Professional Documents
Culture Documents
East Gojjam Communication
East Gojjam Communication
የሳውዲ አረቢያ መንግስት ከ13 ሽህ በላይ ለሚሆኑ የምስራቅ ጎጃም ዞን ስራ ፈላጊዎች የስራ እድል
መፍቀዱን የዞኑ ስራና ስልጠና መምሪያ ገለጸ፡፡
**************
( የካቲት 27/ 2025 ዓ / ም ) ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዮኒኬሽን፣ የመምሪያው ሓላፊ አቶ ፀሐይ
ቦጋለ እንደተናገሩት ሀገራችን ከውጭ ሀገራት ጋር ያላት የዲፕሎማሲ ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ
እየጨመረ በመምጣቱ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ለ 13 ሽህ 78 የምስራቅ ጎጃም ዞን ስራ ፈላጊ
ዜጎች የስራ እድል ፈቅዷል፡፡
የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት እድሉ በዞኑ ውስጥ ለሚገኙ ወረዳና ከተማ አስተዳደር ስራ ፈላጊዎች
ተከፋፍሎ የተሰጠ ነው ያሉት አቶ ፀሐይ ምዝገባው ከየካቲት 27/2015 እስከ መጋቢት 3/2015
ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የእድሉ ተጠቃሚ ስራ ፈላጊዎች ለ20 ቀናት አጫጭር ስልጠናዎችን በኮሌጆች
ከወሰዱ በኋላ የብቃት ማረጋገጫ ፈተናውን ያለፉት መጋቢት 26 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ሳውዲ
አረቢያ በረራ ያደርጋሉ ብለዋል፡፡
የእድሉ ተጠቃሚ ዜጎች ሴቶች ሲሆኑ ሙሉ ጤነኛና መልካም ስነምግባር ያላቸውን ስራ ፈላጎዎች
ሁሉ በወቅቱ በመመዝገብ ተጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚገባ ሓላፊው አሳስበዋል፡፡
የሳውዲ አረቢያ መንግስት ከሀገራችን ጋር ካላት ጠንካራ ዲፕሎማሲ አኳያ በሀገር ደረጃ ለ500 ሽህ
እንዲሁም በክልላችን ደግሞ ከ150 ሽህ በላይ ስራ ፈላጊ ዜጎች የስራ እድሉን እንደፈቀደ መረጃዎች
ያመለክታሉ፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን በተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን
ሊንኩን በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ
https://www.youtube.com/channel/UCyq4rgufD2TbpsN2zUEZp3Q
ቴሌግራም https://t.me/eastgojjamcommunication
ቲውተር https://twitter.com/home?lang=en-gb
ኢንስታግራም
173 42 64
Most relevant
Write a comment…
Press Enter to post.
አማራ ደመላሽ
በአገር አቀፍ ደረጃ ለ500ሺ ኢትዮጵያዊያን የተሰጠ እድል መሆኑን መጀመሪያ
ግለጹት። ምስ/ጎጃም 13ሺ ያገኘው የአገር ኮታ ተከፋፍሎ የደረሰውን ድርሻ
ነው። አጻጻፋችሁ ሳውዲ መንግስት ቀጥታ ለምስ/ጎጃም እንደሰጠ ያስመስላል።
አስተካክሉት። የማያስፈልግ ውዝግብ እያሰነሳችሁ ህዝቡን ማግኘት የሚገባውን
እድል አታሳጡት።
ብአዴን
Like Reply 2w
Melkam Bezaneh
ይህ ነገር ለምን ለአማራ ክልል ብቻ ተፈቀደ ደግሞ ሴት ብቻ እኔ እንጃ በሰላም
አይመስለኝም ደግሞ ሳውድ አረቢያ እንዴው ስሙ ሲጠራ ስሰማውም ደሜ ነው
የሚፈላው ለሰው ሽንት ቤት ለማጠብ ስራ ፈላጊወች ተፈለጎ
Like Reply 2w
Anteneh Wondimu
በስተጀርባው ምን ነገር ይዞ ነው የሚለውን በደንብ ማጤን ይገባል?
