You are on page 1of 5

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን

የ 2016 ዘመን መለወጫ በዓል ፤የመስቀል በዓል እና የኢሬቻ በዓላትን የሚደርሱ አደጋዎችን
ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የኮልፌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የስራ ማስመሰል ልምምድ የተዘጋጀ
ቢጋር (TOR)

ነሃሴ 2015 ዓ/ም

1. መግቢያ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን የኮልፌ ቅርንጫፍ
ጽ/ቤት በከተማው ውስጥ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀድሞ
በመከላከል፣አደጋ ሲከሰትም ፈጥኖ በመድረስና በመቆጣጠር በህብረተሰቡ ህይወትና ንብረት
ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት በመቀነስ ፣በድንገተኛ አደጋዎች ለሚጎዱ የህብረተሰብ
ክፍሎች የቅድመ ሆስፒታል ህክምናና አምቡላንስ አገልግሎት መስጠት እንዲሁም አስቾኳይ
የአደጋ ጊዜ እርዳታ ሰጭ የሥራ ክፍል በመያዝ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
በዚህም መሰረት ቅ/ጽ/ቤቱ የተሰጠውን ኃላፊነትና ተግባር በአግባቡ ለመወጣትና ተልዕኮውን
ለማሳካት ያስችለው ዘንድ በተቋሙ የሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ ህብረተሰቡንና ባለድርሻ
አካላትን በማሳተፍ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ፡፡ በመሆኑም ስራችንን በተቀላጠፈ ሁኔታ
ለመስራት የ 2016 የመስቀል በዓል እና የኢሬቻ በዓላትን የሚደርሱ አደጋዎችን ለመከላከል እና
ለመቆጣጠር የአደጋ ማስመሰለል ልምምድ(ሲሙላሽን) በማስመልከት ስልጠና ለመስጠት
ከአደጋ በፊት አስቀድሞ የቅርንጫፍ ሰራተኞችና ባለድረሻ አካላትን ዝግጁ ለማረግ አስፈላጊ
ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡

2. የስልጠናዉ አስፈላጊነት
 በዓላቱ እንደሌሎች ባዕላት ሰዎች በቤታቸዉ የሚያከብሩት ሳይሀን ወደ አደባባይ
በመዉጣጥ የሚከበር በዓል በመሆኑ የተለየ ስልጠና ስለሚጠይቅ
 በተቋሙ ወይም በቅ/ጽ/ቤቱ ውስጥ የሚገኙ ሰራተኞች እንዲሁም ባለድርሻ
አካላት ከአደጋ ክስተት በፊት ዝግጁ ማድረግ፡፡
 አደጋ ከተከሰተ በኋላ ሁሉም ሰራተኛና ባለድርሻ የስራ ድርሻቸውን አውቀው
ውጤታማ ስራ እንዲሰሩ ነው፡፡

1
 የሰራተኞችንና የባለድርሻ አካላትን በአደጋ ላይ ያለውን ግንዛቤ ለማስፋት ፡፡
3. ስልጠናው የሚሰጠው፡-
 ሰነድ በማዘጋጀት
 የአደጋ አይነቶችን በመለየት
 ቦታዎችን በመለየት
 የመከላከያ መሳሪዎችንንና አልባሳትን በመለየት፡፡
 የመሳሪያ አጠቃቀምና የአልባሳት አጠቃቀምን ግንዛቤ በማስፋት
 የሴፍቲ ሁኔታዎችን ግንዛቤ በማስፋት
 በእያንድንዱ ነጥብ ላይ በቂ ጊዜ ወስዶ የተግባር ልምምድ በመስራት
 ባለድርሻ አካለካትን የድርሻ ተግባራቸውን እንዲያውቁና ኃላፊነታቸውን
እንዲወጡ ለማድረግ፡፡

የኮልፌ ቅ/ጽ/ቤት በስልጠና ወቅት እንዲሁም በእያንዳንዱ ልምምድ ወቅት ስነ


ምግባር በተመለከተ፡፡
 ወጥ የሆነ የግንኙነት ሰዓት መኖር
 ንቁ ተሳትፎእና እውነተኛ አደጋ እንደሆነ ተረድቶ ልምምዱን በተግባር
ማሳየት ፣
 በእያንዳንዱ ልምምድ ላይ መሰላቸት ሳይኖር በጥንቃቄ መስራት ፣
 ሁሉም የስራ ክፍል ኃላፊዎች ልምምዱን በበላይነት መምራት አለባቸው
 እያንዳንዱ ተሳታፊ እንደ ልምምዱ ባህሪ የሚጠበቅበትን አልባሳት
አሟልቶ መገኘት አለበት

2
 ሁሉም ተሳታፊ ከልምምድ በኋል ልምምዱን መገምገም አለበት
 ሪፖርት ማዘጋጀትና ለሚመለከተው መላክ ወይም ማቅረብ ፡፡

4. ክትትልና ድጋፍ መስጠት


የቅ/መ/ቤቱ ስራ አስኪያጅና የስራ ክፍል ኃላፊዎች ልምምድ አስመልክቶ ድጋፍ
ይሰጣሉ ፡፡

5. የጊዜ ሰሌዳ

ከመስከረም 3 /2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 14/2015 ዓ.ም


ለአስር ቀን የ 2016 በጀት ዓመት የስራ ላይ ልምምድ ስልጠና
የስራ ልምመዱን አስመልክቶ የሚያስፈልጉ አጠቃላይ ግብዓቶች ዝርዝር

ተ.ቁ የእቃው መለኪያ የተሳታፊ የአንዱ ዋጋ ለአስር ቀን


ዓይነት ብዛት ብር ሣ ብር ሣ
1 የተሳታፊ በቁጥር 147 100 00 147,000 00
አበል
2 ለውሃ በቁጥር 2800 12 00 33,600 00
3 ቆሎ በኪሎ 50 200 00 10,000 00
4 ቡና በኪሎ 03 450 00 1,350 00
ጠቅላላ ድምር 191,950 00

3
4

You might also like