Professional Documents
Culture Documents
1
1
ዓላማ 1.1፡ በፍልሰት ዙሪያ የህብረተሰቡ ግንዛቤ ማደግና የባህሪ ለዉጥ መምጣት
ዓላማ 1.2: ፍትሃዊና ዘመናዊ የውጭ አገር ሥራ ስምሪት አገልግሎቶችን ማስፋፋት
ግብ 1. በመደበኛና መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ዙሪያ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ችግሩን መቀነስ
ውጤት፡ ግንዛቤው ያደገ ህብረተሰብና የቀነሰ ችግር
የማስፈጸሚያ ተግባራት
1. ለሥራ ወደ ውጭ አገር የሚሰማሩ ዜጎች ተገቢውን የሙያ እና የቅድመ ጉዞ ስልጠና
ማግኘታቸውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
2. በመካከለኛው ምስራቅ እና የባህረሰላጤ ትብብር ሀገራት ያልተጠናቀቁ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን
ማጠናቀቅ፤
3. አዳዲስ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በማዘጋጀት ከተለያዩ ፍላጎት ካላቸው አገሮች ጋር መደራደርና
መፈራረም፤
4. ወደ ውጭ አገር ለስራ የሚሄዱ ዜጎችን መረጃ አያያዝ ማጠናከር፤
5. ለዜጎች ሥልጠና የሚሰጡ ማሰልጠኛ ተቋማትንና የቅድመ ጉዞ መስጫ ማዕከላትን ማጠናከር፣
6. በውጭ አገር ሥራና ሠራተኛ ለማገናኘት ፈቃድ ያወጡ ኤጀንሲዎች ሕግና ስርዓትን ተከትለው
መሥራታቸውን ለማረጋገጥ ቁጥጥር ማድረግ፣
7. ከውጭ አገር ሥራ ስምሪት ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን ተቀብሎ ማስተናገድ እና
በስምምነት እንዲፈቱ ማድረግ፣
8. የውጭ አገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ማሻሻያ እንዲጸድቅ መከታልና ተግባራዊ ማድረግ፣
አምድ 2. የተጎጂዎች ጥበቃ እና መልሶ ማቋቋም
ዓላማ፡ ተጎጂዎች የጥበቃና መልሶ ማቋቋም ስራዎች በተቀናጀ አግባብ ፍትሃዊ፣ ተደራሽና ወጥ የሆነ
ግብ 1. የተሻለ የተጎጂ ፍልሰት ተመላሽ ዜጎችና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ መረጃ ይኖራል፤
ውጤት፡- የተደራጀ የተጎጂ ፍልሰት ተመላሽ ዜጎችና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ መረጃ ስርአት
የማስፈፀሚያ ተግባራት
2. የተጎጂ ፍልሰት ተመላሾችና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ አገር አቀፍ የመረጃ ቋት ተግባር ላይ
እንዲውል ማድረግ፣
ማድረግ፣
5. የተጎጂ ፍልሰት ተመላሾችና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ አገር አቀፍ የመረጃ ቋት አተገባበር ላይ
ግብ 2. በተጎጂ ከፍልሰት ተመላሾች ዙሪያ የፈፃሚና ባለድርሻ አካላት የማስፈፀም አቅም ማሳደግ፤
ውጤት 1- የተጠናከረ የተጎጂዎች እንክብካቤ፤ ጥበቃና መልሶ ማቋቋም ስራዎችን ወጥነት ባለው
መልኩ ለማስፈፀም የሚረዳ የአሰራር ስርዓት፣
የማስፈፀሚያ ተግባራት
ማሳደግ፣
ውጤት 2- እዉቀትና ክህሎቱ ያደገ የተጎጅዎች የድጋፍና መልሶ ማቋቋም ባለሙያና ተቋም፣
የማስፈፀሚያ ተግባራት
7. የተለያዩ ተቋማት የተጎጂዎች ጥበቃና መልሶ ማቋቋም ስራዎችን ያካተተ እቅድና ትግበራ
ማሳደግ፤
ውጤት 1፡- ለተጎጂዎች የተሰጠ ሁሉን አቀፍ እንክብካቤ፤ ጥበቃና መልሶ ማቋቋም ድጋፍ፣
የማስፈፀሚያ ተግባራት
1. የተጎጂ ፍልሰት ተመላሽ የተጋላጭነት እና የድጋፍ ፍላጎቶች በዳሰሳ ጥናት እንዲለይ ማድረግ፣
3. ለተጎጂ ፍልሰት ተመላሾች የቅድመ ቅበላና የተሃድሶ አገልግሎት ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ፣
4. ለተጎጂ የፍልሰት ተመላሽ ዜጎች ተጋላጭነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሳይኮ ሶሻል አገልግሎት
ድጋፍ መስጠት፣
5. ለተጎጂ የፍልሰት ተመላሽ ዜጎች ተጋላጭነትን መሰረት ባደረገ መልኩ የማህበራዊ አገልግሎት
