Professional Documents
Culture Documents
Haile
Haile
የላፍቶ ሌንጫ ቅ/ገ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤት በተለያዩ ግዜያት በመንፈሳዊ አገልግሎት ሲጠናከርና እንዲሁም አንዳንድ ግዜ
ደግሞም አባላቱ በተለያዩ ምክንያቶች ሲበተኑ(ከአገልግሎት ሲቀሩ) ይስተዋላል። ከዚህም በተጨማሪ በማህበረሰቡ
ህሌና የመንፈሳዊ አገልግሎት ይዘት እንዳይኖረው አድርጎታል። በመሆኑ እነዚህን እና መሰል ችግሮችን ለመፍታት
ወይም ለመታደግ የሚከተሉትን የመፍትሔ ሀሳቦችን እንዳቀርብ ተገድጃለሁ።
3.በዕለቱ ፕሮግራም ሰባኪ መምህራን መጋበዝ ( መምህራን በደብሩ ወይም በቀድሞው የሰ/ት/ቤት አባላት ከሌለ)።
4. የቀድሞ የሰ/ት/ቤት አባላትን በርቀት ወይም በማህበር መልኩ ማደራጀት እና የራሱ የሆነ አመራሮች እንዲኖራቸው
ማድረግ።
5. ሰናይ (ጥሩ) መንፈሳዊ ይዘት ያላቸው እህትና ወንድሞችን ከቀድሞ የሰ/ት/ቤት አባላት ወይም አሁን እያገለገሉ
ከአሉ አባላት ጋር ማደራጀት።
4.የሰ/ት/ቤቱ አባላት ምንም ዓይነት የደህነት ስጋት እንዳያድርባቸውና ጠንክረው በቤተክርስቲያን የህይወት
ዘመናቸውን እንዲያሳልፉ ለማስቻልና በቤተክርስቲያን ላይ የሚደርሱ ችግሮችን እንዲታደጉ ለማድረግ።
10.በስራ ወይም በተለያየ ምክንያት ከአከባቢው ርቀው ሲሄዱ በወቅቱ የነበራቸው ቆይታ ቤተክስርስቲያኑንና
ሰ/ት/ቤታቸው እንዲያስታውሱ ትልቅ እድል ይፈጥርላቸዋል።
2.ጠንካራ አገልጋዮች እንዲኖሩ ማስቻል። ለምሳሌ በአግባቡ ትምህርታቸውን የተማሩ ዲያቆናት፣ካህናት፣ መርጌታ፣
መምህራን.... የመሳሰሉትን
4.ቤተ ክርስቲያናችን የሚገጥማትን ማንኛውንም ዓይነት ችግሮች ያለ ማንም ጣላቃ ገብነት በተገልጋዮቿ ብቻ
መፍትሔ እንድታገኝ ለማስቻል።
5.በተለያየ ሱስ የተጠመዱ እህትና ወንድሞችን በመምከርና የመንፈሳዊ ህይወት ምንነት እየኖሩ ለማሳየት ያስችላል።
6.ብቸኝነት እንዳይሰማቸው ያስችላል። ለምሳሌ እህት ወይም ወንድም የሌለው /የሌላት ስለሚኖሩ ለነርሱ ታላቅ ዕድል
ይሆናል።
3.በማህበሩ ውስጥ ያሉ አባላት በተለያየ ምክንያት የሚገጥሟቸውን ከአቅም በላይ ችግሮች በጋራ በመተባበር መፍታት
ለማስቻል።
ለምሳሌ፦
እግዚአብሔር አይበለውና አንድ እህት ወይም ወንድም በአደረበት የህመም ደዌ ለህክምና ወጪ 20,000 ብር ብትጠየቅ
ወይም ቢጠየቅ ነገር ግን የመክፈል አቅም ባይኖራት ወይም ባይኖረውም እንዲሁም ደግሞ የማህበሩ አባላት ብዛት
ሁለት መቶ ቢሆን እያንዳንዱ 200 ብር ብቻ በማዋጣት የእህታችንን ወይም የወንድማችንን ህይወት መታደግ
እንችላለን።
4.ሰበካ ጉባኤ አገልግሎት በቤተክርስቲያናችን በመክፈል በአሉበት ቦታና ግዜ ሁሉ የቤተክርስቲያን አገልግሎት ማግኘት
እንዲችሉ ለማድረግ ያስችላል።
6.በተቻለ መጠን በዓላት አብሮ ለማክበር። ለምሳሌ ጥምቀት፣ ፋሲካ፣ ገና፣ መስቀል....
ታዲያ ይህን ሁሉ አስተዋጽኦ ያለው ማህበር እስከ አሁን ድረስ መደራጀቱ አያስቆጭም ትላላችሁ እህትና ወንድሞቼ
እንዲሁም እናትና አባቶቼ? ስለዚህ ሁላችንም እናስብበት ለማድረግም እራሳችንን እናዘጋጅ ያለማንም ቀስቃሽና
ጎትጓች።
ይህንንም ሀሳብ የሚመለከተው ሁሉ በጥልቀት በመመርመርና በማገናዘብ የየራሱን ሀሳብ ወይም መፍትሔ እንዲሰጥ
በልዑል እግዚአብሔር ስም እጠይቃለሁ።
አስጀምሮ ላስጨረሰኝ ለልዑል እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይግባው፣ ለወለደችው ለእናቱ ለቅድስት ድንግል ማርያም
ክብርና ምስጋና ይድረሳት እንዲሁም የጻርቃን ሰማዕታት የአበው ቅዱሳን የመላእክት ስማቸው እርሱ ልዑል
እግዚአብሔር በአከበራቸው ልክ ክብርና ምስጋና ይድረሳቸው።