Professional Documents
Culture Documents
Soil and Agronmic Data Sharing Directive - Draft - 20221129
Soil and Agronmic Data Sharing Directive - Draft - 20221129
የግብርና ሚኒስቴር
1
መግቢያ
በአገራችን ኢትዮጵያ ለግብርና ልማት እየዋለ ባለው የመሬት ሀብት በአርሶ አደሩ፣ በአርብቶ
አደሩና ከፊል አርሶአደሩ ያልተገባ የመሬት አጠቃቀም ምክንያት በአፈር ሀብት ላይ ከጊዜ ወደጊዜ
መጠነ ሰፊ ጉዳት እየደረሰ የሚገኝ መሆኑ፤
ጉዳቱን ለመቀልበስ በመንግስትና በባለድርሻ አካላት በኩል በተበታተነ መልኩ ጥረት እየተደረገ
ቢሆንም የሥራ ድግግሞሽና የሀብት ብክነት ከማስከተሉ ባለፈ በሚፈለገው ልክ ውጤታማ መሆን
ባለመቻሉ፤
የግብርናን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከጊዜ ወደጊዜ ከህዝቡ ቁጥር መጨመር ጋር ተያይዞ
እያደገ ለመጣው ፍላጎት የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም በአየር ንብረት
ለውጥ የሚከሰተውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመቋቋም የአፈር ጤንነትንና ለምነትን በዘላቂነት መጠበቅ
አስፈላጊ በመሆኑ፤
2
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
. አጭር ርዕስ
. ትርጓሜ
/ “መረጃ” ማለት በተለያዩ መረጃ አመንጪ አካላት ከመስክ የተሰበሰበ ጥሬ-መረጃ፣ ከተለያዩ
ምንጮች የተገኘን በማቀናጀት የተቀነባበረ እና የተከማቸ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ነው፤
/ “የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ” ማለት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና ተፈጥሮ ሀብትን
በዘላቂነት ለመጠቀም የሚያስችል ከአፈር ሀብት አያያዝና አጠቃቀም ጋር የተያያዘ መረጃ ነው፤
/ “ቀዳሚ መረጃ” ማለት በተለያዩ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ የማመንጨት ተልእኮ፡- በአሰሳ ወይም
ምርምርን መሰረት በማድረግ ከመጀመሪያው ምንጭ የተገኘ መረጃ ነው፤ሰ
/ “ውርስ መረጃ” ማለት በተለያዩ ቀደምት መረጃ አመንጪ አካላት- ቀደም ሲል የመነጨና
ለተጠቃሚዎች በግብዓትንት የሚያገለግል ሁለተኛ ደረጃ መረጃ ነው፤
3
/ “በመሳሪያ ተነባቢ መረጃ ” ማለት በተለያየ ፋይል ፎርማት ተዘጋጅቶ በኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ፡-
ሊቀናበር፣ ሊተነተንና ሊነበብ የሚችል መረጃ ነው፤
/ “ምስጢራዊ መረጃ” ማለት ግልፅነት ያለው የአመዳደብ ብያኔን መሰረት በማድረግ የመረጃ
ልውውጥን ሊገደብ የሚችል የተለየ የመረጃ ዓይነት ነው፤
/ “ሜታዳታ” ማለት የመረጃውን ምንጭ፣የተገኝበትን ግዜ፣ አወቃቀር፣ ጥራት፣ ባለቤትና አመንጪ
አካልን የሚገልፅ ነው፤
/ “መረጃ አመንጪ” ማለት የአፈርና አግሮኖሚ መረጃን ለተለያየ ዓላማ ለመሰብሰብ ወይም
ለመፍጠር የተሰማራ ወይም የሚሳተፍ ሰው ነው፤