ድጋፍ መስጠት፣
(ቴክኒክ ክህሎት ስልጠና፣ የስራ ፈጠራ አስተሳሰብ ክህሎት ስልጠና፣ ህጋዊነት ማስፈን አገልግሎት፣
መነሻ ካፒታል ብድር አቅርቦት፣ ገበያ ትስስር፣ ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍና ሌሎችም)
1. በፍልሰት ተጎጂ የሆኑ አካባቢዎችን የመለየት ስራ ማከናወን፣
2. ተጋላጮችንና ተጎጂ የፍልሰት ተመላሾችን ሊያግዙ የሚችሉ ማህበረሰብ አቀፍ የልማት
ስራዎችን መለየት፣
3. ተጋላጮችንና ተጎጂ የስደት ተመላሾችን የጋራ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን
መተግበር፣
ግብ 1. በሰው የመነገድ ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገርና በህገወጥ መንገድ ሰውን ወደ ውጭ
ሀገር ለስራ መላክ ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፍ ስራዎችን
ማጠናከር፣
የማስፈጸሚያ ተግባራት
1. በሰው መነገድና ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀልን አስመልክቶ ለመከላከልና
ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 1178/2012 ን ስራ ላይ ማዋል፤
2. አዋጁንም ለማስፈጸም ዝርዝር ደንብ እና መመሪያ ማዘጋጀት እንዲሁም የአሰራር ስርዓቶችን
መዘርጋት
ውጤት 2. በሰው መነገድና ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር በህገ ወጥ መንገድ ሰውን ለስራ
የማስፈጸሚያ ተግባራት
4. የምስክሮች ጥበቃን ና አቆያየት የተሻለ ለማድረግ ፕሮጅክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ ማስገባት
5. በሰው መነገድና ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር በህገ ወጥ መንገድ ሰውን ለስራ ወደ ውጭ
ሀገር መላክና ተያያዥ ወንጀሎች ላይ ለተጎጂዎች እና ለምስክሮች መጠለያ ግንባታ ማስጀመር
6. የህግ አስከባሪ አካላት እና የመጠለያ እና የተለያዩ አገልግሎቶችን ከሚሰጡ የግል ድርጅቶች ና ድጋፍ
ከሚያደረጉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት መስራት
ግብ 3. የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማሳደግ የህግ ማስከበር ብቃቱ የጎለበተ የህግ ተቋም መገንባት
ውጤት. ተሳትፎው ያደገ ህብረተሰብ እና የህግ ማስከበር ብቃቱ የጎለበተ የህግ ተቋም የማስፈጸሚያ
ተግባራት
7. የማህበረሰቡንና የህግ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን የሚያሳድጉ ተግባራትን ማከናወን፣
8. ህብረተሰቡ ወንጀልን ሪፖርት የሚያደርግበት ቀላል ስርዓት መዘርጋት
9. በአዋጁ አፈጻጸመም ዙሪያ የማህበረሰብ ንቅናቄ መድረኮቸን ማዘጋጀት
ዓላማ. በጥናት እና ምርምር የተደገፈና የተጠናከረ ሁሉን አቀፍ የፍልሰት አስተዳደር ስርአት
መዘርጋት
ግብ 1. ጥራት ያለው እና ችግር ፈቺ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ስራዎችን በተለያዩ የመንግስትና የግል ከፍተኛ
ትምህርት ተቋማት እንደካሄዱ በማድረግ ተደራሽነትን ማሳደግ
ውጤት፡ ለፖሊሲ እና የፍልሰት አስተዳደር የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች እና ምክረ ሃሳቦች መጨመር
የግቡ ማስፈጸሚያ ተግባራት
12. የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት የፍልሰት ጥናትና ምርምር ስራዎችን
በየተቋማቱ የምርምር የትኩረት መስኮች ውስጥ እንዲያካትቱ ማድረግ፣
13. በፍልሰት ጥናትና ምርምር ዙሪያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለተመራማሪዎች ተገቢውን ድጋፍ
እንዲሰጡ ማድረግ፣
14. ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የምርምር ተቋማት ከተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ ባለድርሻ
አካላትና እርስ በርሳቸው በመተሳሰርና በጋራ በመሆን የፍልሰት ጥናትና ምርምር ፕሮጀክቶች
እንዲቀርጹና እንዲተገብሩ ማድረግ፣
15. የፍልሰት ምርምር ውጤቶች ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንዲሆኑ በተለያዩ የሀገሪቱ ቋንቋዎች የተግባቦት
መንገዶችን በመጠቀም እንዲሰራጩ ማድረግ፣
16. ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የምርምር ማዕከላት ለስራ ፈጠራ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን
ማበረታታት
17. ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የምርምር ማዕከላትን እርስ በእርስና ከአቻ የዓለም ተቋማት እና
ማዕከላት ጋር በልምድ ልውውጥ በማስተሳሰር አጋርነት ማሳደግ
ግብ 2. ለፍልሰት አስተዳደር እና ለምርምር ብቁ የሆነ የሰው ሀብት ለማልማት የፍልሰት ትምህርት ክፍል
በተመረጠ የከፍተኛ ትምህርት እንዲቋቋም ማድረግ
ውጤት፡ በዘርፉ የሰለጠነ በብዛትና በጥራት የሰው ሀብት ማፍራት
የማስፈጸሚያ ተግባራት
ዓላማ
በእቅድ ዘመኑ ከቆጠራ እና ከናሙና ጥናት የሚገኝ የፍልሰት መረጃ ሽፋን ማሻሻል እና ከአስተዳደራዊ
መዛግብት የፍልሰት መረጃ የሚመነጭበትን ስርአት መዘርጋት
ግቦች
ግብ 1፡- የስራ ቡድኑን ተቋማት በአይሲቲ መሰረተ ልማት በማስተሳሰር መረጃ የሚለዋወጡበትን ስርአት
መዘርጋት እና መረጃን ከአስተዳደር መዛግብት ማመንጨት
ውጤት፡- ደረጃውን የጠበቀ የፍልሰት መረጃ ከአስተዳደር መዛግብት ማመንጨት
ማስፈጸሚያ ተግባራት
1. በፍልሰት ዙሪያ በሚሰሩ ተቋማት ግንዛቤ በማሳደግ የመግባቢያ ሰነድ በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረግ
ግብ 2፡- ብሄራዊ ስትራቴጂ ለስታቲስቲክስ ልማት lll (NSDS lll) እና የአስር አመት ስታቲስቲክስ መሪ እቅድ
ላይ የፍልሰት መረጃ አያያዝ ስርዓትን ማሳደግ
ማስፈጸሚያ ተግባራት
1. የፍልሰት ናሙና ጥናት ማካሄድ እና በጥናቶች እንዲካተቱ የሚፈለጉ የፍልሰት መረጃ ዓይነቶች
መለየት
2. ለፍልሰት መረጃ አስተዳደር የሚያገለግል ስትራተጂክ ሰነድ ማዘጋጀት
ግብ 3፡- የፍልሰት መረጃ አስተዳደር ስራን አቅም ማጎልበት
ማስፈጸሚያ ተግባራት
1. የፍልሰት መረጃ አመንጪ ተቋማትን የአይሲቲ መሰረተ ልማት የባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት
2. የተቋማት የመረጃ አያያዝ እና ቅብብሎሽ አሰራር ስርዓትን ማዘመን
3. የፍልሰት መረጃ አስተዳደር ላይ ልምድ ካላቸው ተቋማት እና ሀገራት ጋር የልምድ ልውውጥ ማድረግ
1. መርሆች
በዚህ እስትራቴጂክ ሰነድ ውስጥ የተያዙ ዕቅዶችን በአግባቡ በማሳካት ሁሉን አቀፍ ዘለቄታዊ ለውጥ
ለማምጣት ከአለም አቀፍ መለኪያዎች፣ ከህግ ማዕቀፎች፣ ከምርጥ ተሞክሮዎችና ከሀገራችን ነባራዊ
ሁኔታዎች የመነጬ በሰዎች መነገድ፣ ሰዎችን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና በህገወጥ መነገድ ሰዎችን
ለመጠቀምና ብሎም የፍልሰት አስተዳደሩን የተሻለ ለማድረግ ስራው የሚመራባቸው መርሆዎችን በመለየት
1. ሰብአዊ መብት
ይህ መርሆ በዚህ ሰነድ የተገለጹት እና ተያያዥ ወንጀሎች ሰዎች ላይ የሚያደርሱትን የከፋ እና አሰቃቂ
ጉዳቶች በመገንዘብና ለችግሮቹም ምላሽ ለመስጠት የተጎጂውን መብትና ፍላጎቶች ማዕከል ማድረግ፣
ለተጎጂና ተጠቂ የሆኑ ድምጻቸው እንዲሰማና ምላሽ እንዲሰጣቸው የሚያስችል ነው፡፡ የሰብአዊ መብት
የሚያበቃ ነው፡፡
1. የስርዓተ ፆታ እኩልነት
የስርዓተ-ጾታ እኩልነት ማለት ለሴቶች እና ለወንዶች እኩል መብትን፣ ሀላፊነትን እና እድሎችን መስጠት
ሲሆን ይህ ማለት ሴቶችና ወንዶችን በሁሉም ጉዳዮች አንድ ማድረግና ማመሳሰል ማለት ሳይሆን ለሴቶች እና
ስለሆነም ማንኛውም ሰው ሴትም ሆነ ወንድ ራሳቸውን የሚመለከቱ ጉዳዮችን በመወሰን ሂደት ለጥበቃና
