You are on page 1of 1

ሹክ and ቱስ Media

facebook.com/permalink.php

#የአርበኛው መልዕክት/ሼር
"ሁለት ሚሊዮን ፋኖ በፍጥነት ይዘጋጅ!"

አርበኛ ዘመነ ካሴ ከባህርዳር ወህኒ ቤት

መጋቢት 10 ቀን 2015 ዓ.ም

ሁሉም አማራ በአካልም በመንፈስም ይዘጋጅ። ሁሉም አማራ ራሱን ያስታጥቅ። ጠላቶቻችን ወግተው
ሊያጠፉን ታይቶ በማይታወቅ አኳኋን እዚህም እዚያም ራሳቸውን እያዘጋጁ ነው።እንደ ህዝብ መቀጠላችን
የሚወስነው የመጨረሻው ፍልሚያ ሊጀመር የቀሩት ቀናት የተቆጠሩ ናቸው።

ወልቃይት ላይ ከተሸነፍን አውቶማቲካሊ አዲስ አበባም ላይ እንሸነፋለን።አዲስ አበባ ላይ ስንሸነፍ ወልቃይትና


ራያ ላይም እንሸነፋለን። ለሸዋ የተወረወረ ጦር መተከል ላይ ሰው ይጥላል።ደራ ላይ የተተኮሰ ጥይት ወሎ
ቤተአማራ ላይ ይገላል። ጎንደር፣ሸዋ፣ጎጃምና ወሎ የሚሉ አውራጃዊ ስሞችን ለጊዜው ለውብ ባህላዊ
ዘፈኖቻችን እንተዎቸው።ከድል መልስ እንቅጥቅጡንም፣ድልቁንም እናወርድባቸዎለን።

አሁን ጆሯችን አንድ ነገር ብቻ ይሰማል፣አፋችን አንድ ቃል ብቻ ይናገራል፦ አማራ የሚል ብቻ አማራ አማራ
አማራ

ሁሉም ለመጨረሻው ትንቅንቅ ይዘጋጅ። እጣፋንታችን ወይ ማሸነፍ አለበለዚያ ከምድረ ገጽ መጥፋት ነው።
ከ50 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይዞ መሸነፍ ውርደትም፣ ሀፂያትም ነው። ለድል እንሰለፍ! ድል እናደርጋለንም።

ያለበለዚያ ያጠፉናል። የትኛውም ጠላት በየትኛውም አቅጣጫ ጦርነቱን ይጀምረው ከአስር በማይበልጡ ቀናት
ውስጥ አፍንጫውን ተቆርጦ መመለስ አለበት።

አማራም ውድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ቢያንስ የአንድ መቶ አመት የሰላም እንቅልፍ ያስፈልጋቸዎል። የሚያድነን
እግዚአብሔር እና ክንዳችን ብቻ ነው። ስለዚህ በፍጥነት 2 ሚሊዮን የአንድ አማራ ፋኖን አደራጅተን በዬ
አቅጣጫው ለማትመም እንዘጋጅ። የድላችን ውል የተቋጠረው አንድነታችን ላይ ነው።

[ክፋት ለማንም፣በጎነት ለሁልም]

ድል ለአማራ ህዝብ

ድል ለጉራጌ ህዝብ

ድል ለመላዉ ኢትዮጵያዊያን እና ለእዉነተኛ ኢትዮጵያዊነት!

ዘመነ ካሴ ከባህርዳር ወህኒ ቤት

ዘመነ ካሴ ከባህርዳር ወህኒ ቤት

1/1

You might also like