You are on page 1of 4

(ተለይ ) (3/21/2024)

ተለይ፥
ዘፍጥረት 12
¹ እግዚአብሔርም አብራምን አለው፦ ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።
² ታላቅ ሕዝብም አደርግሃለሁ፥ እባርክሃለሁ፥ ስምህንም አከብረዋለሁ፤ ለበረከትም ሁን፤
³ የሚባርኩህንም እባርካለሁ፥ የሚረግሙህንም እረግማለሁ፤ የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ።
⁴ አብራምም እግዚአብሔር እንደ ነገረው ሄደ፤ ሎጥም ከእርሱ ጋር ሄደ፤ አብራምም ከካራን በወጣ ጊዜ የሰባ አምስት ዓመት ሰው ነበረ።

* በዚህ ክፍል እግዚአብሔር አብርሃምን ተለይተህ ውጣ የሚልባቸው ዝርዝር ሁነቶችን ስንመለከት፥ ከምን ከምንድነው የወጣው ?

# መውጣት /መለየት/ - (1)

1, - ከአገርህ ተለይተህ ውጣ ፥ አገር ማለት ፦


ሀ ከቋንቋ ነው/ Language /
ለ ከባህል ነው /Culture/
ሐ ከልማድ ነው /Habit /
መ ማህበራዊ ኑሮ /Social life /
ሠ ከኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ /Economically and political integration/ ውህደት ወይም ግንኙነት ነው ።

2, - ከዘመዶችህ ተለይተህ ውጣ ፥ ዘመድ ማለት፦


- ወላጅ አባትና እናት
- አብሮ የተወለዱት ወንድምና እህት
- ከአባት ወይም ከእናት ጋር የተወለዱት አጎትና አክስት
- ወገን ፣ ነገድ ፣ በስነ-ፍጥረቱና ትውልዱ በስሙም አንድ አይነት የሆነ ማለት ነው ።

3, - ከአባትህ ቤት ተለይተህ ውጣ የሚል ነው ፦


- ከአባትህ ቤት ውጣ ስል ከላይ ከተመለከትነው ውስጥ አባት ፣እናት ፣ ወንድም ፣ እህት ፣ አጎት ፣ አክስት እና አያት የሚባሉትን ያጠቃልላል ።

# አብረሃም እንግዲህ እነዚህን ነገሮች በፍጹም መታመን ተግባራዊ ካደረገ እግዚአብሔርም ህይወቱን ኑሮውን ስራውን ሁሉም ነገሩን
እንደሚቀይርለት ቃልኪዳን ስገባ በዚህ ክፍል እናያለን ፥

ቃልኪዳን /በረከት / (1)

- ታላቅ ሕዝብ አደርግሃለሁ


- እባርክሃለሁ
- ስምህን አከብረዋለሁ
- ለበረከት ሁን
- የሚባርኩህን እባርካለሁ
- የሚረግሙህን እረግማለሁ
-የምድር ነገዶች በእንተ ይባረካሉ
ብሎ እግዚአብሔር አብረሃምን ብቻውን ሕዝብ ወይም አገር እንደሚያደርግ በራሱ ተማምኖ ቃልኪዳን ከአብርሃም ጋር ሲያደርግ እናያለን። ተስፋ
ቆርጦ ዕድሜዬም አርጅቷል ሳራም ከእንግዲህ ልጅ ልትወልድልኝ አትችልም ፤ ሀብትና ንብረቶቼን የሚወርሰው የደማስቆ ሰው አልአዛር ነው ሁሉን
ነገር አክትሟል ብሎ በተቀመጠው ሰዓት መጣና የቃልኪዳንና የበረከት አምላክ ተስፋውን አለመለመ። ሀለ ሉያ አሜን !!

