You are on page 1of 7

Access beyond Limits!

ድጋፍ አነስተኛ ብድር አቅራቢ አክሲዮን ማኅበር የሚስጣቸው አገልግሎቶች የዋጋ ዝረዝር እና
የአከፋፍል ሁኔታ
መግቢያ

ድጋፍ አመስተኛ ብድር አቅራቢ በሁሉም ደረጃ ለሚገኙ የሀገራችን የኅብረተሰብ ክፍሎች የፋይናንስ

አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ በማለም የተመሰረተ እና በዘርፉ ከአስር ዓመታት በላይን ያስቆጠረ ተቋም

ነው፡፡ ድጋፍ አነስተኛ የብድር አቅራቢ አክሲዮን ማኅበር በአሁን ወቅት ለግለሰቦች እና ለአነስተኛ

ኢንተርፕራይዝ ደንበኞቹ አዳዲስ ፈጠራዎችን እና ቀልጣፋ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በመጠቀም የአጭር እና

የመካከለኛ ጊዜ ከገንዘብ ጋር የተያያዙ መፍትሔዎች እና ድጋፎችን በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም ድጋፍ

አነስተኛ ብድር አቅራቢ የፋይናንስ አገልግሎት ኢንዱስትሪውን ቀጣይነት ባለው እና ሁሉን አቀፍ በሆነ ደረጃ

ወደፊት ለማሻግር ራዕይ አድርጎ ራሱን በማስፋፋት በተለያዩ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ እንቅስቃሴ
የሚያደርግ አክሲዮን ማኅበር ነው፡፡

በመሆኑም አክሲዮን ማኅበሩ በገንዘብ ብቻ ሳይሆን በአይነት የሚመደቡ አገልግሎቶችን ከተለያዩ ድረጅቶች ጋር

በመተባበር ለግሰቦችም ሆነ ለአነስተኛ ተቋማት ያለምንም መስተጓጎል በምቹ መንገዶች ተደራሽ እንዲሆኑ

ሌት ተቀን ይተጋል፡፡ ይህም ከጊዜ ወደ ጊዜ ተመራጭ የፋይናንስ አገልግሎት ተቋም እንዲሆን አስችሎታል፡፡

በዚህም መሠረት ድጋፍ አነስተኛ ብድር አቅራቢ አክሲዮን ማኅበር የሚሰጣቸው አቅርቦቶች እና አገልግሎቶች

የሚከተሉትን ይመስላሉ፡፡

ዋና ዋና አቅርቦቶች እና አገልግሎቶች

ደሞዝ አስቸኮይ (pay day)

ይህ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ወርሃዊ ደሞዛቸው ከመድርሱ በፊት የሚያጋጥሟቸውን አስቸኳይ የሆኑ


ወጪዎች ለመሽፍን የሚያግዛቸው የብድር አገልግሎት ሲሆን መጠኑም የተበዳሪውን የወር ደሞዝ 1/3 ኛ
የሚይዝ ነው፡፡

ገፅ |1 https://digafmfi.et/
Access beyond Limits!

 የአከፋፍል ሁኔታ

አገልግሎት ተጠቃሚው የብድር አከፋፈሉን የሚያከናውነው ብድሩን በወሰደበት ወቅት ከሚያገኘው ደሞዝ
ሲሆን መበደር የሚችለው ከፍተኛ መጠን 10000 ብር ይሆናል፡፡ ይህ የብድር አገልግሎት ከወለድ ነፃ ነው፡፡

