Professional Documents
Culture Documents
50291
50291
ሂሩት መለሰ
ብርሃኑ አመነው
አልማው ወሌ
ዓሊ መሐመድ
ፍርድ
ጉዳዩ የቀረበው አመልካች የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 80158 ነሐሴ 26
ቀን 2001 ዓ.ም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ
እንዲታረምልኝ በማለት ህዳር 1 ቀን 2002 ዓ.ም በማመልከቱ ነው፡፡ ክርክሩ በመጀመሪያ የታየው
በፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ነው፡፡ ተጠሪዎች አመልካች የከሰረ በመምሰል በሠራተኛ ቅነሳ
በሚል ከሥራ ያሰናበታቸው በመሆኑ ስንብቱ ሕገ ወጥ በመሆኑ ካሣ፣ የስንብት ካሣ፣ ጫማና ቱታ
የዓመት እረፍት በገንዘብ ተቀይሮና የጡረታ መብታችን እንዲጠበቅ ውሣኔ ይሰጥልን በማለት
በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ክስ አቀርበዋል፡፡ አልካች በበኩሉ በተከሳሽነት ቀርቦ ተጠሪዎች
ከሥራ የተሰናበቱት ድርጅቱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ባከናወነው የሠራተኛ ቅነሳ ነው፡፡ ስለዚህ ውሉ
እረፈት ክፍያ ተከፍሏቸዋል፡፡ ጫማና ቱታ ለሥራ የሚሰጥ በመሆኑ ሊጠይቁን አይገባም የሚል መልስ
ሰጥቷል፡፡
1
የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች ከሥራ የተሰናበቱት በህገወጥ መንገድ መሆኑን
አላስረዱም አመልካች አሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 29 መሠረት ባከናወነው
የሠራተኛ ቅነሳ ተጠሪዎች ከሥራ የተሰናበቱ በመሆኑ በህገወጥ መንገድ የሥራ ውሉ በመቋረጡ ካሣ
እንዲከፈላቸው ያቀረበት ጥያቄ ተቀባይነት የለውም፡፡ አመልካች የአመት እረፍት ክፍያ የሁለት ወር
ደመወዝ የማስጠንቀቂያ ክፍያና ካሣ የከፈለ መሆኑ በጽሑፍ ማስረጃ አስረድቷል፡፡ ተጠሪዎች የሶሶት
ወር የማስጠንቀቂያ ክፍያ እንዲከፈላቸው የጠየቁ ቢሆንም ክፍያው በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ
35(መ) መሠረት የተከናወነ ስለሆነ በህጉ መሠረት የተፈፀመ ነው፡፡ ጫማና ቱታ ለከሳሾች
(ተጠሪዎች) በገንዘብ ተለውጦ ይሰጣቸው፡፡ አመልካች ካሣ የከፈለ መሆኑ ቢረጋገጥም ካሣው በአዋጅ
ቁጥር 377/96 አንቀጽ 40(3) መሠረት በማድረግ አስልቶ አልከፈላቸውም በማለት ልዩነቱን በህጉ
መሠረት አስልቶ አመልካች ለተጠሪዎች እንዲከፍል ውሣኔ ሰጥቷል፡፡ በዚሁ የጡረታ መብት
ለሚመለከተው አካል ያቅርቡ በማለት ወስኗል፡፡ ተጠሪዎች በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ
ለከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርበዋል፡፡ የከፍተኛ ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ
ማስጠንቀቂያ ሣይሰጥ የሥራ ውላቸው መቋረጡ ተጠሪዎች ከሥራ የተሰናበቱት በህገ ወጥ መንገድ
ሊከፍል የሚገባውን ካሣ በአንቀጽ 43(4)ሀ የሁለት ወር የማስጠንቀቂያ ደመወዝ ክፍያ በአዋጅ ቁጥር
377/96 አንቀጽ 41 አንቀጽ 77(5) አንቀጽ 39(1)ሐ) እና 40(2)(3) መሠረት እንዲከፍል የጡረታ
መብት ፎርሟሊቲ አሟልቶ ለማህበራዊ ዋስትና ባለሥልጣን እንዲልክ በማለት ውሣኔ ሰጥቷል፡፡
ክፍያ በራሱ አነሳሽነት በማንሣት እንድንከፍል ወስኗል ለጉዳዩ አግባብነት የሌላቸውን ድንጋጌዎነች
ተገቢነት የሌለው ክፍያ እንድንከፍል ወስኗል፡፡ ክፍያ የፈፀምን መሆኑን በፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ
እንድንከፍል በመወሰን መሠረታዊ የህግ ስህተት የፈፀመ መሆኑ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልን በማለት
2
አመልክቷል፡፡ ተጠሪዎች በበኩላቸው አመልካች የሥር ዋስትናችንን በማሣጣት በህጉ መሠረት
ሊከፍለን የሚገባውን ክፍያ ሣይከፍል ያለማስጠንቀቂያ ከሥራ ያሰናበተን በመሆኑ የከፍተኛው ፍርድ
ቤት ስንብቱ ህገወጥ ነው በማለት አመልካች በአዋጅ ቁጥር 377/96 ድንጋጌዎች መሠረት የለያዩ
ክፍያዎነችን እንድንከፍል የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የለበትም በማለት መልስ
ሰጥተዋል፡፡
ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር የቀረበው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም ጉዳዩን
377/96 አንቀጽ 29 ድንጋጌ ተከትሎ ባከናወነው የሰራተኛ ቅነሳ መሆኑን የከፍተኛው ፍርድ ቤት
ተጠሪዎችን ከሥራ መቀነሱን ያረጋገጠ መሆኑ የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በውሣኔው ገልፆል፡፡
ያሰናበታቸው በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 29 መሠረት ባከናወነው የሠራተኛ ቅነሣ መሠረት
በሚል ምክንያት መሆኑን ከከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሣኔ ለማረጋገጥ ችለናል፡፡ ከዚህ አንፃር
377/96 አንቀጽ 29 የተደነገጉ መስፈርቶች አሟልቶ መሆኑን በውሣኔው ካረጋገጠ በኋላ ከሥራ
ደመወዘ በአንድ መቶ ሰማኒያ ቀናት በማባዛት የመክፈል ሀላፊነት አለበት በማለት የአዋጅ ቁጥር
377/96 አንቀጽ 43(4)(ሀ) በመጥቀስና ለድንጋጌው የተዛባ ትርጉም በመስጠት የሰጠው ውሣኔ ተገቢ
3
መሆኑን በሰነድ ማስረጃ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለጽ ውሣኔው የሰጠባቸውን የሁለት ወር
የማስጠንቀቂያ ክፍያ የአመት እረፍትና የሥራ ስንብት ክፍያ የከፍተኛው ፍርድ ቤት አመልካች
ለተጠሪዎች በድጋሚ እንዲከፍል የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 29 መሠረት የሠራተኛ ቅነሳ በሚደረግበት ጊዜ
በመለየትና በመያዝ ጭብጡን ለመፍታት አግባብነት ያላቸውን የፍሬ ጉዳይ እና የህግ ነጥቦች በመለየት
ሣይሆን አግባብነት በሌለው ሁኔታ የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሣኔ የሻረው መሆኑን
ተገንዝበናል፡፡ ስለሆነም ከላይ በዝርዝር የገለጽናቸው ምክንያቶች የከፍተኛ ፍርድ ቤት የአዋጅ ቁጥር
377/96 የተለያዩ ድንጋጌዎች በመጥቀስና በመተርጐም የሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት
ውሣኔ
ፀ/መ