እግዚአብሔር የሰው ልጆችን ለመባረክ የነበረው የመጀመሪያው ሀሳብ እንደገና በአብርሃምና በዘሮቹ ፍጻሜ እንደሚያገኝ ያመለክታል ።
አብረሃም እግዚአብሔር እንዳዘዘው ወጣ ይህ የሕዝቦች አባት ከእምነት የተነሳ ለእግዚአብሔር ያሳየው ታዛዥነት በህይወቱ ሁሉ የሚታይ ልዩ
ባህሪይ ነው ።
አብረሃም ከሎጥ ተለየ ፥

መውጣት /መለየት/ (2)


አብራምም ሎጥን አለው እኛ ወንድማማች ነንና ፥ በእኔና በአንተ ፣ በእረኞቼና በእረኞችህ መካከል ጠብ እንዳይሆን እለምንሃለሁ ። ምድር ሁሉ
በፊትህ አይደለችምን ? ከእኔ ትለይ ዘንድ እለምንሃለሁ ፤ አንተ ግራውን ብትወስድ እኔ ወደ ቀኝ እሄዳለሁ ፤ አንተ ቀኙን ብትወስድ እኔ ወደ ግራ
እሄዳለሁ ። ሎጥም አይኑን አነሳ በዮርዳኖስ ዙሪያ ያለውን አገር ሁሉ ውሃ የሞላበት መሆኑን አየ ፤ እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን ከማጥፋቱ
አስቀድሞ እስከ ዞአር ድረስ እንደእግዚአብሔር ገነት በግብፅ ምድር አምሳል ነበር ። ሎጥም በዮርዳኖስ ዙሪያ ያለውን አገር ሁሉ መረጠ ፤
ሎጥም ወደ ምስራቅ ተጓዘ አንዱም ከሌላው እርስበርሳቸው ተለያዩ ።
ኦ/ዘፍጥረት 13:8-11

# አብራምም ዘወትር ቸር ስለነበር ደስ ያሰኘውን መርጦ እንድወስድ ምርጫውን ለሎጥ ሰጠ ፤ ይህንንም ያደረገው እግዚአብሔር ካልባረከው
በቀር ሰው ሀብትም ሆነ ደስታ ሠላምም ማግኘት እንደማይችል ስለተረዳ ነው ።
ኦ/ዘፍጥረት 14:22-24

ቃልኪዳን በረከት (2)


፨ ሎጥም ከተለየው በኋላ እግዚአብሔር አብራምን አለው ፦ አይንህን አሰሳና አንተ ካለህበት ስፍራ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ ወደ ምስራቅና ወደ
ምዕራብ ዕይ ፤
- የምታያትን ምድር ለአንተና ለዘርህ ለዘላለም እሰጣለሁና
- ዘርህንም እንደ ምድር አሸዋ አደርጋለሁ ፤ የምድርን አሸዋ ይቆጥር ዘንድ የሚችል ሰው ብኖር ዘርህ ደግሞ ይቆጠራል
- ተነሳ በምድር በርዝመቷም በስፋቷም ሂድ
- እርሷንም ለአንተ እሰጣለሁ ።
ኦ/ዘፍጥረት 13:14-17

ሎጥና አብራም የተለያየ አመለካከት ያላቸው ዘመዳሞች ግን የተለያዩ ሰዎች ናቸው ። ሎጥ ስስታም እና የራሱን ፍላጎት ብቻ ለሟሟላት
የሚሯሯጥ የነበረ ስሆን ፤ አብራም ደግሞ በእግዚአብሔር ፍቃድና ምርት የሚመላለስ የተባረከ ሰው ነበረ ።