/ “መረጃን አስተዳዳሪ” ማለት መረጃን ከአመንጭው አካል ወደ አንድ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት
በማሰባሰብ የሚያስተዳር፣ የሚቆጣጠር እና [በሚደረግ ስምምነትም መረጃዎችን ?] ተደራሽ
የሚያደርግ ሰው ነው፤
/ “የመረጃ ደረጃ” ማለት በተፈጥሮ ሰውና በሕግ የሰውነት መብት ባለቸው አካላት መካከል ጥራት
ያላቸውን መረጃዎች ተደራሽ ለማድረግ፣ ለማጋራትና መልሶ ለመጠቀም የሚያግዝ የመረጃ
ጥራት ማረጋገጫ ስምምነት ሰነድ ነው፤
/ “የቴክኒክ ኮሚቴ” ማለት- በግብርና ሚኒስቴርና በሌሎች መረጃ አመንጪ አካላት ወደ መረጃ
ቋት የሚገባ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃን በተመለከተ በሚወጣ ደረጃ መሰረት ጥራትን፣
ወቅታዊነትንና ተደራሽነትን መሰረት በማድረግ መሰራቱን የሚከታተል አካል ነው፤
/ “የመረጃ መብት ባለቤትነት” ማለት በአዕምሮአዊ ንብረት ፈጠራ ባለቤትነት ወይም ከአዕምሮአዊ
ንብረት ፈጣሪው ጋር በሚደረግ ውል የተገኝ መረጃን በባለቤትነት የመቆጣጠር መብት ነው፤
/ “የሶስተኛ ወገን መብቶች” ማለት በሌላ ወገን በባለቤትነት የተያዙ ለግብዓትነት የሚውሉ
መረጃዎችን በመጠቀም የሚገኝ የተቀነባበረ መረጃ ባለቤትንት መብት፤
4
/ “ሰው” ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው፤
. ዓላማ
/ የስራ ድግግሞሽና የሀብት ብክነትን ለመቀነስ አገራዊ ወጥና ጥራቱን የተጠበቀ መረጃ በአንድ
ማዕከል ማደራጀት፤
/ ለፖሊሲ አውጪዎችና ውሳኔ ሰጪዎች ወቅታዊ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ በቀላሉ ተደራሽ
ማድረግ፤
/ ውርስ መረጃዎችን ከተለያዩ መረጃ አመንጪ አካላት በመቀበል በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውሉ
ማድረግ፤
/ አዳዲስ መረጃዎችን የመረጃ ደረጃ ምደባንና አቀራረብን መሰረት በማድረግ በሚፈለገው ጥራትና
. የተፈጻሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ በመላው ኢትዮጵያ ለግብርና ሚኒስቴር በሕግ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት ወሰን
ልክ፡-
5
. የመረጃ መርሆዎች
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ አያያዝ፣ አጠቃቀምና ልውውጥ አሁን ባለንበት ዲጂታል ሥርዓተ-ምኅዳር
ውስጥ ቀጥሎ በዝርዝር የተቀመጡትን መርሆዎች መሰረት አድረጎ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት
አገልግሎት የሚሰጥ መሆን አለበት፤
/ ተገኝነት (Findablity)፡ በማንኛውም መንገድ የሚገኝ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ በማዕከላዊ የመረጃ
ቋት ተደራጅቶ መከማቸትና በመረጃ ተጠቃሚው ሲፈለግ በቀላሉ የሚገኝ መሆን አለበት፤
ክፍል ሁለት
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ተገኝነት
