Professional Documents
Culture Documents
የሴቶች አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን
የሴቶች አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን
ይህንን ውሳኔ አብዛኞቹ ጳጳሳት እና ካህናት ተቃወሙት፡፡ ምእመናንም ለሁለት ተከ ፈለ፡፡ ነገር ግን
በፕሮቴስታንት እምነት የተለከፉ አገልጋዮች የራሳቸውን ጳጳስ ሾመው ተሐድሶውን ገፉበት፡፡
ተሐድሶዎቹ ቤተ ክርስቲያኒቱን በፍርድ ቤት ከሰሱ፡፡ በ 1879 ዓም የተጀመረውም ክስ በጁላይ 12 1889
ዓም እኤአ ተጠናቀቀ፡፡ ፍርድ ቤቱም የቤተ ክርስቲያኒቱ ሀብት እና አጥቢያዎች ለሁለት እንዲከፈሉ ወሰነ፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱም በሕግ ለሁለት ተከፈለች፡፡ ተሐድሶዎችም «ማር ቶማ ቤተክርስቲያን´ የሚባል መሠረቱ፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱ ሀብቷን፣ አጥቢያዎቿን እና ገዳማቷን በማጣቷ ተዳከመች፡፡ ሕዝቡም ተስፋ ቆረጠ፡፡ ካህናቱ
ደመወዝ አጡ፡፡ አገልግሎቱንም መስጠት ተቸገሩ፡፡ ምእመኑንም ተሐድሶዎቹ እና ፕሮቴስታንቶቹ ይወስዱት
ጀመር፡፡
በዚህ ሁኔታ ያዘኑት የሕንድ እናቶች ተሰብስበው «አንድ ሆነን ቤተ ክርስቲያናችንን እንታደግ» ብለው ወሰኑ፡፡
በሳምነቱ ቀናት ሩዝ ሲቀቅሉ አንድ እፍኝ ሩዝ በማስቀመጥ በሰንበት ይዘው ለመምጣት ተስማሙ፡፡ ያንን
አጠራቅመውም አብያተ ክርስቲያናቱን አስጠገኑ፡፡ ገዳማቱን አሠሩ፡፡ ለካህናቱ ደመወዝ ከፈሉ፡፡ መንፈሳዊ
ኮሌጅ ከፈቱ፡፡ መም ህራንን አሠለጠኑ፡፡ እንዳሉትም ቤተ ክርስቲያናቸውን ታደጉ፡፡ ዛሬ የሕንድ ሴቶች በቤተ
ክርስቲያናቸው ክህነታዊ ባልሆነው አገልግሎት ሁሉ በመሳተፍ ዕድገት እያስመ ዘገቡ ነው፡፡ እኛስ ጋ?
በቤተ ክርስቲያን የሴቶችን ተሳትፎ በተመለከተ ሁለት ዓይነት ጽንፈኛ አስተሳሰቦች አሉ፡፡ የመጀመርያው
ሴቶች እስከ ክህነት ድረስ በሚደርስ አገልግሎት መሳተፍ አለባቸው የሚለውና ከቤተ ክርስቲያን አመሠራረት፣
ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን እና ከተፈጥሮ ጋር የሚጣረስ አመለካከት ነው፡፡
ሐዋርያት ሁሉም ወንዶች ናቸው፡፡ በጥንቷ የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን የሴቶች ተሳትፎ ክህነታዊ ባልሆነው
አገልግሎት ነበር፡፡ ለሴቶች ክህነት የሚሰጥ ቢሆን ኖሮ ከድንግል ማርያም በተሻለ የቀረበ እና የተገባው ባልኖረ
ነበር፡፡
ሁለተኛው ደግሞ እናቶች እና እኅቶች ምግብ ከማብሰል ቢበዛም ቆሞ ከማስቀደስ ያለፈ አገልግሎት
አይገባቸውም የሚለው እና ሴቶችን ፈጽሞ «የሚያገልለው´ አመለካከት ነው፡፡ ይኼኛውም አመለካከት
