Professional Documents
Culture Documents
MOH New Duty
MOH New Duty
ቀደም ብሎ ጸድቆ እና እየተሰራበት ባለው የጤና ተቋማት ሠራተኞች የተረኝነት እና ልዩ ልዩ ጥቅማጥቅሞች ውስጥ
ያልተካተቱ አዳዲስ የጤና አገልግሎትና የትምህርት መስኮች በመከፈታቸው እና በእነዚህ የትምህርት መስኮች የሰለጠኑ
ባለሙያዎች በደንቡ ላይ ባለመካተታቸው የተነሣ ሲሰጡ የነበሩት ማትጊያዎች ባለማግኘታቸው የስራ ተነሳሽነታቸው
ከመቀሱ ባሻገር የመልካም አስተዳደር ችግር መንስኤ ሆኖ በመገኘቱ፤ በአዲስ መመሪያ ማካተት በማስፈለጉ፤
የጤና አገልግሎት ተቋማት ልዩ ልዩ የጥቅማጥቅም እና ሌሎች የማበረታቻ ዓይነቶች ውስጥ በርካታዎቹ ቀደም ሲል
በነበረው መመሪያ ያልተካተቱ በመሆናቸው እና በአሰራር ላይ ከፍተኛ ቅሬታ በመፍጠራቸው እንዲሁም በወቅቱ
የጸደቀው ማትጊያ በተወሰነ ደረጃ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ፤
መመሪያው በተዘጋጀበት ወቅት ዘርፍ ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ የሙያ ዘርፎችን በአግባቡ በመለየት በተገቢው
እና ሚዛናዊ ሆኖ ያልተካተተ በመሆኑ፤እንዲሁም የቀድሞው መመሪያ ማሻሻል በተወሰነ ደረጃ የጤና ባለሙያውን
የኢትዮጵያ ፌዳራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሉክ መንግስት የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአዋጅ ቁጥር 1097/2011 አንቀፅ
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌዎች
1. አጭር ርዕስ
ይህ ደንብ ‹‹የጤና ተቋማት ባለሙያዎችና ሠራተኞች የትርፍ ሰዓት ክፍያ እና ሌሎች ማትጊያዎች ለመወሰን
2. ትርጓሜ
1
1. “የጤና አገልግሎት ሰጪ ተቋም” ማለት በፌደራል መንግስት ስር የሚተዳደር የጤና
አገልግሎት የሚሰጥ ሆስፒታል፤ ጤና ጣቢያና ጤና ኬላ ነው፤
2. “ሠራተኛ” ማለት በጤና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ የሚሠሩ የጤና ባለሙያዎች እና ሌሎች
የአስተዳደር ሠራተኞች ማለት ነው፤
3. “የትርፍ ሰዓት አበል” ማለት በጤና አገልግሎት ተቋም የሚሰሩ የጤናው ዘርፍ ሰራተኞች ከመደበኛ
የመንግስት የሥራ ሰዓት ውጭ ለተሰጠ የትርፍ ሰዓት አገልግልት የሚፈጸም ክፍያ ማለት ነው፤
4. “ሁለት ፈረቃ” ማለት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ አመሻሹ 11፡30 እና ከአመሻሹ 11፡30 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 2፡
30 ድረስ በሁለት ፈረቃ ተከፍሎ የሚሠራበት የጊዜ ሰሌዳ ማለት ነው፤
5. "የተረኝነት አበል" ማለት በአገልግሎት ሰጪ የጤና ተቋም ውስጥ ሠራተኞች ከመደበኛ የስራ ሰዓት
ውጭ በማታ፤በሳምንት የእረፍት ቀናት ወይንም በብሄራዊ በዓላት ቀን ተረኛ ሆኖ ሲመደብ ለሰራበት
የሚከፈል የአበል አይነት ማለት ነው፤
6. “የቤት አበል” ማለት በመንግሥት የጤና ተቋማት አገልግሎት በመስጠት ላይ ለሚገኝ ሠራተኛ
የሚከፈል የመኖሪያ ቤት ክፍያ ነው፤
7. "የኃላፊነት አበል" ማለት የጤና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በአመራር ወይም በኃላፊነት የስራ ደረጃ
8. “ተጠባባቂ ተረኝነት አበል” (On-Call Payment) ማለት ለድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት ከቤት ወይም
