Professional Documents
Culture Documents
2
2
(የመጀመሪያ ረቂቅ)
ጥር/2014 ዓ.ም;u
ማውጫ
ክፍል አንድ.....................................................................................................................................................3
1.1. መግቢያ.....................................................................................................................................3
1.2. የአጋርነትና የትብብር ሞዴል ማስፈፀሚያ ሰነድ አላማ.....................................................................4
1.2.1. ዋና አላማ...........................................................................................................................4
1.2.2. ዝርዝር አላማዎች...............................................................................................................4
1.3. የትምህርት ቤቶች የአጋርነትና ትብብር ሞዴል ምንነት.....................................................................4
1.4. የአጋርነትና የትብብር ሞዴል አስፈላጊነት.......................................................................................6
1.5. የትምህርት ቤቶች የአጋርናትና ትብብር የሚያስገኘው ጠቀሜታ.....................................................8
1.5.1. ለተማሪዎች.......................................................................................................................8
1.5.2. ለትምህርት ቤቶች...............................................................................................................8
1.5.3. ለመምህራን........................................................................................................................9
1.5.4. ለአጋር ድርጅቶች................................................................................................................9
1.5.5. ለወላጆች.........................................................................................................................10
1.6. የአጋርነትና ትብብር ሞዴል ታሳቢ ያደረጋቸው ጉዳዮች..................................................................10
1.7. የትምህርት ቤቶች አጋርነትና ትብብር ሞዴል መርሆች...................................................................11
1.8. የትምህርት ቤቶች አጋርነትና ትብብር ሞዴል የተፈፃሚነት ወሰን.....................................................11
ክፍል ሁለት..................................................................................................................................................13
2. የትምህርት ቤቶች አጋርነትና ትብብር ሞዴል ግቦች እና የአተገባበር ስልቶች..............................................13
2.1. የትምህርት ቤቶች የአጋርነትና ትብብር ሞዴል ግቦች......................................................................13
2.2. የትምህርት ቤቶች የአጋርነት እና ትብብር ሞዴል አተገበባር ስልት....................................................13
ክፍል ሶስት...................................................................................................................................................14
የትምህርት ቤቶች የአጋርነትና የትብብር ሞዴል አደረጃጀትና አመራር.................................................................14
3.1. የአጋርነትና የትብብር ሞዴል መዋቅራዊ አደረጃጀት...............................................................................14
3.1.1. አጋር ልየታ........................................................................................................................14
3.1.2. መዋቅራዊ መስመር...........................................................................................................15
3.1.3. አመክኗዊ መስመር............................................................................................................15
3.1.4. ስሜታዊ/የተነሳሽነት መስመር.............................................................................................15
3.1.5. ቤተሰባዊ መስመር.............................................................................................................16
3.2. የትምህርት ቤት እና የአጋር አካላት የግንኙነት መንገዶች.................................................................17
1
3.3. የትምህርት ቤቶች የአጋርነትና የትብብር ሞዴል አመራር................................................................17