ቢሆን ድንግል ማርያም በሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን የነበራትን ቦታ የዘነጋ፣ ጌታችንም ሠላሳ ስድስት ቅዱሳት
አንስት መምረጡን የማያስ ታውስ አስተሳሰብ ነው፡፡
ትክክለኛው መንገድ ከሁለቱም መካከለኛው ነው፡፡ ለእናቶች እና ለእኅቶች ጾታቸውን ያልረሳ፣ደረጃቸውን
የጠበቀ፣በበቂ ሁኔታ ዕውቀታቸውን እና ጊዜያቸውን ሠውተው ሊያገለግሉበት የሚችሉት ተገቢ ቦታ በቤተ
ክርስቲያን ውስጥ ያስፈልጋቸዋል፡፡
እናቶች እና እኅቶች በብዛት የሚሳተፉባት በቤተ ክርስቲያን የታደለች ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያናች ለሁለት ሺ
ዓመታት ከውጭ ሀገር ምንም ዓይነት ንዋያተ ቅድሳትን ሳታስገባ አገልግሎቷን እንድትቀጥል ያደረጓት እናቶች
ናቸው፡፡ አልባሳቱን ፈትለው፣ መጎናጸፊያውን አዘጋጅተው፣ ሞሰበ ወርቁን ፈትለው፣ መገበርያውን መርጠው
አዘጋጅተው፣ ተማሪውን አብልተው አስተምረው፣ ቤተ ክርስቲያኑን ጠርገው፣ ምንጣፉን አራግፈው፣
ካህናቱን አብልተው ለዚህ ያደረሱን እናቶቻችን ናቸው፡፡ የግሪክ አልባሳት ቦታውን የያዙት ከሠላሳ ዓመታት
ወዲህ ነው፡፡
ሌላው ቀርቶ እንደ እነ እሙሐይ ሐይመት፣ እሙሐይ ገላነሽ የመሳሰሉት አንስት ቅኔውን ተምረው፣
በቅኔውም ተመርቀው፣ የቅኔ መምህራን በመሆን አያሌ ደቀ መዛሙርትን አፍርተዋል፡፡ እንደነ እቴጌ እሌኒ
ያሉት ደግሞ የሃይማኖት መጻሕፍትን አበርክተዋል፡፡ እንደ እነ ወለተ ጴጥሮስ ያሉት በሱስንዮስ ዘመን
ሃይማኖታቸውን እየዞሩ አስተምረዋል፣ ገዳም መሥርተዋል፡፡ እንደ እነ ክርስቶስ ሠምራ ያሉት በሃይማኖት
ተጋድለዋል፣ እንድ እነ መስቀል ክብራ ያሉት ከላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንዱን አንጸዋል፡፡
በዚህ አገልግሎት የሚሳተፉት እኅቶች እና እናቶች ግን ለራሳቸውም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን የመከራ ምንጭ
እንዳይሆኑ መመዘኛዎች ያስፈልጋሉ፡፡ እነዚህ መመዘ ኛዎች ታድያ ወንዶቹንም የሚመለከቱ ናቸው፡፡
መሆን አለባቸው፡፡
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገባቸው እናቶች አና እኅቶች በተገቢው ቦታ እንዲያገለግሉ ካላደረግን
በገንዘባቸው የሚመኩ፣ ሥነ ምግባር የሌላቸው፣ ሴትነ ታቸውን ለክፉ ሥራ የሚጠቀሙበት፣ ደረጃቸውን
የማያውቁ፣ እነርሱ ተሰድበው ቤተ ክርስቲያንን የሚያሰድቡ፣ ለአባቶች የስሕተት ምንጭ የሚሆኑ ሴቶች
ቦታውን ይዘው መከራ ያመጡብናል፡፡
35 comments:
1.
ዳኒ ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡፡
መልካም እይታ ነው ሴት እናቶቻችን እና እህቶቻችን ሊሰሩት የሚገባውን አሳይቶናል
Reply
2.