ከመደበኛ የስራ ቦታቸው ውጭ ለሚጠሩ ስፔሻሊስትና ሰብ-ስፔሻሊስት ሐኪሞችና እና የድንገተኛ ቀዶ
ሕክምና ባለሙያዎች የሚከፈል ማለት ነው፤
9. “ምቹ ባልሆነ የስራ ቦታ የሚመደቡ ስፔሻሊስት ሃኪሞች ልዩ አበል” ማለት ደረጃው “A” “B” እና “C”
ተብሎ ስልጣን ባለው አካል ለተለዩ የሚከፈል አበል ማለት ነው፡፡
2
10. “ልዩ ክሊኒክ speciality clininc” ማለት በማስተማሪያ ሆስፒታል ውስጥ ለአገልግሎት መስጫ እና
ለመማር-ማስተማር የሚከፈቱ የተለያዩ ልዩ ክሊኒኮች እንደ የልብ፤ የኩለሊት፤ የሳንባና የመሳሰሉት
ማለት ነው፤
11. “የተጋላጭነት አበል” ማለት በጤና ተቋም ውስጥ ለህሙማን አገልግሎት በሚሰጥበት ጊዜ
በባለሙያው ወይም ሰራተኛው ላይ ይደርሳል ተብሎ ለሚታሰብ የህመም፣ የአካል ጉዳት ወይም የስነ-
ልቦና ችግር ማካካሻ ማለት ነው፤
12. “የጋራ ቅጥር” ማለት በገበያ ላይ በቀላሉ የማይገኝ እና እጥረት ያለበት ባለሙያ በሁለት ተቋማት
መካከል በሚደረግ ስምምነት መሰረት ለሁለቱም ተቋማት እንዲያገለግል ተደርጎ የሚከናወን ቅጥር
ነው፤
13. “የጤና ጣቢያ ዳይሬክተር እና ምክትል ዳይሬክተር ማለት” ማለት ሐኪም በሌለበት ጤና ጣቢያ በሃላፊነት
የሚመሩ ባለሙያ ማለት ነው፡፡
14. "ከፍተኛ ባለሙያ" ጠቅላላ ሐኪሞች እና በየደረጃ ያሉ ስፔሻሊስት ሐኪሞች ማለት ነው፤
15. "የመግቢያ ኬላ" ማለት ከውጪ ወደ አገር ውስጥና በአየርና በየብስ ወደ አገሪቱ የሚገቡ ሰዎች፤
ዕቃዎች፤ መድሃኒት፤ አስክሬን ቁጥጥር ላይ 24 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጥ ባለሙያ ማለት
ይህ ደንብ በየትኛውም ደረጃ የሚገኙና የሕክምና አገልግሎት በሚሰጡ የመንግሥት የጤና ተቋማት የመግቢያ
ኬላ ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
4. የደንቡ ዓላማ
3
2. በአደጋና በወረርሽኝ ወቅት የአካል ጉዳት ሲደርስባቸው መደገፍ እንዲሁም ሞት ለሚያጋጥማቸው
ክፍል ሁለት
1. የህክምና ጥራትን እና ተደራሽንትን ከማስጠበቅ አንፃር ማንኛውም ተቋም ተጨማሪ ባለሙያዎችን በበቂ ቁጥር
በመቅጠር በሁለት ፈረቃ የሚሰሩበት አሰራር በሁሉም የጤና ተቋማት ሥራ ላይ እንዲውል መደረግ አለበት፤
2. የትርፍ ሰዓት ምደባን አስመልክቶ ተቋሙ የሚሰጠውን አገልግሎት ግምት ውስጥ በማስገባት ሥራን ማዕከል ባደረገ
መልኩ ብቻ ተረኛን መመደብ ይችላል፤
3. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 ቢኖርም በተኝቶ ማከሚያ የሚመደቡ ነርሶች ለ 5 ተከሚዎች ከ 1 ነርስ
4. ማንኛውም የጤና ተቋም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት እስከ አመሻሹ 11፡30 ሰዓት ድረስ የሥራ ሰዓትን
5. ማንኛውም ባለሙያ ከ አመሻሹ 11፡30 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ድረስ በፈረቃ ተመድቦ ከሚጠበቅበት
ሳምንታዊ መደበኛ የመንግሥት የሥራ ሰዓት በላይ አገልግሎት ከሰጠ፤ የሠራው ትርፍ ሰዓት ብዛት በአንድ ሰዓት
የደመወዙ ስሌት ተባዝቶ በገንዘብ ይከፈለዋል፤
6. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 5 የተጠቀሰው ክፍያ በማታ ክፍለ-ጊዜ፤ ቅዳሜና እሁድና በብሔራዊ በዓላት
ተመድበው የሚሠሩ የመግቢያ ኬላ፤ የዕለት ገንዘብ ሰብሳቢና የካርድ ክፍል ሠራተኛንም ይጨምራል፤
4
ማንኛውም በሰንጠረዡ የተመለከተው የጤና ተቋም ከታች በዝርዝር በተመለከተው መሰረት የጤና ባለሙያ እንዲመደብ
ያደርጋል
2. ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት 2 1 1
5. የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት 2 1
1. ከመንግሥት የሥራ ሰዓት ውጪ ተጠባበቂ ተረኛ ሆኖ የሚመደብ ሰራተኛ ተጠባባቂ ሆኖ የሠራበት ሰዓት ብዛት
በአንድ ሰአት የደሞዙ ስሌት ተባዝቶ ይከፈለዋል፤
5
2. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 እንደተጠበ ሆኖ ተጠባባቂ ሆኖ የተመደበ ሠራተኛ በቀን የሠራው ሥራው ድምር
ከ 30% በታች ከሆነ የሚታሰበው የትርፍ ሰዓት ክፍያ የስሌቱ 30% ማነስ የለበትም፤
3. ተጠባበቂ ተረኛ ሆኖ የሚመደብ ሰራተኛ ስራ ሳይኖር ቀርቶ ካልተጠራ የተመደበበት የሥራ ሰዓት በአንድ ሰዓት
የደሞዝ ስሌት ተባዝቶ 30% ይከፈለዋል፤
4. በተጠባባቂ ተረኝነት የሚመደብ ሰራተኛ ከመንግሥት የሥራ ሰዓት ውጪ በቀን ከ 15 ሰዓት መብለጥ የለበትም፤
5. ሚኒስትሩ ከተቋሙ የሚቀርብ ጥያቄ አሳማኝ ሆኖ ከተገኘ በተጠባባቂ ተረኝነት የሚሰሩ ሌሎች ባለሞያዎችን ሊፈቅድ
ይችላል፡፡
1. የጤና አገልግሎት ለኅብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በከፍተኛ የሙያ ደረጃ ላይ ያለ
ሲኒየር ባለሙያ ወደ አመራርና ኃላፊነት ለማምጣት እንዲቻል የሚከተለው የማበረተቻ ክፍያ ተፈቅዷል።
ተ.ቁ. ኃላፊነት የጤና አገልግሎት ተቋማት
ስፔሻላይድ አጠቃላይ የመጀመሪያ ጤና
ሆስፒታል ሆሰፒታል ደረጃ ጣቢያ
ሆስፒታል
የጤና ተቋሙ ዋና ኃላፊ
1. ዋና ኤክስክዩቲቭ ዲይሬክተር/ ፕሮቮስት 2500
2. ምክትል ኤክስክዩቲቭ ዲይሬክተር/ ምክትል ፕሮቮስት 2000
3. ዋና ክሊኒካል ዲይሬክተር/ ም/ፕሮቮስት 2000
4. ዋና የትምህርት ዲይሬክተር/ ም/ፕሮቮስት 2000
5. ዋና ሥራ አስፈጻሚ 2000 1500 1300
6. ሜዲካል ዳይሬክተር 1750 1400 1200 1100
7. የጤና ጣቢያ ዳይሬክተር(ሐኪም በሌለበት) 900
8. የጤና ጣቢያ ምክትል ዳይሬክተር(ጤና መኮንን) 700
የኬዝ ቲም ኃላፊ
የድንገተኛ ክፍል 900 700 500
6
የሕክምና ክፍል ኃላፊ
11. የውስጥ ዳዌ ሕክምና ክፍል 700 500 300
12. የማህጸንና ጽንስ ሕ/ክፍል 700 500 300
13. የሕጻናት ሕክምና 700 500 300
14. የቀዶ-ጥገና ሕክምና 700 500 300
13. የአጥንት ሕክምና 700 500 300
14. የጥርስ ሕክምና 700 500 300
15 የዓይን ሕክምና 700 500 300
16 የፊዚኦቴራፒ ሕክምና 700 500 300
17 የሥነ አህምሮ ሕክምና 700 500 300
14. መድሃኒት የተለማመደ ቲቢ ሕክምና 700 500 300
15. ከአንገት በላይ ሕክምና 700 500 300
የ
17. የልብ ሕክምና 700 500 300
ኦ
20. ፎረንሲክ ሕክምና 700 500 300
የክፍል አስተባባሪ
29. የራጂ 350 300 200
30. የላቦራቶሪ 350 300 200
31. የፋርማሲ 350 300 200
32. የማዋለጃ 350 300 200
33. የሕናቶችና ሕጻናት 350 300 200
34. የ”ART” 350 300 200
7
35. ላይዘን 350 300 200
2. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 ከተዘረዘሩት የኃላፊነት ክፍያ ውጪ ሌላ የሥራ ክፍል ካለ እና አስፈላጊነቱ
በሚኒስትሩ ከታመነበት የኃላፊነት ክፍያ ሊወሰን ይችላል፤
9. የተገላጭነት አበል
1. የሥራ ጸባያቸው ተገላጭ የሚያደርጋቸው ከዲፕሎማ እስከ ማስተርስ ድግሪ ድረስ ያሉ ባለሙያዎችና ሌሎች
ሠራተኞች እንደሚከተለው የተጋላጭነት ያገኛሉ
የአስተዳደር ሰራተኞች
17.
