Professional Documents
Culture Documents
Commitee Report
Commitee Report
አዘጋጅ ኮሚቴ
አቶ ሙላቱ አበበ-----------------------------
ሰብሳቢ
ወ/ሮ በላይነሽ ወረኛ-------------------------
አባልና ጸሐፊ
አቶ አበባው መኮነን------------------------ አባል
ባህር
ወ/ሮ መልሽው ምህረቴ-------------------- "ኦገስት
አቶ ጌታቸው አስረስ------------------------ "
i|Page
ማውጫ
1. መግቢያ..................................................................................................................................................1
2. አላማ.....................................................................................................................................................1
2.1. አጠቃላይ አላማ................................................................................................................................1
2.2. ዝርዝር አላማዎች.............................................................................................................................1
3. የውሳኔ ሃሳብ ለማዘጋጀት መነሻ የሆኑ ሁኔታዎች...............................................................................................2
4. የካፍቴሪያ አገልግሎቱ በተሟላ ሁኔታ መጀመሩ ያለው ጠቀሜታ...........................................................................2
4.1. ለተቋሙ.........................................................................................................................................2
4.2. ለሰራተኞች......................................................................................................................................3
4.3. ለመረዳጃ ማህበሩ..............................................................................................................................3
5. በተቋሙ ግቢ ውስጥ የተሟላ የካፍቴሪያ አገልግሎት ለማስጀመር የሚያስችል የውሳኔ ሃሳብ ለማቅረብ የታዩ ጉዳዮች........3
5.1. የተለያዩ ተቋማትን ልምድ መወሰድ.......................................................................................................4
