚዎች የተሻለ የሰነዶች ዝግጅትና ትግበራ እና
የደረጃዎችና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ስርዓት እንዲኖር በማስቻል፣ ግንዛቤ ማስጨበጫና በአተገባበር
የታዩ የአቅምና አፈፃፀም ክፍተቶችን ሊሞሉ የሚችሉ የስልጠና ፕሮግራሞች በማዘጋጀት፣
የፈፃሚዎች አቅምና ግንዛቤ በማሳደግ፤ ተሞክሮዎችን በማፈላለግ ከስራዉ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር
በማጣጣም ተግባራዊ በማድረግ ይፈታሉ፡፡

3.2. ራስን ችሎ መስራት


3.2.1 ሥራው የሚከናወንበት አግባብ
 ሥራው ሀገር አቀፍ ግቦችን፣ ተልእኮዎችን፣ አጠቃላይ ፖሊሲዎችን ስትራቴጂዎችን፤
ፕሮግራሞችን፣ ልዩ ልዩ አዋጆችን፣ የማስፈጸሚያ ደንቦችንና መመሪያዎችን መሠረት በማድረግ
ይከናወናል፡፡

3.2.2 ሥራው የሚጠይቀው የክትትልና ድጋፍ ደረጃ


 ሥራው ከአጠቃላይ ከሀገሪቱ ፖሊሲ፣ ከዘርፉ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች የተቋሙ

ስትራቴጂያዊ ዕቅድ እና የአሰራር ስርአቶች ግቦች ከማሳካት አንጻር ይገመገማል፡፡

3.3. ተጠያቂነት
3.3.1 ተጠያቂነት ለሥራ ውጤት /Responsibility for Impact/፣
 ሥራው ለከተማ መሰረተ ልማቶች የከተሞችን ደረጃ በሚመጥን መልኩ ጥራት ያለው ዲዛይን

እንዲዘጋጅ ማድረግ፣ አዳዲስ የመሰረተ ልማት የስታንዳርዶች እንዲዘጋጁ ማድረግ፣ በውጭ አቅም
ለሚዘጋጁ ሰነዶች/ስታንዳርዶች/ የአማካሪ ግዥ ሰነዶች ማዘጋጀትና ሰነዶችን መገምገምና
ግብረመልስ መስጠት፣ የግንባታ ደረጃውን ጥራት ለማስጠበቅ ጥናት እንዲካሄድ በማድረግ ጥራት ያለው ደረጃ
ማውጣትን፣ የከተማ መሰረተ ልማቶች የጥራት ስታንዳርድ በተመለከተ ጥናት ማድረግና እንዲሻሻሉ

ማድረግ፤ ጥናቱን በበላይነት መምራት መከታተልና መገምገምን፣ የተዘጋጁና የተሻሻሉ የስታንዳርድ


ሰነዶች ከአገራዊና ከዘርፉ ፖሊሲና ስትራቴጂ ጋር የተገናዘበና የተጣጣመ መሆኑን መገምገምና
ማረጋገጥን፣ ከአፈጻጸም ክትትል ቡድኑና ከአስፈጻሚ አካላት የቀረቡ የአፈጻጸም ሪፖርቶችን
መገምገምንና ለታዩ የአፈጻጸም ክፍተቶች ግብረመልስ መስጠት፣ የወጡ የመሰረተ ልማት
6
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

ፖሊሲዎች፣ ሕጐች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በተግባር ያስከተሉትን ለውጥ መገምገም፣ የተለያዩ


ሀገራትን ተሞክሮ ከተጨባጭ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉትን መንገድ መቀየስን
ይጠይቃል፣ እነዚህ ተግባሮች በአግባቡ ባይከናወኑ የከተማ መሰረተ ልማት አቅርቦቱ ወጥ በሆነ
ስታንዳርድ ስርዓት እንዳይመራ ያደርጋል፣ ከፍተኛ የመሰረተ ልማት ሀብት ብክነት
ያከትላል፣የከተሞች ለአየር ብክለት እንዲጋለጡ ያደርጋል፣ የመሰረተ ልማት አቅርቦት እጥረትን
ያስከትላል እና የተቋሙ ግብ እንዳይሳካ ያደርጋል፡፡

3.3.2 ተጠያቂነት ለሚስጥራዊ መረጃ፣

 ያልጸደቁና በረቂቅ ሂደት የሚገኙ የደረጃና ስታንዳርድ ዝግጅት በሚስጥር መያዝ ወይም መጠበቅ
ያለባቸው ሲሆን እነዚህን ሰነዶች በማይመለከታቸው እጅ ቢገቡ በተቋሙ ላይ ተአማኒነትን ያሳጣል፡፡