ለተሳትፎ ተመሳሳይ መብት አላቸው፡፡ ሴቶች ለማህበራዊ ጉዳይም ሆነ በፍልሰት ዙሪያ እንዲሁም
ሊኖራቸው ይገባል፡፡
ሶስቱን ወንጀሎች ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም ለተጎጂዎች የሚሰጡ ምላሾች ሲቀረጹ ለተለያዩ
ተጠቂ ለሆኑ ሴቶችና ወንዶች ፍላጎቶች የሚያማክል መሆን አለበት፡፡ ለምሳሌ ሴት ተጎጂዎች በሴት ፖሊሶች
እንዲጠየቁ፣ ሪፖርቶች፤ ጥናትና ምርምሮች እንዲሁም የተለያዩ መረጃዎች ሲሰበሰቡም ሆነ ሲደራጁ በፆታ
ያካትታል፡፡
2. የህፃናት መብት ማክበር
እንደሚታወቀው በሀገራችን በሰው የመነገድና ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀሎች ላይ ህፃናት
በከፍተኛ ሁኔታ ተጎጂዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም እነዚህን ወንጀሎች ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ብሎም
ምላሽ ለመስጠት የሚነደፉ ስትራቴጂዎች እና ማንኛውም ስራዎች ታዳጊ ሴቶችንና ወንዶችን የሚያበቃ፣
የሚደርስባቸውን ጥቃት የሚቀንስ፣ የከለላና የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ የሚያሰጥ እንዲሁም የህፃናት ልዩ
የተሟላ ሁሉን አቀፍ ምላሽ መስጠትን ማዕከል ባደረግ መልኩ መሆን ይኖርበታል፡፡
መንግስት የዜጎችን መብትና ደህንነት የመጠበቅ እና የማረጋገጥ ጉዳይ ህገ-መንግስታዊ ኃላፊነት በመሆኑ
በሰው የመነገድ፣ ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እንዲሁም በህገወጥ መንገድ ሰውን ለስራ ወደ
የመምራት ስራው ፕሮግራም በመንደፍ፣ በጀት በመመደብና ሁሉንም አካላት በማሳተፍና የማስተባበር
4. የህብረተሰብ ተሳትፎ
የህብረተሰብ አቀፍ እንቅስቃሴ ውስጥ ህብረተሰቡን በአግባቡና በሙሉ አቅም ማሳተፍን ላይ ትኩረት
ያደርጋል፡፡
6. ግልጽነትና ተጠያቂነት
ይሆናል፡፡
7. ሚስጥራዊነት
3.5.8 አጋርነት
የፍልሰት ስራዎች በአንድ ተቋም ብቻ የሚከናወኑ እነዳለመሆናቸው እና የተለያየ አካላትን ትብብርና ቅንጅት
የሚጠይቅ በመሆኑ በዚህ ዙሪያ የሚሰሩ ሁሉም አካላት በዚህ ስትራቴጅ አተገባበር ሂደት ውስጥ
አስፈላጊውን ቅንጅትና ትብብር ይፈጥራሉ።
ምዕራፍ አራት
4 የአተገባበር/አፈጻጸም/ አደረጃጀት
ኢትዮጵያ የፍልሰተኞች መነሻ፤ መተላለፊያና መዳረሻ ሀገር እንደሆነች ይታወቃል፡፡ በሰው የመነገድ፣ ሰውን
በሕገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር፣ በህገወጥ መንገድ ሰውን ለሥራ ወደ ውጭ ሀገር መላክ ወንጀሎች እና
የሀገር ውስጥ መፈናቀሎች ከመደበኛ ካልሆነ ፍልሰት ማሳለጫ መንገዶች ውስጥ የሚጠቀሱ ሲሆን በርካታ
ኢትዮጵያዉያንን ለአካላዊ፣ ስነልቦናዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶችና እና ለሞት እንዲዳረጉ
ከማድረጋቸው በተጨማሪ የሀገር ገጽታንም ከማበላሸት አኳያ ተጽዕኖው ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል
ይታመናል፡፡
መንግስትም በሀገራችን ስር እየሰደደና ስፋቱ እየጨመረ የመጣውን በሰዎች መነገድና ሰዎችን በህገ ወጥ
መንገድ ድንበር ማሻገር እና በህገወጥ መንገድ ሰዎችን ለስራ ወደ ውጭ ሀገር መላክ ወንጀሎችን ለመግታት
እንዲሁም የፍልሰት አስተዳደሩን ለማጠናከር በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራ ብሔራዊ ም/ቤት
በማቋቋም በስሩ በኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐ/ሕግ የሚመራ የትብብር ጥምረት በማዋቀር ባለፉት ዓመታት
እቅዶችን በማዘጋጀት ወደ ስራ የተገባ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተመሳሳይ መልኩም በክልል መንግስታትና በከተማ
አስተዳደሮችም አደረጃጀቱን ከክልል ጀምሮ እስከ ቀበሌ ድረስ በተዋረድ ለማዋቀርና ችግሩን ለመከላከል
