You are on page 1of 5

FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.

facebook.com/fanabroadcasting/posts/pfbid02UXf8Dpnu8sRTG9Fgqm4jaue6qCRukXzDrTG3Qp9sZxcXmdXp2cK3Dz
2Dt877EmWml

በአዲስ አበባ ከያዝነው ወር ጀምሮ በመንግሥት መስሪያ ቤቶች የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከመጋቢት ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ላይ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እንደሚጀመር የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት
ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ገለጸ፡፡

በኤጀንሲው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ እንደገለጹት÷ ተጠሪነታቸው ለከተማ አሥተዳደሩ በሆኑ
የመንግሥት ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞችን በወሳኝ ኩነት ሥራው ተደራሽ ለማድረግ እየተሠራ ነው፡፡

ለዚህም ኤጀንሲው እና የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ በሥራው አተገባበር
ላይ የየራሳቸውን ድርሻ ለይተው ተፈራመዋል ነው ያሉት፡፡

ስምምነቱም በየደረጃው ባሉ በከተማዋ የመንግስት መስርያ ቤቶች ተፈፃሚ ይደረጋል ነው ያሉት፡፡

የመንግስት ሠራተኞችም÷ ለወሊድ እረፍት የሚወጡ ወላጆች (አባት እና እናት) የልጆቻቸውን የልደት ምዝገባ
ማስረጃ እንዲሁም ለጋብቻ እረፍት የሚወጡ ተጋቢዎች የጋብቻ ምዝገባ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ይገደዳሉ
ብለዋል፡፡

በተጨማሪም የቅርብ የቤተሰብ አባል ህልፈት በመከሰቱ እረፍት የሚወጡ የሞት ምዝገባ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ፣
የጉዲፈቻ እና የፍቺ ኩነት ሲከሰትም በተመሳሳይ ሁኔታ የምዝገባ ማስረጃውን ማቅረብ አስገዳጅ ነው ተብሏል፡፡

ሥራውም ከመጋቢት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ነው አቶ ዮሴፍ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት


የተናገሩት፡፡

ልደት በ90 ቀናት እንዲሁም ጋብቻ፣ ሞት፣ ፍቺ እና ጉዲፈቻን በ30 ቀናት ውስጥ ማስመዝገብ ይጠበቃል ነው
ያሉት፡፡

ምዝገባው በዲጂታል እንደሚከናወን እና ለተመዝጋቢዎች የሚሰጡ የህትመት ግብዓቶችም ዝግጁ መሆናቸውን


አረጋግጠዋል፡፡

ሠራተኞች ምዝገባውን ማከናወን ያለባቸው በሚሠሩበት መስሪያ ቤት ሳይሆን በሚኖሩበት ወረዳ መሆኑንም
አስረድተዋል።

ኤጀንሲው እስካሁን በአዲስ አበባ ከሚገኙ የጤና ተቋማት፣ ዕድሮች እና ፍርድ ቤቶች ጋር የወሳኝ ኩነት ሥራውን
እያከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በዮሐንስ ደርበው

#Ethiopia
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

1/5
All reactions:

296 296
13

Like

Comment

Share

13 comments

Oldest


Natinael Samuel
እኔ ደሞ አስቤዛ ይሰጣችኋል የምትሉ መስሎን

Like

Reply

4h

2/5
Getachew Tefera
Kkkkkkk ለደትና ሞት መመዝገብ አልነበረም እንዴ ስራው ወደ ሰራተኛ ምዝገባ ዞረሳ

Like

Reply

4h
Edited

Melese Gobezie
hulam yemiwotaw heg seratgnawun lemasakek eng lmetekmema kere

Like

Reply

4h

የወይራው መዶቃድቅ
ቢሔራችውን ለመለየት ነው??

Like

Reply

4h

Nebiyu Negede
የጨነቀለት አለ አዝማሪው

አሁን የህዝቡ አንገብጋቢ ጥያቄ ምንድን ነው ብላቹ ለምን አትጠይቁም

Like

Reply

4h

3/5
Kelelaw Gedle
የግድያና ሞት መጠን ለመመዝገብ አይበዛባችሁም

Like

Reply

4h

Top fan
Muzei Abbas
የምታቀርቡት መረጃ ለህዝቡ ምንም የማይፈይድ ነው

Like

Reply

4h

Hawult Tesfa
ጅል አይሙት አሉ ይልቅስ ገበያውን አረጋጉ

Like

Reply

4h

Asnakech Gelan

Like

Reply

4h

4/5
Wondu Wagaye Yanda
Please understand the people first then everything will be comes later

Like

Reply

4h

Üm Zøllå Yē Kīrkös
በ ሸገር ከተማስ

Like

Reply

3h

Teshme Konjo
ባለግዜ አጀንዳ መፍጠሩ ነው በቤቱ ሰራተኛው ዱሮም ዱሮ ነው አሁን የነሱን ኢ-ፍታዊ ያሃብት ክፍፍል
ማዘናጊያ ስራ ቆሞ ባለ ጉዳይ ይንገላታል እግዚኦ

Like

Reply

2h

Write a comment…

Press Enter to post.

5/5

You might also like