 የአገልግሎት ክፍያን በተመለከተ

ከላይ የተመለከተውን አገልግሎት ለማግኘት የሚፈፀመው ክፍያ እንደሚከተለው ይሆናል፡፡

o ከ 500-1000 ለሚደርስ ብድር - 75 ብር የአገልግሎት ክፍያ

o ከ 1001-2500 ለሚደርስ ብድር - 200 ብር የአገልግሎት ክፍያ

o ከ 2501-5000 ለሚደርስ ብድር - 300 ብር የአገልግሎት ክፍያ

o ከ 5001-10000 ለሚደርስ ብድር - 575 ብር የአገልግሎት ክፍያ ናቸው፡፡

 አገልግሎቱን ለማግኘት መሟላት የሚኖርባቸው ቅድመ ሁኔታዎች

ሀ. ለፋይናስ ተቋማት እና የመንግስት መ/ቤቶች ስራተኞች

1. የመስሪያ ቤቱ ወይም የተቋሙ መታወቂያ


2. አንድ ጉርድ ፎቶ
3. የሶሰት ወር የቅረብ ጊዜ ተከታታይ ደሞዝን የሚያሳይ ባንክ መግለጫ (ይህ ቅድመ ሁኔታ ድጋፍ
አነስተኛ ብድር አቅራቢ አክሲዮን ማኅበር ውል የገባቸውን ተቋማት ስራተኞችን የማይመለከት
ይሆናል)

ለ. ከ”ሀ“ ስር ከተጠቀሱት ውጪ ላሉ ስራተኞች (ለምሳሌ፡ መንግስታዊ ላልሆኑ መስርያ ቤት ሰራተኞች)

1. የታደስ መታወቂያ
2. አንድ ጉርድ ፎቶ
3. ቋሚ ስራተኛ ስለመሆናቸው እና የደሞዝ መጠንን የሚገልጽ ደብዳቤ
4. የሶሰት ወር የቅረብ ጊዜ ተከታታይ ደሞዝን የሚያሳይ ባንክ መግለጫ

ምሳሌ፡-

ገፅ |2 https://digafmfi.et/
Access beyond Limits!

“ሀሁ” የተባለ ተበዳሪ ደሞዙ 6000 ብር ቢሆን መበደር የሚቻለው የደሞዙን 1/3 ኛ ማለትም 6000/3 = 2000
ብር ይሆናል፡፡ በዚህም መሠረት ሰኔ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ብድሩን ቢወስድ እና የሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ደሞዝ ሰኔ
27 ቀን 2015 ዓ.ም የሚወጣ ቢሆን ከደምወዙ 2200 ብር ማለትም 2000 ብር በዋና ክፍያነት 200 ብር ደግሞ
በአግልግሎት ክፍያነት ወደ ድጋፍ የባንክ አካውንት ገቢ ወይም ተቆራጭ ይደረጋል፡፡

 የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን የሚያስችሉ አማራጮች

የደሞዝ አስቸኳይን የብድር አገልግሎት ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች መጠቀም ይቻላል፡፡

1. ወደ 6575 መደወል

ማንኛውም አገልግሎቱን መጠቀም የሚፈልግ እና ቅድመ-ሁኔታዎችን ማሟላት የሚችል ግለሰብ ወደ 6575


በመደወል እና ከድጋፍ ጥሪ ማዕከል ስራተኞች ጋር በመገናኘት የስራ ቦታ፣ ስም፣ የደሞዝ መጠን እና ሌሎች
አስፈላጊ መረጃዎችን በመስጠት ምዝገባ ካደረገ በኋላ የመረጠው የአስቸኳይ ብድር መጠን ወደ ባንክ ሂሳቡ
ቁጥሩ ገቢ እንዲሆን ማድርግ ይቻላል፡፡

2. በበይነ መረብ በማመልከት

ማንኛውም አገልግሎቱን መጠቀም የሚፈልግ እና ቅድመ-ሁኔታዎችን ማሟላት የሚችል ግለሰብ


“https://digafmfi.et/ “ በሚል የበይነ መረብ አድራሻ በመግባት እና የሚጠየቀውን ሙሉ መረጃ በሟሟላት
ምዝገባ ካደረገ በኋላ “pay day” የሚለውን አማራጭ በመጫን ቀጣይ መጠይቆችን በመምላት እና
በማጠናቀቅ ”apply” የሚለውን ተጭኖ ለአገልግሎቱ ማመልከት ይችላል፡፡