ክፍል አራት..................................................................................................................................................19
4. በትምህርት ቤቶች አጋርነትና ትብብር ሞዴል የትኩረት አቅጣጫዎችና ተግባራት.....................................19
4.1. የትምህርት ቤቱን አሰራር ስርዓት ማሻሻል....................................................................................19
4.2. የተማሪዎችን የመማር ውጤቶች ማሻሻል፣.................................................................................19
ክፍል አምስት...............................................................................................................................................20
በየደረጃው ያሉ የትምህርት መዋቅሮች ተግባርና እና ኃላፊነት፣ የተጠያቂነት ስርዓት..............................................20
5.1. በየደረጃው ያሉ የትምህርት መዋቅሮች ተግባር እና ኃላፊነት...........................................................20
5.1.1. ትምህርት ሚኒስቴር..........................................................................................................20
5.1.2. የክልል/ከተማ አስተዳደር/ ዞን/ክፍለ ከተማ ትምህርት ቢሮዎች................................................20
5.1.3. የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት....................................................................................................21
5.1.4. በትምህርት ቤት ደረጃ........................................................................................................21
5.2. የተጠያቂነትና የማበረታቻ ስርዓት...............................................................................................22
5.2.1. የተጠያቂነት ስርዓት...........................................................................................................22
5.2.2. የማበረታቻ ስርዓት............................................................................................................22
ክፍል ስድስት................................................................................................................................................23
ክትትል ግምግማና መማማር.........................................................................................................................23
6.1. ክትትል.....................................................................................................................................23
6.2. ግምግማ...................................................................................................................................23
6.3. መማማር.................................................................................................................................24
7. ማጠቃለያ........................................................................................................................................24
ተቀጽላ አንድ...............................................................................................................................................25
የአጋርነት/ሽርክና እና ትብብር ሞዴል የስምምነት ሰነድ......................................................................................25
ተቀጽላ ሁለት..............................................................................................................................................30
የትምህርት ቤት አጋር አካላት ግብረኃይል የስራ እንቅስቃሴ መከታተያና መገምገሚያ ቼክሊስት..............................30
2
ክፍል አንድ
የትምህርት ቤቶች የአጋርነትና የትብብር ሞዴል አጠቃላይ ገጽታ
1.1. መግቢያ
ይህንን መሰረት በማድረግ በ 2012 ዓ.ም በተፋጠነ መልኩ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የተፋጠነ
የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻ ስትራቴጂ አንድ እና ሁለት በማዘጋጀት ተግበባራዊ ቢደረግም በሰው ሰራሽ
በተፈጥሮ ችግሮች ምክንያት የተፈለገውን ያህል ውጤት ማምጣት አልቻለም። ስለሆነም ይህንን ስትራቴጂ
በተሟላ መልኩ ተግባራዊ በማድረግ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ይህ የትምህርት ቤቶች የአጋርነትና
የትብብር ሞዴልን ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኗል።
3
በየደረጃው ያሉ የትምህርት መዋቅሮች ተግባርና እና ኃላፊነት እና ክፍል ስድስር ክትትል ግምግማና
መማማር እንዲሁም ተቀጽላዎችን በውስጡ ይዟል።
4
