Professional Documents
Culture Documents
( ) Ethiopian Human Rights Council (Ehrco)
( ) Ethiopian Human Rights Council (Ehrco)
1 https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/card/5EhBh4Xf5z/
2 https://www.usaid.gov/news-information/press-releases/may-03-2023-pause-us-food-aid-tigray-ethiopia
3 https://www.wfp.org/news/wfp-statement-diversion-food-aid-ethiopia-0
4https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia?ct=t%28EMAIL_CAMPAIGN_11_May_2023_COPY_04%29&goal=0_82a80d2ffe-
b21fbbd1d1-109596177
የኢሰመጉ ጥሪ፡
በትግራይ ክልል የተከሰተውን የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ችግርና ከፍተኛ የሆነ የምግብና የመድሀኒት አቅርቦት እጥረት ተከትሎ
ለኢሰባዊ ቀውስ ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ሴቶችን፣ ህፃናትን፣ አካል ጉዳተኘኞችን፣ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን እና
አረጋውያንን ጨምሮ ልዩና አፋጣኝ ትኩረት በመስጠት ነፍስ አድን የሆኑ የምግብና መድሀኒት እርዳታዎችን የክልሉ ጊዜያዊ
አስተዳደር፣ የፌደራል መንግስትና ሌሎች ድጋፍ ሰጪ አካላት እንዲያቀርቡ፣
ወደ ትግራይ ክልል የሚገቡ ሰብዓዊ እርዳታዎች ምግብን እና መድሀኒትን ጨምሮ በተገቢው መንገድ ለተጎጀዎች እና እርዳታው
ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች እንዲደርስ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በሰብዓዊ እርዳታ ቁሳቁሶች ላይ የሚደረጉ ስርቆቶችን እና ህገ-ወጥ
ንግዶችን እንዲቆጣጠር እና በእዚህም የፌደራል መንግስቱ የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ፣
በትግራይ ክልል ዋነኛ ሰብዓዊ ድጋፍ የሚያቀርቡት የአሜሪካ ኤጀንሲ ለዓለም አቀፍ ልማት (USAID) እና የዓለም አቀፍ የምግብ
ፕሮግራም (WFP) ድጋፋቸውን እንዲያቆሙ ምክንየት የሆነውን የሰብዓዊ እርዳታ ቁሳቁሶች ስርቆት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር
እንዲሁም የፌደራል መንግስት ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ድርጊቱን የፈጸሙ አካላትን በህግ እንዲጠይቁ እና በሰብዓዊ እርዳታ
ቁሳቁሶች ላይ ተገቢውን በቂ ቁጥጥር እንዲያደርጉ፣
በትግራይ ክልል ከምግብ እጥረት ጋር ተያይዞ ለተከሰተው ከፍተኛ ርሀብ የፌደራል መንግስት እንዲሁም የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር
ተገቢውን በቂ ትኩረት በመስጠት ካስከተለው ጉዳት የከፋ ጉዳትን እንዳያደርስ እና ከቁጥጥር ውጪ እንዳይወጣ ተቀናጅተው
በመስራት አፋጣኝ ምላሽ እንደሰጡ፣
ሰዎች ምግብ የማግኘት መብት እንዳላቸውና የእዚህም መብት ዝቅተኛ ዋና ግዴታ ከርሀብ የመጠበቅ መብት መሆኑን በመረዳት
መንግስት ይህንን መብት የማሟላት ተቀዳሚ ኃላፊነቱን እንዲወጣና በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የፌደራል መንግስት
ድጋፍ ሰጪ የሆኑትን USAID እና WFP በማስተባበር ቀድሞ ከሚሰጠው የተሻለ፣ ወቅቱን እና ነባራዊ ሁኔታን ከግምት ያስገባ
ድጋፍ እንዲሰጡ በማስተባበር ረገድ የበኩሉን ግዴታ እንዲወጣ፣
የአሜሪካ ኤጀንሲ ለዓለም አቀፍ ልማት (USAID) እና የዓለም አቀፍ የምግብ ፕሮግራም (WFP) በትግራይ ክልል ያቋረጡትን
የምግብ እና የመድሀኒት ድጋፍ እየደረሰ ያለውን ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ ከግምት ውስጥ በማስገባት እንዲያስጀምሩ፣
አገር አቀፍ፣ አህጉር አቀፍና ዓለም አቀፍ የሆኑ ድጋፍ ሰጪ ተቋማት በትግራይ ክልል ያለው ከፍተኛ የምግብና መድሀኒት እጥረት
እያስከተለ ያለው ጉዳት ከፍተኛና አጣዳፊ መሆኑን በመረዳት አቅም በፈቀደ መጠን እርዳታዎችን በፍጥነት እንዲያቀርቡ እና
የፌደራሉም መንግስት ይህንን እንዲያመቻች ኢሰመጉ ይህን አስቸኳይ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
በመጨረሻም ኢሰመጉ በትግራይ ክልል ውስጥ የተፈጸሙ ሌሎች የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን የክትትልና የምርመራ ስራ ለመስረት
እንዲሁም ቀድሞ የነበረውን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዳግም ለመክፈት በዝግጅት ላይ መሆኑን በእዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ ይወዳል፡፡