8
ተ.ቁ ባለሙያ ወርሃዊ የተጋላጭነት ማብራሪያ
ክፍያ
1. የቀዶ ሕክምና 1838
2. የማህጸንና ጽንስ 1838
3. የአጥንት ሐኪም 1838
4. የተቀናጀ ድንገተኛ ቀዶ ጥገና ኦፍሰር 1838
5. የድንገተኛ ሕክምና ስፔሻሊስት 1838
6. የድንገተኛ ሕክምና ሐኪም 1838
7. ክሊኒካል ፓቶሎጅ 1838
8. ኦንኮሎጂስት 1838
9. የአኒስቴዥያ ስፔሻሊስት 1838
10. ፓቶሎጂስት 1838
11. ራዲዮሎጂስት 1838
12.
13.
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 የተጠቀሰው እንተጠበቀ ሆኖ ከላይ ከተጠቀሰው ሙያ አዲስ የሙያ ዘርፍና የሥራ
ጠባዩ ለተገላጭነት የሚደርግ መሆኑ ሚኒስትሩ ካመነበት ተመጣጣኝ የተገላጭነት እንዲከፈለው መወሰን ይችላል፤
1. ከፍተኛ ባለሙያዎች በሚሠሩበት የጤና ድርጅት ውሰጥ ወይም አቅራቢያ መንግሥት የመኖሪያ ቤት ያቀርባል፤
የመኖሪያ ቤት ማቅረብ ካልተቻለ በየወሩ የሚከተሉት ክፍያ ያገኛሉ፤
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 (ሀ፤ለ እና ሐ) የተጠቀሰው ቢኖርም ከ 15 ዓመት በላይ ያገለገሉ የጤና ዘርፍ
ሠራተኞችም መኖሪያ ቤት ይቀርባል፤ የመኖሪያ ቤት ማቅረብ የማይቻል ከሆነ የሰራተኛውን ደመወዝ 30%
ለቤት ኪራይ መደጎሚያ ይከፈላል፤
9
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተጠቀሰው ባለሙያ ከ 15 ዓመት በላይ ከገለገለና የወር ክፍያው የደመወዙ
30% በታች ከሆነ በንዑስ አንቀጽ 2 የተጠቀሰውን ክፍያ ያገኛል፤
4. በተቋሙ ያለው መኖሪያ ቤት በቅድሚያ የሚሰጣቸውን ባለሙያዎችን በተመለከተ በተቋሙ ነባራዊ ሁኔታ
ላይ ተመስርቶ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት ተፈጻሚ ይሆናል፤
5. ከተቋሙ መኖሪያ ቤት ለመቀበል ፈቃደኛ ላልሆነና ለተሰጠው ሠራተኛ ምንም የቤት ኪራይ ማካካሻ ክፍያ
አያገኝም፤
ባለሙያ እና ሠራተኛ ተረጋግቶና ለረዥም ጊዜ በሥራ ገበታው ላይ ቆይቶ ለኅብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት
ለመስጠት እንዲችል የሚከተለው ሁኔታ ሲሟላ ከታክስ ነጻ የቤት ተሸከሪካሪ ግዥ ተፈቅዷል፤
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 በተመለከተው መሠረተት ከታክስ ነጻ የተሸከሪካሪ ግዥ ታጠቃሚ የሆነ
ባለሙያ ለ 10 ዓመት በጤና ሴክተሩ የማገልገል ግዴታ አለበት፤
3. ከ 10 ዓመት በታች አገልግሎት ስጥቶ ከመንግሥት ተቋም የለቀቀ ባለሙያ የተሰጠው የታክስ ነጻ ዕድል
