Professional Documents
Culture Documents
5
5
ንግድ ቢሮ
የብሎክ ማናጅመንት
(ቀጠና-ተኮር የክትትልና ቁጥጥር የአሰራር ስርዓት)
አሰራር መመሪያ (ረቂቅ)
አዲስ አበባ
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌ
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ የብሎክ ማናጅመንት (የቀጠና-ተኮር የንግድ ክትትልና ቁጥጥር የአሰራር ስርዓት) የአሰራር ስርዓት
መመሪያ ቁጥር ----------/2013" ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
1
2. አጠቃላይ ሁኔታዎች
2.1. ስያሜ
ይህ መመሪያ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የብሎክ ማኔጅመንት የንግድ ክትትልና ቁጥጥር የአሰራር መመሪያ
ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
2.3. የመመሪያው ግብ
የዚህ መመሪያ ግብ የአዲስ አበባ የከተማ አስተዳደር የንግድ አሰራር የንግድ አዋጆችን ደንቦችና የአሰራር
መመሪያዎችን ተከትሎ እንዲከናወን በማስቻል ፍትሃዊ፤ ፈጣን፤ ውጤታማ፤ ጥራትና ምቹነት ያለው አገልግሎትና
የንግድ ክትትልና ቁጥጥር አሰራር ስርዓት እንዲኖር በማድረግ ደንበኛውን/ተገልጋዩን/ ማርካት ነው፡፡
የንግድ የአሰራር ስርዓቱን ህጋዊነት እንዲላበስ በማስቻል የወጡ አዋጆችን፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና
የአሰራር ማንዋሎችን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ በሁሉም ክ/ከተሞች እና ወረዳዎች ወጥ ለማድረግና
የበለጠ ግልጸኝነትን ይፈጥራል፣
በባለሙያው፣ በነጋዴውና በሸማቹ ዘንድ የሚታዩ አላስፈላጊ መጉላላት ጊዜንና ንብረትን በአግባቡ
ለመጠቀም ይረዳል፣
በህገ-ወጦች የንግድ ስራ ተሰማርተው የሚገኙ በሚገኙት ላይ የሚወሰደዉ እርምጃ ፍትሃዊ እና
አስተማሪ እንዲሆን ያስችላል፣
የንግድ አሰራር ስርዓት ለማስያዝ ስልጣንና ኃላፊነት የተሰጠው በየደረጀው ለሚገኘው አስፈፃሚ አካላት ግልፀኝነት፣
ተጠያቂነት ለማስፈን ይረዳል፤
ባለሙያዎች በኃላፊነት በያዙት ብሎክ/ቀጠና/ የሚገኙ ውጤቶችን ለማበረታታትና ለሚፈጠሩ
ክፍተቶች የተጠያቂነት ስርዓትን ለመዘርጋት ያስችላል፤
2
በያንዳንዱ የንግድ ድርጅት የሚዘረጋ የብሎክ ማናጅመንት የንግድ ክትትልና ቁጥጥር የአሰራር ስርዓት ነው፡፡
ከተጠቃሚነት አንጻር በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ የሚገኙ የንግድ ባለሙያዎች፣ ህጋዊ ነጋዴዎች ፣ ሸማቾችና
ሌሎች ባለድርሻ አካላትና ለተቋሙ ደንበኛ የሆኑ ሁሉ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
ክፍል ሁለት
3
2.6 . የመለኪያ መሣሪያን ትክክለኝነት ማረጋገጥ /verfiction/፡- ማለት የመለኪያ መሣሪያ በሕግና በአስገዳጅ የኢትዩጵያ
ደረጃዎች የተቀመጡ መስፈርቶችን ማሟላቱን ለማረጋገጥ የሚደረግ ምርመራን ፈትሸን ምልክት ማድረግንና የትክክለኛነት
ማረጋገጫ ሰርተፍኬት መስጠትን የሚጨምር ተግባር ነው
2.7 “የንግድ ሕግ”፡- ማለት በኢትዮጵያ የወጣ የንግድ ህግ ማለት ነው
2.8 . "ሰው" ማለት ማንኛውም የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው፡፡
2.9 . አዋጅ ፡-ማለት እንደ ሁኔታው የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008 እና የንግድ ውድድርና ሸማች
ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006 ማለት ነው፡፡
2.10 “የንግድ ዕቃዎች”፡- ማለት ገንዘብና ገንዘብነት ካላቸው ሰነዱች በስተቀር ማናቸውም የሚገዙ
ወይም የሚሸጡ ወይም የሚከራዩ ወይም በሌላ ሁኔታ በሰዎች መካከል የንግድ ስራ የሚከናወንባቸው የሚንቀሳቀሱ እቃዎች
ማለት ነው፡፡
2.11 የፀና የንግድ ሥራ ፈቃድ” ማለት በበጀት አመቱ የተሰጠ ወይም የታደሰ ወይም በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር
980/2008 አንቀጽ 27 መሰረት ያለቅጣት የሚታደሰበት ጊዜ ያላለፈበት የንግድ ሰራ ፈቃድ ነው፤
2.12 ነጋዴ፡- ማለት ንግድን የሙያ ሥራው አድርጐ ጥቅም ለማግኘት ሲል በንግድ ሕጉ ላይ የተዘረዘሩትን ሥራዎች የሚሠራ
ወይም አገልግሎት የሚሰጥ ወይም የንግድ ሥራ ነው ተብሎ በህግ የሚወሰነውን ሥራ የሚሠራ ማንኛውም ሰው ነው፤
2.13 ሸማች፡-ማለት ለማምረት ስራ ወይም መልሶ ለመሸጥ ሳይሆን ዋጋውን ራሱ ወይም ሌላ ሰው የሚከፍልለት ሆኖ ለራሱ
ወይም ለቤተሰቡ ፍጆታ የሚሆን የንግድ ዕቃ ወይም አገልግሎት የሚገዛ የተፍጥሮ ሰው ነው፤
2.14 ተገቢ ያልሆነ የንግድ ሥራ፡- ማለት ንግድን የሚመለከት የሕግ ድንጋጌዎችን የሚጥስ ማንኛውም ድርጊት ነው፣
2.15 የውጭ ኢንስፔክሽን፡- ማለት በንግድ ምዝገባና ፈቃድ እንዲሁም በንግድ አሰራርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ድንጋጌ
መሰረት በንግድ መደብር /ድርጀት/ በር ለበር መጎብኘት/ኢንስፔከት ማድረግ ማለት ነው፤
2.16 የንግድ ድርጅት፡- ማለት ለንግድ ሥራ መስሪያ ለማዋል በንግድ ዋና ምዝገባ በግልጽ ተመዝግቦ የሚታወቅ የንግድ
መደብር ነው፤
2.17 የንግድ ድርጅት ጉብኝትና የፍተሻ ሰዓት፡- ማለት በውጭ ኢንስፔክሽን የንግድ ድርጅቶች የፍተሻና የጉብኝት የሚደረግብት
የመንግስት ሥራ ሰዓት ሲሆን እንዳስፈላጊነቱ በኃላፊ በሚሰጥ ፍቃድ ከመንግስት ስራ ሰዓት ውጪ የሚካሄድበትን ጊዜ
ያመለክታል፣
2.18 የንግድ ድርጅት ማሸግ/መዝጋት ማለት፡-የንግድ ሥራው የሚፈጽምበትን መደብር ሥራውን ለማስቆም መስኰቶችንና
በሮቹን በባለ ድርጅቱ እንዲዘጋ አድርጐ መቆለፉን በማረጋገጥ የመስሪያ ቤቱ ማህተም ባለበት ስለመታሸጉ የሚገልጽ ደብዳቤ
በማጣበቂያ በበሩ/ በመስኮቱ መክፈቻ ወይም መገጣጠሚያ ላይ እንደተዘጋ መለጠፍ ነው፤
2.19 ቢሮ ማለት ይህን መመሪያ ለማስፈፀም ከንግድ ቢሮ ጀምሮ በየደረጃው የሚገኝ የክፍለ ከተማና ወረዳ የንግድ ጽ/ቤት
ያጠቃልላል፤
2.20 የንግድ ድርጅት ማገድ፡- ማለት የንግድ ድርጅቱ በሮችና መስኮቶች ሳይታሽጉ /ሳይዘጉ ነጋዴው ሥራውን እንዲያቆም
ፈቃዱ ለጊዜው የታገደ መሆኑን በደብዳቤ/ በጽሁፍ መግለጽ ማለት ነው፤
4
ክፍል ሶስት
ክፍል አራት
5
የቢሮው ተግባርና ኃላፊነት
6
በቀጠናው የሚገኝ የነጋዴ ብዛት በመለየት በቋሚ በባህር በመመዝገብ በየእለቱ እያንዳንዱ የበር ከበር
የክትልና ቁጥጥር ስራ በመስራት በእለት መመዝገቢያ ቅፅ ይመዘግባል፤
በየእለቱ በሚፈጽመው የክትትልና ቁጥጥር ተግባር በንግድ ህጎችና አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና
ማንዋሎች ውስጥ የተቀመጡ የነጋዴ ግዴታዎች በተገቢው መከበራቸውን ያረጋግጣል፡፡
በእየለቱ የራሱን እቅድ በማዘጋጀት በሚፈጽመው ተግባር በኃላፊነት በያዘው ብሎክ/ቀጠና ለሚፈጠር
የተባባሰ የንግድ ህገ-ወጥነት ኃላፊነት ይወስዳል፡፡
4.4 መብትና ግዴታ
4.4.1 ቁጥጥር ባለሙያ ግዴታ
እንዲከናውን የማድረግ፣
በንግድ ስራ ፈቃድና በንግድ ምዝገባ ላይ ባስመዘገበው የንግድ ስም መሰረት በንግድ ድርጅቱ መጠሪያና