3.4. ፈጠራ
 ሥራው በዘርፉ ለሚዘጋጁ አዋጅና ደንቦች ዝግጅት የሚያስፈልጉ ሀሳቦችን ማመንጨት፣ የሚዘጋጁ
ስታንዳርዶች ሀገራዊ ተጨባጭን ያገናዘቡ እንዲሆኑ ማሰላሰልንና ሲተገበሩ በማህበረሰብ ላይ
የሚያሳድሩን ተጽዕኖ አሰላለስሎ ማሰራት፣ የዲዛይን ዝግጅቶች አዳዲስ አሰራር እንዲያካትቱ
ማድረግና አንደምታቸውን ማጤን የሚፈልግ መሆኑ፣ የሚደረጉ ጥናቶች አዳዲስ ዕይታዎችን
እንዲካትቱ ማድረግና በማሰላሰል ገምግሞ ግብረመልስ መስጠትን፣ ተሞክሮዎችን በመቀመር እና
ክፍተቶች ላይ ጥናት በማድረግ አዳዲስ ወይም የተሻሻሉ የስታንዳርዶች የአሰራር ስርአትን
ማዘጋጀትና ማሻሻል ይጠይቃል፣
3.5. የሥራ ግንኙነት /Work Communication/
3.5.1. የግንኙነት ደረጃ

 ሥራው ከውስጥ ከቅርብ ኃላፊውና ከክፍሉ ባለሙያዎች፣ ከሌሎች ሥራ ክፍሎች ባለሙያዎችና


ዴስኮች፣ ከተቋሙ የበላይ ኃላፊዎች፣ ከውጭ ደግሞ ከአማካሪዎች፣ ከሥራ ተቋራጮች ከሙያ
ማሕበራት፣ ከክልሎች፣ ከግሉ ዘርፍ፣ ከተማ አስተዳደሮች እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላትና ተቋማት
ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር ግንኙነት ማድረግን ይጠይቃል፡፡

3.5.2. የግንኙነቱ ዓላማ

7
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

 ሥራው መመሪያ ለመቀበል፣ ውሳኔ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ለማማከርና ለመወያየት፤ በጋራ የሚሰሩ
ሥራዎችን ለመወሰን፣ የታቀዱ ስራዎችን በተያዘላቸዉ ጊዜ መፈጸማቸዉን ለመከታተል
ለመገምገም፣ በአሰራር ችግሮች ዙሪያ ለመወያየት፣ ለተዘጋጁ ረቂቅ ሰነዶች ግብዓት ለማሰባሰብና
ለማፀደቅ፣ በስራ ላይ በዋሉ ሰነዶች አፈጻጸም ዙሪያ ማብራሪያ ለመስጠትና ለማስረዳት፣ የግሉ
ሴክተር በግልና በመንግስት አጋርነት እንዲሳተፍ ለማመቻቸት፣ የስልጠና ሂደቶችን ለመከታተልና
አፈጻፀሙን ለመገምገም ነው፡፡

3.5.3. የግንኙነቱ ድግግሞሽ


 ሥራው ከሥራ ጊዜው 40 በመቶ የሥራ ግንኙነት ማድረግን ይጠይቃል፡፡
3.6. ኃላፊነት
3.6.1. ኃላፊነት ለሰው ሀብት
3.6.1.1 በኃላፊነት የሚመራቸው ሠራተኞች ብዛት
 በሥራ ክፍሉ 8 ባለሙያዎች ይገኛሉ፡፡

3.6.1.2 የኃላፊነት አይነትና ደረጃ


 የማስተባበር፣ የመምራት፣ የመከታተል እና የመገምገና ኃላፊነት አለበት፡፡

3.6.2. ኃላፊነት ለንዋይ


 የለበትም፡፡
3.6.3. ኃላፊነት ለንብረት
 ሥራውን ለማከናወን ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ ኮምፒዩተር(ዴስክ ቶፕና ላፕቶፕ)፣ ፕሪንተር፣ ፋክስ፣ የፋይል ካቢኔት እስከ
ብር ሁለት መቶ ሺህ(200,000.00) የሚገመት ንብረት የመረከብ ኃላፊነት አለበት፡፡