ወቅታዊ ጉዳይ በማንሳትህ በጣም አመሰግንሃለሁ ዲ.ዳኒ፡፡ ሴቶቻችን ከእልልታ ባለፈ የጎላተሳትፎ በቤተክርስቲያን
ዉስጥ ሲያደርጉ አይታዩምና መልካም ብለሃል፡፡ እንደ እኔ ግን የችግሩ መንስኤዎች እኛዉ ወንዶች ሳንሆን አንቀርም
ባይ ነኝ፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን ለሴቶች የምትፈቅደዉን አገልግሎት በደንብ ስለ ማናዉቅ ሴት ይህ
አልተፈቀደላትም እያልን ክልከላዉን እናበዛለን ይመስለኛል፡፡ አፍ አዉጥተን ባንከለክል እንኳ በአይናችን
እናስደነግጣቸዋለን፡፡
እግዚአብሔር የአገልግሎት ዘመንህን ያርዝምልህ፡፡
Reply
3.
Reply
4.
100 % agreed !
Reply
5.
dani i do agree with all ur idea.ሴቶች የቤተክርስቲያን ትልቅ ፈተናዎች እየሆኑ ነው በተለይ አባቶች ከሴቶች
ምክር ለመቀበል በጣም ጥንቁቅ መሆን አለባቸው። ነኮሳት አባቶቻችን በሁሉም ነገር የሚረዳቸው አስተዋይ ረድእ
የሚያስፈልጋቸው ሲሆን ቢችሉ ምግብ እንኳን በወንዶች እንዲሰራላቸው ማድረግ ቢችሉ ፡ ባይቻል ግን
የቀረቧቸውን ሴቶች በአስተዳደር ጉዳይ እንዳይገቡ ማድረግ (ሃላፊነት ተሰጥቷቸው ካልሆነ) ግድ ነው። አሁን አሁን
ግን እንደምንሰማው ሁሉም አባት ምንአልባት ሁሉም ጳጳስ አንድ አንድ ዔልዛቤል አለው። በወሬ ፡ በአስተሳሰብ ፡
በስራ ተጽእኖ የምታሳድር። አባቶች ምን አለ ስለሁሉም ነገር አመዛዝነው ማድረግ ቢችሉ ፡ የሰው ወሬ ባይሰሙ ፡
በራሳቸው አይን ያዩትን ለቤተክርስቲያን የሚጠቅመውን ብቻ ቢያደርጉ ብሎ በሚያስቆጭ ሁኔታ። አቤቱ
አባቶቻችንን ጠብቅ እባክህ
Reply
6.
I do agreee what ever you raised here. I wanna to draw your attention , especially,to two
points
1. እነርሱ የቤተ ክርስቲያንን ነገር በሚገባ ካወቁ ልጆቻቸውን ለቤተ ክርስቲያን የሚመቹ አድርገው ማሳደግ
ይችላሉ፡፡
This reminded me what HH Pope Shenuada III said for an interview he had with a
westoxicated journalist; "Why you (Orthodox)are not allowing priesthood of women",
HH was asked. They (women)have had more than this, "they are the one who give us
bishops, evanglists, priests, deacons.....", HH Pope Shenuada replied.So, having ritually
coached women is the timely necessity for our church.
2. «ሴት የላከው ጅብ አይፈራም´ ይባላልና ወንዶቹን በትክክለኛው መንገድ እንዲጓዙ መንገዱን ማመላከት እና
መግፋትም ይችላሉ፡፡
This is the one of the nicest observations of you. Dani, we have lost so many brothers to
the Protestant churches as they have used this principle effectively. I have lost one of my
friend who joined them due to love a girl there.
3. Your views are supported by economic philosophies too. Let me quote one of the
bests, "It must be remembered that aesthetic tastes and prefernces are usually guided by
the women in the family". We ususally heard of the fact that "missing women in an
economy means missing half of labour force;above and more, missing the positive
external effects due to elited women". It is not surprise, given this, to set empowering
women at the top of the Millenium Development Goals (MDGs)
4.At last, but not least, the trend of Indian Orthodox Church women is still visible. This
trend can easily seen from the fact that most of church business groups (they have so
many colleges and schools inspite of thier faithful number, by the way)have in women in
thier top positions. I was speechless, while I saw a women (who is PhD actually)adresses
a speech for the crowd that get together for special Christmas festival. I wondered to
happen in out church, many thanks to you to whom you raised the isssue timely.
I hope many thoughts will be exchanged over this issue.Thus, waiting them as usual
eagerly!
Reply
7.
Reply
8.
Reply
9.