በተቀናጀ እና በተደራጀ አግባብ ፍልሰት ለመምራትና ለማስተዳደር እንዲሁም አጥጋቢ በሆነ መልኩ ምላሽ
ለመስጠት ይቻል ዘንድ ጠንካራ አደረጃጀት ለመፍጠር የ 5 ዓመት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ
ይህን ስትራቴጅክ እቅድ ከግብ ለማድረስ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብረኃይል አደረጃጀት ጠንካራና ደካማ
ጎኖች በመገምገም በአዋጅ ቁጥር 1178/2012 መሰረት በማድረግ የሚከተለው አደረጃጀት ውጤታማ ይሆናል
1. በሰው የመነገድ ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር እና በህገወጥ መንገድ ሰውን ለስራ
ምክር ቤቱ በአዋጅ 1178/2012 መሰረት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ሰብሳቢነት ጉዳዩ የሚመለከታቸውን
የሀይማኖት መሪዎችና ታዋቂ ሰዎችን አካቶ የተደራጀ ሲሆን ተግባርና ኃላፊነቱም በአገር አቀፍ ደረጃ
በተመሳሳይ ሁኔታም በክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደሮች የሚመራ ክልላዊ ምክር ቤቶች በየክልሉ ይደራጃሉ፣
2. በሰው መነገድ ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር እና በህገወጥ መንገድ ሰውን ለስራ
መንገድ ሰውን ለስራ ወደ ውጭ መላክ ወንጀል ተከላካይ ብሔራዊ የትብብር ጥምረት ጉዳዩ የሚመለከታቸው
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን፣ ሲቪክ ማህበራትን፣ የሀይማኖት ተቋማትን፣ የሴትና የወጣት አደረጃጀትን
በማካተት የተደራጀ ነው፡፡ የጥምረቱ የስራ ኃላፊነትም የፍልሰትን አሉታዊ ውጤቶች ለመቀነስና ከፍልሰት
የሚገኙ ጥቅሞችን በአግባቡ ለመጠቀም እንዲቻል የትብበር ጥምረቱን አባል ተቋማትን እና ሌሎች ባለድርሻ
አካላትን ከዕቅድ ዝግጅት እስከ አፈጻጸም ድረስ የሚያከናውኗቸውን ከፍልሰት ጋር የሚገናኙ ተግባራት
ይከታተላል፤ ያስተባብራል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አባል ተቋማትና ሌሎች በፍልሰት ጉዳዮች ዙሪያ ኃላፊነት
ያለባቸው ባለድርሻ አካላት ስለፍልሰት ወቅታዊ ኩነቶች ተመሳሳይ የሆነ አረዳድና ወጥ የሆነ
መድረኮችን ያመቻቻል፤ በክልሎች የትብብር ጥምርቶች እንዲደራጁ ድጋፍ ያደርጋል፣ በትብብር ጥምረቶች
መካከል ተከታታይነት ያለው የመረጃና የእውቀት ልውውጥ እንዲኖር መድረኮችን ይፈጥራል፤ ያስተባብራል፡፡
ተመሳሳይ አደረጃጀት በክልሎች እስከ ቀበሌዎች የየአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት
በአዋጁ መሰረት ይደራጃሉ፡፡ የብሔራዊ የትብብር ጥምረቱ ጽ/ቤት ኃላፊነትም ብሔራዊ ትብበር ጥምረቱ
በተያያዘ የሚያስፈልጉ ፖሊሲዎችና ህጎች እንዲዘጋጁ ለትብብር ጥምረቱ ምክረ ሃሳብ ያቀርባል በአጠቃላይ
ለጥምረቱ የሴክሬታሪያት አገልግሎት ይሰጣል፡፡ የስራ ቡድኖች እና የክልል ጽ/ቤቶች አፈፃፀም ሪፖርት
ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ማለትም አለም አቀፍና አገር አቀፍ ድርጅቶች እና ከሌሎች መሰል
የሚጠይቅ በመሆኑ እንደ ምላሹ አግባብ ስድስት ዋና ዋና ተግባራት ላይ ያተኮረ የስራ ቡድን ተዋቅሯል፡፡ እነዚህ
የስራ ቡድኖች በአስተባባሪ ተቋማት የሚመሩ ሆነው የተለያዩ ተቋማትን፣ የግል ድርጅቶችን፤ የሚዲያ
አካላትን፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን፣ የወጣትና የሴቶች አደረጃጀቶችን ያቀፉ ይሆናል፡፡ የአስተባባሪ
ተቋማቱም በስራቸው ያሉ ተቋማትን የስራ እንቅስቃሴ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋሉ፡፡ የቡድኖችን እንቅስቃሴ
የተደራጀና ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል የቅርብ አመራርና ድጋፍ የሚያደርግ በሰብሳቢ ተቋማት የሚወከል
