You are on page 1of 1

ለምን አትሰግድም ወንድሜ?

ለምን አትሰግጂም እህቴ?


በዱንያ_ላይ፦

1• እስካልሰግድክ ድረስ ከእድሜህ ላይ በረካ ይነሳል ...


2• እስካልሰገድክ ድረሰ ከፊትህ ላይ ኑር ይገፈፋል...
3• እስካልሰገድክ ድረስ ምትሰራው ስራ ሁሉ ተቀባይነት የለውም.
4• እስካልሰገድክ ድረስ ዱዓህ ተሰሚነት አያገኝም.
5• እሰካልሰገድክ ድረስ ሌሎች ሚያደርጉልህ ዱዓም አይጠቅምህም.

ስትሞት፦

1• እስካለሰገድክ ድረስ እማትረባና የተዋረድክ ሆነህ ትሞታለህ.


2• እስካልሰገድክ ድረስ እንደተራብክ ትሞታለህ.
3• እሰካለሰገድክ ድረስ እንደተጠማህ ትሞታለህ. የባህርን ውሃ እንዳለ ብትጠጣ ጥምህን አይቆትጥልህም.

ቀብር_ውስጥ፦

1• እስካለሰገድክ ድረስ ጎንና ጎንህ እስኪተላልፈ ድረስ ቀብርህን አሏህ ያጠብብሃል.


2• እስካለሰገድክ ድረስ ቀብርህ ውስጥ እሳት ተቀጣጥሎብህ ነጋ ጠባ ትሰቃያለህ.
3• እስካለሰገድክ ድረስ በቀን አምስት ጊዜ ከእባብ ጋር ቀጠሮ ይኖርሃል ! የፈጅርን ሰላት ባለመስገድህ
ሲያሰቃይህ ዙሁር ይደረሳል፤የዙሁርን ሰላት ባለመሰገድህ ሲያሰቃይህ አስር ይደርሳል ፤እንደዚህ እያለ
ስቃይህ ይቀጥላል (አንድ ጊዜ ምትመታው እሰከ 70 ክንደ ያህለ መሬት ውስጥ ያሰምጠሃል)..
የቂያማለት፦

1• እስካለሰገድክ ድረስ ወደ ጀሃነም እሳት . በፊትህ እየተጎተትክ ትወሰዳለህ .


2• እሰካልሰገድክ ድረስ አሏህ ፊት ቆመህ ስትተሳሰብ አሏህ (ሱ,ወ)
በቁጣ አይን ይመለከትህና ፊትህ ላይ ያለ ስጋ ይነሳለ.
3• እስካልሰገድክ ድረስ ከአሏህ (ሱ.ወ) ጋር የምትተሳሰበው ሂሳብ የከፋ ይሆነንና ወደ ጀሃነም እሳት
እንደትወረወር ይደረጋል .
ወንድሜ አሁንም አትሰግድም ??
እህቴ አሁንም አትሰግጂም ??
በሂወት ያሉና የሌሉትንም ወንድምና እህቶቻችንንም ወንጀል ማርልን!!!

You might also like