Reply
10.
+++
ድንቅ የ 21 ኛው ክ/ዘመን አመለካከት ይህ ነው። ቤ/ክ ከተዘፈቀችብት ችግር ትወጣ ዘንድ የመንፈሳውያት
እህቶቻችንና እናቶቻችን አስትዋጾ ቀላል አይደለምና ከሰ/ት/ቤት ጀምሮ በየደረጃው ተግባራዊ ልናደርገው ይገባል።
ይህን ቀድመን ጀምረነው ቢሆን ኖሮ ዛሬ እንደ እጅጋየሁ ያሉ በጥባጮች በቤተ ክርስቲያናችን አይፈነጩባትም
ነበር።
እግዚአብሔር ይስጥህ ዲ/ን ዳኒ
ፍስሓ
Reply
11.
Reply
12.
Daniel you are trying to teach people the role of women in the church. While you are
talking about the church you never mention what the holy bible teachs about the role of
women in church.What kind of christianity is this (that you are teaching) that doesn't base
its thinking and practice on the bible teaching but on self-annointed (self-ordianed to
teach) indivduals' opinions (view) or some church practice like you mention (in
India).This is deceptive way of devil to pervert orthodox christians from Gospel(Holy
bible). Please in the name of Our Lord and Saviour Jesus Chrsit name ,come to your
sense and stop misleading people in pretext of "orthodoxawi theaching"
Reply
13.
by the way,
if you need to find unique typography, you can go to our website.
best regards;
Reply
14.
Dear Dn Daniel,
I loved all of your issues, but this one is the best one. I thanks God for giving you all
rounded knowlege. Do you know most of the points which you raised why woman are
better than men, are scientifically approved, so many article wrote on it.
The wise manegement ablity of woman can be seen from your mum, sister and wife. You
know if woman are in working team that team is very peacful and joyful. But the number
of the woman should be below half of the team, unless the opposite might happen.
I wish a happy new year for your family
Reply
15.
Reply
16.
AnonymousSeptember 8, 2010 5:14 PM
ከደብረ ቁሰቋም
ይእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅር ለናንተ ይሁንና ወንድማችን የጻፈው ጽሁፍ ለሁላችንም አስተማሪ ከመሆኑም በላይ
ለወደፊቱ ምን ብናደረገ ወይም ምን ማድረግ አለብን የሚለውን የሚለውን ጭምር የሚያሳስብ መላእክት ያለው
ነው።በቤተክርስትያን የእናቶችና የእህቶች አገልግሎት ቀላል እንዳልሆነ ሁላችንም ልንገነዘበ ይገባል.
እንኩዋን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ
Reply
17.
Reply
18.
My message is to the guy above, who tried to criticize Daniel's article for not being
"Orthodoxawi".
Please, try to see positively where the deacon is trying to point at for the emancipation of
our church from the shackles of sin and indolence.
Stay blessed,
Reply
19.
Reply
20.
yes it is a very great idea. our sisters also should get closer to the church services other
than the ordinary activities they have been thru
Reply
21.
ቃለ ሕይወት ያሰማልን !ትክክል ነው ! የቀደሙ እናቶቻችን ለቤተ ክርስቲናችን ለሀገሪቱም ትልቅ አስተዋዸ
አድረገዋል ለትውልዱም የሚተርፍ ስራ ሰርተው አልፈዋል ፡፡ በዚሀ ዘመን ያለን እናቶቸ ሆንን እህቶቸ ከማጀት
ወይም ከቤታቸን ባለፈ ዲ.ዳንኤል እንዳልከው በቢሮ ስራ ላይ ተሰማርተን ልንገጘኝ እንችል ይሆናል እንጂ
ለትውልድ የሚተላለፍ ሀገርን የሚያኮራ ለቤተ ከርስቲያናችን የሚበጅ ተግባሮችን አልተገበርንም እየተገበርንም
አንገጘም፡፡ በእውነቱ በሚገባ ልናጤነው ይገባል በትውልዱም እንወቀሳልን እንደ እናቶቻችን ያለ ጀግንነት
ይጠበቅብናል በከፉ ስራም የምንጠራ መሆን የለብንም እናቶቻችን ያለፉበትን ዘመን እኛ ዛሬ እንድገመው በአዲሰ
ዘመን አዲሰ ስራ አዲስ መንፈስ ይዘን መነሳት ይኖርብናል፡፡
ዘ አርሴማ
Reply
22.