Like Reply 2w
1 Reply
Sintayehu Assefa
አሁን በእናንተ ቤት ሥራ ፈጠራ መሆኑ ነው አይደል? ሰው በሀገሩ ሰርቶ
መለወጥ ሲገባው የመኖር ዋስትናውን እና ብሔራዊ ሰላሙን በማሳጣት ተዘዋዋሪ
ቅኝ ግዛት እና ዘመናዊ የባርያ ንግድን አስፈጻሚ መሆናችሁን አሳይታችሁናል።
Like Reply 2w
Tadesse Mengesha
ጥሩ ነገርግን እንዴት ለአንድ ዞን ብቻ ስራድል ይፈጥራሉ ሌሎችን ለማዳረስ
ቢሞክሩ
Like Reply 2w
1 Reply
Belsti Takele
ባርነት ለመላክ ነዉ እንዴ 2
Like Reply 2w
1 Reply
Hilm Endefechew Nw
Ere eferu mn ayinet worada nachu ehitochachen
asalfachu letshetu endebaria ere niku be egziabhere
Like Reply 2w
Kefale Getenet
እኔ አልቀበለውም የጠቀሙን መስለው ስልታዊ ጥቃት ሊፈፅሙብን ነው.
እንደወረደ አንቀበል
3
Like Reply 2w
Habtie Marelign
ከበስተጀርባው ምን አንግቦ ይሆን??????!!!! እንደወረደ የምንቀበላት ነገር ግን
????? ለምን ምስራቅ ጎጃም ተመረጠ??? ምናልባት ተመሳሳይ ባህል፣ወግ
ማህበራዊ ኑሮ ያልተበረዘ፣እምነት ፥ተመሣሣይ የአኗኗር ዘይቤ ጀግንነትና
የመሳሰሉ ነገሮችን ለመበረዝ ወይስ እውነተኛ ስራ ፈጠራራራ???? ኧሯሯሯ እኔ
እንጃጃጃጃጃ
Like Reply 2w
Nati Dawit
ይኼ ውሻ ባዴን መቸም አይሰለጥም መቸም ብሎ ከተኝአበት አይነሳም ሳውዲያ
አረቢያ ምሥራቅ ጎጃም ብቻ ለምን ነው የተፈለገው ከርሳሙ ውሻው ባዴን
ልታሳርዳቸው ልታስበላቸው ይሆናል እንጅ ባዴን ማለት ፈረስ ማለት ነው
ወይም አህያ ነው ፈረስ ሊሞት ደርሶ ነፍሱ እስከምትወጣ ድረስ መብልን
አይተውም ባዴንም እንደዚአው ነው ባዴን የአማራን ህዝብ ባንድ ጎን ለኦነግ
አሺከር ሁኖ ያስጨፈጭፋል ባኔድ … See more
Like Reply 2w
Negese Yesawku
የሚያበረታታ ጥሩ ጅማሮ ነው ብዙ የሀገራችን ወጣቶች ስራ ፍለጋ በህገወጥ
መንገድ ባህር እንዲሁም በረሃ አቁርጠው ሲሄዱ ስንቶች የአውሬ እራት ሆነዋል
ግን ያልገባኝ ነገር process የሚያልቅበት ሂደት like visa በመንግስት በኩል
ነው ወይስ ህጋዊ በሆኑ የግል ኤጄንሲ ነው?
Like Reply 2w
Sisay Sis
Good job
Like Reply 2w
Bamlaku Temesgen
እውነት ከሳውዲ ጋር ጠንካራ ግንኙነት አለን? ያ ከሆነ በሳውዲ ይኖሩ በነበሩ
ኢ/ያን ላይ ያነን አይረሴ ዘግናኝ በደል ያአደረሰችባቸው ለምን ነበር? የፖለቲካን
ቆሻሻነት የምታየው በእንደዚህ አይነት ኢ-ተገማች ተግባሩ ነው!! በአንድ ወቅት
ዓይንህን ላፈር ያለህ በሌላ ጊዜ ያላንተ .... ይልሀል። እውነት ሆይ የት ነሽ?