የዚህ የሥራ ቡድን ከፍተኛ የሥራ ሃላፊነትና ድርሻ የሚኖረው ሲሆን ዋና ዋና ተግባሩም የግንዛቤ
በተለይም የአመለካከት ባህሪ ለውጥ ላይ ትኩረት ማድረግ የሥራ እድል ፈጠራ አማራጮችን
ማፈላለግ፣ የዜጎችን ክብር ደህንነት ሞራልና ጥቅም የሚያረጋግጥ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት
በዋናነት በሠራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚመራ ሲሆን ሌሎች ጉዳይ የሚመለከታቸው
የመንግስት መ/ቤቶች ድርጅቶች ማሕበራትና ተቋማት ያቀፈ ይሆናል፡፡ በክልልም በተመሳሳይ ሁኔታ
የዚህ ቡድን አወቃቀር በዋነኛነት ለሰው የመነገድና ሰውን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ተጎጂዎች
ድጋፍ እንክብካቤና መልሶ ማቋቋም ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ ሲሆን ጉዳይ በቀጥታ ከሚመለከታቸው
የመንግስት ተቋማት ተወካዮች በተጨማሪ በጉዳዩ ላይ የሚሰሩ የተለያዩ አለም አቀፍ ድርጅቶችና አገር በቀል
አገልግሎቱን ለመስጠት የተሟላ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት እንዲኖር በማድረግና በአጠቃላይ ከተጎጂዎች
ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ስራ ጋር የተገናኙ አስፈላጊ የአሰራር ስርዓቶችን የሚዘረጋ ይሆናል፡፡ ቡድኑ በዋናነት
በከተማ ስራ ዕድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ የሚመራ ሲሆን ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸውን
መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ያቀፈ ይሆናል፡፡ በክልልም በተመሳሳይ ሁኔታ በክልል
የስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ቢሮ ወይም ከክልሉ ነባራዊ ሁኔታ ይህን ስራ የሚመራው የመንግስት
ያፀደቀቻቸውን እንዲሁም የህግ አካል ያደረገቻቸውን ዓለም አቀፍ ሰነዶች፣ ህጎች ደንቦች ፕሮቶኮሎች
ተፈጻሚነት መከታተልና ማስተግበር፣ የድንበር አካባቢን ቁጥጥር እንዲጠናከር ለጉዳዩ ባለቤቶች የአቅም
ግንባታ ስራን ማከናወን፣ በህግ ጉዳዮች ዓለም አቀፍ ትብብሩ እንዲጠናከር የተለያዩ ፕሮግራሞችን ነድፎ
የሚንቀሳቀስ ነው፡፡ የስራ ቡድኑ የሚመራው በጠቅላይ ዐ/ሕግ ሆኖ የተለያዩ የህግ አስከባሪ አካላትን ያቀፈ
ከመመስረትና የድንበር ቁጥጥር ሁኔታንም የእለት ተእለት ተግባሩ በማድረግ ያከናውናል፡፡ በክልልም
የዚህ የስራ ቡድን ኃላፊነት የተቀናጀ የፍልሰት አስተዳደር ለመዘርጋት የሚያስችል ጥናት ከስራ ቡድኖች እና
ከብሔራዊ የትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር እንዲካሄድ ያደርጋል፤ ከዚህ ቀደም
በፍልሰት ዙሪያ የተጠኑና በየወቅቱ የሚከናወኑ ጥናቶችን በማሰባሰብ ስራ ላይ እንዲውሉ ያደርጋል፤ የከፍተኛ
የትምህርት ተቋማት በፍልሰት ዙሪያ ጥናት እንዲካሄዱ የማስተባበር ስራ የሚሰራ ሲሆን የስራ ቡድኑ
የሚመለከታቸውን አካላት በማስተባበር በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሰብሳቢነት የሚመራ
ይሆናል፡፡ በየክልሉ የሚገኙ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከዚህ የስራ ቡድን ጋር በጋራ እና በቅንጅት የሚሰሩ
ይሆናል፡፡
ይህ የስራ ቡድን በዳያስፖራ ኤጀንሲ ሰብሳቢነት የሚመለከታቸውን ተቋማት በማካተት የተደራጀ ሲሆን
ኃላፊነቱም የዳያስፖራ አባላትን በሀገራቸው የልማት ጉዳይ በተለይም የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ከማሳደግ፤
በኢንቨስትመንት መስክ እንዲሁም በሌሎች ተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ በያገባኛል ስሜት የበኩላቸውን
አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ምቹ ሁኔታዎች መዘርጋታቸውን ይከታተላል፤ ከዳያስፖራው የሚገኙ የእውቀት እና
የቴክኖሎጂ ሽግግር እድሎችን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋቱን ይከታተላል፤
የዳያስፖራው ማህበረሰብ ባህላቸውንና ታሪካቸውን የሚያውቁበትና የሚያዳብሩበት ምቹ ሁኔታዎች
እንዲፈጠሩ ይሰራል እንዲሁም ያስተባብራል፡፡
በክልል ይህን የስራ ቡድን በመስተዳደር ጽ/ቤት ስር የሚገኙት የዳያስፖራ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የሚመራ ሆኖ
የሚመለከታቸውን አካላት በማካተት የሚደራጅ ይሆናል፡፡
የዚህ የስራ ቡድን ዋነኛ ኃላፊነት ከመረጃ አሰባሰብና ትንተና ብሎም ስርጭት ጋር የተያያዙ የአሰራር
ስርዓቶችን በመቅረጽ በተለያዩ ኩነቶች ለአብነት በህዝብና ቤት ቆጠራ ሥራዎች፣ በስነ-ህዝብ እና ሌሎች
የናሙና ጥናቶች ውስጥ የስደት፣ የሀገር ውስጥ መፈናቀል እና አጠቃላይ የፍልሰት ጉዳዮች በማካተት መረጃ
የሚመለከታቸውን አካላት ያማክራል፤ ድጋፍ ያደርጋል፤ ሀገራዊ የተጣጣመ የፍልሰት መረጃ እንዲኖር
ከሚመለካተቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ይሰራል፡፡ በተጨማሪም የስራ ቡድኑ በፍልሰት ጉዳይ
ለሚወሰኑ ውሳኔዎች፣ ለሚወጡ ፖሊሲዎች፣ ህጎች እና ስተራቴጂዎች ግብዓት የሚሆን መረጃ አደራጅቶ
የስራ ቡድኑም የሚመለከታቸውን በጉዳዩ ዙሪያ መረጃ የሚሰበስቡ ተቋማትን በማካተት በማዕከላዊ
በሰው መነገድ እና ሰውን በህገወጥ ድንበር ማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚከናወኑ ተግባራት ብሎም
አጠቃላይ እንደ ሀገር ያለውን የፍልሰት አስተዳደር ስርዓት ለማጠናከርና በአግባቡ ለመምራት እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ
ከፍልሰት ጋር ተያይዞ የሚወጡ ፖሊሲዎችና የእስትራቴጂክ አቅጣጫዎች በተጨባጭ ተግባራዊ ለማድረግ የብሔራዊ
የትብብር ጥምረቱ ከክልሎች ጋር የሚኖረው ግንኙነት መሰረታዊና ወሳኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም ብሔራዊ የትብብር ጥምረቱም ሆነ የስራ ቡድኖች ከክልል የትብብር ጥምረትና የስራ ቡድኖች የሚኖረውን
ግንኙነት ማሰቀመጡ ተገቢ በመሆኑ እንደሚከተለው ለማሳየት ተሞክሯል፡፡
በዕቅድ ዝግጅት የሚኖር ግንኙነት፡- የብሔራዊ የትብብር ጥምረቱ አጠቃላይ እንደ ሀገር በሚከናወኑ ዕቅዶች እና
እስትራቴጂክ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከክልል የጥምረት አደረጃጀቶች ጋር የተናበበ ስራ ለመስራት ያስችል ዘንድ በዕቅድ ዝግጅት
ወቅት የሚኖር ግንኙነት ወሳኝ ነው፡፡ ይህ ማለት በብሔራዊ የትብብር ጥምረቱ ስር የተደራጁት ስድስቱ የስራ ቡድኖች
በክልሎች ከሚደራጁ ተመሳሳይ የስራ ቡድኖች ጋር በዕቅድ ዝግጅት ላይ ወጥነት ያለው እና የተናበበ ዕቅድ ያዘጋጃሉ ማለት
ነው፡፡ ሁሉም የሚታቀዱ ስራዎች በፌዴራል ደረጃ ብቻ የሚፈጸሙ እንዳለመሆናቸው መጠን በዕቅድ ዝግጅት የሚኖር
ግንኙነት በክልል እና በፌዴራል ደረጃ የሚከናወኑ ተግባራትን ለመለየት እና በጋራ የሚፈጸሙ ጉዳዮችንም ለማየት ወሳኝ
ምዕራፍ ነው የሚሆነው፡፡ ስለሆነም የመጀመሪያውና ዋነኛው የግንኙነት ስርዓት በዚህ አግበብ የሚታይ ይሆናል፡፡ እዚህ
ጋር አብረን የምናየው ጉዳይ በፌዴራል ደረጃም ሆነ በክልል ደረጃ አጠቃላይ የጥምረቱን ስራ የማስተባበር ኃላፊነት
የተጣለባቸውን የጠቅላይ ዐ/ሕግ አደረጃጀቶችን ሲሆን እነዚህ ተቋማትም እነደ ስራ ቡድን የሚኖራቸው ግንኙነት እንዳለ
ሆኖ የፌዴራሉ ጥምረት ጽ/ቤት እና የክልል ጥምረት ጽ/ቤቶችም በተመሳሳይ ሁኔታ በዕቅድ ዝግጅት ወቅት የመናበብና
የመቀናጀት ስራ ወሳኝ ነው፡፡ በአጠቃላይ በየወቅቱ በየዘርፉ በሚለዩ የግንኙነት አግባብ ላይ በመመርኮዝ ሌሎች የግንኙነት
ዘርፎችን ይኖራሉ፡፡
ምዕራፍ አምስት
5 የክትትል፤ የድጋፍ እና የግምገማ ስርዓት
1. የክትትል፣ የድጋፍና የግምገማ ሥርዓት፣
