You are on page 1of 16

ማህበረሰብ መር የተፋጠነ የውሃ፣ ንጽህናና ሀይጅን

ፕሮጀከት (ኮዋሽ)

በኮዋሽ ምዕርፍ 3 ፕሮጀክት ማራዘሚያ ወቅት (6 ወራት)


ለኮቪድ-19 ምላሽ ለመስጠት በቤተሰብ ደረጃ በሚደረጉ ስራዎች
አካል ጉዳተኞችን የማካተት ተግባራት መመሪያ
(ሐምሌ 2012 አስከ ታህሳስ 2013)

አዲስ አበባ

የአማርኛ ቅጅ ተዘጋጀ: ጰጉሜ 2012


1
በኮዋሽ ፕሮጀክት ለኮቪድ-19 ምለሽ ለመስጠት በቤተሰብ ደረጃ በሚደረጉ ስራዎች አካል
ጉዳተኞችን የማካተት ተግባር

አካል ጉዳተኛ (በተለይም ሩቅ በሆኑ ገጠራማ አካባቢዎች የሚኖሩት) በጣም ተጋላጭ የሆኑ እና ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ
ምለሽ ለመስጠት/ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ የሚረሱ/የሚዘነጉ የማህበረሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡ በማህበረሰብ
ደረጃ፣ በትምህርት ቤቶች እና በጤና ተቋማት አካባቢ የሚከናወኑ ተግባራት አካታች (አካል ጉዳተኞችን ግምት ውስጥ
ያስገቡ) እየሆኑ እየመጡ ቢሆንም በቤተሰብ ደረጃም ሊሰሩ የሚገቡ ብዙ ተግባራት ያስፈልጋሉ፡፡ አብዛኞቹ አካል ጉዳተኛ
የሆኑ ልጆች ትምህርት ቤት የማይሄዱ/ከትምህርት የተገለሉ እና በቤት ውስጥ የተቀመጡ ናቸው፡፡ ስለዚህ ይህ አጭር
ማስታወሻ በቤተሰብ ደረጃ ሊከናወኑ ስለሚገባቸው ተግባራት እና የማህበረሰቡ አባላት በቤተሰብ ደረጃ የኮሮና ቫይረስን
ስርጭት እና በቫይረሱ መያዝን ለመቀነስ እንዲሁም የተወሰኑ የቤተሰብ አባላት በቫይረሱ ከተያዙ ምን ማድረግ
እንዳለብን የሚጠቁም ነው፡፡

አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ የኮዋሽ ፕሮጀክት ትኩረት የሚያደርግባቸው ዋናዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፡፡
- አካል ጉዳተኞች የሉበትን እውነታ (ያለባቸው የአካል ጉዳት አይቶችን) መሰረት ባደረገ መልኩ
መልእክቶች/መረጃዎች እና የውሃ፣ ንጽህናና ሀይጅን ተቋማት ላይ ተደራሽ እንዲሆኑ ማድረግ፡፡
- የውሃ ንጽህናና ሀይጅን አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለአካል ጉዳተኞች አካል ጉዳት አልባ ከሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች
እኩል ተደራሽ እንዲሆኑና እና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ፡፡
- አካል ጉዳተኞች ተገማች ከሆኑ ጎጂ ስጋቶች ነጻ እንዲሆኑ ማድረግ ናቸው፡፡

አካል ጉዳተኞች ላይ ትኩረት ማድረግ ለምን አስፈለገ?

አካል ጉዳተኞች በሚከተሉት ምክንያቶች ለኮሮና ቫይረስ በጣም ተጋልጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡:
- የተወሰኑት አካል ጉዳተኞች በኮሮና ቫይረስ ቢያዙ ለከፋ ህመም የመጋለጥ ከፍተኛ አስጊ ሁኔታ ላይ ስለሚገኙ፡፡
ለዚህም ምንክያቹ ስር የሰደደ ጉዳት መኖር ወይም የደከመ በሽታን የመከላከል አቅም መኖር ይገኙበታል፡፡
- የተወሰኑ አካል ጉዳት አይነቶች አካላዊ ርቀትን ለመጠበቅ አስቸጋሪ ስለሚሆኑ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በቤተሰብ አባል
ወይም በሌሎች ተንከባካቢዎች እገዛ የሚንቀሳቀሱትን የአካል ጉዳተኞች ይገኙበታል፡፡ እንዲሁም አንዳንድ
የአዕምሮ ህመም ያለባቸው ሰዎች የአካላዊ ርቀትን አስፈላጊነት ላይረዱ ይችላሉ፡፡
- እንዳንድ አካል ጉዳተኞች መሰረታዊ የግል ንጽህናን ለመጠበቅ ያለመቻል ተግዳሮቶች ሲኖርባቸው፤ አንዳንዶች
ደግሞ የፊት ጭምብል/ማስክን በአግባቡ የመጠቀም ተግዳሮቶች ሊኖሩባቸው ይችላሉ፡፡
- አብዛኘውን ጊዜ በገጠር አካካቢ ለሚኖሩ ቤተሰቦች የውሃ፣ ንጽህናና ሀይጅን ተቋማት የእንቅስቃሴ ወይም
የእይታ ችግር ላለባቸው ሰዎች ተደራሽ አይሆኑም፤ በዚህም ምክንያት አስፈላጊውን የግል ንጽህና ለመጠበቅ
አለመቻል ናቸው፡

2
-

ኮሮና ቫይረስ እና አካል ጉዳት

አካል ጉዳተኞች ለኮሮና ቫይረስ በጣም ተጋላጭ


የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ናቸው ምክንያቱም፡-

የንጽህና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት


ላይ ለመድረስ ስለሚቸገሩ
ቁሶችን ለመንካት ስለሚገደዱ

አካላዊ ረቀትን ለመጠበቅ መቸገር

መረጃን ለማግኘት ስለሚቸገሩ፡፡

አካል ጉዳተኞችን ከኮሮና ቫይረስ ኢንፌከክሽን/መጠቃት ለመከላከል ምን ምን ተግባራት እና


እንዴትስ መከናወን አለባቸው?

የኮሮና ቫረስን ስርጭት ለመግታት በቤተሰብ ደረጃ የሚከተሉት ሶስት ተግባራት መከናወን አለባቸው፡፡

1. መረጃን ተደራሽ ማድረግ- እዝል 1


የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን በተመለከተ ሁሉም የቤተሰብ አባላት መረጃ ማግኘት አለባቸው፡፡ መረጃውን እንዴት ማግኘት
አንዳለባቸው የሚወሰነው የቤተሰቡ አባል ባለበት የአካል ጉዳት አይነት እና እድሜው ነው፡፡ ሩቅ በሆኑ ገጠራማ አካባቢዎች
መረጃው የሚሰራጭበት መንገድ ቀላል እና ግልጽ በሆኑ ቋንቋዎች በመግለጽ እንዲሁም መስማት ችግር ላለባቸው
ደግሞ በምልክት ቋንቋዎች ይሆናል፡፡

በጣም አስፈላጊ የሆኑት መረጃዎች ስለጤና እና የግል ንጽህና አጠባበቅ፣ በቫይረሱ የመያዝ እድልን/አደጋን ስለመቀነስ፣
ወይም የበሽታውን ስርጭተት ለመግታት በማህበረሰቡ አካባቢ የተጣሉ እገዳዎች ካሉ (ለምሳሌ፣ ስብሰባን አለማድረግ
ወይም ጎረቤት ለጎረቤት በአካል አለመቀራረብ/አለመገናኘት) የመሳሰሉት ናቸው፡፡ እነዚህ መረጃዎች ለማህበረሰቡ በወረዳ
እና በቀበሌ ባለሙያዎች፣ እንዲሁም በትምህርት ቤቶች፣ በጤና ጣቢያና በጤና ኬላ ባለሙያዎች እና በጤና ኤክስቴንሽን
ሰራተኞች መሰራጨት/መሠጠት አለባቸው፡፡ መረጃው በአካል ጉዳተኛው ተንከባካቢ ወይም ረዳት ቀጥታ ሊሰጥም
ይችላል ምክንቱም ግለሰቡ ካለበት የአካል ጉዳት አንጻር አግባብበት ያለውን መረጃ የመስጠት ዘዴ ስለሚያውቅ እና
በቀላሉ ሊግባቡ ስለሚችሉ ነው፡፡ በአካባቢው የሚገኙ ከሆነም የአካል ጉዳተኛ ማህበራት በተለይም የመስማት፣ የእይታ
እና የአዕምሮ ጉዳት ላለባቸው አባሎቻቸው አስፈላጊውን መረጃ ቀጥታ መስጠት ይችላሉ፡፡