ከዚህ ቀጥሎ ከሎጥ መለየትና ከሁለተኛ ቃልኪዳን እስከ ሦስተኛው መለየትና ቃልኪዳን ድረስ ያለው ፦

- የአብራም ወደ አጋር መግባትና የእስማኤል መወለድ 16:4/15


- የግርዘት ቃልኪዳን 17:10-14
- የአብራም የሶራ ስማቸው መቀየር 17:5/15
- የእስማኤል መወለድ 17:19
- የአብርሃም እና በቤቱ ያሉት ሰዎች መገረዝ 17:23-27
- ወደ ሰዶምና ገሞራ የተላኩ የአብርሃም እንግዶች 18:1-2
- ጻድቁን ከኃጥአተኛ ጋር ታጠፋለህ? የአብርሃም ሙግት 18:23-33
- የሎጥና ቤተሰቡ ወደ ሎዛ መሸሽ 19:22-23
- የሰዶምና ገሞራ በእሳት ዲን መጥፋት 19:2
- የሎጥ ሚስት ጨው ሀውልት መሆን 19:26
- የሎጥ ሴት ልጆች ከእርሱ ጋር መተኛትና ልጆች መውለዳቸው 19:31-38
- የአብርሃም ለአቤመለክ ቤት ወደ እግዚአብሔር መፀለይ 20:17
- የሣራ መፀነስና የይስሐቅ መወለድ 21:1-3
የአጋር ከልጇ ጋር ወደ ምድረበዳ መሰደድ 21:14 19
በጥቂቱ ይህንን ይመስላል ።

አብረሃም ከሎሌዎቹ ወይም ከአገልጋዮቹ ተለየ ፦

ከእነዚህም ነገሮች በኋላ እግዚአብሔር አብረሃምን ፈተነው ፥ እንዲህም አለው ፦ አብረሃም ሆይ ። አብረሃምም እነሆ አለሁ አለ። የሚትወደውን
አንድ ልጅህን ይዘህ ወደ ሞሪያ ተራራ ሂድ ። እኔም በሚነግርህ በአአድ ተራራ ላይ በዚያ መስዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ ። አብረሃምም በማለዳ
ተነስቶ አህያውን ጫነ ፤ ሁለቱን ሎሌዎችና ልጁን ይስሐቅን ከእርሱ ጋር ወሰደ እንጨትም ተሰነጠቀ ፤ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ
በሶስተኛውም ቀን አብረሃም አይኑን አነሳና ቦታውን ከሩቅ አየ ። አብረሃምም ሎሌዎቹን አላቸው አህያውን ይዛችሁ እዚህ ቆዩ ። እኔና ልጄ ወደዚያ
ሄደን እንሰግዳለን ወደ እናንተም እንመለሳለን ።
ኦ/ዘፍጥረት 22:2-5

መለየት /መወጣት /(3)


በዚህ ክፍል አብረሃም አገልጋዮቹን እናንተ እዚህ ቆዩ እኔና ልጄ ግን ሄደን ለእግዚአብሔር ሠውተን እንመለሳለን ስል እንመለከታለን አብረሃም
በቀደም ከወንድሙ ልጅ ከሎጥ ጋር ወጥቶ በመካከላቸው የተፈጠረውን ነገር ያውቃል ። ምንአልባትም ይኼኛው ከዚያኛው የሚብስ እንጂ ቀላል
አይሆንም ። ምክንያቱም አብረሃም የሰማው የእግዚአብሔር ድምፅ ልጅህን ይስሐቅን ሰዋልኝ የሚል ነው ። ያንን ልያደርግ ወይም ልፈጽም
እየሄደ ነው ያለው ። በዚህ ጊዜ ታዲያ እነዚህ አገልጋዮች አብረውት ሄደው ብሆን ኖሮ በእርግጥ አብረሃም ይህንን ሲያደርግ በምን ልብ ቆሞ
ያያሉ ? ምክንያት -1, አብረሃም የሰማውን ድምፅ እነዚህ ሰዎች አልሰሙም ፥
ምክንያት -2, በስተእርጅናዋ ያም በ90 ዓመቷ የወለደችው ሣራ ይህን ጉድ ከሰማች በሕይወት የመትረፍ ዕድሏ ጠባብ ነው ፥
ምክንያት -3, አብረሃምም ዕድሜው ወደ 120ዎቹ እየገባ ስለሆነ ጃጅቷል ወይም አዕምሮው በትክክል እየሠራ አይደለም ቃዥቷል ብለው
ሊያስቡ ይችላሉ ፥

ስለዚህ በእነዚህ ምክንያቶች መስዋዕት እንዳይስተጓጎል አብረሃም ከእነዚህ ሰዎች ተለይቶ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በመፈጸም ኪዳኑን ወይም
የተስፋውን ቃል ማረጋገጥ አለበት ።