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃዎች ተገኝነት ግብ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃን ከመስክ በመሰብሰብ ወይም
የተለያዩ መረጃዎችን በማቀናበር የተገኘ መረጃንና ሜታዳታን በየፈርጁ ተደራጅቶ በቀላሉ መገኘት
እንዲችል ማረጋገጥ ነው፡፡
. መረጃ ማመንጨት
6
ማንኛውም የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ በምርምር ወይም በፕሮጄክት ድጋፍ ሲመነጭ የመረጃ
መብት ባለቤትነትንና የማስተዳደር ኃላፊነትን ጨምሮ ስለ መረጃው አጠባበቅ በተዘረዘሩት
የተዘጋጀ ቅፅ መሰረት በፅሁፍ ተዘጋጅቶ በስምምነት ውስጥ መካተት አለበት፤
/ የቀዳሚ መረጃ ሲመነጭ ብሔራዊ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ አሰባሰብን አሰራር ደረጃን የተከተለ
መሆን አለበት፣
/ የተቀነባበረ መረጃን ለማመንጨት የመረጃውን ውጤት ለማግኘት ቀድመው የነበሩት ውርስ
መረጃዎችን የማጠራቀም፣ሳንሳዊ ሞዴሎችን በመጠቀም የመተንተን እና የመተርጎም ስራዎችን
ያካትታል፤
/ የተቀነባበረ መረጃ ሲመነጭ ከአፈር መረጃና ማከማቻ የአሰራ ሂደት ጋር የተጣጣመ መሆን
አለበት፤
/ የተቀነባበረ መረጃ አመንጪዎች ለግብዓት የሚውሉ መረጃዎች ባለቤት ያወጧቸውን የፈቃድ
ግዴታዎች መከተል አለባቸው፤
/ በተቀነባበረ መረጃ ላይ ገደብ ለመጣል የሚፈጠሩት ለግብዓት የሚውሉ ግዴታዎች አስቀድመው
መቃኘትና መረጋገጥ አለባቸው፤
. የመረጃ ሜታዳታ
/ ሜታዳታ ከታወቀና ስምምነት ከተደረሰበት ግልጥ ደረጃ ጋር የተጣጣመ መሆን አለበት፤
/ የግብርና ሚኒስቴር ለመረጃ ፍላጋ ቀላል የሆነ ተገቢ ሜታዳታ ቅጽ መኖሩን ወይም መዘጋጀቱን
የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት፤
7
/ ለአዲስም ሆነ ቀድመው ላሉ መረጃዎች ሜታዳታ መመዝገብ አለበት፤
/ የግብርና ሚኒስቴር የሜታዳታ ደረጃ በዓለም አቀፍ ግልጥ ደረጃ መሰረት መዘጋጀቱን እና
ከስምምነት ላይ መደረሱን የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት፤
/ የሜታዳታው መዝገብ ቢያንስ የሚከተሉትን መረጃዎች ጨምሮ የያዘ መሆን አለበት፤
ሀ/ የመረጃ መብቶች ባለቤት፤
ለ/. የመረጃ ጠባቂው/አስተዳዳሪው፤
ሐ/ የተፈጠረበት ቀን፤
መ/ የመረጃው መልከዓ ምድራዊ ሽፋን (ተገቢ ከሆነ)፤
ሠ/ ለጂኦስፓሻል መረጃ የጂኦግራፊክ ፕሮጄክሽን፤
ረ/ የመረጃው ዓላማ፤
ሰ/ የመረጃው የፈቃድ አሰጣጥ፤
ሸ/ ለተቀነባበረ መረጃ የመረጃው ምንጭ ማብራሪያ፤
ቀ/ የታተመ ከሆነ የመረጃው ድረ-ገጽ ትስስር/ሊንክ፡፡
ክፍል ሶስት
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ተደራሽነት
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃዎች ተደራሽነት ግቡ በመረጃ አሰተዳዳሪው ከመረጃ አመንጭዎች የተከማቹ
መረጃዎችን የአሰራር ስምምነት በሚፈቅደው መሰረት ለተገልጋዮች ተደራሽ መሆኑን ማረጋገጥ
ነው፡፡
. መረጃን ስለማከማቸት
/ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ - ከተሰበሰበ ወይም ከመነጨ በኋላ በተቻለ መጠን ወዲያውኑ