ስለሆነም በተመሳሳይ ችግር ውስጥ ያለፉ ሀገሮች ቸግሩን ለመቅረፍ ትምህርት ቤቶችን በመገንባትና በማደስ፣
የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት (ፋሲሊቲ) በማሟላት፣ የተሻሻለ የትምህርት አገልግሎት ለተማሪዎች ለማቅረብ
እንዲችሉ ባለድርሻ አካላትን እና ህብረተሰቡን በማስተባባር አጋርነትን በመመስረት ያሉባቸውን ችግሮች ለመቅረፍ
ሲሰሩ ይታያሉ።
የአጋርነት/ሽርክናና የትብብር ሞዴል በግለሰቦች እና በድርጅቶች ደረጃ ተግባራዊ ሊደረግ ይችላል። ሆኖም ግን ወጥ የሆነ
የአሰራር ስርዓት ያስፈልገዋል። ይህ ትብብራዊ ሞዴል አጋር አካላት ያላቸውን ሰብአዊና ቁሳዊ ህብታቸውን በማቀናጀት
በተናጠል ማሳካት የማይችሉትን ዓላማ ማከናወን እንዲችሉ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ነው። በዚህም ሁለቱም
ተባባሪ አካላት በመጀመሪያ ትብብር እንዲያደርጉ ስገደዳቸውን መሰረታዊ ችግሮች የመለየት እና ችግሩን መፍታት
በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ የአጋራ ስምምነት በማድረግ እና ወጥ የሆነ የአሰራር ስርዓት በመፍጥር ችግራቸውን
እንዲፈቱ እድል ይሰጣል።
በትምህርት ቤቶችና በአጋር ድርጅቶች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ በተለይ ተቋሟት መካከል የሚደረጉ
መደጋገፎችንና መረዳዳቶች ለትምህርት ቤቶች መሻሻል በተለይ ለተማሪ ውጤትና ስነምግባር መሻሻል ከፍተኛ የሆነ
አስተዋጽኦ አለው። ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው የትምህርት አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያደርገው አስተዋጽኦ
ከፍተኛ ነው።
በአጠቃላይ የአጋርነትና ትብብር ሞዴል ትምህርት ቤቶች በአካባቢያቸው ያሉ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ
ዙሪያ በማሳተፍ የተማሪዎችን ውጤትና የመማር ውጤት ለማሻሻል የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ነው።
የትምህርት ቤት አመራሮች በትምህርት ቤቶች ዙሪያ ያለውን አካባቢያዊ ሀብት/ጸጋ በተለይም ከሃብት ማሰባሰብ
በተጨማሪ በክፍል ውስጥ የሚካሄደውን የመማር ማስተማር ሂደት ከመምህሩ ጎን ሆነው ድጋፍ እንዲሰጡ የሚያደርግ
ነው። ለአብነት ታዋቂ/ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተማሪዎችን የሚመክሩበትና የሚያንጹበት፣ መንግስታዊ የሆኑና
የሚያለማምዱቡት፣ ትምህርት ቤቶች ከግቢ ውጭ ያለውን ሃብት የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማሻሻል
የአጋርነትና ትብብር ሞዴል የሚስፈልጋቸው ተግባራትን ማለትም የትምህርት ቤቶች ግንባታ፣ መሰረተልማት
አቅርቦትና የትምህርት ቤቶች አግልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል በሚደረጉ ሁለገብ እንቅስቃሴዎች በትምህርት ቤቶችና
በግል ሴክተሩ ወይም የልማት ድርጅት ወይም በህብረተሰቡ መካከል የሚመሰረት የአጋርነት ስምምነት ነው። በዚህም
መሰረት አጋር ድርጅቶችና ግለሰቦች ፣ የትምህርት ቤቶችን ብቃት በማሻሻል፣ አካባቢያዊ የፈጠራ ውጤቶችን
5
በማስተዋወቅ፣ የበጀት ድጎማ በማድረግ፣ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በማመቻቸት በትምህርት ቤት ማሻሻል
ይህ የትብብርና የአጋርነት ሞዴል በተፈለገው ደረጃ ተግባራዊ እንዲሆን ከአሁን በፊት ያሉ የመንግስት የአሰራር
ስርዓቶችን እና መዋቅሮችን ይጠቃማል። ሆኖም ግን እንደ አስፈላጊነቱ ከክልል ክልል የተለያዩ የአተገባባር ስልቶችን
ሊከተል ይችላል። በትምህርት ቤት ደረጃ ይሄ ሞዴል ውጤታማ እንዲሆን የአጋርነት ስምምነት የፈረሙ አጋር አካላት
የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የተደራጁ አደረጃጀቶች ውስጥ በመግባት ከዕቅድ ዝግጅት እስከ ግምገማ ባሉት
ሂደቶች እንዲሳተፉ ይደረጋል። በዚህ ሞዴል የሚከናወኑ ተግባራት ከአሁን በፊት ወጥተው ስራ ላይ የዋሉ የሕግ
ማዕቀፎች፣ ደንቦች፣ ፖሊሲዎች፣ መመሪዎችን እና የጋራ የመግባቢያ ሰነዶችን የተከተለ እንዲሆን ይደረጋል።
ለምሳሌ፡- የ 2013 ዓ.ም የትምህርት አመራር የመረጃ አመታዊ መጽሄት መሰረት 40% የመጀመሪያ ደረጃ
እና 66.7% የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የውሃ አገልግሎት አላቸው፣ 30% የመጀመሪያ ደረጃ እና 76%
ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት አላቸው፣ 34% የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት
ቤቶች የትምህርት መስጫ ሬዲዮና 79፣ 7% ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ኮምፒውተር አላቸው፣
በተመሳሳይ 14% የመጀመሪያ ደረጃ ቴፕ ሪከርደር እና 17% የሚሆኑት ደግሞ ቪዲዮ ሪከርድ አላቸው፣
55.7% የመጀመሪያ እና 88.2% ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ቤተመፃህፍት አላቸው፣ 46.7%
የመጀመሪያ እና 90% ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ቤተ ሙከራ አላቸው እና 49.6% የመጀመሪያ አና
64.4% ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ማበልፀጊያ ማዕካለት አላቸው። ይህ የሚያሳየው ትምህርት ቤቶች
የመማር ማስተማር ስራውን ሊያሳልጹ የሚችሉ የትምህርት ግብዓት እንዳሏቸው ነው። ምንም እንኳን
ትምህርት ቤቶች መሰረታዊ የሚባሉ ግብዓቶች ቢኖሩም በ 2013 የትምህርት አመራር መረጃ ዓመታዊ
መጽሄት መሰረት 7.8% የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ብቻ ናቸው ለደረጃው የተቀመጠውን ዝቅተኛ መመዘኛ
የሚያማሉ ትምህርት ቤቶች ያሉት። ከዚህ መረዳት የምንችለው ግብዓት በራሱ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ
6
ለማሻሻል በቂ እንዳልሆነ ነው። ለምሳሌ የ 2013 የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ካገኙ
ትምህርት ቤቶች ውስጥ በግብዓት በሂደት እና በውጤት ተመዝነው በአጠቃላይ ውጤታቸው ደረጃ 4 ላይ
የደረሱ ትምህርት ቤቶች አምስት ትምህርት ቤቶች ብቻ ናቸው። በተመሳሳይ በዚሁ አመት የኢንስፔክን
አገልግሎት ካገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 7.8% ደረጃ 3፣ 69% ደረጃ 2 እና 23.2% የሚሆኑት ደግሞ ደረጃ