ማስታወሻ ፡- በማመልክት ሂደት ውስጥ ችግር በሚያጋጥምበት ወቅት ዕርዳታ ለመጠየቅ ወደ 6575 በመደወል
መፍትሔ ማግኘት ይቻላል፡፡

ደሞዝ ጥሪት(Salary Advance)

ይህ አገልግሎት አንድ ደሞዝተኛ የብድር ተጠቃሚ የአንድ ወር ደሞዙን አምስት እጥፍ ወይም የአምስት ወር
ደሞዙን በአንዴ መበደር የሚያስችለው ነው፡፡ በዚህም መሠረት ትልቁ የብድር መጠንም 150,000 ብር ነው፡፡
በመሆኑም የአገልግሎቱን መስፈርት የሚያሟላ ማንኛውም ስራተኛ ለተለያዩ ጉዳዮች ወይም ዓላማ
የሚያውለውን ጠርቀም ያለ ገንዘብ በብድር መልክ በዚህ አማራጭ ማግኘት ነው፡፡

ገፅ |3 https://digafmfi.et/
Access beyond Limits!

 የአከፋፍል ሁኔታ

አንድ ተበዳሪ የአንድ ወር ደሞዙን ቢወስድ በሶሰት ወር፤ የሁለት ወር ደሞዙን ቢወስድ በስድሰት ወር እና
የአምሰት ወር ደሞዙን ቢወስድ በአስራአምሰት ወራት ክፍሎ ማጠናቅቅ ይኖርበታል፡፡

ምሳሌ፡-

አቶ “ሀሁ” ደሞዛቸው አምሰት ሺ ብር ቢሆንና የሶሰት ወር ደሞዛቸውን ያህል መጠን ያለው የ 15000 ብር
ብድር ቢፈልጉ ከሚበደሩት ብር ላይ የአገልግሎት ክፍያ 5% እና የሕይወት ዋሰትና ክፍያ 1.5% ተቀናሽ ተድርጎ
በሂሳብ ቁጥራቸው ገቢ እንዲሆን ይደረጋል፡፡ በዚህም መሠረት ከ 15000 ብር ብድር ላይ

5%*15000 =750 ብር

1.5%*15000 = 225 ብር

750 ብር+ 225 ብር= 975 ብር ተቀናሽ ሆኖ 14,025 ብር ወደ ሀሁ የባንክ ሂሳብ ቁጥር ገቢ ይሆናል:: አቶ
“ሀሁ” ብድሩን ከወስዱ በኋላ በየወሩ በተቀናሽ ወለድ አስራር /Declining balance method/ ከዋናው
ብድር ጋር የተደመረ 15,985.32 ብር ለዘጠኝ ተከታታይ ወራት (15,985.32 /9 ወራት=1776.15 ብር በየወሩ)
በመክፈል ያጠናቅቃሉ፡፡1

ድጋፍ ዱቤ

ድጋፍ ዱቤ የብድር አገልግሎት ደንበኞች ከተለያዩ ሱቆች እና ድርጅቶች በዱቤ አገልግሎት የወደዱትን እና
የመረጡትን መሸመት የሚያስችላቸው የብድር አስራር ነው፡፡ በአሁን ወቅት ከድጋፍ አነስተኛ ብድር አቅራቢ
አክሲዮን ማኅበር ጋር ‘’የድጋፍ ዱቤ ‘’ የብድር አገልግሎትን ለማቅረብ በትብብር የሚሰሩ ጥቂት ሱቆች እና
ድርጅቶች የሚገኙ ሲሆን እንደአስፈላጊነቱ እና እንደ ደንበኞች ፍላጎት ቁጥራቸው የሚጨምር ይሆናል፡፡

 “ዱቤ እቃ” የዱቤ አገልግሎት (buy know pay later)