ከመረጃው ባለቤት በሚገኝ ፈቃድ ወይም ውል መሰረት በግብርና ሚኒስቴር የመረጃ ቋት
እንዲከማች መደረግ አለበት፤
8
/ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ወደ መረጃ ቋት ገብቶ እንዲከማች በመደረጉ ምክንያት የፈጠራ ወይም
የአእምሮአዊ ንብረት መብት አይተላለፍም፤
. የመረጃ ተደራሽነት
/ ማንኛውንም የአፈርና አግሮኖሚ መረጃን በባለቤትነት የያዘ አካል የሰበሰበውን ወይም ያመነጨውን
/ የመረጃ ልውውጥ በግብርና ሚኒስቴር እና ከባለድረሻ አካላት ጋር በሚዘጋጅ ውስጠ ደንብ መሰረት
በመሆን በጋራ ይዘጋጃል፤
/ ምስጢራዊ ነው ተብሎ የተለየ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ተደራሽ እንዳይሆን ሊገደብ ይችላል፤
9
ለ/ ብሔራዊ ደህንነትን አደጋላይ የሚጥል ሆኖ ሲገኝ ፤
ሐ/ በመረጃው ባለቤት ጥያቄ በበቂ ምክንያት መረጃው እንዳይሰራጭ የጊዜ ገደብ የተጣለበት ሲሆን
ግዜው እስኪ ጠናቀቅ ድረሰ፤ እና
መ/ የሶስተኛ ወገንን መብት የሚጎዳ ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡
/ በመረጃው ባለቤት ጥያቄ ለተወሰነ ጊዜ እንዳይሰራጭ የታገደ መረጃ ታግዶ ሊቆይ የሚችለው አስከ
ሁለት ዓመት ብቻ ሲሆን በልዩ ምክንያት አስከ አምስት ዓመት ሊራዘም ይችላል፤
/ በመረጃው ባለቤት ጥያቄ ለተወሰነ ጊዜ መረጃ ታግዶ እንዳይሰራጭ የጊዜ ገደቡ በመረጃው ባለቤትና
በግብረና ሚኒስቴር በሚወከል የቴክኒክ ኮሚቴ የጋራ ሥምምነት ይወሰናል፤
ክፍል አራት
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ተናባቢነት
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ተናባቢነት ግቡ መረጃዎች በዓለም-አቀፍ ስምምነት በተፈረመባቸውና
በሀገር-አቀፍ በወጡ ደረጃዎች መሰረት ጥራታቸውን ጠብቀው መሰራታቸውንና ለመረጃ ልውውጥ
አመችነት በኤሌክትሮኒክ ማሽኖች የሚናበቡ መሆናቸውን ማረጋገጥ ነው፡፡
10
. የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ደረጃ
/ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ደረጃ ሲዘጋጅ የሚከተሉትን መስፈቶች መሰረት በማድረግ መሆን
አለበት፤
/ በመረጃ ባለቤቶች አማካኝነት ወደ አገር አቀፍ ጥብቅ የመረጃ ቋት እንዲገባ የሚደረግ መረጃ በመረጃ ቋት
አስቀድሞ ከተከማቸና ከተረጋገጠ መረጃ ጋር ተናባቢ መሆን አለበት፤
/ በአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ቋት ያልተከማቸ ምንጩ ያልታወቀና ያልተረጋገጠን መረጃ ማጋራትና ጥቅም
ላይ እንዲውል ማድረግ የተከለከለ ነው፤
/ የግብርና ሚኒስቴር ከባለድረሻ አካላት ጋር በመመካከር ዝርዝር የመረጃ ልውውጥ የአሰራር ስርዓት
በማዘጋጀት በሥራ ላይ እንዲውል ሊያደረግ ይችላል፤
/ በመረጃ ባለቤቶች አማካኝነት ወደ አገር አቀፍ ጥብቅ የመረጃ ቋት እንዲገባ የሚቀርብ መረጃ በመረጃ ቋት
ውስጥ ካለ ሌላ መረጃ ጋር የማይናበብ ሆኖ ከተገኝ፡- አጠራጣሪ የሆነው መረጃ በሁለት ሳምንት ጊዜ