ይነሳበታል፤
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተጠቀሰው ቢኖርም በሴክተሩ ከ 15 አመት በላይ ያገለገሉ ሌሎች የጤና
ዘርፍ ሰራተኞች ከታክስ ነጻ የተሸከሪካሪ ግዥ ታጠቃሚ ይሆናሉ፤
በተሰጠው አካል የጤና ተቋሙ ደረጃ “C” ላይ ተመድበው ለሚሰሩ ስፔሻሊስትና ከዚያ በላይ የጤና
10
ሰ
1. በሁሉም የጤና ተቋም ደረጃ ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ የተሻለ አገልግሎት የሰጠ ባለሙያ
2. የዕውቅና የሽልማት ማበራታቻ ይዘቶችም እንደ ተቋሙ አቅምና የስራ አመራር ውሳኔ
ሠ). ዋንጫ
ረ). ሜዳሊያ
ለ). ለሰጡት ራዥም አገልግሎት የዋንጫ ወይም ሜዳሊያ ወይም የምስክር ወረቀት
ሐ). በገንዘብ፤
መ). በአይነት፣
11
ለመሥራት ፍላጎት ካለው በለው ክፍት ቦታ ተቀጥሮ እንዲሠራ የስራ ዕድል
ሊመቻችለት ይችላል፤
1. ለጤና ትምህርት ወይም ለጤና አገልግሎት ተቋማት ተፈላጊ የሆነ ባለሙያ ለመቅጠር ከሁለት ጊዜ በላይ
ማስታወቂያ ወጥቶ ከጠፋ በላኪና ተቀባይ መ/ቤት በሚደረግ ስምምነት የጋራ ቅጥር ማከናወን ይቻላል፡፡
2. በጋራ በሚደረግ የቅጥር ስምምነት ወደ ተቀባይ መ/ቤት የሚመጣ ባለሙያዎች በላኪ መ/ቤት የሚከፈለው
ደመወዝ 70% ድረስ ሊከፈለው ይችላል፡፤
3. በጋራ ቅጥር በተቀባይ ተቋም ቢያንስ በሳምንት 20 ሰዓት አገልግሎት መስጠት አለበት፡፡
1. በስራ አፈጻጸማቸው የተሻለ ውጤት ያገኙ ሰራተኞች ተቋሙ ባለው የሰው ሀብት ልማት ዕቅድ መሰረት
አስፈላጊውን መስፈርት ሲያሟሉ ቅድሚያ የትምህርት ዕድል ያገኛሉ፡፡
2. ተቋሙም የትምህርት ዕድል አግኝተው ትምህርታቸውን ላጠናቀቁ ሰራተኞች የስራ ዕድል ይሰጣል፡፡
1. አለማቀፋዊ ወይም ሀገራዊ ወረርሽኞች መከሰቱን በመንግሥት ሲታወጅ ለጤና ዘርፉ ሰራተኞች የህይወት
መድን ዋስትና በመንግስት እንዲሸፈን ይደረጋል፡፡
12
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተገለጸ ወረሪሽኝ በሚከሰትበት ወቅት በሥራ ላይ ተሳታፊ የሆኑ
ሠራተኞች ወረርሽኙ መቆሙ አስኪታወጅ ጊዜ ድረስ በአገልግሎት ላይ ከተሰማሩ ባለሙያዎች
እየተሰበሰበ ያለው ታክስ በመንግሥት እንዲሸፈን፤
ክፍል ሶስት
ልዩ-ልዩ ድንጋጌዎች
18. ከጤና ዘርፉ ሠራተኞች የተረኝነትና ልዩ ልዩ ጥቅማ-ጥቅም የሚገኝ ገቢ ሥራ ግብሩ በመንግሥት
የሚሸፈን ሆኖ ለሠራተኛው ምንም ሳይቆረጥ እንዳለ ይከፈለዋል፤
2. ይህንን ደንብ የሚቃረኑ መመሪያዎች፤ ሰርኩላሮችና የአሠራር ሥርዓቶች በዚህ ደንብ ተሸሯል፡፡
13