Professional Documents
Culture Documents
መጋቢት 2006
ኢ/ከ/ል/ቢሮ
ባህር ዳር
መመሪያ ቁጥር 15/2006 ዓ.ም
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የእምነት ተቋማት
የአምልኮና የመቃብር ቦታ አሰጣጥ መመሪያ
የከተሞችን የመሬት ሃብት አጠቃቀም ከብክነት የጸዳ በማድረግ ውስን የሆነውን ይህንኑ
ሀብት በቁጠባና በተፈቀደው ፕላን መሰረት መጠቀም አስፈላጊ በመሆኑ፣
በተሸሻለው የብሔራዊ ክልሉ ህገ-መንግስት አንቀጽ /27/ ንዑስ አንቀጽ /1/ መሰረት
የሃይማኖት፣ የእምነትና የአመለካከት ነፃነት የተከበረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የተለያዩ
የእምነት ተቋማት የአምልኮ ቦታ ጥያቄ እየተበራከተ በመምጣቱ በክልሉ ከተሞች ውስጥ
አሁን በተዘበራረቀ መንገድ እየተሰጠ ያለውን የአምልኮ እና የመቃብር ቦታ አሰጣጥ
ወጥነት ባለው መንገድ ማስተናገድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣
የከተማን ቦታ በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004ዓ.ም አንቀጽ /12/ ንዑስ
አንቀጽ /1/ ፊደል ተራ ቁጥር /መ/ እና በተሻሻለዉ የከተማ ቦታ ሊዝ ይዞታ ማስተዳደሪያ
ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 103/2004 ዓ.ም አንቀጽ /23/ ንዑስ አንቀጽ
/4/ መሰረት የእምነት ተቋማት ቦታ አሰጣጥ የክልሉ መስተዳድር ም/ቤት በሚሰጠው ውሳኔ
መሰረት እንደሚስተናገድ አስቀድሞ የተደነገገ በመሆኑ፤
የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተሻሻለው የብሄራዊ ክልሉ ህገ-መንግስት
አንቀጽ /58/ ንዑስ አንቀጽ /7/ እና የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር
721/2004 ዓ.ም አንቀጽ /33/ ንዑስ አንቀጽ /2/ ስር በተሰጠው ስልጣን መሰረት ይህንን
መመሪያ አውጥቷል፡፡
ክፍል አንድ፡
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ “የእምነት ተቋማት የአምልኮ እና የመቃብር ቦታ አሰጣጥ ክልል
መስተዳድር ምክር ቤት መመሪያ ቁጥር 15/2006ዓ.ም ”ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
2. ትርጓሜ
የቃሉ አግባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ፡-
1) “አዋጅ” ማለት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 ዓ.ም
ነው፡፡
2) “ከተማ” ማለት ማዘጋጃ ቤት የተቋቋመበት ወይም ሁለት ሺህ ወይም ከዚያ በላይ
የህዝብ ቁጥር ያለውና ከዚህ ውስጥ ከሃምሳ በመቶ (ከ50%) በላይ የሚሆነው ነዋሪ
ከግብርና ውጭ በሆነ ሥራ ላይ የተሰማራ ሆኖ የሚገኝበት አካባቢ ነው፤
3) "የአምልኮ ቦታ" ማለት ህጋዊ እውቅና ባገኙ የክልሉ ከተሞች ውስጥ የሚገኝ ስፍራ
ሆኖ አግባብ ባለው ከተማ ፕላን መሰረት ለአምልኮ አገልግሎት እየዋለ ያለ፣
የተመደበ ወይም የሚመደብ ቦታ ነው ፤
4) " የሃይማኖት ተቋም" ማለት የአምልኮና የእምነት አገልገሎቶችን ለማካሄድ የተቋቋመ
ማናቸውም አካል ነው ፤
5) " የመቃብር ቦታ " ማለት በአንድ ከተማ የእድገት ፕላን ላይ ለቀብር አገልግሎት
የተመደበ ወይም ለዚሁ አላማ በመዋል ላይ ያለ ማናቸውም ስፍራ ነው ፤
6) “አግባብ ያለው አካል’’ ማለት የከተማ መሬትን ለማስተዳደር እና ለማልማት በህግ ስልጣን
የተሰጠው አካል ነዉ፤
7) “ምክር ቤት’’ ማለት የክልሉ መስተዳድር ም/ቤት ነው፤
8) "ቢሮ" ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ነው፡፡
3. የተፈፃሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ በክልሉ ውስጥ በሚገኙ ከተሞች ሁሉ ተፈፃሚነት ይኖረዋል፡፡
4. ዓላማ
ክፍል ሶስት
ቦታ ፕላን ጥናት፡-
ሀ/ በአንድ ከተማ ዉስጥ በጥናት የሚመላከት የአምልኮ ማከናወኛ ቦታ ድንበር/ወሰን
ከሌላ እምነት የአምልኮ ማከናወኛ ቦታ ያለው ርቀት ቢያንስ ከ500 ሜትር ሬድዬስ
በላይ መሆኑን፤
5) በከተማው ውስጥ ባሉት የመቃብር ቦታዎች ቀብር የማይቻልበት ሁኔታ ሲያጋጥም በከተማ
አስተዳደሩ ባለቤትነት የሚተዳደር ሌላ የመቃብር ቦታ መዘጋጀት ይኖርበታል፡፡
ክፍል አራት
ክፍል አምስት፡
የአምልኮ እና የመቃብር ቦታ ስለማስረከብና ስለግንባታ ክትትል
2) የአምልኮ ማከናወኛ ህንጻ ስራው ከመጀመሩ አስቀድሞ ፕላኑ እና ዲዛይኑ አግባብ ላለዉ
አካል ቀርቦ መረጋገጥና መፈቀድ ይኖርበታል፤
5) አግባብ ያለዉ አካል በዚህ አንቀጽ ከንኡስ አንቀጽ /1/ እስከ /4/ የሰፈሩትን ድንጋጌዎች
አፈፃፀም በቅርብ የመከታተል እና የመቆጣጠር ሀላፊነት ይኖርበታል፡፡
ክፍል ስድስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
16. የመተባበር ግዴታ
ማንኛውም ሰው ይህንን መመሪያ ለማስፈጸም በሚደረግ ማናቸውም እንቅስቃሴ አስፈጻሚውን
አካል የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡
17. ተፈጻሚነት ስለማይኖራቸው መመሪያዎች
ቀደም ሲል ወጥተው በክልሉ ውስጥ በስራ ላይ የቆዩ የአምልኮና የመቃብር ቦታ ምደባ
መመሪያዎች በዚህ መመሪያ የተተኩ በመሆናቸው በመመሪያው ውስጥ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ
ተፈጻሚነት አይኖራቸውም፡፡
ባህርዳር
መጋቢት 30 ቀን 2006 ዓም