ቫይረሱን በተመለከተ ቁልፍ የሆኑ መልእክቶች እና እንዴት መከላከል እንድምችል የሚያሳዩ ምስሎች በእዝል
1 ላይ ቀርቧል፡፡

2. ቤተሰቡን በመጠበቅ/በመንከባከብ የበሽታውን ስርጭት መከላከል፤ ቤትና አካባቢን ማጽዳት፣ የግል


ንጽህና መጠበቅ፣ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ፣ የፊት ጭንብል/ማስክ ማድረግ፡፡
ለሁሉም የቤተሰብ አባላት በተለይም ለአካል ጉዳተኞች ቤትን ማጽዳት እና የግል ንጽህናን መጠበቅ አስፈላጊነት
ተገቢውን ትኩረት ላያገኝ ይችላል፡፡ እጆችን በተደጋጋሚ መታጠብ እንዲሁም እጅ መታጠቢያ ቦታዎች እና መጸዳጃ ቤቶች
ለሁሉም የቤተሰቡ አባላት ተደራሽ መሆን አለባቸው፡፡ ለእጅ መታጠቢያነትም ሳሙናና ውሃ ወይም ከ60 በመቶ ያላነሰ
የአልኮል ይዘት ያለው የእጅ ማጽጃ ኬሚካል መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ ለአካል ጉዳተኞች የሚያስፈልጉ አጋዥ መሳሪያዎች
ለምሳሌ ተሸከርካሪ ወንበር፣ ክራንች፣ ዱላ፣ ነጭ ቀለም የተቀባ የአይነ ስውራን ዱላ ወዘተ…. በተደጋጋሚ በውሃና በሳሙና
መጸዳት/መታጠብ አለባቸው፡፡

3
አንደማንኛውም የማህበረሰብ ክፍል አካል ጉዳተኞችም ከሌሎች ሰዎች አካላዊ ርቀታቸውን መጠበቅ ይኖርባቸዋል፡፡
አንዳንድ አካል ጉዳተኞች በእያንዳንዱ የህይወት አንቅስቃሴያቸው ረዳቶች ስለሚስፈልጋቸው አካላዊ ርቀትን መጠበቅ
አይችሉም፡፡ በገጠር አካባቢ የቤተሰብ አባላት አስፈላጊ በሚሆንበት ጌዜ አካል ጉዳተኞችን ማገዝ የተለመደ ነው፡፡ በተቻለ
መጠን የተወሰኑ የቤተሰብ አባላት ብቻ እገዛውን እንዲያደርጉ ማድረግ እና እገዛውን በሚያደርጉበት ወቅትም
ማስክ/ጭምብል እንዲጠቀሙ ቢደረግ ጥሩ ነው፡፡ በየአካባቢው የማህበረሰብም ስብሰባዎች መደረግ አይኖርባቸውም፡፡

ትምህርት ቤቶች ከተከፈቱና ልጅዎን ለቫይረሱ ሊያጋልጡ የሚችሉ (ለምሳሌ አስም/ለመተንፈስ የሚያስቸግር በሽታ)
ወይም ሌሎች የቫይረሱ ምልክቶች ያልታየባቸው አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት
መሄድ አለባቸው፡፡ ልጅዎ የግል ንጽህናን በጥሩ ሁኔታ ለመጠበቅ የሚቸገር ወይም አካላዊ ርቀትን ለመጠበቅ የሚቸገር
ከሆነ የቤተሰቡ አባል/ተንከባካቢ/መምህር ልጆን በትምህርት ቤት ውስጥ መርዳት አለባቸው፡፡ ይህ የማይቻል ከሆነ፣
ልጅዎ በቤት ውስጥ በወንድሞቹ እና በእህቶቹ እንዲታገዝ መደረግ አለበት፡፡

የቤተሰብ አባልም ሆነ ሌሎች የአካል ጉዳተኛው ረዳቶች ቫይረሱን በመፍራት ለአካል ጉዳተኛው የሚያደርጉትን
አገዛ ማቆም የለባቸውም ምክንያቱም ይህ ድርጊት በአካል ጉዳተኛው ህይወት ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ
ስለሚኖረው ነው፡፡ ነገር ግን የቫይረሱን ስርጭት ለመቀነስ የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎች መወሰድ ይኖርባቸዋል፡፡
ከእርምጃዎቹ ዋና ዋናዎቹም፡-
- በተቻለ መጠን የተወሰኑ የቤተሰብ አባላት ብቻ እገዛ/እርዳታ እንዲያደርጉ፣
- እገዛ/እርዳታ/ የሚያደርጉ ሰዎች ከሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች/ሰዎች አካላዊ ርቀትን እንዲጠብቁ እና
እንዲጠነቀቁ፣ እጆቻቸውን በመታጠብ የግል ንጽህናቸውን እንዲጠብቁ፣ እና በተቻለ መጠን ማስክ/ጭምብል
እንዲጠቀሙ፣
- እገዛ/እርዳታ የሚያደርጉ ሰዎች በአካባቢው ህዝብ በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች መገኘት አይኖርባቸውም
(ለምሳሌ ቤተ ክርስቲያን፣ መስጊድ)፡፡ እገዛ/እርዳታ የሚያደርገው ግለሰብ ተማሪ ከሆነ ትምህርት ቤት መሄዱን
ሳያቆም አካላዊ ርቀትን መጠበቅ፣ በትምህርት ቤት ባለበት ወቅት የእጅ ማታጠብን እንደሁም ሌሎች የግል
ንጽህናዎችን መጠበቅ አለበት፡፡

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት፣ የአካል ጉዳተኛው የቤተሰብ አባል ወይም ረዳት ለአካል ጉዳተኛው የሚከተሉትን
አገዛዎች ማድረግ አለበት፡፡ አካል ጉዳተኛው፡-
- የመከላከል ተግባራትን አንደ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እና የግል ንጽህናን መጠበቅ የመሳሰሉትን
እንዲጠቀም/ተግባራዊ እንዲያደርግ ማገዝ፣
- አንዳንድ የበሽታውን/የኮሮና ቫይረስ/ምልክቶች ካሳየ የምርመራ እና የህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ማገዝ፣
- ግለሰቡ ስለበሽታው ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እንዲረዳ ማገዝ (ለምሳሌ በእዝል 1 ላይ የታዩት)፣
- አስፈላጊ በሚሆንበት ወቅት የተለመደውን የህክምና ድጋፍ/አገልግሎት እንዲያገኙ ማገዝ፣
- ለራሱ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ የመመገቢያ እቃዎች እንዲኖሩት፣ እንዲሁም የመኝታ ልብሶችን እና ሌሎች
ልብሶችን ለብቻቸው በማጠብ ማገዝ፣
- አካላዊ እና አዕምሮአዊ ጤንነቱ እንዲጠበቅ እንዲሁም ደስተኛ እንዲሆን እና የብቸኝነት ስሜት እንዳይሰማው
ማገዝ ናቸው፡፡
በተቻለ መጠን፣ በአካባቢው እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቀት (ለምሳሌ ሱቆች ወይም የውሃ ተቋም በሚሄዱበት ወቅት)
የፊት ማስክ/ጭምብል መጠቀም አለባቸው፡፡ አንዳንድ አካል ጉዳተኞች ካለባቸው የአካላዊ፣ የጤንነት እና ባህሪያዊ
ምክንያቶች አንጻር ማስኮችን በአግባቡ ማድረግ አይችሉም፡፡ እነዚህ አካል ጉዳተኞች ከእነሱ ጋር ከሚኖሩ የቤተሰብ
አባሎቻቸው ውጭ ካሉ ሰዎች አካላዊ ርቀቶቻቸውን መጠበቅ በጣም አስፈላጊ ነው/ይኖርባቸዋል፡፡