1 ላይ ናቸው። ስለሆነም የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ሂደት ላይ ያሉ አሰራሮችን ማሻሻል እና
የትምህርት ቤት አጋርነት/ሽርክና እና ትብብር ሞዴልን በትምህርት ቤት ደረጃ ተግባራዊ ማድረግ
ያስፈልጋል።
ስለሆነም ይህ የአጋርነት/ሽርክና ሞዴል አጋር አካላት በተለይ ደግሞ ወላጆች በትምህርት ዙሪያ በቂ ግንዛቤ
እንዲኖራቸው በማድረግ ለልጆቻቸው ትምህርት ተቆርቋሪና አጋዥ እንዲሆኑ በማድረግ ለትምህርት ቤቶች
መሻሻል የድርሻቸውና አጋርነታቸው እንዲወጡ ተነሳሽነታቸውን ይጨምራል፤ በተማሪዎችም ውጤት
መሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ትምህርት ቤቶችና አጋር ድርጅቶች በተመሳሳይ መንገድ አንድ ላይ ተጋግዘው ሲሰሩ ለትምህርት ቤቶች
መሻሻል መጠነ ሰፊ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ። ለአብነት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች፣ ሲቪክ
ማህበራትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ለትምህርት ቤቶች የተግባር፣ የንድፈ ሀሳብ፣ የሀብትና መሰል
ድጋፎች ሲያደርጉ ትብብራዊ አጋርነት ያጠናክራል። የተጠናከረ ትብብር ወደ ውጤት ያመራል በተለይ ደግሞ
የትምህርት ቤቶችን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ያሻሻል፣ ሀብትን በብቃት ለመጠቀምና የትምህርትን ዓላማ
ለማሳካት ያስችላል በትምህርት ቤት ዙሪያ ለሚከናወኑ ተግባራት ወጥ የሆነ የአሰራር ስርዓት ይፈጥራል።
በአጠቃላይ ይህ ሞዴል በትምህርት ቤቶች ደረጃ ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊ የሆነበት ዋናው ምክንያት
በትምህርት ቤት ውስጥ እና ከትምህርት ቤት ውጭ ያለውን ሃብት (የሰው እና የፋይናንስ) አቀናጅቶ
በመጠቀም የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል በማስፈለጉ ነው። የትምህርት ቤቶች ደረጃ ሲሻሻል ደግሞ
የተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር ይሻሻል።
የትምህርት ቤት አመራሮች በትምህርት ቤቶች ዙሪያ ያለውን አካባቢያዊ ጸጋ በክፍል ውስጥ የሚካሄደውን
የመማር ማስተማር ሂደት ከመምህሩ ጎን ሆነው ድጋፍ እንዲሰጡ የሚያደርግ መርሃ ግብር ነው።
7
ተማሪዎች የትምህርት አቀባበላቸውን የሚያሳድጉ ነገር ግን በራሳቸው ሊያገኙ
የማይችሏቸውን ግብዓቶች እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ( ሙዚየሞችን መጎብኘት ይችላሉ፣
የብቃት ማዕከላትን መጠቀም ይችላሉ፣ ከውጩ ጋር መገናኘት ይችላሉ፣የትምህርት ድጋፍ
ማገኘት ይችላሉ)
ተማሪዎች የራሳቸውን ፍላጎት በማበልጸግ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ የተለያዩ ሀገራዊና
አለማቀፋዊ ተሞክሮዎችን እንዲያገኙ፣
የተማሪዎችን ስነምግባር ለማሻሻል አወንታዊ ሚና ይጫወታል፣
ተማሪዎች በትምህረት ቤታቸው አፈፃፀም ዙሪያ እንዲወያዩ እና የራሳቸውን ኃላፊነት
እንዲወጡ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፣
1.5.3. ለመምህራን
8
የመምህራን የስራ ተነሳሽነትን ያሳድጋል፣
የመምህራን የመኖሪያ ቤት ችግር ይቀርፋል፣
መምህራን ለመማር ማስተማር ይደቱ የተሻለ ግብአት እንድያገኙ ይረዳቸዋል፣
ትምህርቱ ይበልጥ ተግባር ተኮር እንድሆን ያግዛል፣
የመምህራንና የአካባቢው ህብረተሰብ የተሻለ ግንኙነት ይፈጥራል፣
መምህራን በኃላፊነት እና በተጠያቂነት እንዲሰሩ ያግዛል፣
1.5.5. ለወላጆች
ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ይልካሉ፣
የልጆቻቸው የትምህርት ውጤት ያሻሽላል፣
ወላጆች ልጆቻቸውን እንዲያግዙ ያደርጋል፣
በትምህርት ቤት የሚያደርጉትን ተሳትፎ ያሳድጋል
9
ከላይ የተቀመጡትን ታሳቢዎች ወደ ተግባራ ለመለወጥ የርዕሰ መምህራን እና በየደረጃው ያለው
የትምህርት መዋቅር የክትትልና ድጋፍ ስራ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል። እንዲሁም በትምህርት ቤቶች ዙሪያ
ያለው አካባቢያዊ አቅምና ጸጋ ለተማሪዎች የትምህርት ውጤት ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው እና
የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ሁሉንም አቅም ያማከለ ስልት አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል።
በተጨማሪም የአካባቢን ሃብት በአግባቡ ወይም በፍትሃዊነት ለመጠቀም ከክልል እስከ ትምህርት ቤት
ድረስ ያለው የትምህርት መዋቅር ከባቢያዊ የሆነ የሃብት ስርጭት የሚያሳይ ካርታ ወይም የአሰራር ስርዓት
በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል። የመማር ማስተማር ስራንም ውጤታማ ለማድረግ ሙያዊ
እገዛ ሊያደርጉ የሚችሉ የሰው ሃይል ልየታና ስምሪት ማድረግ ያስፈልጋል። ከዚህ አንጻር ደግሞ
የትምህርት ክፍሎች (በዲፓርትመንቶች) ከፍተኛውን ሚና መጨወት አለባቸው።
ሀ. ግልጽነት:- ስለሚከናወኑ ጉዳዮች ወይም ተግባራት በግልጽ መረጃዎችን መለዋወጥ ፤በሚፈጠሩ የአጋርነት
መርሀግብሮች ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅድሚያ ዓላማውንና አተገባበሩን እንዲረዱ እንዲሁም መረጃ
እንዲደርሳቸው ማድረግ ፤
ሐ. ሕጋዊነት: -አጋር አካላት ለሚያደርጓቸው ክንዋኔዎች ደህንነት ሕጋዊነትን ማግኘትና ሕጋዊነትን ተላብሰው መስራት
አለባቸው።
መ. ቀጥተኛነት:- በቀጥታ ተገቢ አጋርነትን ሊያሳልጡና የትምህርት ቤቶችን ፍላጎቶች ብቻ ሊያሟሉ በሚችሉ
ትብብሮች ብቻ መወሰን
ሠ. ተለማጭነት:- ተለማጭነት በሁሉም የአጋርነት ድርጊቶች አስፈላጊና በፈጣን የዕድገት ለውጦች ስለሚወሰኑ
በያንዳንዱ የተግባር ክንውን ተለማጭ ስልቶችን መጠቀም አስፈላጊ ይሆናል፤
ረ. ካለፉት ተግባራት መማር:- ከየእለት ተግባራትና ገጠመኞች በመማር የአሰራር ለውጦችን ማምጣት ልምዶችን
ማካፈል፤
ሰ. ፍትሐዊነት:- ሁሉም የህብረተሰብ አካላትን ተጠቃሚ የሚያደርግ የአጋርነት ማዕቀፎችን ተግባራዊ ማድረግ ፤
ሸ. አካታችነት:- የሁሉንም ተሳትፎ ና ተጠቃሚነት ለማሳደግ በአገልግሎት አቅርቦት ውሳኔ አሰጣጥ፣ የአሰራር ፖሊሲ
ዝግጅት በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙትን ከግምት ማስገባት፤
10
ቀ. የጋራ ኃላፊነት፡- አጋር አካላት በትብብር ለማከናወን በጋራ የተስማሙባቸውን ተግባራት በሃላፊነት መንፈስ
ማከናወን.