23.
Dn Daniel as u explain our sisters doing in our orthodox church is infinite till now. even
now they are working in sebeka gubae as the member of church administration is
apriciable. to be enhanced such kind of usable service first we all orthodox church
members seport them, second u yourself write such kind of supportive education write on
easily availabeld ours' news papers, because u now the access of internet very limitted to
us.
Egeziabehere Yesetelgne!
mulugeta negn from jimma.
Reply
24.
ነገሩ ጥሩ ነው ግን በአብዛኛው ሴቶች ቤተክርስቲያነ አካባቢ ለሚነሱ ስህተቶች እንደ ምክንያት እሆኑ ነው
የሚታየው ለምሳሌ ለአባቶች እና ወንድሞች መሳሳት ዋነኛዎቹ ናቸው
የጥንት አባቶቻችን እኮ በጣም አርቆ አሳቢዎች ናቸው ደግሞም ጸጋ መንፈስ ቅዱስ አልተለያቸውም ነበር በዚህ
ሁኔታ ውስትጥ ሆነው ሴቶች ጥሩ ችንደሆኑ በያውቁም የመመጣውን ችግር አስቀድመው በማየት ብዙም ወደ ቤ/ክ
አገልግሎት እንዲቀርቡ አያበረታቱም ቤተክርስቲያን ፈተና ያለባት ቦታ ስለሆነች እነርሱን ወደዚ እንዲቀርቡ
ማድረግ ፈተናውን ማብዛት ይመስለኛል ብርግጥ በጥንቃቄ ከሆነ ያነሳሀው ሃሳብ ጥሩ ነው ዐንድ ቦታ የገጠመኝ
ችግር ስለነበረ ነው ፡፡
ሊ/ስ አዩ
Reply
25.
I totally disagree with the above comment. I don't think the women are to blame for most
of the problems facing our church. After-all, it is the men who are in position of power
and they are the one running havoc in the church.
I also reject the idea that having a greater involvement of women will somehow
exacerbate the situation. What is the evidence for that? You may point to a few women
who have become a bad influence on church leaders but they are not representative of the
majority the women in our church.
I am proud to say that Ethiopian women are for the most part well-behaved, hardworking,
and devout Christians. They need to be encouraged and empowered to broaden their
service to the church.
Reply
26.
I agree with kaleab. Men usually acuse women for their wrong doings. the basic thing is
trying to find a reason for your failures can not cure from your sins. Please, think twice
before you write. As dn. Daniel pointed out above, the church needs to have mechanisms
to evaluate the overall personality and "menfesawi tinkare" of a woman before giving key
role. This should of course be done for men as well. Haimanotawi meseret yelelachew
wendoch meselugn betechristianachinin eyanawetsuat yalut. So dear annonymous, don't
make hesty generalizations.
There are very strong women who are doing great for the church. Don't try to break their
heart.
Reply
27.
+++
D/n Daniel Happy new year.
I wish for you & your family zemene lukas be promises of good health, peace and
stability,new more dreams to fulfill,
new goals to achieves and new joys to discover.
Reply
28.
Reply
29.
AnonymousSeptember 15, 2010 3:43 PM
Reply
30.
kale hiwoten yasemalen abete ena be sedete yemnenure setuoche bebelte kale hiwote
yasemalen enlalen betecherstyen seratua temskakel senel semeye yatanbete seate
wendmachen egziabher angerhe yehene mekre sethacheu ewnete sentu yanbeuo yeuone
abesuo abatuoch melequsate ena bezhe ketel wendmachen d.d
Reply
31.
ከአንጎላ
ቃለ ህይወት ያሰማልን!!!
በጣም አስደሳች እይታ ነው
Reply
32.
Qale Hwiot Yasmalne , its seems nice page but i want to gave a comment , why u post
the sebket link if u post it its more intrested page
Reply
33.
AnonymousSeptember 18, 2010 9:24 PM
Reply
34.
Reply
35.
kalehiwot yasemalin.
Reply