5.2. ንጋት ኮርፖሬት የሻይ ቡና መስተንግዶ ሁኔታ............................................................................................5
5.3. የንጋት ኮርፖሬት የዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት የሰራተኞች መረዳጃ ማህበር ሁኔታ.........................................6
5.4. የንጋት ኮርፖሬት ማዕከል የሰራተኞች በካፍቴሪያ እንዲኖር የሚፈለግ አገልግሎት የዳሰሳ ጥናት ውጤት...................6
6. በጥናቱ የተገኘ መልካም ልምድና ተግደሮት......................................................................................................7
6.1. የተገኘው መልካም ልምድ....................................................................................................................7
6.1.1. መዝናኛ ክበቡን አከራይቶ በማሰራት..............................................................................................7
6.1.2. መዝናኛ ክበቡን በተቋሙ ባሉ ማህበራት (መረዳጃ ማህበር) በማሰራት...................................................8
6.2. ያጋጥሙ ተግዳሮቶች..........................................................................................................................8
6.2.1. መዝናኛ ክበቡን አከራይቶ በማሰራት..............................................................................................8
6.2.2. መዝናኛ ክበቡን በተቋሙ ባሉ ማህበራት በማሰራት............................................................................8
7. የኮሚቴው መነሻ የውሳኔ ሃሳብ.....................................................................................................................9
7.1. አማራጭ አንድ ማህበሩ አከራይቶ ቢጠቀምበት.........................................................................................9
7.1.1. የሚኖረው ጠቀሜታ...................................................................................................................9
7.1.2. የሚኖረው ተግዳሮት..................................................................................................................9
7.1.3. ትኩረት የሚሹ ጉዳዩች...............................................................................................................9