ይህ የትምህርት ቤቶች የአጋርነት እና የትብብር ሞዴል ማንዋል በዋነኛነት ለቅድመ አንደኛ፣ ለአንደኛ፣
ለመሃከለኛ እና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀ ነው። በሌላ መልኩ በዚህ የአጋርነት/ሽርክና እና
የትብብር ሞዴል ስምምነት ውስጥ የሃይማኖት ተቋማትና የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት በሽርክና ስርዓቱ
ውስጥ አይካተቱም። ሆኖም ግን የኃይማኖት አባቶች እና የፖለቲካ ድርጅት አመራሮች እንደ ግለሰብ መሳተፍ
ይችላሉ።
11
ክፍል ሁለት
ማሻሻል፣
ግብ 2፡- የመማርና የስልጠና ዕድሎችን በተለይም የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማስፋትና
ማበልፀግ፣፣
ግብ 3፡- ሁሉም አጋር አካላት በሚፈቅዱት የትምህርት ፕሮግራሞች በትምህርርት ቤቱ እንዲሳተፉ
ማድረግና ሚናቸውን ማሻሻል፣
ግብ 4፡- ትምህርት ቤቶች ከአጋር አላካትና ከህብረተሰቡ የሚያገኙትን ሃብት (በገንዘብ፣ በአይነት፣
በጉልበት እና በዕውቀት) ማሳደግ
ግብ 5፡- ከእንስፔክሽን ደረጃ አሰጣጥ አንፃር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል
12
ክፍል ሶስት
13
3.1.2. መዋቅራዊ መስመር
ማሻሻል፣
14
3.1.5. ቤተሰባዊ መስመር
ወላጆች/አሳዳጊዎች የልጆቻቸውን ትምህርት የሚከታተሉበት ስርዓት መዘርጋት
15
የትምህርት ቤት የሪፖርት ካርድ፣
የትምህርት ቤቶች የውስጥ እና የውጭ የተማሪዎች የጠቅላላ እውቀት የጥያቄና መልስ
ፕሮግራሞች፣
በትምህርት ቤት ደረጃ የሚካሄዱ የግጥም እና የንባብ ፕሮግራሞች፣
በተማሪዎች የሚመሩ የተለያዩ ትምህርታዊ ጉባኤዎች/መርሃ ግብሮች፣
የተማሪዎች ስራ ማሳያ አውደ ርዕይ/ኤግዚቢሽን
መረጃን ሰጪ የሆኑ ፕሮግራሞች ( የተማሪ ጥረቶችን ፣ የመምህራን፣ የአመራሩን)
ወላጆችን የሚያነቁ መልዕክቶች
ስፖርታዊ ውድድሮች
የየሩብ አመት የአፈጻጸም ውይይት
የወላጆች ቀን በዓላት
የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል በትምህርት ቤት ውስጥ የሚከናወኑ ሁሉንም ተግባራት ር/መምህሩ
ብቻ በቂ እንዳልሆነ እስከአሁን የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻ የሄድንበት መንገድ ያመላክታል።
በተመሳሳይ መልኩ በትምህርት ቤት ውስጥ የሚከናወኑ አብዛኛዎቹ ተግባራት ከትምህርት ቤቱ
ር/መምህር አቅም በላይ እንደማይሆኑ ግልጽ ነው። ትምህርት ቤቶችን በዘላቂነት ደረጃቸውን ለማሻሻል
ትምህርት ቤት ውስጥ ያለውን እና ከትምህርት ቤት ውጭ ያሉትን አቅሞች አቀናጅቶ መጠቀም
ውጤታማ እንደሚያደርግ ጥናቶች እና የተለያዩ ሪፖርቶች ያመላክታሉ። የትምህርት ስራ ማህበራዊ
እንደመሆኑ በየትኛውም የስራ ዘርፍ የተሰማራ እና የትኛውንም የአኗኗር መንገድ የሚከተሉ የህብረተሰብ
ክፍሎችን ይመለከታል። በዘርፉ ላይ የተደረጉ ጥናቶችም እንደሚያሳዩት የአንድ ሃገርን እድገት
ከሚወስኑት እና ከሚያፋጥኑት ሁኔታዎች ውስጥ ትምህርት ግንባር ቀደሙ ነው። ስለሆነም እስከ አሁን