መላ ቤተሰቡን በተለይም አካል ጉዳተኛ የቤተሰብ አባላትን ከበሽታው እንዴት መጠበቅ እንደሚቻል የሚያሳዩ
መሰረታዊ ሂደቶች ስዕላዊ በሆነ መልኩ በእዝል 1 ላይ ይታያሉ፡፡

4
3. ለዓይነ ስውራን እና የእንቅስቃሴ ችርግ ላለባቸው የአካል ጉዳተኞች ተደራሽ የሆኑ የውሃ፣ ንጽህና ሀይጅን
አገልግሎትና ተቋማት (ንጽህና መጠበቂያ፣ ለመታጠቢያ አገልግሎት፣ለመጠጥ አገልግሎት) - እዝል 3
አካል ጉዳተኞች ራሳቸውን ከበሽታው እንዲከላከሉ/እንዲጠብቁ እና የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ማንኛውም በቤት
ውስጥ የሚገኝ የውሃ፣ ንጽህናና ሀይጅን አገልግሎት መስጫ ተቋማት (የመጠጥ ውሃ፣ የእጅ መታጠቢያ፣ የገላ መታጠቢያ
እና መጸዳጃ ቤት) ተደራሽ መሆን አለባቸው፣ በተቻለ መጠንም ካለ ሌሎች ረዳት በራሳቸው ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ
መሆን አለባቸው፡፡ ለወረርሽኙ ምላሽ ለመስጠት በምናስብበት ወቅት ይህ ጉዳይ አስፈላጊ የሚሆነው ለግለሰቦች ብቻ
ሳይሆን ለሁሉም ቤተሰብ እና ለአካባቢው ማህበረሰብም ጭምር ነው፡፡

ተደራሽነት ማለት አንድን የአገልግሎት ሰጪ ተቋም ለመጠቀም መምረጥ፣ መቅርብ/መድረስ ወይም መጠቀም ነው፡፡
የእንቅስቃሴ ውስንነት ላለባቸው ሰዎች ፍላጎታቸው እንደየአካል ጉዳቱ ዓይነት ይወሰናል (የእጅ፣ የእግር፣ የጀርባ ወዘተ.)፡
፡ በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ቤተሰብ በቤተሰብ ደረጃ ያለውን የመጸዳጃ ቤት እንደየ ግለሰቡ የአካል ጉዳት ሁኔታ
ሊያዘጋጅ ይችላል፡፡ ነግር ግን፣ በጣም አስፈላጊው ጉዳይ መጸዳጃ ቤቱ/እጅ መታጠቢያው/የመጠጥ ውሃ አገልግሎት
መስጪያዎች ከቤቱ መራቅ የለባቸውም፣ ወደ አገልግሎት መስጫ ተቋሞቹ የሚወስደው መንገድ የተስተካከለ፣
እንዲሁም አገልግሎት ሰጪ ተቋሙ ለመጠቀም ቀላል እና ምቹ መሆን አለበት፡፡ አስፈላጊ ከሆነ፣ ለምሳሌ መንሸራተቻ
/ramp/፣ የእጅ ድጋፍ /hand rails/፣ በቀላሉ የሚከፈትና የሚዘጋ በር /easy to operate door/ ፣ በጣም ክፍም ሆነ ዝቅ
ያላሉ የውሃ መዝጊያና መክፈቻ ፎሴቶች /taps that not too high or low/፣ ከፍ ያለ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ /raised
seat in the latrine/ ሊሰሩ ይችላሉ፡፡ ለአይነ ስውራን/የእይታ መጠናቸው በጣም ለቀነሰ ሰዎች መሪ ገመድ /guiding
rope/ ወይም ሌሎች አጋዥ ምልክቶች መጠቀም በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ ለእጅ መታጠቢያ የሚያገለግሉ ቁሶች እንደ
ሳሙና፣ የእጅ እጣቢ ውሃ ማጠራቀሚያ ባሊ ወዘተ… አይነ ስውራኑ በቀላሉ ሊያገኟቸው እና መጠቀም እንዲችሉ
በመጸዳጃ ቤቱ አቅራቢያ መቀመጥ አለባቸው፡፡

ሁሉም ቤተሰቦች ለሴቶች እና ለልጅ አገረዶች የወር አበባ ንጽህና አጠባበቅ ትኩረት መስጠት አለባቸው፡፡ በተቻለ መጠን
በቂ የሆኑ የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ቁሶች በቤት ውስጥ መቀመጥ አለባቸው (ይህም የሚሆነው አስፈላጊ በሚሆንበት
ወቅት ይህን ፍለጋ ወደማህበረሰቡ ላለመሄድ/ላለመቀላቀል ነው) ፡፡ በተጨማሪም የወር አባባ ንጽህናን በሚጠብቁበት
ወቅት ውሃ እና ሳሙና በመጸዳጃ ቤቱ ውስጥ መኖራቸው መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ እነዚህ አገልግሎቶች አካል ጉዳተኛ ለሆኑ
ሴቶች እና ልጃገረዶችም በጣም አስፈላጊ እንደሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡

ተደራሽ ለሆኑ የተለያዩ የውሃ፣ ንጽህናና ሀይጅን አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ምስሎች በእዝል 2 ይመልከቱ

አካል ጉዳተኛ የቤተሰባችን አባል በኮሮና ቫይረስ ከተጠቃ/ች ምን ማድረግ አለብን?

ግለሰሱ የኮሮና ቫይረስ ምልክሎችን ካሳየ ወይም መተንፈሽ ችግር ካጋጠመው፣ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማድረግ በጣም
አስፈላጊ ነው፡፡ ምልክቶቹ (በእዝል1 ላይ እንደታዩት) ከጉንፋን ጋር ተመሳሳይ ናቸው፣ ነገር ግን ከጉንፋን በተለየ ሁኔታ
የኮሮና ቫይረስ ምልክት የሆነው የማሽተት እና የመቅመስ አቅም መቀነስ ነው፡፡

የወረዳ እና የቀበሌ ባለሙያዎች እንዲሁም የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ማህበረሰቡ በኮሮና ቫይረስ የመያዝ ጥርጣሬ
ሲኖራቸው ምን ማድረግ አንዳለባቸው ለማህበረሰቡ ማስረዳት/ማስገንዘብ አለባቸው፡፡ ማሰገንዘብ ካለባቸው ነገሮች
በቅርባቸው ካለው የጤና ጣቢያ መሄድ አለባቸውን፣ በጤና ጣቢያውስ የመመርመሪያ መሳሪያ አለን፣ ወይስ ለምርመራ
ወደ ሆስፒታል መሄድ አለባቸውን የመሳሰሉትን ጉዳዮች ያካትታል፡፡ እንዲሁም በቅርብ የሚነገኘው የለይቶ ማቆያ ወይም
የማገገሚያ ቦታ የት እንደሆነ እና አካል ጉዳተኞች በዚህ ማእከል ውስጥ እንዴት መግባት እንደሚችሉ (ተደራሽነት እና
የአካል ጉዳተኛው ረዳት እንዴት ሊያስታምመዉ እንደሚችል) ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ የሚገባቸው ተጨማሪ ጉዳዮች
ናቸው፡፡ ወደ ጤና ጣቢያ በሚሄዱበት ወቅት የህዝብ ማመላለሻ ዘዴን አለመጠቀም እና ማስክ መጠቀም ይኖርባቸዋል፡
፡ አስፈላጊ በሚሆንበት ወቅት አካል ጉዳተኞቹ ከቤተሰብ አባላት ወይም ከረዳቶቻቸው ጋር መሄድ ይኖርባቸዋል በዚህም
ወቅት የህዝብ ማመለለሻ ዘዴን አለመጠቀም፣ ከሌሎች ሰዎች አካላዊ ርቀታቸውን መጠበቅ እና ማስክ/ጭምብል

5
ማድረግ የመሳሰሉት ጥንቃቄዎች መደረግ አለባቸው፡፡ የበሽታው ምልከቶቸ ከታዩነባቸው አካል ጉዳተኞች
እንደማንኛውም ሰው መመርመር አለባቸው፡፡