7.2. አማራጭ ሁለት በማህበሩ ራሱ ቢጠቀምበት..........................................................................................10
7.2.1. የሚኖረው ጠቀሜታ.................................................................................................................10
7.2.2. የሚኖረው ተግዳሮት.................................................................................................................10
7.2.3. ትኩረት የሚሹ ጉዳዩች.............................................................................................................10
8. አባሪ.......................................................................................................................................................1
ii | P a g e
1. መግቢያ
ንጋት ኮርፖሬት ምቹ የስራ አካባቢ ከመፍጠር አኳያ ሻይ ቡና በማቅረብ ሰራተኞቹን ተጠቃሚ እያደረገ
ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኮርፖሬቱ የተከራየው ህንጻ ይህን የሻይ ቡና እና ሌሎች አገልግሎቶችን ጨምሮ
ለሰራተኛው ለማቅረብ የመዝናኛ ክበቡ አመች በመሆኑ የተቋሙ ሰራተኞች በመወያየት አገልግሎቱን
በተጠናከረ ሁኔታ መስጠት የሚያስችል መነሻ ሃሳብ እንዲቀርብ ኮሚቴ መርጠዋል፡፡
ስለሆነም ኮሚቴው የተለያዩ ተቋማትን ልምድ፣ ከአሁን በፊት የነበረውን የንጋትን የሻይ ቡና መስተንግዶ
ሁኔታ፣ የንጋት ኮርፖሬት የሰራተኞች መረዳጃ ማህበር ሁኔታን በማጥናት የተሻለውን የውሳኔ ሃሳብ መነሻ
የሚሆን አዘጋጅቷል፡፡
2. አላማ
2.1. አጠቃላይ አላማ
የተቋሙን መዝናኛ ክበብ ምቹ በማድረግ፣ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ሰፋ ባለ እና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ
ለሰራተኛው ማቅረብ የሚቻልበትን አመራጭ የውሳኔ ሃሳብ መነሻ ማቅረብ፡፡
1|Page
4. በተቋሙ የለውን የሠራተኞች የመረዳጃ ማህበር አሁን ካለው በተሻለ የሰራተኛውን ማህበራዊ ትስስር የበለጠ
አጠናክሮ እንዲሰራ ማድረግ በማስፈለጉ፣
5. በንጋት የሚቀርበው የሻይ እና ቡና አገልግሎት በተደራጀ ካፍቴሪያ ሆኖ ለዚህ አገልግሎት የሚሰማሩ ሠራተኞች
በሌሎች የተቋሙ ስራ ላይ የበለጠ ተጠናክረው እንዲሰሩ ማድረግ ጥሩ አማራጭ በመሆኑ፤
4.2. ለሰራተኞች
1. የሚፈልጉትን አገልግሎት በቅርበት በተመጣጣኝ ዋጋ እና ጥራት ማግኘት ያስችለዋል፣
2. ትኩስ ምግብ መመገብ እና ጤናማ አምራች እንዲሆን ያደርገዋል፣
3. የስራ ሰዓት ሳያባክን ሙሉ የስራ ስዓቱን ስራ ላይ እንዲያሳልፍ ያደረገዋል፣
4. በሻይ ቡና፣ በምሳ ስዓት በከፌው በሚኖረው ቆይታ የሰራተኛውን ማህበራዊ ግንኙነት የበለጠ
እንዲያጠናከር ያደርገዋል፣
2|Page
5. በተቋሙ ግቢ ውስጥ የተሟላ የካፍቴሪያ አገልግሎት ለማስጀመር የሚያስችል
ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች የተገኘው ውጤት ወይም በእይታው የተገኘው መረጃ እንደሚከተለው ቀርቧል፤
ሲሆን አተገባበሩ ከዚህ በፊት ይፈጸምበት ከነበረው የተለየ በመሆኑ በባህር ዳር ከተማ ያሉ መሰል ተቋማት ላይ
ያለውን ተሞክሮ መውሰድ የግድ ሆኖአል፡፡ ተሞክሮ ለመውሰድ የሚያስችል ቼክሊስት በማዘጋጀት ከ 5
የእያንዳንዱን ተቋማት የካፍቴሪያ ግልጋሎት ተሞክሮ በስራ ቦታ ያለን ካፍቴሪያ ህንጻ እና ቁሳቁስ
የሚጠቀሙበት መንገድ፤ በካፍቴሪያው የሚያቀርቡ አገልግሎቶች፣ ተቋማቱ ለካፍቴሪያው የሚሰጡት
ድጋፍ በአጭር ተጠቃሎ ሲታይ በሚከተለው ሠንጠረዥ የቀረበ ሲሆን ዝርዝር ጉዳዮች ደግሞ በአባሪ
ተቀምጧል፡፡
ተ.ቁ ልምድ የተገኘባቸው መዝናኛ ክበብ ውን የሚጠቀሙበት የሚያቀርቧቸው አገልግሎቶች ተቋሙ ለመዝናኛ ክበብ ምርመራ
ተቋማት መንገድ የክትትልና ቁጥጥር ሁኔታ ው ያው የሚያደርገው
ድጋፍ
በተቋሙ በኪራይ በመረዳጃ/ ትኩስ ምግብ ለስላሳ በገንዘብ በአይነት
ሰራተኛ ነገሮች መጠጠች
ማህበር
1 አህስኮድ √ √ √ √ √ √ በጨረታ
2 አውስኮድ √ √ √ √ √ √ በጨረታ
3 አዲቁድ √ √ √ √ √ በጨረታ
4 አመልድ √ √ √ √ √ √ መረዳጃ
ማህበሩ
3|Page
5 አማራ ፓይፕ √ √ √ √ √ √ √ በጨረታ
መገጣጠሚያ
6 የአ/ብ/ክ/መ ት/ት ቢሮ √ √ √ √ √ √ በጨረታ
7 የአ/ብ/ክ/መ/ሲ/ሰ ቢሮ √ √ √ √ √ በጨረታ
8 የአ/ብ/ክ/መ/ዋ/ኦ/ ቢሮ √ √ √ √ √ መረዳጃ
ማህበሩ
ማብራሪያ፡- ከላይ በሰንጠረዡ በኪራይና በመረዳጃ ማህበሩ በሚል ምልክት የተደረገበት ሁኔታ ምንም
እንኳን መዝናኛ ክበቡን አከራይተው የሚጠቀሙበት ቢሆንም መረደጃ ማህበራቸውም ከኪራይ ገቢ
እና ከመከታተልና ከመቆጣጠር አኳያ ድርሻ ስላለው የተቀመጠ መሆኑ ይታወቅ፡፡
ከላይ በተቀመጠው ሰንጠረዥ መሰረት 6 ተቋማት መዝናኛ ክበቡን በማከራየት እና ገቢው ለሰራተኛ መረደጃ ማህበር
እንዲሆን፣ 2 ተቋማት ደግሞ ገቢውንም የማስተዳደር ስራውንም ሙሉ በሙሉ በሰራተኛ ማህበሩ/መረዳጃ ሆኖ
እንዲመራ አድርገዋል፡፡ ሁሉም ተቋማት መዝናኛ ክበብ ውን በማከራየት አገልግሎት እንዲሰጥ ቢያደርጉም ቋሚ
እቃዎችን (ፍሪጅ፣ ወንበር፣ጠረጴዛ፣ ሰቶቭ ወዘተ) እና መብራትና ውሃ በተቋማት የሚሸፈን መሆኑን አይተናል፡፡
ሰራተኛ/መረዳጃ ማህበር የሚያስተዳድሩት ተቋማት የፋይናንስና የንብረት ምንጫቸው ተቋማቱ ሲሆኑ አመልድ መነሻ
መንቀሳቀሻ ካፒታል እና አማራ ፓይፕ ደግሞ የምግብ ክፍያ እንደሚከፍል አይተናል፡፡ በአጠቃላይ ከተቋማቱ የተገኘው
ልምድ የመዝናኛ ክበብ ስራ በውስጥ አቅምም ተሰራ በውጭ አካላት በጣም ጠንካራ የማኔጅመንት ስራ የሚጠይቅ
መሆኑን ለመገንዘብ ተችሏል፡፡
ንጋት ኮርፖሬት የዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት ባለፉት አመታት ጀምሮ የሻይና ቡና መስተንግዶ በራሱ ወጭ
ለሰራተኞቹ እያቀረበ ያለ ሲሆን በዚህም ከአማራ ፓይፕ በመቀጠል ከሌሎች ተቋማት የተሻለ ልምድ ያለው
መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በዚህ የሰራተኛ ደመወዝን ሳይጨምር ለሻይ ቡና ብቻ ብር 67,729.86 በላይ በየአመቱ
ወጭ ያደርጋል፡፡
ስለሆነም አሁን ያለው የካፍቴሪያ ቦታ ሌሎች ተጨማሪ አገልግሎቶችን ለማቅረብ ምቹ በመሆኑ ቢያንስ
ለሻይና ቡና የሚያወጣው ወጭ እንደተጠበቀ ሆኖ ለዚሁ አገልግሎት የሚሰጡ ሰራተኞች በሌሎች ስራዎች
ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ ትኩረት እንዲያደርጉ አድርጎ እና የማስተዳደር ስራውን
ከተቋሙ ውጭ ማድረግ የተሻለ እንደሆነ ከሌሎች ተቋማት የተገኘው ልምድ ያሳያል፡፡ ኮሚቴውም ይህ
አማራጭ የተሻለ መሆኑን በጥናቱ ባገኘው ልምድና ተሞክሮ ለመገንዘብ ችለናል፡፡
በተቋሙ ውስጥ ለመዝናኛ ክበቡ አገልግሎት የሚሰጡ ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ የሻያና ቡና ሰኒ፣ ስቶቭ የመሳሰሉት
ንብረቶች ያሉት ሲሆን ተጨማሪ የሚያስፈልጉ ንብረቶች ማሟላት የሚጠበቅ ይሆናል፡፡
4|Page
5.3. የንጋት ኮርፖሬት የዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት የሰራተኞች መረዳጃ ማህበር ሁኔታ
የንጋት ኮርፖሬት የዘለቄታ በጎ አድራት ድርጅት የሰራተኞች መረዳጃ ማህበር 90 አባላት ያሉት ሲሆን
ከእያንዳንዱ ሰራተኛ ብር 30 ወርሃዊ መዋጮ በአመት ብር 32,400 በመሰብሰብ ለሰራተኛውም በሃዘን፣
በደስታ (ለጋብቻ፣ ወላድ መጠየቅ፣ ምረቃ፣ ሽኝት) ፣ በችግር (ጡረታ ሲወጣ፣ ከፍተኛ ህመም/አዳጋ
ሲያጋጥም፣ ከስራ ሲታገድ) በመተደዳደሪያ ደንቡ በተቀመጡ የዝምድና ሐረጋትና አሰራር መሰረት ድጋፍ
ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህ ፕሮፖዛል በሚሰራበት ወቅት ከወጭ ቀሪ ብር 107,000 አለው፡፡
ሆኖም ማህበሩ ከዚህ ቀደም ከሚሰጠው አገልግሎት በተጠናከረ ሁኔታ ስራውን እንዲሰራ እና የሰራተኛውን
ማህበራዊ ትስስር የበለጠ ለማጠናከር የአባላት መዋጮ ከማሻሻል ጀምሮ ተጨመሪ ገቢ የሚያገኝባቸውን
አማራጮችን ማየት ተገቢ ነው፡፡ ከዚህም አንዱ የተቋሙን የመዝናኛ ክበብ አገልግሎት በበላይነት
በማስተዳደር ገቢ እንዲያገኝ ማድረግ አንዱ ነው፡፡
5.4. የንጋት ኮርፖሬት ማዕከል የሰራተኞች በካፍቴሪያ እንዲኖር የሚፈለግ አገልግሎት የዳሰሳ
ጥናት ውጤት
ኮርፖሬቱ በማዕከሉ ጠቅላላ 90 የስራ መሪዎችና ሰራተኞች ያሉት ሲሆን በተለያዩ የስራ ምክኒያቶች ከስራ ቦታ
የለሉትን ሳይጨምር ለ 54 ሰራተኞች መጠይቁ ተበትኖ በመዝናኛ ክበብ አጠቃቀም ዙሪያ ያላቸውን ፍላጎት ለማዎቅ
ዳሰሳ ጥናት ተደርጓል፡፡ መጠይቁ ከተበተነላቸው ውስጥ ወንድ 28 ሴት 17 በድምሩ 45 ሰራተኞች ማለትም 83 በመቶ
መጠይቁን ሞልቶ መልሰዋል፡፡
በኮርፖሬቱ ውስጥ ከሚሰሩ እና መጠይቁን ከሞሉት ሰራተኞች ውስጥ በተቋሙ የደመወዝ እርከን እና በኮሚቴው
በወጣው ደረጃ መሰረት 24 በመቶ የሚሆኑት ከ 2000 እስከ 5000፣ 13 በመቶ ከ 5001 እስከ 8000፣ 52 በመቶ
ከ 8001 እስከ 15000 እና 11 በመቶ ደግሞ ከ 15000 በላይ ናቸው፡፡
መጠይቁ ከሞሉት ውስጥ 97 በመቶ በመዝናኛ ክበብ ው የሚሰጡ አገልግሎቶችን የመጠቀም ፍላጎት ያላቸው
መሆኑን የገለጹ ሲሆን 3 በመቶው ደግሞ ፍላጎት የሌላቸው መሆኑን ገልጻዋል፡፡
5|Page
በመዝናኛ ክበቡ እስካሁን ይቀርቡ ከነበሩ ትኩስ መጠጦች በተጨማሪ በትእዛዝ የሚዘጋጁ እና ለብልሽት
የማይዳረጉ ቁርሳና ምሳ አቅርቦቶች እንዲሁም ለስላሳ መጠጦች እንዲቀርቡ ሁሉ ሰራተኛ ይፈልጋል፡፡
6|Page
4. ማህበራቱ/ኮሚቴው በቁርጠኛነትና በሃላፊነት ስሜት ከሰራ የተሻለ ትርፍ የሚያስገኝ መሆኑ፣
7|Page