በተበጣጠሰ መልኩ ይሰራበት የነበረውን የትምህርት ቤት እና የአጋር አካላት ግንኙነትን ወጥ የሆነ
አደረጃጀት በመፍጠር ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ ለትምህርት ቤቶች እንዲያበረክቱ ማድረግ አስፈላጊ
ነው። ስለሆነም በቀጣይ የትምህርት ቤቶችንና የአጋር አካላትን ግንኙነት ለማጠናከር ሊኖረን የሚችለው
አደረጀጃት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከ ወረዳ ባለው የትምህርት ዋቅር ውስጥ የትምህርት ቤት መሻሻል
ዳይሬክቶሬት አንድ ተጠሪ ባለሙያ በመመደብ ስራውን በበላይነት እንዲያስተባብር ይደረጋለ።
በትምህርት ቤት ደረጃ ደግሞ የትምህርት ቤት መሻሻል ኮሚቴ የአጋርነት/ሽርክና እና ትብብር ሞዴል
ውጤታማ እንዲሆን ያስተባብራል። ሆኖም ግን ክልሎች ይህ ሞዴሉን በተሻለ መልኩ
ማስተግበር/ማስፈፀም ያስችለኛል የሚሉትን አደረጃጀቶች ሊጠቀሙ ይችላሉ።
16
ክፍል አራት
17
ትምህርት ቤቱ በአጋር አካላት የሚሰሩ ስራዎችን በመለየት እና በዙሪያው ያለውን እምቅ
አቅም በመጠቀም የትምህርት ቤቱን ደረጃ በማሻሻል ለተማሪዎች ጥራት ያለው የትምህርት
አገልግሎት መስጠት፣
የትምህርት ቤቱ ራዕይ፣ ተልእኮና እሴቶች ለማሳካት ሊያግዙ የሚችሉ አጋር ድርጅቶች
(የንግድ ተቋማት፣ አሰልጣኝ ተቋማት፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣
የሃይማኖት ተቋማት፣ እድሮች፣ ሙያ እና ሲቪክ ማህበራት) እና ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች
አቅምን በተደራጀ መልኩ መጠቀም ፣
ክፍል አምስት
18
• የትምህርት ቤቶች የአጋርነትና የትብብር ሞዴልን ለሚመለከታቸው አካላት ያስተዋውቃል፣
• የዞን/ክፍለ ከተማ መነሻ በማድረግ አጋርነትና የትብብር የአሰራር ስርዓትን ለማጠናከር የመግባቢያ
ሰነድ ያዘጋጃል፣ይፈራረማል፣ አፈፃፀሙን ይከታተላል፣
19
• በትምህርት ቤት መሻሻል ፕሮግራም አተገባበር ጥንካሬና ክፍተት ይለያል፣
የተጠያቂነት ስርዓትን በየደረጃው ተግባራዊ ለማድረግ ክልሎች እንደ አስፈላጊነቱ የክልሉን ነበራዊ ሁኔታ
በመዳሰስ የተጠያቂነት ስርዓት ያዘጋጃሉ።
20
በዚህ ስምምነት ሰነድ ውስጥ በተገባው ስምምነት መሰረት የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ያሻሻሉ ትምህርት
ቤቶች፣ ባለሙያዎች እና አመራሮችን ለማበረታታት የማበረታቻ ስርዓት ይዘረጋል።
ክፍል ስድስት
ክትትል የታቀዱ ዓላማዎች በግባትና በውጤት ዕድገታቸው የሚመዘንበት ተከታታይ ግምገማ ነው።
በትብብራዊ አጋርነት አካላቱ የክትትል ተግባራት በተቻለ ፍጥነት ትክክለኛ ወይም ሊሆኑ የሚችሉ
21
የክትትል ውጤቶች ለታዩ ችግሮች መፍትሔ በመጠቆም ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አላቸው። ስለሆነም
በትብብራዊ አጋርነት ትግበራ ወቅት በሂደት የተገኙ የክትትል ውጤቶች በትምህርት ቤቶች የሚደረጉ ዓመታዊ
ዕቅዶችንና ስራ ማስኬጃ በጀቶችን ከማሻሻላቸው ባሻገር በአጋራት መካከል የሚከናወኑ የጋራ ስምምነቶች