መመርመር የማይቻል ከሆነ፣ ግለሰቡ ላይ የታዩት ምልክቶች ቀላል ከሆኑ ወይም ግለሰቡ ተመርምሮ ቫይረሱ ከተገኘበት፣
ሁሉም የቤተሰቡ አባላት በአካባቢው ከሚገኙ ሌሎች ማህበረሰቦች እራሳቸውን በመለየት በሽታው እንዳይሰራጭ
ማድረግ አለባቸው፡፡ የምርመራው ውጤት እስኪደረስ ድረስም (አባዛኛው ጊዜ የተወሰኑ ቀናትን ስለሚወሰወድ)
ለጥንቃቄ ሲባል ቤተሰቡ ራሱን በመለየት ውጤቱን መጠበቅ አለበት፡፡

አንድ የቤተሰቡ አባል በኮሮና ቫይረስ ምልክቶች ካሳየ/ከተጠቃ ምልክቶቹ ሙሉ በሙሉ እስኪጠፉ ድረስ ሁሉም የዚህ
ቤተሰብ አባላት ከሌሎች የማህበረሰቡ አባላት አካላዊ ርቀታቸውን በበቂ ሁኔታ በመጠበቅ አለባቸው፡፡

በቤተሰብ ውስጥ የተከሰተ ኮሮና ቫይረስ ህመምን አካታች በሆነ መልኩ ለማስተዳደር/ለመቆጣጠር አስፈላጊ
የሆኑ መሰረታዊ ጥንቃቄዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

አካል ጉዳተኛ አባል ያለው የቤተሰብ አባል በኮሮና ቫይረስ ህመም ቢታመም፤ በቤት ውስጥ መቆየት አለበት፡፡
በዚህ ወቅት ታማሚው ግለሰብ፡-
• በተቻለ መጠን በቤት ውስጥ ከሚኖሩ ሰዎች በመራቅ በእንድ ክፍል ውስጥ ይቆዩ፡፡ የክፍሉንም በር ይዝጉት፡፡
• 1 ወይም 2 ሰዎች ብቻ ታማሚውን እንዲንከባከቡ ማድረግ፡፡ እነዚህ ሰዎች ራሳቸውን በአካባቢው ካሉ ሌሎች
ማህበረሰቦች እንዲለዩ መምከር፡፡
• የሚቻል ከሆነ ንጽህ አየር ክፍሉ ውስጥ እንዲገባ መስኮቶችን መክፈት፡፡
• ከታማሚው ውጭ ሌላ ሰው በክፍሉ ውስጥ ካለ/ከገባ የፊት መሸፈኛ ማስክ/ጭምብል ያድርጉ፡፡
ተንከባካቢዎቻቸውም ማስክ ማድረግ አለባቸው፡፡
• 65 ዓመት እና ከዛ በላይ እድሜ ካላቸው ወይም ከታመሙ ሰዎች (በሌሎች በሽታዎችም ቢሆን) ይራቁ፡፡

የዓለም ጤና በኮሮና ቫይረስ ለተጠረጠሩ ወይም እንዳለባቸው የተረጋገጡ


ድርጅት ሰዎችን የቤት ወስጥ እንክብካቤ
ራስዎን እና ቤተስብዎን ይንከባከቡ!
ለታማሚዎች
ትኩሳት እና ሳል
ከለዎት

በቤትዎ ይቆዩ! ወደ ስራ፣ ወደ ትምህርት ቤት ወይም


እጅዎትን በታደጋጋሚ በውሃ እና ሳሙና
ህዝብ ወደሚሰበሰብበት ቦታ አይሂዱ፡፡ እረፍት ያድርጉ፣
ወይም የአልኮል ይዘት ባለው ማጽጃ ያጽዱ፡፡
ብዙ ውሃ ይጠጡ እንዲሁም የተመጣጠነ ምግብ ይመገቡ፡

ከሌሎቹ የቤተስብ አባላት ተለይተው በአንድ ክፍል


ውስጥ ይቆዩ፣ ነገር ግን ይህን ማድረግ ካልተቻለ ማስክ በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱ ወቅት አፍና አፍንጫዎን
ያድርጉ እንዲሁም ከሌሎች ሰዎች ቢያንስ 2ሜትር በክርንዎ ይሸፍኑ ወይም ለስላሳ ወረቀት ይጠቀሙ፡፡
አካላዊ ርቀት ይኑርዎት፡፡ ያሉበት ክፍልም ንፁህ አየር ለመተንፈስ የሚቸገሩ ከሆነ ለሚንከባከብዎት የህክምና
የሚያስገባ መሆን አለበት፡፡ ባለሙያ ይደውሉ፡፡

6
የአካል ጉዳተኛው አስታማሚ/ተንከባካቢ ወይም ረዳት የሚከተሉትን ማድረግ አለበት፡-
• ታማሚው በቂ እርፍት ማግኘቱን፣ ብዙ ውሃ መጠጣቱን እና የተመጣጠነ ምግብ መመገቡን ማረጋገጥ፡፡
• እጅዎትን በተደጋጋሚ በውሃና በሳሙና ይታጠቡ፣ በተለይም ከሰዎች ጋር ከተገናኙ በኋላ፣ ምግብ ከማዘጋት
በፊት፣ እያዘጋጁ እያሉ እና ካዘጋጁ በኋላ፣ ምግብ ከመመገብዎ በፊት ወይም ታማሚውን ከመመገብዎ በፊት፣
መጸዳጃ ቤት ከተጠቀሙ በኋላ፣ ወይም ታማሚውን መጸዳጃ ቤት እንዲጠቀም ካገዙ በኋላ፡፡
• ብዙ ጊዜ በሰዎች የሚነካኩ እቃዎችን ጨምሮ፣ ቤቱን በተደጋጋሚ በውሃ እና በሳሙና ማጠብ፡፡
• በተቻለ መጠን ከታማሚው ጋር አንድ ክፍል በሚሆኑበት ወቅት ወይም በሚንከባከቡበት ወቅት
ማስክ/ጭምብል ያድርጉ፡፡ ማስኩን አንድ ጊዜ ካደረጉ/ካጠለቁ በኋላ በእጅዎ አይነካኩት፡፡
• ለታማሚው ብቻ የሚያገለግሉ የመመገቢያ ሳህኖች እና ኩባያዎች፣ ፎጣዎች እና ብርድ ልብሶች ይዘጋጁ፡፡
የጥርስ ቡርሾች፣ ፎጣዎች፣ ኩባያዎች እና የመመገቢያ ሳህኖች ቤተሰቡ በጋራ መጠቀም አይኖርበትም፡፡
በታማሚው ሰው አገልግሎት ላይ የዋሉ ልብሶች ለብቻቸው በሞቀ ውሃና በሳሙና መታጠብ አለባቸው፡፡
በኮሮና ቫይረስ ለተጠረጠሩ ወይም እንዳለባቸው የተረጋገጡ
የዓለም ጤና
ሰዎችን የቤት ወስጥ እንክብካቤ
ድርጅት
ራስዎን እና ቤተስብዎን ይንከባከቡ!

ለተንከባካቢዎች ከታማሚው ጋር በአንድ ክፍል


ታማሚው በቂ እርፍት
በሚሆኑበት ወቅት የህክምና
ማግኘቱን፣ ብዙ ውሃ
ማስክ ያድርጉ፡፡ ማስኩን አንዴ
መጠጣቱን እና
ካደረጉ በእጅዎ አይነካኩት፡፡
የተመጣጠነ ምግብ
ከክፍሉ በሚወጡበት ወቅትም
መመገቡን ማረጋገጥ፡፡
ማስኩን በአግባቡ ያስወግዱት፡
እጅዎን በውሃና በሳሙና ወይም ፡
የአልኮልነት ይዘት ባለው የእጅ ማጽጃ ለታማሚው ብቻ የሚያገለግሉ
በሚከተሉት ጌዜያቶች ያጽዱ፡፡ የመመገቢያ ሳህኖች እና
- ከታማማው ሰው ጋር እና ከቁሶች ጋር ኩባያዎች፣ ፎጣዎች እና ብርድ
ከተነካኩ በኋላ፣ ልብሶች ይዘጋጁ፡፡ ልብሶቹ
- ምግብ ከማዘጋጀት በፊት፣ እያዘጋጁ ለብቻቸው በሞቀ ውሃና
እና ካዘጋጁ በኋላ፣ በሳሙና መታጠብ አለባቸው፡፡
- ምግብ ከመመገብዎ በፊት፣
- መጸዳጃ ቤት ከተጠቀሙ በኋላ፡፡
ታማሚው ህመሙ እየከፋበት
በታማማው በተዳጋጋሚ ወይም የመተንፈስ ችግር
የሚነኩ ቁሶችን/ገጾችን እያጋጠመው ከሆነ
በመለየት በየቀኑ ለሚከታተለው የህክምና
ያጽዷቸው፡፡ ባለሙያ ይደውሉለት፡፡

7
እዝል 1. ኮሮና ቫይረስን በተመለከተ ቀላል በሆኑ ቋንቋዎች እና ምስሎች የተዘጋጁ መረጃዎች

ኮሮና ቫይረስ ምንድን ነው?