በንግድ መደበሩ የሚለጠፈው (የሚፃፈው) ስም ተመሳሳይ እንዲሆን የማድረግ፣
በተለያዩ የንግድ አዋጆችና የአሰራር መመሪያ ውጭ የንግድ እቃዎች እንዳይከማቹ የማድረግ
ማንኛውም ነጋዴ ትክለኛነቱ በተረጋገጠ ሚዛንና የመስፈሪያ መሳሪያ አገልግሎት እንዲሰጥ የማድረግ፤
በመሰረታዊ ሸቀጥ መመሪያው የተቀመጡ የድጎማ ምርቶች ስርጭት አሰራሮች እየተከበሩ መሆኑን
ማረጋገጥ፤
7
ማንኛውም ነጋዴ የመሸጫ ዋጋ በንግድ መደበር ላይ በሚታይ ቦታ የዋጋ ዝርዝር የመለጠፍ፣
ማንኛውም ነጋዴ የገዙበትና የሚሸጥበት ደረሰኝ የመያዝና የመስጠት ፣
ማንኛውም ነጋዴ በጣት አሻራ የተረጋገጠ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የመያዝ፣
ማንኛውም ነጋዴ በንግድ ምዝገባ ሰርተፊኬት የመያዝ፣
ማንኛውም ነጋዴ ለተሰማራበት የንግድ ስራ መስክ የፀና የንግድ ስራ ፈቃድ የመያዝ፣
8
ደረሰኝ ሳይዝ፣ደረሰኝ መስጠት የሚጠበቅበት ሆኖ ሳለ ደረሰኝ የማይሰጥ ከሆነ፣ ኦሬጅናል የንግድ ስራ
ፈቃድ ሳይሰቅል ከተገኘ፣መለያ ኮድ ሳይለጥፍ የተገኘ ከሆነ፣
4.5.2 እርምጃ አወሳሰድ በተመለከተ
ሀ. በተራ ቁጥር 4.5.1 ከሀ እስከ ቀ ድርሰ የተጠቀሱትን የጥፋት አይነቶች ፣
ጥፋት የፈፀመ ማንኛውም ነጋዴ በንግድ አዋጅ ቁጥር 980/2008፣ በንግድ ምዝገና ፈቃድ ማሻሻ አዋጅ ቁጥር
1150 /2011፣ በንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006፣ በመሰረታዊ ሸቀጥ ስርጭት መመሪያ
እንዲሁም በንግድ ስርዓት ማስከበር የአሰራር ማንዋል 2011 ዓ.ም ላይ የተቀመጡ አስተዳደራዊ የእርምጃ ተፈፃሚ
ይሆናል፣
እንደ አስፈላጊነቱና የጥፋቱ መጠን ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ የማድረግ ስራ ይሰራል፤
ለ. በብሎክ ተለይቶ የተሰጠው የቁጥጥር ባለሙያ በተመደበበት ብሎክ በተራ ቁጥጥር 4.5.1 ተ
የተጠቀሱ ጥፋቶች ሲገኙ
ለመጀመሪያ ጊዜ በተመደበበት ቀጠና የተባባሰ የንግድ ህገ-ወጥነት የተገኘበት ባለሙያ በፅ/ቤት ኃላፊው
ባለበት በክትትልና ቁጥጥር ሂደት ጥፋቱን ያገኘው አካል ቃለ-ጉባኤ አስይዞ እንዲገመገም በማድረግ
በተመደበበት ቀጠና የተባባሰ ህገ-ወጥነት የሚገኝበት ባለሙያ ሁኔታው ለሁለተኛ ጊዜ ከሆነ የመጀመሪያ
በተመደበበት ቀጠና የተባባሰ ህገ-ወጥነት የሚታይበት ባለሙያ ሁኔታው ለሶስተኛ ጊዜ ከሆነ በዲስፕሊን
እንዲጠየቅ ይደረጋል፡፡
ሀ. በዚህ መመሪያ በሚሸፈን ማናቸውም ጉዳይ በሚሰጡ ውሳኔዎች ቅሬታ ያለው ማንኛውም አካል ቅሬታውን
በ 10 ቀናት ውስጥ ቅሬታውን ማቅረብ ይችላል፡፡
ለ. የበየደረጃው በሚገኝ የንግድ የንግድ ተቋም የበላይ ኃላፊ የቀረበውን አቤቱታ ሰምቶ በ 7 ቀናት ውስጥ
ውሳኔውን ለአመልካቹ በጽሁፍ ማሳወቅ አለበት፤
9
ክፍል አምስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
5.1 ቅጣት
ይህን መመሪያ የጣሰ ማንኛዉም ግለሰብ ወይም ድርጅት በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008
እና በንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006 ተከልክለው በሚገኙ ጉዳዮች በወንጅል
ተጠያቂ ይሆናል፡፡
5.2 የመተባበር ግዴታ
ማንኛውም ሰዉ ሆነ ድርጅት ይህንን መመሪያ በማክበርና በማስከበር ረገድ የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡
5.3 መመሪያዉን ስለማሻሻል
ይህንን መመሪያ ቢሮዉ እንደአስፈላጊነቱ ሊያሻሽለዉ ይችላል፡፡
5.4 መመሪያዉ የሚፀናበት ጊዜ
10
1