3. በየወቅቱ ባለው የገበያ መናር ምክንያት የዋጋ ይሻሻልልኝ ጥያቄዎች ከተከራዩ መነሳት፣
የሚያስችል መሆኑ፣
8|Page
5. የፋይናንስና ሃብት ብክነት ሊያጋጥም የሚችል መሆኑ፣
6. በየወቅቱ የሚያጋጥመው የገበያ አለመረጋጋትና መናር፣
መዝናኛ ክበቡ በሁለቱም አማራጮች አገልግሎት ቢሰጥ ሰራተኛውን ለማበረታታት፣ እርካታውን ለመጨር እና
በመዝናኛ ክበቡ የተሸለ ተጠቃሚ መሆን እንዲችል ተቋሙ ከሻይ ቡና በተጨማሪ የምግብ ድጎማ የሚያደረግት ሁኔታ
ቢኖር መልካም ነው፡፡
የኮሚቴው ውሳኔ
በአጠቃላይ ከላይ በተቀመጡት አማራጫ የውሳኔ ሃሳብ መነሻዎች መሰረት እና ከተለያዩ ተቋመት ከተገኘው ልምድ
አኳያ የሰራተኛ መዝናኛ ክበቡን መረዳጃ ማህበሩ የሚከታተለውና የሚቆጣጠረው ሆኖ ለውጭ ተከራዮች በጨረታ
አወዳድሮ አገልግሎት እንዲሰጥ ቢደረግ እና የክራዩ ገቢው ለማህበሩ እንዲሆን በሚል ኮሚቴው የውሳኔ ሃሳብ መነሻውን
ያቀርባል፡፡
9|Page
8. አባሪ
ተሞክሮ የተወሰደባቸው ተቋማት ዝርዝር መረጃ
1|Page
በጨረታ ወቅት የሚቀርቡ አገልግሎቶችን መነሻ ዋጋ በድርጅቱ ቀርቦላቸው ከመነሻ ዋጋው በታች
መሙላት አይቻልም ምክኒያቱ ተጫራቹ በብዛት ተጠቃሚ የሌላቸውን አቅርቦቶች ሞልቶ አሸናፊ
እንዳይሆንና ስራ እንዳይበደል በማሰብ፣
አብዛኛው ሰራተኛው በመዝናኛ ክበብ ው የመጠቀም ልምዱ የተሻለ ነው፡፡
በተቋሙ ያሚኖሩ ማንኛውንም ዝግጅቶች አቅርቦት ያቀርባሉ፡፡ የክፍያ ሁኔታ ለተቋማት ሃላፊዎች ከሆነ
በየወሩ ለሰራተኞች ደግሞ በየቀኑ ገንዘቡ ይሰበሰባል፡፡
የመዝናኛ ክበብ ው የክራይ ዋጋ ብር 1000 ነው፡፡
4. አመልድ
ይህ ተቋማ መዝናኛ ክበብ ን የሚጠቀምበት ሁኔታ በመረዳጃ ማህበሩ ሲሆን የሚሰጠውን አገልግሎት
በመከታተልና በቆጣጠር እንዲሁም ሰራኞችን በቅጠር እን አቅርቦቶችን በማቅረብ የመረዳጃ ማህበሩ
የሚመለከት ነው፡፡
መዝናኛ ክበብ ው የሚመሩ ሰራተኞች ቋሚ ተቀጣሪ ያለውና የራሱ አደራጀጀት አለው፡፡ የሰው ሃይልም
ስራ አስኪያጅ፣ ሸፍ፣ ረዳት ሸፍ፣ ካሸር፣ 2 አስተናጋጅ እና የጀበና ቡና ሰራተኛ አላቸው፡፡ ለሰራተኞችም
ከብር 1200 እሰከ ብር 3500 ድረስ ይከፍላሉ፡፡
መዝናኛ ክበብ ውን የሚሰራበት እቃዎች በሙሉ፣ የካፍተሪ እድሳት ወጭ እና መነሻ ካፒታል በድጋፍ
መልክ ከድርጅት የተበረከተላቸው ሲሆን በአጠቃላይ ከብር 600000 በላይ ወጭ ተደርጎላቸዋል፡፡
የመብራትና የውሃ ወጭ ይሸፈንላቸዋል፡፡
ለሰራተኛው የሚቀርቡ አገልግሎቶችን ዋጋ ተመን ጥናት በማድግ በማህበሩ በኩል ተቀምጧል፡፡ ለውጭና
ለውስጥ ሰራተኛም መተለያየ ዋጋ ተቀምጧል፡፡
ከ 300 በላይ ሰራተኛ ያለ ሲሆን አብዛኛው ሻይ ቡና፣ 50% የሚሆነው ምግብ በመዝናኛ ክበብ ው
የመጠቀም ልምዱ አለው ነው፡፡ የውጭ ደንበኛም ይጠቀማል፡፡
በተቋሙ ያሚኖሩ ማንኛውንም ዝግጅቶች አቅርቦት ያቀርባሉ፡፡ የክፍያ ሁኔታ ለተቋማት ሃላፊዎች ከሆነ
በየወሩ ለሰራተኞች ደግሞ በየቀኑ ገንዘቡ ይሰበሰባል፡፡
ካፌውን የማስተዳደርና የመምራት ጉዳይ በጣም አስቸጋሪና ከተጨማሪ ስራ ጋር የሚሄድ ባለመሆኑ
በቀጣይ ሌላ አማራጭ ሊያሱቡ እንደሚችሉ ተረድተናል፡፡
5. አማራ ፓይፕ
1. ይህ ተቋማ መዝናኛ ክበብ ን የሚጠቀምበት ሁኔታ ለውጭ አካላት አከራይቶ ሲሆን የሚሰጠውን
አገልግሎት በመከታተልና በቆጣጠር የሰራተኛ ማህበሩ የሚመለከት ነው፡፡
2. መዝናኛ ክበብ ውን የሚሰራበት ድርጅት ጨረታ እንዲገባ የተደረገ ሲሆን ከተቋሙም ቋሚ እቃዎች