ውስጥ ተስተካክሎ መቅረብ አለበት፤
11
ክፍል አምስት
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ እንደገና ጥቅም-ላይ-ዋይነት፤
የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ እንደገና ጥቅም-ላይ-ዋይነት ግቡ መረጃ አመንጪ አካላት ያመነጯቸውን
መረጃዎች ከመረጃ አስተዳሪው ጋር በሚደረግ ስምምነት ወደ መረጃ ማዕከላዊ መረጃ ቋት
መግባታቸውን የባለቤትነት መብት ባከበረ መልክ ጥቅም ላይ መዋላቸውነ ማረጋገጥ ነው፡፡
/ መረጃ አመንጭ አካላት ማንኛውም የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ አቅራቢ አካል ያመነጨውን መረጃ
ለማዕከላዊ መረጃ ቋት የማቅረብ ግዴታ አለበት፤
12
/ የአፈርና አግሮኖሚን መረጃ መብት ባለቤቶች መረጃቸው ጥቅም ላይ ሲውል እውቅና ሊሰጣቸው
ይገባል፤
/ ጥርጣሬን ለማስወገድ ሲባል ይህ መመሪያ በሌሎች የአእምሯዊ ንብረት መብት ህጎች አፈፃፀም
ላይ ምንም ተፅእኖ የለውም፡፡
/ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ አስተዳዳሪው አካል (ግብርና ሚኒስቴር) የአፈርና አግሮኖሚ መረጃን
የሚያመነጩና የሚጠቀሙ አካላት የሚሳተፉበት የተለዩ መድረኮችን ያመቻቻል፤ ከመድረኮቹ
የሚገኙ ምክረ-ሐሳቦችን ለመመሪያው ስኬታማ አተገባበርና ለቀጣይ የግብርና መረጃ ልውውጥ
ፖሊሲ ዝግጅት እንደግብዓት ይጠቀምበታል፡፡
ክፍል ስድስት
የሥራ ኃላፊነት፣ መብትና ግዴታ
. የግብርና ሚኒስቴር ተግባርና ኃለፊነት
/ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ የዚህን መመሪያ ዝርዝር የትግበራ ማንዋል ዝግጅት
ያስተባብራል አፈጻጸሙን ይከታተላል፣ ይገመግማል፣ በአተገባበር ወቅት ክፍተቶች ወይም
ግድፈቶች ሲኖሩ የማስተካከያ እርምጃዎችን ይወስዳል፤
13
/ በሀገር-አቀፍ ደረጃ በተለይ በግዙፍ ፕሮጀክቶች ጥናት የመነጨ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ ቅጂ
በሚኒስቴሩ መረጃ-ቋት በየፈርጁ ተደራጅቶ እንዲከማች እና የአመንጪውን የባለቤትነት መብት
ባከበረ መልኩ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ያደርጋል፤
/ የሥራ ድግግሞሽን እና ሀገራዊ የሀብት ብክነትን ለመቀነስ መረጃዎችን በአፈርና አግሮኖሚ መረጃ
አሰባሰብ፣ ምርመራና ትንተና ስታንዳርድ መሰረት ማመንጨት፤
/ አንድ መረጃ ተጠቃሚ መረጃ መውስድ የሚችለዉ የመረጃ መውሰጃ መስፈርቶች በድረ-ገጽ ወይም
በአካል ቀርበዉ የተዘጋጁትን ቅጾች ማሟልት ሲችሉ ነው፡፡
14
/ ማንኛዉም በግብርና ምርትና ምርታማነት ልማት ዙሪያ በቀጥታ ልማትና ምርምር ላይ በመሳተፍ
ያሉ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ የግል ድርጅቶች እንዲሁም ተመራማሪና ሌሎች ግለሰቦች
የዚህ መረጃ ተጠቃሚዎች ናቸው፤
/ ከመረጃ አስተዳዳሪው በህጋዊ መንግድ የወሰዱትን መረጃ በራሳቸዉ ማስተካከያ ሳያደርጉ ከመረጃ
አመንጨዉ በወረደዉ መሰረት እንደ ግብዓት በመዉሰድ የራሳቸዉን መረጃ ማመንጭት