“ዱቤ እቃ” የዱቤ አገልግሎት አንድ ደንበኛ ከታች የተጠቀሱትን አገልግሎቶች መጠቀም በሚፈልጉብት
ወቅት በድጋፍ አነስተኛ ብድር አቅራቢ አ.ማ አማካኝነት በቀላሉ ዱቤ ማግኛት የሚችልበት አማራጭ ነው፡፡

እነዚህ አገልግሎቶች
1
ተበዳሪ ደምበኞች ጠቅላላ ወለዱን እንደዚሁም በየወሩ የሚከፈለውን የክፍያ መጠን በይነመረብ ላይ “calculatornet” ብለው

በመግባት ማረጋገጥ ይችላሉ፡፡

ገፅ |4 https://digafmfi.et/
Access beyond Limits!

o የሱፍ ልብስ

o አስቤዛ

o የጤና መድኅን

o የትምህርት ቤት ክፍያ

o ሞባይል ቀፎ ናቸው፡፡

1. ዱቤ ሱፍ ልብስ (Garment)

ድጋፍ አነስተኛ ብድር አቅራቤ ይህንን አገልግሎት ለደንበኞቹ ለማቅረብ ከ አምስት የልብስ ስፌት ድርጅቶች
ጋር በትብብር ይሰራል፡፡

1.1 . አማዞን ሱፍ

የሁሉም የሱፍ ልብስ ወጥ የሆነ የ 6500 ብር ዋጋ ያለው ሲሆን ሁሉም አይነት የወለድ፣ የአገለልግሎት እና
የሕይወት መድኅን ክፍያዎች አማዞን ሱፍ በሚያደርገው ልዩ ቅናሽ /discount/ የሚሸፈን በመሆኑ ደንበኛው
መክፍል የሚጠበቅበት የተጠቀስውን ዋጋ ብቻ ይሆናል፡፡

 የአከፋፈል ሁኔታ

አንድ አግልግሎቱን ለማግኘት ፍላጎት ያለው ደንበኛ ከሚከፈለው የደሞዝ መጠን ላይ በሚሰራበት ድርጅት
ፋይናንስ በኩል ተቆራጭ ተደርጎ ለድጋፍ አነስተኛ ብድር አቅራቢ አ.ማ በባንክ ቋሚ ክፍያ ትዕዛዝ /standing
instraction/ ገቢ ይሆናል፡፡

ምሳሌ፡-

አቶ “ሀሁ” የተባለ ደንበኛ ከአማዞን ሱፍ በ 6500 ብር ሙሉ የሱፍ ልብስ ቢወስድ በስድሰት ወር ውስጥ
እዳውን ከፍሎ ማጠናቀቅ ይጠበቅበታል፡፡

ይህም “6500/6 = 1083 ብር” ለስድሰት ተከታታይ ወራት በየወሩ ከደሞዙ ተቆራጭ ተድርጎ በባንክ ቋሚ
ክፍያ ይከፍላል እንደማለት ነው፡፡

በተጨማሪም ድሞዛቸው አነስተኛ የሆነ ስራተኞች ይህንኑ ሙሉ የሱፍ ልብስ ዋጋ ለ 12 ወራት ማለትም
6500/12 = 541.67 ብር ብቻ ተቆራጭ አድረገው ክፍያቸውን ማጠናቀቅ ይችላሉ፡፡

ገፅ |5 https://digafmfi.et/
Access beyond Limits!

