Professional Documents
Culture Documents
Eotc
Eotc
17/11/2015
ለ:ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሚድያ ዝግጅት ክፍል
በቅድሚያ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እያልን ማኅበራችን ማኅበረ ኀዳፌ ነፍስ ላለፉት ሦስት
አመታት የበገና፣ክራር እና መሰንቆ መሳሪያዎችን በማስተማር ከ 300 በላይ የሚሆኑ ኦርቶዶክሳዊያን ያስመረቀ
ሲሆን። በተለያዩ የቤተክርስቲያን አገልግሎቶች ላይ ተማሪዎቹን በማሳተፍ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት
እየሰጠ ያለ ማኅበር ሲሆን።
እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ በ 2015 ዓ.ም ከሦስት ወር ጀምሮ እስከ ስድስት ወር ማኅበሩ
ሲያስተምራቸው የነበሩትን የበገና፣የክራር እና የመሰንቆ ተማሪዎች በቀጣይ ወር ማለትም በነሐሴ 27 ቅዳሜ
ዕለት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ባለው ትልቅ አዳራሽ ምርቃቱን ለማድረግ በሥራ ላይ
ይገኛል።
ስለዚህም የቤተክርስቲያናችን ትልቁ ሚዲያ የሆነው ኢ.ኦ.ተ.ቤ ቴቪ በእዚህ መርኀ ግብር ላይ ይገኝልን ዘንድ
ከላይ በጉዳዩ እንደጠቀስነው እንጋብዛለን። መርኀ ግብሩን 7:00 የሚጀምር ሲሆን እስከ 10:30 የሚቆይ
ይሆናል።
የማኅበሩ ሰብሳቢ