ኮቪድ-19 ኮሮና ቫይረስ በሚባል ቫይረሰ ከሰው ወደሰው የሚተላለፍ አዲስ የመተንፈሻ አካል ህመም ነው፡፡ የኮቪድ-19
ቫይረስ ከኢንፍሎዋንዛ እና ከጉንፋን ህመም ጋር በጣም ተመሳሳይ ነው፡፡ ምርመራ ካላደረጉ በስተቀር በኮሮና ቫይረስ
መያዘዎትን ወይም አለመያዝዎትን ማረጋገጥ አይቻልም፡፡

በኮሮና ቫይረስ እንዴት ሊያዙ ይችላሉ?


ኮሮና ቫይረስ ከሰው ወደሰው ይሰራጫል/ይተላለፋል፡፡

ኮሮና ቫይረስ ከአንድ ሰው ወደ ሌላ ሰው


ይሰራጫል/ይተላለፋል፡፡

ኮሮና ቫይረስ በሚከተሉት ምክንያቶች ሊይዞዎት ይችላል፤


• በኮሮና ቫይረስ ተይዞ አስከአሁን ምንም ምልክት ካላሳየ ሰው ጋር አካላዊ ቅርርብ ከኖረዎት፣
• በኮሮና ቫይረስ ተይዞ ምልክት ካሳያ ሰው ጋር አካላዊ ቅርርብ ከኖረዎት፣
• ኮሮና ቫይረስ ያረፈበትን ገጽ/ቁስ ለምሳሌ ጠረጴዛ፣ የበር እጀታ ነክተው እጅዎን ሳይታጠቡ ፊትዎን ከነኩ፡፡

ኮሮና ቫይረስ በሚከተሉት ምክንያቶች ሊይዞዎት ይችላል፤

በኮሮና ቫይረስ ተይዞ አስከአሁን ምንም ምልክት


ካላሳየ ሰው ጋር አካላዊ ቅርርብ ከኖረዎት፣

በኮሮና ቫይረስ ተይዞ ምልክት ካሳያ ሰው ጋር


አካላዊ ቅርርብ ከኖረዎት፣

ኮሮና ቫይረስ ያረፈበትን ገጽ/ቁስ ለምሳሌ


ጠረጴዛ፣ የበር እጀታ ነክተው እጅዎን ሳይታጠቡ
ፊትዎን ከነኩ፡፡

በመካከላችን አካላዊ ርቀታችንን ከጠበቅን፣ የኮሮና ቫይረስን ስርጭት ለመግታት እንችላለን፡፡

አካላዊ/ማህበራዊ ርቀት ማለት በእኛ እና በሌሎች ሰዎች


መካከል ያለውን የአካል/የንክኪ ርቀት መጠበቅ ማለት እንጂ
በሀሳብ መራራቅ አይደለም፡፡

8
አካል ጉዳተኞች እና በእድሜ የገፉ ሰዎች በየቀኑ እንክብካቤ እና እገዛ ሊያስፈልጋቸው ስለሚችል በዚህም ምክንያት አካል
ጉዳት አልባ እነደሆኑት ሰዎች አካላዊ ርቀትን መጠበቅ አይችሉም ይሆናል፡፡ ለአካል ጉዳተኞቹ እንክብካቤ የሚደርጉት
ሰዎች ከተጎጂዎቹ ጋር በቂ ጊዜ እንዲያሳልፉ አስፈላጊ ቢሆንም በተመሳሳይ ሁኔታ ራሳቸውን ከሌሎች
የማህበረሰብ ክፍሎችም መለየት አለባቸው፡፡

የኮሮና ቫይረስ ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው?

አብዛኞቹ ምልክቶች ከእንፍውሌንዛ እና ጉንፋን ምልክቶች ጋር ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ምልክቶቹም ትኩሳት፣ሳል እና


መተንፈስ መቸግር ናቸው፡፡ አንዳንድ ሰዎች የራስ ህመም ሊኖራቸው ይችላል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች የማሽተት
ወይንም የመቅመስ አቅም መቀነስም ይታይባቸዋል፡፡

ከፍተኛ የሰውነት ሳል እና የጉሮሮ የራስ የመተንፈስ


ሙቀት ማስነጠስ መከርከር ህመም ችግር

ሎሎቹ ምልክቶች፤ ንፍጥ፣ የጡንቻ ህመም፣ የመገጣጠሚያ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ማቅለሽለሽ/ማስታወክ፣ ምግብ
ፍላጎት መቀነስ የመሳሰሉት ናቸው፡፡

ከላይ ከተጠቀሱት ምልክቶች አንዱ እንኳን ከታየብዎት፡-


ራስዎን ከሌሎች ይለዩ/ያግልሉ፡፡
የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ቢያደርጉም ጥሩ ነው፡፡

የኮሮና ቫይረስን ስርጭት እንዴት መግታት ይቻላል?


እጅዎን በተደጋጋሚ በውሃ እና በሳሙና መታጠብ ወይም ቢያነስ 60 በመቶ የአልኮል ይዘት ባለው የእጅ መጸጽጃ ኬሚካል
ማጽዳት፡፡ ይህ መደረግ ያለበት ምግብ ከመመገባችን በፊት እና ከተመገብን በኋላ እንዲሁም በመጸዳጃ ቤት ከተጸዳዳን
በኋላ ያሉትን ጊዜያት ያካትታል፡፡ አካል ጉዳተኞችም እጃቸውን በራሳቸው መታጠብ የማይችሉ ከሆነ
ይርዷቸው/ያግዟቸው፡፡
በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱበት ወቅት አፍና አፍንጫዎትን በለስላሳ ወረቀት /soft paper/ ወይም በክርንዎት
ይሸፍኑ፡፡
ፊትዎን፣ አፍንጫዎን፣ አፍዎን እና አይንዎን ከመነካካት ይቆጠቡ፡፡ እጅ ለእጅም አይጨባበጡ፡፡
የጤንነት ስሜት የማይሰማዎት ከሆነ ከቤትዎ አይውጡ፡፡
አካላዊ ርቀት መጠበቅን ተግባራዊ ያድርጉ፤ ይህም ከሌሎች ሰዎች ቢያንስ 2 ሜትር መራቅን ይይዛል፡፡

9
የቫይረሱን ሰርጭት ለመግታት ሁላችንም ተግባራዊ ልናደርጋቸው የሚገቡ 5 ጉዳዮች፡-
ገዶች፡- እጅዎን በተደጋጋሚ በውሃ እና በሳሙና መታጠብ ወይም የአልኮል
ይዘት ባለው የእጅ መጸጽጃ ኬሚካል ማጽዳት፡፡
በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱበት ወቅት አፍና አፍንጫዎትን በለስላሳ
ወረቀት /soft paper/ ወይም በክርንዎት ይሸፍኑ፡፡
ትዎ አይውጡ፡፡
ፊትዎን፣ አፍንጫዎን፣ አፍዎን እና አይንዎን ከመነካካት ይቆጠቡ፡፡
“እጅ ለእጅም አይጨባበጡ፡፡
ትዎ አይውጡ፡፡
የጤንነት ስሜት የማይሰማዎት ከሆነ ከቤትዎ አይውጡ፡፡