በስትራቴጂክ ዕቅዱ ዘመን የዕቅዱን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የክትትል፣ የድጋፍና የግምገማ ሥርዓት መዘርጋት
ያስፈልጋል፡፡
2. የክትትል፣ የድጋፍና የግምገማ ሥርዓት ዓላማ፡-
1. በብሔራዊ የትብብር ጥምረቱ ስትራቴጂ የተቀመጡ ግቦች፣ ውጤቶች፣አቅጣጫዎች የማስፈጸሚያ ስልቶች
የሥራ ቡድኖች በዓመታዊ ዕቅድ ተካተው እየተፈጸሙ ስመሆናቸው ለማረጋገጥ፣
2. የሚከናወኑ ሥራዎች ወደፊት ተጠናክረው የሚሄዱበትን አቅጣጫ ለማመላከት፣
3. በአፈጻጸም ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመለየት፣ ትክክለኛና ወቅታዊ መፍትሔ ለማፈላለግና ድጋፍ
ለመስጠት እንዲሁም ቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ
በዚሁ መሠረት የክትትል፣ የድጋፍልና የግምገማ ዓላማዎችን ለማሳካት ከፌዴራል ጀምሮ በየደረጃው የምንከተላቸው
የክትትል፡ ድጋፍና ግምገማ ስትራቴጂዎች እንደሚከተለው ይሆናል ፦
1. ስትራቴጂክ ዕቅዱን መሠረት ያደረገ ዓመታዊ ዕቅድ በጥምረቱና በሥራ ቡድኖች አማካይነት
ይዘጋጃል፣
2. ስትራቴጂክ ዕቅዱን መሠረት ያደረገ ዝርዝር ድርጊት መርሃ ግብር በጥምረቱና በሥራ ቡድኖች
አማካይነት ይዘጋጃል፣
3. በዕቅድ ዘመኑ የጥምረቱ አባላት የግማሽ ዓመትና ዓመታዊ የአፈጸጸም ሪፖርቶች አዘጋጅው ያቀርባሉ;
4. የአፈጻጸም ግምገማ መድረኮች ይዘጋጃሉ፣ ግብረ መልስ ይሰጣል፣ ምርጥ ተሞክሮዎች ይቀመራሉ፣
5. በተሰጠው ግብረ መልስ መሠረት አስፈላጊው ማስተካከያዎች ይደረጋሉ፣
6. በፌዴራልና በየደረጃው የመስክ ምልከታዎች /ሱፐርቪዥን/ ይደረጋል፡፡ እንዲሁም ሌሎች የግንኙነት
ዘዴዎችን በመጠቀም የክትትል፣ የድጋፍና የግምገማ ሥራዎች ይሰራሉ፣
7. የትራቴጂክ የዕቅዱ የመካከለኛ እና የመጨረሻ ጊዜ አፈጻጸም (ግምገማ ይደረጋል)፣
8. በግምገማው በተገኘው ግብረ መልስ መሠረት ቀሪ የዕቅድ ዘመኑ እንዳስፈላጊነቱ ክለሳ ሊደረግ
ይችላል፡፡
9. በክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ሂደት የብሔራዊ ምክር ቤት ሚና ፣
1. ብሔራዊ የፍልሰት አስተዳደር አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል፣
2. የዕቅድ አፈፃፀም ወቅታዊ ሪፖርቶች የሚመለከታቸው አካላት እንዲያቀርቡ ያደርጋል፣
3. የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቶችን ይገመግማል፣ ግብረ መልስ ይሰጣል፣
4. በአፈጻጸም ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት ክትትልና ድጋፍ ይሰጣል፣የእርምት አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል፡፡
5. በክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ሂደት የብሔራዊ የትብብር ጥምረት ሚና፣
1. የጥምረቱንና የሥራ ቡድኖችን ዕቅድ እንዲዘጋጅ ያደርጋል፣
2. ወቅታዊ የአፈጻጸሞ ሪፖርቶችን ይገመግማል፣ አቅጣጫ ይሰጣል፣
3. በየደረጃው ለተዋቀሩ የክልል የትብብር ጥምረት መዋቅሮች ይከታተላል ይደግፋል፡፡ እንዲሁም የመስክ
ጉብኝት ፕሮግራም ያዘጋጃል፣ ያስተባብራል፣ ግብረ-መልስ ይሰጣል፡
4. በክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ሂደት የየቡድን አስተባባሪ ተቋማት ሚና፣
1. ከስትራቴጂክ ዕቅድ የተቀዳ የቡድን ዓመታዊ ዕቅድ ያዘጋጃሉ፣
2. የዕቅድ አፈጻጸማቸውን ሪፖርት በየጊዜው በማዘጋጀት ያቀርባሉ፣
3. በየደረጃው ለተዋቀሩ የክልል የትብብር ጥምረት የሥራ ቡድኖች ይከታተላሉ፣የደግፋሉ፣ የዕቅድ አፈጻጸማቸውን
ይገመግማሉ፣
4. የየክልሉን የሥራ ቡድኖች ሪፖርት በመሰብሰብ ለብሔራዊ ትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ያቀርባሉ፣
5. የዕቅድ አፈጻጸሙ ከተገመገመ በኋላ በሚሰጣቸው ግብረ መልስ መሠረት የማስተካከያ እርምጃ ይወስዳሉ፡፡