ወደተግባር መመንዘራቸውን መከታተያና ውጤቱም ለስራዎች መሻሻል ትልቅ አቅም እንዲፈጠር ይደረጋል።
6.2. ግምግማ
ግምገማ መረጃዎች በተደራጀ ሁኔታ የሚሰባሰቡበትና የሚተነተኑበት ሥርዓት ነው። በመሆኑም በትብብራዊ
አጋርነት የስራ ክንዋኔዎች የመጡት ለውጦችና የተገኙ ፋይዳዎች ይገመገማሉ፤ ይህንንም በማድረግ
የመርሀግብሩ ብቃት፣ ውጤታማነት፣ ተገቢነትና ዘለቄታዊነቱ ይዳሰሳል። የግምግማውም ሂደት በአጋር
ድርጅቶች ወይም ግለሰቦችና በትምህርት ቤቱ መካከል በተገባው ስምምነት መሰረት ይፈፀማል።
6.3. መማማር
መማማር በትግበራ ሂደት ተገኙትን ምልካም ልምዶችና ተሞክሮዎች በመቀመርና በማሰራጨት የተሻለ
ትምህርትና ቅስሞሽ ለቀጣዩ እንቅስቃሴ የምንጠቀምበት የመማማሪያ ዘዴ ነው።በተመሳሳይ ሁኔታ
በትብብራዊ አጋርነት መርሀግብር ውስጥ አፈፃፀም የተገኙ መልካም የስራ እንቅስቃሴዎችን አጉልቶ
በማውጣት ለተሻለ ትግበራ መጠቀም ያስፈልጋል።ከተቻለም ሌሎች የትብብራዊ አጋርነት አካላት በልምዱ
እንዲጠቅሙ ለማድረግ ተሞክሮዎቹን በመቀመር ማስተላለፍ ተገቢነት ይኖረዋል።
7. ማጠቃለያ
የአጋርነትና የትብብር ሞዴልን በትምህርት በቶች በትክክል ተግባራዊ በማድረግ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል
እንደሚቻል ይታመናል። ስለሆነም ሞዴሉ በትምህርት ቤት ውስጥ እና ውጭ የአሉ አቅሞችን አቀናጅቶ በመጠቀም
የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል እና የትምህርት ቤቱ ማህነረሰብ ትምህርት ቤቶችን በባለቤትነት እንዲመራቸው
የሚያስችል ነው። የትምህርት ቤቱ አመራር ከትምህርት ቤት ውጭ ያሉ አካላት ከእቅድ ዝግጅት እስከ ትግበራ ድረስ
እንዲሳተፉ እና የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ማድረግ ይኖርበታል። እንዲህ ሲሆን የትምህርት ቤቶችን ደረጃ
በዘላቂነት ማሻሻል ያስችል። ይህ ሲሆን የተማሪዎች ውጤት እና ስነምግባር አብሮ እንዲሻሻል ያደርጋል። ስለሆነም
ይህንን ሞዴል ተግባራዊ ለማድረግ ከላይ እስከ ታች ያለው የትምህርት መዋቅር እጅ ለእጅ ተያይዞ ተግባራዊ ሊያደርገው
ይገባል።
22
ተቀጽላ አንድ
I. መግቢያ
ሁለቱ አጋር አካላት [ አጋር አካል ] እና [ ትምህርት ቤት ] ይህን የመግባቢያ ሰነድ ሲፈርሙ
ዓላማቸው ያደረጉት በትምህርት ቤተ ውስጥ ያሉትን ክፍተቶች በመለየት በትምህርት ጥራት
መሻሻል ላይ በመስራት የተማሪዎችን ውጤትና ስነምግባር በሚሻሽሉ ተግባራት ላይ በጋራ
በመሰማራት አገልግሎት መስጠት ነው። በዝግጅት ሂደቱም የትምህርት ቤት፣
የወላጆች፣የተማሪዎች፣ የማህበረ ሰብ፣ የግል ተቋማት ተወካዮች ይሳተፋሉ።.
የፕሮግራሙ ዓላማ የትምህርት ሚኒስቴር በ 2014 ዓ.ም ካወጣው ዝርዝር መመሪያ ጋር በቀጥታ
የሚዛመድ ሆኖ
23
[አጋር አካል] በሰነዱ የተቀመጡትን ዓላማዎች ዕውን ለማድረግ የራሱን ጥረት
ያደርጋል።በማስቀጠልም ሰነዱ በአጋር አካላት መካከል መፈጠር ያለባቸውን የስራ ግንኙነቶችና
የቅንጅት ማዕቀፍ ዘርግቷል፤በማከልም ለፕሮግራሙ ማስፈፀሚያ የሚውለውን በጀትና ከያንዳንዱ
የሚጠበቀውን ሀብትና አገልግሎት በግልጽ አስቀምጧል። .