አካላዊ
“ ርቀት መጠበቅን ተግባራዊ ያድርጉ፤ ይህም ከሌሎች ሰዎች
ቢያንስ 2 ሜትር መራቅን ይይዛል፡፡

አካል ጉዳተኞችም ሆኑ እነሱን የሚያግዙ ሰዎች የሚጠቀሙባቸውን የመርጃ/የእገዛ ማሳሪያዎች ማጽዳት


ይኖርባቸዋል፡፡ እነዚህም መርጃ መሳሪዎች ተሸከርካሪ ወንበር፣ ክራንች፣ ዱላ ወዘተ… ሲሆኑ በውሃና በሳሙና በደንብ
መታጠብ አለባቸው፡፡

የአካል ጉዳተኞች አጋዥ መሳሪያዎችን ማጽዳት

በሚከተሉት ጊዜያቶች እጅዎትን በውሃና በሳሙና በደንብ መታጠብ፤


• ከሳሉ ወይም ካስነጠሱ በኋላ፣
• የታመመ ሰው ከተንከባከቡ በኋላ፣
• ምግብ ከማዘገጀትዎ በፊት፣ እያዘጋጁ እና ካዘጋጁ በኋላ፣
• ምግብ ከመመገብዎ በፊት እና ከተመገቡ በኋላ፣
• በመጸዳጃ ቤት ከተጸዳዱ በኋላ፣
• እጅዎ በሚታዩ ቆሻሻዎች ከቆሸሸ፣
• እንሰሳትን፣ምግባቸውን እና አይነምድራቸውን ከነካኩ በኋላ፡፡

10
ራሰዎን እና ሌሎችን በኮረና ቫይረስ ከመታመም ይጠብቁ፡፡

በሚከተሉት ጌዜያት እጅዎትን በውሃና በሳሙና በደንብ ይታጠቡ፡-

ከሳሉ ወይም ካስነጠሱ በኋላ፡፡

ታማሚን በሚንከባከቡበት ወቅት፡፡

ምግብ ከማዘጋጀትዎ በፊት፣


እያዘጋጁ እና ካዘጋጁ በኋላ፡፡

ምግብ ከመመገብዎ በፊት፡፡

በመጸዳጃ ቤት ከተጸዳዱ በኋላ፡፡

አጅዎት በዓይን በሚታዩ ቆሻሻዎች


ከቆሸሹ፡፡

እንሰሳትን፣ ምግባቸውን እና
አይነምድራቸውን ከነካኩ በኋላ፡፡

ቫይረሱ በተለያዩ ገጾች እና ቁሶች ላይ ስለሚኖር መኖሪያ ቤቱን ማጽዳት አስፈላጊ ነው፡፡ በተደጋጋሚ የሚነካኩ ገጾቻን
እና ቁሶችን ለምሳሌ ጠረጴዛዎችን፣ ወንበሮችን እና የምግብ ማብሰያ ቦታዎችን ማጠብ እና ማጽዳት፡፡

ቤትን ማጽዳት በጣም አስፋላጊ ነው፡፡


ጀርሞች እንድ ሰው ካሳለ ወይም ካስነጠሰ በኋላ ከሰውየው አካል
ወጥተው በአየር ላይ እንዲሁም በቁሶች ላይ መኖር/መቆየት ይችላሉ፡፡
ሸሹ፡፡
በተደጋጋሚ ማጽዳት የሚከተሉት ጥቅሞች ይኖሩታል፡፡
ው፡፡
የጀርሞችን ስርጭት ይቀንሳል፡፡ እንዲሁም፡-

በእንድ ቁሶች/ገጾች ላይ የሚቆዩትን የጀርሞች ብዛት ይቀንሳል፡፡


የጀርሞችን ስርጭት ይቀንሳል፡፡ እንዲሁም
በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ ምን ማድረግ አለብዎት?
ከታመሙ፣ ከሌሎች ሰዎች ቢያነስ 2 ሜትር ይራቁ፡፡ ይህ ማድረግ ያለብዎት በጣም አስፈላጊው ጉዳይ ነው፡፡

ከታመሙ፣ በቤትዎ ይቆዩ፡፡

11
በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱበት ወቅት አፍና አፍንጫዎትን ይሽፍኑ፡፡

በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱበት ወቅት አፍና አፍንጫዎን ይሽፍኑ፡፡ በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱበት ወቅት ለስላሳ
ወረቀት /soft paper/ ይጠቀሙ፣ ወረቀቱንም የቆሻሻ ማጠራቀሚ እቃ ውስጥ ይጨምሩት፡፡ በሚስሉ ወይም
በሚያስነጥሱበት ወቅት ለስላሳ ወረቀት /soft paper/ ከሌለዎት ክርንዎትን በማጠፍ ይጠቀሙ፡፡ እጅዎትን በውሃና
በሳሙና መታጠብ ካልቻሉ እጅ ማጽጃ ኬሚካል /sanitiser/ ይጠቀሙ፡፡ ኬሚካሉም ቢያንስ 60 በመቶ የአልኮል ይዘት
ሊኖረው ይገባል፡፡ ይህንንም ለማወቅ በማጽጃ ኬሚካል መያዣው እቃ ላይ የተጸፈውን መረጃ ማንበብ ያስፈልግል፡፡

በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱበት ወቅት ለስላሳ


ወረቀት /soft paper/ ይጠቀሙ፣ ወረቀቱንም የቆሻሻ
ማጠራቀሚ እቃ ውስጥ ይጨምሩት፡፡

በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱበት ወቅት ለስላሳ


ወረቀት /soft paper/ ከሌለዎት ክርንዎትን በማጠፍ
ይጠቀሙ፡፡

በሚስሉ ወይም በሚያስነጥሱበት ወቅት አፍና


አፍንጫዎትን ይሽፍኑ፡፡

እጅዎትን መታጠብ ካልቻሉ እጅ ማጽጃ ኬሚካል /


/sanitizer/ ይጠቀሙ፡፡

12
እዝል 2 በቤተሰብ ደረጃ ተደራሽ የሚሆኑ የውሃ፣ ንጽህናና ሀይጅን ተቋማት

1. ወደ መጸዳጃ ቤቱ መሄድ እና መጸዳጃ ክፍሉ ውስጥ መግባት

በቤተሰብ ደረጃ የሚገኙ መጸዳጃ ቤቶች እና ሌሎች የመጠጥ ውሃ እና ንጽህና አገልግሎት መስጫ ተቋማት
በተቻለ መጠን ለተጠቃሚዎቹ ቅርብ መሆን አለባቸው፡፡ በዋነኝነት የቤተሰብ ንጽህና አገልግሎት መስጫ ተቋማት
ከመኖሪያ ቤት ከ 15 ሜትር በላይ በሆነ ርቀት መሰራት የለባቸውም፡፡

