Professional Documents
Culture Documents
Betesayda
Betesayda
መስራቾች:
በተለያየ ምክንያት ከወሊሶ ወጥተው በአዲስ አበባ የሚገኙ የቤተሳይዳ ደብረምጥማቅ ቅድስት ድንግል ማርያም ሃይመተ
ዲዮስቆሮስ ሰንበት ትምህርት ቤት ልጆች፤
- የሃይመተ ድዮስቆሮስ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በትምህርት፣ በሥራ፣ ወዘተ ምክንያቶች ከወሊሶ ከወጡ
በኋላ፣ በሚኖራቸው አቅም ልክ ለሰንበት ት/ቤታቸው የበለጠ አስተዋፅኦ ማድረግ ሲችሉ፣ በቦታ ርቀት በመገታት፣
ሰንበት ት/ቤቱን መልቀቃቸው ለዓመታት በመቀጠሉ፤
- ይሄም ሰንበት ት/ቤቱን በቀጣይነት ነባር አባላት በማሳጣት ከአቅም በታች እንዲከውን በማድረጉ፤
- በአዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች ለሚገኙ ነባር አባላት፣ እንደ ስበት ማዕከል ሊያገለግል የሚችል ሕብረት
በማቋቋም፣ የሃይመተ ዲዮስቆሮስ ሰንበት ትምህርት ቤት ነባር አባላትን እንደ አባል መቀጠል የሚችሉበትን
መንገድ ምቹ በማድረግ፣ ሰንብት ት/ቤቱ ከነባር አባላቱ ማግኘት የሚገባውን በቀጣይነት ማግኘት መቻሉን
ማረጋገጥ በማስፈለጉ፤
የሕብረቱ አባላት
- ከወሊሶ ውጪ በአዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች የሚገኙ የሰንበት ት/ቤቱ ነባር አባላት
- የሰንበት ት/ቤቱ አባል ለመሆን የሚፈልጉ፣ ነገር ግን በአዲስ አበባ የሚገኙ የቤ/ሳይዳ ልጆች
የሕብረቱ ርእይ
የሃይመተ ድዮስቆሮስ ሰንበት ትምህርት ቤትን በ 2020 ዓ.ም በደቡብ ምእራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ትልቁ ሰንበት ት/ቤት እና
ስመ-ጥር መንፈሳዊ ተቋም ማድረግ፤
የሕብረቱ ተልዕኮ
በእውቀት ሁሉ የበረቱ፣ በመንፈሳዊ ፍሬዎች ያጌጡ፣ ለሐዋርያዊ አገልግሎት የሚተጉ፣ መንፈሳዊ አገልግሎቷን የሚረከቡ፣
የቅድስት ቤ/ክርስቲያንን እምነት የሚያስተምሩና የሚያስጠብቁ፣ በሀገራዊም ሆነ በዓለም ዓቀፋዊ ክስተቶች ላይ በጎ ተጽዕኖ
መፍጠር የሚችሉ የቤተክርስቲያን ልጆችን ማፍራት፤
እሴቶች
- መንፈሳዊነት
- መደጋገፍ፣ አንድነት
- ዘመኑን መቅደም
- ተምሳሌትነት
ዓላማ
- የሰንበት ትምህርት ቤቱን መሰረተ-ልማቶችንና አሰራሮችን ማዘመን፣
- ለአባላት የቤተ ክርስቲያን ዕውቀትና ሕይወት ተኮር ትምህርትን ማስተማር፣
- መንፈሳዊ ኮርሶችን ቀጣይነትና ጥልቀት ባለው ሁኔታ በመስጠት፣ ሰንበት ት/ቤቱ በመምህራን ሙሉ በሙሉ ራሱን
ማስቻል፣
- በቂ ሪሶርስ ያለው ቤተ መፃህፍት ማደራጀት፣
- የሰንበት ት/ቤቱ አባላት በአለማዊ ትምህርታቸው የላቀ ውጤት ባለቤት እንዲሆኑ ማስቻል፣
- ሐዋርያዊ አገልግሎትን ከወሊሶ ከተማ ወጣ ብለው በሚገኙ የአገልጋይ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች
ባሉ አብያተ ክርስቲያናት በተለያየ መንገድ (በጽሁፍ፣ በአካል፣ በድምፅ፣ በቪዲዮ) መስጠት