3.7. ጥረት
3.7.1. የአዕምሮ ጥረት

 ሥራው ለከተማ መሰረተ ልማቶች የከተሞችን ደረጃ በሚመጥን መልኩ ጥራት ያለው ዲዛይን እንዲዘጋጅ ማድረግን፣
አዳዲስ የመሰረተ ልማት የስታንዳርዶች እንዲዘጋጁ ማድረግ፣ የግንባታ ደረጃውን ጥራት ለማስጠበቅ ጥናት
እንዲካሄድ በማድረግ ጥራት ያለው ደረጃ ማውጣትን፣ የከተማ መሰረተ ልማቶች ስታንዳርድ በተመለከተ ጥናት
ማስደረግና እንዲሻሻሉ ማድረግ፤ ጥናቱን በበላይነት መምራት መከታተልና መገምገምን፣ የተዘጋጁና የተሻሻሉ
የስታንዳርድ ሰነዶች ከአገራዊና ከዘርፉ ፖሊሲና ስትራቴጂ ጋር የተገናዘበና የተጣጣመ መሆኑን መገምገምና
ማረጋገጥን፣ ከአፈጻጸም ክትትል ቡድኑና ከአስፈጻሚ አካላት የቀረቡ የአፈጻጸም ሪፖርቶችን መገምገምንና ለታዩ
የአፈጻጸም ክፍተቶች ግብረመልስ መስጠት፣ የወጡ የመሰረተ ልማት ፖሊሲዎች፣ ሕጐች፣ ደንቦችና መመሪያዎች
በተግባር ያስከተሉትን ለውጥ መገምገም፣ የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮ ከተጨባጭ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆኑ

8
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

የሚችሉትን መንገድ መቀየስ አዕምሮ የሚያደክሙ ሲሆኑ፣ ይህም ከቀን የሥራ ጊዜው 75 በመቶ ይወስዳል፡፡

3.7.2. ስነልቦናዊ ጥረት


 ሥራው ከባለድርሻ እና አስፈጻሚ አካላት ጋር በመሰረተ ልማት ስታንዳርድ ዝግጅትና አፈጻጸም ስራዎች በምክክር
መድረክ በሚፈጠሩ ክርክሮች እና የሀሳብ አለመግባባቶች ስነልቦናን የሚፈታተኑ ሲሆኑ እነዚህን በትዕግስትና በተረጋጋ
ስሜት ተቋቁሞ ሥራዎችን ውጤታማ ማድረግ ይጠይቃል፡፡
3.7.3. የዕይታ ጥረት፣
 ሥራው የዋና ስራ አስፈጻሚውን ሥራ ማቀድ፣ በክፍሉ የሚዘጋጁ የሞዴል ዲዛይኖችን በትኩረት ማስተንተንን፣
የተከናወኑ የጥናት ሰነዶችን አንብቦ ማረምና መገምገምን፣ በባለሙያዎች የተዘጋጁ የመሰረተ ልማት ስታንዳርድ
ሰነዶች መገምገምን፣ የስልጠና ማንዋሎችን ዝግጅት፣ የክትትልና ድጋፍ ሪፖርቶች እና ሌሎች ሥራዎችን
መገምገምና ማረም፣ የዘርፉን አዋጅና ደንብ ዝግጅት ሐሳቦችን ለማመንጨትና የዋና ስራ አስፈጻሚውን ጠንካራና
ደካማ ጎን ለማጥናት የተለያዩ ማጣቀሻዎችን ማገናዘብ፣ የዋና ስራ አስፈጻሚውን የተጠቃለለ ሪፖርት ማዘጋጀትና
በኮምፒዩተር መጻፍ እይታን የሚያደክም ሲሆን ይህም ከሥራ ጊዜው 45 በመቶ ይሆናል፡፡
3.7.4. የአካል ጥረት
 ሥራው 70 % በመቀመጥ፣ 30 % በመንቀሳቀስ የሚከናወን ይሆናል፡፡
3.8. የሥራ ሁኔታ
3.8.1. ሥጋትና አደጋ
 የለበትም፡፡
3.8.2. የሥራ አካባቢ ሁኔታ
 የለበትም፡፡
3.9. እውቀትና ክህሎት፣
3.9.1. ትምህርት
የትምህርት ደረጃ የትምህርት አይነት
ኢኮኖሚክስ፤ በከተማስራ አመራር፣ ማናጅመንት፣ በአርክቴክቸር፣ በሲቪል ኢንጂነሪንግ፣
በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ማኔጅመነት፣ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት፣ኢንቫይሮንመንት፣
በተፈጥሮ ሀብት አያያዝና አስተዳድር፤አግሪካልቸራል ኢንጀር፣አካባቢ ሳይንስ፣ ኢንቫሮመንታል
የመጀመሪያ ዲግሪ ኢንጂነር፣ ኢኮሎጅካል ሳይንስ ወይም ደን ሳይንስ፣ በአርባን ፎርስትሪ ወይም በዕጽዋት ሳይንስ
ወይም በከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት፣

3.9.2. ሥራውን ለመጀመር የሚያስፈልግ የሥራ ልምድ


የሥራ ልምዱ ለማግኘት የሚጠይቀው ጊዜ ልምዱ የሚገኝበት የሥራ ዓይነት
9 ዓመት ቀጥታና አግባብነት ያለው የስራ ልምድ

9
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ

የሥራ ትንተና ባለሙያ ሥም ፊርማ ቀን

የሥራ ዝርዝሩን ያጸደቀው የኃላፊው ሥም የሥራ መደቡ መጠሪያ ፊርማ ቀን

10

You might also like