ማለትም ፍሪጅ፣ የሻይ ማሽን፣ ወንበር ጠረጴዛ፣ በተቋሙ የነበሩ የመስተንግዶ እቃዎች በሙሉ
እንዲሁም የመብራትና የውሃ ወጭ ተሸፍኖለቸዋል፡፡
3. በጨረታ ወቅት በቀረበው የምግብ ዝርዝር መሰረት በአጠቃላይ ዋጋ ዝቅተኛ ያቀረቡ ተጫራቾች
እንዲያሸንፉ ተደርጓል፡፡ የሚያቀርቧቸውን የምግብ ዝርዝር የተመረጡና የተወሰኑ ናቸው፡፡
2|Page
4. አብዛኛው ሰራተኛው በመዝናኛ ክበብ ው የመጠቀም ልምዱ የተሻለ ነው፡፡ ምክንያም ሰራተኛው 600
ብር የምግብ አበል ያለው በመሆኑ ነው፡፡ በቀጣያም 75% በተቋሙ 25% በሰራተኛው ተሸፍኖ
ተጠቃሚ እንዲሆን ውሳኔ ላይ የተደረሰ እና ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ነው፡፡
5. በተቋሙ ያሚኖሩ ማንኛውንም ዝግጅቶች አቅርቦት ያቀርባሉ፡፡ የክፍያ ሁኔታ ለተቋማት ሃላፊዎች
ከሆነ በየወሩ ለሰራተኞች ደግሞ በየቀኑ ገንዘቡ ይሰበሰባል፡፡
6. የመዝናኛ ክበብ ው የክራይ ዋጋ በነፃ ነው፡፡
6. ኦዲት ቢሮ
ይህ ተቋም መዝናኛ ክበብ ን የሚጠቀምበት ሁኔታ በመረዳጃ ማህበሩ ሲሆን የሚሰጠውን አገልግሎት
በመከታተልና በቆጣጠር እንዲሁም ሰራተኞችን በቅጠር እን አቅርቦቶችን በማቅረብ የመረዳጃ ማህበሩ
የሚመለከት ነው፡፡
መዝናኛ ክበብ ው የሚመሩ ሰራተኞች ማህበሩ የሚመርጣቸው ኮሚቴዎች ሲሆኑ የተቋሙ ቋሚ
ተቀጣሪ ናቸው፡፡ ለካፌው ስራተኛ 2 የሰው ሃይል አንድ ምግብ አዘጋጅ እና አንድ አስተናጋጅ ቀጥረው
ያሰራሉ፡፡ ለሰራተኞችም ደመወዝ ለእያንዳንዳቸው ብር 1500 ይከፍላሉ፡፡
መዝናኛ ክበብ ውን የሚሰራበት እቃዎች በሙሉ፣ የተቋሙ ሲሆን የመብራትና የውሃ ወጭ
ይሸፈንላቸዋል፡፡
ለሰራተኛው የሚቀርቡ አገልግሎቶችን ዋጋ ተመን ጥናት በማድግ በማህበሩ በኩል ተቀምጧል፡፡
ሰራተኛ በመዝናኛ ክበብ ው የመጠቀም ልምዱ ዝቅተኛ ነው፡፡ የውጭ ደንበኛ የለውም፡፡
በተቋሙ የሚኖሩ ማንኛውንም ዝግጅቶች አቅርቦት ያቀርባሉ፡፡ የክፍያ ሁኔታ ለተቋማት ሃላፊዎች ከሆነ
በየወሩ ለሰራተኞች ደግሞ በየቀኑ ገንዘቡ ይሰበሰባል፡፡
ካፌውን የማስተዳደርና የመምራት ጉዳይ በጣም አስቸጋሪና ከተጨማሪ ስራ ጋር የሚሄድ ባለመሆኑ
በቀጣይ ሌላ አማራጭ ሊያሱቡ እንደሚችሉ ተረድተናል፡፡
7. ት/ት ቢሮ
መዝናኛ ክበብ ውን በጨረታ ለውጭ ባለሀብት አከራይተው የሚጠቀሙ ሲሆን ገቢው ለተቋሙ
የመረዳጃ ማህበር የሚውል ነው፡፡
ተከራዩ ምግብ የሚሸጥበት ዋጋ የተጋነነ እና ከተማ ላይ በውድ ቤት ተከራይቶ የሚሰራ የሚመስል ነው፡፡
የውጭ ተጠቃሚም ገብቶ ከካፌው ይጠቀማል፡፡
8. ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ
ካፌውን በጨረታ ለነጋዴ አከራይተው እየተጠቀሙ ይገኛሉ፣
የኪራዩ መጠንም ብር 4400 ነው፣
የኪራዩ ገንዘብ ለመረዳጃ ማህበሩ ማጠናከሪያነት ይውላል፣
3|Page
ወምበር፣ ጠረጴዛ ፍሪጅ እና መሰል ቁሳቁሶች የተቋሙ ሲሆኑ የጎደሉትን ቁሳቁሶች ተከራዩ አሟልቶ
ይጠቀማል፣
መዝናኛ ክበብ ው በተቋሙ ወይም በተቋሙ ባሉ ማህበራት (በሰራተኛ ማህበር/መረዳጃ ማህበር) የሚሰራ ከሆነ
አጠቃላይ አደረጃጀቱ እና የአሰራር ስርዓቱ ምን ይመስላል
4|Page
5. መዝናኛ ክበብ ው በተቋሙ ባሉ ማህበራት (በሰራተኛ ማህበር/መረዳጃ ማህበር) የሚሰራ ከሆነ ስራ ለማስጀመር
የሚያስችል የበጀት ምንጭ እንዴት እና ከማን ተሟላ