በዚህ መሀል ይስሐቅ አባቱን አንድ የሚያስደነግጥ ጥያቄ ይጠይቃል ጥያቄውም ፦


እሳትና እንጨት ይኸው አለ ፤ የመሥዋዕቱ በግ ግን ወዴት ነው ? አለ 22:8
አብረሃምም ልጄ ሆይ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው ። 22:8

ቃልኪዳን/በረከት/(3)

እግዚአብሔርም አብረሃምን ከሰማይ ለሁለተኛ ጊዜ ጠራውና እንዲህ አለው ፦


- በራሴ ማልሁ
- በእውነት በረከት እባርክሃለሁ
- ዘርህን እንደባህር ዳር አሸዋና እንደሰማይ ከዋክብት አበዛዋለሁ
- ዘርህ የጠላቶችን ደጅ ይወርሳል
- የምድር አሕዛብ ሁሉ በዘርህ ይባረካሉ
ቃለን ሰምተሃልና ።
ኦ/ዘፍጥረት 22:15-18

$ እኛስ ዛሬ የአዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች ወይም አገልጋዮች ከየት ወዴት እንውጣ ወይም ከምን እንለይ ?

""ከማያምኑት ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ ፤ ጽድቅ ከአመጽ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና ? ብርሃን ከጨለማ ጋር ምን ህብረት አለውና ?
ክርስቶስ ከበልሆር ጋር ምን መስማማት አለው ? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው ? ለእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ከጣዖት ጋር
ምን መጋጠም አለው ?
እኛ የሕያው የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ነንና እንዲሁም እግዚአብሔር ተናገረ እንዲህም ሲል፦
በእነርሱ እኖራለሁ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ ፤ አምላካቸው እሆናለሁ እነርሱም ህዝቤ ይሆናሉ ።
ስለዚህ ጌታ ፦ ከመካከላቸው ውጡና የተለያችሁ ሁኑ ረኩስንም ነገር አትንኩ ይላል ፤ ሁሉንም የሚገዛ ጌታ ፦ እኔም እቀበላችኋለሁ አባት
እሆናለሁ እናም ለእኔ ወንድ ልጆችና ሴት ልጆች ትሆናላችሁ"" ። 2ቆሮንቶስ 6:14-18

በሌላ ክፍል ደግሞ


"እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ ፤ የንጉሥ ካህናት ፤ ቅዱስ ሕዝብ ለርስቱ
የተለየ ወገን ናችሁ ።
1ጴጥሮስ 2:9
- አብረሃም ከአገር ከሕዝብ ከቋንቋ ከባህል ወዘተ ነበር የወጣው ፤
- እኔና እናንተ ግን ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን ነው የወጣነው
- አብረሃም ከሀገር ወደ ሀገር ነበር በእምነት የወጣው ፤
- እኛ ግን ከሞት ወደ ህይወት ወይም ከስኦል ወደ ገነት ነው ያፈለስነው
- አብረሃም ልጁን ይስሐቅ ነበር መሥዋዕት ያቀረበው፤
- ለእኛ ግን የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው መሥዋዕት የሆነልን ፥

በመጨረሻም እግዚአብሔር በዚህ በእላቅው ዘመን ከእኛ የሚፈልገው ነገር ብኖር በቅድስናና በጽድቅ ህይወት እንድንመላለስ ነው ። ሐዋርያው
ጳውሎስ በሮሜ ለነበሩት ቅዱሳን መልዕክት ስጽፍ እንዲህ ይላል ፦

''እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ህያው ቅዱስም መስዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ ፥
በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ ። እርሱም ለአዕምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው ። የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ
ፍጹምም የሆነ ነገር ምን እንደሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህንን አለም አትምሰሉ
። ሮሜ 12:1-2

ጌታ በነገር ሁሉ ይርዳን !! አሜን !!

አዘጋጅ አገልጋይ አስታረቀኝ ባዳነህ


አድራሻ ስ.ቁ. 0916036909
አላታ ጩኮ ከተማ መካነየሱስ ቤተክርስቲያን

You might also like