ሀ. አማዞን ጫማ

ይህ አገልግሎት ደንበኛው የሙሉ ሱፍ አገልግሎቱን ከነጫማው በሙሉ ጥቅል ማግኘት የሚያስችለውን


አማራጭ ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ በመሆኑም ደንበኛው ከወለድ፣ ከአገልግሎት እና ከሕይወት መድኅን
ተጨማሪ ክፍያዎች ነፃ የሆነ የ 2500 ብር የብድር አገልግሎት ማግኘት የሚችል ይሆናል፡፡

 የአከፋፈል ሁኔታ

አንድ አግልግሎቱን ለማግኘት ፍላጎት ያለው ደንበኛ ከሚከፈለው የደሞዝ መጠን ላይ በሚሰራበት ድርጅት

ፋይናንስ በኩል ተቆራጭ ተደርጎ ለድጋፍ አነስተኛ ብድር አቅራቢ አ.ማ በባንክ ቋሚ ክፍያ ትዕዛዝ /standing

instraction/ ገቢ ይሆናል፡፡

ምሳሌ፡-

አቶ “ሀሁ” የተባለ ደንበኛ ከአማዞን ሱፍ በ 2500 ብር ጫማ ቢወስድ በስድሰት ወር ውስጥ እዳውን ከፍሎ
ማጠናቀቅ ይጠበቅበታል፡፡

ይህም “2500/6 = 416.67 ብር” ለስድሰት ተከታታይ ወራት በየወሩ ከደሞዙ ተቆራጭ ተድርጎ በባንክ ቋሚ
ክፍያ ይከፍላል እንደማለት ነው፡፡

በተጨማሪም ድሞዛቸው አነስተኛ የሆነ ስራተኞች ይህንኑ ሙሉ የሱፍ ልብስ ዋጋ ለ 12 ወራት ማለትም
2500/12 = 208 ብር ብቻ ተቆራጭ አድረገው ክፍያቸውን ማጠናቀቅ ይችላሉ፡፡

ለ. አማዞን ሽሚዝ

ይህ የአማዞን ሙሉ ልብስ ጥቅል ከሚይዛቸው አገልግሎቶች መካከል አንዱ ሲሆን ደንበኛው ከወለድ፣
ከአገልግሎት እና ከሕይወት መድኅን ተጨማሪ ክፍያዎች ነፃ የሆነ የ 1300 ብር የብድር አገልግሎት ማግኘት
የሚችል ይሆናል፡፡

 የአከፋፈል ሁኔታ

ገፅ |6 https://digafmfi.et/
Access beyond Limits!

ደንበኛ ከአማዞን ሱፍ በ 1300 ብር ሸሚዝ ቢወስድ በስድሰት ወር ውስጥ እዳውን ከፍሎ ማጠናቀቅ
ይጠበቅበታል፡፡

ይህም “1300/6 = 216 ብር” ለስድሰት ተከታታይ ወራት በየወሩ ከደሞዙ ተቆራጭ ተድርጎ በባንክ ቋሚ ክፍያ
ይከፍላል እንደማለት ነው፡፡

በተጨማሪም ድሞዛቸው አነስተኛ የሆነ ስራተኞች ይህንኑ ሙሉ የሱፍ ልብስ ዋጋ ለ 12 ወራት ማለትም
1300/12 = 108.33 ብር ብቻ ተቆራጭ አድረገው ክፍያቸውን ማጠናቀቅ ይችላሉ፡፡

1.2. ሚላኖ እና ሽብሌ ፋሽን

በእነዚህ ሁለት የዱቤ ልብስ አቅራቢ ድርጅቶች የሚቀርቡ አገልግሎቶች ሶሰት አይነት የዋጋ ደረጃ ያላቸው
ሲሆን ምንም አይነት ልዩ ቅናሽ ያልተደረገባቸው ናቸው፡፡

በዚህም መሰረት

1. 12000 ብር

2. 15000 ብር

3. 20000 ብር የዋጋ ደረጃዎች ያላቸው ልብሶችን ለደንበኞች በዱቤ መልክ ያቀርባሉ፡፡

ይህንንም ተከትሎ ደንበኞች አገልግሎቱን ሲጠቀሙ፣

o 15.5 % = ወለድ

o 1.5% = የብድር የሂይወት ዋስትና

o 5% = የአገልግሎት ክፍያ የሚፈፅሙ ይሆናል፡፡

ገፅ |7 https://digafmfi.et/

You might also like