Like Reply 2w Edited
Hiwot Zelalem
ሰለሜ!ሰለሜ!,,,,,አረብ ሀገር ነዉ ያላችሁ?አፈርኩባችሁ ሰዉ ባገሩ ምነዉ ሰርቶ
እንዲኖር ምቹ ሁኔታ ብትፈጥሩለት ለግርድና አረብ አገር ድረስ ያዉም
ከበስተጀርባዉ ብዙ ሴራ ይኖረዋል።ከአረብ ሀገርስ ስንቱ ነዉ እየታፈሰ በቅርብ
ይመለስ የነበር???
Like Reply 2w
Tesfaye Best
ቀጥላችሁ ደግሞ በሀገሪቱ 500,000 ዜጎች የስራ እድል ተፈጠረ ልትሉ ነው
አይደል
Like Reply 2w
አባይ ዳር ነው ቤቴ
አይጣል ነው ሽንት ቤት ለማጠብ ነው የተማረ ሀይል የፈለጉት የገባው
ሰው ካለ በትህትና አስረዱኝ ለምንስ ሴት ብቻ ተፈለገ? ከጀርባው የማን እጅ
አለበት? በክፍያ ዙሪያስ?
Like Reply 2w
1 Reply
Tigist Tesfaye
Keep up the good work!
Like Reply 2w
Alemker Dawit
የጋራ ግንኙነትን ማጠንከር ለስራ እድል ፈጠራ ጉልህ ድርሻ አለው፡፡
Like Reply 2w
Kassahun Abebe
የምዝገባ ቦታ እና የስልጠና ሁኔታ በደንብ ይገለጽ ።
Like Reply 2w
Lisa Mesel
ሰምምነት ነዉ ብላችሀል ግን የወር ክያቸዉም በግልፀ መቀምጥ አለበት??
Like Reply 2w
ደረብ ዘለቀ
በሽታ ምን አይነቱን የስራ እድል ተፍጥሮአል አያ
Like Reply 2w
Přıņčə Thəø
ሴቶችን ብቻ ለምን
Like Reply 2w
Agnto Dagnaw
ኧረ ሴቶች ብቻ አዝናለሁ ለምን ሴት ብቻ ፈለጉ
Like Reply 2w
Bernabas Anagaw
Next you are preparing for a member of UAE. I do not
blame for having a job for jobless but I have doubt on
ideological transfer.
Like Reply 2w
Yibeltal Shiferaw
ስንቶች በህገወጥ መንገድ እየሄዱ በየበርሀዉ ከሚቀሩ በህጋዊ መልኩ መሄዳቸዉ
የተሻለ ነዉ
Like Reply 2w
Tsehay Bogale
በቸና፣ደ/ማርቆሥ፣ደጀን፣ሞጣ እና ሉማሜ ቴክኒክና ሙያዎች ላይ ሥልጠናው
ይሠጣል።
Like Reply 2w
2 Replies
Mihretu Yizengaw
ጥሩ መሻሻል ነው፤ ሕዝባችን በሕገ መንገድ እየሔደ ሲሰቃይ ነበር አሁን ላይ
በሕጋዊ መንገድ መጀመሩ የተሻለ ያደስገዋል።
Like Reply 2w
Fikadie Zewdu
እንዲ እያደረጋችሁ አገራችን አዋርዷት
Like Reply 2w
Denkew Lengerw
ምን ዋጋአለው አሁን የድሃ ልጅ የስራ እድላ የጠበበ
ይህም በሙስ እና የባለስልጣን ዘመዶች ብቻ ይሆናል።
Like Reply 2w
1 Reply
py
Yilma Demeke
ምነው ሴቶችን ብቻ ፈለጉ
Like Reply 2w
1 Reply
Most Relevant is selected, so some comments may have been filtered out.