ወይም ቀጥታ መጠቀም ይችላሉ፤
/ ማንኛዉም የመረጃ ተጠቃሚዎች የወሰዱትን መረጃ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት
የተከለከለ ነዉ፤
15
ሀ/ ማንኛዉም የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ መረጃ አመንጪ አካላት ለወሰዱት የሙያም ሆነ የስራ
ፈቃድ በየዓመቱ ማሳድስ አለበት፣
ክፍል ሰባት
16
/ በኢትዮጵያ የወጣዉን ወይንም ሀገሪቷ የተቀበለችዉን የጥራት ደረጃዎች ያላሟል መረጃ
ያመነጨ፤
/ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀቱ ከመሪያዉ አሰራር ዉጭ በሆነ መንግድ የተገኘ ከሆነ፤
/ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀቱ በማናቸዉም መንገድ ለሌላ ወገን አስተላለፎ ከተገኘ፤
17
ለ/ የዘህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) አጠቃላይ አነጋገር እንደተጠበቀ ሆኖ፤
ለ/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) በተወሰነው የጊዜ ገደብ ውስጥ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት
የቅሬታውን ማመልከቻ ሊያቀርብ ያልቻለ ቀሬታ አለኘ የሚል አካል ከአቅም በላይ የሆነው
ምክንያት በተወገደ በአስር የሥራ ቀናት ውስጥ ማመልከቻውን ሊያቀርብ ይችላል፤
/ ቅሬታን ስለማጣራት
18
ሀ/ በዚህ መመሪያ መሰረት የተቋቋመው የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ የቅሬታ ማመልከቻ ሲቀርብለት
በዚህ ደንብ አንቀጽ ….. የተደነገገውን አሟልቶ የቀረበ መሆንኑን በማረጋገጥ ተቀብሎ
ይመዘገባል፡፡
ለ/ ኮሚቴው፡-
/ የውሳኔ አሰጣጥ
ሀ/ የመሥሪያቤቱ የበላ ኃላፊ ወይም ወኪሉ የቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ ሪፖርት በደረሰው ከአሥር
የሥራ ቀንናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የኮሚቴውን የውሳኔ ሃሳብ ማጽደቅ ወይም በቂ ምክንት
ሲኖረው ፤
የቅሬታ ሰሚው
19
3/ የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተት፤
4/ ሁኔታዎችን ከሚመለከቱ ሌሎች ጉዳዮች ፤ጋር በተያያዘ ምክንያት በደል ደረሰብኝ
የሚል ቅሬተውን ሊያቀርብ ይችላል፡፡
5/ በመስሪያቤቱ የበላይ ኃላፊ የመጨረሻ ውሳኔ ያልረካ ቅሬታ አቅራቢ በመደበኛ
ፍርድቤት ጉዳዩን አቅርቦ እንዲታይለት የማድረግ መብቱ የተጠበቀነው፡፡
/ የቅሬታ አጣሪ ኮሚቴው ተግባር
የቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ፡- ከመመሪያው አተረጓጎም ወይም አፈጻጸም፤ ከመብቶችና ጥቅሞች አጠባበቅ፤
የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተት ጋር በተያያዘ የአፈርና አግሮኖሚ መረጃ መብት ባለቤቶችና የመረጃው
ተጠቃሚዎቸ የሚያቀርቡዋቸውን ቅሬታዎች እያጣራ የውሳኔ ሃሳብ ለመስሪያቤቱ የበላይ ኃላፊ የማቅረብ
ኃላፊነት አለበት፡፡
ዑመር ሁሴን
20