ወደ መጸዳጃ ቤት የሚወስደው መንገድ የተስተካካለ ነገር ግን የማያዳልጥ መሆን አለበት፡፡ ወደ መጸዳጃ ቤት


በሚወስደው መንገድ ላይ ሳሮች እና ሌሎች ተክሎች መኖር የለባቸውም (መቆረጥ አለባቸው)፣ ጉድጓዶችም ካሉ
በድንጋይ በመሙላት መስተካካል አለባቸው፡፡ የመንገዱም ስፋት ቢያንስ 90 ሳንቲ ሜትር መሆን አለበት፡፡ ለዓይነ
ስውራን የመንገዱን ዳር ዳር በድንጋይ ማገድ/መገደብ ወይም በነጭ ቀለም መቀባት፣ እና አቅጣጫ መሪ ገመድ ማሰር
በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ ምክንያቱም ድንጋዮቼ
ወይም አቅጣጫ መሪ ገመዱ ግለሰቡን ቀጥታ
ወደ መጸዳጃ ቤቱ
ስለሚያድርሰው/ስለሚመራው ነው፡፡ ነጭ
ቀለም መቀባቱ ደግሞ የእይታ መጠናቸው
ለቀነሰ ነግር ግን ሙሉ በሙሉ አይነ ስውራን
ላልሆኑ ሰዎች መንገዱን ለመጠቀም
ያገለግላቸዋል ምክንያቱም ነጭ ቀለም
የተቀባው መሬት ከሌላው መሬት ጋር ሲታይ
ደምቆ ስለሚታይ የመንገዱን አቅጣጫ ግልጽ
ወደ መጸዳጃ ቤት የሚወስድ አቅጣጫ መሪ ገመድ ስለሚያደርገው ነው፡፡
ehold latrine
ወደ መጸዳጃ ቤቱ ለመሄድ/ለመግባት ደረጃዎች የሚያስፈልጉ ከሆነ (ከመሬቱ አቀማማጥ የተነሳ)፣ ደረጃዎቹ ክፍታቸው
ትናንሽ እና ሰፋፊ መሆን አለባቸው፣ እንዲሁም የእያንዳንዱ ደረጃ ከፍታ እና ስፋት አንድ አይነት መሆን አለበት፡፡
የእያንዳንዱ ደረጃ ስፋት ከ 30 ስንቲ ሜትር ያላነሰ እና ከፍታውም ከ 16 ሳንቲ ሜትር ያልበለጠ መሆን አለበት፡፡ ከ70-
90 ሳንቲ ሜትር ከፍታ ያለው የእጅ መደገፊያም ቢኖርም ጥሩ ነው፡፡ የእጅ መደገፊያ በሚኖርበት ወቅት ብዙ
ተጠቃሚዎች መጸዳጃ ቤቱን በቀላሉ ለመግባት እና ለመጠቀም ይችላሉ፡፡

የተሸከርካሪ ወንበር መንሸራተቻ /Ramps/፤ የተሸከርካሪ ወንበር ለሚጠቀሙ ሰዎች ብቻ ሳይሆን ክራንች
ለሚጠቀሙ፣ ሌሎች የእንቅስቃሴ ችግር ላለባቸው ወይም ለዓይነ ሰውራን ለሆኑ ሰዎችም ነው፡፡ በቂ ቦታ ካለ እና አስፈላጊ
ከሆነ የእጅ መደገፊያ ያለው መንሸራተቻ ቢሰራ ጥሩ ነው፡፡ መንሸራተቻው በጣም ተዳፋታማ መሆን የለበትም፡፡ ይህም
ማለት በ 1ሜትር የመንሸራተቻ ዝርመት ውስጥ ከፍታው ከ10 ሳንቲ ሜትር መብለጥ የለበትም፡፡ ተሸከርካሪ ወንበር
በቀላሉ መጻዳጃ ቤቱ ክፍል ውስጥ ለመግባት እነዲችል ወደ መጸዳጃ ቤቱ መግቢያ በር ፊት ለፊት ከ 100-120 ሳንቲ
ሜትር ስፋት ያለው ቦታ መኖርም አለበት፡፡ መንሸራተቻው በተለይም ውሃ ሲነካው እንዳያዳልጥ በጣም መለስለስ
የለበትም፡፡ መንሸራተቻውን በአካባቢ በሚገኙ ቅሶችም ለምሳሌ ከእንጨት፣ ከቀርቀሃ፣ ከድንጋይ እና በስሚንቶ መሰራት
ይችላል፡፡ መንሸራተቻው እንዲሁም ተንቀሳቃሽ (ሳያስፈልግ ሊነሳ የሚችል) ሊሆንም ይችላል፡፡

13
2. መጸዳጃ ቤት

በሮች እና መግቢያዎች፤ በነጻነት መጠቀም እንዲቻል መጸዳጃ


ቤቱ በር ሊኖረው ሲገባ በሩም በቂ ስፋት ሊኖረው ይገባል (ቢያንስ
90 ሳንቲ ሜትር) እና ለጥያለ (በመጸዳጃ ቤቱ የውስጥ እና የውጭ
ወለል ከፍታ አለመለያየት ወይም ልዩነት ቢኖርም በጣም አነስተኛ
እንዲሆን ማድረግ)፡፡ በሩም በቀላሉ የሚከፈት እና የሚዘጋ
እንዲሁም በአካባቢው ከሚገኙ ቁሶች ለምሳሌ ከጨርቅ፣
ከእንጨት ወይም ከብረት ሊሰራ ይችላል፡፡ በሩም ወደ ውጭ
መከፈት አለበት፡፡ በሩ ወደ ውስጥ የሚከፈት ከሆነ ተሸከርካሪ
ወንበር መጸዳጃ ቤቱ ውስጥ ከገባ በሩን መዝጋት አይቻልም፡፡

ወለሎች፤ መጸዳጃ ቤቱ የተስተካካለ (ነገር ግን የማያዳልጥ) እና


በቀላሉ መጸዳት የሚችል እንዲሁም ከአካላዊ ጉዳታቸው
ምክንያት እና በአጋዥ መሳሪዎች እጦት ምክንያት በመሬት ላይ
እየተንሸራተቱ/እየተሳቡ ለሚሄዱ አካል ጉዳተኞችም አመቺ
አመቺ የሆነ መግቢያ ቦታ፣ ሰፊ በር፣ ከቀርቀሃ መሆን አለበት፡፡ ስለዚህ ማንኛውም የመጸዳጃ ቤት ተጠቃሚ
የተሰራ መቀመጫ ያለው እና በነጸነት መጠቀም ማጸዳጃ ቤቱን ከተጠቀመ በኋላ ማጽዳት አለበት፡፡
የሚያስችል የቤተሰብ መጸዳጃ ቤት፡፡
ብርሀን/መብራት፤ በመጻደጃ ቤቱም ሆነ ወደ መጻዳጃ ቤቱ
በሚውስደው መንገድ ላይ ብርህን/መብራት መኖር በተለይም የእይታ ውስንንት/ችግር ላለባቸው አካል ጉዳተኞች በጣም
ወሳኝ ነው፡፡

የመጸዳጃ ቤቱ ውስጥ፤ መጸዳጃ ቤት ላይ ሲቀመጡ ለመደገፍ እና ሚዛናቸውን ለመጠበቅ እንዲችሉ ከ 70-90 ሳንቲ
ሜትር ከፍታ ያለው ጠንካራ የሆነ የእጅ መደገፊያ (ከብረት፣ ከእንጨት ወይም ከቀርቀሃ የተሰራ) ከመጸዳጃ ቤቱ ወለል
ወይም ግድግዳ ላይ መያያዝ/መገጠም አለበት፡፡ መደገፊያው ከመጸዳጃ ቤቱ መቀመጫ ጎን ወይም ፊት ለፊት መሰራት
እዳለበት የሚወሰነው እንደኣካል ጉዳተኛው ሁኔታና ፍላጎት መሆን አለበት፡፡ አይነ ስውራን የመጸዳጃ ቤቱን መቀመጫ
በቀላሉ እንዲያገኙት አንዳንድ መጠቆሚያ ዘዴዎችን (ለምሳሌ በግድግዳው ላይ መጸዳጃ ቤቱን አቅጠጫ በድምጽ
የሚገልጽ ቴክኖሎጂ ወይም በመጸዳጃ ቤቱ ወለል ላይ የተለየ ድምጽ የሚሰጥ ምልክት ማድረግ) ይቻላል፡፡

የበር እጀታ እና የበር አዘጋግ ሁኔታ፤ ማንኛውም የመጸዳጃ ቤት ተጠቃሚ በተለይም ሴቶች እና ልጃገረዶች በመጸዳጃ
ቤቱ ወስጥ በነጻነትና በምቾት መጠቀም አለባቸው፡፡ በአነስተኛ ወጪ የሚሰሩ የበር እጀታዎች እንዱ ከእንጨት የሚሰራ
እና ከወለሉ ከ 90-120 ሳንቲ ማትር ባለው የበሩ ክፍታ ላይ ሊሰራ ይችላል፡፡ በሩም ሙሉ በሙሉ ወደውጭ የሚከፈት
እና ለተሸከርካሪ ወንበር ተጠቃሚዎች፣ ለክራንች ተጠቃሚዎች ወይም አቅም ላነሳቸው ሰዎች በቀላሉ ለመዝጋትም ሆነ
ለመክፈት እንዲያመች በውጭ እና በውስጥ በኩል መያዣ/እጀታ ሊኖረው ይገባል፡፡