6. መዝናኛ ክበብ ውን ተከራይቶ የሚሰራ ከሆነ ድርጅቱ ስንት ተከራየው እንዲከራዩ የተጋበዛሁበት ሁኔታ፣ የውሃና
የመብራት አጠቃቀም ሁኔታ፣
7. ተከራይተዉ የሚሰሩ ድርጅቶች ከአከራዩ ድርጅት የሚያገኙት ወይም የሚሟላላቸዉ ቅድመ ሁኔታ ካለ ቢዘረዘር
8. አከራዩ ተቋም ከተከራዩ ድርጅት እንዲሟሉለት የሚፈልጋቸው ቅድመ ሁኔታዎች ካሉ ቢዘረዘሩ
9. መዝናኛ ክበብ ው ተከራይቶ ከሆነ የሚሰራው የሚያቀርቡት አገልግሎቶች በምን እና እንዴት ባለ ሁኔታ ነው
9.1. ድርጅቱ በሚፈልገዉ አጠቃቀም መነሻ በማድረግ
9.2. በተከራይታዉ እና በድርጅቱ ስምምነት መነሻ በማድረግ
9.3. በተከራይታዉ በሚያቀርበዉ አጠቃቀም መነሻ በማድረግ
9.4. የተጣሉ ግዴታዎችስ አሉ ወይ
10. በመዝናኛ ክበብ የሚቀርቡ የምግብ፣ የመጠጥና ትኩስ ነገሮች ምን ምን ናቸዉ ለማን ለማን ይቀርባሉ ዋጋቸዉ
ቢገለፅ
11. በመዝናኛ ክበቡ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ሰራተኛው የመጠቀም ባህሉ እንዴት ነው ? ምን ያህል የድርጅቱ
ሰራተኞች በመዝናኛ ክበብ ዉ በአማካይ ይጠቀማሉ
12. ከድርጅቱ ሰራተኞች ዉጭ የሚጠቀሙ ካሉ በአማካይ ምን ያህል ይሆናሉ
13. የድርጅቱ ሰራተኞች ከመዝናኛ ክበቡን ሲጠቀሙ የአከፋፈል ሁኔታ እንዴት ነዉ
13.1. በየቀኑ በተጠቀሙት መጠን
13.2. በየሳምንቱ የተጠቀሙትን በመደመር
13.3. በወር የተጠቀሙትን በመደመር
13.4. ሌላ ካለ ይገለፅ
14. ለመዝናኛ ክበብ አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶችን የአቅርቦት ሁኔታ (ከማን፣ እንዴት፣ በምን ያህል ጊዜ ወዘተ) ምን
ይመስላል?
15. የመዝናኛ ክበብ ው የፋይናንስ፣ የንብረትና የሰው ሃይል አስተዳደሩ ምን ይመስላል?
16. በተቋማችሁ ለሰራተኛው የመዝናኛ ክበብ አገልግሎት በመኖሩ ለሰራተኛውና ለተቋሙ ያለውን ጠቀሜታ እንዴት
ታዩታላችሁ?
17. በተቋማችሁ የመዝናኛ ክበብ አገልግሎት ስትሰጡ ያጋጠማችሁ ተግዳሮት ካለ ቢገለጽልን
18. በአጠቃላይ የመዝናኛ ክበብ አገልግሎት ላይ የምትሰጡን አስተያየት ካለ?
እናመሰግናለን!
5|Page
ንጋት ኮርፖሬት ምቹ የስራ አካባቢ ከመፍጠር አኳያ ሻይ ቡና በማቅረብ ሰራተኞቹን ተጠቃሚ እያደረገ
ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኮርፖሬቱ የተከራየው ህንጻ ይህን የሻይ ቡና እና ሌሎች አገልግሎቶችን ጨምሮ
ለሰራተኛው ለማቅረብ የመዝናኛ ክበቡን አመች በመሆነ መልኩ መጠቀም እንዲቻል የተቋሙ ሰራተኞች
ፍላጎት ማሰባሰብ አስፈልጓል፡፡
ስለሆነም እርሰዎ በመዝናኛ ክበቡን አገልግሎት ዙሪያ የሚኖረዎትን ሃሳብ ማወቅ በማስፈለጉ መጠይቁን
ጊዜዎትን ሰጥተው በአግባቡ እንዲሞሉልን በአክብሮት እየጠየቅን በቅድሚያ እናመሰግናልን፡፡
1. የመረጃ አሞላል
ስም መጻፍ አያስፈልግም፣
2. መሰረታዊ መረጃ
1. ጾታ ወንድ ሴት
2. የደመወዝ መጠን ከ -------- እስከ ------------ ከ ----------- እስከ -------- ከ ----------- እስከ
------------ ከ ----------- እስከ ------------ ከ ---------እስከ ------------
3. በመዝናኛ ክበብ ው የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለመጠቀም ፍላጎት አለዎት
አወ የለኝም
እናመሰግናለን!
6|Page