II. ዓላማ
የስምምነቱ ዝርዝር ዓላማ ይጠቀሳል
ለምሳሌ:
የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት - የትምህርት ቤቱን መምህራን፣ አመራር፣ ተማሪዎች እና ወላጆች
የሚያካትት የዕውቀት ሽግግር ሊሆን ይችላል
የገንዘብ ድጋፍ - የትምህርት ቤቱን ችግር ሊፈቱ የሚችሉ የገንዘብ ድጋፎች ሊሆኑ ይችላሉ
ለምሳሌ:
አጋር አካሉ ከትምህርት ቤቱ ጋር በዚህ ውል መሰረት ለሁለቱም የጋራ ጥቅም የሚያከናውናቸው
ተግባራት ተለይተው ይገለፃሉ።
24
ለምሳሌ:
2. [ትምህርት ቤት ]:
[የአጋር አካል ተጠሪ ስም]
[ማዕረግ]
[አድራሻ]
[የስልክ ቁጥር]
ይህ የመግባቢያ ውል በሁለቱ አካላት ከተፈረመ በኃላ የፀና ሲሆን ውሉ [ለሁለት (2)] ዓመት ያገለግላል።
ውሉን ያለሁለት ስምምነት መሰረት ማንኛውንም ሀሳብ መጨመር መቀነስ ወይም ማሻሻል አይቻልም።
ሁለቱ አካላት በውሉ ማቢቂያ መጨረሻ ዓመት ላይ በፅሁፍ በሚያቀርቡት የጋራ ሓሳብ ለተጨማሪ ዓመታት
ውሉን ሊያድሱ ይችላሉ። እንዲሁም የመግባቢያ ውሉን ሁለት አጋር አካላት ከተስማሙ ውሉን በጽሁፍ
ማደስ ወይም መሰረዝ ይችላሉ።
25
ሆኖም ማንኛውም አጋር አካል በሆነ ምክንያት በማንኛውም ሰዓት ውሉን ከሁለት ወር በፊት በጽሁፍ
በማሳወቅ ውሉን መሰረዝና የገንዘብ ድጋፍም ሆነ እገዛውን ማቆም ይችላል።
በዚህ ውል ውስጥ አጋር አካላቱ በማናቸውም ላይ ተጨማሪ ገንዘብ እንዲያዋጡ ወይም እንዲደጉሙ ጫና
አያደርግም።በተጨማሪም አጋር አካላቱ በማናቸውም መልክ የአጋርነትን ዓላማ በሚጥስ ሁኔታ የጋራ የንግድ
ሽርክና ማቋቋም አይቻልም።
አጋር አካላቱ በተጋባው የውል ቃል መሰረት በመሃከላቸው ምናልባት አለመግባባት ቢፈጠር በመጀመሪያ
ጉዳያቸውን በግላቸው ተወያይተው ይፈታሉ። በአጋጣሚ መግባባት ላይ በ 60 ቀናት ባይደረስ በሌላ የግልግል
አካል አለመግባባቱን ያስወግዳሉ።, ይህም ካልተሳካ አንደኛው አጋር አካል መብቱን በሕግ ሊያስከብር ይችላል።
ይህ ውል መግባባት በሁለቱ አጋር አካላት በፊርማ ካልፀደቀ በስተቀር ተግባራዊ ማድረግ አይቻልም።
26
[ስም] [ስም]
[ማዕረግ] [ማዕረግ]
ቀን: ቀን
ፊርማ________________________________
ፊርማ________________________________
ውሉ የሚጠናቀቅበት ጊዜ:
ፊርማ
የእማኝ ስም ቀን
ፊርማ
የእማኝ ስም ቀን
27
ተቀጽላ ሁለት
ይህ ቼክ ሊስት የትምህርት ቤት የአጋር አካላት ግብረኃይል/ኮሚቴ የግማሽ ወይም የሙሉ ዓመት የስራ ክንውን
ለመከታተልና ለመገምገም የሚያስችል መሣሪያ ነው።ቼክ ሊስቱ ክትትልና ግምገማ ከማድረግ ባሻገር እንደሁኔታው
መሣሪያውን እንደአካባቢ ሁኔታ በማዛመድ ለግለ-ግምገማ መገልገል ይቻላል። መጠይቁ በሚሞሉበት ወቅት
በተስማሙበት ስፍራ /ሳጥን ውስጥ የ “X” ምልክት በማድረግ ያሳዩ። በመጨረሻ ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽዎን
በጽሁፍ ያስፍሩ።
28
ክፍል ሁለት:- በትግበራ ወቅት
ክፍል ሦስት:-ማጠቃለያ
23. በሂደት ከአጋር አካላት መካከል የአጋርነቱን ስራ የቋረጡ/ያቆሙ አጋር አካላት አሉ? አሉ የሉም
29
ካሉ ያቋረጡበት ምክንያት ቢጠቀስ/ቢብራራ
______________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________
____________________________________________________________
24. የአጋር ትብብሩ ግብረሀይል ያከናወናቸው ቁልፍ ስራዎችና የተገኘ ውጤት ቢገለጽ
______________________________________________________________________________
______________________________________________________________________________
___________________________________________________________________
25. በፕሮግራሙ የትግበራ ሂደት የታዩ ጥንካሬዎች
______________________________________________________________________________
__________________________________________________________________
26. በፕሮግራም የትግበራ ሂደት የታዩ ድክመቶች /ክፍተቶችና የተሰጡ መፍትሔዎች
______________________________________________________________________________
_______________________________________________________________________
27. ባጠቃላይ የፕሮግራሙ የስኬት ደረጃ እንዴት ይገመግሙታል/ይገልጹታል?
______________________________________________________________________________
_________________________________________________________________________
30