የክፍሉ መጠን፤ አስፈላጊ ከሆነ ተሸከርካሪ ወንበር በቀላሉ መዞር እንዲችል መጸዳጃ ቤቱ ስፋት ከ120-150 ሳንቲ ሜትር
ዲያሜትር ያለው ቦታ እና ተሸከርካሪ ወንበሩን መጸዳጃ ቤቱ ውስጥ በአግባቡ ለማስቀመጥ ከመጸዳጃ ቤት መቀመጫው
እስከ ክፍሉ ግድግዳ ቢያነስ 80 ሳንቲ ሜትር ያላነሰ ከፍተት ያለው ቦታ ሊኖረው ይገባል፡፡ ለጊዜው በቤተሰቡ ውስጥ
የተሸከርካሪ ወንበር ተጠቃሚ ከሌለ፣ በመጸዳጃ ቤቱ ክፍል ውስጥ ምን ያህል ቦታ እንደሚያስፈልግ ለማወቅ
የሚከተለውን ዘዴ መጠቀም ይቻላል፡፡ መሬት ላይ ያለውን ቦታ በድንጋይ ወይም በእንጨት ምልክት ማድረግ ከዚያም
የተለያዩ ተጠቃሚዎች የተደረገው ምልክት ውስጥ እየገቡ በመንቀሳቀስ እና መጸዳጃ ቤት መቀመጫ ላይ እንዲቀመጡ
በማሰብ በቂ ቦታ መሆኑን መሞከር እና አስፈላጊ በሚሆንበት ወቅት የቦታውን ስፋት ማስተካከል /ማስፋት ወይም
ማጥበብ/፡፡ ክራንች ወይም ረዳት/አጋዥ ለሚያስፈልጋቸው የአካል ጉዳተኞች እንዲያገለግል ክፍሉ ተጨማሪ ስፋት
እንዲኖረው ማድረግ ሊያስፈልግ ይችላል፡፡ የክፍሉ ከፍታ ሁሉም የቤተሰብ አባላት (አካል ጉዳተኛም ሆነ ጉዳት አልባ)
በቀላሉ ሊገቡበት እና በአግባቡ ሊጠቀሙበት የሚችል መሆን አለበት፡፡

14
የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ፤ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ላይ
መቀመጥ ለሚቸገሩ፣ ለነፍሰ ጡሮች፣ ለአረጋውያን እና
ለአካል ጉዳተኞች አመቺ መሆን ይኖርበታል፡፡ መቀመጫው
በቦታው ላይ በቋሚነት የሚቀመጥ ወይም ሌሎች
ቤተሰቦች እንዲጠቀሙበት ሲፈለግ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቃሽ
መሆን ይችላል፡፡

በገጠር አካባቢ ለሚኖሩ ቤተሰቦች ተንቀሳቃሽ የመጸዳጃ


ቤት መቀመጫ በአካባቢ በሚገኙ ቁሳቁሶች (እንጨት፣
ቀርቀሃ፣ ፕላስቲክ) መስራት ጥሩ፣ ወጪ ቆጣቢ እና ቀላል
አማራጭ ነው፡፡ መቀመጫው በቀላሉ እንዲጸዳ እና ጠንካራ
እንዲሆን ቀለም ወይም ቫርኒሽ ሊቀባ ይችላል፡፡

ለአካል ጉዳተኞች አመቺ እንዲሁም የተሰራው መቀመጫ


ተንቀሳቃሽ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫን ከብረት እና
ለቤተሰቡ በተሰራው መጸዳጃ ቤት መቀመጫ ስላብ/ክዳን
ከእንጨት መሰራት ይቻላል፡፡
ላይ ሊቀመጥ ይቻላል ወይም ከመቀመጫው/ወንበሩ ስር
ባሊ በማስቀመጥ እንደመጸዳጃ ቤት ሊቀመጥ ይችላል፡፡ ባልዲን እንደመጻዳጃ ቤት መጠቀም የአጠቃቀም ነጸነት ላይሰጥ
ይችል ቢሆንም መንቀሳቀስ ለማይችሉ/የእንቅስቃሴ ውስንንት ላለባቸው ሰዎች ግን በጣም ጠቃሚ ይሆናል፡፡

አይነ ምድሩ እንዳይረጭ እና አካባቢውን እንዳያበላሽ ለመከላከል፣ እንደመከላከያና/መጋረጃ እንዲያገለግል


በመቀመጫው በፊትለፊት በኩል መስራት ይቻላል፡፡ ለምሳሌ አገልግሎት የሰጡ የፕላስቲክ የውሃ ጠርሙሶችን
በቁመታቸው በመቁረጥና በመዘርጋት በፊት ለፊት ባሉት የመቀመጫው/የወንበሩ እግሮች አግዳሚ ላይ በማሰርና
በመሸፈን እይነ ምድሩ ከመቀመጫው ውጭ እንዳይረጭ ማገድ ይችላል፡፡

3. የመጠጥ ውሃ

በጀሪካን የተጠራቀመ ውሃን መጠቀም ለማይችሉ አካል ጉዳተኞች የቤተሰብ መጠጥ ውሃን በተለያዩ የውሃ
ማጠራቀሚያዎች ለምሳሌ በደንብ በሚከደን፣ ፎሴት በተገጠመለት እና አካል ጉዳተኛው (አቅሙ ደከም ላለ፣ ሚዛኑን
መጠበቅ ለሚቸገር፣ በአንድ እጁን ብቻ ለሚጠቀም ወዘተ…) በቀላሉ እና በራሱ ሊጠቀምበት በሚችል ባልዲ ውስጥ
ማጠራቀም ይቻላል፡፡

4. እጅ እና ገላ መታጠብ

እጅ መታጠብ፤ ከመሬት በላይ በተለያየ ከፍታ (እንደ አስፈላጊነቱ ከ50 እስከ 90 ሳንቲ ሜትር) የተዘጋጁ የእጅ መታጠቢያ
ከውሃና ሳሙና ጋር በግቢው ውስጥ እና በመጸዳጃ ቤቱ አቅራቢያ መዘጋጀት አለበት፡፡ አቅሙ ደከም ላለ ወይም በአንድ
እጅ ብቻ ለሚጠቀም ሰው ትናንሽ ጀሪካኖች ወይም የፕላስቲክ ጠርሙሶችን ለእጅ መታጠቢያነት መጠቀም ተመራጭ
ናቸው፡፡ የእጅ መታጠቢያው አካባቢ እንዳይጨቀይ እና እናዳያዳልጥ የእጅ እጣቢ ውሃውን ለመያዝ በእጅ መታጠቢያው
አካባቢ ጠጠር መበተን ወይም ባሊ ማስቀመጥ ያስፈልጋል፡፡

15
የተለያዩ የእጅ መታጠቢያ አማራጮችን ከመሬት ባላይ የሚኖራቸውን ከፍታ በማስተካከል ወይም የሰው
መቀመጫ በማዘጋጀት ተደራሽ ማድረግ ይቻላል (ምስሉን እንደሚከተለው ይመልከቱ)፡፡

1.5 ሊትር ውሃ በፕላስቲክ ውህዱን በደንብ ይነቅንቁት በጣም ቀላሉና


ጠርሙስ ውስጥ እና 30
ርካሽ/አዋጭ የሆነው
ግራም ኦሞ ያዘጋጁ
በቤተሰብ ደረጃ የእጅ
ማታጠቢያ ፈሳሽ ሳሙና
ኦሞውን ወደ አሰራር ዘዴ የፕላስቲክ
ጠርሙሱ ይጨምሩ ጠርሙስ /highland/
ውስጥ ውሃ እና ኦሞ
በመጨመር በደንብ
በመነቅነቅ እንዲቀላቀሉ
በማድረግ ነው፡፡ በቀላሉ
ፋሻሹን በአጅ አጥበት
ወቅት ለመጠቀም
እንዲቻል የጠርሙሱን
ክዳን መብሳት
የጠርሙሱን ክዳን ሳሙናማ ውሃውን ያስፈልጋል፡፡ አሰራሩንም
የሳሙና ይዘት ያለው
በሚስማር ይብሱት ውሃ በመጠቀም እጅዎን ይታጠቡ የሚያሳዩ ምስሎች በግራ
በኩል ይታያሉ፡፡

16

You might also like